Finote Democracy: The Voice of Ethiopian Unity!    
Finote Democracy: Voice of Ethiopian Unity!

                


ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ በሳተላይት
የሚተላለፍ የራዲዮ ፕሮግራም
(EPRP's Satellite Radio transmissions to Ethiopia and Horn of Africa.)
 ||Home || About Us  || Contact Us  || Links  ||   ||
�����
   
   
   
   
   
   
   

ሚያዚያ 20 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø ቦኮ ሃራምን ለመቋቋም የተቋቋመው የአምስት አገሮች የጋራ መከላከያ ኃይል አዛዥ ሚያዚያ 19 ቀን 2008  በሰጡት መግለጫ የጋራው ወታደራዊ ኃይል ውጤት ያለው ስራ እንዲሰራ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ ያስፈልገዋል ብለዋል። በመጨረሻው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ላይ ረጅዎች ለጋራ ኃይሉ 250 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት መመደባቸው የተገለጸ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ገንዘቡ ለጋራው ኃይል ያልደረሰ መሆኑኑ አዛዡ ተናግረዋል፡፡ ገንዘቡ ይሰጣል ተብሎ ቃል የተገባ ከመሆኑ ባሻገር እስካሁን የጋራው ኃይል የደረሰው የተወሰኑ የመገኛኚያ መሳሪያዎችና 11 ወታደራዊ መኪናዎች ብቻ ነው ብለዋል። 8500 ወታደሮችን የያዘው የጋራ ወታደራዊ ኃይል ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ሰንዝሮ ቦኮ ሃራምን አዳክሟል ቢባልም ውጤት ያለው ስራ ለመስራት እርዳታ ያስፈልገዋል ተብሏል፡፤

 

Ø ረቡዕ ሚያዚያ 19 ቀን 2008 ዓም. በደቡብ አፍሪካ በሚገኙት በጆሃንስበርግ፤ በኬፕ ታውንና በደርበን ከተሞች በርካታ የደቡብ አፍሪካ ዜጎች ፕሬዚዳንት ዙማ ከስልጣን እንዲነሱ በመጠየቅ ሰላማዊ ሰልፎች አካሄደዋል። ሰልፈኞቹ ፕሬዚዳንት ዙማ በሙስናና እና በዝምድና ስራ ውስጥ የተዘፈቁ በመሆናቸው አገራችውን ለመምራት ብቃት የላቸውም የሚሉ መፈክሮችን ሲያሰሙ እንደነበር ታውቋል። ከጥቂት ቀናት በፊት በአገሪቱ ምክር ቤት ውስጥ  ከስልጣናቸው እንዲወገዱ ተካሄዶ የነበረውን እንቅስቃሴ በድል ያሸነፉት ፕሬዚዳንት ዙማ በደቡብ አፍሪካ ነጻ ምርጫ የተካሄደበትን 22 አመት ለማክበር በተዘጋጀ ስነስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የአገሪቱ መሪዎች የሚለወጡት በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንጅ በአቋራጭ እና በመፈንቅለ መንግስት አይደለም ብለዋል። በዴሞክራሲ ውህዳን የአብዛኛውን ሕዝብ ውሳኔ ተቀብሎ የመሄድ ግዴታ አለባቸው ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ ያለው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መምጣቱ እየታየ ያለ ክስተት ሲሆን ከተወሰኑ ወራቶች በኋላ የሚደረጉት የከተሞች አስተዳድር ምርጫዎች የሕዝቡን ስሜት በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሊያሳዩ ይችላሉ በማለት ታዛቢዎች አስተያየታችውን ይሰጣሉ። በሚቀጥሉት የከተሞች አስተዳደር ምርጫዎች ገዥው ፓርቲ ከተሸነፈ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ በአገሪቱ ላይ ባለው የስልጣን ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ሊኖረው እንደሚችል ብዙዎች ይተቻሉ።

 

Ø በግብጽና በሊቢያ ወሰን ከሕገ ወጥ ስደተኞች ጋር በተደረገ ግጭት 16 የሚሆኑ ግብጻውያን ስደተኞች የተገደሉ መሆናቸውን ረቡዕ ሚያዚያ 19 ቀን 2008 ዓ.ም. የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ ገልጿል። ግድያው የተፈጸመው ባኒ ዋሊድ በተባለችው ከተማ ውስጥ ሲሆን  ከአስተላላፊዎች ጋር በተነሳ ግጭት ስደተኞቹ የተገደሉ መሆናቸው ተነግሯል። በሊቢያ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ተልእኮ መስሪያ ቤት መሪ በሰጡት መግለጫ  12 ግብጻዉያን እና ሶስቱ ሊቢያውያን መገደላቸውን ተናግረው ድርጊቱን በጽኑ ኮንነዋል። በሊቢያ በተለያዩ ወገኖች መካከል የእርስ በርስ ግጭት ከተጀመረና አለመረጋጋት ከተፈጠረ ወዲህ አገሪቱ ከልዩ ልዩ አገሮች የመጡ ስደተኞች ወደ አውሮፓ የሚሰደዱባት ማዕከል ሆና የቆየች ስትሆን የስደተኛ ማስተላለፍ ንግድም ደርቶ የሚገኝባት ቦታ ናት።  በሊቢያ በኩል ከሚተላለፉ ስደተኞች መካከል በወያኔው ዘረኛና አምባገነን ስርዓት አፈናና ብዝበዛ ተማረው አገራቸውን ጥለው የሚሰደዱ ኢትዮጵያን የሚገኙበት መሆኑም ይታወቃል። በዚህ አጋጣሚ ባለፈው አመት አይሲስ በሚባለው የአክራሪና የአሸባሪ ቡድን አባላት ግፍ በተሞላበት መንገድ በስለት የታረዱ  ኢትዮጵያን ሰማዕታት ወገኖችን የምናስታውሰው በከፍተኛ ሀዘን ነው።  

 

 

Ø ረቡዕ ሚያዚያ 19 ቀን 2008 ዓም. በሱዳን ካርቱም የዩኒቨርስቲ የተማሪዎችን ሰልፍ ለመበተን ፖሊሶች በተኮሱት ጥይት አንድ ተማሪ ተመቶ የሞተ መሆኑ ተነገረ። በኦምዶርማን የሚገኘው የአህሊያ ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢ የሚማሩ ተማሪዎች ቀደም ብሎ በተደረገ ሰልፍ ተይዘው በቁጥጥር ስር የነበሩት ተማራዎች እንዲፈቱ ለመጠየቅ ሲያካሂዱ የነበረውን ሰልፍ ለመበተን ነጭ ለባሽ ፖሊሶች በፈጠሩት ግርግር አንድ ተማሪ በጥይት ተመቶ ወዲያውኑ የሞተ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል። ረቡዕ ማታ የገዥው ፓርቲ ቃል አቀባይ ተማሪው ከዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ ውጭ በሽጉጥ ተመቶ መሞቱን አምኗል። የሟቹን ተማሪ አስከሬን በርካታ ተማሪዎች ተሸክመው ወደ መኖሪያው አካባቢ በመውሰድ እንዲቀበር ያደረጉ ሲሆን በርካታ ተማሪዎች ተማሪ መግደል አገርን እንደመግደል ይቆጠራል ብለዋል። የዩኒቨርስቲው አስተዳደር የተማሪውን መገደል አውግዞ ዩኒቨርስቲው ላልተወሰነ ጊዜ የዘጋ መሆኑን ገልጿል። የካርቱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በየጊዜው ከጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት ቢደርስባችውም አገዛዙን በመቃወም ተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፎች ሲያደርጉ መቆየታቸው  ይታወቃል።

 

Ø በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ተልእኮ መሪ በሰጡት መግለጫ የአይሲስ አሸባሪዎች በየጊዜው በአገሪቱ የነድጅ ማውጫ አካባቢዎች ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት ከፍተኛ ስጋት የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የአሸባሪዎቹ ጥቃት የነዳጅ ምርቱን የሚያስተጓግለው መሆኑን የተናገሩ ሲሆን ጥቃቱም የአገሪቱን ኢኮኖሚና በነዳጅ ምርቱ ገቢ በሚተዳደሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሊቢያ ዜጎችን የኖሮ ሁኔታ ይጎዳል በማለት ኃላፊው ተናግረዋል።

Ø በተያይዘ ዜና የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ከሊቢያ የአማጽያን አካባቢ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ነዳጅ ጭኖ መንቀሳቀሱ በተደረሰበት በአንድ በህንድ የተመዘገበ የጭነት መርከብ ላይ ማዕቀብ እንዲደርግ የወሰነ መሆኑ ታወቀ። ከሁለት ዓመት በፊት የጸጥታው ምክር ቤት በሊቢያ አማጽያን ቁጥጥር ስር ካሉ የነዳጅ ማምራቻ ቦታዎች ነዳጅ እንዳይጫን መከልከሉ የሚታወስ ሲሆን ይህንን  ህግ በመተላለፍ ነዳጅ ጭኖ ወደ ማልታ አቅንቷል የተባለው የጭነት መርከብ ማዕቀብ የተጣለበትና ጉዞው የቅርብ እየተደረገበት መሆኑ ተነግሯል። መርከቡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለማይታወቅ ሰው የተሸጠ ሲሆን ስሙም የተቀየረ መሆኑ ተነግሯል።

 

 

 

ሚያዚያ 19 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የዓለም አቀፉ ህብረተሰብ በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ እንደ ችግሩና መጠንና ስፋት አስፈላጊውን እርዳታ ባያቀርብም ከፍተኛ መጠን ያለው እርዳታ መስጠቱ ይታወቃል። የወያኔ መሪዎች የእርዳታ እህሉን ከወደብ ለማንሳት እግራቸውን እየጎተቱ የራሳቸውን ማዳበሪያ እያጓጓዙ ሲሆን ወደ መሀል አገር የገባውን የእርዳታ እህልና ሸቀጣ ሸቀጥን ደግሞ በየመደብሩ በመውሰድ መቸብቸብ ጀምረዋል፡፤ በረሃብተኛ ሕዝብ ስም በተማጽኖ የመጣውን የእርዳታ እህል የወያኔ መሪዎችን ኪስ ማደለቡና የዘርና የቋንቋ ፖለቲካው ማራመጃ የፖለቲካ መሳሪያ እንደሆነ ተገልጿል፡፤

 

Ø በአሜሪካ የሚረዳው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል በሶማሊያ በየጊዜው ከአልሸባብ ጥቃት እየደረሰበት መሆኑና አሜሪካንም በድሮንና በጦር አውሮፕላን በአልሸባብ መሪዎችና የጦር አበጋዞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ስትፈጽም መቆየቷ ይታወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህም በአልሸባብ ቁጥጥር ስር የነበሩ ከተሞችና የገጠር መንደሮች በአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል በሚታገዙ የሶማሊያ ወታደሮች ቁጥጥር ስር መዋላቸው ይዘገብ እንጅ አልሸባብ ከተሞቹን እንደገና በጦርነትና ያለ ጦርነት እየወሰደ መሆኑ ከሶማሊያ የሚመጣው ዜና አስረድቷል። ከታችኛው  ሸብሌ ግዛት ከሞቃዲሾ ደቡባዊ ምዕራብ በ 110 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ጃናሌ ከተማ በአልሸባብ እጅ የወደቀች ስትሆን ከተማዋን ይቆጥጠሩ የነበሩ የኡጋንዳ ወታደሮች ያለ ምንም ጥቃት ከተማዋን ለቀው መውጣታችው ታውቋል። ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ በጃናሌ ከተማ በርካታ የኡጋንዳ ወታደሮች መገደላቸው ይታወሳል።

 

Ø ተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ህብረት ልኡክና የቀድሞ የሞዛምቢክ ፕሬዚዳንት ሚስተር ቺሳኖ ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ባሰሙት ንግግር በምዕራብ ሳህራ ያለውን ችግር አስመልክቶ  ተገቢ እርምጃዎች ካልተወሰዱ  ከፍተኛ ችግር ሊከተል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። በአሁኑ ጊዜ ችግር አነስተኛ ቢመስልም ትልቁን የደን እሳት የምታቀጣጥለው ትንሽ እሳት መሆኗን በማወቅ ለችግሩ ተገቢ ትኩረት መስጠት ይኖርብናል ብለዋል። ከጥቂት ወራት በፊት የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን የምዕራብ ሳህራን ግዛት በሞሮኮ የኃይል ቁጥጥር ስር ያለ ግዛት ነው በሚል ንግግር ማድረጋችውን ተከትሎ ሞሮኮ በወሰደችው የአጸፋ እርምጃ ከ 20 የሚበልጡ የተመድ የሰላም አስከባሪ ሉኡካን ከምዕራብ ሳህራ ግዛት እንዲወጡ መደረጋቸው ይታወሳል። በ1983 ዓም በምዕራብ ሳህራ የተመደበው የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል የልዑካን ቡድን የአገሪቱን የወደፊት እድል አስመልክቶ ሕዝቡ በምርጫ እንድወስን የሚችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸትና ለማደራጀት ኃላፊነት ቢሰጠውም  ድምጽ መስጠት የሚችለው ማነው በሚለው ላይ ልዩነት በመፈጠሩ እስካሁን ምርጫው ሳይካሄድ ቆይቷል። የሞሮኮ መንግስት ግዛቱ የሞሮኮ ነው ሲል ከ1967 ዓም. ጀምሮ የትጥቅ ትግል ሲያካሄድ የቆየው የፖሊሳሪዎ ድርጅት ደግሞ ሕዝቡ በውሳኔ ህዝብ መወሰን አለበት ሲል ቆይቷል። የአፍሪካ ህብረት የሳህራዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ግዛትን አባል አገር አድርጎ በመቀበሉ ሞሮኮ የአፍሪካ ህብረት እንደ ገለልተኛ አካል አታየውም። በምዕራብ ሳህራ የተመድ ተልእኮ ስለመቀጠል እና አለመቀጠሉ የጸጥታው ምክር ቤት በሚቀጥለው ሳምንት ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን የምክር ቤት አባላት የተከፋፈሉ መሆናቸው ታውቋል። ፈርንሳይ ስፔን ግብጽ እና ሴኒጋል ሞሮኮን ሲደግፉ ሌሎች ይቃወማሉ ተብሏል። የምዕራብ ሳህራ ጉዳይ ተገቢ መልስ ካላገኘ የማያባራ ጦርነት ሊከተል እንደሚችል ብዙዎች ይጠቁማሉ።

 

Ø በምዕራብ አፍሪካ በምትገኘው የኬፕ ቬርዴ ደሴት 8 ወታደሮችና ሶስት ሰላማዊ ሰዎች በጥይት የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ግድያውን የፈጸመው አንድ ከስራ ገበታው ላይ ተሰውሮ የነበረ ወታደር ነው የሚል ጥርጣሬ ያለ ሲሆን ድርጊቱን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው ግን የታወቀ ነገር የለም። ከሞቱት ሰዎች መካከል ሁለቱ የስፔን ዜግነት ያላቸው ቴክኒሺያኖች ሲሆኑ አንዱ የደሴቷ ዜግነት ያለው ነዋሪ መሆኑ ታውቋል። መንግስት በሰጠው መግለጫ ሕዝቡ እንዲረጋጋ ጥሪ ያደረገ ሲሆን አውሮፕላን ማረፊያውን ጨምሮ በዋና ከተማዋ አንዳንድ ቦታዎች ዝግ ሆነዋል በሚል የተስፋፋው ወሬ መሰረተ ቢስ ነው በማለት አስተባብሏል። የግድያው መነሻን ለማወቅ ምርመራ መጀመሩን ገልጾ እስካሁን ድረስ ያሉት መረጃዎች የሚያመለክቱት ግድያው የተካሄደው በግል ችግር ምክንያት ነው ብሏል። የቀድሞ የስፔን ኮሎኒ የነበረቸውና ከሴኒጋል ወደብ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የኬፕ ቬርዴ ደሴት  ግማሽ ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ የሚኖርባት አገር ነች ነው።

 

Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ ሚስተር ማቻር እንደተጠበቀው  ሚያዚያ 18 ቀን 2008 በአገሪቱ ዋና ከተማ  የገቡ ሲሆን ለምክትል ፕሬዚዳንትነቱ ስልጣን ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ በተናገሩት ቃል በሁሉም ወገን ላይ የተፈጠረው ቁስል ባስቸኳይ እንዲድን አድርገን ሕዝባችንን ወደ አንድነት ማምጣት አለብን ብለዋል። የሰላም ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ በሙሉ ልብ እንደሚሰሩና የእርቁ ሂደት ባስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጥሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።  ሬክ ማቻርን ለመቀበል በተደረገው የአቀባበል ስን ስርዓት ላይ የደቡብ ሱዳን ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኬር በበኩላቸው “ ወንድሜን ማቻር ስቀበል ደስታ ይሰማኛል ካሉ በኋላ የአሳቸው ወደ ጁባ መመለስ የጦርነቱን ማብቃትና የሰላሙ ሁኔታን መጀመር እንደሚያበስር ጥርጥር የለኝም”  ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን የማቻር መመለስ ለሰላሙ ጥረት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን ገልጸው የአንድነቱ መንግስት ባስቸኳይ ተመስርቶ ስራ መጀመር አለበት ብለዋል። ሁኔታው በሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ባለመሆኑ የሰላሙን ጥረት ተግባራዊ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ። በየካምፑ ያሉት የሁለቱ ወገኖች ወታደሮች ከኃይል እርምጃ እንዲቆጠቡ ማድረግ  ቀላል ስራ አይደለም።  ለሁለቱም ወገኖች ታዛዦች ያልሆኑ የሚሊሺያ ኃይሎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች አሁንም ጦርነት እያካሄዱ ነው። በአንድነት መንግስቱ ውስጥ የሚነሱ ልዩነቶችንም በተገቢው መንገድ የማስተናገድ ኃላፊነትም ይኖራል። በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች በአገሪቱ ውስጥ ውጥረቱ ከፍተኛ ውጥረት የሚታይ ሲሆን የሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ወሳኝ ይሆናሉ በማለት አስተያየታቸው የሚሰጡ ወገኖች ብዙ ናቸው።

 

 

Ø በግብጽ በሲና ባህረሰላጤ መንገድ ውስጥ በተቀበረ ፈንጅ ሶስት የፖሊስ ሰራዊት አባላት የተገደሉ መሆናቸውን የግብጽ መንግስት የዜና ወኪል ገለጸ። ረቡዕ ሚያዚያ 19 ቀን 2008 ዓም በሲና ባህረ ሰላጤ የፖሊስ ሠራዊት አባላትን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አንድ ወታደራዊ መኪና የፈንጅው ጥቃት ደርሶበት የተገለበጠ ሲሆን ከሞቱት በተጨማሪ  8 ወታደሮች በጽኑ የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል።  የቆሰሉት ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን ለድርጊቱ ኃላፊነትን የወሰደ አካል የለም። ላለፉት ሁለት ዓመታት በአካባቢው ጥቃት ሲፈጽም የቆየው የአይሲስ ቅርንጫፍ የሆነው ቡድን ድርጊቱን ሳይፈጽም አይቀርም ተብሎ ተጥርጥሯል።

በተያያዘ ዜና በግብጽ ዋና ከተማ በካይሮ ተገድሎ አስከሬኑ እንዳልነበር ሆኖ ተጥሎ የተገኘውን የጣሊያን ተወላጅ ጉዳይ አስመልክቶ የእንግሊዝ መንግስት ሰኞ ሚያዚያ 17 ቀን ባወጣው መግለጫ ላለፉት ሶስት ወራት የግብጽ መንግስት  ስለግለሰቡ ገዳዮች ያካሄደው ምርመራ ምንም ውጤት አለማስገኘቱ የእንግሊዝ መንግስትን ቅር ያሰኘ መሆኑን ገልጿል። መግለጫው የጣሊያን መንግስት ከግብጽ መንግስት የሚፈለገውን ትብብር አለማግኘቱ የእንግሊዝ መንግስትን ያሳዘነ መሆኑን ገልጾ ምንም እንኳ የግብጽ የጸጥታ ክፍሎች በግድያው ላይ አሉበት የሚለው ግምት የተረጋገጠ ባይሆንም ትክክለኛውን ገዳይ ለማወቅ ማናቸውም ጥረት እንዲደረግ ለዓለም አቀፍ ማህበርሰብ ጥሪ አስተላልፏል፡፤

 

 

 

ሚያዚያ 18 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ጋምቤላ 18 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ባለው የደቡብ ሱዳን የጀዊ ስደተኞች ሰፈር የፈነዳው ግጭትና ግድያ ትላንትም ቀጥሎ እንደነበር በቦታው ያሉ ምስክሮች ገልጸዋል በቦታው የሰፈሩት ስደተኞች መቶ በመቶ የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ የሪያክ ማሻር ተከታዮችና የኑዌር ተወላጆች ሲሆኑ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን ሾፌር የነበረው ኢትዮጵያው ሁለት ስደተኛ ህጻናትን በመኪና ገጭቶና ገድሎ በመሰወሩ ኑዌሮቹ በሰፈሩ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ለመግደል ተነስተው ብዙዎችን እንደገደሉ ይታወቃል ከተገደሉት ውስጥ የስደተኛው ኮሚሽን ኢትዮጵያዊ ሰራተኞችም እንዳሉበት ታውቋል። ጀዊ የአንዋኮች አካባቢ ስትሆን ወያኔ ኑዌሮችን በዚያ ያሰፈረው ለተንኮል ነው ተብሎም ተጋልጧል። ወያኔ ከግድያው በኋላ ዜጎችን ለመከላከል ምንም እርምጃ ባለመውሰዱ ኢትዮጵያውያኑ ተደራጅተው የስደተኛውን ሰፈር ማጥቃታቸው ታውቋል። የሟቹ ቁጥርም ቀላል አልሆነም የተባበሩት መንግስታት የስድተኛ ኮሚሽን ሰራተኞቹን ከጀዊ አካባቢ አሽሽቷል። ግጭቱ ገና አልበረደም ሲል ዛሬም የደረስ ዜና ያረጋግጣል

 

Ø ወያኔ ለዘረፋና ለስርቆት እንዲያመቸው ከ 100 ሺ ሄክታር በላይ የጋምቤላ መሬትን ለጥጥ እርሻ በማለት ለንግድ ሸሪኮቹ በመስጠትና ለልማትም በማለት 3 ቢሊዮን ብድር በመፍቀድ የጥጥ ምርትን እናሳድጋለን በማለት ፕሮፓጋንዳውን ካሰራጨ ወዲህ የጥጥ ምርቱም ሳይኖር ልማቱም ሳይካሄድ ደን ተጨፍጭፎ ከቆየ በኋላ በብድር የተሰጠው ገንዘብ ለምን ተግባር እንደዋለ እንኳ ለማወቅ አለምቻሉ ተገልጿል። ለጥጥ ልማት በማለት መሬት ወስደው ደን መንጥረው ገንዘብ ተበድረው ጠፉ የተባሉ ሰዎችና ኢንቬስተሮች እነማን እንደሆኑ ባይገለጽም  ወያኔ ምርመራና ማጣራት ጀምሬያለሁ ብሏል። ጉዳዩን የተከታተሉ ወገኖች ግን ዘረፋውና  የተፈጥሮ ወድመቱ በወያኔ አባላትና በንግድ ሸሪኮቻቸው መፈጸሙን ይናገራሉ።

 

 

Ø በአባይ ወንዝ ግድብና አጠቃቀም ዙሪያ ወያኔና ግብጽ የገቡበትን የፖሊቲካና የዲፕሎማሲ ውዝግብ ለማብረድ በወያኔ ፓርላማ አፈጉባዔ የሚመራ አንድ የልኡካን ቡድን ግብጽንና ሱዳንን መጎብኘቱ ይታወሳል። የጉብኝቱ ዓላማ የታሰበለትን ግብ ይምታ አይምታ ባይታወቅም በወቅቱ የነበረውን የዲፕሎማሲ ውጥረት ግን ሳያለዝበው እንዳልቀረ ተገምቷል፡፤ ወያኔ ከሱዳን ጋር መልካም ወዳጀነት ፈጥሮ በድንበር አካባቢ ለም መሬቶችን አሳልፎ ከሰጠና ሱዳንም በአገሩ የሚገኙ የወያኔ ተቃዋሚዎችን እያፈነ ለወያኔ ለመስጠት ጥረት በሚያደርግበትና በሁለቱ አገሮች መካከል የድንበር ጥበቃ ውል ተፈርሞ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሱዳን ሕዝብ ዲፕሎማሲ የተባለ ቡድን የወያኔን ባለስልጣኖችን እንደሚያነጋግር ተገልጿል። ጉብኝቱ ግንቦት 1 ቀን 2008 ዓም የሚጀመር ሲሆን የዲፕሎማሲው ቡድን ከወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ጀምሮ ከሌሎች የወያኔ ባለስልጣኖችን ያናገጋራል ተብሏል፡፤

 

Ø መጭውን የትንሳዔ በዓል አስታኮ የወያኔ አገዛዝ ሱቆችን በማደራጀት አባ ወራዎችን በቡድን እየመደበ እንደሚያሰማራ ታውቋል። ከአስራ አምስት እስከ ሃያ የሚደርሱ አባወራዎች በአንድና በሁለት ሱቆች ሸቀጦች እንዲሸጡ በማደራጀትና በማስገደድ ነዋሪዎንና የነጋዴው ህብረተሰብን ለማጋጨት እየተሞከረ መሆኑ ተገልጿል። ሱቆቹ በዋናነት ስኳርና ዘይት የሚያቀርቡ ሲሆን ሌሎች ሸቀጦችንም ሊጨምሩ እንደሚችሉ ተነግሯል። የወያኔ አገዛዝ በመላ ኢትዮጵያ ላንሳራፋው የኑሮ ውድነት ተጠያቂ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም የችግሩ መነሻና ምንጭ የነጋዴው ህብረተሰብ እንደሆነ አድርጎ በማቅረብ ነጋዴዎችን ከሕዝብ ጋር ለማጋጨት የሸማቾች ማህበራትን ማቋቋሙ ይታወቃል። የፋሲካ በዓልን ተንተርሶ እንደ ቅቤ እንቁላል ዶሮ በግና በሬዎች የመሳሰሉ የምግብ አቅርቦቶች ዋጋ ጭማሪ እያሳየ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ለወያኔ ማስረከብ የለመደበት የኬንያ መንግስት የታይዋን ተወላጅ ሆነው በህገወጥነት የወነጀላቸውን የታይዋን ተወላጆች አስሮ ለሀገራቸው ሳይሆን ለቻይና ማስረከቡ ተጋለጠ ቻይና ታይዋን ግዛቴ ናት ብትልም ቻይናና ታይዋን ሁለት የተለያዩ ሀገሮች ሆነው እንድሉ ይታወቃል። ወያኔ በበኩል ኬንያ እንደ የመን የሚመጡ ተቃዋሚዎችን አግታ እንድታስረክብ ዝርዝር ስሞችን ሰጧል ተብሎም መረጃ አለ

 

 

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በብሩንዲ አንድ የጄኔራል ማእርግ ያላቸው ከፍተኛ ባለስልጣን ከነባለቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን  ገዳዮችን አፈላልገው እንድይዙ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለወታደሮቻቸው የአንድ ሳምንት የጊዜ ገደብ ያለበት ጥብቅ መመሪያ የሰጡ መሆናቸው ታውቋል።  ፕሬዚዳንቱ ለሟቾቹ ቤተሰቦች ሀዘናቸውን የገለጹ ሲሆን የአገሪቱ የጦር ኃይልም አንድነቱን አጠናክሮ ሁኔታውን በቁጥጥር ስር እንዲያደርግ ተማጽነዋል። የፕሬዚዳንቱ ትእዛዝ በብሩንዲ እየተካሄደ ያለውን ግድያ ያፋፍማል የሚል ስጋት ፈጥሯል። የብሩንዲ የእርስ በርስ ግጭት ከጀመረ ወዲህ የመንግስት ባለስልጣኖች ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች ሲገደሉ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎ ደግሞ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የጅምላ ግድያ እያካሄዱ ከመሆናቸውም በላይ በርካታ ሰዎችን አስረው ሰቆቃዊ ድርጊት እየፈጸሙባቸው መሆኑ ይነገራል። 

 

Ø በሱማሊያ ከዋናዋ ከተማ ከሞጋዲሾ ሰሜን ምዕራብ 250 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ከባይደዋ ከተማ አጠገብ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት እና የሱማሊያ መንግስት የጦር ካምፕ ላይ አልሸባብ ጥቃት ሰንስዝሮ ቢያንስ 20 ወታደሮችን የገደለ መሆኑ ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል። ከተወሰነ የተኩስ ልውውጥ በኋላም የአፍሪካ ህብረት የሰላም አሰከባሪ ሃይሎች እና የሱማሊያ ወታደሮች የጦር ሰፍሩን መልሰው መቆጣጠራቸው ተነግሯል።  የአልሸባብ አጥቂዎችም ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ቢገልጽም ከአልሸባብ በኩል የተሰማ ዜና የለም።

 

Ø መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ በሱማሊያ የገባውን ከፍተኛ ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ድርጅቶቹ በጋራ መግለጫቸው ላለፉት አራት አመታት በሱማሊያ ዝናም በመጥፋቱ ምክንያት ከ5 ሚሊዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ መሰደዱን ገልጸው ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ከፍተኛ እልቂት ሊኖር እንደሚችል ተናግረዋል። ከስድስት ዓመት በፊት በሱማሊያ በገባው ድርቅ ምክንያት ከ250 ሺ ሰው በላይ የሞተ መሆኑን አስታውሰው ተመሳሳይ የሕዝብ እልቂት እንዳይደርስ ከፍተኛ እርዳታ መሰብሰብ አለበት ብለዋል።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት ከአንድ የቱርክ የንግድ መርከብ ላይ በባህር ላይ አፋኞች ተጠልፈው ተወስደው የነበሩ ስድስት የመርከቡ ሰራተኞች የተለቀቁ መሆናቸውን የንግድ መርከቡ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ሚያዚያ 3 ቀን 2008 ዓም. ማንነታቸው ያለታወቀ የባህር ላይ አፋኞች መርከቧ ላይ በመውጣቱ ካፕቴኑ የሚገኝበትን ስድስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው የታወቀ ሲሆን ማክሰኞ ሚያዚያ 18 ቀን 2008 ለቀዋቸዋል ተብሏል። የተለቀቁት የመርከቧ ሰራተኞች በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ መሆናቸው ቢነገርም ለመለቀቃቸው ካሳ መከፈሉ እና አለመከፈሉ የተገለጸ ነገር የለም። በዚህ ዓመት ብቻ በናይጄሪያ ወደብ አካባቢ ከ32 በላይ የመርከብ ጠለፋዎች የተካሄዱ መሆናቸው ከተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት አካባቢ የተገኙ ዜናዎች ይጠቁማሉ።

 

Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ ሪክ ማቻር ለአንድ ሳምንት ያህል ጉዟቸው ካዘገዩ በኋላ በዛሬው ቀን ጁባ ገብተዋል። የአማጽያኑ ድርጅት ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ ሚስተር ማቻር ዛሬ ሚያዚያ 18 ቀን  ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ጁባ የሚገቡ መሆናቸውን ገልጾ የነበረ ሲሆን  በታቀደው መሰረት ለምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦታ ለመያዝ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ተብሏል። ሚስተር ማቻር ጁባ ይገባሉ ተብሎ ታቅዶ የነበረው ሚያዚያ 10 ቀን የነበረ ሲሆን ከዚያ በኋላ በተደጋጋሚ በታቀዱት ቀናት ወደ ጃባ ባለመለሳቸው  በዓለም አቅፉ ህብረተሰብ በሌሎች ላይ ከፍተኛ  ስጋት ፈጥሮ እንድነበር አይዘነጋም።

 

 

 

 

ሚያዚያ 17 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø የእንግሊዙ ዕለታዊ ጋዘጣ ዘ ቴሌግራፍ የእርዳታ ድርቶችንና በመስክ ላይ ያሉ ሰራተኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው በኢትዮጵያ ያለው ድርቅና ረሃብ ከ18 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን እያጠቃ መሆኑን ግልጽ አድርጓል። እስከ አሁን ድረስ በወያኔና በዕርዳታ ድርጅቶች በኩል የረሃብና የድርቁ ተረጅ ወገኖች ቁጥር እስከ 12 ሚሊዮን ይገመት እንደነበር ይታወቃል። በአዲሱ አሀዝ መሠረት ከኢትዮጵያ ሕዝብ 20 ከመቶ የሚሆነው በአሁኑ ጊዜ የእርዳታ ፈላጊ አድርጎታል። የወያኔ ባለስልጣኖች የተረጅውን ሕዝብ ቁጥር መጨመር ደፍረው ባያናግሩትም የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ  ለረሃብና ለድርቁ የሚሰጠው ዕርዳታ ከተረጅው ቁጥር ጋር አይመጣጠንም በማለት አድበስብሰው ለማለፍ ሙከራ እያደረጉ መሆኑ እየተነገረ ነው።

Ø በጋምቤላ ከደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂዎች በመቶ የሚቆጠሩ ገድለው በመቶ  በሚቆጠሩ ህጻናት አፍነው ከወሰዱና በሺ የሚቆጠሩ ከብቶችን ከነዱ ወዲህ በጋምቤላ ያለው ዘግናኝ እልቂት የዓለም ሕዝብ ዓይንና ጆሮ እየሳበ ነው።  በጃዊ ስደተኛ ጣቢያ አቅራቢያ አንድ ኢትዮጵያዊ አሽከርካሪ የደቡብ ሱዳን ስደተኛ ላይ የመኪና አደጋ በማድረሰ ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል በሚል ምክንያት በካምፕ ውስጥ የነበሩት  ስደተኛች አብዛኞቹ የኦሮሞ እና የአማራ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን  በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸው የሚታወስ ሲሆን ድርጊቱን ለመቃወም አደባባይ በወጡ ዜጎች ላይ የወያኔ ፖሊሶችና ወታደሮች  በወሰዱት እርምጃ ግድያና የመቁሰል አደጋ ማድረሳችው ታውቋል። ለተቃውሞ ከወጡት መካከል 5 መገደላቸውና ከ 15 በላይ መቁሰላቸው ተገልጿል። በጋምቤላ ውጥረቱ እየከረረ ሲሆን ቁጣውም እየባሰ መምጣቱ ይነገራል ወያኔ በስደተኞቹ ስም የሚሰጠው ገንዘብ እንዳይጓደልበት ጥቃቱን ችላ ከማለቱም በላይ እያባባሰው ይገኛል።

Ø በግብጽ በተለያዩ ቡድኖች የተድራጀና የተቀናጀ ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ስልፍ መታቀዱን ተከትሎ የአገሪቷ ፕሬዚዳንት ሲሲ ሰልፉን ለማስቆም በቴሌቪዥን ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።  የግብጽ ሕዝብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገሪቱ የኢኮኖሚ ሁኔታ መዳከምና እንዲሁም የጸጥታ ኃይሎች በሰላማዊ ሕዝብ ላይ በሚወስዱት አፈና ምክንያት መማረሩን በመግለጸ ተቃውሞ እያሰማ ሲሆን ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሁለት በግብጽ ቁጥጥር ስር ያሉ ደሴቶችን የሲሲ መንግስት ለሳኡዲ አረቢያ መስጠቱ ደግሞ ምሬቱ ይበልጥ እንዲባባስ አድርጎታል። የተለያዩ ቡድኖች የተቃውሞ ስልፍ ለማድረግ መወጣናቸው በመታወቁና ሰልፉም ሊያስከትለው የሚችለው ከፍተኛ ችግር ስጋት ስለፈጠረ ፕሬዚዳንት ሲሲ በይፋ ማስጠንቀቁያ መስጠት ተገደዋል። በንግግራቸው ላይ “የግብጽን መጥፋት የሚፈልጉ ኃይሎች እንደገና ጸጥታዋን ለማድፍረስ እየተዘጋጁ ነው ካሉ በኋላ የኛ ተግባር የህዝቡን ደህንነትና ጸጥታ መጠበቅ ስለሆነ አስፈላጊውን ርምጃ እንወስዳለን” ብለዋል። የጸጥታ ኃይሎች በተለያዩ ቦታዎች የተሰማሩ ሲሆን ሰላማዊ ስልፎችን ያደራጃሉ፤ ግለሰቦችን ይቀሰቅሳሉ ብለው የሚገምቷቸውን ግልሰሰቦችን ጋዜጠኞችንና የህግ ባለሙያዎችን ከየቤታቸው በመልቀም ያሰሯቸው መሆኑ ታውቋል።  በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ሲሲ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከ 1000 ሰዎች በላይ የተገደሉ ሲሆን ወደ 40 ሺ የሚገመቱ ሰዎች መታሰራቸውም ይነገራል።

 

Ø በብሩንዲ የተናጠል ግድያው እየቀጠለ መሆኑ ተገለጸ። ሰኞ ሚያዚያ 16 ቀን 2008 ዓ..ም የብሩንዲ ምክትል ፕሬዚዳንት የጸጥታ አማካሪ የሆኑት ጄኔራል ካሩዛ እና ባለቤታቸው በመኪና ልጃቸውን ትምህርት ቤት ካደረሱ በኋላ ባልታወቁ ሰዎች የተገደሉ መሆኑ ተነግሯል። ለድርጊቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን የለም። ባለፈው ነሐሴ ወር የፕሬዚዳንቱ የግል የጸጥታ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑት ጄኔራል ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች መገደላቸው አይዘነጋም። እሁድ ሚያዚያ 15 ቀንም የብሩንዲ የሰብአዊ ጉዳይ ሚኒስትር ከቤተክርስቲያን ሲወጡ ቦምብ ተወርውሮባቸው ሳይጎዱ በህይወት ሊያመልጡ ችለዋል።  በብሩዲ በተለይ በከፍተኛ ባለስልጣኖችና የጦር መኮንኖች ላይ የሚካሄደው የተናጠል ግድያ የብሩንዲን ፕሬዚዳንት አስተዳደር እያናጋው ነው ተብሏል። የብሩንዲ የውስጥ ችግር ከጀመረ ጀምሮ ከ400 በላይ የሆኑ ሰዎች መገደላቸው ይታወቃል።

በተያያዘ ዜና ሄግ የሚገኘው የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት በብሩንዲ እየተካሄዱ ባሉ ወንጀሎች ላይ ክስ ለመስረት አቃቤ ህጉ የመጀመሪያ ደረጃ ጥናትና ምርመራ እያካሄደ መሆኑ ታውቋል።  የመጀመሪያ ደረጃው ጥናት እንደተጠናቀቀ ሙሉ የሆነው የምርመራና ማስረጃ የማሰባብ ስራ የሚጀመር መሆኑና  ጥፋተኛ ናቸው ተብለው የሚከሰሱ ሰዎችም ለፍርድ እንደሚቀርቡ ተነግሯል።

 

Ø በዳርፉር ለሶስት ተከታታይ ቀኖች በተካሄደ የውሳኔ ሕዝብ ምርጫ አብዛኛው ሕዝብ ዳርፉር  በአምስት ክልሎች መከፋፈሏን መደገፉን የሱዳን መንግስት ገልጿል። በመንግስቱ መግለጫ መሰረት በተካሄደው ምርጫ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገበው መካከል በምርጫው የተሳተፈው 97 በመቶ የሚሆነው እንደሆነ ሲነገር ድምጽ ከሰጠው መካከል ደግሞ 98 በመቶ የሚሆነው መራጭ ዳርፉር ለአምስት ክልሎች መከፋፈሏን መርጧል ተብሏል። በርክታ ተፈናቃዮች ድምጽ መስጠት በማይችሉበት ሁኔታና  ኃይልና ማስፈራሪያ በሰፈነበት ሁኔታ የሚካሄድ የውሳኔ ሕዝብ ምርጫ እውነተኛ የሕዝብ ፍላጎት አያንጸባርቅም በማለት አማጽያኑ ኃይሎች ምርጫው እንዳይካሄድ አድማ ያደረጉ ሲሆን የምዕራብ አገሮችም የጸጥታው ሁኔታ ለነጻና ርቱዓዊ ምርጫ ምቹ ባለመሆኑ ምርጫው መካሄድ የለበትም ማለታቸው ይታወሳል። የሱዳን መንግስት ባለስልጣኖች ምርጫው የአረብ አገሮችና ሌሎች ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ባሉበት የተካሄደ በመሆኑ የሕዝቡን እውነተኛ ስሜትና ፍላጎት ያንጸባርቃል እያሉ ናቸው።

 

 

 

ሚያዚያ 15 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በጋምቤላ ንጹሃን ዜጎች ድንበር ተሻግረው በመጡ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች እልቂት ከተፈጸመባቸው አንድ ሳምንት ባስቆጠረበትና በታጣቂዎቹ ታግተው የተወሰዱ ህጻናት ጉዳይ አሁንም ምንም ምላሽ ባላገኘበትና እንዲሁም ዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ድርጊቱን አውግዞ ህጻናቱ አለምንም ቅደመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጥሪ እያቀረበ ባለበት ሰዓት ደቡብ ሱዳናውያን አሁንም 14 ኢትዮጵያውያንን መግደላቸው ታውቋል። ግድያው የተፈጸመው ከጋምቤላ ከተማ 17 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ጃዊ የስደተኞች ካምፕ አቅራቢያ መሆኑ የተነገረ ሲሆን መንስኤው አንድ ኢትዮጵያዊ ሹፌር በአንድ የደቡብ ሱዳን ስደተኛ ላይ የመኪና አደጋ በማድረሱ ነው ተብሏል። በአራቢያው የነበሩ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ለአደጋው ምላሽ በአቅራቢያው የነበሩ 14 ኢትዮጵያውያንን በጭካኔ ገድለዋል። በስደተኛ ካምፕ ውስጥ የሚገኙት ደቡብ ሱዳናውያን ግድያውን የፈጸሙት በገጀራ በድንጋይ በቢላዋ መሆኑ ሲታወቅ አንድም የወያኔ ፖሊስ ሆነ ወታደራዊ ኃይል ወደ አካባቢው አለመላኩ ብዙዎችን አስገርሟል።

Ø ከአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች በተገኘው መረጃ በመንግስት ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሲያገለግሉ የነብሩ 1500 የአዲስ አበባ መምህራን የስራ መልቀቂያ አስገብተው 700 ያህሉ መሰናበታቸው ተገልጿል። መምህራኑ በሚደርስባቸው የፖሊቲካ ጫና የደሞዝ ማነስና ዓይን ያወጣ የዘር መድልዎ የተነሳ በመማር ማስተማሩ ሂደት መቀጥል ባለመቻላቸው ሥራውን ለመልቀቅ መገደዳቸው ታውቋል። መምህራን ወያኔ ባሰማራቸው የደህንነት መስርያ ቤት ባልደረባ ምመህራንና በወያኔ ስር በተደራጀ የወጣት ማህበራት ሰላዮች ክትትል እንደመደረግባቸው ታውቋል።

Ø የታንዛኒያ ባለስልጣኖች በታንዛኒያ የእስር ዘመናቸውን የጨረሱትን 74 ኢትዮጵያውያን በኬኒያ ድንበር ላይ በመጣላቸው በኬኒያ እና በታንዛኒያ መካከል ውዝግብ የቀሰቀሰ ከመሆኑ በላይ የኬኒያ ፖሊስ ስድስት ኢትዮጵያውያንን በህገ ወጥ መንገድ አገር ውስጥ ገብተዋል በማለት ማሰሩን አርብ ሚያዚያ 14 ቀን 2008 ዓ.ም.በሰጠው መግለጫ ገልጿል።  እንደ ኬኒያ ፖሊስ ከሆነ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሞምባሳ በኩል አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊጓዙ ሲሉ በጥቆማ መያዛቸው ሲታወቅ ከስደተኞቹ ጋር አንድ የኬኒያ ሹፌርም አብሮ ተይዟል። ኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ ያለ ህጋዊ የጉዞ ሰነድ ኬኒያ በመግባት ወንጀል ሲከሰሱ የኬኒያው ሾፌር ደግሞ ስደተኞችን በማስረግ ወንጀል እንደሚከሥ ተጠቁሟል። ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በብዙ የአፍሪካ አገሮች ውስጥ የከፋ መከራና ስቃይ ይደርስባቸው እንደነብር የሚታወቅ ሲሆን አሁን ደግሞ ስደተኛነታቸው እንደ ጥፋት እየተቆጠረ መታሰር እየተለመደ በመጣቱ ድምጽ አልባ ለሆኑት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሁሉም ወገን በሚችለው አቅሙና መንገድ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ኤጄንሲ እንዲያሳውቅ ሀገር ወዳድ ዜጎች ጥሪ ያቀርባሉ።

Ø የሶማሊያው አልሸባብ ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ዓም ስድስት የወያኔ ወታደሮችን መንገድ ላይ በተቀበረ ፈንጅ መግደሉን አስታውቋል። የፈንጅ አደጋውን በደቡባዊ ባይ ግዛት ውስጥ አውደሊን ከተማ አቅራቢያ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በጥቃቱ ወቅት የአፍሪካ ኅብረት በሶማሊያ ያሰማራቸው ሰላም አስከባሪ በወታድር አጀብ ይጓዝ እንደነበረና ከሞቱት የወያኔ ወታደሮች ውስጥ ከፍተኛ አዛዦች እንደሚገኙበት አብራርቷል። በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ኃይል አልሸባብ አደረስኩ ስለሚለው ጥቃት የተናገረው ነገር የለም። የወያኔ አገዛዙም እንደተለመደው የተነፈሰውና ያለው ነገር አልተመዘገበም።

Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ ሚስተር ሪክ ማቻር ቅድሜ ሚያዚያ 15 2008 ዓ.ም.  ጁባ እንዲገቡ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች የተሰጠውን ቀነ ቀጠሮ አሁንም ያልተከበረ መሆኑ ታውቋል። ባለፈው ዓመት በተደረሰው ስምምነት መሠረት ሚስተር ማቻር ጁባ እንዲገቡ ታቅዶ የነበረው ሚያዚያ 10 ቀን 2008 መሆኑ የሚታወስ ሲሆን አጅበው በሚገቡ ወታደሮች ብዛት ላይ እና ሊይዟቸው በሚችሉ የመሳሪያ ዓይነቶች ላይ ከሱዳን መንግስት ባለስልጣኖች ጋር ስምምነት ባለመደረሱ ጉዟቸው የዘገየ መሆኑ ተነግሯል፡፤ ትናንት አርብ ሚያዚያ 14 ቀን 2008 ዓም በነፍስ ወከፍ ኤኬ 47 አውቶማቲክ መሳሪያ ከታጠቁ 190 አጃቢዎች  እና 20 መትረየሶችና ከ20 አርፒጂ ጋር እንዲገቡ ስምምነት ላይ የተደረሰ በመሆኑ በሚቀጥለው ሳምንት ጁባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። የደቡብ ሱዳን የማስታወቂያ ሚኒስትር እንደገለጹት ሚስተር ሪካ ማቻር የሚጓዙበት አውሮፕላን ወደ ክልሉ እንዲገባ የሚፈቀድለት ከጋምቤላ አውሮፕላን ማረፊያ ከመነሳቱ በፊት የሚመጡት ሰዎች ቁጥርና የያዙት መሳሪያ በስምምነቱ መሰረት መሆኑን የዓለም አቀፍ ድርጅት አባላት ማረጋገጫ ከሰጡ በኋላ ብቻ ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ እንዲሁም አሜሪካ እንግሊዝ እና ኖርዌይ ሚስተር ሪክ ማቻር እንዲመለሱ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸው ተነግሯል።

 

Ø በግብጽ የቀድሞው ፕሬዚዳንት መሀመድ ሞርሲ የካታር መንግስት ሰላይ ናቸው በሚል ቀርቦባቸው የነበረው ክስ ዛሬ ሚያዚያ 15 ቀን ሊታይ ታቅዶ የነበረ ሲሆን ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ ዝግጅት ያስፈልጋል በሚል ለሚያዚያ 30 ቀን 2008 ዓ.ም.  ያስተላለፈው መሆኑ ተነግሯል። ካታር የሚስተር ሞርሲን አስተዳደርና የግብጽን የሙስሊም ወንድማማቾች ማህበር ስትረዳ መቆየቷ የሚታወቅ ሲሆን  የፕሬዚዳንት ሲሲ አስተዳደር ካታር በግብጽ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብታለች በሚል ክስ ትታሰማ መቆየቷም ይታወቃል። በፕሬዚዳንት ሲሲ እና በተባባሪዎቻቸው አማካይነት በተካሄደ ወታድራዊ መፈንቅለ  መንግስት በስልት ከስልጣናቸው የተነሱት ሞርሲ ከዚህ ቀደም በሶስት የተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው የሞት ፍርድ፤ የእድሜ ልክ እስራትና የሃያ አመታት እስራት የተበየነባቸው መሆኑ ሲታወቅ ይህኛው ክስ አራተኛው መሆኑ ነው። ሞርሲ እና ሌሎች አስር ሰዎች የግብጽ የጸጥታ ሁኔታን የሚመለከቱ ሚስጥራዊ ሰነዶች በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተቀብለው ከካታር ሸጠዋል የሚል ክስ አቃቤ ህጉ ያቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።

 

Ø በዚህ ሳምንት በማሊ በአማጽያን ታግተው የነበሩ ሶስት የቀይ መስቀል ሠራተኞች አለምንም ቅደመ ሁኔታ የተለቀቁ መሆናቸው ተነገረ። በሰሜን ማሊ የሚንቀሳቀሰውና ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለው አንሳር ዲን የተባለው ድርጅት ባለፈው ሐሙስ በሰጠው መግለጫ ሰራተኞቹን ያገተው ድርጅቱ መሆኑንና ሊፈቱ የሚችሉት በፈረንሳይ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ያለው ሚያቴን አግ ማያሪስ የተባለው የድርጅቱ አባል ሲፈታ ብቻ መሆኑን ገልጾ እንደነበር ይታወሳል። አርብ ዕለት ታግተው የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች መለቀቃቸው የተነገገረ ሲሆን ሊለቀቁ የቻሉትበፈረንሳይ ወታደሮች ቁጥጥር ስር የሚገኘው ግለሰብ ስለተለቀቀ ይሁን አይሁን አልታወቀም። ሰላም በማስከበር ስም ፈረንሳይ በሰሜን ማሊ ከ3500 በላይ የሆኑ ወታደሮች እንዳላት ይታወቃል።

 

Ø በምስራቅ ሊቢያ ራሱን መንግስት ነኝ የሚለው ክፍል ፓርላማ በተመድ አማካይነት የተቋቋመውን መንግስት ለመደገፍ ውደ ኋላ ሲል መቆየቱ ይታወሳል። ባለፈው ሐሙስ 198 ከሆኑት የምክር ቤቱ አባላት መካከል 108 የሚሆኑት የአንድነት መንግስቱን መደገፋቸውን በመግለጽ መግለጫ ያወጡ ቢሆንም በዙዎቹ በግል ማስፈራሪያ ስለደረሳቸው ድምጽ ሊሰጥበት የሚችል ስብሰባ ማካሄድ ያልቻሉ መሆኑ ተገልጿል። አርብ ሚያዚያ 14 ቀን የምዕራብ መንግስታት አምባስደሮች በሰጠቱ መግለጫ ማስፈራሪያውን በጽኑ አውግዘው አንዳንድ የምክር ቤቱ አባላት የተደረገባቸውን ተጽእኖ ተቋቁመው ድምጻቸውን ለማሰማት መቻላቸውን አወድሰዋል። ምከር ቤቱ ተሰብቦ ውሳኔዎችን በህጋዊ መንገድ እንድያስወስንም ተማጽነዋል።

 

 

 

ሚያዚያ  14 2008 ዓ ም

Ø በጋምቤላ የደረሰውን አሰቃቂና ዘግናኝ እልቂት በመቃወም ዜጎች በተለያዩ መንገዶችና ዘዴዎች ተቃውሟቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በዚህ መሰረት በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 14 ቀን 2008 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ሰንጋ ተራ በሚባለው አካባቢ ተማሪዎች ፊታቸውን ጥቁር ቀለም በመቀባት በጋምቤላ የደረሰውን ፍጅት በመቃወወም አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈለግ እየጠየቁ ባለበት ሰዓት ከሆቴል ደ  አፍሪክ ከሚባለው ሆቴል አካባቢ የነበረው የወያኔ የፖሊስ ኃይል ተማሪዎቹን በዱላ በመደብደብ ማባረሩን በቦታው የነበሩ የአይን እማኞች ተናግረዋል። እነዚህ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡና  በራሳቸው ፍላጎት ለወገኖቻቸው ሞትና መታፈን የቆሙ ወገኖች መደብደባቸው ብቻ ሳይሆን ተይዘው መታሰራቸው ታውቋል።

 

Ø በጋምቤላ የተፈጸመውን ዘግናኝ እልቂት ተከትሎ ልዩ ልዩ አገራትና ድርጅቶች የውግዘት ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። ዓለም አቀፉ የህጻናት መርጃ ድርጅት ፍጅቱን በማውገዝ የታገቱት ህጻናት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ መጠየቁን የዘገብን ሲሆን ሀሙስ ዕለትም የአውሮፓው ህብረት በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት ህጻናት እንዲፈቱ ጥሪ አድርጓል። የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣኖች ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተው የደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት በአስቸኳይ የታገቱት ልጆች ወደ ቤተሰባቸው እንዲመለሱ ጥረታቸውን እንዲጨምሩና ፍጅቱን ያካሄዱት ለህግ እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል።

 

 

Ø የጋምቤላውን እልቂት ተከትሎ ደቡብ ሱዳን መንግስት ባለስልጣኖች እርስ በርስ መካሰስ መጀመራቸው ታውቋል። የሱዳኑ ዕለታዊ ጋዜጣ ሱዳን ትሪቡን እንደዘገበው የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና ጀኔራሎች ለጋምቤላው ፍጅት የቦማ ግዛት ኃላፊዎችን ተጠያቂ አድርገዋል። ግዛት ገዥ ባባ ሜዳ ለጥቃቱ ጀርባ እንደሆ የመርሌ ጎሳ አባል የሆኑት /ጄኔራል ዲቪድ ዋዩ ተናግረው መረጃውን ከአካባቢው መሰብሰባቸውን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም ግዛት ኃላፊዎች ለእልቂቱ የጦር መሳሪያ በማቀበል በኑር ጎሳ አባላት ላይ ጥቃቱ ንዲፈጸም አስተባብረዋል በማለት የቦማ ባለሥልጣኖች የያገተቱን ህጻናት በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። የቦማ ግዛት ኃላፊዎች ግን የተሰነዘረባቸውን ክስ በማስተባበል በጋምቤላው ጥቃት እጃቸው እንደሌለና በግዛቱ ያሉ ታጣቂዎችም የደቡብ ሱዳን ጦር አባል ሆነው መካተታቸውን ተናግረዋል።

 

Ø ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ዓም አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ባወጣው ዘገባ ባለፈው ታህሳስ ወር የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም  350 የሚሆኑ የሺያ እስላም ተከታዮችን ገድሏል፣ አስከሬናቸውን በአንድ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ቀብሯል፣ እንዲሁም ድርጊቱን ለመሸፈን የተለያይ እርምጃዎችን ወስዷል በማለት ወንጅሎታል። የሰብአዊ ድርጅቱ በመግለጫው ላይ ሟቾቹ የተገደሉት የአንድ ወታደራዊ ክፍል መሪ የነበሩትን ጄኔራል ለመግደል ሙከራ ሲያደርጉ ነው በሚል ከናይጄሪያ መከላከያ ተቋም የተሰጠውን ምክንያትም መሰረተ ቢስ ነው በማለት አጣጥሎታል። የናይጄሪያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል  በአምነስቲ የቀረበው ዘገባ ነጻና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ የተዘጋጀ አለመሆኑን ገልጾ ዘገባውን ከማውጣቱ በፊት ስለዝርዝሩ ሊያሳውቀንና አስተያየታችንን ሊጠይቅ ይገባው  ነበር ብሏል። ትክክለኛ መረጃ አለን ካሉ ያቅርቡና ያሳምኑን የሚል ቃልም አሳምቷል።  ባለፈው ታህሳስ ወር የኢስላሚክ ሙቭመንት ኦፍ ናይጄሪያ የተባለው የሺያ ሙስሊም ድርጅት  አባላት በሰሜን ናይጀሪያ ውስጥ በጸሎት ላይ እያሉ በነበረት ወቅት የወታደራዊ ተቋም መሪ የየሆኑት ጄኔራልን አጅቦ የነበረው ኮንቮይ በአካባቢው እንዳያልፍ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ በማሰማታቸው  ወታደሩ በወሰደው የበቀል እርምጃ ከ350 ሰዎች በላይ ለመግደል ችሏል ተብሏል። ይህንንም ሀቅ ባለፈው ሳምንት አንድ የናይጄሪያ ከፍተኛ ባለስልጣን የመሰከረ  መሆኑ ተገልጿል። አምነስቲ ኢንተናሽናል በዘገባው ላይ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ በጉዳዩ ላይ ምርመራ ተካሄዶ አስፈላጊው እርምጃ ይወሰዳል ብለው ቃል ቢገቡም እስካሁን የተወሰደ እርምጃ የለም ሲል  ዘግቧል። እንዲያውም በተጻራራው  የናይጀሪያ የዜና አውታሮች ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን  በዘገቡት ዜና ካዱና በተባለችው ከተማ 50 የሚሆኑ የሺያ እምነት ተክታይ አባላት አንድ ወታደር ገድለዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው የሞት ቅጣት እንዲፈጸምባቸው እየተጠየቀ መሆኑ ተገልጿል።

በተያያዘ ዜና በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ቤት ንብረታቸውን ጥለው በተሰደዱ ዜጎች ካምፕ አጠገብ አንዲት የቦኮ ሃራም  አጥፍቶ ጠፊ ባፈነድችው ቦምብ ሰባት ሰዎች የተደሉ መሆናቸውን የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ ሐሙስ ዕለት ከሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። የቦምቡ ፍንዳታ የደረሰው ባለፈው ረቡዕ ሚያዚያ 12 ቀን 2008 ዓም በንጋቱ ላይ ሲሆን ማይዱጉሪ ከተባለው ከተማ 130 ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኝ የናይጄሪያና የካሜሩን ወሰን ላይ ነው። ቦምቦችን ለማፈንዳት  ቦኮ ሃራም ከላካቸው ሁለት ሴቶች መካከል አንደኛዋ የያዛቸውን ቦምብ ሳታፈንዳ እጅ ከፍንጅ ተይዛለች ተብሏል። ቦኮሃራም አእምሮ የሚመረዝ እጽን እየሰጠ ቦምብ እንዲያፈነዱ የሚልካቸው ሴቶችና ህጻናት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱ ይታወቃል።

 

Ø ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ይፋ ባደረገው ዘገባ በግብጽ ፖሊሶች ቁጥጥር ስር ያሉ እስረኞች ሰቆቃዊ ድርጊት እየተፈጸመባቸው መሆኑን አጋልጧል። ከእነዚህ መካከል የተወሰኑት ህጻናት መሆናቸውንም ገልጿል። የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቱ ይፋ ባደረገው ዘገባ ባለፈው የካቲት ወር ህገ ወጥ በሆኑ የተቃዋሚ ስልፎች ላይ ተሳትፋችኋል፤ የንብረትና መዝረፍና የማቃጠል ወንጀል ፈጽማችኋል ተብለው  በአሌክሳንድሪያ የታሰሩ ዜጎች በእስር ላይ እያሉ ከፍተኛ ድብደባና የአካል ስቃይ የደረሰባቸው መሆኑን ለቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ዘግቧል። ድርጅቱ ከ20 በላይ በሚሆኑ እስረኞች ላይ ድብደባ እንደተፈጸመ መረጃ የደረሰው መሆኑን ገልጾ የግብጽ መንግስት ከፍተኛ ድብደባ የፈጸመባቸው እስረኞች በቁጥጥር ስር መደረጋቸውን በመጀመሪያ ክዶ የነበረ መሆኑን የሰብአዊ መብት ድርጅት መግለጫ ያጋልጣል። የግብጽ ባለስልጣኖች ዘገባው የፈጠራ መረጃው የያያዘ ነው በማለት አጣጥለውታል።  ወታደራዊ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ በዜጎች ላይ የሚወስደው አሰቃቂ እርምጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ በየጊዜው የተገለጸ ሲሆን ባለፈው ዓመት በቁጥጥር ስር የሚገኙ እስረኞችን በድብደባ  ገድላችኋል ተብለው በርካታ የግብጽ ፖሊሶች ክስ ተመስርቶባቸው የተፈረደባቸው መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø የቻዱ ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዲቢ ለአምስተኛ ጊዜ በምርጫ አሸንፈው ስልጣን የተቀዳጁ መሆኑ ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ተነገረ። ኢድሪስ ዲቢ  የድምጹን 60 ከመቶ በማግኘት  17 የሚሆኑ ተወዳዳሪዎቻቸውን አሸንፈው ነው ድል ተቀዳጅተዋል የተባለ ሲሆን ያገኙት ከድምጹ 50 ከመቶ በላይ በማግኘታቸው ሁለተኛ ዙር ምርጫ ማካሄድ አላስፈለጋም። ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫው የተጭበረበረ ስለሆነ አንቀበለውም ብለዋል። በርካታ የምርጫ ሳጥኖች የተሰረቁ መሆናቸውንና ፤ ወታደሮችን ጨምሮ ኢድሪስ ዲቢን  በመቃወም ድምጽ የሰጡ ግለሰቦች መታሰራቸውና መዳረሻቸው መጥፋቱን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ታዛቢዎች ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ ነው ቢሉም በርካታ ሰዎች ያልተዋጠላቸው መሆኑ ታይቷል። በምርጫው ወቅት የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን በሞባይል ስልኮች መልክቶችን መለዋውጥ ሳይቻል ቀርቷል። ከጥቂት ቀናት በፊት አራት የሲቪል ማህበራት መሪዎች ሕዝቡን ለስላማዊ ስልፍ አነሳስታችኋል በማለት መታሰራቸው ይታወሳል። ምርጫው የተካሄደው የሆስፒታል ሰራተኞች የትምህርት ቤት አስተማሪዎችና የዩቢቨርስቲ ፕሮፈሰሮች የተወዘፈ ደሞዛቸው እንዲከፈል የስራ ማቆም አድማ ባደረጉበት ወቅት ነው። ቻድ በ1995 ዓም በአገሪቱ የተገኘውን የነዳጅ ምርት መጠቀም ብትጀምርም 13 ሚሊዮን የሚሆነው የአገሪቱ ዜጋ ከድህነት በታች በሆነ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ የሚኖር ሲሆን  ከቻድ ዜጎች መካከል ከ 10 ሩ  ሰባቱ መጻፍ እና ማንበብ እንደማይችሉ መረጃዎች ይፋ አድርገዋል።

 

 

Ø 36 የጋምቢያ  የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችና አባላት ሐሙስ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው በልዩ ልዩ ወንጀሎች የተከሰሡ መሆናቸው ተገለጸ፡፤ የዩናይትድ ዴሞክራቲክ ፓርቲ መሪ ሚስተር ዳርቦይ ከተከሰሱት መካከል አንዱ ሲሆኑ ተካሶቹ በስድስት የተለያዩ ክሶች የተከሰሱ መሆናቸውና በዋስ ለፈቱ መቻላቻውና አለመቻላቸው በሚቀጥለው ሳምንት እስከሚወሰን ድረሰ በእስር ቤት እንዲቆዩ የተደረገ መሆኑም ተነግሯል። የዩናይትድ ዴሞክራቲክ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ጸሐፊ ሚስተር ሳንዴንግ እና ሌሎች ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት ያልተፈቀደ ሰላማዊ ስልፍ አደራጅታችኋል በሚል ሰበብ የታሰሩ መሆናቸው ሲታወቅ ግለሰቡና ሌሎች ሁለት ሴቶች በእስር ቤት በድብደባ ህይወታቸው ያለፈው መሆኑ ተነግሯል። የፓርቲው መሪ ሚስተር ዳርቦይ እና ሌሎች ተከሳቾች የታሰሩት ባለፈው ቅዳሜ ቀደም ብለው የታሰሩት አባሎቻቸው የታሰሩበት ምክንያት አለአግባብ አለመሆኑን ለመግለጽ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ሲያደርጉ ነው ። የአፍሪካ የሂውማን ራይትስ ኮሚሽን እና ሌሎች የሰብአዊ መብት ድርጅቶች የታሰሩትን  ለመጎብኘት እንዲችሉ ፈቃድ የጠየቁ መሆናቸው ታውቋል። 

 

 

 

ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø ስድስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የጋምቤላ እልቂት በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱ ሕጻናት ሊገኙ አለመቻላቸው አጠያያቂ እየሆነ ነው። ዓለም አቀፍ የሕጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሲኤፍም ከጋምቤላ የተጠለፉ ሕጻናት አለምንም ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አድርጓል። በጋምቤላው እልቂት ከ200 ሰው በላይ ተገድለው በመቶ የሚቆጠሩ ቆስለው ከ20 ሺ በላይ ከቀየው ተፈናቅሎ መሰደዱም ታውቋል። የወያኔ መሪዎች ከቀያቸው ለተፈናቀሉት ዜጎች የሚያደርጉት እንክብካቤ በጋምቤላ ካሉት የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በጣም ያነሰ እንደሆነ እየተገለጸ ሲሆን የወያኔ ወታደራዊ አለቆች ህጻናቱን ለማስለቀቅ ፍንጭ አግኘተናል አካባቢውን እየከበብን ነው ይበሉ እንጅ ዝርዝር ጉዳዮችን ግን አላብራሩም።

Ø የአባይን ግድብ አስመልክቶ በወያኔ በግብጽና በሱዳን መካከል የሚደረገው የዙር ንግግር ባለበት እርገጥ በሆነበት በአሁኑ ሰዓት የወያኔ የግብጽና የሱዳን የውሃ ሚኒስትሮች ካርቱም ላይ አንድ ዝግ ስብሰባ ማድረጋቸውን የሱዳን ሚዲያዎች ዘግበዋል። በዋናነት የአባይ ግድብን በሚመለከት መምከራቸው ታውቋል።

 

Ø ባለፈው ሳምንት በምዕራብ አፍሪካ በምትገኘው ጋምቢያ ውስጥ የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ አደራጅታችኋል በሚል ወደ 40 የሚጠቁ ዜጎች ተከሰው ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸው ተገለጸ። ባለፈው ሳምንት በጋምቢያ ውስጥ ሀገሪቱ የምርጫ አሰራርና ህግ እንዲሻሻል ለመጠየቅ በተቃዋሚ ፓርቲዎች አደራጀነት ከፍተኛ የተቃውሞ ስልፍ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ፖሊስ ስልፉን ለመበተን ጥያት የተኮሰ መሆኑና በርካታ ሰዎችም ይዞ ተነግሯል። ተይዘው ከነበሩት መካከል ሶስት የተቃዋሚው ፓርቲ ነባር አባላት በእስር ቤት ውስጥ መገዳላቸው ይታወቃል። ጋምቢያ በሚቀጥለው ዓመት ታህሳስ ወር ውስጥ ብሄራዊ ምርጫ ለማካሄድ ማቀዷ ታካሄዳለች ተብሏል።

 

Ø በብሩንዲ ዋና ከተማ በብጁምብራ አንድ የኮሎኔል ማዕረግ ያለው ወታደራዊ መኮንን ባልታወቁ ሰዎች መገደሉ የአገር ውስጥ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ኮሎኔል አማኑኤል ቡዙቦና የተባለው መኮንን የተገደለው ከአንድ ሌላ ሰው ጋር በሞተር ቢስክሌት እየተጓዘ በነበረበት ወቅት ላይ ሲሆን አብሮት የነበረውም ሰው የተገደለ መሆኑ ታውቋል። በብሩንዲ ውስጥ የርስ በርስ ግጭት ከተጀመረ ወዲህ   ወታደራዊ መኮንኖች ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በተደጋጋሚ እየተገደሉ መሆናቸው ሲታወቅ የመንግስቱን ስልጣን በያዘው ኃይልና በተቃዋሚዎች መካከል እርቅ እስካልሰፈነ ድረስ ችግሩ ሊቀጥል እንደሚችል ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይናገራሉ።

 

Ø ባለፈው ማክሰኞ ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓም ለረቡዕ አጥቢያ  የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች  በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ዳማቱሩ ከተማ በሚገኝ አንድ መንደር ውስጥ በፈረስ ሆነው ወረራ ከአካሄዱ በኋላ 11 ሰዎች የገደሉ መሆናቸው በአካባቢው የነበሩ የዓይን እማኞች ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። ከሁለት ሳምንት በፊትም ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመው 20 ሰዎች መግደላቸው ተነግሯል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች እኩለ ሌሊት ላይ ወደ መንደሯ ገብተው የእሩምታ ተኩስ ሲከፍቱ ነዋሪዎች በመደናገጥ ቤታቸው እየጣሉ የወጡ ሲሆን በነበረው ተኩስ አስራ አንድ ሰዎች መገደላቸውና እና ሌሎች ቀጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ነዋሪዎቹ ተናግርዋል፡፤  አጥቂዎቹ እህል ንብረትና ከብቶች ከዘረፉ በኋላ መንደሩን አቃጥለው የሄዱ መሆናቸው ታውቋል፡፤ አሸባሪዎቹ  የድብቅ ካምፖችን በመስራት የጦር ስፈር አድርገው ከቆዩበት ሳምቢሳ ከተባለው ጫካ ሳይመጡ አልቀረም የሚል ግምት አለ። የናይጀሪያ ወታደራዊ ተቋም ቦኮ ሃራምን ማጥቃቱንና ማዳከሙን በመግለጽ በተደጋጋሚ መግለጫ የሰጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ቡድኑ  ጎላ ያለ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚያካሂዳቸው ጥቃቶች አለመዳከሙን ያሳያል የሚሉ በርካታ ናቸው።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ ላለፉት አራት ዓመት ከመስሪያ ግዥ ጋር ተያይዞ ፕሬዚዳንት ዙማ እና ሌሎች ባለስልጣናት ከፍተኛ ሙስና ፈጸመዋል በሚል ቀርቦ የነበረው ክስ ሲያጣራ የነበረው ኮሚሽን ስራውን መፈጸሙንና ፕሬዚዳንቱን ነጻ ማውጣቱን ፕሬዚዳንት ዙማ በሰጠቱ መግለጫ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ ሐሙስ ሚያዚያ 13 ቀን 2008 ዓ.ም በሰጡት መግለ ኮሚሽኑ ዘገባውን ያቀረበው ከአራት ወራት በፊት ቢሆንም አሁን ለሕዝብ ይፋ ሆኗል ካሉ በኋላ ባደረገው ምርመራ መሰረት በእሳቸውም ሆኖ በሌሎች ላይ ምንም ጥፋት ያላገኘ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሬዚዳንት ዙማ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው በነበሩበት ወቅት እሳቸውና አማካሪዎቻቸው ከዓለም አቀፍ የመስራሪያ ሻጭ ድርጅቶች በርካታ ገንዘብ ወስደዋል ተብለው ተከሰው የነበሩ ሲሆን አማካሪያቸው በተመሳሳይ ክስ የአስራ አምስት ዓመት እስራት የተፈረደባቸው መሆኑና ተቃዋሚዎች በአቃቤ ህጉ ላይ ያልሆነ ተጽእኖ አምጥተዋል በሚል ምክንያት በዙማ ላይ የነበረው ክስ እንዲነሳ ተድርጎ የነበረ መሆኑ ይታወሳል። ዙማ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ በኋላ ጉዳዩን እንዲመረምር አዲስ ኮሚሽን ቢያቋቁሙም፤ አካሉ ኃይል እና ስልጣን ኖሮት አለተጽእኖ  ስራውን ሊያከናውን የሚችል አይደለም በማለት አንዳንድ ወገኖች  ሲያጣጥሉት እንደነበር አይዘነጋም።

 

 

 

 

ሚያዚያ 12 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø የወያኔ መሪዎች የአምስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን ዘመን እያሉ በሚጠሩት የህልም እቅድ ሰባትና ከዚያም በላይ ስኳር ፋብሪካ እንገነባለን፤ ስኳር ከእኛ ፍላጎት በላይ አምርተን ወደ ውጭ እንልካለን በማለት ፕሮፓጋንዳ ሲነፉ የቆዩ መሆናቸውና  የወያኔም የፕሮፓጋንዳ ወፍጭዎች ይህን ተቀብለው ማስታጋባታቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን ደግሞ የስኳር እጥረት በመኖሩ ስኳር ከውጭ ለማስገባትና ዋጋውን ለማናር ዝግጅት መደረጉ እየተነገረ ነው። የወያኔ መሪዎች የስኳር ፋብሪካ ይገነባበታል የተባለውን በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ብር ከመዘበሩ ወዲህ አሁን ደግሞ ስኳር ከውጭ በማስመጣት ና በመቸብቸብ ትርፍ ለማግኘት ያቀዱ ሲሆን የአንድ ኪሎ ስኳር ዋጋ አሁን ባለበት 18 ብር ከ60 ሳንቲም ወደ 21 ብር ከፍ እንደሚል ታውቋል። የዋጋ ጭማሪው ስኳሩ ከውጭ ስለሚመጣ የውጭ ምንዛሬ ማጣጫ ነው ተብሏል።

Ø በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱና የነዳጅ ማዳያዎችም በመኪናዎች ስልፍ መጨናነቃቸው ታውቋል። የነዳጅ ዕጥረቱ በተለይ በናፍታ ላይ የበረታ ሲሆን ይህን ተከትሎ በአዲስ አበባ የትራንስፖርት ችግር እየፈጠረ መሆኑ ተደርሶበታል። በአሁኑ ወቅት  የነዳጅ ዕጥረቱ ለምን እንደተከሰተ የወያኔ መሪዎች የሰጡት ይፋ ማብራሪያ የሌለ ሲሆን አንዳንድ ከፍተኛ ካድሬ ነን ባዮች በቅርብ በጣለው ኃይለኛ ዝናም  በጂቡቲ መስመር የሚገኙ መንገዶችንና ድልድዮች ከጥቅም ውጭ በማድረጉ የመጫኛ ቦቴዎች እንደልብ መንቀሳቀስ ባለማቻላቸው በማለት ለመግለጽ ይሞክራሉ።

Ø በኢትዮጵያ ውስጥ ካለው የመኪና ብዛትና በመኪና ግጭት ምክንያት የሚሞተው ሰው ተመጣጣኝ አለመሆኑና በትራፊክ አደጋ የሚሞቱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ሪፖርት በሚደረግበት ሰዓት በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓም. በሰሜን ወሎ በቆቦ ከተማ እጅግ አሳዛኝ የመኪና አደጋ የደረሰ ሲሆን በዚህ አደጋ በትንሹ የ 25 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ ታውቋል። አደጋው ከጠዋቱ አስር ሰዓት መድረሱን የገለጸው መረጃ  ሸቀጣ ሸቀጦችን ጭኖ ከመቀሌ ይመጣ የነበረ አንድ ከባድ ካሚዮን 16 ተሳፋሪዎችን ይዞ ከቆቦ ወደ አላማጣ ይጓዝ ከነበረ ሚኒባስ ጋር በመጋጨቱ መሆኑ ሲታወቅ በግጭቱ አቅራቢያ የነበሩ በእግርና በብስኪሌት ይጓዙ የነበሩም ህይወታቸው መጥፋቱ ታውቋል።

Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ ሪክ ማቻር በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ በጁባ እገባለሁ ባሉበት ቀን ባለመግባታቸው በደቡብ ሱዳን ሰላም ሊወርድ ይችላል የሚለውን ተስፋ ያጨለመ  መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። ማቻር ጁባ ይገባሉ ተብሎ የነበረው ሰኞ ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ሲሆን ላለመሄዳቸው የሎጂስቲክስ ችግር እንደ ምክንያት ሆኖ ሲገለጽ ቆይቷል። የደቡብ ሱዳን መንግስት ማክሰኞ ዕለት ከሰጠው መግለጫ ለማወቅ እንደተቻለው ለጉዞው መዘግየት ምክንያት የሆነው ጉዳይ ማቻር ከስምምነቱ ውጭ በርካታ መሳሪዎችን የፀረ ታንክ የሆኑኑ በሌዘር የሚመሩ ሚሳየሎችና እንዲሁምከባድ መሳሪዎችን ይዘው ለመምጣት በመፈለጋቸውና በመከልከላቸው ነው ተብሏል።  እርቁን በማስተባበር  በኩል ግምባር ቀደም ሚና የነበራቸው የቀድሞ የቦትስዋና ፕሬዚዳንት ሁለቱም ወገኖች ስምምነቱን የፈረሙበትን መንፈስ እንዲጠብቁና እንዲያከብሩ ተማጽነዋል። አሜሪካ እና ሌሎች የምእራብ አገሮች ሚስተር ማቻር ቃል በገቡት መሰረት ወደ ጁባ አለመሄዳቸው በሰላሙ ሂደት ላይ ከፍተኛ አደጋ ፈጥሯል ብለዋል። የአማጽያኑ ቃል አቀባይ ለሚስተር ማቻር ጉዞ መዘግየት አሁንም የሎጂስቲክስ እና የአስተዳደር ችግር መሆኑን ገልጾ ረቡዕ ዕለት ወደ ጁባ ይገባሉ የሚል ቃል ሰጥቷል።

 

Ø ሳምንቱ መጀመሪያ ጀምሮ በዛምቢያ ዋና ከተማ በሉሳካ በውጭ ዜጎች በተለይም በሩዋንዳ ዜጎች ላይ ሲካሄድ የነበረው ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሎ ቢያንስ ሁለት ሰዎች በህይወታቸው መቃጠላቸው ታውቋል። ችግሩ የጀመረው  በዛምቢያ የሚኖሩ የሩዋንዳ ዜጎች ባህላዊ ተግባራቸውን ለመወጣት በሚል ሰባት የሚሆኑ ዛምብያውያንን ገድለውና  የአካሎቻቸውን አንዳንድ ክፍሎች ወስደው፣ አስከሬናቸውን መንገድ ላይ ጥለዋል በሚል በተነሳ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ነው። ዜጎችን ገድለዋል የተባሉ 10 ሩዋንዳውያን በፖሊስ ቁጥጥር ስር ቢደረጉም ተቃውሞ ቀጥሎ የሩዋንዳ ስደተኞች  ሱቆች የተዘረፉ መሆናቸውና ብዙዎችም በድንጋይና በሌሎች መሳሪያዎች ጥቃት ሲደርስባቸው የቆየ መሆኑ ተገልጿል። እስከማክሰኞች ሚያዚያ 11 ቀን ድረስ ከ62 በላይ ሱቆች የተዘረፉና የወደሙ ሲሆን መኪኖችና ሌሎች ንብረቶች ተቃጥለዋል። ፖሊስ ግጭቱን ለማብረድ በወሰደው እርምጃ በውጭ ዜጎች ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ ተገኙ ያላቸውን ከ200 ሰዎች በላይ በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑን ገልጿል። በ1986 ዓም ከሩዋንዳው እልቂት ያመለጡ ከ6500 በላይ የሚሆኑ ሩዋንዳውያን በዛምቢያ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል።

 

 

Ø በሰሜን ማሊ በእርዳታ መስጠት ተግባር ላይ ተሰማርተው ይሰሩ የነበሩ ሶስት የቀይ መስቀል ሰራተኞች ከቅዳሜ ጀምሮ ግንኙነት ያቋረጡ መሆናቸው ተነገረ። የእርዳታ ሰጭው ድርጅት ሠራተኞች መዳረሻቸው የጠፋው በሰሜን ማሊ ከአንድ መንደር ተነስተው ኪዳል ወደ ተባለው ከተማ በመገዝ ላይ እያሉ ሲሆን ምናልባት በአካባቢው ባሉ አማጽያን ኃይሎች ተጠልፈው ሳይወሰዱ አይቀርም የሚል ስጋት ፈጥሯል። የጠፉት ሰዎች ዜግነት ምን እንደሆን ባይታወቅም በደፈናው አፍርካውያን መሆናቸውን የቀይ መስቀል ቃል አቀባይ ገልጿል። በሰሜን ማሊ ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባል የአማጽያን ቡድን የሚንቀሳቀስ ሲሆን ከሁለት ዓመት በፊት ቡድኑ የጠለፋቸው  አራት የቀይ መስቀል ሰራተኞች በፈረንሳይ ወታድሮች አማካይነት ሊለቀቁ የቻሉ መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ማክሰኞ ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓም ሞሮኮ ያስወጣቻቸው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ባስቸኳይ እንዲመለሱ ጠይቀው ይህ ካልተደረገ ሁኔታውን አክራሪ ኃይሎች ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ አስጠንቀቀዋል። ባንኪ ሙን ሰኞ ሚያዚያ 10 ቀን ለተመድ የጸጥታ ምክር ቤት በላኩት ዘገባ የተባበሩት መንግስታት አካል ከምዕራብ ሳህራ ግዛት እንዲወጣ መደረጉ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ተጥሶ ጦርነቱ እንደገና የሚጀመርበትን እድል ያጎለብተዋል ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ሚያዚያ 20 ቀን 2008 በምዕራብ ሳህራ ግዛት የተመድ ተልእኮ ስለመቀጠሉና አለመቀጠሉ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የባንኪ ሙን ዘገባ በጉዳዩ ላይ ሞሮኮን ደግፈው በሚገኙት በፈረንሳይና በስፔን ላይ ተጽእኖ ሊያደርግ ይችላል የሚል ግምት ተወስዷል። በምዕራብ ሳህራ የስፔን ቅኝ ግዛት ሲያበቃ ሞሮኮ ግዛቱ የኔ ነው ብላ ለመጠቅለል ያደረገችውን ሙከራ በመቃውሞ ፖሊሳሪዮ የተባለ ነጻ አውጭ ድርጅት ለረጅም ዓመታት የትጥቅ ትግል ሲያካሄድ መቆየቱ ይታወሳል። በ1983 ዓም በተመድ አካማካይነት የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረገ በኋላ የግዛቱን ህልውና በውሳኔ ሕዝብ ለማስወሰን የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ግዛቱ መላኩ ይታወሳል። ድምጽ ሊሰጥ የሚችለው ማን ነው በሚለው ላይ ስምምነት ሊደረስ ባለመቻሉ እስካሁን ድረስ በውሳኔ ሕዝብ የአገሪቱን እድል ለመወሰን አልተቻለም። በቅርቡም የፖሊሳሪያ ድርጅት መሪ ተመድ ጠንከር ያለ እርምጃ ካልወሰደ ጦርነቱ እንደገና ሊጀመር እንደሚችል የሚገልጽ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው አይዘናጋም።

 

 

 

ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በኢኩዌዶሮ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 413 የደረሰ ሲሆን ከ2500 በላይ የሚሆኑት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል። ሰው የማዳኑ ፍለጋ  አሁን የቀጠለ ሲሆን ጊዜው እየጨመረ በሄደ መጠን የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከዚህ ከፍ ሊል እንደሚችል ተገምቷል። በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት የፈረሰውን እንደገና ለመጠገን በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ወጭ እንደሚያስፈልግ ተገምቷል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ላለፍት ሰባ አመታት በአገሪቱ ላይ ከደረሱት አደጋዎች መካከል ይህኛው ከፍተኛ ነው ብለዋል። ሰኞ ሚያዚያ 10 ቀን  በምዕራባዊ ግዛት የተለያዩ አነስተኛ የመሬት መንቀጥቀጦች መድረሳቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከፍተኛው ኃይል 5.1  ነው ተብሏል።

 

Ø ዛሬ ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓም በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ በካቡል አንድ አንድ መኪና ላይ የተጫነ ቦምብ ከፈነዳ በኋላ ታጣቂዎች በአደረጉት የተኩስ ጥቃት 28 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና 329 ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል። የታሊባን ቃል አቀባይ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኗል። ጥቃቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ጠዋት ላይ በከተማዋ መኖሪያ ቤቶች መስጊዶች ትምህርት ቤቶች እና የንግድ ሱቆች በብዛት በተከማቹበት አካባቢ ከሆነው ከመከላለክያ ሚኒስቴር ቢሮ አጠገብ ነው። ከተገደሉትና ከቆሰሉት መካከል ወታደሮችና የጸጥታ ኃይል አባላት እንደሚገኙበት ተገልጿል። ያልተረጋገጡ ምንጮች አጥቂዎቹ የብሔራዊ ጸጥታ መስርያ ቤትን እንዳጠቁ የተገለጸ ሲሆን ከፍንዳታው ቦታ በጥቂት ርቀት ላይ የሚገኘው የፕሬዚዳንቱ ቤተመንግስትም ለጥቃቱ የተጋለጠ መሆኑ ተነግሯል። ከፕሬዚዳንቱ ቢሮ በተሰጠ መግለጫ የአፍጋኒስታን መንግስት ድርጊቱን የኮነነ ሲሆን “ይህ ዓይነቱ የፈሪዎች ተግባር ጽናታችንንና ቁርጠኛነታችንን አይበግረውም” ብሏል።

 

Ø በኮንጎ ብራዛቪል ፑል ተብሎ በሚጠራው ደቡባዊ ግዛት ከሶስት ሳምንት በፊት የመንግስት ወታደሮች በሄሊኮፕተር አማካይነት ባካሄዱት የአየር ድብደባ ቢያንስ 30 የሚሆኑ ሰላማዊ ሰዎችን የገደሉ መሆናቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅት አጋልጧል።  የአየር ጥቃቱ ኒንጃ የተባሉት የቀድሞ የሚሊሺያ ቡድን አባላት ቀደም ብሎ በሰነዘሩት ጥቃት 17 ሰዎችን መግደላቸው ተከትሎ የተደረገ መሆኑን የመንግስት ቃል አቀባይ ቢገልጽም ሄሊኮፕተሮቹ የአየሩን ድብደባ ያካሄዱት በመኖሪያ ቤቶች፤ በትምህርት ቤቶች በአብያተ ክርስቲያን እና በህክምና አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ላይ በመሆኑ ከሰላሳ የበለጡ ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል በማለት አምነስቲ አጋልጧል።

 

Ø ባለፈው እሁድ ሚያዚያ 9 ቀን 2008 ዓም በመካከለኛው አፍሪካ ረፐብሊክ በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ተሰማርቶ የነበረ የሞሮኮ ዜግነት ያለው ግለሰብ በአልታወቀ ሰው የተገደለ መሆኑ ተነግሯል። ግለሰቡ የተገደለው በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በምትገኘው ራፋይ በተባለችው ከተማ ሲሆን በኡጋንዳ ውስጥ መሰረት ያደረገው የሎርድ ረዚስታንስ አርሚ የሚባለው ቡድን አባላት ሲያካሄዱ የነበርውን ጥቃት ለመከላከል ሙከራ ሲያደርግ ነው ተብሏል። የተመድ ዋና ጸሐፊ ድርጊቱን ኮንነው ገዳዩ ተይዞ ለፍርድ እንዲቀርብ ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት ማሳሰቢያ ልከዋል፡፤

 

Ø ሰኞ ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ በጁባ ይገባሉ ተብለው ሲጠበቁ የነበሩት የደቡብ ሱዳን የአማጽያን መሪ ሪክ ማቻር እስከማክሰኞ ሚያዚያ 11 ቀን ድረስ ያልገቡ መሆናቸው ታውቋል። ቀደም ብሎ አንዳንድ የሎጂስቲክስ ችግር ጉዟቸውን ያዘገየ መሆኑን ተጠቅሶ ሰኞ ወደ ማታ ገብተው ቃለ መሀላ ይፈጻማሉ የሚል መግለጫ ቢሰጥም እንደተጠበቀው ሳይሆን ቀርቷል። በዛሬው ዕለት የደቡብ ሱዳን አማጽያን ቃል አቀባይ ከጁባ እንዳስታወቀው አሁንም ቢሆን የሎጂስቲክስ ችግሩ ያልተፈታ መሆኑን ገልጾ መች ሊመጡ ይችላሉ የሚለውን መናገር እንደማይችል አስታውቋል። የተባለው የሎጂስቲክስ ችግር ምን እንደሆነ ባይታወቅም ችግሩ ከሳልቫ ኬር መንግስት ባለስልጣኖች ጋር ያለመስማማት ሳይሆን አይቀርም የሚል ሀሳብ በመስጠት ታዛቢዎች ጥርጣሬያቸውን ያስቀምጣሉ።

 

 

Ø በሊቢያ ምስራቃዊ ክፍል ያለውና ራሱን መንግስት ነኝ የሚለው ክፍል ፓርላማ   ትሪፖሊ በገባው የአንድነት መንግስት ላይ አቋም ለመውሰድ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 11 ቀን ስብሰባ ለማካሄድ አቅዶ የነበረ ቢሆንም በአባላቱ መካከል ያለው ልዩነት ከፍተኛ በመሆኑ ስብሰባው ሳይካሄድ የቀረ መሆኑ ተገልጿል። በውይይትና በድርድር የጋራ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረሰ የአንድነት መንግስቱን የሚደግፉና የሚቃወሙ የምክር ቤት አባላት የወከሏቸው ግለሰቦች የሚገኙበት ኮሚቴ  የተቋቋመ ሲሆን ይህ ኮሚቴ ሁሉንም ሊያስማማ የሚችል ሀሳብ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። በምክር ቤቱ አባላት መካከል የአቋም መሸጋሸግ ሊኖር ይችላል ከሚል ተስፋ ስብሰባውን ረቡዕ ሚያዚያ 12 ቀን ለማድረግ የታቀደ ቢሆንም እስከዚያው ድረስ ምን ያህሉ አቋማቸውን ሊለውጡ እንደሚችሉ ግልጽ አይደለም።

 

 

 

ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø  ዓርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ጋምቤላ ውስጥ 140 ሰላማዊ ሰዎችን መግደላቸውን መዘገባችን ይታወሳል። እሁድ ዕለት የወያኔ ባለሥልጣኖች እንደገለጹት በጋምቤላው ፍጅት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 208 መድረሱን 108 ደግሞ ታፍነው መወሰዳቸውን ና 75 የሚሆኑት ቆስለው ህክምና እየተከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የድቡብ ሱዳን ታጣቂዎች 2000 ከብቶችንም መዝረፋቸው ተገልጿል። የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ወደ ጋምቤላ በመግባት በሕዝብ ላይ እልቂት መፈጸማቸው ተራ የጎሳ ግጭት እንደማይመስል የተገመተ ሲሆን ትክክለኛው ምክንያት ግን እስካሁን እንዳልተገኘና የመላ ምት ሀሳቦች እየተወረወሩ መሆናቸው ታውቋል። በጋምቤላ የወያኔ አገዛዝ ሕዝብን ለማሸበርና ለማስጨነቅ በርካታ ጦር ያስፍር እንጅ ድንበር ዘለል ታጣቂዎችን ለማስቆምና ሕዝብን ከእልቂት ለማዳን አለመቻሉ የወያኔ ጦር በጋምቤላ የተቀመጠው የሕዝብን ደህንነትና ድንበር ለማስጠበቅ ሳይሆን የአገዛዙን ህልውናና የአንድ ዘር የበላይነት ለመጠበቅ ብቻ ነው በማለት የሚተቹ ወገኖች ብዙ ናቸው። የወያኔ ጦር ከእልቂቱ በኋላ ታጣቂዎችን እየተከታተልኩና እየደመሰስኩ ነው በማለት መግለጫ አውጥቷል።

 

Ø  የወያኔ አገዛዝ ለመምህራን የመኖሪያ ቤትና ነፃ ትራንስፖርት ሊያቀርብ መሆኑን የወያኔው ትምህርት ሚኒስትር ሽፈራው ሽጉጤ አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትር ይህን እርምጃ ለመውሰድ የተገደደው የመምህራን ፍልሰትና እጥረትን ለመቋቋም መሆኑ የተነገረ ሲሆን በቅርቡም የደሞዝ ማስተካከያ የደረጋል ተብሏል። በዕቅዱ መሠረት በከተማና በገጠር ያሉ መምህራን በትምህርት ቤታቸው አካባቢ ቤት እንዲሰጣቸው፣ በገጠር ያለ ሊዝ ክፍያ መሬት እንዲሰጣቸው የሚደረግ ሲሆን በከተማ ደግሞ በአነስተኛ ወይንም በመነሻ ሊዝ መሬት እንዲያገኙ ይደረጋል ተብሏል። በአዲስ አበባ ከተማ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመምህራን ለማከራየት ጊዜያዊ መፍትኄ እንደተባለና በዘላቂነት ግን መምህራኑ በኅበረት የቁጠባ ቤት እንዲሰሩ ይደረጋል። ከዚህ በተጨማሪ የአዲስ አበባ መምህራን በተዘጋጀላቸው ልዩ መታወቂያ በአንበሳ አውቶቡስ በአዲስ አበባ ውስጥ በነጻ ይጓጓዛሉ። ይህ ዕቅድ ከሚቅጥለው ወር ግንቦት ወር ላይ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል። ወያኔ ለመምህራኑ የደሞዝ ጭማሪና ጥቅማ ጥቅም ለመስጠት የተገደደው በመምህራኑ  ግፊትና ተጽእኖ መሆኑ ታውቋል።

 

 

Ø  የወያኔ አገዛዝ መሪዎች የሕዝብና የአገር ሀብትን ለመዝረፍና ለመክበር ልዩ ልዩ ፕሮጀክት ነደፍን የልማት ዕቅድ አወጣን በማለት ገንዘብ መሰብሰብና ገንዘብ መዝረፉ በየወቅቱ የተጋለጠና የተዘገበ መሆኑ ይታወሳል። የወያኔ መሪዎች ለዓባይ ግድብ በማለት ገንዘብ በመሰብሰብ ቦንድ በመሸጥ የራሳችውን ኪስ እንደሚያዳብሩ ለትግራይ ተወላጅ ብቻ ተቋራጭና የንግድ ድርጅቶች ኮንታራት እንደሚሰጡ መገለጡ የሚታወስ ሲሆን አሁን ደግሞ ለአባይ ግድብ የተዋጣ 400 ሺህ ብር መድረሻው አለምታወቁ ተገልጿል። ገንዝቡ ከቦሌ መድኃኒ ዓለም ቤተክርሲትያን ካህናትና ሠራተኞች በወር በወር ከደሞዛቸው የተቆረጠ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን በምን ዓይነት ሁኔታ እንደጠፋና የት እንድደረሰ አልታወቀም። ይህ ከአራት ዓመት በፊት የተሰጠ የግድቡ መዋጮ የት ደረሰ ብሎ ሲጠየቅ እስከዛሬ ድረስ ምላሽ ያላገኘው ጉዳይ የወያኔ መሪዎች ከራሳችው ካባ ለባሽ ካድሬዎቻቸውና ከድርጅት ሰዎች ጋር የዘረፉት መሆኑ የታወቀ ሲሆን የበላይ ባለስልጣኖችም ስርቆቱን እያድበሰበሱት ይገኛሉ።

 

Ø  በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ፖለቲካዊና ወታደራዊ ሁኔታን ያከረዋል የተባለ የጦር ሠፈር አሰብ ላይ መቋቋሙን ወታደራዊ ጉዳይን የሚከታተሉ ምንጮች አስታውቀዋል። ሻዕቢያ በአሰብ ወደብ አቅራቢያ ያለውን የአውሮፕላን ማረፊያ ለተባበሩት አረብ ኤምሬት የጦር ሰፈር አገልግሎት የሰጠ ሲሆን የተባበሩት አረብ ኤምሬትም በአሰብ ወደብ ላይ አንድ የባህር ኃይል የጦር ሠፈር እየገነባች መሆኗ ታውቋል። የባህር ኃይሉ የጦር ሰፈር ለ30 ዓመት ኮንትራት የተገነባ ሲሆን ለሻዕቢያ የተሰጠው ክፍያ ግን አልተገለጸም። ሻዕቢያ በየመን የእርስ በርስ ጦርነት ከአረብና ከገልፍ አገሮች ጎን በመቆም 400 ወታደሮቹን በሁቲዎች ላይ ማዝመቱ ይታወቃል። ሳኡዲ አረቢያም ከተባበሩት አረብ ኤምሬት ጎን በመሆን ቀይ ባህርን ሙሉ በሙሉ በአረብ አገሮች ቁጥጥር ስር በማድረግ በምስራቅ አፍሪካ የፖሊቲካና ወታደራዊ ተጽእኖዋን ለማጠናከር ጥረት እያደረገች ናት ተብሏል። የአረብና የገልፍ አገሮች በተለይም ሳኡዲ አረቢያና የአረብ ኤምሬት የኢራን ፖለቲካዊና ወታደራዊ እንቅስቃሴን ለመገደብ የአሰብ ወደብን እንደመንደረደሪያ እየተጠቀሙበት መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø  ቅዳሜ ሚያዚያ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. በኢኩዌዶር በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት እስካሁን ድረስ 278 ሰዎች መሞታቸውና ከ2000 በላይ የአካል ጉዳተኞች መሆናቸው ሲታወቅ ቁጥሩ ከዚህ በላይ ከፍል ሊል እንደሚችል በጣሊያን አገር ጉብኝታቸውን አቋርጠው የተመለሱት የኢኳደር ፕሬዚዳንት በቴለቪዥን ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል።  መጠኑ 7.8 የሆነው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ የኢኳደርን የወደብ አካባቢዎች በሙሉ ያጠቃ ሲሆን አንዳንድ ከተሞችን ክፉኛ የጎዳ መሆኑ ተነግሯል።  የሰው ህይወትን ለማዳን 10 ሺ ወታደሮችና 3 ሺ አምስት መቶ ፖሊሶች ወደ አካባቢ የተላኩ መሆኑም ተነግሯል። ከመሬት መንቀጥቀጡ ማዕከል አጠገብ የምትገኘው ፔዴርናሌስ በምትባለዋ ከተማ ውስጥ በርካታ ህንጻዎች የተደረመሱ ሲሆን ከ 400 ሰዎች በላይ ሊሞቱ ይችላሉ የሚል ስጋት አለ። 300 ሺ ሰው የሚኖርባት ፖርቶቪየጆ በተባለችው ከተማ ውስጥም ህንጻዎችና መንገዶች የተደረመሱ ሲሆን የሰው ህይወትን ለማትረፍ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተገልጿል። በኢኩዌዶር በደረሰውና ቅዳሜ ጠዋት በጃፓን በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ መካከል ግንኙነት የሌለ መሆኑ ሳይንቲስቶች ይናገራሉ።

 

Ø  እሁድ ሚያዚያ 9 ቀን ከግብጽ ወደብ ወደ አውሮፓ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ በሚዴትራኒያን ባህር ላይ የሰጠመች መሆኑ ተነግሯል። ጀልባዋ 400 ስደተኞችን ጭና የነበረ ሲሆን ከስደተኞች አብዛኞች የሱማሌ ዜጎች መሆናቸው ተገልጿል። በህይወት ከዳኑት መካከል ጥቂቶቹ ወደ ግሪክ ደሴት የተወሰዱ መሆናቸውም ታውቋል። ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ 180 ሺ የሚሆኑ ስደተኞች ወደ አውሮፓ ለመግባት ጥረት ማድረጋቸውን የተባበሩት መንግስታት ምንጮች ሲናገሩ  ከ800 በላይ የሆኑ ስደተኞች ባህር ውስጥ በመስጠምም ሆነ በሌላ ምክንያት  ህይወታቸው ያለፈ መሆኑን  ገልጸዋል።

 

 

Ø  በሱማሊያ ውስጥ የአፍሪካ አንድነት የሰላም አስከባሪ ወታደሮች ሰላማዊ ሰዎችን በመግደላቸው ነዋሪው ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማቱን ከአካባቢው የሚገኘው ዜና ያስረዳል።  የሰማንያ ዓመት አሮጊትና ዘጠኛ አመት ያላት የልጅ ልጃቸው ታመው በአንድ መኪና ወደ ሞቃዲሾ ሲወሰዱ የአፍሪካ አንድነት የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ወታደሮች በመንገድ ላይ ተኩስ ከፍተው አሮጊቷንና የልጅ ልጃቸውን እንዲሁም በመኪና ውስጥ የነበሩትን ሌሎች ሁለት ሰዎች የገደሉ መሆናቸው ተነግሯል። የታችኛው ሸብሌ ግዛት ነዋሪዎች ድርጊቱን በማወገዝ ተቃውሞ አሰምተዋል። የሰላም አስከባሪው ኃይል ባለስልጣኖች ድርጊቱ የተፈጸመ መሆኑን ያመኑ ቢሆንም ወታድሮቹ ተኩስ ሊከፍቱ የቻሉት መኪናው እንዲቆም ቢጠየቅ ለማቆም ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነው ብለዋል። ከስደስት አገሮች የተወጣጣ 22 ሺ ጦር በአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ስም  በሶማሊያ ውስጥ እንደሚገኝ ይታወቃል።

 

Ø  ሰኞ ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በሚገኘው በቦርኖ ግዛት ውስጥ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የናይጀሪያን ወታደሮች ያጠቁ መሆናቸው ተነግሯል። ውጊያው የተካሄደው ከሜይዱጉሪ ከተማ አጠገብ በምትገኘው ካሬቶ በተባለቸው መንደር ሲሆን ታጣቂዎቹ ስላደረሱት  ሆነ ስለደረሰባቸው ጉዳት ዝርዝር መረጃ አልተኘም።

 

 

Ø  በጋምቢያ ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በእስር ላይ እንዳሉ መገደላቸው ታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የተያዙት ሐሙስ ሚያዚያ 6 ቀን 2008 ዓም የጋምቢያ ወጣቶችና ሌሎች ተቃዋሚዎች በአገሪቱ ውስጥ የምርጫ ሕግና ሂደት ማሻሸያ እንዲደረግበት የሚጠይቁ ሃሳቦችን በማቅረብ ትእይንተ ህዝብ ሲያደርጉ ነው ተብሏል። በወቅቱ ፖሲሶች በተኩስ ስልፉን የበተኑት ሲሆን 25 የሚሆኑ ሰልፈኞችን ያሰሩ መሆናቸውም ታውቋል።  እሁድ ሚያዚያ 9 ቀን 2008 ዓ.ም. የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ባወጡት መግለጫ የተቃዋሚው ፓርቲ አባላት በእስር ቤት ውስጥ መገደላቸው በእጅጉ ያሳዘናቸው መሆኑን ገልጸው ስለአገዳደላቸው አስቸኳይ ምርመራ እንዲካሄድ ጠይቀዋል። ጋምቢያ ባለፈው ታህሳስ ወር ብሔራዊ ምርጫ ያካሄደች ሲሆን የሰብአዊ መብት በማፈን የሚከሰሱትና ከ1986 ዓ.ም፣ ጀምሮ በስልጣን ላይ ያሉት ሚስተር ጃሜህ ለሌላ የስልጣን ዘመን የተመረጡ መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø  በብሩንዲ በስልጣን ላይ የሚገኘው ፓርቲ አባላት የሆኑ አራት ሰዎች ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው ተነገረ። ሰዎቹ የተገደሉት ቅዳሜ ሚያዚያ 8 ቀን በአንድ ቡና ቤት ውስጥ ተቀምጠው እየተዝናኑ ሳለ የወታደር ልብስ በለበሱ የማይታወቁ ሰዎች መሆኑን ከግድያው ያመለጠና ስሙን መጥቀስ የማይፈልግ ግለሰብ ከሰጠው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ባለፈው ሳምንት ብቻ በግድያ የሞቱት የገዥው ፓርቲ አባላት 10 መድረሱ ይነገራል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የእርቅ ውይይት ማድረግ ባለመፍቀዳቸው አገሪቱ ወደ ከፍተኛ የእርስ በርስ እልቂት እያመራች መሆኑን ብዙዎች ሲያሳስቡ ቆይተዋል።   

 

 

 

 

 

 

 

 

መጋቢት 08 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በዘንድ ድርቅና ረሃብ የተጎዱና ዕርዳታ ማግኘት ባለማቻላቸው ወደ አዲስ አበባ በስደት ያቀኑ ተረጅዎች አዲስ አበባ  አዲስ አበባ እንዳይገቡ መከልከላቸው ታውቋል። ተረጅዎቹ የመልካም ገጽታ ታበላሻላችሁ ተብሎ ከትውልድ ቀያቸው ደብረ ብርሃን ድረስ የተሰደዱና ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት ሙከራ ሲያደርጉ ነው በወያኔ ፖሊስና ወታደር የተከለከሉት። ተረጅዎቹ ዜጎች ከወሎ ክፍለ ሀገር ከባቴ ከሐይቅና አቅራቢያ ካሉ ከተሞችና  ገጠሮች በድርቁና በረሃብ የተነሳ የተሰደዱ እንደነበረ ታውቋል። ቀደም ሲል ደብረብርሃን የገባ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተረጅዎች በደብረ ብርሃን አውቶቡስ ተራ ግቢ ውስጥና በአካባቢው በከፍተኛ ችግር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። የወያኔ ፖሊስ ወታደርና ካድሬ ድርቅና ረሃብን እየተቋቋመ ነው፣ ከቀየው የተሰደደም የሞተም ሰው የለም በማለት ዓለምና ሀገርን እየዋሸ ባለበት ሰዓት የድርቅና የረሃብ ተረጅዎችና ጉዳተኞቹን በነጻ እንኳን የመንቀሳቀስ መብታቸውን መንፈጋቸው የአገዛዙን ጭካኔ የሚያሳይ ነው።

Ø በመላ ኢትዮጵያ በተንቀሳቀሰው ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ የተደናገጡት የወያኔ መሪዎች ከ300 በላይ ገድለው በሺህ የሚቆጠሩ ደብድበውና አስረው ተቃውሞውንና ቁጣውን አብርደናል በማለት በሚደሰኩሩበት በአሁኑ ሰዓት ሕዝባዊ ተቃውሞው አሁንም በመቀጠሉ አንዳንድ እርምጃዎች መውሰድ ጀምሯል። በተለይ በኦሮሞ አካባቢ ለነበረው አመጽ ለችግሩ መንስኤ የሆነው የመልካም አስተዳደር ጉድለት ነው በማለት ከ900 በላይ ከፍተኛ መካከለኛና ዝቅተኛ ካድሬዎችንና ኃላፊዎችን ከኃላፊነት ዝቅ በማድረግ በማባረርና በማሰር ተቃውሞን ለማብረድ እግረ መንገዱንም ለተቃውሞ ድርሻ አላቸው ያላቸውንም ማግለሉም ይታወሳል።  አሁን ደግሞ በ 2.4 ሚሊዮን ብር 800 ሺ የኦሮሞ ወጣቶችን ስራ ለማስያዝ እቅድ አውጥቻለሁ ብሏል። የኦሮሚያ ምክር ቤት የተባለው የወያኔ ታዛዥ እና አሽከር ተቋም ኃላፊዎች በዚህ ዓመት ብቻ ለ80 ሺ349 ስራ አጥ ወጣቶች የስራ እድል እንደሚፈጠር፣ ምን ምን ዓይነት ፕሮጀክት እንደሚከፈትና ምን ዓይነት ሥራ እንደሚፈጥር አብራርተዋል። በዚህ መሰረት ማኑፋክቸሪንግ ዘመናዊ እርሻና የማእድንና የግንባታ ሥራዎች ይፈጠራሉ ተብሏል። 200 ትራክተሮች 1400 የውሃ ፖምፖች 101 መሬት መቆፈሪያዎች መዘጋጀታቸውና ከሥራ ዕድሉም መካከል 60 በመቶው በምዕራብ ወለጋና በምዕራብ ሸዋ ላሉ ወጣቶች እንደሚውልና  ቀሪው ከ40 ከመቶ በሌሎች አካባቢዎች እንደሚውል ተነግሯል።

Ø 6021 ስደተኞች ካለፈው ማክሰኞ ከሚያዚያ 4 ቀን 2008 ጀምሮ አስቸጋሪውን የሜድትራኒያን የባህር ጉዞ አቁርጠው ጣልያን መድረሳቸውን ዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት አርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓ ም አስታቋ:: በዚህ ግዜ ውስጥ ወደ ግሪክ የተጓ ስደተኞች  174 ብቻ መሆናቸውን ጠቅሶ የአሮፓ ህብረት ከቱርክ ጋር ሰደተኞችን አስመልክቶ ያደረገው ስምምነት ስደተኞቹ በቀታ ወደ  አውሮፓ አገሮች ያመሩ ሳይገፋፏቸው ንዳልቀረ ተግምቷል::  ስደተኞቹ ለዓለም አቀፍ የስደኞች ድርጅት ንደተናገሩት ሁሉም ከሊቢያ መነሳታቸውን ገልጸው በላስቲካ ጅልባ ላይ በመሆን ጣልያን መግባታቸውና በየአንዳንዱ የላስቲክ ጀልባ ላይ 130 ስደተኞች ተጭነው አንደነበረም ተናግረዋል:: አብዛኛዎቹ ስደተኞች ከሰሃራ በታች ካሉ አገሮች ይሁን አንጅ ከአፍሪካ ቀንድ የመጡት ብዛት ንዳላቸውና በሻብያ ስር ካላቸው ኤርትራ የተሰደዱትን ግ ከፍተኛ  ቁጥር ንዳላቸው የስደተኞቹ ድርጅት ከሮም ቢሮ ግልጽ አደርጉዋል;; በያዝነው የፈርንጆች አመት 23 ሺ ስደተኞች ጣልያን ሲገ 153 ሺ 500 ደግሞ ግሪክ መድረሳቸውን ዓለም አቀፉ የስደተኛ ድርጅት አስታውቋል:: ከስደተኛ ውስጥ ምን ያህሉ ኢትዮጵያውያን አንደሆኑ የተለሰ ነገር የለም::

Ø አርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓ.. የደቡብ ሱዳን መንግስት ወታደሮችና ሙርሌ የተባለ ጎሳ አባላት ታጣቂዎች በአንድ ላይ በመሆን ተንቀሳቅሰው ወደኢትዮጵያ ግዛት በመግባት 10 የሚሆኑ መንደሮችን አጥቅተው 170 የኑዊር ጎሳ አባላትን የገደሉ መሆናቸውን ሱዳን ትሪቡን የተባለው ጋዜጣ በአርብ ዕለት እትሙ ዘግቦታል። ከተገደሉት ውስጥ አብዛኞቹ ሴቶች እና ሕጻናት መሆናቸው ተነግሯል። የተገደሉት የኑዌር ጎሳ አባላት ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ በወረራው ወቅት የሚደርስላቸው ኃይል ባለመኖሩና መሳርያ አልባ በመሆናቸው ሊጠቁ ችለዋል ተብሏል። በግጭቱ ቢያንስ 51 የሚሆኑ የሙርሌ ጎሳ አባላትም የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ከተገደሉት የሙርሌ ጎሳ አባላት መካከል ከፊሎቹ የተገደሉት ጥቃቱን ሲፈጽሙ የተወሰኑት ደግሞ ሲሸሹ ሲሆን ከአስከረኔአቸው የሙርሌ ዜጋ አባላት መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል ተብሏል።

 

Ø በኢትዮጵያ ባህላዊ ሙዚቃ ድገት የራሱን ከፍተኛ ድርሻና ሚና የተጫወተው የማሲንቆ ተጫዋችና ድምጻዊው ጌታ መሳይ አበበ በተወለደ 72 ዓመቱ ማረፉ ተገለጠ አርቲስ ጌታ መሳይ ከልጅነቱ አስከ ጎልምስናው የሙዚቃና የኪነት ሙያን ተቀላቅሎ የኖረ ሲሆን በአዲስ አበባ በቀድሞ የቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ የባህል ከል በኋላም በሀገር ፍቅር ትያትር በሙዚቀኛነት በድምጻነት አገልግሎት የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ አምባሰደር በመሆንም በተለያዩ የዓለም አገሮች በመዘዋወር በማንቆ ተጫዋችነትና በድምጻነት አገልግሏል አርቲስት ጌታ መሳይ አበበ በሕይወት ዘመኑ 200 በላይ ዜማዎችን የተጫወተ ሲሆን ከአስር በላይ ትያትሮችንም በመድረክ ላይ ከውኗል በኪነት ዓለም ውስጥም በማንቆ ተጫዋችነት በድምጻነት በመህርነትና በኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ባህል በዓለም ያስተዋወቀው አርቲስ ጌታ መሳይ አበበ 966 ድምጽ ባደረበት የጭንቅላት  ህመም የተነሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ::

 

 

Ø ሀሙስ ሚያዚያ 6 ቀን በከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ የተመታውና ገና በማገገም ላይ የነበረው  የደቡብ ጃፓን ግዛት ነዋሪ አርብ  ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓ.ም. መጠኑ 7.3 በሆኑ ሌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ተመቷል። በዚህኛው የመሬት መንቀጥቀጥ እስካሁን 20 ሰዎች መሞታቸውና በመቶ የሚቆጠሩ መቁሰላቸው ተዘግቧል። በርካታ ህንጻዎች በመድርመሳቸው ከህንጻዎች ስር ብዙ ሰዎች ከእነህይወታቸው ተቀብረው ይገኛሉ የሚል ስጋት አለ።  በአካባቢው የሚገኙትን ፖሊሶችና የእርዳታ ሰጭ ሠራተኞችን ለመርዳት 20 ሺ ወታደሮች ወደ አካባቢው ተልከዋል። መንገዶች የፈራረሱ ሲሆን ከፍተኛ የሆነ የመሬት መድርመስ የደረሰ መሆኑም ታይቷል። መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ዝናም ይዘንማል የሚል ግምት ስላለም የመሬት መደርመሱ በስፋት ሊቀጥል ይችላል የሚል ስጋት አለ።  ከ200 ሺ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ውጭ መሆናቸውም ተነግሯል። የቅዳሜው የመሬት መንቀጥቀጥ መጠን ሚያዚያ 6 ቀን ከደረሰው ጠንካራ ሲሆን ያጠቃቸው ክልሎችም ሰፊ እንደሆኑ ታውቋል። በአሁኑ ወቅት ከ2000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች የሆስፒታል አገልግሎት እየተሰጣቸው ሲሆን ከ92 ሺ ሰዎች በላይ ቤታቸው ለቀው በመጠለያ ካምፖች መቆየት ተገደዋል። ሰንዴ በሚባለው ቦታ ላይ የሚገኘው የኑክሊየር ቦታ የመፍረስ አደጋ ያላጋጠመው መሆኑ ተገልጿል። የቅዳሜው የመሬት መንቀጥቀጥ መጠን ከአምስት ዓመት በፊት ከደረሰውና ሱናሚ አስነስቶ በተለይ በፉኪሽማ በሚገኘው የኑክሊየር ቦታ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ካመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ የሚበልጥ መሆኑን አዋቂዎች ይናገራሉ።

 

Ø “በቤት ውስጥ ካሉ በረሮዎች ጋር የሚመሳሰሉት የቱስ ብሔርሰብ አባላት መጥፋት አለባቸው” በማለት በ 1984 ዓም ቅስቀሳ አካሄዶ ነበር የተባለው ሊዮን ሙጌሴራ የተባለው ግለሰብ ሩዋንዳ ውስጥ የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት መሆኑ ታወቀ። ግለሰቡ ይህንን ቅስቀሳ ያደረገው በ1984 ዓም ሩዋንዳ ውስጥ ባለስልጣን በነበረበት ወቅት ሲሆን 1000 ለሚሆኑ የፓርቲ አባላት ባደረገው ንግግር ቱሲዎችን ገድለው ሬሳቸውን ወንዝ ውስጥ እንዲጨምሩ ቅስቀሳ አካሂዷል የሚል ተጨባጭ ማስረጃ ተገኝቶበታል ተብሏል። በሩዋንዳ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ግለሰቡ ወደካናዳ መጥቶ በኩቤክ ግዛት በአንድ ኮሌጅ ውስጥ አስተማሪ ሆኖ የቆየ ሲሆን ካናዳ ውስጥ ክስ ቀርቦበት ለ12 ዓመት ያህል ከተከራከረ በኋላ ከአራት ዓመት በፊት ወደ ሩዋንዳ የተወሰደ መሆኑ ይታወሳል።  

 

Ø አርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008  በግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ ውስጥ የፕሬዚዳንት ሲሲን አስተዳደር በመቃወም ቁጥራቸው ከ 1000 በላይ የሚሆኑ ግብጻውያን የተቃውሞ ሰልፍ ማካሄዳቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ሰልፉ የተጠራው ቀደም ብሎ ሁለት የግብጽ ደሴቶች ለሳኡዲ አረቢያ መሰጣቸውን ለመቃወም ቢሆንም ሰልፈኞች ያሰሙ በነበረው መፈክር ውስጥ  የሲሲ መንግስት የሚያወግዙና ሲሲ ባስቸኳይ ከስልጣን እንዲወገዱ የሚጠይቁ እንደሚገኙበት ታውቋል።  ስልፉ እስከምሽት ድረስ የቆየ ሲሆን አብዛኛው ሰልፈኛ ከሄደ በኋላ የቀሩትን ጥቂት ሰዎች ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ መሆኑ ተገልጿል። ቀደም ብሎ በሌላው የከተማው ክፍል የተደረገውን ስልፍ ለመበተን ፖሊስ እርምጃ የወሰደ ሲሆን 12 ሰዎች ተይዘው መታሰራቸውም ተዘግቧል።

 

 

 

 

 

 

መጋቢት 07 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø  በመላ ኢትዮጵያ የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ አነጣጥሮ የተነሳው ስግብግብና  አልጠግብ ባይ የሆኑት መሪዎቹ የሚያካሂዱትን ዝርፊያና ቅሚያን ለመቃወም ሆኖ እያለ  የወያኔ መሪዎች ለችግሩ ሁሉ መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግር ነው በማለት በኦሮሞ አካባቢ የሚገኙ ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ካድሬዎችን ማባረር መጀመራቸውና አንዳንዶቹን ለማሰር መዘጋጀታቸው ታውቋል። የወያኔው የኦሮሚያ ክልል ኃላፊዎች እንደገለጹት በ 929 የስራ ኃላፊዎችና ካድሬዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልጾ ከእነዚህም ውስጥ 829 የሚሆኑት ከፍተኛና መካከለኛ የስራ ኃላፊነት የነበራቸው መሆኑን አስረድቷል። 121 ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከደረጃቸው ዝቅ እንዲሉ የተደረገ ሲሆን 708 መካከኛና ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሥልጣናቸው የተባረሩ መሆናቸው ተገልጿል።  ገሚሶቹ በሙስና ተከሰው ወደ እስር ቤት ይወረወራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ብዙ የፖሊቲካ ታዛቢዎች ግን በኦሮሞ አካባቢ የተፈጸመው የሕዝብ በድል ስርቆትና የመ ንጥቂያ በወያ መሪዎች ፊታውራሪነት መፈጸሙ እየታወቀ የኦሮሞ ባለስልጣናትን ተጠያቂ አድርጎ ማባረሩ ምናልባት በሕዝባዊ ተቃውሞምና ቁጣ ወቅት ከሕዝብ ጋር የወገኑትን ለመበቀል የወሰደው እርምጃ ነው ብለው ይናገራሉ።

 

Ø  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በዓለም የሰብአዊ መብት ይዞታን አስመልክቶ የሚያወጣውን ዓመታዊ ዘገባው ይፋ አድርጓል። ሪፖርቱ በዓለም የስብአዊ መብትን በመርገጥና በማፈን በዋናነት ከጠቀሳቸው አገሮች አንዱ የወያኔ አገዛዝ ሲሆን የሲቪል ማህበራትን በማገድ በሚድያና በኢንተርኔት ላይ ቁጥጥር በማድረግና በማፈን ተቃዋሚዎችን በመግደል በማሰርና በማዋከብ ወያኔ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፈው ዓመት አካሄድኩ ያለውን የምርጫ ድራማና ሁሉንም አሸነፍኩ ያለበትን ውጤት ዴሞክራሲያ ነበር በማለት ተችቶታል። የአሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በየዓመቱ የወያኔን ፀረ ዴሞክራሲያዊነትና የሰብአዊ መብት ረጋጭነት ይግለጥ እንጅ ጥርስ ያለው እርምጃ ያለመውሰዱ ይልቁንም የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሳይቀሩ ወያኔን በምርጫ ስልጣን ላይ የወጣ ዴሞራሲያዊ መንግስት ነው በማለት ማወደሳቸውን የሚያስታውሱ ወገኖች ዘገባው ጉንጭ አልፋ ከመሆን አይዘልም ይላሉ። ከጥቂት ቀናት በፊት አሜሪካ ከወያ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን ለመቀጠል ስምምነት መፈረሟንም በማስታወስ የአሜሪካው ዘገባ እና መግለጫ የሕዝብን ቁጣና ተቃውሞ ለማዘናጋት የሚደረግ  ይመስላል የሚሉ ወገኖች ሪካ ሞክራሲና ለሰባዊ መብት ከቆመች መጀመሪያ እንደ ወያኔ ባሉት አገዛዞች ላይ የፖሊቲካና የዲፕሎማሲ እርምጃ መውሰድ ነበረባት ይላሉ።

 

Ø  የእንግሊዝ መንግስት ሐሙስ ሚያዚያ 6 ቀን 2008 ዓም ጎቹ ባወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ እንግሊዛውያን በተለይም ወደ  አፋር፤ ኢትዮጵያና ሻእቢያዋ ኤርትራ ወሰን ወዳለው አካባቢ፤ በኢትዮጵያና በሱዳን ወሰን አካባቢ እንዲሁም ወደ ጋምቤላና ወደ ኦጋዴን እንዳይጓዙ ሲያስጠነቅቅ ወደ ምዕራብ ሸዋም የሚጓዙ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መክሯል። የእንግሊዙ የውጭና የኮመንዌልዝ ቢሮ ያወጣው የጉዞ ምክር መላ ኢትዮጵያን ያዳረሰና በአራቱም ማዕዘናት ያሉ ቦታዎች በሙሉ ለጉዞ ምክር የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ጠቅሷል። በየዓመቱ 20 የሚሆኑ የእንግሊዝ ዜጎች ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ ተጠቅሷል። 

 

 

Ø  የመጣለትን በጭብጨባና በፉጨት የሚቀበለው የወያኔ ፓርላማ በቅር የወያኔ መሪዎች የፍትህ ሚኒስቴርን አፍርሰው በጠቅላይ አቃቤ ህግ /ቤት ለመተካት ያውጡትን የህግ ረቂቅ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል። ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሚሆነውንና በምክትልነት የሚሰሩትን ግለሰቦች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማው አቅርቦ ያሾማል ተብሎ ይጠበቃል። አዲሱ የአቃቤ ህግ ቢሮና የወያኔው ፌዴራል ፖሊስ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ  ይሆናል መባሉና ጠቅላይ አቃቤ ህጉ በህግ ጉዳይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መክሮ ይስራ መባሉ በወያኔ ስርዓት ህግ አጥፍቶ የፖሊካ አሠራርን  ማስፈን የታቀደ  የወያ ሕግ ነው በማለት ብዙዎች ይተቹታል።

 

Ø  ሕዝብን ፀጥና ለጥ አድርጎ አስፈራርቶና አሸብሮ መግዛት የተለያዩ ዘዴዎችን ሲሞክር የቆየው  የወያኔው አገዛዝ የአዲስ አበባ ከተማን እንደገና ለማዋቀር በአዲስ መልክ ለማደራጀት ማቀዱን ከአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የተገኘው መረጃ አመልክቷል። በመረጃው መሠረት ማዘጋጃ ቤት ከዚህ በፊት ያከናውናቸው የነበሩ ተግባራት በሙሉ ወደ ወረዳ ተግባር የሚቀየሩ ሲሆን በደርግ ጊዜ ይሰራበት የነበረውና ወያኔ ያጠፋውን የቀጠና ምደባም እንደገና ሊጀምር ነው ተብሏል። ማዘጋጃ ቤት ከክዚህ ቀደም ሲያከናውናቸው የነበሩ የመሬት ጽዳት የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገድ የባይተዋር ቀብር ማስፈጸምና የመሳሰሉት ተግባራት ወደ ወረዳ እና ቀበሌ ዝቅ ብለው የሚሰሩ ይሆናሉ። የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ ከንቲባም ስራዎችን መከታተል ብቻ መደበኛ ስራው እንደሚሆንና የአዲስ አበባ መስተዳድር የሚለውን ስያሜ በከንቲባ ሹመት መስተዳደር ቀርቶ ወደ ርእሰ መስተዳድር ለማሳደግ መታቀዱን ምንጮች ገልጸዋል።  

 

 

Ø  ሐሙስ ሚያዚያ 6 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ጃፓን ኩማማቶ ከተባለው አካባቢው በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት 9 ሰዎች መሞታቸውና 860 በላይ የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል። አብዛኞቹ ሰዎች የሞቱት ማሺኪ በምትባል ከኩማማቶ ከተማ አጠገብ በምትገኝ አነስተኛ ከተማ ውስጥ አንድ የመኖሪያ አፓርትመንት በመደርመሱ ምክንያት መሆኑ ተዘግቧል። የመሬት መንቀጥቀጡ አደጋ በተከተሰተበት ወቅት በአካባቢው የሚኖሩ 40 ሰዎች ቤታቸውን ጥለው የተሰደዱና የአደሩ ሲሆን የመሬት መንቀጥቀጡ ርዝራዥ አሁንም እየተከሰተ ባለበት ሁኔታ ብዙዎቹ  ወደ ቤታቸው የተመለሱ መሆናቸው ተነግሯል። የአደጋ መከላከል ሰራተኞች በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት ከተደረመሱ ፍርስራሾች ውስጥ በህይወት ያሉ ሰዎችን የመፈለጉንና ነፍስ የማዳኑን ተግባር የቀጠሉ መሆናቸው ታውቋል። የመሬት መንቀጥቀጡ መጠን በመጀመሪያ 6.5 ነው ተብሎ የነበረ ቢሆንም በኋላ ወደ 6.1 እንዲወርድ ተደርጓል። በኩማማቶም ሆነ በአካባቢው ባሉ ከተሞች በርካታ ከፍተኛ ርዝመት ያላቸው ህንጻዎች ያሉ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን  በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው በጣም አነስተኛ መሆናቸው የህንጻ ሥራውን ደረጃ ከፍተኛነትና ጥራት ያሳያል ተብሏል። በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች ከተሞች የሚሰሩት ህንጻዎች መንቀጥቀጥ ቢደርስ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል የሚል ማሳሰቢያ ከአዋቂዎች ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።ንጻዎች በዝቀተኛ ደረጃ ሲምንቶና ደረጃቸውን ባልጠበቀ የህንጻ መሳሪያዎች በመሆኑ እንዲህ ዓይነት የመሬት

 

Ø  በአይቮሪ ኮስት ተይዞ በምርመራ ከሚገኝ አንድ ግለሰብ ላይ ተገኘ የተባለ ሰነድ አክራሪ እስላማውያን ጋናን ቶጎን ለማጥቃት ያቀዱ መሆናቸውን ማጋለጡ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።  ጋናና ቶጎ እስካሁን ድረስ የሽብር ጥቃት ያልተካሄደባቸው  የምዕራብ አፍሪካ አገሮች ሲሆኑ  ተገኘ የተባለው ሰነድ ያጋለጠው ዜና በጋናና በቶጎ ፍርሃትና ስጋትን ያሰራጨ መሆኑ ታውቋል። የጋና ፕሬዚዳንት በህዝቡ ውስጥ የተሰራጨውን ፍርሃት ለማስወገድ በሬዲዮ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ በመገናኚያ ብዙሃን አማካይነት ለሕዝብ ሳይሰራጭ ልንቆጣጠረው ብንችል ጥሩ ነበር ካሉ በኋላ አሁንም ቢሆን የጸጥታ ኃይሎች ጉዳዩን በቁጥጥር ስር ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ በመሆናቸው ሕዝቡ ፍርሃት አስወግዶ የሚሰራውን መቀጠል  አለበት ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ በመቀጠልም ሽብሩ ሊካሄድ የሚችለው በአገር በቀል አሸባሪዎች አማካይነት ስለሆነ ሕዝቡ በየቦታው ነቅቶ እንዲከታተልና እንዲጠብቅ አሳስበዋል።

 

 

Ø  አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት አርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በደቡብ ሱዳን ያለፍርድ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች የታሰሩ 35 ሰዎች ባስቸኳይ እንዲፈ ጠይቋል። ከታሰሩት መካከል ጋዜጠኞችና በጁባ ዩኒቨርስቲ ዲን የሆኑት ግለሰብ እንደሚገኙበት ተነግሯል። ድርጅቱ በመግለጫው ላይ ከታሰሩት መካከል ማንኛቸውም ጠበቃ እንዲቆምላቸው ያልተደረገ መሆኑን ዘርዝሮ  አብዛኞቹ በእስር ላይ እንዳሉ መደብደባቸውን ገልጿል። በደቡብ ሱዳን በመንግስት ኃይሎች በጅምላ ከታሰሩት የፖሊቲካ እስረኞች መካከል 35 ቃላይ ከታሰሩት ውስጥ ጥቂቶች መሆናቸውን ቁሞ በመቶ የሚቆጠሩ ዜጎች ሁኔታ ያልታወቀ መሆኑን ገልጿል።

 

Ø  በብዙ የሚቆጠሩ የደቡብ አፍሪካ ዜጎች አርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 .. በጆሃንዝበርግ ከተማ ፕሬዚዳንት ዙማ ከስልጣን እንዲወርዱ በመጠየቅ ትእይንተ ህዝብ ያደረጉ መሆናቸው ተነግሯል። ሰላማዊ ሰልፉና ያዘጋጁት የተቃዋሚ ድርጅቶች ሲሆኑ ሰልፈኞቹ " ሙስና ይቁም" " ለለውጥ ድምጻችንን እንሰጥ የሚሉ መፈክሮችን ይዘው እንደነበር ማወቅ ተችሏል። ከጥቂት ቀናት  በፊት የደቡብ አፍሪካ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቱ ለገጠር ቤታቸው ማስፋፊያ በርካታ የመንግስት ገንዘብ መውሰዳቸው አግባብ አለመሆኑን ገልጾ ገንዘቡን እንዲመልሱ መወሰኑ ይታወሳል። ተቃዋሚ ፓርቲዎች ታዋቂ ግለሰቦችና የሃይማኖት ድርጅቶች መሪዎች ሚስተር ዙማ ከስልጣን እንዲወርዱ ቢጠይቁም ከገዥው ፓርቲ አባላት በኩል ያላቸው ድጋፍ ከፍተኛ በመሆኑ በምክር ቤት ውስጥ እሳቸውን ከስልጣን ለማስወገድ የቀረበው ሕዝበ ውሳኔ ውድቅ መሆኑ ይታወቃል፡፤

በተመሳሳይ ዜናም ሐሙስ ሚያዚያ 6 ቀን 2008 .. ዚምባብዌ ውስጥ በተቃዋሚ ፓርቲ የተደራጀና የተቀነባበረ ከፍተኛ ተቃውሞ ሰልፍ የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ሰልፈኞቹ ፕሬዝዳንቱ ሚስተር ሙጋቢ ስልጣን እንዲለቁ የሚጠይቁ ልዩ ልዩ መፈክሮችን ይዘው የነበረ ሲሆን በርካታ ሴቶችና ወጣቶች እንደነብሩበት ለማወቅ ተችሏል። ስልፉን ቀደም ብሎ የጸጥታ ኃይሎች ከልክለው የነበረ ቢሆንም ረቡዕ ሚያዚያ 5 ቀን 2008 ዓም የዚምባብዌ ፍርድ ቤት የፖሊስ እገዳ እንዲነሳ 'እዛዝ በመስጠቱ ምክንያት ሰልፉ ሊካሄድ ችሏል። ሙጋቤ የሚመሩት የዚምባብዌ ገዥ ፓርቲ ዛሬ አርብ ዕለት በሰጠው መግለጫ ፕሬዚዳንቱ ስልጣን እንዲለቁ ተቃዋሚዎችን የሚጠይቁትን ጥያቄ አውግዞ ፕሬዚዳንቱን ከስልጣን ለማውረድ ትክክለኛው መንገድ ምርጫ ነው ብሏል። ከሶስት አመት በፊት በተካሄደው ምርጫ ሚስተር ሙጋቤ በድጋሚ የተመረጡ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን በወቅቱ በርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የምዕራብ አገሮች ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም በማለት ድምጽ ማሰማታቸው ይታወሳል። 

 

Ø  የምእራብ  ሳህራ ግዛትን አስመልክቶ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተለይም የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በሞሮኮ መንግስት ላይ ተገቢውን ተጽእኖ ማድረግ ካልቻ ሞሮኮ በምእራብ ሳህራ ሕዝብ ላይ የምትፈጸመው አፈናና በደል ሊፋፋም እንደሚችል የፖሊሳሪዮ ግምባር መሪ ሚስተር ሞሃመድ አብዱላዚ አስታወቁ። በሕዝብ ላይ የሚካሄድ አፈናና በደል የሚቀጥል ከሆነ ደግሞ ይህን ለመቋቋም ትጥቅ ትግልን ጀምሮ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንገደዳለን በማለት ጦርነት እንደገና ሊጀመር የሚችልበትን ሁኔታ ጠቁመዋል። ማስጠንቂቂያው የተሰጠው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በምእራብ ሳህራ ስለሚገኘው የተመድ ተል እኮ የወደፊት እጣ እየመከረ ባለበት ወቅት ነው። ባለፈው ወር ሞሮኮ በተመድ ዋና ጸሐፊ መግለጫ በመቆጣት ከአገሩዋ ዲፕሎማቶችን ማስወጣቷ ይታወቃል። የተባበሩት መንግስታት 1983 ዓም የምእራብ ሳህራን ጉዳይ ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም ጥረቱ እስካሁን ጥረቱ ያልተሳካ መሆኑ ይታወቃል። የአገሪቱን የወደፊት እጣ ለመወሰን ውሳኔ ሕዝብ ይደረግ ቢባልም በፖሊሳርዩ ግምባርና በሞሮኮ መካከል በጉዳዩ ላይ ልዩነት በመፈጠሩ እስካሁን ሳይካሄድ ቆይቷል። ግዛቱ የሞሮኮ ነው የሚለውን ሀሳብ ፈረንሳይና ሴኒጋል የሚደግፉት ሲሆን ሌሎች የጸጥታው ምክር ቤት አባላት የሚቃወሙት መሆኑ ይታወቃል። 

 

 

 

 

መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በአየር ንብረት  መዛባትና እንዲሁም በወያኔ አስከፊ አገዛዝ ምክንያት  በኢትዮጵያ የተንሰራፋው ድርቅና ረሃብ እያየለ ሄዶ ከወር ወደ ወር፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተረጅው ቁጥር እየጨመረና የአደጋው አስጊነት ይበልጥ እየሰፋ መምጣቱን የተመድ የሰብዓዊ ዕርዳታ አገልግሎት ቢሮ አስታውቋል። እንደ ተመድ ከሆነ በኢትዮጵያ አሁን የዕርዳታ ፈላጊው ቁጥር ወደ 20 ሚሊዮን መጠጋቱና ይህ አሀዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት አንድ አምስተኛውን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጿል። በረሃብና በድርቅ የተጎዱት አካባቢዎች ከ186 ወደ 219 ክፍ ያሉ ሲሆን ተረጅዎችም በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን በአንዳንድ አካባቢ ስደት መጀመሩና በዚህ ከቀጠለ የረሃብ አደጋ ዕልቂትን ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር በመሆን በድርቅና በረሃብ ለተጎዱ ኢትጵያውያንና በጦርነት ለተጎዱ ሶርያውያን 2.2 ሚሊዮን ዕርዳታ እየተማጸኑ ሲሆን 480 ሚሊዮን ዶላር በድርቁና በረሃንብ ሳቢያ ጤንነታቸው ለተዛባ ኢትዮጵያውያንና በጦርነት ለተጎዳ ሶርያውያን ይውላል ተብሏል። የወያኔ ባለስልጣኖች  በወደብ የተከማቸ የእርዳታ እህል ለማንሳት ከመረባረብ ይልቅ በረሃብተኞች ህይወት ቁማር እየተጫወቱ መሆናቸው እየተጋለጠ ነው ተብሏል ።

 

Ø የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያ ደሣለኝ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሰባት ከመቶ ያድጋል ሲል አማካሪው አርከበ እቁባይ ደግም 11 ከመቶ ያድጋል ብሏል። የወያኔ የጡት አባት የሆነው ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት IMF ደግሞ የወያኔን የኢኮኖሚ እድገት ወደ 4.5 ከመቶ ያወርደዋል። የገንዝብ ድርጅቱ የወያኔ የኢኦኖሚ እድገት ያስቆለቆለው በኢትዮጵያ ባለው ድርቅና ረሃብ በዓለም አቀፉ የገበያ ዋጋ መቀነስ ነው ይበሉ እንጅ የወያኔ ኢኮኖሚ ወትሮም ቢሆን የፕሮፓጋንዳ እድገት እንጅ በተጨባጭ በሕዝብ ጥቅምና ኑሮ ላይ ያመጣው ለውጥ አለመኖሩ የተረጋገጠ ነው። ቀድሞም ቢሆን ደካማ የነበረው ኢኮኖሚ  ዛሬ  በድርቅና ረሃብ፣እንዲሁም በዓለም አቀፉ ገበያ መቀነስ ምክንያት ቀንሷል ተብሏል። ወያኔ በፕሮፓጋንዳ በሚያስፋፋው ዕድገት ስም ከ17 ቢሊዮን ዶላር በላይ በአገሪቱ ስም መበደሩና የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሊሸከምው የማይችል ብድር መውሰዱ የኢኮኖሚው ባዶነት የሚያሳይ መሆኑን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

 

Ø ላለፉት ሶስት ዓመታት በወያኔ ፖሊሶች በግፍ ተይዞ በፈጠራ ወንጀል ተከሶ ወደ ወያኔው ፍርድ ቤት ይመላለስ የነበረው የሙስሊሞች ጉዳይ ጋዜጣ ማኔጅንግ ዲሬክተር ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 5 ቀን 2008 ዓም.ከእስር መፈታቱ ታውቋል። ጋዜጠኛ ስለሞን ከበደ ለጋዜጠኛነት ሙያው ታማኝ በመሆኑና የጋዜጠኛነት ምግባሩን በተግባር በማሳየቱ በወያኔ ካድሬዎች ጥርስ ተነክሶበት ቆይቶ እንደነበርና ከሶስት ዓመት በፊት በፈጠራ ወንጀል ታስሮ ሰቆቃ ሲካሄድበት መቆየቱ ይታወሳል።  ልዮ ልዮ የጋዘጠኛ መብት አስከባሪና ተከራካሪ ድርጅቶች  ጋዜጠኛው በነጻ እንዲፈታ ሲወተውቱና ሲጠይቁ እንደነብረ ይታወቃል። የወያኔው የፖሊቲካ ፍርድ ቤት ጋዘጠኛ ሰለሞን ከበደን ሊያስቀጣውና ሊያሳስረው የሚችል ምንም ጥፋት ባለማግኘቱና ተጽእኖውና ግፊቱ ስለበረታ ከእስር ለመፈታት ተገደዱ እንጅ ዛሬም በወያኔ ወህኒ ቤት ውስጥ የጋዘጠኛነት ሙያቸውን በማክበራቸውና ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብቻ በእስር የሚማቅቁ ጋዜጠኞች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን በግፍ ለታሰሩ ጋዜጠኞችና ዜጎች ሁሉ ድምጽ ማሰማት የማይታለፍ የአገር ወዳድ ዜጋ ግዴታ ነው ነው የሚሉ በርካታ ናቸው።

 

Ø ከሚያዚያ 8 እስከ ሚያዚያ 9 2008 ዓም. ድረስ በባህር ዳር ከተማ የሚካሄደውን አምስተኛ የጣና ፎረም ስብሰባን ምክንያት በማድረገ የባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወታደራዊና የደህንነት ጥበቃ ስር መውደቋ ታውቋል። የወያኔ ደህንነት አባላት በባህር ዳር ከተማ በሚገኙ የእንግዳ መቀበያና የመኝታ አገልግሎት መስጭያ ቤቶች እየዞሩ ማናቸውንም ፀጉረ ልውጥ ሰው አገልግሎት በፈለገ ጊዜ አስፈላጊውን መረጃ መያዝ ግዴታቸው እንደሆነና ለወያኔ ፖሊስም ማሳወቅ እንዳለባቸው ትዕዛዝ መስጠታቸው ታውቋል። በዚህ የጣና ፎረም ጉባዔ ላይ በሥልጣን ላይ ያሉ አምባገነን የአፍሪካ መሪዎችና ከስልጣን የወረዱ ፕሬዚዳንቶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ለባህርዳር ደህንነት ጥበቃ የወያኔ ቡድን መሪዎች ዘርን የተንተራሰ ምርጫ ማካሄዳቸውና ጠቅም ያለ አበል የሚከፈልበት በመሆኑ የትግራይ ተወላጆችን ማሰማራታቸው ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል።

 

 

Ø ዛሬ ሐሙስ ሚያዚያ 5 ቀን 2008 ዓ.ም በጃፓን ኩማሞቶ በሚባለው አካባቢ መጠኑ 6.4 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰ መሆኑን የጃፓን የሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት ገልጿል። የመሬት መንቀጥቀጡ ያደረሰው ጉዳት እስካሁን ባይገልጸም የሱናሚ ስጋት እንደሌለ ተገልጿል። ባለፈው እሁድ በደቡብ እስያ መጠኑ 6.6 የሚደረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ደርሶ በህንድ በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን ህንጻዎችን መጉዳቱና  በተወሰኑ ሰዎች ላይም የአካል ጉዳት ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን እንዲሁም ረቡዕ ሚያዚያ 5 ቀን መጠኑ 6.9 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰሜን ሚያንማር (በርማ) የደረሰ መሆኑ ተዘግቧል።   

 

Ø በሰሜን ናይጄሪያ ቺቦክ ከተባለችው ከተማ 276 የሚሆኑ በትምህርት ቤት ውስጥ የነበሩ ልጃገረዶች ቦኮ ሃራም በተባለው አሸባሪ ቡድን ተጠልፈው ከተወሰዱ ሁለት ዓመት ሆናቸው ተባለ። ባለፈው ታኅሳስ ወር በተደራዳሪዎች አማካይነት ከቦኮ ሃራም ተገኘ ከሚባለውና የሲ ኤን ኤን የቴሌቪዥን ጣቢያ ካሳየው የቪዲዮ ቅጅ በርከት ያሉት ልጃገረዶች በህይወት መኖራቸው ታውቋል። ረቡዕ ሚያዚያ 5 ቀን 2008 ዓም ሲ ኤን ኤን ያሳየው ቪዲዮ ተቀረጸ የተባለው ታኅሳስ 15   ቀን 2008 ዓ.ም. በፈረጆቹ የገና በዓል ዕለት ሲሆን ከተጠለፉት ልጃገረዶች መካከል 15 ቱ በቪዲዮ ላይ ታይተዋል። ቪዲዮን የተመለከቱት አንዳንድ እናቶችና በዚያን ወቅት ያመለጡና ጓደኞቻችው የተመሰቃቀለ ስሜት ያደረባቸው መሆኑንና  በአንድ በኩል ልጆቹ በህይወት መኖራቸው ሲያስደስታቸው በሌላ በኩል ያሉበት ሁኔታ በጣም እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል። ቦኮ ሃራም የተባለው አሸባሪ ድርጅት ለዓመታት ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርስ የቆየ ቢሆንም ልጃገረዶችን በጅምላ ጠልፎ ሲወስድ በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ዘንድ ከፍተኛ ውግዘት የደረሰበት  መሆኑ ይታወሳል፡፤ በወቅቱ የነበረው የናይጄሪው የሚስተር ጉድላክ ጆናታን መንግስት በመጀመሪያ ልጃገረዶቹ መጠለፋቸውን ቢክድም በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ግፊት ለመቀበል ተገዷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ልጆቹን ለማስፈታት  በድርድርም ሆነ በሌላ መልክ ጥረት ቢደረግም እስካሁን የተገኘ መፍትሄ እንደሌለ ታውቋል።  ባለፈው ሳምንት የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቦኮ ሃራም ከሚቆጣጠራቸው ቦታዎች 11698 ሰላማዊ ሰዎችን ነጻ ማውጣቱን ቢገልጽም ነጻ ወጡ የተባሉት ሰዎች ከቺቦክ የተያዙ ልጃገረዶችን አያካትቱም። ላለፉት ሁለት ዓመታት በቺቦክና በአካባቢው ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ምክንያት ከ20 ሺ በላይ ህጻናት የትምህርት ዕድል ተነፍገው ይገኛሉ።

 

Ø በብሩንዲ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘው የሚወሰዱ ሰዎች መዳረሻቸው የሚጠፋ መሆኑ ተነገረ። የመንግስቱ ተጻራሪ ናቸው ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች በጸጥታ ኃይሎች ተወሰደው ከታሰሩ የሚጠብቃቸው በእስር ቤት በምርመራ መሰቃየትና ሞት ብቻ መሆኑን በርካታ ሰዎች እየተናገሩ ይገኛሉ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከቤታቸው፤ከስራ ቦታቸው እና ከሌሎች ቦታዎች በጸጥታ ኃይሎች ታፍነው የሚወሰዱና መዳረሻቸው የሚጠፋ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ ሲሆን ቤተሰቦቻቸውና ወገኖቻቸው ያሉበትን ለማወቅ በርካታ ገንዘብ በጉቦ መልክ እንዲከፍሉ እየተደረገ መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ ወገኖች እየተናገሩ ይገኛሉ። አይ ብሩንዲ የተባለ በህቡዕ የተቋቋመ የኢንተርኔት ቡድን በጸጥታ ኃይሎች ተጠልፈው መዳረሻቸው የጠፉትን ሰዎች ስም እያሰበሰበ ሲሆን እስካሁን በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ታፍነው መወሰዳቸውና የጠፉትን ሰዎች ለማግኘት የሚከፈለው ጉቦ  ከ250 ዶላር እስከ 2500 ዶላር መድረሱን ገልጾ ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ ህብረተሰብ እያጋለጠ እንደሆነ አስታውቋል።  የብሩንዲ መንግስት አፈናውን ይካድ እንጅ ጸጥታውን ለማረጋጋት ማናቸውንም ዓይነት እርምጃ እንዲወስዱ ለጸጥታ ኃይሎች መመሪያ መስጠቱ ይታወቃል። በቅርቡ በዋናው ከተማ በቡጁምቡራ  ሙሳጋና ያካቢጋ በተባሉ ቀበሌዎች መሳሪያ ለማስፈታት የጸጥታ ኃይሎች የሚያካሄዱትን አሰሳ ለማምለጥ የመንደሮቹ ነዋሪዎች አብዛኞቹ ቤት ንብረታቸውን ጥለው በመሰዳዳቸው የተሰደዱትን ዜጎች ቁጥር ከ250 ሺ በላይ ያደረሰው መሆኑ ተገልጿል።

 

 

Ø ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓም. ከፍተኛ የአውሮፓ ህብረት ቡድን ሊቢያ መግባቱና ከሊቢያ አንድነት መንግስት አባሎች ጋር መነጋገሩ ተገልጿል። የፈረንሳይ አምባሰደር እንዲሁም የእንግሊዝ እና የስፔን ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በሊቢያ ወደብ በባህር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ከአንድነቱ መንግስት ባለስልጣኖች ጋር ተገናኝተው የተነጋገሩ ሲሆን የአውሮፓው ህብረት የሊቢያን የአንድነት መንግስት ለመርዳት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 4 ቀን የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተመሳሳይ ጉብኝት አድርገው እርዳታና ትብብር ለማድረግ ቃል መግባታቸውና ባጭር ጊዜ ውስጥ ጣሊያን ኤምባሲዋን በትሪፖሊ ልትከፍት  እንደምትችል መናገራቸው ተገልጿል። ከጥቂት ቀናት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራ የሊቢያ የአንድነት መንግስት አካል ትሪፖሊ ገብቶ በወደቡ አካባቢ ከባህር ኃይል ጦር ሰፈር ውስጥ ስራዎችን እያካሄደ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከአንዳንድ ወገኖች ድጋፍ ቢሰጠውም በትሪፖሊ የሚገኘው ራሱን መንግስት ነኝ የሚለው ክፍልና እንዲሁም በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና የዓለም አቀፍ እውቅናና አግኝቶ የነበረው ምክር ቤት አብዛኞቹ የአንድነት መንግስቱን እየተቃወሙ መሆናቸው   ይታወቃል።

 

 

 

 

 

ሚያዚያ 05 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወያኔ አገዛዝ ለስልጣኑ ተቀናቃኝ ይሆናሉ የሚሰጋባቸውን ጉዳዮች  ሁሉ መቆጣጠርና እና መከታተል ሥራዬ ብሎ ከያዘ ወዲህ ሰሞኑን ደግሞ የኮምፒውተር ወንጀል ቅጣት  በአዋጅ መልክ ህግ ሆኖ እንዲወጣ  ጉዳዩን ለፓርላማ አቅርቧል። የመጣለትን ሁሉ በጭብጨባ ብቻ የሚቀበለው  የወያኔ ፓርላማም ረቂቅ ህጉን ይቀበላዋል ተብሎ ይጠበቃል። የወያኔ መሪዎች የኮምፒወተር ረቂቅ ህግን ለማውጣት የተገደዱበት ምክንያት ተቃውሞና አመጽ ያቀዱ መልእክቶች ያለ ተጠያቂነት በብዛት ሲሰራጩ በመቆየታቸው ነው ተብሏል። በተጨማሪም በኮምፒውተር ደረጃ ወንጀል እየበረከተ መምጣቱም ለረቂቅ አዋጁ መውጣት ሌላው ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል። የወያኔው ረቂቅ አዋጅ የአገዛዙን ተቋማት በተለይም ወታደራዊ መረጃዎችን የሚገኙባችው የኮምፒውተር ፋይሎች እንዳይጠፉና እንዳይሰረቁ ልዩ ትኩረት ያደርጋል የተባለ ሲሆን ወያኔን ከስልጣን ለማባረር ይንቀስቃሳሉ የሚባሉ ቡድኖችና ግለስቦችን ለመቆጣጠርም ታስቦ ነው። በዚህ የኮምፒውተር ወንጀል የተከሰሰ ሰው ከ 15 እስከ 25 ዓመት ጽኑ እስራት እንደሚጠብቀው ረቂቅ ህጉ ይደነግጋል።

Ø በደቡብ ኢትዮጵያ በሻሸመኔ ከተማ ቀድሞ መጸዳጃ ቤት የነበረ ቦታ ላይ የአምልኮት መፈጸሚያ አዳራሽ ተሰርቶ አዳራሹ በመደርመሱ አስር ሰዎች መሞታቸው ታወቀ። ይህ በአሌሉ ክፍለ ከተማ ቀበሌ አስር ውስጥ ያለው መጻዳጃ ቤት መቼ እንደተቆፈረና መቼ እንደተዘጋ ባይታወቅም ህያው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን የሚባል የአምልኮ ማካሄጃ ቤት ከአንድ ዓመት በፊት መገንባቱ ታውቋል፡፤ አዳራሹ በሚደረመስበት ሰዓት አስራ ስምንት ሰዎች አምልኮ ይፈጽሙ የነበሩ ሲሆን በሕዝብና በነዋሪው ትብብር ስምንት ሰዎችን ሰባት ሜትር ጥልቀት ካለው ጉድጓ ሊያወጧቸው ተችሏል። አደጋው ሰኞ ሚያዚያ 3 ቀን 2008 ዓም መድረሱ ሲታወቅ በህይወት የተረፉትን ሰዎች ለማውጣት ለሳብት ሰዓታት ከፍተኛ ጥረት መደረጉ ታውቋል።

Ø አሜሪካና ወያኔ በሱማሊያ ጉዳይ ላይ ያተኮረ አንድ የትብብር ስምምነት መፈራርማቸውን የአሜሪካ መንግስት ባለሥልጣኖች  አስታውቀዋል። ስምምነቱ በጸጥታና በመከላከያ ዙሪያ ሲሆን በአሜሪካ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት በአሜሪካ ጦር ኃይል የአፍሪካ ኮማንድ አዛዥ ጄኔራል ዴቪድ ሮድሪዚግ ሲሆኑ በወያኔ በኩል የወያኔው ኤታ ማጆር ሹም የተባለው የጦር አለቃ ሳሙራ ዩኒስና የወያኔ መከላከያ ሚኒስትር ተብዬ ስራጅ ፈርጌሳ ናቸው። እአአ በ2007 ዓ.ም. በአሜሪካ ቡራኬ ወያኔ  ሱማሊያ ውስጥ ወረራ ማካሄዱ ይታወሳል።  አልሸባብን ለመዋጋት በሚል አሜሪካ ለወያኔ ጋር ከፍተኛ ወታደራዊ ትብብር ስትሰጥ መቆየቷ የሚታወቅ ሲሆን   ድሮን ለተባለው አብራሪ አልባ መንኮራኩሮች ማረፊያና የጦር ስፈር በገሙጎፋ አርባ ምንጭ ከወያኔ ተችራ እንደነበርም ይታወቃል። አሜሪካ የጦር ሠፈሯን ከአርባ ምንጭ ነቅላ ከወጣች ወዲህ ከወያኔ ጋር አዲስ ወታድራዊና የጸጥታ ስምምነት ስትፈርም ይህ የመጀመሪው ነው።

Ø በደቡብ ሱዳን ሁለት የእርዳታ ሰጭ ድርጅት ሠራተኞች በታጣቂ ኃይሎች የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ዳኒሽ ዲማይኒንግ ግሩፕ (Dannish Demining Group) ለሚባለው የቦምብ አምካኝ የሰብአዊ መብት ድርጅት ይሰሩ የነበሩት ሁለቱ ግለሰቦች የደቡብ ሱዳን ዜጎች ሲሆኑ ወደስራ ከሚሄዱበት መኪና በታጣቂዎች እንዲወርዱ ተገድደው በጥይት ተመተው የተገደሉ መሆናቸውን የዓይን እማኞች ገልጸዋል።  እስካሁን ድረስ በደቡብ ሱዳን በታጣቂዎች የተገደሉ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች አባላት 51 የደረሰ ሲሆን ግጭቱ እስከቀጠለ ድረስ ቁጥሩ ሊቀጥል እንደሚችል ተገምቷል፡፡

Ø በተያያዘ ዜና የደቡብ ሱዳን አማጽያን ኃይል ምክትል መሪ ሚስተር አልፍሬድ ላዱ ጎሬ በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ የገቡ መሆናቸው ተነግሯል። በተደረገው ስምምነት መሰረት የጸጥታውን ሁኔታ የሚያስከብር 1300 የሚሆኑ የአማጽያኑ ኃይል ወታደሮችና የጸጥታ ኃይሎች ቀደም ብለው ጁባ መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን ዋና መሪ ሚስተር ሪክ ማቻርም በሚቀጥለው ሰኞ ጁባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። የምክትል መሪው ጁባ መግባት በእርግጥም በአገሪቱ ላይ ሰላም እየሰፈነ ነው የሚለውን ግምት ከፍ አድርጎታል ተብሏል። ሚስተር ጎሬ ጁባ ሲገቡ በተናገሩት ቃል ከእንግዲህ ሰላም አይቀለበስም የሚል መልእክት ያስተላለፉ  ሲሆን 16 የአማጽያኑ ኃይል አባላት በመንግስት ኃይሎች መታሰራቸውንና ተደብድበው መለቀቃቸውን አውግዘዋል።

ከዚህ ሌላ አንድ የአፍሪካ ህብረት የመልክተኛ ቡድን በደቡብ ሱዳን የአንድነቱን የሽግግር መንግስት ለማጠናከር ጁባ የገባ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø በማሊ የታጠቁ ኃይሎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አሁንም ያልተዳከመ መሆኑ ተነግሯል። በቅርቡ በመንገድ ላይ በተቀበረ የፈንጅ አደጋ ሶስት የፈረንሳይ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት የተገደሉ መሆናቸው የፈረንሳይ መንግስት ቃል አቀባይ ገልጿል፡፡ ሶስቱ ወታደሮች የተገደሉት በሰሜን ማሊ ሽብረተኞች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ወታድሮችን የጫኑ 60 ተሽከርካሪ ካሚዮኖች የሚገኙበት ኮንቮይ በሰሜን ማሊ ሲንቀሳቀስ ሟቾቹ የነበሩበት መኪና በፈንጅው በተመታበት  ጊዜ ሲሆን  ሌሎች ወታደሮችም የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተነግሯል። ፈረንሳይ 3500 ወታደሮች በሰላም አስከባሪ ኃይል ስር በአምስት የምዕራብ አፍሪካ አገሮች   ያሰማራች ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማሊ ውስጥ የተገደሉት የፈረንሳይ ወታደሮች ከአሁኑቹ ጋር ወደ ሰባት መድረሱ ተገልጿል።  

 

Ø ሚያዚያ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. በደቡብ ሱማሊያ ኪስማዮ በተባለው የወደብ ከተማ አሜሪካ በሰው አልባ መንኮራኩር አማካይነት ባካሄዳችው የአየር ጥቃት 12 የአልሸባብ አባላት መግደሏን ገልጻለች። የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋም የፔንታጎን ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ የተገደሉት የአልሸባብ አባላት በአሜሪካ እና በሱማሌ መንግስት ወታደሮች ላይ አደጋ ለማድረስ ሲያቅዱ የነበሩ ናቸው ብሏል።  በከተማዋ የሚኖሩ የአይን እማኞች በሰው አልባው መንኮራኩር ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ገልጸው ከተገደሉት መካከል አብዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው ብለዋል።

 

Ø ባለፈው ታህሣስ ወር በሰሜን ናይጀሪያ 347 የሚሆኑ የሺያ ሙስሊም እምነት ተክታዮች በናይጄሪያ ወታደራዊ ኃይል አባላት በግፍ ከተገደሉ በኋላ በጅምላ መቃብር ውስጥ ተቀብረዋል በማለት አንድ የቀድሞ የአካቢው ባለስልጣን ለመርማሪ ቡድን የሰጡትን ቃል ተከትሎ ሰዎቹ ተቀብረውበታል የተባለው ቦታ ታጥሮ በጥበቃ ስር እንዲቆይና ምርመራ እንዲካሄድበት  የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት የሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል በመግለጫው ውስጥ በሰሜን ናይጄሪያ ውስጥ የሚገኘው የካዱኑ ግዛት የመንግስት ኃላፊዎች ሚስጥሩን ማውጣቸውን አድንቆ ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ ለማምጣት እና የሚገባቸውን ቅጣት ለመበየን ገለልተኛ በሆነ ኃይል ጉዳዩ መመርመር አለበት ብሏል። በተያዙበት ጊዜ በደረሰባቸው ድብደባ እና እንግልት አይናችው ጠፍቷል የሚባሉት የእምነቱ ተከታዮች  መሪም ባስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ጠይቋል።

 

 

ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም.

Ø የእድገትና የልማት ከበሮ በሚደበድባት የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ጣራ ደርሷል እየተባለ የሚለፈፍላት ኢትዮጵያ በመረጃ ልማት ሰንጠረዥ የመጨረሻ ሶስተኛ ቦታ ላይ እንደምትገኝ አንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ግልጽ አድርጓል። የኢንፎርሜሽን ዲቨሎፕመንት ኢንዴክክ ባለፈው ዓመት በ1967 የዓለም አገሮች ያደረገውን ጥናት ሰሞኑን ይፋ አድርጓል። ጥናቱ በየአየገሮቹ ያለውን የኢንተርኔት አገልግሎት ስፋትና ጥራት የተንቀሳቃሽ ስልኮች ስርጭትና ኔትወርክ የማግኘት አቅም የኢንተርኔት ተጠቃሚ ብዛትን ለኢንተርኔት የደረሱ ዜጎች ቁጥርን ግምት   ውስጥ ያስገባ እንደነረ ሲታወቅ በውጤቱ በሰንስጠረዥ መጨርሻ 167 ኛ ያወጣቸው ቻድ ስትሆን 166ኛ የሻዕቢያዋ ኤርትራ 165 ኛ ደግሞ ወያኔ በዘረኛንት የሚገዛት ኢትዮጵያ ሆናለች በጥናቱ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጆ ለዜጎቻቸው በአስተማማኝ መንገድ ብቻ ሳይሆን በጥራት በማቅረብ ኮሪያ ቀዳም ስትሆን ዴንማርክና አይስላንድ አንደ ቅደም ተከተላችው ሁለተኛና ሶስተኛ ሆነዋል። በጥፋቱ ሰንጠረዥ ትናንት ነጻነት አገኘሁ ያለችው ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ በልጣና ተሽላ መገኘቷዘረኛዎቹ ወያኔዎች በኢትዮጵያ ላይ የሚሸርቡን ደባ ሸርና በግልጽ አሳይቷል

 

Ø በተያያዘ ዜና የወያኔ ቡድን ባለስልጣኖች በከፊል ኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ በደቡብ አካባቢ  ለሚገኘው ተጠቃሚ የትዊተር የዋትስ አብፕ ና የሌሎች የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ከአንድ ወር በላይ ለሆነ ጊዜ ዘግቶ የነበረ መሆኑ ብሉመርግ የተባለ የዜና ወኪል አጋልጧል። የወያኔ አገልጋይ የሆነው የኢትዮጵያ የቴሌኮሙኒከሽን መስሪያ ቤት የአገሪቷን የኢንተርኔት አገልግሎት በሞኖፖል የያዘ ሲሆን ተቀጣጥሎ ከተያያዘው ሕዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የኢንተርኔት አገግልጎትን በተለይም የሞባይል አገልግሎት ለመግዛት ማቀደቀዱ ቀደም ብሎ የተዘገበ መሆኑ ይታወቃል። የወያኔ ባለስልጣኖች የኢንተርኔት አገልግሎት ደካማ መሆን ነው እንጅ ሆን ተብሎ የተወሰደ የመንግስት እርምጃ አይደለም ብለው በማለት መግለጫ ለመስጠት ቢሞክሩም አፈናው እንቅስቃሴውን ለማዳከም የተጠቀሙበት እርምጃ መሆኑ የተረጋገጠ መሆኑና ብሶት የገፋፋው የሕዝብ አመጽ በማናቸውም ዓይነት አፈና ሊዳከም እንደማይችል ብዙዎች ይናገራሉ፡፡

 

Ø የወያኔ አገዛዝ ትውልድ ገዳይ የሆነ የትምህርት ፖሊስ ቀርጾ አንድ ዘርን ብቻ በዕውቀትና በሞራል ኮትኩቶ በማሳደግ ሌላውን ኢትዮጵያ ከንቱና ገልቱ ትውልድ ብቻ ሳይሆን በልዩ ልዩ ሱስና በጎጂ ባህል የታሰረ በማድረግ ተተኪ ትውልድ ለማሳጣት ጠንከሮ እየሰራ መሆኑ ታውቋል። በትግራይ ውስጥ በትምህርት ቤት አካባቢ መጠጥ መሸጥ ጫት መነገድ በት/ቤት ግቢ ስጋራ ማጤስ የከለከለው የወያኔ የትምህርት ፖሊስ በአዲስ አበባ ከተማ በትምህርት ቤቱ ግቢ አጥር ተጠግቶ ወይም ተሸንቆ በተሰራ የንግድ ቤት አልኮል መጠጥና ሲጋራ እንዲሸጥ ማድረግ ይፈቅዳል። ለትምህርት ቤቱ ልዩ ገቢ ያስገኛል ተብለው የተከፈቱት የንግድ ሱቆች ከልዩ ልዩ ገቢ ጀምሮ የአልኮል መጠጦችን የሚሸጡ ሲሆን ተማሪዎችና መምህራን በእረፍት ጊዜያቸው ወደ ሱቆቹ ጎራ ማለታቸው እየተዘወተረና በትምህርት ሰዓትም መጠጥ የሚጠጡና ሲጋራ የሚያጨሱ መበርከታቸው ታውቋል። በአዲስ አባባ በደጃጅ ገነሜ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይህ ሁኔታ በግልጽ የሚታይ ሲሆን ወላጆችችና ኅብረተሰብ አንድ ካላሉ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ገበታ መሆናቸው ቀርቶ የሱስ መሸመቻ ይሆናል በማለት የሚያስጠነቅቁ ዜጎች ብዙ ናቸው።

 

Ø በወያኔ ጦር ውስጥ በሚካሄዱት ስብሰባና ግምገማ  ላይ ሕዝባዊና  አገራዊ ጥያቄ ያነሱ ወይንም ሃሳባቸውን በነጻነት የገለጹትን ማስርና ደብዛ ማጥፋት የተለመደ ተግባር ሲሆን ሰሙኑንም በምስራቅ ዕዝ ውስጥ የተካሄደውን ስብሰባና ግምገማ ተከትሎ ቁጥራቸው ሃያ ሰባት የሚደርስ የበታች መኮንኖችና ወታደሮች ተይዘው መታስራቸው ታውቋል። ወታደሮቹና የበታች መኮንኖቹ የታሰሩት ጦሩን ልታሳምጹ ነው በማለት ሲሆን በወታደር ፖሊስ ተይዘው ለቀናት በሐረር ጦር አካዳሚ ከታስሩ በኋላ በአሁኑ ሰዓት በድሬደዋ አየር ኃይል ግቢ ውስጥ ታስረው ድብደባና ስቃይ እየተፈጸመባቸው መሆኑ ታውቋል። የወታደሮቹና የበታች መኮንኖች እስር አሁንም ድረስ ለምስራቅ ዕዝ ጦር አባላት ሚስጥር ተደርጎ መቀመጡ ታውቋል። ወታደራዊ ተመልካቾች የወያኔ መሪዎች ለሥልጣን ማራዘሚያና ለህልውናቸው በየጦሩ ውስጥ የራሳቸውን ዘርና ፓርቲ አባላትን  በአዛዥነት በመሾም ጦሩን ለመቆጣጠር መቻላቸውን በመግለጽ የወያኔ መሪዎች ያስሯቸውን የሕዝብና የሀገር ልጆች ለማስፋፋት የወያኔ የጦር አለቆችን ማገትና መያዝ ከአዛዥነት ማባረርና ለፍርድ ማቅረብ ሊታሰብበትና የሚገባ እርምጃ ነው ይላሉ።

 

Ø ቦኮ ሃራም የተባለው አሸባሪ ቡድን  በአጥፍቶ ጠፊነት የሚጠቅማባቸው ህጻናት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ተነገረ። በአሁኑ ወቅት  በአጥፍቶ ጠፊነት ቦምብ ከሚያፈነዱ ሰዎች መካከል ከአምስት አንድ የሚሆኑት አዕምሯቸው በአደንዛዥ ዕጽ የተበከለ ህጻናት መሆናቸው ታውቋል።  የዛሬ ሁለት ዓመት ቦኮ ሃራም በአጥፍቶ ጠፊነት ራሳቸውን እንዲገድሉ ያደረጋቸው ህጻናት 11 ሲሆኑ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ 44 ህጻናትን ቦምብ በማፈንዳት ተጠቅሞባቸዋል። አደንዛዥ ዕጽን በመጠቀም ህጻናትን በዚህ ተግባር ላይ ማሰማራቱ ቡድኑ መዳከሙን ያሳያል የሚሉ ወገኖች ከካሜሩን ከቻድ ካናይጄሪያና ከናይጀር ጠልፎ የወሰዳቸውን ወደ 1.3 ሚሊዮን  የሚደርሱ ሕጻናት በመጠቀም ብዙ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።

 

Ø ሰኞ ሚያዚያ 03 ቀን 2008 ዓም. ሩዪጊ በሚባለው የብሩንዲ ምስራቃዊ ግዛት  ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በገበያ ቦታ ላይ በተኩሱት የእሩምታ ተኩስ ቢያንስ አምስት ሰዎችን የገድሉ መሆናቸውና ሌሎች ሰባት ሰዎች የመቁሰል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል። የእሩምታውን ተኩስ በመተኮስ ጉ በዜጎች ላይ ጉዳት ያደረሱት ታጣቂዎች ቁጥር ሶስት ሲሆን ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ሳያዙ ያመለጡ መሆናቸው የአይን እማኞች ገልጸዋል። በብሩንዲ የፖሊቲካ ውጥረት ከተፈጠረ ጀምሮ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት የጠፋ ሲሆን ከ250 ሺ ሰዎች በላይ መሰደዳቸው ይታወቃል። 

 

Ø የደቡብ ሱዳን አማጽያን ቡድን ቃል አቀባይ ሰኞ ሚያዚያ 3 ቀን በሰጠው መግለጫ የደቡብ ሱዳን መንግስት የጸጥታ ኃይሎች 16 የሚሆኑ የደቡብ ሱዳን አማጽያን አባላትን አስረው ደብድባ ፈጽመውባችዋል ብሎ ከሷል። የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ በሚቀጥለው ሚያዚያ 10 ቀን በዋናዋ ከተማ ጁባ ይገባሉ እየተባለ በሚጠበቅበት  ጊዜና የጸጥታውንም ሁኔታ ለመጠበቅ የተወሰኑ የአማጽያኑ ወታደሮች ጁባ በገቡበት ሁኔታ በሰዎቹ ላይ የተፈጸመው እስርና ድብደባ የሰላሙን ሁኔታ ሊያበላሽ ይችላል የሚል ፍርሃት ፈጥሯል። በተጨማሪም ባህር ዔል ገዛል በተባለው ሰሜናዊ ግዛት የመንግስት ኃይሎች በአማጽያኑ ላይ ያካሄዱትን  አዲስ ወታደራዊ ጥቃት በማውገዘ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሚያዚያ 10 ቀን መግለጫ ሰጥቷል።  መስሪያ ቤቱ የደቡብ ሱዳን ኃይሎች ያከሄዱት ጥቃት የተኩስ አቁሙን ስምምነት የሚጥስ መሆኑን ገልጾ የተጀመረውን የሰላም ሂደት ያደፈርሳል ብሏል።

 

Ø የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፓውሎ ጀንቲሎኒ  ለሊቢያ የአንድነት መንግስት የፖሊቲካና የዲፕሎማሲያዊ እርዳታ ለማድረግ ማክሰኞ ሚያዚያ 4 ቀን 2008 ዓም ትሪፖሊ መግባታቸው ተነገረ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግፊትና አስተባባሪነት የተቋቋመው የአንድነት መንግስት በባህር በኩል ትሪፖሊ ከተማ ከገባ ጀምሮ አንድ የአውሮፓ ባለስልጣን በሊቢያ ጉብኝት ሲያደርግ ጀንቲሎኒ የመጀመሪያ መሆናቸው ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከአንድነት መንግስቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሚስተር ፋየዝ ሴራጅ ጋር ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ በሰጡት መግለጫ የአውሮፓ አገሮች አዲሱን መንግስት ለመርዳት እና ለማጠናከር ሙሉ በሙሉ የቆረጡ መሆናቸውን ገልጸው ከእሳችው በኋላ በርካታ ባለስልጣኖች ወደሊቢያ በመምጣት የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ዋናው ቁልፉ አይሲስ እንዳይጠናከርና እንዲወገድ ማድረግ ነው ካሉ በኋላ በርካታ የአውሮፓ አገሮች ኢምባሲዎቻቸውን በትሪፖሊ ሊከፍቱ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

 

 

 

 

ሚያዚያ 03 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የደቡን ሱዳን አማጽያን መሪ ሪክ ማቻር ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓ.ም ዋናዋ ከተማ ጁባ ይገባሉ ተብሎ ቀደም ብሎ የተነገረ ሲሆን ቀደም ብሎ በተደረገው ስምምነት መሰረት የምክትል ፕሬዚዳንቱና የሌሎች ባለስልጣናትን ደህንነት ለመጠበቅ 1370 የሚሆኑ የደቡብ ሱዳን አማጽያን ወታደሮችና የፖሊስ አባላት ጁባ ከተማ የገቡ መሆናቸው ተዘግቧል። ወታደሮቹ ወደ ከተማ የገቡት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አውሮፕላን ሲሆን የተመደበላቸውን ቦታ ይዘዋል ተብሏል። በአማጽያኑና በደቡብ ሱዳን መንግስት መካከል ባለፈው ዓመት የተደረገው ስምምነት ከሁለቱም ወገኖች የተውጣጣ አነስተኛ የወታደርና የፖሊስ ኃይል ብቻ በከተማዋ እንዲኖር የሚወስን ሲሆን ይህኛው የመጀመሪያው ዙር መሆኑ ታውቋል።  የደቡብ ሱዳን አማጽያን ቡድን ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ የደቡብ ሱዳን መንግስት ጁባ ውስጥ የሚገኙትን ወታደሮችና ፖሊሶች በስምምነት መሰረት ያልቀነሰ መሆኑን ገልጾ እንዲያውም የወታደሩ ቁጥር ከነበረብት ጨምሯ የሚል ክስ አሰምቷል።

 

Ø እሁድ ሚያዚያ 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በቻድ በኮሞሮ ደሴቶችና እና በሱዳን ዳርፉር ግዛት ምርጫዎች ተካሄደዋል። በቻድ በተካሄደው ምርጫ ከሃያ ስድስት ዓመት በፊት በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ የወጡት ኢድሪስ ዴቢ እና ሌሎች 12 ግለሰቦችም ተወዳዳሪ ሆነው ቀርበዋል።   በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የማጭበረበር ተግባሮች በየቦታው ተከስተዋል፤ ወታድሮች መራጩ ሕዝብ ድምጹን ለፕሬዚዳንቱ እንዲሰጥ አስገድደድዋል፣ በአንዳንድ ቦታም ድምጾች በገንዘብ ተገዝተዋል የሚሉ ክሶች መንግስቱን ከሚቃውሙ ተወዳዳሪዎች ቀርበዋል።   የመራጩ ብዛት ከፍተኛ መሆኑ የታየ ሲሆን ታዛቢዎች  ፕሬዚዳንቱ ያሸናፋሉ የሚል  ግምት ሰጥተዋል። ከአስራ ሶስት አመታት በፊት በሀገሪቱ ውስጥ የነዳጅ ምርት ተገኘ ቢባልም  ከአገሪቱ ሕዝብ መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነው ከድህነት እርከን በታች እንደሚኖር ተዘግቧል። ከ10 የቻድ ዜጎች መካከል 7 ቱ መጻፍና ማንበብ የማይችሉ ማሃይማን መሆናቸውም የተመድ ምንጮች ይገልጻሉ። በመንግስት ላይ ያለው ተቃውሞ ከፍተኛ ሲሆን የጽጥታ ኃይሎችም ከፍተኛ አፈና ግድያ በሰፊው እንደሚያካሄዱ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተደጋጋሚ አቅርብዋል።

 

 

በኮሞሮ የአሁኑኑ ፕሬዚዳንት ለመተካት የሁለተኛ ምርጫ ሚያዚያ 2 ቀን ተካሄዷል። ምርጫው የተካሄደው በመጀመሪያ ዙር ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ ባመጡት በሶስት ተወዳዳሪዎች መካከል ሲሆን ውጤቱ ከረቡዕ በፊት አይታወቅም ተብሏል። በጥር ወር በተካሄደው በመጀመሪያ ዙር ምርጫ 19 ተወዳዳሪዎች ምርጫው ማጭበርበርና ማታለል የበዛበት ነው በማለት መክሰሳችው ይታወሳል።

ለረጅም ጊዜ የእርስ በርስ ጦርነት ሲካሄድበት በቆየው በሱዳን የዳርፉር ግዛትም ለሶስት ቀናት የሚቆየው የውሳኔ ሕዝብ ምርጫ እሁድ ሚያዚያ 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ተጀመሯል። የበሽር መንግስት ዳርፉር በአምስት የግዛት አስተዳደሮች ይከፋፈል ወይስ በአንድ አስተዳደር ስር ይቆይ የሚለውን ሀሳብ ሕዝብ እንዲወስነበት ምርጫውን ያዘጋጀ ሲሆን አንድ የአስተዳድር ግዛት ነው የሚያስፈልጋት የሚሉት ተቃዋሚዎች ሀሳቡን ተቃመው መራጩ እንዳይሳተፍ ጥሪ አድርገዋል፡፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሁን ዳርፉር ውስጥ በሚገኘው የጸጥታ ሁኔታ ትክክለኛ ምርጫ ሊካሄድ አይቻልም ብሏል። እስካሁን ድምጹን ለመስጠት የወጣው ዜጋ በጣም አነስተኛ መሆኑ ሲነገር ብዙዎችም ወደ ምርጫ የወጡት  በወታደሮች እየተጃቡ መሆናቸው ተገልጿል።

 

Ø ሰኞ ሚያዚያ 3 ቀን 2008 በስማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሹ በአንድ የምግብ ቤት አቅራቢያ የፈነዳው ቦምብ ቢያንስ አምስት ሰዎች የተገደሉ መሆናችው የዓይን እማኞች ገለጹ። ሬስቶራንቱ የሚገኘው ሀመረወይን በሚባለው አካባቢ ከከተማው አስተዳድር አቅራቢያ በመሆኑ የመንግስት ሰራተኞችን ለመጉዳት ሆን ተብሎ የተወሰደ እርምጃ ነው በማለት ታዛቢዎች ግምታቸውን ይሰጣሉ። ለፍንዳታው እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ግለስብ ወይም ቡድን ባይኖርም አለሸባብ እንደሆነ ይገመታል፡፡ የዛሬው የቦምብ ፍንዳታ የደረሰው ቀደም ብሎ ኬኒያ ውስጥ ተይዞ ወደ ሱማሊያ እንዲመጣ የተደረገና ጋዜጠኞች ገድሏል ተብሎ የተፈረደበት አንድ የበጥይት ተደብድቦ ተገድሏል የሚል ይፋ መግለጫ የሱማሌ መንግስት በሰጠ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ነው።

 

 

 

ሚያዚያ 01 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የወያኔ ዘረኛ ቡድን የድከመውንና የተነቃነቀውን አገዛዙን በኃይልና በሽብር ለመቀጠል ግድያ እስርና ድብደባ የቀጠለ መሆኑ ሲታወቅ ተዳፍኖ የነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ በየቦታው በግልጽ መውጣቱ እንቅልፍ የነሳቸው የወያኔ መሪዎች በቤተ ክህነት ውስጥ ያስቀመጧቸውን ካባ ለባሽ ካድሬዎች ማነቃነቅ መጀመራችው ታውቋል። በዚህ መሠረት የወያኔው ቀንደኛ መሪ አባይ ፀሐዬ በሰጠው መመሪያ መሠረት በአባ ማትያስ አስፈጻሚነት ቤተ ክህነት በአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተሞች የሰላም ጉባዔ በማለት ማደራጀት መጀመራችው ታውቋል። የሰላም ጉባኤው ተደራጅቶ ወደ ምዕመናኑ ሲደርስ የሰላም ጉባዔ ተደረገ ተብሎ መግለጫና ውሳኔ የሚጠበቅ ሲሆን ውሳኔዎቹ የሕዝባዊ ተቃውሞውን ማውገዝ፣ በስደት የሚገኘውን ህጋዊ ሲኖዶስ መርገም፣ ፀረ ወያኔ የሆነውን ትግል ሁሉ በሽብረተኛነት እንዲፈረጁ ማድረግ መሆኑን ከቤተ ክህነት ያፈተለከው መረጃ አመልክቷል። ቤተ ክህነት ሰላምና እርቅን ይቀር ባይነት ማስተማርና ማስፈጸም ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ቢሆንም ካባ ለባሽ ካድሬዎቹ ቤተ ክህነትንና የእግዚአብሔር ቤትን ለሁሉም ምዕመናን ሳይሆን ለአንድ ዘረ የበላይነት አገልጋይና ታዛዥ ማድረጋቸው በምድር ወንጀል በሰማይም ሀጢያት መሆኑን ምእመናን ይገልጻሉ።

Ø የአንድ ዘር የበላይነት ያሰፈነውን ዘረኛ አገዛዝ ዕድሜ ለማስቀጠል የወያኔ ቡድን መሪዎች በየወቅቱና በየጊዜው የወታደርና የፖሊስ ኃይል ምልመላ ሲያካሂዱ አንዳንድ ጊዜም በግዳጁና በማጭበርበር ሲፈጽሙ መቆየታቸው ይታወሳል። ሰሞኑን ደግሞ በማናችውም ዕድሜ ክልል ውስጥ ያለ ሰው ደግሞ በሚሊሺያነት ለመመልመል ጥሪ ማቅረባቸው ከባቲ የመጣው መረጃ አመልክቷል። እንደ መረጃው ከሆነ በባቲ አፋር በአካባቢው ከሚገኙ ነዋሪዎች ታጣቂ ሚሊሺያ ምልምሎ ለማሰልጠን እንቅስቃሴ መጀመሩን የዓይን ምስክሮች ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ የሚኖር ማንኛውም ሰው ለሚልሺያነት መመዝገብ ግዴታ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የሚሊሺያ ምልመላው ለምን እንዳስፈለገ የተገለፀ ነገር የለም። አምባገነን አገዛዞቹ የሥልጣን የመጨረሻ ዘመናቸው ሁሉንም ነገር በጦር ኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ ወታደራዊ ቅጥርና የሚሊሺያ ምልመላ የተለመደ ተግባር ነው የሚሉ ታዛቢዎች አገዛዞች እየሳሱና እየላሉ በሄደ ቁጥር ወታደርና ፖሊስ ማብዛት ሚሊሺያ ማስቀጠር ልማዳቸው ነው ይላሉ።

Ø የወያኔ የኢሕአዴግ ምክር ቤት ያደረገው ስብሰባ ማጠናቀቁ ተገለፀ። የምክር ቤቱ ስብሰባ መጠናቀቁን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ እንደተመለደውና እንደተጠበቀው ባለፈው ስድስት ወራት አመርቂ ውጤቶች ተገኝተዋል ብሏል። ኢኮኖሚው በፈጣን እድገት ላይ ነው፤ ማኑፋክቸሪንግ እየጎለበተ ነው፤ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል፤ ወደ ውጭ የሚላከውን በዓይነት በጥራት አጠናክረን እንቀጥላለን ወዘተ…የሚሉ ምኞትን ብቻ የያዙ ቃላትን ቢደረድሩም ሁኔታው ከሚሉት የተለየ መሆኑ ግልጽ ነው። በተጨባጭ የሚታየው ፖሊቲካው እየከረረ ኢኮኖሚው እየቀጨጨ ሲሆን ወያኔ ይህን ለማስታገስ የጋራ መግባቢያ በሚል የያዘውን አዲስ ፈሊጥ በሚዲያው ለማደንቆር የወሰነ ሲሆን በሀገር ውስጥ ምንም ዓይነት ተቃውሞ ለማድረግ የተሳናቸውን ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በጋራ ምክር ቤት ውስጥ ብቻ ተሳትፏቸው እንዲያጠናክሩ ጠይቋል። የወያኔው ኢሕአዴግ በመግለጫው ላይ ከ15 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ህይወትን እያወከ አለውንንና አደጋው አስጊ ነው በተባለለት ድርቅ ዙሪያ ዕርዳታ እያቀረብኩ ነው ከማለት ሌላ የገለጸው ነገር የለም። ብዙ የፖሊቲካ ታዛቢዎች ግን ወያኔ ዋና የመነጋገርያ አጀንዳ አድርጎት የነበረው በመላ ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞና ቁጣ ለማስቆም ስለሚቻልበት ሁኔታና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ዙሪያ መምከሩን ይናገራሉ።

Ø ህጻናትን አድን (Save the Children) የተባለው መንግስታዊ ያልሆነው ድርጅት አርብ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓ.ም. እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ ውስጥ ስድስት ሚሊዮን ህጻናት አስጊ የሆነ የምግብ እጥረት ውስጥ እንዳሉ ገልጿል። የዘንድሮ ድርቅና ረሃብ በጣም ሰፊና 30 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበትን አካባቢ ያዳረሰ መሆኑን የጠቀሰው የሕጻናቱ አድን ድርጅት  ከዚህ ውስጥ ሢሶው ማለትም አስር ሚሊዮን የሚሆነው የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ፈላጊ መሆኑን ገልጿል። ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 14 ሺህ በከብት እርባታ የሚተዳደሩ አባወራዎች አካባቢያቸውን ለቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን በመጥቀስ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ርብርብ ካላደረገ አስጊ ና አደገኛ ሁኔታ እንደሚፈጠር በማስጠንቀቅ በተለይ ህጽናት በምግብ እጦትና በውሃ ወለድ በሽታ እየተጠቁ መሆናችውን ገልጿል። የተለያዩ ድርጅቶች የቅድመ ማስጠንቀቂያ ቢሰጡም እልቂት ሊያስከትል የሚችል ሁኔታ እንዳለ ቢነገርም የተፈለገውን ያህል ለጋሽና ረጅ እንዳልተገኘ አስታውቋል።

 

Ø በዚህ ዓመት ህዳር ወር ውስጥ በፓሪስ ከተማ በደረሰውና የብዙ ሰው ህይወት ባጠፋው የቦምብ ጥቃት ቀንደኛ ተሳታፊ የነበረውና እስካሁን ሲፈለግ የነበረው ሙሀመድ አብሪኒ አርብ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓ.ም ብራስልስ ውስጥ በቤልጀየም ፖሊሶች የተያዘ መሆኑ ተነገረ። ባለፈው ወር በብራስልስ አውሮፕላን  ማረፊያ በደረሰው  ጥቃት ላይ ተሳትፎ ያመለጠው ሶስተኛው ግለስብ ይኸው ሙሀመድ አብሪኒ መሆኑንና አለመሆኑንም ፖሊሶች ምርመራ እያካሄዱ ነው ተብሏል። የፖሲስ ቃል አቀባይ አብሪኒ ከሌሎች ስማቸው ያልተገለጸ ሁለት ሰዎች ጋር የተያዘ መሆኑን አረጋግጠዋል። የአብሪኒ የጣት አሻራ በብራስልስ ከተማ በሁለት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ እና እንዲሁም የፓሪሱን ሽብር ለማካሄድ  አጥፍቶ ጠፊዎቹ የተጠቀሙበት መኪና ውስት የተገኘ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም በብራስልስ ከተማ በተካሄዱትና ለስላሳ ሶስት ሰዎች  ህይወት መጥፋት ምክንያት በሆኑት  የቦምብ አደጋዎች ላይ ተሳትፈዋል የተባሉት ኦሳማ ክራየም የተባለ የስዊድን ዜግነት ያለው ግለሰብ እና ሌሎች ስማቸው ያልተገለጠ ሶስት ሰዎች መጋቢት 30 ቀን በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆናቸውም ተነግሯል። ኦሳማ ክራየም በብራሰልስ ማየልቤክ አውሮፕላን ጣቢያ ላይ ቦምቡን በማፈንዳት ራሱን የገደለው የካሊድ ባክራዊ ተባባሪ የነበረ እና ቦምቡ የፈነዳበትን የስፖርት ቦርሳ ከገበያ ቦታ ገዝቶ የሰጠ ነው ተብሏል።

 

Ø ትናትንት መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓም በጂቡቲ በተካሄደው ምርጫ እንደተጠበቀው የስድሳ ስምንት ዓመቱ ፕሬዚዲንት ሚስተር ገሌህ የድምጹን 87 ከመቶ በማግኘት አሸንፈዋል ተብሏል። ሚስተር ገሌህ ላለፉት 17 ዓመታት በስልጣን ላይ የነበሩ ሲሆን ለአራተኛ ጊዜ አልወዳደርም በማለት ቀደም ብለው የሰጡትን ቃል አጥፈው ለውድድር መቅረባችው ይታወሳል። ከምርጫው በፊት በጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ አፈና መደረጉ የተነገረ ሲሆን መገናኚያ ብዙሃኖችም በሚያስገርም ሁኔታ ለገሌህ ድጋፍ ይሰጡ እንደነበር ታይቷል ተብሏል፡፤ በዚህ ምክንያትም ሶስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫው ላይ ሳይሳተፉ ቀርተዋል። አሜሪካ ጂቡቲ ውስጥ ቋሚ ወታደራዊ ካምፕ በመመስረቷ እና የአገሪቱ ስትራቴጂያዊ ቦታ ለአውሮፓ አገሮች የኢኮኖሚ እና የጸጥታ ጥቅም ከፍተኛ አስተዋጾ ያለው በመሆኑ  ሚስተር ጉሌህ ሲያካሂዱ የቆዩትን  አፈናና የትናንቱን የይስሙላ ምርጫ በዝምታ እንዳለፉት ተስተውሏል።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት ካይሮ ውስጥ ተገድሎ ሬሳው ተጥሎ የተገኘውን የጣሊያኑን ተወላጅ የጁሊዮ ሬጂኒ  ጉዳይ አስመልክቶ  የግብጽ የጸጥታ ቡድን ወደ ሮም ዘልቆ ከጣሊያን መንግስት ባለስልጣኖች ሲያካሄድ የነበረው ውይይት ውጤት አልባ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ጣሊያን በግብጽ ያለው አምባሳደሯን ለውይይት በሚል ባስቸኳይ የጠራች መሆኑ ተገልጿል። የጁሊዮ ገዳዮች በአሰሳ የተገደሉት የሽብረተኛ ቡድን አባሎች ናቸው  በማለት የግብጽ መንግስት ያቀረበውን ማስረጃ ቡድኑ ጁሊዮን ለመግደሉ የሚያረጋግጥ መረጃ አልተገኘም በሚል  የጣሊያን መንግስት ውድቅ ያደረገው መሆኑ ታውቋል።  የግብጽ የጸጥታ ኃይሎች ጁሊዮን በቁጥትር ስር ካደረጉ በኋላ በምርመራ አካሉን ጎድተው ሬሳውን ጥለውታል የሚለው ጥርጣሬ ከበድ እያለ በመምጣቱ የጣሊያን መንግስት እና የግብጽ መንግስት ግንኙነት እየተበላሸ ይሄዳል የሚል ስጋት አለ።

 

Ø ዛሬ ሚያዚያ 1 ቀን 2008 ዓም በሱማሊያ ዋና ከተማ ሁለት የአልሸባብ አባላት  በተወሰነባቸው ፍርድ በጥይት ተደብደበው ሞተዋል። ሁለቱ የአልሸባብ አባላት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ባለፈው ታኅሳሥ ወር በመኪና ላይ ፈንጅ በማጥመድ ሂንዲዮ ሃጅ መሀመድ የተባለውን የቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ገድለዋል በሚል ነው። ሱማሊያ ለጋዜጠኞች ስራ አደገኛ የሆነች አገር ስትሆን የፕሬስ ነጻነትም ዝቀተኛ ከሆኑባቸው የዓለም አገሮች ውስጥ አንዷ ነች። የድንበር የለሽ ጋዘጠኞች ድርጅት በ2002 ባካሄደው ጥናት  በፕሬስ ነጻነት ሱማሊያ ከ176 አገሮች 172ኛ መሆኗን አመልክቷል።

 

Ø የዳርፉርን ግዛት በአምስት የአስተዳድር ክልሎች ከፋፍሎ ለማስተዳደር ከበሽር መንግስት የቀረበውን ሀሳብ ህዝብ በውሳኔ ሕዝብ እንዲያጸድቀው ከሰኞ ጀምሮ ለሶስት ቀና ዳርፉር ውስጥ ሕዝቡ ድምጽ እንዲሰጥ ይደረጋል ተብሏል። በዳርፉር የሚገኙ አማጽያን ኃይሎች በጦርነት ቀጠና ውስጥ ባለ አካባቢ ነጻና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የድምጽ አሰጣጡ ተግባር ስለማይፈጸም ሕዝቡ በምርጫው እንዳይሳተፍ እየቀሰቀሱ ይገኛሉ። የአስተዳድሩ በአምስት ክልሎች መከፋፈል በተገቢው መንገድ ለማስተዳደርም ሆነ የኢኮኖሚ እድገት ለማግኘት አስፈላጊ መሆኑ የበሽር መንግስት እየገለጸ ሲሆን የአስተዳድር ክልሉን ክሶስት ወደ አምስት ከፍ ያደረገው የበሽብር አገዛዝ ዳርፉር ላይ ያለው ቁጥጥር ከፍ እንዲል ለማድረገ ነው ይላሉ””

Ø በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ የሃይማኖት መሪዎች አርብ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓም በጋራ ባወጡት መግለጫ ፕሬዚዳንት ዙማ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው እንዲለቁ ጠየቁ። የሃይማኖት አባቶቹ በሰጡት መግለጫ የፕሬዚዳንት ዙማ የሙስና ተግባር የሞራል የበላይነትን ያሳጣቸው ስለሆነ አገር ለመምራት ብቃት የላቸውም ብለዋል።  የሃይማኖት መሪዎቹ ቀደም  ከገዥው ፓርቲ አባላት ጋር ውይይት ያደረጉ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን የውይይቱ ውጤት ምን እንደነበር ግን ለማወቅ አልተቻለም። የፕሬዚዳንት ዙማ ልጅ በከፊል ባለቤት በሆነበት ኩባንያ ከኃላፊነት ቦታዎች ራሱን ማግለሉን ያስታወቀ ሲሆን ጉብታ የሚባለው የህንዱ ቤተሰብ አባላትም እንዲሁ ከኩባንያው ኃላፊነት ቦታዎች ራሳቸውን ያነሱ መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል።

 

 

 

 

 

መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም.

Ø ተጨማሪ የቤት እስራዔሎች ቤተሰቦች በዚህ አመት ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ሊመጡ ስለሚችሉበት ሁኔታ የእስራዔል ገዥ ፓርቲ ከአጋሮቹ ጋር ስምምነት የደረሰ መሆኑን ሐሙስ መጋቢት 29 ቀን ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ገልጿል። በዚህ 1300 የሚሆኑት እንዲመጡ የተፈቀደ ሲሆን ወደፊት ቁጥሩ  ከዚህ በላይ ሊጨምር የሚችል መሆኑን ተገልጿል። ባለፈው ወር በእስራዔል አገር የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዘመዶቻቸው ወደ እስራኤል እንዲመጡ በመጠየቅ ከፍተኛ ትዕየንተ ሕዝብ ማካሄዳቸው የሚታወስ ሲሆን የእስራዔል መንግስት ነገሩን ችላ በማለት ኢትዮጵያውያኑን  የፈቃዱን ውሳኔ ሲያስተላልፍ መቆየቱ ይታወሳል። ባለፉት ጥቂት ቀናት አንዳንድ የፓርላማ አባላት ባደረጉ ጥረትና እንዲሁም ተቃውሞውና አድማው የጋራ መንግስቱን ህልውና አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል መሆኑ ስለገባው  ገዥው ፓርቲ ሀሳቡን ቀይሮ ቤተእስራኤሎቹ ወደ እእስራኤል እንዲመጡ ፈቅዷል።

 

Ø በጂቡቲ ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2008 ዓም  ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን የጂቡቲው ፕሬዚዳንት አሸናፊ ሆነው እንድሚቀርቡ አስቀድሞ ታውቋል። ስድስት ተወዳዳሪዎች ለምርጫው ቢቀርቡም ላለፉት 17 ዓመታት በስልጣን ላይ የቆዩት ፕሬዚዳንት አሸናፊ እንደሚሆኑ ጥርጥር የለውም በማለት ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከተቃዋሚዎች ውስጥ የተወሰኑት በምርጫው ላለመሳተፍ የወሰኑ ሲሆን ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት ደግሞ የፖሊሶች አፈና መጠናከሩንና የመገናኚያ ብዙሃን አድላዊነትን በመግለጽ ክስ እያሰሙ ይገኛሉ። ድምጹን የሚሰጠው  የጂቡቲ ሕዝብ ቁጥር አነስተኛ ነው የተባለ ሲሆን ፕሬዚዳንት ጉሌህ ከየመን የመጡ ስደተኞችን አስመዝገበው ድምጽ እንዲሰጡ እያደረጉ ነው ተብሏል። የተቃዋሚዎች መከፋፈል ጉሌህን ሊጠቅም ችሏል የሚሉ አልጠፉም። ከሶስት አመት በፊት የጉሌህ ተቃዋሚ የሆኑ ፓርቲዎች ትብብር ቢፈጥሩም ጉሌህ ተወዳድሮ ሊያሸንፍ የሚችል አንድ የጋራ ተወዳዳሪ ማውጣት ላይ ሊስማሙ አልቻሉም።  የምዕራብ አገሮች ጂቡቲ ውስጥ ባላቸው ጥቅም ምክንያት ስለምርጫው አስተያየት ሲሰጡ አይሰማም።

 

 

Ø በሊቢያ የአይሲስ አባላት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋም አዛዥ ተናገሩ። አዛዡ ላለፉት 12 እስከ 18 ወራት ባሉት ጊዚያት ወደሊቢያ የገቡት የአይሲስ አባላት ቁጥር ከ4 ሺ ወደ 6 ሺ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸው አሸባሪዎቹ በብዛት ሊገቡ የቻሉት በአገሪቷ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ እና የጸጥታ አለመረጋጋት ተጠቅመው ነው ብለዋል። አብዛኞቹ ከውጭ የመጡ በመሆናቸውና አገር በቀል የሆኑ አባሎች አነሰተኛ በመሆናቸው እንደ ኢራክና እንደ ሶሪያ የተወሰነ ክልል ይዘው ለመቆጣጠር አይችሉም የሚል አስተያያት አዛዡ ጨምረው ገልጸዋል። በሊቢያ የሚገኙት ልዩ ልዩ የሚሊሺያ ቡድኖች በየቦታው ከአይሲስ ኃይሎች ጋር እየተጋጩ ስለሆነ በራሳቸው የሚጠናከሩበት ሁኔታ አነስተኛ መሆኑን ይናገራሉ።

 

Ø የሴየራ ሊዮን ፕሬዚዳንት በአገራቸው የኢቦላ በሽታ የታደከመ መሆኑን ገልጸው የአገሪቷ ኢኮኖሚ ከወደቀበት ቦታ እንዲያንሰራራ ለማደረግ የውጭ አገር መዋእለ ንዋይ እንደሚያስፈልግ ተናገሩ። ከምዕራብ አፍሪካ አገሮች 11 ሺ ዜጎችን የገደለው የኢቦላ በሽታ የሲየራ ሊዮንን ኢኮኖሚ በተለይም የእርሻውን መስክ ክፉኛ ያጠቃው በመሆኑ የውጭ አገር ሀብታሞች ገንዘባቸውን በልዩ ልዩ የስራ መስክ ላይ በማዋል ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ እንዲያደርጉ ተማጽነዋል። ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ ቱርክ ውስጥ  በሚደረገው የእስላማውያን አገሮች አመታዊ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ተመሳሳይ ልመና የሚያቀርቡ መሆናችውን ገልጸዋል። 

 

Ø የሞሮኮ መንግስት 8 የውጭ አገር ዜጎችን ከአገሩ ያባረረ መሆኑን ገለጸ። ተባረሩ የተባሉት ግለሰቦች ሁለት የፈረንሳይ አንድ የቤልጂክ እና አምስት የስፔይን ዜጎች ሲሆኑ ለመባረራቸው ምክንያት የሆነው በእስር ላይ ለሚገኙት የምዕራብ ሳህራ ዜጎች እርዳታና ትብብር አድርገዋል የሚል ነው። ከስድስት ዓመት በፊት ግድም ኢዚክ (Gdem Izik) በሚባለው በምዕራብ ሳህራ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ የተቀጣጠለው ዓመጽ  ከሞሮኮ የጸጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት 11 ፖሊሶችና ሁለት ሰላማዊ ሰዎች መገደላችው አይዘነጋም። ፖሊስ  አመጹን ለማስቆም  ካምፑ እንዲፈርስ ያደረገ ሲሆን በርካታ ሰዎችን ወስዶ ማስሩ ይታወቃል። ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት ባለፈው ህዳር ወር ተይዘው የሚገኙት የምዕራብ ሳህራ ዜጎች እንዲፈቱ መጠየቁ ይታወሳል።

 

 

Ø በዳርፉር አካባቢ የሽብር ተግባር ፈጽመዋል በሚል ክስ አንድ የሱዳን ፍርድ ቤት በ22 የደቡብ ሱዳን ዜጎች ላይ የሞት እና የእድሜ ልክ እስራት ቅጣት የበየነ መሆኑ ተገልጿል። ክስ የቀረበባቸው 22 ሰዎች ጀስቲስ ኤንድ ኢኩዋሊቲ ሙቭመንት የሚባለው የዳርፉ አማጽያን ቡድን አባላት ሲሆኑ ድርጅቱ ከሶስት አመት በፊት ከሱዳን መንግስት ጋር የእርቅ ስምምነት ፈርሞ የተቃውሞ እንቅስቃሴውን ማቆሙ ይታወቃል። ባለፈው ጥር ወር 22 የደቡብ ሱዳን ዜጎች የአማጽያኑ ድርጅት አባል ሆነው መንቀሳቀሳቸው በመጋለጡ የውጭ አገር ዜጎች በመሆናችው ብቻ በቁጥጥር ስር ውለው ለፍርድ እንዲቀርቡ ተደርጓል። ባሁኑ ጊዜ በደቡብ ሱዳን እና በሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ዝቅተኛ ሆኖ የሚታይበት ሲሆን በሰዎቹ ላይ የተበየነው የፍርድ ውሳኔ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ይበልጥ ሊያሻክረው እንደሚችል ተገምቷል። የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት በፕሬዚዳንት በሽር ላይ የወንጀለኛነት ክስ ለመመስረት ምክንያት በሆነው በዳርፉር ጦርነት 300 ሺ ሰው ያህል ህይወቱ ሲጠፋ ከ2.5 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከቤት ንብረቱ ተፈናቅሎ ስደተኛ መሆኑ ይታወቃል።

 

 

 

መጋቢት 29 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በሱሉልታ ከተማ በወያኔ ወታደሮችና በከተማዋ ወጣቶች መካከል ፍጥጫና ውጥረት መፈጠሩ ታወቀ። ፍትጫው የተነሳው በሱልልታ ከተማ የሚገኝ አንድ የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር መፈንዳቱን ተከትሎ የወያኔ ፖሊሶችና ጦር የከተማዋን ጥበቃ በማጠናከራቸው ሲሆን ወጣቶቹ ተቃውሞ በማሰማታቸው የወያኔ ፖሊስና ጦር ስትተኩስ ለመበተን የሞከሩ ሲሆን ከፍተኛ የዱላ ድብደባም መፈጸማቸው ታውቋል። የወጣቶቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሚደግበት ወቅት የወያኔ የንግድ ሸሪክ የሆነው የመሀመድ አላሙዲን ንብረት የሆኑ 3 መኪኖች ሲያልፉ በድንጋይ ተደብድበዋል።

 

Ø በሐረር ዓለማያ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች መኝታ ቤት ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ስለደረሰበት ተማሪዎች ትምሀርት አቋርጠው ወደ ቤተ ሰቦቻቸው ለመሄድ የተገደዱ መሆናቸው ከዓለማያ የመጣው መረጃ ያመለክታል። የእሳቱ አደጋ እንዴት እንደተቀሰቀሰና ለምን ሳይጠፋ ረጅም ሰዓት እንደቆየ የታወቀ ነገር ባይኖርም የዓለማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ነዋሪዎች ግን የወያኔ ደህንነት ኃይሎች የተማሪዎቹን መኝታ ክፍሎች ሆን ብለው በማቃጠል ያነጣጠሩባቸው ተማሪዎችንን መምህራንን በሽብረተኛነት ለመክሰስ በማሰብ ነው በማለት ይናገራሉ።

 

 

Ø 10 አመት በፊት በጋምቤላ ከ400 በላይ አኙዋኮች ግድያን ተከትሎ ከወያኔ ጋር ሆድና ጀርባ በመሆን ከሀገር ወጥቶ በኖርዌይ በጥገኝነት ይኖር የነበረው ኦኬሎ አኳይ በወያኔው ፖለቲካ ፍርድ ቤት በሽብረተኛነት ጥፋተኛ ተብሎ የተፈረደበት ሲሆን ከሶስት ሳምንት በኋላ የቅጣቱ ብይን እንደሚሰጠው ተገልጿል። ኦኬሎ አኳይ በአኝዋኮች ፍጅት ወቅት የጋምቤላ ፕሬዚዳንት የነበረ ሲሆን በጋምቤላ የአኙዋኮችንና የኑዌር ግጭትን ወያኔዎች እንደቀሰቀሱት እና የአኙዋኮቹ ፍጅት በወቅቱ የወያኔ መሪ በነበረው በመለሰ ዜናዊ ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ቀደም ሲል አስታውቆ የነበረ ሲሆን አሁንም በወያኔው የፖሊቲካ ፍርድ ቤት ደግሞታል። የወያኔ ወታደሮች 400 አኙዋኮችን ገድለው 60 ብቻ ነው የሞቱት የሚል ማስተባበያ ኦኬሎ እንዲሰጥ አስገድደውት እንደነበርና አዲሱ ለገሰ በረከት ስምኦንና ገብረአብ ባርናባስ የወያኔው ትዕዛዝ በማስፈጸም እጃቸው እንዳለበት ገልጿል። አኮሌ አኳይ ከዓመታት በፊት ወደ ደቡብ ሱዳን በሄደበት ወቅት የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣኖች ከወያኔ ደህንነት ጋር በመሳጠር ከጁባ ጠልፈውት ወደ አዲስ አበባ እንደመለሱትና በሽብረተኛነት ክስ እንደመሰረቱበት ይታወሳል።

 

Ø በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ውስጥ በከፍተኛ ኃላፊነትና ስልጣን ተቀምጠው እጅግ አስነዋሪ ተግባር ሲፈጽሙ የተገኙ የወያኔ ካባ ለባሽ ካድሬዎች ከስልጣናቸው መባረር መጀመራቸውና ዋና ጠባቂው አቡነ ማትያስም ምንም ማድረግ ባለመቻላቸው ለማባረር መገደዳቸው ታውቋል። የአቡነ ማትያስ ቀኝ እጅ የነበረውና የአዲስ አበባ ሀገር ስብከት ስራ አሲያጅ የነበረው የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ከየቤተክርስቲያኑና ገዳማቱ ያለውን ንብረት መዝረፉ ብቻ ሳይሆን ለልጁ መታከሚያ በሚል ሰበብ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ከቤተ ክርስቲያኗ ካዝና በመሰብሰቡ ከስልጣኑ የተባረረ ሲሆን በእርሱ ምትክ ሌላው ካባ ለባሽ ካድሬ ጎይቶም ያይኔ ተተክቷል። ከየማነ በተጨማሪ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ኃላፊዎችም ተባረዋል። የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ያሉ ማንኛውም ከፍተኛ ኃላፊነትና ስልጣን በትግራይ ተወላጆች ብቻ እንዲያዝ ባወጣው መመሪያ መሠርት በመንፈሳዊና ሐዋርያዊ ስራ በምትሰራው ቤት ክርስቲያን ውስጥ የዘር መድልዎን በማምጣት ቤተ ክርስትያኗን እያመሳት መሆኑ ምዕመናኑን ካህናቱ በጀመሩት ግፊት ካባ ለባሽ ካድሬዎች ቢነሱም ሌላ ዘረኛ ካባ ለባሽ መተካት ውጤት ስለሌለው ቤተ ክርስቲያኗን ከዘረኛ ካድሬ ቄስና መነኩሴ ማጽዳት የዛሬ ሰራ ነው የሚሉ ምዕመናን ብዙ ናቸው።  

 

 

Ø በአስመራ ከተማ በግድ ታፍሰው በካሚዮን ተጭነው ወደ ጦር ማሰልጠኛ ሲወሰዱ የነበሩ ወጣቶች ከተሳፈሩባቸው መኪናዎች ዘለው ለማምለጥ ሲሞክሩ በሻዕቢያ ወታደሮች በጥይት የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። የተገደሉትና እና ምን ያህል እንደሆኑ ለጊዜው ባይታወቅም ቁጥራቸው ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል። በተጨማሪም  ካሚዮኖቹ የሚሄዱበትን መንገዶ በአውቶቡስ አማካይነት  ለመዝጋት ሙከራ ያደረጉ የወጣቶቹ ዘመዶችና ጓደኞች በሙሉ በጥይት የተገደሉ መሆናቸው ተነግሯል። የሻዕቢያ መንግስት እስካሁን በጉዳዩ የሰጠው መግለጫ የለም። በሻዕቢያ ውስጥ የወታደራዊ አገልግሎት የጊዜ ወሰን የሌለው መሆኑ ሲታወቅ አብዛኛዎቹ እድሜ ልካቸውን ሲያገለግሉ የሚቆዩ መሆናቸውና  የኑሮው ሁኔታቸውም በጣም አሰቃቂ እንደሆነ ይነገራል። ይህ አሰቃቂ የኑሮ ሁኔታና የሻዕቢያን አፈና ለማምለጥ በርካታ ወጣቶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገሮች እና ወደ አውሮፓ መሰደዳቸው በየጊዜው የተገለጸ መሆኑ ሲታወቅ የሻዕቢያ አገዛዝ ከፍተኛ አፈናና ጭፍጨፋ ከሚያካሄዱ የአለም አገሮች ውስጥ ዋነኛው ነው በማለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ድምጻቸው በተደጋጋሚ ሲያሰሙ ቆይተዋል።

 

Ø በሊቢያ በፌስ ቡክ እና በሌሎች የማህበረሰባዊ መገናናዎች አማካይነት በድብቅ የሚካሄድ የመሳሪያ ገበያ በከፍተኛ ደረጃ እየደራ መምጣቱን ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 29 ቀን ይሰራጫል የተባለ አንድ ጥናታዊ ዘገባ አመለከተ። ለአርባ ዓመት ሊቢያን ሲገዛ የቆየው የኮሎኔል ጋዳፊ አገዛዝ በየጊዜው ያከማቸው መሳሪያ አገዛዙ ሲወድቅ በተለያዩ አማጽያን እጅ የገባው መሳሪያ ዛሬ በጥቁር ገበያ በሰፊው እየተሸጠ መሆኑን ጥናቱ ይዘረዝራል። በፌስ ቡክ፣ በኢንስታግራም፣ በዋትስ አፕ፣ እና በቴሌግራም አማካይነት በብዛት እየተሸጡ ያሉት መሳሪያዎች እንደሽጉጥና ካላሽንኮቭ የመሳሰሉት የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ሲሆኑ ለሽብርተኞች መገልገያ የሆኑ በትከሻ ላይ ሆነው የሚተኩሱ ጸረ አውሮፕላንና ሌሎች ከባድ መሳሪያዎችም የሚሸጡ መሆናቸውም ተጠቁሟል። አንድ ካላሽንኮፍ መሳሪያ እስከ 1800 ዶላር ሲያወጣ በተለይ የመጓጓዣ አውሮፕላንን ሊመታ የሚችል ጸረ አውሮፕላን መሳሪያ ደግሞ እስከ 62 ሺ የአሜሪካን ዶላር እንደሚሸጥ ዘገባው ይገልጻል። የመሳሪያ ሽያጮቹ የሚከናውኑት በአብዛኛው እንደ ትሪፖሊ፣ ቤንጋዚ እና ሳብራታ በመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች ሲሆን ንግዱ የሚካሄደው ወጣቶች በሆኑ የተለያዩ የሚሊሺያ አባላት መካከል መሆኑም ተድርሶበታል።  የፌስ ቡክ ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ ይህን የመሰለ ንግድ በፌስ ቡክ አማካይነት መካሄዱ ወንጀል ገልጾ መረጃውን እየፌስ ቡክ አገግሎቱን እንዘጋዋለን ብሏል። የአውሮፓ ባለስልጣናትም ጉዳዩ ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፤

    በተያያዘ ዜና ትሪፖሊን መሰረት አድርጎ ሲንቀሳቀስ  የነበረው የመንግስት አካል በትናንተናው ዕለት ደም መፋሰስን ለማስወገድ ከስልጣን ወርጃለሁ የሚል መግለጫ በፍርድ ሚኒስቴሩ አማካይነት መስጠቱ የሚታወስ ሲሆን የዚሁ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት ሚስተር ካሊፋ ገውሊ  ደግሞ በድረ ገጻቸው ላይ ባወጡት መግለጫ ቀደም ብሎ የወጣውን መግለጫ መቃወማችውን ገልጸዋል። መግለጫ  ማንም ሚኒስቴር ሆነ ሌላ ኃላፊነት የተሰጠው ግለስብ በተመድ ከተሰየመው የአንድነት መንግስት ጋር እንዳይተባበር የሚያሳስብ ሲሆን ተባባሪ ሆኖ ከተገኘ ከፍተኛ እርምጃ እንደሚወሰድበት ይገልጻል። ሚስተር ካሊፋ ገውሊ በተመድ የተቋቋመውን የአንድነት መንግስት በጽኑ ከሚቃወሙ ግለሰቦች መካከል አንዱ መሆናችው የሚታወቅ ሲሆን መግለጫቸው በሌሎች ዘንድ ምን ያህል ተቀባይነት እንዳለው ለጊዜው ለማወቅ አልተቻለም። በአሁኑ ወቅት ሚስተር ካሊፋ ይህንን እርምጃ እንዲወስዱ የገፋፋቸው ምክንያቶች ለጊዜው ግልጽ ባይሆኑም በቡድኑ ውስጥ ከፍተኛ ክፍፍል መኖሩን ያሳያል በማለት ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ።

Ø የሱዳኑ ፕሬዚዳንት አልበሽር ለቢቢሲ ጋዘጠኛ በሰጡት ቃለ ምልልስ የአሁኑ የስልጣን ዘመናቸው በ2013 ዓም ሲያልቅ ስልጣናቸውን የሚያስረክቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ግለሰቡ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ስልጣን የሚለቁ መሆናቸውን በመግለጽ የገቡትን ቃል በተደጋጋሚ ሲያጥፉ የነበሩ በመሆናቸው እለቃለሁ ብለው መናገራቸው የተለመደው ማጭበርበር ነው  የሚሉ በርካታ ናቸው። ፕሬዚዳንቱ በቃለ ምልልስ ወቅት በዳርፉር ከ10 ሺ በላይ ዜጎች ቤታቸው ጥለው ተሰደዋል፤ 2.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ በካምፕ ውስጥ ይኖራሉ  በሚል ተመድ ያሰራጨው መረጃ የተጋነነ ነው ከማለታቸውም በላይ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች በዳርፉር የሚቆዩበት ምንም ምክንያት ስለሌለ ባስቸኳይ መውጣት አለባቸው ብለዋል። የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለፖሊቲካ ማራመጃ ተብሎ የተቋቋመ መሆኑን በመግለጽ በአገራቸው ሕዝብ ተወዳጅነት ስላላቸው የተመሰረተባችውን ክስ እንደማይቀበሉት በቃለ ምልልሱ ገልጸዋል።

 

·        በተያያዘ ዜና ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ከሳልቫ ኪር ጋር ከጥቂት ወራት በፊት እርቅ የተፈራረሙት  ሪክ ማቻር በሚያዚያ 10 ቀን 2008 ዓም ጁባ የሚገቡ መሆናቸውንና በዚያም ከሳልቫ ኬር ጋር በመሆን የአንድነነቱን የሽግግር መንግስት እንደሚያቋቁሙ ገልጸዋል። ባሁኑ ጊዜ በአንዳንድ ቦታዎች የሚደረጉት ጦርነቶች ሙሉ በሙሉ ያልቆሙ በመሆናቸው ስምምነት የተደረገበት የአንድነት መንግስት ስራ አለመጀመሩ ብዙዎችን ሲያሳስብ ቆይቷል። በሌላ በኩል በደቡብ ሱዳን  መድኃኒት እና ሌሎች የህክምና አገልግሎት መሳሪያዎች ከፍተኛ እጥረት በመፈጠሩ ርዳታ ፈላጊዎችን ለመርዳት አዳጋች እየሆነ መምጣቱን ድንበር የለሽ ሃኪሞች የተባለው ድርጅት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 29 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ገልጿል። መግለጫው የእርዳታ ድርጅቶችና ሌሎች የአለም አቀፍ ተቋሞች ይህን ከፍተኛ የሆነ እጥረት ለማሟላት ባለመቻላቸው የብዙ ሰዎች ህይወት አደገኛ ሁኔታ ላይ ሊወድቅ ችሏል ብሏል።  የአለም የምግብ ፕሮግራም እና የዓለም አቀፉ የእርሻ እና የምግብ ድርጅት ማክሰኞ መጋቢት 27 በሰጡት መግለጫ በደቡብ ሱዳን የእርዳታ እህል እጥረት በመኖሩ ከፍተኛ ረሃብ እየተከሰተ መሆኑን የገለጹ መሆናቸው ይታወሳል።

 

 

 

መጋቢት 28 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በሊቢያ የትሪፖሊ ከተማን ማዕከል አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ራሱን መንግስት ነኝ ብሎ ሲጠራ የቆየው አካል ስልጣን የለቀቀ መሆኑን የፍርድ ሚኒስትሩ ባሰራጨው መግለጫ አሳታውቋል። መንግስቱ በመግለጫው ላይ ይህንን እርምጃ የወሰደው በአገሪቱ ውስጥ ተጨማሪ ደም መፋሰስን ለማስቀረት ነው ብሏል። የመንግስት ማህተም ያለበትና በማን እንደተፈረመ የስም ዝርዝር የማያሳየው በይፋ የተሰራጨው መግለጫ ከዛሬ ጀምሮ ፕሬዚዳንቱም ሆኑ ሚኒስትሮቹ ስራ መስራት ያቆሙ መሆናቸውን ገልጿል። ባለፈው ረቡዕ ትሪፖሊ ወደብ የገባው በተመድ አስተባባሪነት የተቋቋመው የሊቢያ የአንድነት መንግስት ተወካዮች ቡድን ከባህር ኃይል ቅጥር ግቢ ውስጥ ስራውን እያካሄደ መሆኑና ከአንዳንድ ክፍሎች ድጋፍ እያገኘ መምጣቱ የተነገረ ቢሆንም  በርከት ያሉ የመንግስት መዋቅር አባላትና የሚሊሺያ መሪዎች አሁን ድረስ ተቃውሞ እያሰሙ በመሆናቸው በምን ያህል ጊዜና በምን ዓይነት ሁኔታ ተቀባይነት አግኝቶ አገሪቱ ሊያረጋጋ እንደሚችል እስካሁን ግልጽ አይደለም።

 

Ø የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ በወንጀል ተከሰው ከስልጣን እንዲወገዱ የደቡብ አፍሪካ ምክር ቤት ተወያቶ እንዲወስንበት በተቃዋሚ ክፍሎች የቀረበው ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ እንደተጠበቀው ውድቅ መደረጉ ታውቋል። የፕሬዚዳንቱ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ አብላጫውን መቀመጫ የያዘበት የደቡብ አፍሪካ ምክር ቤት ትናንት ባካሄደው ስብሰባ 233 የምክር ቤት አባላት ድምጽ በመስጠት የውሳኔ ሀሳቡን ውድቅ አድርገውታል። የውሳኔ ሀሳቡን የደገፉት የተቀዋሚ ድርጅቶች አባላት ቁጥር 143 ብቻ ነበር። የውሳኔ ሀሳቡ ሊያልፍ የሚችለው ከምክር ቤቱ መቀመጫዎች ሁለት ሶስተኛው ከደገፈው ብቻ ነው የሚል ሕግ በመኖሩ የውሳኔ ሃሳቡ ውድቅ ሆኗል። ፕሬዚዳንቱ በሙሥና በመዘፈቃቸውና የዝምድና ስራ በማስፋፋታቸው ምክንያት የደቡብ አፍሪካ ሕዝብ ከፍተኛ ጥላቻና ጥርጣሬ እያሳየ ባለበት ሁኔታ የአፍሪካ ብሔራዊ  ኮንግሬስ እሳቸውን ለመደገፍ ሙሉ ድምጽ መስጠቱ ፓርቲው በሚቀጥለው ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ እንዳይሆን ሊያግደው ይችላል የሚሉ ታዛቢዎች አልጠፉም። ፕሬዚዳንቱን የሚቃወሙ ድምጾችም እየበረከቱ መጥተዋል። ትሬቨር ማኑዔል የተባሉት የቀድሞ የፋይናንስ ሚኒስትር እና አህመድ ካትራዳ የተባሉት የኔልሰን ማንዴላ የእስር ጓደኛ ፕሬዚዳንቱ በግላቸው ስልጣናቸውን እንዲለቁ ጠይቀዋል። የሃይማኖት፤ የምሁራንና የሌሎች የብዙኅን ማህበራት ድርጅቶች አባላት ፕሬዚዳንቱ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ለመግፋት ተከታታይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለማድርግ ዝግጅት እያደረጉ ነው።

Ø የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ባካሄደው ተከታታይ ወታደራዊ እርምጃ 11 ሺ 595 ሰዎችን ከቡድኑ ጥቃትና ቁጥጥር ነጻ ያወጣ መሆኑን ገልጾ የተያዙትንም ሆነ በነጻ እጃቸውን የሚሰጡትን የቦኮሃራም ታጣቂዎች ወደሰላማዊ ኑሮ እንዲመለሱ የማስተማሪያና የማሰልጠኛ ካምፖች ያቋቋመ መሆኑን ገልጿል። ግለሰቦች ራሳቸውን ችለው በህብረተስብ ውስጥ ድርሻቸውን እንዲወጡ በካምፑ ውስጥ ልዩ ልዩ የሞያ ትምህርቶች የሚሰጡ መሆናቸውም ተገልጿል። እስካሁን ድረስ እጃውን ሰጥተው ወደ ካምፑ የገቡ የቦኮሃራም ታጣቂዎች ምን ያህል እንደሆኑ ባይታወቅም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቡድኑ ወደተሸሸገባቸው ቦታዎች ምግብና ሌሎች ቁሳቁሶች እንዳይደርሱ መንግዶች በመዘጋታቸው በረሃብ የተጠቁ በርካታ የቦኮሃራም አባላት እጃቸውን የሰጡ መሆናችው ተዘግቧል። የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቦኮ ሃራምን ለመደምሰስ ጫካውን ሁሉ ለማጠርና ለመቆጣጠር አቅም ባይኖረውም የምግብና መሰል ቁሳቁሶች የሚጓጓዙበትን መስመር መዝጋቱ ከፍተኛ ውጤት አስገኝቷል ተብሏል።

 

Ø የፓናማ ሰነድ የሚል መጠሪያ ያገኘው በድብቅ የተለቀቀው መረጃ ከሚያጋልጣቸው ከፍተኛ ባለስልጣኖችና ታቃቂ ግለሰቦች መካከል የአፍሪካ ባለስልጣናት እንደሚገኙበት ታወቀ። ሞሳክ ፎንሴካ የተባለው የፓናማ የሕግ ኩባንያ የንግድ ግንኙነት ከመሰረታቸው ታዋቂ የአፍሪካ ግለሰቦች መካከል ክላይቭ ኩሉቡሴ ዙማ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት  የወንድም ልጅ፤ ካልፓና ራዋል የኬኒያ ምክትል የፍርድ ሚኒስትር፤ ጆን አድዶ ኩፎር የቀድም የጋና ፕሬዚዳንት ልጅ፤ ማማዲ ቱሬ የቀድሞ የጊኒ ፕሬዚዳንት ባለቤት፣ ሙኒር ማጃዲ የሞሮኮ ንጉስ የግል ጸሐፊ፣ ጆዜ ቫስኮንሴሎስ የአንጎላ የነዳጅ ሚኒስትር፤ ኢያን ከርቡ የቦትስዋና የይግባኝ ፍርድ ቤት ኃላፊ፤ ጃኔት ካቢላ የኮንጎው ፕሬዚዳንት ካቢላ እህት፤  ኮጆ አናን የቀደሞ የተመድ ዋና ጸሐፊ የኮፊ አናን ልጅ ይገኙባቸዋል። እስካሁን የተጋለጡት እነዚህ ሲሆኑ ስም አይዘርዘር እንጅ ከኢትዮጵያውም ሰዎች እንዳሉበት ተጠቁሟል። ብዛታቸው 1.5 ሚሊዮን የሆነው እነዚህ ልዩ ልዩ ሰነዶች ምርመራቸው ሲያበቃ በርካታ ሰዎች ይጋለጣሉ የሚል ግምት ተወስዷል።

 

 

 

 

 

መጋቢት 27 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø የወያኔ ቀኝ እጅ እና ጉዳይ ፈጻሚ የሆነው ኢሕአዴግ መደበኛ የምክር ቤት ጉባዔ የተባለለትን ስብስባ ዛሬ መጋቢት 27 ቀን 2008 ዓም ጀምሯል። ስብሰባው ነገ መጋቢት 28 ቀን 2008 ዓም ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ጉባኤው በይፋ ያለፉትን ስድስት ወሮች የስራ ሂደት ይገመግማል ተብሎ ቢነገርም በዋናነት ግን በመላ ኢትዮጵያ ስለተቀጣጠለው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ የድህረ ገጾች ግንኙነት መደናቀፍና የቴሌኮም መረጃ መለዋወጥ ላይ የተፈጠረውን ችግር ይመክርበታል ተብሏል። ለወያኔ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ኢሕአዴግ ምክር ቤት ወያኔ በኦህዴድ ላይ ስለሾማቸው ሰዎችና ታፍነው ስለተወሰዱ ሰዎች ውሳኔ የሚሰጡ ሲሆን ፍትህ ሚኒስትርን አፈርሰው ጠቃላይ አቃቤ ህግ ስለሚለው ህግና ማሪሚያ ቤት ለዓቃቤ ህግ ተጠሪ ስለሚሆንንበት ጉዳይ እንዲሁም የፌዴራል ፖሊስ የተባለው ተቋም  ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሆን ስለሚያዘው ህግና የወያኔ ድርጅት ሰዎች የድህንነት ከለላና በተመለከተ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል።

 

Ø ስግብግብነት፣ አልጠግብ ባይነትና  ነጥቆ መውሰድ መለያቸው የሆነው የወያኔ ባለስልጣናት ጥቅም የሚገኝበትንና ገንዘብ አትራፊ የሆነውን ሁሉ መጠቀሚያ ማድረግ ባህሪያቸው ሲሆን ሰሞኑን ደግሞ ኢንተርኔትን በመጠቅም ከማንኛውም የዓለም ክፍል ጋር በነጻ ስልክ መገናኛ የነበሩትን ቫይበርና ዋትስ አፕን በክፍያ እንዲሰሩ ለማድረግ ያቀደ  ከውጭ አገር የሚገቡ  ስልኮችም ለክፍያ እንዲያመቹ ልዩ ቁጥጥር ተደርጎባቸው ከውጭ የሚገቡ የግለሰስብ ስልክ ቁጥሮች ላይ ቀረጥ ይጣላል ተብሏል።፡ወያኔ ተጨማሪ ክፍያ መጠየቁ ብቻ ሳይሆን ተጨማሪ የቀረጥ ገቢም ለማግኘት ጭምር አዲሱን መመሪያ ማውጣቱ ተገልጿል። በዘመናዊ የዲጂታል ዘመን ዜጎች የቴክኖሎጂው ውጤትን ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የገንዘብ ክፍያ መጠየቁም ሆነ ዘመናዊ የስልክ ቀፎዎች ላይ ቀረጥ ለመጣል ማቀዱ የወያኔ አገዛዝ ቴክኖሎጂውን ሰው እንዳይጠቀምበት እያደረገ ያለ ሲሆን ከተጠቀመም ውድ ዋጋ በማስከፈል ሕዝብን ከማኅበራዊ ጎዳናና ከሶሻል ሚዲያ በማራቅ ደህንነቱን ለመጠበቅ ሆን ብሎ የተጠቀመበት ዘዴም መሆኑን ብዙ ዜጎች ይናገራሉ።

 

Ø የወያኔ ዘረኛና አምባገነን አገዛ በሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ የተነሳ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሰራቸው ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱና ቁጥራቸውን አለመግለጹ ይታወቃል። ጉዳዩን በደንብ የተከታተሉና መረጃ ያሰባሰቡ ወገኖች እንደገለጹት ከሆነ ደብዛቸው የጠፋ እስረኞችን ወደ ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እንደተወስዱና በጦር ካምፕ ውስጥ ከፍተኛ እንግልት እየተፈጸመባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ጉዳዩን የተከታተሉ ወገኖች በአሁኑ ጊዜ ከ2800 በላይ ሰዎች በጦላይ እንደሚገኙና ከሀረር የመጡ የሰባት ልጆች እናትም እንደሚገኙበት አስታወቀዋል። ለወያኔ ታማኝ በመሆን የጦር ካምፑን የሚመሩና የእስረኞቹን ሁኔታ የሚከታተሉ በዙ ዋቅቤላ፤ ቀንአ ያደታ፣ ተሾመ ዱጋሳ ፤ ጸሐይ ነጋሽና የወያኔው ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን መሆናቸው ሲታወቅ የወያኔ መሪዎችንና ኃላፊዎች ከእነዚህ ተላላኪ ግለሰቦች ጀርባ ሁኔታዎችን የሚዘወሩ መሆናቸው ተገልጿል። በጦር ካምፑ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ወጣቶች በብዛት ይኑሩ እንጅ ከመላ ኢትዮጵያ የተሰበስውና በወያኔ ላይ ተቃውሞና ቁጣ ያሰሙ የሕዝብ ልጆች የታጎሩበት የጦር ማሰልጠኛ መሆኑ ተብራርቷል።

 

 

Ø አንጋፋው የዘመናዊ ሙዚቃ የሳክሲፎን ተጫዋን ጌታቸው መኩሪያ ባደረበት ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ከቆየ በኋላ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ሙዚቀኛው ጌታቸው መኩሪያ ዘመናዊ ሙዚቃን በኢትዮጵያ ስር እንዲሰድ ካደረጉና ሳክሲፎን መጫወት ከጀመሩ ኢትዮጵያውያን የመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚቀመጥ እንደነበረና በብሔራዊ ቲያትር በማዘጋጃ ቤትና በፖሊስ ሠራዊት ኦርኬስትራ ውስጥ ከሙዚቃ ተጫዋችነት እስከ ዋና መምህር በመሆን ለዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት የበኩሉን ድርሻ የተወጣ ሙዚቀኛ ነበር። ሙዚቀኛ ጌታቸው መኩሪያ በሳክሲፎን አጨዋወቱና የሙዚቃን መሳሪያ እንደልብ ማዘዝ በመቻሉ የሳክሲፎን ንጉስ የሚል ቅጽል ከሙዚቃ አፍቃሪዎች የተቸረ የተዋጣለት የሙዚቃ ባለሙያ ነበር። ሙዚቀኛ ጌታቸው መኩሪያ የዘጠኝ ልጆች አባትና የ81 ዓመት የእድሜ ባለጸጋ የነበረ ነው። የፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ በዚህ ታላቅ የሙዚቃ ሰው ሞት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፤ ለዘመዶቹ ለወዳጆቹ እና ለአድናቂዎቹ ሁሉ መጽናናትን ይመኛል።

 

Ø ሞሳክ ፎንሴካ ከተባለ የፓናማ የሕግ ስራ ኩባንያ በድብቁ የወጡ 11.5 ሚሊዮን የሚሆኑ ልዩ ልዩ ሰነዶች የተለያዩ መሪዎችና ታላላቅ ሰዎች ታክስ ባለመክፈል እና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ገንዘቦችን በማስተላለፍ በኩል የሰሩትን ወንጀል ያጋለጡ መሆናቸው ተገለጸ። ምንጫቸው ካልታወቀ በአንድ የጀርመን የጋዜጣ ተቋም መጀመሪያ ተሰራጭቶ ከመቶ በላይ የሚሆኑ ተመራማሪ ጋዜጠኞች ተሳትፈውበት የወጣውና በርካታዎችን የሚያጋልጠው ዘገባ በወንጀሉ ውስጥ 140 የሚሆኑ ታላላቅ የፖሊቲካ ሰዎች 12 የወቅቱና የቀደሞ የአገር መሪዎችን ያጋልጣል። ከእነዚህም ውስጥ የአሁኑ የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ዘመዶች፤ የራሺያው የሚስተር ፑቲን የቅርብ ረዳቶች፤ የአይሳላንዱ ጠቃላይ ሚኒስትር፤ ሟቹ የእንግሊዙ መሪ የሚስተር ካምሪን አባት፤ የዩክሬኑ መሪ ፖሮሼንኮ፤ የሳኡዲ አረቢያ ንጉስ ተጠቅሰዋል። ከዚህ በተረፈ ለአርባ አመታት ያክል በኩባንያው የተስተናገዱ 214 ሺ የውጭ ኩባንያዎችን የሚያጋልጥ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የሰሜን ኮሪያ የሶሪያ ኩባንያዎች፤ በእንግሊዙ HSBC በስዊዘርላንዱ Credit swiss በፈረንሳዩ ሶስይቴ ጄኔራል የተቋቋሙ ኩባንያዎች ከሞሳክ ፎንሴካ ጋር መስራታቸው ተጋልጧል።  የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ስለጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት መልስ ለዚህ ዓይነት መሰረተ ቢስ ክስ የምንለው የለም ሲሉ የክሪምሊን ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ ደግሞ ሰነዱን አወጡት የተባሉት ብዙዎቹ ጋዜጠኞች የቀድሞ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ የሲአይ ኤ እና የልዩ አገግሎት ሰራተኞች መሆናቸውን ገልጾ ይህ በሩሲያ ውስጥ አለመረጋጋት እንዲፈጠር የተደረገ  የአሜሪካ ሴራ ነው ብሎታል። የአይስላንድ ጠቅላይ ሚኒስትርም ስልጣን እንዲለቁ ከፍተኛ ግፊት የተደረገባቸው ሲሆን ፓርላማው ፈርሶ አዲስ ምርጫ እንዲካሄድ  እንዲያፈርሱ ፕሬዚዳንቱን ጠይቀዋል ተብሏል። አውስትራሊያ ፈረንሳይና ኒዘርላንድ ጉዳዩን እንመረምራለን ብለዋል።

  

Ø በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ተሰማርተው የነበሩና ህጻናትን አስገድደው በመድፈር የተከሰሱ ሶስት የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ወታደሮች እስር ቤት እንዳሉ በአንድ ወታደራዊ  ፍርድ ቤት ላይ የቀረቡ መሆናቸው ተነገረ። ሁለቱ ህጻናትን አስገደደው ደፍረዋል የሚል ክስ የቀረባባቸው ሲሆን አንደኛው ለመድፈር ሙከራ አድርጓል የሚል ክስ ቀርቦበታል። ሶስቱም የቀረበባቸውን ክስ ሀሰት ነው በማለት ክደዋል። በማዕከላዊ አፍሪካ ረፐብሊክ በተሰማሩ የተመድ እና የፈረንሳይ ወታደሮች ተፈጽማዋል የተባሉና ከተበደሉ ዜጎች አቤቱታ የቀረበባቸው ህጻናትን ጨምሮ ሴቶችን አስገድዶ የመድፈር ወንጀሎች ከ100 በላይ የደረሱ ሲሆን ከእነዚህ ተከሳሾች ውስጥ በወታደራዊ ፍርድ ቤት ለፍርድ ሲቀርቡ ይህኛው እስካሁን የመጀመሪያ መሆኑ ነው። የፈረንሳይ ወታደሮች በአዲስ መልክ የቀረበባቸውን ክስ እየመረመሩ መሆናቸው ኤኤፍ ፒ የተባለው የዜና ወኪል ቢያስታውቅም ከዚህ በፊት ለቀረቡት የተወሰደ እርምጃ አለመኖሩ ይታወቃል። በሌላ በኩል በኮንጎ ዴሞክራቲክ ተሰማርተው የነበሩና አስገድዶ በመድፈር አቤቱታ የቀረበባቸው የታንዛኒያ ወታደሮች ልጆች ያስወለዱ መሆናቸውንም ተጎጅዎች ክስ አቅርበዋል። ክስ የቀረበባችው አስራ አንድ ወታደሮች ሲሆኑ 4 ቱ በቅርቡ የተሰማሩ የተቀሩት ሰባቱ ደግሞ ቀደሞ ባለው ስምሪት ውስጥ የነበሩ መሆናቸው ተገልጿል። ባለፈው ዓመት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ 69 የሚሆኑ ሰዎች በደል የተፈጸማብቸው መሆኑን ሲያመለክቱ ወንጀሉን የፈጸሙት ከ10 አገሮች የተውጣጡ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት መሆናቸው ተነግሯል። በዚህ ወር ውስጥ የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት አቤቱታ የቀረባባቸው የሰላም አስከባሪ ኃይል ቡድኖች ሁሉ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መወሰኑ ይታወሳል። አንድ ገለልተኛ የሆነ የጥናት ቡድን የተመድ ኃይላፊዎች ጉዳዩን በሚገባ አለመከታተላቸውና ለችግሩ መፍተሄ በመስጠት በኩል ከፍተኛ ድክመት ያሳየ መሆኑ መግለጹ የሚታወቅ ሲሆን ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወርም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የተመድ ቋሚ መልክተኛ የሆኑት ከኃይላፊነት እንዲነሱ የተደረገ መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø በሱማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ተልእኮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የአፍሪካ ህብረተ የሰላም አሰከባሪ ኃይል አባላትና የሱማሌ መንግስት ወታደሮች በጋራ ባካሄዱት የጥቃት እርምጃ ስድስት የአልሸባብ መሪዎችን የገደሉ መሆናችውን ገልጸዋል። ከተገደሉት መካከል አንዱ በዜግነት የመናዊ የሆነና ቦምብ በመስራት በኩል የተካነ ነው የተባለ ሲሆን ሌላኛው በስልጠና ስራ ላይ የተሰማራ ኬኒያዊ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያም አንድ ሌላ ወታደራዊ መሪ መገደሉ የተገለጸ መሆኑ ይታወሳል። አልሸባብ እስካሁን ለመግለጫው የሰጠው መልስ የለም።

 

Ø በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዑክ ሚስተር ማርቲን ኮብለር ወደ ሊቢያ ተጉዘው በቅርቡ ከተመሰረተውና ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ወደሊቢያ ከገባው የአንድነት መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸው ተገልጿል።  የአንድነት መንግስቱ በሊቢያ ውስጥ  ተቀባይነት እንዲኖረው ከፍተኛ ጥረት በሚደረግበት ወቅት  ሚስተር ኮብለር ወደ ዚያ ሄደው መገናኘት መቻላቸው ሁኔታዎችን በማመቻቸት በኩል አጋዥ ሊሆን ይችላል ተብሏል። ባለፈው ወር ኮብለር ወደ ትሪፖሊ ለመግባት ጠይቀው በባለስልጣኖች የተከለከሉ መሆናቸው ይታወሳል። ባለፈው ረቡዕ ትሪፖሊ የገባው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የአንድነት መንግስት ተወካዮች ቡድን እስከአሁን ድረስ በወደቡ አካባቢ በሚገኘው የባህር ኃይል ወታደራዊ ካምፕ ውስጥም በመሆኑ ለመስራት እየሞከረ  ሲሆን በተለያዩ የሊቢያ ክፍሎች ድጋፍ እያገኘ መምጣቱ ይነገራል። የሊቢያ የኢንቬስትመንት ባለስልጣን፤ የሊቢያ የነዳጅ ኮርፖሬሽን እና የሊቢያ ማዕከላዊ ባንክ የአንድነት መንግስቱን የደገፉት ሲሆን 10 የሚሆኑ የሊቢያ የወደብ ከተሞችም የተለያዩ የሚሊሺያ ቡድኖች ድጋፋቸውን የሰጡት መሆኑ ተገልጿል፡፡

 

Ø ቦካ ሃራም ላይ ለመዝመት የተቋቋመው የጋራ ኃይል ለሶስት ቀናት ያህል በናይጀሪያ በካሜሩንና በቻድ ወሰን አካባቢ ባካሄደው አሰሳ 300 የሚሆኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑና ከ 2000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች አስሮ የፈታ መሆኑን በጋራው ኃይል ውስጥ የካሜሩን  ወታደራዊ ኃይል  አዛዥ የሆኑት ግለሰብ ማክሰኞ መጋቢት 27 ቀን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።  ዘመቻ የተካሄደው ኩምሸ ከምትባለው የሰሜን ናይጄሪያ ከተማ 35 ኪሎሜትር ላይ ርቆ በሚገኝ ቦታ ላይ መሆኑንና  በአሰሳውም የቦኮ ሃራም የማስልጠኛ ተቋሞችና ልዩ ልዩ መገልገያ መሳሪያዎች የተደመሰሱ መሆናቸውን ጨምረው ገልጸዋል። ቦኮ ሃራምን ለመደምሰስ ካሜሩን ናይጄሪያ እና ቻድ በጋር 9000 አባላት ማቋቋማቸው አይዘነጋም፡፤  

 

 

 

 

መጋቢት 26  ቀን 2008 ዓ.ም

 

 

Ø በኢትዮጵያ ያለውን ድርቅና ረሃብ ለማስወገድ ከውጭ መንግስታት በእርድታና በልገሳ የተገኘ እህልና ምግብ የጂቡቲ ወደብ በመጨናነቁ ምክንያት የእርዳታ እህል ለማራገፍ ያልተቻለ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል። የወያኔ ቡድን መሪዎች የእርዳታ እህል በጂቡቲ ወደብ ለማራገፍ ባለመቻሉ በሱዳንና በበርበራ ወደብ ለመጠቀም መወሰኑን የወያኔ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢትዮጵያ ድርቅን ረሃብ አሳሳቢነት ወደ አስጊነት ደረጃ በደረሰበትና  የተረጀው ቁጥር እየጨመረ ነው በሚባልበት ሰዓት በሱዳን ወደብ በኩል የወያኔ መሪዎች የሚገግዱትን 100 ሺ ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ለማስገባት ውል ሲፈራረሙ ለተራቡና በድርቅ ለተገጎዱ ወግኖች ደግሞ በሱማሊያ በርበራ ወድብ በኩል 25 ሺ ሜትሪክ ቶን የእርዳታ እህል ለማስገባት ወስኗል። ድርቅና ረሃብ በበረታበትና የዓለም አቀፍ ኅብረተሰብ ለእርዳታ በሚረባረቡበት ሰዓት የወያኔ መሪዎች በንግድ ድርጅቶቻቸው አማኝነት ያስመጡትን ማዳበሪያ ከእርዳታ እህል ይልቅ ቅድሚያ መስጠታቸው የአገዛዙ ሆነ የመሪዎቹ አረመኔትን በግልጽ የሚያሳይ ሆኗል። በረሃብ የተጠበሰው ወገን  የሚቀምሰውና የሚልሰው አጥቶ የእርዳታ እህል በየወደብ የሚያራግፈውና የሚያነሳው ባጣበት ሰዓት የወያኔ መሪዎች በየቀኑ 10 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ከሱዳን ወደብ እያነሱ ሲሆን የጭነት መኪናዎችም ቅድሚያ የወያኔን ማዳበሪያ እንዲያነሱ መታዘዛቸው ታውቋል።

 

Ø የወያኔ መሪዎች የነፍስ አድን ዕርዳታውን ከማስገባት ይልቅ  የንግድ ማዳበሪያዎችን ቅድሚያ ሰጥቶ በማስነሳት በረሃብተኛው ሕዝብና በድርቅ ጉዳተኞች ህይወት ቁማር ሲጫወቱ በመሃል ሀገር የወያኔ ካድሬዎችና ሹማምንት የዕርዳታ እህልና አልሚ ምግቦችን ከተራቡ ወገኖች ጉሮሮ በመንጠቅና በመስረቅ እየሸጡ መሆናቸው ታውቋል። በስልጢ ወረዳ የወያኔ መሪዎች የመደቧቸው ባለሥልጣናት በረሃብና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች እንዲፋፈል የተመደበውን 500 ኩንታል አልሚ ምግብ ማለትም ወተት ዘይትና በፕሮቲን የበለጸጉ ምግቦችን በቀጥታ ወደ ገበያ በመውሰድ እየቸበቸቡት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።  እነዚህ የአካባቢው  ባለሥልጣኖች ከወያኔ መሪዎች ጋር በመመሳጠር የእርዳታ እህሉንና አልሚ ምግብን ገበያ ማውጣታቸው የግለሰቦቹ ጭካኔና ስግብግብነት ብቻ ሳይሆን የወያኔ መሪዎችን ችላ ባይነትም አጋልጧል። የወያኔ መሪዎች ጫካ በነበሩበት ወቅት በድርቅና በረሃብ መነገድ የዘወትር ተግባራቸው የነበረ ሲሆን ስልጣን ከያዙ ወዲህም የእርዳታ እህልን እንደ ፖሊቲካ መሳሪያ በመጠቀምና በመሸጥ የግል ኪሳቸው ሲያደልቡ መቆየታቸው ይታወቃል። በኢትዮጵያ ከ450 ሺ በላይ ሕጻናትና አልሚ ምግብ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን ስልጢ ወረዳ ውስጥ ከ26 ሺ በላይ  እርዳታ ፈላጊዎች ናቸው።

 

 

Ø ማኅበረ ቅዱሳን ከመጋቢት 15 ቀን 2008 ዓም እስከ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓ.ም በኤግዚቢሽን ማዕከል ሊያካሂድ አቅዶት የነበረውን ዐውደ ራዕይ በልዩ ልዩ ተልካሻ ምክንያትና ሰበብ እንዳይካሄዱ ካደረገ  ወዲህ ማኅበሩ ጉዳዩን በቅርብ በመከታተል ባደረገው ጥረት ዐውደ ራዕይ እንዲካሄድ ወያኔ የፈቀደ መሆኑ ተገልጿል። ፈቃዱ እንደገና ተሰጥቷል ይባል  እንጅ በተባለበት ቀንና ጊዜ ለምን እንደተከለከለና ማን እንደከለለከለ ወያኔ የሰጠው ምንም ዓይነት መግለጫ የለም። የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ደጋፊዎች አሁን ፈቃድ መገኘቱን ይናገሩ እንጅ ዕውደ ራዕዩ መቼና የት እንደሚካሄድ ገና በንግግር ላይ መሆናቸውን አልሸሸጉም።  የማኅበረ ቅዱሳን ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምሮትን  ድርሻችንን እንወቅ በሚል ርዕስ ዐውደ ጥናት አዘጋጆችን ዝግጁነቱን አጠናቆ ባለበት ሰዓት በወያኔ መሪዎችና ከፓትርያርኩ ጽ/ቤት ባሉ ሰዎች አማካኝነት መታገዱን በማስታወስ አሁንም የማኅበሩን ዓላማ ተሳክቶ ዐውደ ራዕዩ ተግባራዊ እስካልሆን ድረስ የወያኔ ሸርና የካባ ለባሽ ካድሬዎቹ ተንኮልን በተጠንቀቅ መጠበቅ ይገባናል ይላሉ።

 

 

Ø ዛሬ መጋቢት 26 ቀን 2008 ዓም በኮንጎ ሪፐብሊክ ዋና ከተማ በብራዛቪል ከፍተኛ የጥይትና የከባድ መሳሪያ ድምጽ ሲሰማ መቆየቱን ነዋሪዎች ለዜና ምንጮች ካስተላለፉት መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ማከለከሌ በተባለው ቀበሌ አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ ክፍሎች በአንድ የፖሊስ ጣቢያና በአንድ የመንግስት ህንጻ ላይ ጥቃት የፈጸሙ መሆናቸው ተነግሯል። የሬውተር የዜና ምንጭ በዘገባው እንደገለጸው የተቃዋሚ ደጋፊዎች የሆኑ ወጣቶች በአንዳንድ ቦታዎች “ ሳሱ ሥልጣን ልቀቅ” የሚል መፈክር ደጋግመው ሲያሰሙ እንደነበር ገልጿል።  ከ1971 ዓም ጀምሮ በሥልጣን ላይ የነበሩት ዴኒስ ሳሱ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአገሪቱ በተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ በድጋሚ ለሌላ አምስት ዓመታት የስልጣን ዘመን መመረጣቸውና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ አይደለም  በማለት መቃወማቸው ይታወቃል። በዛሬው ግጭት ፖሊሶች  ከታጠቁ ኃይሎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲያደርጉ የነበሩ መሆናቸው የዜና ምንጮች የዘገቡ ሲሆን ይኸው ታጣቂ ቡድን የኒንጃ ሚሊሺያ ቡድን ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ይሰጣሉ።

 

Ø 16 000 አባላት ያሉት የደቡብ አፍሪካ የመከላከያ ሠራዊት ማህበር ባለፈው ሳምንት ፕሬዚዳንቱ የሠራዊቱ ጠቅላይ አዛዥ ለመሆን ብቃት ስለሌላቸው ስልጣናቸውን መልቀቅ አለባቸው ብሎ መወሰኑ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት የማህበሩን ውሳኔ በመቃወም የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የመከላከያ ኃይል አዛዥ ውሳኔው ለእርስ በርስ ግጭት የሚጋብዝ ከመሆኑም በላይ ህገወጥ ነው ብለውታል። ተቃዋሚዎች የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ በስልጣን መባለግ ተከሰው ከስልጣን እንዲወገዱ ያቀረቡት ጥያቄ ማክሰኞ መጋቢት 27 ቀን በምክር ቤቱ ላይ ቀርቦ ውይይት የሚካሄድበት ሲሆን የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ፓርቲ አብዛኛውን መቀመጫ በመያዙ በተቃዋሚዎች የቀረበው ሀሳብ ውድቅ ይሆናል ተብሎ ተገምቷታል። በሌላ በኩል የጸረ አፓርታይድ ትግል መሪና ከሚስተር ኔልሰን ማንዴላ ጋር በሮበን ደሴት ታስረው የነበሩት እውቁ አህመድ ካታራዳ ሚስተር ዙማ ከስልጣን መልቀቅ አለባቸው ብለዋል። ባለፈው ሳምንት ሚስተር ዙማ የተፈጸመው ስህተት ሆን ተብሎ የተደረገ አለመሆኑን ጠቅሰው ይቅርታ መጠየቃቸው ይታወሳል።

 

Ø ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለውና አንሳሩ እየተባለ የሚጠራውን የጂሃዲስት ድርጅት ይመራ የነበረና በአሜሪካ መንግስት በከፍተኛ ደረጃ ሲፈለግ የቆየው ካሊድ አል ባርናዊ የሚባለው ግለሰብ በናይጄሪያ ውስጥ የተያዘ መሆኑ ተነገረ። ከአራት ዓመት በፊት አሜሪካ ግለሰቡን ዋና አሸባሪ ብሎ የሰየመ ሲሆን ግለሰቡን ለያዘ ወይም ለገደለ አምስት ሚሊዮን ዶላር ካሳ ለመክፈል መዘጋጀቱን  ገልጾ የነበረ መሆኑ ይታወሳል። ከቦኮ ሃራም የተገነጠለውን ድርጅት አንሳሩን ይመራ የነበረው ካሊድ ባርናዊ በተለያዩ ጊዜያት በርከት ያሉ የውጭ አገር ሰዎችን በመግደል የሚጠረጠር ሲሆን ከአራት ዓመት በፊት በናይጀሪያ ዋና ከተማ አቡጃ ውስጥ ባለው ዋና እስር ቤት ላይ የተደረገውን ጥቃት አስተባበሮ በርካታ እስረኞች ያስፈታ መሆኑ ይነገርለታል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ትናንት መጋቢት 25 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በሱዳን በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በዚህ ዓመት ወደ 400 000 (አራት መቶ ሺ) የሚሆኑ ሰዎች የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ገልጿል። ድርቁ የተከሰተባችው አካባቢዎች ምስራቅ ሱዳን በምስራቅ ዳርፉር እና  በመካከለኛው ኮርዶፋን ግዛት ሲሆን በድርቁ የተጎዳው በጠቅላላው 3.8 ሚሊዮን ሕዝብ የተለያየ እርዳታ ሲደርግለት መቆየቱ ተነገርዋል። የምግብ እርዳታው በዚህ ዓመት በጠቅላላው 12.5 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑ ቃል አቀባዩ ገልጾ በጦርነት የተፈናቀሉትን ከመርዳቱ ጋር ተዳምሮ የበጀት ችግር ሊገጥም እንደሚችል ጠቁሟል።     

  

 

 

 

መጋቢት 24 ቀን 2008 ዓም

 

Ø ዘረኛነትና አድልዎ ታማኝነትና ቡድናዊ አሠራር በተለመደበት የወያኔ ሥርዓት ውስጥ ለትግራይ ተወላጆች ልዩ እንክብካቤና ጥቅም እንዲያገኙ መደረጉ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል። በቅርብ ከሚያዚያ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. እስከ ሚያዚያ 9 ቀን 2008 ድረስ ባህርዳር ከተማ ለሚደረገው የጣና ፎረም የአፍሪካ እምባገነን መሪዎችና የታዋቂ ግለሰቦች ስብሰባ የወያኔው ደህንነት መስሪያ ቤቱ ለጥበቃ የትግራይ ተወላጆችን በብዛት መምረጡ ታውቋል። ይህ ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ይደረጋል በተባለው ስብሰባ ለጥበቃ የሚሰማሩ አባላት ጠቀም ያለ ገንዘብና አበል የሚከፋል በመሆኑ የትግራይ ደህነነት አባላት በብዛት ተመርጠዋል። የድህንነት ምንጮች የትግራይ ተወላጆቹ በብዛት የተመረጡት ጥቅም እንዲያገኙ ብቻ ሳይሆን የአማራና የኦሮሞ ደህንነት አባላት ታማኝነታቸው አጠራጣሪ በመሆኑ ነው። የአፍሪካ አምባገነን መሪዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ያሉበትን የጣና ፎረም ስብሰባን የቀደሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሲንጎ ኦባሳንጆ ይመሩታል ተብሏል።

 

Ø በአዲስ አበባ ከተማ የስራ አጥነት ማስረጃ ለማግኘት የአምስት ቀን ስልጠና መውሰድ ግዴታ ነው ተባለ። ማስረጃውን የሚሰጠው የሚኖሩበት ቀበሌ ሲሆን እስከ ዛሬ ይሰራበት ከነበረው አሠራር የተለየ መሆኑንና ስራ አጡ ስራ ካገኘ በሰለጠነበት ካልሆነ አትሰራም ተብሎ እንደሚከለክልና እሰራለሁ ካለ ከቀበሌው ማስረጃ እንዲያቀርብ ይጠየቃል። ይህ የስራ አጥ ስልጠና የተባለውን ለወያኔ የገንዘብ መሰብሰብያ ድርጅቶች ስራ የፈጠረ ከመሆን ውጭ ለአዲስ አበባ ስራ አጦች የፈየደው ነገር አለመኖሩንም እንዲያውም የሥራ ዕድሉ ያገኙ ወጣቶች አንተ በዚህ ሙያ አለሰለጠንክም አንተ ለዚህ አትመጥንም እየተባሉ የሥራ ዕድሉን ከማጥበብ ውጭ የሰጠው ጠቀሜታ እንደሌለ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በከተሞች ከፍተኛ የሆነ የሥራ አጥ ቁጥር ያለ ሲሆን ወያኔ በሚከተለው ዘረኛና አምባገነን አድላዊ አገዛዝ ምክንያት ስራ የማግኘት ዕድል በእጅጉ እንደጠበበባ ተወላጅነትና የፖለቲካ ታማኝነት ዋና መስፈሪያ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በአባይ ወንዝ አጠቃቀምና በአባይ ግድብ ዙሪያ ወያኔና ግብጽ ያላቸውን ልዩነት ለማቻቻል ተደጋጋሚ የዲፕሎማቲክ ምንጮች እየገለጸ ባለበት ሰዓት የወያኔ አገዛዝ የዓባይ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ 6000 ሜጋ ሞት የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያመርቱና 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሚትር ውሃ ሊይዝ እንደሚችል እየገለጹ ነው። የወያኔ መሪዎች ግድብ ሲጀመር 5250 ሚጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመርታል ይበሉ እንጅ አሁን ቁጥሩን ከ6000 በላይ ማለታቸው ታውቋል። ግድብ ከኃይል ማመንጫነት በተጨማሪ ለመስኖ ለዓሣ እርባታና ለትራንስፖርት ይውላል ይበሉ እንጅ የግብፅ መንግስት ግድብ አሁንም በታሪካዊ የዓባይ ወንዝ ውሃ አጠቃቃሜ ላይ ችግር ይፈጥራል በማለት ተቃውሟውን በማሰማት ላይ ይገኛል። የቀድሞዎቹ የግብጽ ፕሬዚዳንቶች በአባይ ግድብ ላይ ወታደራዊ ኃይል መጠቀም እንደአማራጭ እንደሚወስዱት መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ግብጽ መሪዎች የበለጠ ለዲፕሎማሲ ለሕግና ለቴክኒካል ኮሚቴ ጥናት ጊዜ ይሰጡ እንጅ የከረረ ፍትጫ ውስጥ እንደሚገባ የማይቀር መሆኑ ይነገራል። ወያኔ ስለ አባይ ግድብ ተጨማሪ ፕሮፓጋንዳ ለመንዛትና በተለይ ከውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵይውያን ገንዝብ ለመሰበብ ግድብ የተጀመረበት አምስተኛ ዓመት በማለት ስብሰባ ለመጥራት ማቀዱ ተገልጧል።

 

 

Ø በሶማሊያና በኬኒያ ወሰን አካባቢ  ጂብ እየተባለ በሚጠራው ቦታ የአሜሪካው ወታደራዊ ተቋም  ሰው አልባ መንኮራኩርን በመጠቀም  ሶስት የአልሸባብ መሪዎችን ይዟል የተባለ ተሽከርካሪን በማጥቃት የደመሰሰ መሆኑን አንድ የፔንታጎን ቃል አቀባይ ገልጿል። በተሽርካሪው ውስጥ ነበረበት ተብሎ የሚጠረጠረውና ለመግደል ኢላማ የተደረገው ሃሰን አሊ ዳሁር የተባለው የአልሸባብ መሪ ሲሆን ግለሰቡ በቅርቡ በሱማሊያ ውስጥ አሜሪካውያንን ጨምሮ በርከት ያሉ ሰዎች የገደሉትን  የቦምብ ጥቃቶች ሲያደራጀና ሲያስተባብር  የቆየ ነው ተብሏል። የተወሰደው እርምጃ  ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃ ቃል አቀባዩ  ገልጾ  ግምገማ እያካሄደ መሆኑን አብራርቷል።

 

Ø በተያያዘ ዜና ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2008 ዓም  በኬኒያ ከአንደ ዓመት በፊት በጋሪሳ ዪኒቨርስቲ በአልሸባብ  ታጣቂዎች የተገድሉትን 148 ተማሪዎች ሌሎች ሰራተኞች ለማስታወስ የተለያዩ ስነስርዓቶች ሲደረጉ ውለዋል። በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰብስበው የሞቱትን ያስታወሱ  ሲሆን  በኬኒያ ዋና ከተማ በናይሮቢ የተገደሉትን ለማስታወስ የጸሎትና የሻማ መብራት ሥነ ስርዓቶች የተካሄዱ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ትናንት መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓም በቴሌቪዥን አማካይነት ለሕዝቡ ባደረጉት ንግግር በቅርቡ የግል መኖሪያ ቤታቸውን ለማሻሻል የተደረገው ግንባታ  በርካታ ውዝግብ ማስነሳቱን ገልጸው ለተፈጠረው ሁኔታ በይፋ ሕዝቡን ይቅርታ ጠይቀዋል። የደቡብ አፍሪካ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት ያስተላለፈውን የፍርድ ውሳኔ የሚቀበሉ መሆኑን ገልጸው ለመዋኛ ቦታና ለቲያትር መመልከቻው ሕንጻ የወጣውን ወጭ እንደሚከፍሉ ቃል ገብተዋል። ለዚህ ጉዳይ የተቋቋመ አንድ የጸረ ሙስና ተቋም የተጠቁስትን ሕንጻዎች ለመገንባት ከመንግስት ካዝና 23 ሚሊዮን ዶላር የወጣ መሆኑን ገልጾ ሚስተር ዙማ ይህንን ገንዘብ መክፈል ያለባቸው መሆኑን በማስረገጥ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወቃል።  በሚስተር ዙማ በኩል ገንዘቡን ለመክፈል ፈቃደኛነት ባለመገኘቱ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ሄዶ የደቡብ አፍሪካ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት  ባለፈው ሐሙስ ሚስተር ዙማ የተጠቀሰውን ገንዘብ እንዲከፍሉ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል። በሌላ በኩልም ሁለት ዋና ዋና የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምክር ቤቱ ሚስተር ዙማ በስልጣን መባለግ ክስ ወንጅሎ ከስልጣን እንዲያባርራቸው አጀንዳ አስይዘው ውይይት እየተካሄደበት ነው። የሚስተር ዙማ የቴሌቪዥን ንግግር  ስልጣኔ በፈቃዴ ለቅቄያለሁ ሲሉ ለመስማት ጠብቆ የነበረውን ክፍል ያበሳጨ ቢሆንም ሚስተር ዙማ አሁንም ቢሆን ለምን ያህል ጊዜ በሥልጣን ይቆያሉ የሚለው ጥያቄ አሁንም አነጋጋሪ ሆኗል። ገሚሱ ሚስተር ዙማ በማጭበርበርና በማሳዘን የሕዝብን አስተያየት በማስቀየር በኩል የተካኑበት መሆኑን በተደጋጋሚ ያሳዩ በመሆናቸው በቅርቡ የተፈጠረውን ሁኔታ በተመሳሳይ መልክ ይወጡታል ሲል በአሁኑ ወቅት በፕሬዚዳንት እየተካሄደ ያለው ሙስናና ዓይን ያወጣ የዘመድ ስራ ይፋ በመውጣቱ ከዚህ ችግር የሚወጡበት መንገድ ጠባብ ነው የሚል ግምት የሚሰጡ በርካታ ናቸው።  ክፍሎች

 

Ø በኮንጎ በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ተመድበው የሚሰሩት የታንዛኒያ ወታደሮች በእድሜ አነስተኛ የሆኑ ህጻናትን አስገድደው ደፍረዋል የሚል ክስ የቀረበባቸው መሆኑ ተገልጿል። ወንጀሉን ፈጽመዋል የተባሉት  ማቪቪ በተባለው መንደር አካባቢ የተሰማሩ የታንዛኒያ ወታደሮች ሲሆኑ ክሱ የተረጋገጠ ከሆነ አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ ለታንዛኒያ እና ለኮንጎ መንግስት ባለስልጣኖች መረጃው መተላለፉን የተመድ ቃል አቀባይ ገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ ከካምፕ እንዳይወጡ የተደረገ ሲሆን በደል ለደረሰባቸው ህጻናትም የስነ ልቡናና የማህበረሰባዎች ርዳታዎች እየተደረገላቸው መሆኑ ተነግሯል። የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና በኮንጎ ተመሳሳይ ክሶች ሲቀርቡባቸው መቆየቱ አይዘነጋም።

 

Ø በትናንትናው ዕለት መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓም ሲካትሴሬ በተባለችው የናይጄሪያ ሰሜናዊ ግዛት ከተማ ከሶስት ወር በላይ አለምንም ፍርድ በግፍ የታሰሩት የሺያ ሃይማኖት ተከታይ መሪ ሚስተር ዛክዛኪ ከእስር እንዲፈቱ ሰላማዊ ስልፈኞች አደባባይ በመውጣት ጠይቀዋል። ከአንድ ሳምንት በፊት አንድ  የኮሎኔልነት ማዕረግ ያለው የናይጀሪያ ወታደራዊ መኮንን  በሺያ ሃይማኖት ተከታዮች ቡድን ተጠልፎ ከተወሰደ በኋላ ተገድሏል የሚለውን ክስ  ቡድኑ መካዱ ይታወቃል። የሺያ ሃይማኖት መሪ በቁጥጥር ስር የዋሉት በዚህ ዓመት ታህሣር ወር ውስጥ ሲሆን ለመታሰራቸው ምክንያት የሆነው የእምነቱ ተከታዮች አንድ የናይጄሪያ ጄኔራል ጠልፎ ለመያዝ መከራ አድርገዋል በሚል ነው። በወቅቱ በአካባቢው የነበረው የናይጄሪያ ወታደር ሶስት የሺያ መስጊዶችን  የደመሰሰ ሲሆን መሪውን ዛክሳኪን በሥስት ጥይት አቁሰለው ከመያዛቸውም በላይ የዛክዛኪን ልጆች ጨምሮ በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ይታወቃል። የናይጄሪያ ፍርድ ቤት አንድ ተጠርጣሪ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት ብሎ ቢያዝም ከሶስት ወር በላይ የተቀመጡ መሆናቸው ታውቋል። ዛክዛኪ ከ 37 ዓመት በፊት ከኢራን ጎብኝተው ሲመለሱ የመሰረቱት የሺያ ሙስሊም ሃይማኖት በሚሊዮን የሚቆጠር ተከታዮች ቢኖሩትም በአካባቢው ከሚኖሩ የሱኒ ሙስሊም አባሎች ጋር ሲወዳደር በቁጥር አነስተኛ በመሆናቸው ከፍተኛ በደል የደረሰባቸው መሆኑ ይታወቃል። ባለፈው ሳምንት የሺያ ሃይማኖት እንቅስቃሴ የሚባለው ድርጅት በአካባቢው ከ 1000 ሰዎች በላይ ሰዎች በመገደላቸው በዐለም አቀፉ ፍርድ ቤት ክስ መመስረቱ ይታወሳል።

 

 

 

 

መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በትናንትናው ዕለት መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓም ደብረ ዘይት ውስጥ አዋሽ በተባለ ሆቴል ውስጥ የተወረወረ የእጅ ቦምብ አንድ ሕጻን ገድሎ ሌሎች አራት ሰዎችን በጽኑ ማቁሰሉ ታውቋል። የቦምቡን ፍንዳታው ተከትሎ የወያኔ ጸጥታ ኃይሎችና ወታደሮች ደብረዘይትን አስጨንቀዋት እንደሚገኙ ተገልጿል። የዓይን ምስክሮች የእጁ ቦምብ አንድ ግለሰብ እንደወረወረውና እነደተሰወረ ሲገልጹ ለፍንዳታው ኃላፊነትን የወሰደ ግለሰብም ሆነ ቡድን የለም። ብዙ ሀገር ወዳድ ዜጎች ግን በመላ ኢትዮጵያ ከተሞች በደብረዘይትም ጭምር ከተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ጋር በተያያዘ የወያኔ የፀጥታና የደህንነት ኃይሎች የጣሉት አደጋ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ ድርጊቱን የፈጸሙትም የሕዝብ ወገንና ልጆችን ለማሰር የተሸረበ ሴራ ሊሆን እንደሚችል ከፍተኛ ግምትና ጥርጣሬ እንዳላቸው ይናገራሉ። የወያኔ ባለሥልጣናትም ሆነ የደብረ ዘይት ከተማ ሹማምንት የቦምብ አደጋውን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት የሰጡት መግለጫ አለተመዘገበም።

 

Ø መቀመጫውን እንግሊዝ አገር ያደረገው ላንሴት የህክምና ጆርናል የዘንድሮውን የሰውነት ክብደትና ይዘት መለኪያ (Body Mass Index) ይፋ አድርጓል። ሰንጠረዡ እንደሚያሳየው የዓለም ሕዝብ ውፍረት በአስደንጋጭ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል። በ1967 በተደረገው ተመሳሳይ ጥናት 105 ሚሊዮን ሕዝብ ወፍራም ተብሎ እንደተፈረጀና ባለፈው ዓመት የተጠናቀቀው ና በ200 አገሮች በተካሄደው ጥናት 647 ሚሊዮን ሕዝብ ወፍራም መሆናቸው አስደንጋጭ ነው ተብሏል። ወፍራም የተባሉት አብዛኞቹ የሚገኙት በበለፀጉና ሀብታም በተባሉ አገሮች ውስጥ ሲሆን አሜሪካ ወፍራሞችን በብዛት በማስመዝገብ ቀዳሚነቱን ስታሳይ ጃፓን ደግሞ የበለጸገችና ሀብታም ሆና የወፍራሞችን ቁጥር አነስተኛ ቁጥር አነስተኛ የሆኑባት አገር ሆናለች። ከአሜሪካ ቀጥሎ አውስትራሊያ፣ ካናዳ ፣አየር ላንድ፣ኒውዚላንድና ብሪታኒያ ወፍራሞችን በብዛት እንደቅድመ ተከተላቸው ያስመዘገቡ ሲሆን በቀጫጫነት ደግሞ ምስራቅ ቲሞር ኢትዮጵያና የሻዕቢያዋ ኤርትራ አነስተኛ ቁጥር ያለው ወፍራሞችን አስመዝግበዋል፡፤ የሕክምና ባለሙያዎች ወፍራምነትን ተከትለው የሚመጡ በርካታ የጤና ችግሮች መኖራቸውን በመግለጽ ተመጣጣኝ የሰውነት አቋም  ከክብደትና ከቁመት ጋር እንዲኖር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አነስተኛ ክብደት መኖርም ለጤንነት አስጊ መሆኑን ይገልጻሉ። የሰውነት ክብደት የሚያሰጋቸው ሰዎች ከመጡበት አካባቢና ከኑሮ ደረጃቸው ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችልም ይገመታል።

 

Ø የወያኔ ቡድን ጠፍጥፎ የሠራው ብአዴን የተባለው ቡድን እወክለዋለሁ በሚለው የአማራ ሕዝብ ላይ በየወቅቱና በየጊዜው አሳፋሪና አሳዛኝ ድርጊቶችን ሲፈጽም መቆየቱ ይታወቃል። ሰሞኑን ደግሞ የወልቃይት ሕዝብ ለማንነቱና ለመብቱ ያነሳውን ጥያቄ በግድያ በአፈናና በእስር ምላሽ እየሰጠ ባለበት ሰዓት በሁመራ የሃይማኖት አባቶች የተባሉት የወልቃይትን ነዋሪ ሃሳብ እንዲቃወሙ ስብሰባ መጥራቱ ታውቋል። የሃይማኖት አባት የተባሉት ስብሰባ የተጠሩት የወልቃይት ሕዝብን እንዲያወግዙ መሆኑ ተገልጿል። የወያኔው ተላላኪ ብአዴን ለወልቃይት ሕዝብ ጥያቄ የወያኔን ነፍሰ ገዳይ ጦር አግአዚ በመጥራት የጥይት ምላሽ ሲሰጥ የውግዘትና የተቃውሞ ድምጻቸውን ያላሰሙት የሃይማኖት አባት የተባሉት ዛሬ ከወያኔ ጋር በመሆን ለውግዘት መሰልፋቸው የሃይማኖት አባት የሀገር ሽማግሌ ሳይሆኑ ተራ ተላላኪ መሆናቸውን አሳይተዋል። የጎንደር ነዋሪዎች የሃይማኖት አባቶቹ ከወያኔ ጎን በመቆም ይህን ዓይነት ወራዳና ሕዝብ የሚጎዳ ተግባር መፈጸማቸው ከሃይማኖት አባት የማይጠበቅ የተራ ቀበሌ ካድሬ ስራ ነው በማለት ለመብትና ለማንነት የሚደርገው ትግል ይቀጥላል ይላሉ።

 

Ø የወያኔው የንግድ ሸሪክ የሆነው መሀመድ አላሙዲን ቤት ከዓመታት በፊት ግዥ የፈጸመባቸውን የንግድና የእርሻ ድርጅቶች ክፍያን በወቅቱ ባለመፈጸሙ ወደ ግማሽ ቢሊዮን የሚጠጋ ብር እንዲከፍል በወያኔው ፍርድ ተፈርዶበታል። ወያኔ የመንግስትና የሕዝብ ሀብት የነበሩትን ጎጀብ  እርሻ ልማትን፤ አዲስ ጎማን የሊሙና የበበቃ የቡና እርሻን ለመሀመድ አላሙዲ ሜድሮክ ኩባንያ መሸጡ ይታወሳል። መሀመድ አላሙዲ የልማት እርሻዎቹን ሆርዘን ፕላንቴሽን በማለት ስያሜ ሰጥቶ ክፍያ ግን ባለመፈጸሙ ጊዜ ቢሰጠውም በገንዘብ ቀውስ ሊከፍል አለመቻሉ ታውቋል። የወያኔው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ችሎት ጉዳዩን ለወራት መርምሮ የልማት እርሻዎቹ ባለንብረት መሀመድ አላሙዲን ድርጅቶቹ ያላቸውን አጠቃላይ ዕዳ 433 ሚሊዮን 571 ሺህ 241 ብር በጊዜ ገደብ እንዲከፍል ካልከፈለ ከነወለዱ እንዲከፍል ወስኗል። የፖሊካ ተመልካቾች የወያኔ የፖለቲካ ፍርድ ቤት በወያኔ የንግድ ሸሪካ ላይ ይህን ውሳኔ የጣለው በቱጃሩና በውያኔ መካከል ያለው ፍቅር አልቆ ነው ወይስ ስግብግብና አልለጠግብ ባይ የሆኑት የወያኔ መሪዎች ውትሮችም በዘዴና በስልት የሰጡትን የሀገርና የሕዝብ ንብረት በህግና በፍርድ ቤት ስም ሊቀበሉት በማሰብ ነው በማለት ይጠይቃሉ።

 

 

Ø በህንድ አገር ካልከታ ከተማ ውስጥ ከመንገድ በላይ የተሰራ አንድ ድልድይ በመደርመሱ ከ 24 ሰዎች በላይ ሞተው በርካታ የቆሰሉ መሆናቸው ታውቋል። ከተደመረሰው ድልድይ ስር ያሉትን ሰዎች ለማውጣት አስቸጋሪ በመሆኑ በዚህ ምክንያት ሊሞቱ የሚችሉ ሰዎች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆኑ እንደሚችል ተሰግቷል። እስከ ዛሬ ድረስ 90 የሚሆኑ ሰዎችን ከተደረመሰው ድልድይ ስር በማውጣት ለማዳን የተቻለ ሲሆን አብዛኞቹ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታል ተልከዋል።  2 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው ድልድይ ከተጀመሩ ስድስት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የተደረመሰው በግምባታ ጥራት ጉድለት ነው ይባላል። ፖሊስ ድልድዩን ሲሰራ የነበረው ኩባንያ ኃይላፊዎችን በቁጥጥር ያደረገ ሲሆን በወንጀል ክስ የሚመሰርትባቸው መሆኑን ገልጿል። በአገራችንም አብዛኞቹ መንገዶች ድልድዮችና ህንጻዎች የሚሰሩት ጥራታቸውን ባልጠበቀ ሲሚንቶና ሌሎች የህንጻ መሳሪያዎች መሆኑን በመናገር እንደ መሬት መንቀጥቀጥ ዓይነት ያሉ የተፈጥሮ አደጋዎች  ከተከሰቱ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ለጉዳዩ እውቀት ያላቸው በርካታ መሀንዲሶች መምከር ከጀመሩ ዓመታት ተቆጥረዋል።

 

Ø የሊቢያ የአንድነት መንግስት ተቀባይነት አግኝቶ ሁኔታውን መቆጣጠር ከቻለ ሊቢያ የተያዘባት የአገሪቱ ገንዘብ ወዲያውኑ ሊለቀቅ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። ላለፉት አምስት አመታት 67 ቢሊዮን ዶላር የአገሪቱ ገንዝብ እንዳይነቃነቅ በተመድ የተያዘ መሆኑ ይታወቃል። ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓም ትሪፖሊ ወደብ የገባው በተመድ ግፊት የተቋቋመው የሊቢያ የአንድነት መንግስት በከተማው ውስጥ ተኩሶች በመበርከታቸው እና የጸጥታው ሁኔታ ያልተረጋጋ በመሆኑ ምክንያት  ከወደቡ አካባቢ በመውጣት ወደ ሌሎች የከተማዋ ክፍሎች ያልተንቀሳቀሰ መሆኑ ተገልጿል።  በትሪፖሊ የራሱን መንግስት ያቋቋመው አካል  መሪ ካሊፋ ገዊል በቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ የውጭ መንግስት አስጠባቂና ሰርጎ ገብ የሆነው የአንድነት መንግስት የሚባለው አካል በእኛ አካባቢ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። አያይዘውም ወደ ትሪፖሊ የገቡት የአንድነት መንግስት የልኡካን ቡድን አባሎች ወይ እጃቸውን ለእኛ በሰላም ይስጡ ካለበለዚያም ይመለሱ የሚል መግልጫ ሰጥተዋል። በትሪፖሊም የአንድነት መንግስቱን የሚቃወሙ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሄደዋል።  ከአምስት ዓመት በፊት የጋዳፊ መንግስት ከተገለበጠ ጀምሮ በሊቢያ ምስራቅና ምዕራብ ሁለት ራሳቸውን መንግስት ነን ብለው የሚጠሩ የታጠቁ ክፍሎች መመስረታችው ይታወቃል። ባለፈው ታኅሳስ ወር በተመድ አማካይነት ከሁሉም የተውጣጣ መንግስት ለማቋቋም የተጠነሰሰው ሀሳብ በአንዳንድ ክፍሎች ስምምነት እንዲቋቋም ቢደረግም በምስራቅም ሆነ በምዕራብ የአንድነት መንግስቱን መቋቋም የሚቃወሙ ክፍሎች በማየላቸው መንግስቱ ተመስርቶ ሊንቀሳቀስ አልቻለም። ሰሞኑን ከዚህ ጋር በተያያዘ የአንድነት መንግስቱ እንዳይንቀሳቀስ እንቅፋት ሆነዋል ብሎ በሰየማቸው ሶስት የሊቢያ ባለስልጣኖች ላይ  የአውሮፓው ህብረት ማዕቀብ የጣለ መሆኑ ገልጿል። ማዕቀብ የተጣለባቸው ግለሰቦች አጊላህ ሳላህ በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው መንግስት የፓርላማ መሪ፤ ካሊፋ ገዊል የትሪፖሊ መንግስት መሪ እና አቡ ሳህማን የጠቅላላ ብሔራዊ ኮንግሬስ መሪ መሆናቸውም ተነግሯል።  ሶስቱ ግለስቦች ወደ አውሮፓ እንዳይገቡ የተከለከሉ ሲሆን በአውሮፓ ውስጥ የሚገኝ ገንዘብና ንብረታቸው እንዳይንቀሳቀስ እገዳ ተጥሎበታል። የምዕራባውያን ጣልቃ ገብነት የአሁኑን የሊቢያን ሁኔታ ፈጥሯል የሚል አስተያየት የሚሰጡ  ወገኖች የጋራ ስምምነት እስከሌለ ድረስ የሊቢያ ቀውስ ይቀጥላል በማለት ስጋታቸውን ይገልጻሉ።

 

Ø ከአስራ ሰባት ዓመት የስልጣን ጊዜ በኋላ የጅቡቲው ገለህ በሚቀጥለው ሳምንት መጋቢት 30 ቀን 2008  በሚካሄደው ምርጫ የሚመረጡ መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ነው በማለት በርካታ ታዛቢዎች እየተናገሩ ይገኛሉ። የዛሬ ስድስት ዓመት ፓርላማው የጂቡቲን ሕገ መንግስት በመቀየሩ ምክንያት ገለህ ለሶስተኛ ጊዜ የተመረጡ ሲሆን የአሁኑ አራተኛው የስልጣን ዘመናቸው ይሆናል።  የተቃዋሚዎች ህብረት በአንድ ላይ ለመቆም ችግር ያለበት ቢሆንም ከሰባት ተቃዋሚ ድርጅቶች መካከል ሶስቱ የታቀደው ምርጫ መሰረታዊ የሆነ የነጻና ፍትሃዊ ምርጫ መመዘኛዎች ያላሟላ የይስሙላ ምርጫ  ስለሚሆን አንሳተፍም ብለዋል። ነጻና ገለልተኛ የሆነ የምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ እንዲቋቋም የቀረበውን ጥያቄ የገለህ መንግስት ውድቅ አድርጎታል። ጅቡቲ ውስጥ አሜሪካ በየመን፤ በሶማሊያና በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጸረ ሽብር ጥቃቶችን የምታስተባብርበት የጦር ማዕከል ሲኖራት ፈረንሳይ፤ ጃፓን እና ቻይናም ወታደራዊ የጦር ሰፈሮች የመሰረቱ መሆናቸው ይታወቃል። አገሪቱ ባለፉት አመታት የኢኮኖሚ እድገት አሳይታለች ተብሎ ብዙ ቢወራላትም በአግሪቱ ውስጥ የስራ አጡ ቁጥር 60 ከመቶ የደረሰ ከመሆኑም በላይ ቢያንስ አንድ አራተኛ የሚሆነው የጂቡቲ ሕዝብ በከፍተኛ ድህነት ክልል እንደሚኖር ይታወቃል።  

 

Ø ዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓም የተባበሩት መንግስት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት 100 የሚሆኑ ዓለም አቀፍ የፖሊስ ኃይል አባላት  በብሩንዲ ስላም ለማስከበር ስለሚሰማሩበት ሁኔታ በፈረሳይ መንግስት በቀረበው ረቂቅ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ይሰጥበታል ተባለ። ቁጥራቸው ከ100 የማይበልጥ ፖሊሶች ወደ ጅቡቲ ተልከው በብሩንዲ የሰብአዊ መብትን ለማስከበር ስለሚቻልበት ሁኔታ እርዳታ ያደርጋሉ ተብሏል። በብሩንዲ የእርስ በርስ ግጭት ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎች በገፍ የሚገደሉበት፤ የሚያዙበትና ተይዘውም በምርመራ ከፍተኛ ስየል የሚካሄድባቸው የዜና ምንጮችና የተመድ ባለስልጣኖች በየጊዜው መግለጻቸው ይታወቃል።  በቀረበው ሀሳብ መሰረት 100 ፖሊሶችን ለመላክ የታቀደ ሲሆን ጸጥታን ለማስከበር ቁጥሩን እንደማይበቃ ብዙዎች ይናገራሉ። የብሩንዲ ችግር በጀመረ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ400 በላይ የብሩንዲ ዜጎች ሲገደሉ ከ12 000 ሰዎች በላይ እንደተሰደዱ ተዘግቧል። 

 

 

 

 

መጋቢት 22 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች ውስጥ የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ዛሬም በልዩ ልዩ ከተሞች በተለያየ ማዕዘናት ውስጥ ውስጡን እንደቀጠለ መሆኑን ከየአካባቢው የሚመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። በምዕራብ ሐረርጌ ፈዲስ ወረዳ አሁንም ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ እየፋመ ሲሆን የወረዳ ገዥ የተባለውን ሕዝብ አባሮታል። በአርሲ በተለያዩ ከተሞች የተማሪዎች ተቃውሞ እንደ አዲስ የተቀሰቀሰ ሲሆን የወያኔ ቡድን መሪዎች ነፍስ ገዳይ ጦራቸውን አግአዚንም ቢልኩ ሞት ያልፈሩ ወጣቶችና ሕዝብ በመጋፈጣቸው ውጥረቱ ከፍተኛ ሆኗል። በኢሊባቦርም ሕዝቡና ተማሪዎች በአንድ ላይ በመሆን የታሰሩት እንዲፈቱ የወያኔ ነፍሰ ገዳይ ጦር ከከተሞችና ከገጠር ለቆ እንዲወጣ በመጠየቅ ተቃውሟቸውን በአደባባይ እየገለጹ መሆናቸው ታውቋል። የወያኔ ቡድን የሚዘሯቸው መገናኛ ብዙኀን የሕዝብ ተቃውሞና ቁጣ ወያኔ በሰጠው መልስ ተደስቶ ተቃውሞ ጠፍቷል፤ በርዷል በማለት ራሳቸውን ብቻ የሚያሞኝ ፕሮፓጋናዳ ይንዙ እንጅ የተቃውሞ ትግሉ በየአቅጣጫውና በየማዕዘኑ አሁንም እንደቀጠለ ነው።

 

Ø የያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት ከማለቁ በፊት የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ከሀገሩ እንደሚያባርር አስታውቋል። የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ 11 ሺ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ለማባረር ማቀዱን የገለጸ ሲሆን ስደተኞቹን ለማባረር የሚያስተባብርና የሚያቀናብር አዲስ የሚመጡትንም የሚቀበልና የሚያስተናግድ ግብረ ኃይልም አቋቁሟል። የፈረንሳይ መንግስት ለጊዜው ከሶሪያ ከኢራቅና ከሻዕቢያ ኤርትራ የሚመጡ ስደተኞችን ብቻ ለመቀበል መወሰኑ ታውቋል። በኢትዮጵያ የኦስትርያ አምባሳደር APA ለተባለ የዜና ወኪል በሰጡት ቃለ ምልልስ በአውሮፓ ጥገኝነት ከጠየቁ ኤርትራውያን ውስጥ 40 ከመቶ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ተናግረዋል። አምባስደሩ አያይዘውም በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳኡዲ አረቢያና ደቡብ አፍሪካ እንደሚገቡ ገልጸው ወደ አውሮፓ የሚመጡ ስደተኞች ግን የፖለቲካ ጥገኛነት ለማግኘት የተሻለ ዕድል እንዲያገኙ ኤርትራውያን ነን እንደሚሉ ተናግረዋል። ማንም ብዙ ያላወራለት በዓመት ከ 100 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ መካከለኛ ምስራቅ መሄዳቸውንም ገልፀዋል። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የተቃዋሚ ፖሊቲከኛ በአውሮፓ ጥገኛነት እንደማይሰጠው አምባሰደሩ ተናግረዋል። የኢትዮጵያውያን መከራና ስቃይ የሚያውቅና የሚቀበል እየጠፋ መምጣቱ የሚያሳየው መከራና ስቃይ በስደት የሚከተል ከሆነ በሀገር ውስጥ የመከራና የስቃይ ምንጩን የወያኔ አገዛዝን መታገል ብቸኛ መፍትሔ ነው የሚሉ ወገኖች በዙ ናቸው።

 

 

Ø የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የሰብዓዊ መብት፣ የዴሞክራሲና የሠራተኛ ጉዳይ ረዳት ኃላፊ የሆኑት ቶም ማሊኖውስኪ በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ጉብኝት ጀምረዋል። ረዳት ኃላፊው ማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ መግባታቸው ሲታወቅ እስከ መጋቢት 28 ቀን 2008 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ በሩዋንዳ ብሩንዲና ኬኒያ እንደሚያደርጉ ከወያኔ መሪዎችና ባለሥልጣናት ጋርም እንደተነጋገሩ ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ ከሲቪክ ድርጅት መሪዎች ጋርም ንግግርና ምክክር ማድረጋቸው ታውቋል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ረዳት ኃላፊ የኢትዮጵያ ጉብኝት ባለፈው ሐምሌ ወር የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ አቦማ በኢትዮጵያ ካደረጉት ጉብኝት ጋር የተያያዘና ቀጣይነት ላይ የተመረኮዘ መሆኑ ተነግሯል።

 

Ø የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ ከጥቂት ዓመታት በፊት በገጠር በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው የመዋኚያ ቦታ እና ሲኒማ የመመልከቻ ትልቅ አዳራሽ እንዲኖረው ለማድረግ የሚያስፈልጉ  ግንባታዎች ለመስራት  የተጠቀሙበትን የመንግስት ገንዘብ ባለመመለሳቸው የሕገ  መንግስቱን ደንብ ጥሰዋል በማለት የአገሪቱ የመጨረሻው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፈረደ መሆኑ ተገልጿል።  ፍርድ ቤቱ ቢያንስ የተወሰነውን ገንዘብ ፕሬዚዳንቱ መመለስ ያለባቸው መሆኑን የተጠቀሰ ሲሆን ምን ያህል መክፈል እንዳለባቸው የአገሪቱ ግምጃ ቤት እስከሚቀጥለው ሁለት ወራት ድረስ ወስኖ እንዲያስታውቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ከሁለት ዓመት በፊት የደቡብ አፍሪካ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ፕሬዚዳንቱ የገጠር ቤታቸውን ለማሻሻል የተጠቀሙት ገንዘብ 23 ሚሊዮን ዶላር መሆኑን ገልጾ ቢያንስ የተወሰነውን ገንዘብ ለመንግስት መመለስ እንዳለባቸው መውሰኑ ይታወሳል። ክሱን የመሰረቱት ሁለት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በፍርድ ቤቱ ውሳኔ የተደሰቱ መሆኑን ገልጸው በምክር ቤቱ ላይ ፕሬዚዳንቱ ክስ ቀርቦባቸው ከሥልጣን እንዲነሱ ለማድረግ ጥረታቸውን የሚቀጥሉ መሆኑን  ገልጸዋል።

 

Ø በብሩንዲ ታስረው የነበሩት የቀድሞ የሩዋንዳ ሚኒስትር እና አምባሳደር በእስር ላይ እንዳሉ መሞታቸው ተገለጸ። ስለአማሟታቸው ከብሩንዲ መንግስት በኩል የተሰጠ ይፋ መግለጫ ባይኖርም  ግለስቡ የሞቱት በእስር ቤት ውስጥ ባለው ሆስፒታል በደረሱ በጥቂት ጊዜ ውስጥ መሆኑን በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች ተናግረዋል።  የብሩንዲ የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትር እና አምባሳደር የነበሩት እኚህ ግለሰብ ከሩዋንዳው እልቂት በፊት በብሩንዲ ይኖሩ የነበሩ ሲሆን ከዚያ በኋላ በየጊዜው ወደ ብሩንዲ ይመላለሱ እንደነበር ይታወቃል። ባለፈው ታህሣስ ወር በስለላ ጉዳይ ተጠርጥረው ከተያዙ በኋላ ጉዳዮቸው ወደፍርድ ቤት አለመቅረቡ ብዙ ወገኖችን ሲያሳስብ ቆይቷል። ሩዋንዳ የብሩንዲ መንግስት አማጽያንን ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠች ወደ ብሩንድ ትልካለች የሚል ክስ የብሩንዲ መንግስት በተደጋጋሚ ካቀረበ በኋላ በሩዋንዳና በብሩንዲ መካከል ያለው ግንኙነት እየተበላሸ መጥቷል። የሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ለዜና ምንጮች በሰጠው መግለጫ ግለሰቡ ቀደም ብሎ የተያዙትም ከህግ ውጭ ሲሆን አሁን በድንገት መሞታቸውም ብዙ ጥያቄዎችን የሚያነሳ መሆኑና የብሩንዲ መንግስት ባስቸኳይ መልስ መስጠት ያለበት መሆኑን ገልጿል።

 

v ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008 በናይጀርና በናይጄሪያ ወሰን አካባቢ ቦኮ ሃራም ባካሄደው የደፈጣ ውጊያ 6 የናይጀር ወታድሮች የተገደሉ መሆኑ ተገልጿል። ደፈጣው የተደረገው ዲፋ በተባለቸው የወሰን ከተማ አቅራቢያ መሆኑና ሌሎች  ሶስት ወታደሮች መቁሰላቸው በተጨማሪ ተነግሯል።  ደፈጣውን ያካሄዱት የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰባቸው አልታወቀም። ከጥቂት ቀናት በፊት በአገሪቷ ላይ በተካሄደው ምርጫው ሚስተር ኢሱፉ በፕሬዚዳንት አሸንፈዋል ተብሎ በምርጫ ኮሚሽኑ የተሰጠውን ውሳኔ በመቀበል ትናንት ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን  የናይጀር የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት  ማረጋገጫ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫውን እንደማይቀበሉ ቀደም ብለው አስታውቀዋል።

 

Ø ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 22 ቀን 2008 ዓም ጋልካዮ በተባለ የሱማሊያ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ  የአልሸባብ አባል የሆነ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ ከራሱ ሌላ ቢያንስ 9 ሰዎች የገደለ መሆኑና ከ10 በላይ ሰዎች ያቆሰለ መሆኑ ተዘግቧል። በማዕከላዊ የሶማሌ ግዛት ውስጥ የሚገኘው ጋልካዩ የተባለው ከተማ  ለሁለት የተከፈለ ሲሆን  ከፊሉ ከተማ በፑንታላንድ አስተዳደር ስር ሲሆን የተቀረውን የከተማዋን ክፍል በሞጋዲሹ ያለው የሶማሊያ መንግስት ያስተዳድረዋል። ለቦምቡ ጥቃት ኃላፊነቱን የወሰደው አልሸባብ የጥቃቱ ኢላማ የፑንትላንድ ባለስልጣኖች ነበሩ ብሏል።

በተያያዘ ዜና በትናንትናው ዕለት በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞጋዲሾ ውስጥ የአልሸባብ ታጣቂዎች መኪና ላይ ሆነው ባካሄዱት የጥይት እሩምታ ሁለት የቱርክ ዶክተሮችን ጨምሮ በጠቅላላው 6  ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። የዛሬ አራት አመት አልሸባብ ከዋና ከተማዋ እንዲወጣ ቢደረግም አሁንም ሰፊ የሆነውን የገጠር ቦታ እንደሚቆጣጠር ይነገራል።

 

Ø በተመድ አማካይነት የተመሰረተው የሊቢያ የአንድነት መንግስት አባሎች ትናንት ረቡዕ መጋቢት 21 ቀን 2008  በመርከብ ትሪፖሊ የገቡ መሆናቸው ታውቋል። ቀደም ብሎ የአንድነት መንግስት በአውሮፕላን ወደ ትሪፖሊ ለመግባት ያቀረበውን ጥያቄ ትሪፖሊ ላይ መሰረት ያደረገው ራሱን መንግስት ነኝ ብሎ የሰየመው ቡድን እንደማይቀብለው በተደጋጋሚ የገለጸ ሲሆን ይህን ባለመቀበል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚገኙበት የሰባት ሰዎች የልኡካን ቡድን የአንድነት መንግስቱን በመወከል በመርከብ ትሪፖሊ የደረሰ መሆኑ የደረሰ መሆኑ መነገሩ ብዙዎችን አስገርሟል። ልዑኩ ወደ ትሪፖሊ የመጣው ከአካባቢ ከሚገኙ  የባህር ኃይል አባሎች ከፖሊስ አካላትና ከሌሎች ታጣቂ ኃይሎች ጋር ተነጋግሮና ተስማምቶ እንደሆነ ቢገልጽም በተለያዩ የሚሊሺያ ኃይሎች ሲደገፍ የቆየው የትሪፖሊው መንግስት ባለስልጣኖች የቡድኑን መገኘት በጽኑ ተቃውመዋል። የአንድነት መንግስት የልኡካን ቡድን አባላት  በሰላም እጃቸውን እንዲስጡ  አለበለዚያም በሰላም ወደ መጡበት እንዲመለሱ አስጠንቀቅዋል። በከተማው አንዳንድ ቦታዎች የመንገድ መዘጋት ከመታየታቸውና አልፎ አልፎ የጥይት ድምጽ ከመሰማቱ በስተቀር እስካሁን ብዙም ችግር እንዳልተፈጠር ነዋሪዎች ያወራሉ። በትናንትናው ምሽት መንግስት ነኝ የሚለው ቡድን የሰጠውን መግለጫ ያስተላልፍ የነበረ አንድ የራዲያና የቴሌቪዥን ጣቢያ በአካባቢው ሚሊሺያዎች ተወርሮ መዘጋቱ ተሰምቷል። ከበድ ያለ የእርስ በርስ ግጭት ይኖራል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ስጋት እስካሁን አለመከሰቱ እና ሰላም መውረዱ በሊቢያ ላለው አካል ድጋፋቸውን ሲሰጡ የነበሩት የተለያዩ የሚሊሺያ ኃይሎች አሁን ድጋፋቸውን ወደ አንድነቱ መንግስት ማዞራቸውን ያሳያል   የሚሉ ታዛቢዎች አልጠፉም። ትናንት ትሪፖሊ የገቡት የአንድነት መንግስት ልኡካን አባላት እርቅና ስምምነትን ፈጥረው ሰላም ለማስፈን ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርጉ በተደጋጋሚ ተናግረዋል። በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የሚፈጠረው ሁኔታ የአገሪቱን የወደፊት እድል ይወስናል በሚል ታዛቢዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።  

 

 

 

መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ማክሰኞ ዕለት እንዳስታወቀው ከእርስ በርስ ጦርነት የምትዳክረው የመን 485 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን  ከቅዳሜ መጋቢት 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ማስወጣቱን ገልጿል። ስደተኞቹ በመርከብ ወደ ጅቡቲ ከተሻገሩ በኋላ ከጅቡቲ በአውቶቡስ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከየምን ከተመልሱ ስደተኞች ውስጥ 122ቱ ሴቶች ሲሆኑ 261 ወንዶችና 101 ደግሞ ለአቅመ አዳም ያልደረሱ መሆናቸው ታውቋል። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ከዚህ ቀደም 4222 ኢትዮጵያውያንን ከየመን ያስወጣ ሲሆን ባለፈው ዓመት መስከረም ባጋጠመው የገንዘብ እጥረት ምክንያት ስደተኞችን መመለስ ማቆሙ ይታወሳል። ይኽው የተመድ የስደተኛ ጉዳይ ድርጅት አሁን በያዘው ፕሮጀክት 1212 ስደተኞችን ለመመለስ ማቀዱ ታውቋል። ተመላሽ ስደተኞች በአስራጊዎቹና ስደተኞችን በመያዣ በሚይዙ ወንጀለኞች የከፋ ስቃይና እንዲሁም ግድያ ይገጥማቸው እንደነበር ተናግረዋል። የመን እስከ አሁን ድረስ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የሚጎርፉባት አገር መሆኗ የሚረጋገጠው የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ሪፖርት ባለፈው ዓመት 92 ሺ ስደተኞች የመን እንደገቡና ከነዚህ ውስጥ 89 ከመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን መግልጹ ነው። ስደተኞቹ  በጦርነት አረንቋ ውስጥ ወደምትዳክረው የመን  መሄዳቸው  ዘረኛ የሆነው የወያኔ አምባገነን አገዛዝ ቅጥ ያጣው ድህነት አስከፊነቱ በጣም  ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን  ያሳያል የሚሉ ወገኖች ብዙ ናቸው።

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በኢትዮጵያ የዘረጉትን የአንድ ዘር የበላይነትን ዘላለማዊ ለማደረግና የአምባገነናዊ አገዛዛቸውን ለማስቀጠል የፖሊስ ቅጥር ማስታወቂያ ማውጣቸው ታወቀ። ይህ ለወያኔ 18ኛ ዙር የፖሊስ ቅጥር ጥሪ የተባለለት ማስታወቂያ ከመጋቢት 20 ቀን 2008 እስከ ግንቦት 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረሰ የሚከናወን ይሆናል ተብሏል።  ለ 18ኛው ዙር የፖሊስ ምልመላ የተቀጥሩ ወጣቶች የአንድ ሺህ ሁለት መቶ ስልሳ ብር ደመወዝና አራት መቶ አምሳ ብር አበል እንደሚከፍሉ የተገለጸ ሲሆን ማስታወቂያውም በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በኩል እንዲሰራጭ የተደረገ መሆኑም ታውቋል። ለፖሊስና ለወታደር ምልመላ ወያኔ አዲስ አበባን ትቶ መቆየቱና  ትኩረቱን  ወደ ተለያዩ ክፍለ ሀገሮች አድርጎ የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን   አሁን በአዲስ አበባ ምልምል ፖሊሶችን ለመቅጠር የወጣው ማስታወቂያ በእርግጥ ለፖሊስነት መሆኑ የሚጠራጠሩ ወገኖች  በፖሊስነት ስም  ለውትድርና ምልመላ ሳይሆን አይቀርም ይላሉ።   

Ø የወያኔ ቀንደኛ መሪ የተባለውና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ በአማካሪነት ስም የኃይለማርያም ደሳለ አዛዥ የሆኔው ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ለፓርላማው ባቀረበው ሪፖርት ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ በተቀሰሰበት ወቅት በኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች ውስጥ የወያኔ ድህረ ገጾች ተሰብረው እንደነበር ገልጿል። ደብረጽዮን የወያኔ የመገናኚያና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር የተባለ ተጨማሪ ማዕረግ እንዳለውም ይታወቃል። የወያኔ ድህረ ገጾች ሰበራ በአብዛኛው ያትኮሩት በወረዳ ላይ ባሉ ኔትዎርኮች ላይ ሲሆኑ ወረዳዎቹ ለወያኔ መሪዎች የሚያቀርቡት የጸጥታና የድህንነት ሪፖርቶች ሁሉ ይወሰዱ እንደነበር ገልጾ ለማስቆም ጥረት መደረጉን ተናግረሯል። በሌላ በኩል ደግሞ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል መጥፋትና መቆራረጥ በቴሌ አገልግሎት ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ መምጣቱን ገልጾ ቴሌ በኤሌክትርክ  አሁን ግን ቴሌ የራሱ የኃይል አማራጭ ይኖረዋል ይበል እንጅ በኢትዮጵያ መፍተኄው ስለጠፋለት የኤሌክትሪክ መቋረጥና መጥፋት የተነፈሰው ነገር የለም።  ደብረጽዮን ቴሌ በአሁኑ ጊዜ 42.3 ሚሊዮን የሞባይል ደንበኛ፤ 890 ሺ የመደበኛ የስልክ ደንበኞች እንዲሁም 12.4 ሚሊዮን የኢንተርኔት ተጠቃሚ እንዳለውና ገልጾ ይህም  ከአፍሪካ ሁለተኛ ነው ይበል እንጅ ኢትዮጵያ ካላት የሕዝብ ብዛት አኳያ የተጠቃሚው ቁጥር ከአፍሪካ የመጨረሻዎቹ አገሮች ናት ተብላ መመደቧ ይታወቃል። ደሃ የሆነውችውና ጦርነት ያላባራባት ሶማሊያ እንኳ ከሕዝቧ 90 ከመቶ የሆነው የሞባይልና የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆኑ ይነገራል።    

 

Ø በያዝነው የፈረንጆቹ የፈረንሳይ ወታደሮች ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ዓመት ጨርሰው የሚወጡ መሃናቸውን የፈረንሳይ የመከላከያ ሚኒስትር ኤኤፍፒ ለተባለው የዜና ወኪል በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ጨምረው እንደገለጹት ምንም እንኳ ሁሉም የአገሪቱ ችግሮች የተፈቱ ባይሆንም  የፈረንሳይ ወታደሮች ተልዕኮ ግቡን ስለመታ ጣልቃ ገብነቱ በዚህ ዓመት ያበቃል ብለዋል። ከሶስት ዓመት በፊት የታጠቁ አማጽያን  በወቅቱ የነበረውን የፕሬዚዳንት ፍራንስዋ ቦዚዜን መንግስት ሲገለብጡ ፈረንሳይ ሁኔታውን ለማረጋጋት በሚል ምክንያት  ወደ አገሪቱ ጦሯን መላኳ አይዘነጋም። በቅርቡ በተደረገው ምርጫ ሚስተር ቱዋዴራ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል።

 

Ø በጊኒ የኑሮ ውድነት እየጨመረ በመሄዱና መንግስቱም የነዳጅ ዋጋ እንዲቀንስ የቀረበለትን ጥያቄ ባለመቀበሉ ሕዝቡ ለሁለት ቀናት ጠቅላላ አድማ እንዲያደርግ ተቃዋሚ ኃይሎች ጥሪ አድርገዋል። የተቃዋሚ ኃይሎች መሪዎች በሰጡት መግለጫ ሁሉም ዜጋ ለሁለት ቀናት በቤት ውስጥ በመቀመጥ አድማ እንዲያካሂድ ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን ዘረፋና ሌሎች የወንጀል ተግባራት እንዳይከናውኑ በጥብቅ ተማጽነዋል። የጊኒ መንግስት በሕዝቡ ላይ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት መቆጣጠር ያልቻለ ሲሆን በኢቦላ በሽታ ምክንያት የአገሪቱ ኢኮኖሚ መናጋቱን በመግለጽ የነዳጅ ዋጋ እንዲቀንስ የቀረበውን ጥያቄ አንቀበልም ብሏል። 

 

Ø በትናንትናው ዕለት አንድ የግብጽ የመንገደኞች አውሮፕላንን ጠልፎ ወደ ቆጵሮስ የወሰደው መሀመድ ሙስጠፋ የሚባለው የ58 ዓመቱ ግብጻዊ ዛሬ መጋቢት 21 ቀን ፍርድ ቤት መቅረቡ የተገለጸ ሲሆን ለሚቀጥለው ስምንት ቀን  በዕስር ላይ ሆኖ ምርመራው እንዲቀጥል ዳኛው የፈቀደ መሆኑ ታውቋል። መሀመድ ሙስጠፋ አውሮፕላኑን አስገድዶ ወደ ቆጵሮስ እንዲሄድ ያደረገው የሀሰት ቦምብ ታጥቄያለሁ ብሎ  በማስፈራራት ሲሆን ይህን እርምጃ የወሰደው በቆጵሮስ የምትገኘውን የቀድሞ ሚስቱንና የልጆቹን እናት ለማየት ነው ተብሏል። የአይምሮ በሽተኛ ነው የተባለው  መሀመድ ሙስጠፋን  በጠለፋ እና በሽብር ወንጀሎች ሊከሰስ እንደሚችል ተጠቁሟል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም ይፋ ባደረገው ዘገባ በማሊ የሚገኘው የጸጥታ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን ገልጾ የማሊ መንግስት የጸጥታው ሁኔታ እየተባለሸ ወደ ሚገኝበት ወደ ሰሜን ማሊ ባስቸኳይ ወታደሮቹን እንዲልክ ጠይቋል። በትናንትናው ዕለት በተመድ ዋና ጸሐፊ አማካይነት ለጸጥታው ምክር ቤት የቀረበው ይኸው ልዩ ዘገባ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ በተጻራሪ ኃይሎች መካከል የሰላም ስምምነት ቢፈረምም አክራሪና አሸባሪ ኃይሎች በሰሜን እና በመሀል ማሊ ጸጥታውን ለማደፍረስ እየተንቀሳቀሱ በመሆኑ ሁኔታው አሳሳቢ ሆኗል ብሏል።   ከአራት ዓመት በፊት በማሊ የተካሄደው መፈንቅለ መንግስት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቅም የሰሜን ማሊን ግዛት ይዘው የነበሩት አማጽያን በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ ከአካባቢው ቢወገዱም የሰሜንና የማዕከላዊ ማሊ ግዛቶች ጸጥታቸው ሲደፈርስ መቆየቱ ይታወቃል። ከጥቂት ወራት በፊት በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ላይ አማጽያን ባካሄዱት ጥቃት ሰባት ወታደሮች እና ሁለት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን እንዲሁም በዋና ከተማ በሚገኘው በራዲስን ሆቴል የተካሄደው የአሸባሪዎች ጥቃት በርካታ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወቃል። አሸባሪዎች በማሊ በአይቮሪ ኮስት እና በቡርኪና ፋሶ ጥቃታቸውን እያስተባበሩ መሆኑን ዘገባው ጠቅሶ ሁኔታውን ለመቋቋም የማሊ መንግስት ከሚወስዳቸው እርምጃዎች በተጨማሪ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል መጠናከር አለበት ብሏል። ባሁኑ ወቅት በማሊ 10 700 የሚሆን የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ያሉ ቢሆንም አንድ ልዩ የተዋጊ ኃይል 134 ወታደራዊ ካሚዮኖች አንድ ተዋጊ ሄሊኮፕተርን ሌሎች ለወታደራዊ ስራ የሚያገለግሉ ሄሊኮፕተሮች ያስፈልጉታል ተብሏል።     

 

 

 

 

መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የኖርዌይ መንግስት  የፖሊቲካ ጥገኝነት የጠየቁ 800 ኢትዮጵያውያንን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ የተዘጋጀ ሲሆን ከሚላኩት ውስጥ  60ዎቹ  ህጻናት እንደሆኑ ተገልጿል። መንግስቱ ስደተኞች ያቀረቡት የፖሊቲካ ጥገኝነት ጥያቀ ተቀባይነት አላገኘም በማለት በግዳጅ ለመመልስ ይወስን እንጅ የስደተኛ ከለላ ጠባቂ የሆኑ ድርጅቶች ግን ስደተኞቹ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱ በአካላቸውና በመንፈሳቸው ጉዳት ከማምጣቱ በተጨማሪ  ለህይወታቸው አስጊ እንደሚሆን በመጥቀሰ  መንግስት ጉዳዩን እንደገና እንዲመለተው ውትወታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በቅርቡም በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኖርዌይን መንግስት ውሳኔ በመቃወም ኦስሎ ላይ ታላቅ የተቃውሞ ስለፍ ማድረጋቸው ይታወሳል። የወያኔ ቡድን መሪዎች በሀገር ውስጥ ሕዝብን በዘረኛ አምባገነን አገዛዝ ረግጦ መግዛት ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገር የሚኖሩትም ገጽታችንን ያበላሻሉ በማለት ከየቦታው ለማስወጣት ከየአገሮቹ ጋር ልዩ ልዩ ስምምነት እየፈጠሩ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከፍተና መከራና ስቃይ እየደረሰባቸው ነው።

 

Ø ከጥቂት ቀና በፊት በአዲስ አበባ ከተማ የታክሲ ሹፌሮችና ባለንብረቶች አዲስ የወጣውን የትራፊክ ህግ በመቃወም የሥራ ማቆም አድማ በማድረጋቸው የወያኔ መሪዎች ሕጉ እንደገና እንደሚታይና  ለሶስት ወር ተግባራዊ እንደማይሆን በመግለጽ  የሥራ ማቆም አድማውን ለጊዜውም ቢሆን ማስቆማቸው ይታወሳል። ሰሞኑን  ውስጡን አዲሱን የተራፊክ ሕግ ተግብራዊ እያደረጉ በመምጣታቸው ምክንያት አንዳንድ የታክሲ ሹፌሮች ትናንት መጋቢት 19 ቀን 2008 ዓም ለአገልግሎት ሳይወጡ የቀሩ መሆናቸው የታየ ሲሆን በወያኔ ካድሬዎች ለታክሲዎቹ መጥፋት የገብርኤል በዓል እንደምክንያት ሲሰጥ ውሏል ። በዛሬው ዕለት መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም በስራ መግቢያ ሰዓት ላይ ከፍተኛ የታክሲ ዕጥረት እንደነበር ታውቋል፡፤ ይህ የታክሲ ዕጥረት የተከሰተው በርካታ አሸከርካሪዎች ለሥራ ባላመውጣታቸው  መሆኑ ሲታወቅ ምናልባት የታክሲ ማኅበራቱ አጥቃላይ አድማ ሊጠሩ ይችላሉ ተብሎ ተገምቷል። አሁን ያለው የታክሲ ሥራን የማቀዝቀዝ አድማ አዲስ አበባ ከተማን ውጥረት ውስጥ ከቷል።

 

Ø ከምርኮኛ ወታደሮች ወያኔ በአምሳሉ ጠፍጥፎ የሰራው ኦህዴድ የመሠረተበትን 24 ኛ ዓመት አከብራለሁ ይበል እንጅ እንደታሰበውና እንደታቀደው መከበሩ አጠያያቂ እየሆነ ነው። የወያኔው ኦህዴድ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተዋረድ ታች ያሉትን አባላትና ደጋፊዎች ሰብስቦ ለማነጋገር ይታቀድ እንጅ ከሕዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ ከሕዝብና ከታች አባላት ጋር መገናኘቱ አስቸጋሪ እንደሚሆን ከወያኔው ኦህድዴ ጽሕፈት ቤት አካባቢ የተገኘው መረጃ አመልክቷል።  ኦህዴድ ቀደም ሲል በያዘው መርሀ ግብር መሠረት የድርጅቱ ባለሥልጣናት በየቦታውና በየአዳራሹ እየተገኙ የኦህዴድን በዓል እንዲያስከብሩ የታቀደ ቢሆንም የወገኖቻችንን ደም በአግአዚ ወታድሮች እያፈሰሰ እንዴት በዓልና ፌስታ ይኖራል? ኦህዴድ የአሰገዳይና የገዳዮች ተባባሪ ሆኗል በማለት ካድሬዎቹ እርስ በርስ መነጋገራቸው የኦህዴድ በዓል መከበሩ አጠያያቂ ሆኗል። ከዚህ በዓል አካባበር ጋር በተያያዘ ዋና የተባሉ ካድሬዎች በዓሉ ከተከበረ ላለመገኘት የዓመት ፈቃድና የህክምና ፈቃድ እየጠየቁ ከስራ እየወጡ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ለከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው እንዲያመች አድላዊና ዘረኛ አምባገነን አገዛዝን ከመሠረቱ ጊዜ ጀምሮ የትግራይ ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመነጠል የኢኮኖሚ የፖሊቲካ የወታደራዊ የትምህርት የልማትና የኢንቨስትመንት የሚዲያዎች ወዘተ ሥራዎች ለትግራይና ለትግራይ ተወላጆች ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል። ሰሞኑን ደግሞ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል የማይታሰበውን በትግራይ አዲስ ቤት የሚሰራበትን ቦታ ስፋት በመጨመር መመሪያ አውጥቷል።  በመመሪያው መሠረት ቀደም ብሎ ቤት ሰሪዎች ከ180 ካሬ ሜትር በላይ የማይፈቅድላቸው የነበረ ሲሆን አሁን ከዚያ በላይ በሆነ የቦታ ስፋት ላይ መስራት እንደሚችሉ ተፈቅዶላቸዋል።  የወያኔ ቡድን መሪዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመላ ኢትዮጵያ እየተቀጣጠለ የመጣውን የተቃውሞ እሳት በትግራይ ሕዝብ ኪሳራ ለማዳፈን ትግራይ ውስጥ አንድ ግዙፍ የኬሚካል ፋብሪካ ለማቋቋም ከወስኑ ወዲህ አሁን ደግሞ የቤት ሠሪዎችን የቦታ መጠን ለማስፋት መፍቀዱ የትግራይ ሕዝብ ከጎኑ ለማሰልፍ የሚደርግ ጥረት መሆኑ ታውቋል። ብዙ ሀገር ወዳድ ዜጎች ወያኔ ከትግራይ ውጭ ባሉ ኢትዮጵያያኖች ላይ የሚፈጽመው ግድያ እስር በደልና አድልዎችን በትግራይ ሕዝብ ላይ ለለላው መጠን እንዲፈጽም ፍላጎት ባይቦራቸውም  እንደ ትግራይ ግን ልማትና እንክብካቤ ቢኖራቸው እንደማይጠሉ ይናገራሉ።

 

Ø ሰሞኑን በሰሜን ሶማሊያ በአልሸባብና መንግስቱን በሚደግፉ ወታድሮች መካከል በተካሄደ ውጊያ 115 የአልሸባብ ወታድሮች መገደላቸውን የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ አስታውቋል።  110 የአልሸባብ ታጣቂዎች መማረካቸንና ሌሎች ወደ ገጠር ማምለጣቸውን መግለጫው ጨምሮ ገልጿል። ታጣቂዎቹ ሽንፈት የገጠማቸው ለአራት ተከታታይ ቀኖች በተደረገ ጦርነት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የሶማሊያ መንግስት በውጊያ ስለደረሰበት ጉዳይ የሰጠውም መግለጫ የለም።ይህ የመንግስት መግለጫ በሌላ በሶስተኛ ወገን አልተረጋገጠም። አልሸባብ በደቡብ ሶማሊያ በርካታ ሽንፈት ስለገጠመው በሰሜን የጦር ሰፈር ለመመስረት እየሞከረ ነው ተብሏል። 22000 የሚደርሱ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል በሱማሊያ የሚገኝ ሲሆን የሶማሊያ መንግስትን አልሸባብን ለመደምሰስ የቆረጠ መሆኑን በተደጋጋሚ ቢዝትም የቡድኑ እንቅስቃሴ ጎላ እያለ መምጣቱን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች ይጠቁማሉ።

 

Ø አሌክሳንድሪያ ከምትባለው የወደብ ከተማ ወደ ካይሮ ሲበር የነበረው የግብጽ የመንገደኛ አውሮፕላን ተጠልፎ ወደ ቆፕሮስ (ሳይፕረስ) መወሰዱ ተነገረ። ጠለፋው ከሽብረተኛነት ጋር የተያያዘ አይደለም የተባለ ሲሆን አውሮፕላኑ በቆፕሮስ  አውሮፕላን ማረፊያ እንዳረፈ ተሳፋሪዎቹ በሙሉ ተለቀዋል። በአውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት 55 መንገደኞች መካከል  21 ዱ የውጭ አገር ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል። ጠላፊው በእጁ ላይ የያዘው ምንም ዓይነት ፈንጅ ወይም መሳሪያ ያልተገኘ ሲሆን ጠለፋውን ለመፈጸም ያስገደደው በቆፕሮስ የምትኖረውን ፍቅረኛውን ለማይት መሆኑን ገልጿል። ጠላፊው በቁጥጥር የተደረገ ሲሆን በቆፕሮስ የፖሊቲካ ጥገኛነት ጠይቋል።

 

Ø በአይቮሪ ኮስት  ሰሜናዊ ግዛት ባለፈው ሳምንት ረቡዕ መጋቢት 14 ቀን 2008 በአርብቶ አደሮችና በአካባቢው ገበሬዎች መካከል በግጦሽ ምክንያት በተነሳ የእርስ በርስ ግጭት የአስራ ሰባት ሰዎች ህይወት የጠፋ ሲሆን ከ 1300 የሚሆኑ ሰዎች  በላይ የሆኑ ሸሽተው ወደ ቡርኪና ፋሶ የገቡ መሆናቸው ተገልጿል። ከተሰደዱት መካከል አብዛኞቹ  ሴቶችና ህጻናት ናቸው። በአይቮሪ ኮስት በዘላኑ ህብረተሰብ እና በገበሬዎች መካከል በግጦሽና በውሃ አጠቃቀም ብዙ ግጮት ሲደደሩ የቆዩ ቢሆንም የአሁኑ ከፍተኛ የነበረ መሆኖ ተገልጿል።

 

Ø በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ የሚገኙ ሁለት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በወሲብ ወንጀል የተከሰሱ መሆናቸውን የተመድ ቃል አቀባይ ሰኞ መጋቢት 19 ቀን ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ገለጹ። ተጠርጣሪዎቹ አንዱ የብሩንዲ ሌላው የሞሮኮ ወታደሮች ሲሆኑ በማዕካለአዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር ክስ የተመሰረተባችደውን የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ቁጥር ወደ 25 ከፍ አድርጎታል። በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ ብሩንዲ 1128 ወታድሮች  ሞሮኮ ደግሞ 741 ወታድሮች  ሲኖሯቸው ሞሮኮ በወታደሩ ላይ የተሰነዘረውን ክስ  የምትመረምር መሆኗን ገልጻለች። ባለፈው ሳምንት አስፈላጊ ከሆነ በቻድ ውስጥ የሚገኘው ወደ 12 000 የሚደረሰው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል በሙሉ በለላ ኃይል ሊለውጥ እንደሚችል የተመድ ዋና ጸሀፊ ባንኪ ሙን መግለጻቸውና ይህንን አስመልክቶ በመጋቢት 2 ቀን 2008 ዓም ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡

 

Ø በምግብ እጥረት ምክንያት ከደቡብ ሱዳን ወደ ሱዳን የሚሰደደው ሕዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መሄዱ ተነገረ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2008 ዓም እንዳስታወቀው በደቡብ ሱዳን ውስጥ በሰሜን ምዕራብ ግዛቶች ብቻ 38000 ሺ የሚሆኑ ስደተኛች ወደ ምስራቅና ደቡብ ዳርፉር ግዛት የተሰደዱ መሆናቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ የስደተኞቹ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ እንደሆነ ገልጾ ልጆች ከወላጆቻቸው የተለዩ መሆናቸውንና ከፍተኛ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑ አብራርቷል። ባለፉት ሶስት ዓመታት በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት 2.3 ሚሊዮን የሚሆን የደቡብ ሱዳን ዜጋ ከሚኖርበት ተነቅሎ ወደ ሌሎች ቦታዎች የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ከተማ  የኖርዝ ዌስት ዩኒቨርስቲ  ለአንድ ወር ያህል ከተዘጋ በኋላ እንደገና መከፈቱ ተነገረ። ከጥቂት ወራት በፊት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የትምህርቱ ክፍያ እንዲቀንስ፤ የኖሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና ለነጮች ፍላጎት የተዘጋጀው የትምህርት ሥርዓት እንዲሻሻል በመጠየቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሲካሄድ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ባለፈው ወር የኖርዝ ወስት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ባደረጉት ተቃውሞ የአስተዳድሩን ቢሮና የሳይንስ ማዕከሉን ማቃጠላቸው ይታወሳል። ሁኔታው ተረጋግቶ በዛሬው ዕለት ትምህርት መጀመሩ ተነግሯል።          

 




 

Ø የአዲስ አበባን አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ለመጠቅለል የወጣውን ማስተር ፕላን በመቃወም በተለያዩ ቦታዎች ሕዝባዊ ተቃውሞ ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። ለዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ አስፈላጊውን እርምጃ አልወሰዳችሁም፤ ተባባሪ ነበራችሁ በማለት ከወያኔ መሪዎች በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣኖችን ከፓርቲው የኃላፊነት ቦታ ማባረሩም ይታወሳል። ሰሞኑን ከሚደመጡና ከሚነበቡ ሪፖርቶች ደግሞ የወያኔው ፓርላማ አፈ ጉባዔ አባዱላ ገመዳና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የተባለው ዲሪባ ኩማ እንቅስቃሴያቸው በወያኔ ደህንነት ራዳር ስር መውደቁ ተዘግቧል። ሁለት ከፍተኛ የአገዛዙ ባላሥልጣናትና የወያኔ ኦህዴድ መሪዎች ከተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ጋር በተያያዘ በዓይነ ቁራኛ ውስጥ እንዲወድቁ መደረጉ ሲታወቅ ወደ ውጭ ሀገራም እንዳይወጡ ፓስፖርታቸውን መነጠቃቸው ተገልጿል። የወያኔ መሪዎች ላጠፉት ህይወትና ላወደሙት ንብረት  አገልጋዮችና አሽከሮች የሆኑትን ከፍተኛ የኦህዴድ ካድሬዎችና መሪዎች ጭዳ ለማድረግ መዘጋጀታቸው ቀደም ሲል መገለጹ ይታወሳል።

 

Ø የወያኔ መሪዎች የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም እንዲያስችላቸው በውጭ ሀገራት የማግባቢያ ሥራ  (የሎቢ ሥራ) ለሚሰሩላቸው ኩባንያዎች የአገሪቱን  ሀብት ማዕድኗን እንዲበዘብዙ  መንገዶችን ሲያመቻቹ መቆየታቸው ይታወቃል። ከአፋር ግዛት ከሰመራ የሚመጡ መረጃዎች  እንደሚያመለክቱት ከአስር ዓመት በፊት ለቀድሞ የወያኔ መሪና ጠቅላይ ሚኒስትር  ለመለሰ ዜናዊ ሽልማት የሰጠው ያራ የተባለው የኖርዌይ የማዳበርያ አምራች ድርጅት በአፋር ዳሎል የሚገኘውን የፖታሽ ክምችት እንዲያወጣ ፈቃድ ተሰጥቶታል። ከኖርዌይ ያራ በተጨማሪ አንድ የእንግሊዝ የማዕድን ኩባንያም ይህንኑ የአፋር  ማዕድን እንያወጣ ተፈቅዶለታል። ኢትዮጵያ በከርሰ ምድሯ ያላትን ሃብት የወያኔ መሪዎች ከንግድ ሸሪኮቻቸውና ከባለውለታና አጋር ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ጋር በመሆን እየበዘበዙና በባዕድ ሀገርም ከፍተኛ መጠን ያለው ሀብትና ንብረት እያከማቹ መሆናቸው ይታወቃል። የኖርዌይና የእንግሊዙ ማዕድን አውጭዎች በቅርብ ጊዜ ወደ ማዕድን ቁፋሮ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø ከጎንደር የሚመጡ ሪፖርቶችና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ የጎንደር ሕዝብ የወልቃይት ጠገዴ ነዋሪ ያነሳውን የማንነት ጥያቄ በመደገን ለወያኔ አገዛዝ ያለውን ተቃውሞ ባገኘው አጋጣሚና ሁኔታ እየገለጸ መሆኑ ታውቋል። መጋቢት 18 ቀን 2008 ዓም በጎንደር ከተማ በጎንደር ስታዲዩም ለብሔራዊ ሊግ በጎንደር ከነማና በአዲግራቱ ውልዋሎ ክለብ መሃል የእግር ኳስ ግጥሚያ በሚደረግበት ሰዓት የስታዲየሙ ተመልካች በቦታው መሰብሰቡን እንደ አጋጣሚ በመጠቅም ተቃውሞን ሲያሰማ፤ ብሶቱን ሲገልጽ ቁጣውን ሲያሳይ ውሏል። በዕለቱ በስታዲየሙ የነበረው ተመልካች “የወያኔ ኖር ይለያል ዘንድሮ”፤ “ወልቃት ይመለስ”፤ “አማራ ነን”፤ “የትግራይ የበላይነት ያብቃ”፤ “አፈና ይቁም” የሚሉትን መፈክሮችና ልዩ ልዩ የተቃውሞ መዝሙሮችን ሲያሰሙ ውለዋል። ወያኔ ህዝብ እንዳይሰበሰብና ተቃውሞውን እንዳይገልጽ ቢገድብም በስፖርት ሜዳና በጸሎት ቦታ ሳይቀር ሕዝብ ሲሰባሰብ ብሶቱን መግለጽ መጀምሩ ምናልባት ነገ ተሰባስቦ አደባባይ መውጣቱ የማይቀር ነው የሚሉ ታዛቢዎች አሉ።

 

Ø የወያኔ አጃቢና ሻማ ያዥ የሆኑት የፖሊቲካ ፓርቲ መሪ የተባለት ግለሰቦች ከወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸውን ወያኔ አስታውቋል። ይህ በወያኔ መሪዎች ትዕዛዝ በኃይለማርያም ደሳለኝ ፈጻሚነት የተካሄደው የብሔራዊ መግባባት የተባለለት ስብሰባ ከፕሮፓጋንዳ ወፍጮነት ባለፈ እንደ ስሙና አጀንዳው ምንም የተግባር ምላሽ ያልሰጠና ይልቁንም በወያኔ የምርጫ ድራማ ወቅት ስለሚከፈላቸው የገንዘብ መጠን የተጨነቀ ንግግር ሲያደርጉ መዋላቸው ታውቋል። የወያኔ ፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ግን ለመልካም አስተዳድር ችግር ብሔራዊ መግባባት ዋና መሳሪያ ስለሆነ  ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር ውይይት ተደረገ  ቀጥሎ ከሕዝብ ጋር ይሆናል  በማለት ሲያናፉ ሰንብተዋል። የፓለቲካ ታዛቢዎች  ወያኔ በአራቱም ማዕዘና የተነሳበትን ተቃውሞና አገዛዙ  በቃን በማለት ሕዝብ እያካሄደ ያለውን የአመጽ እንቅስቃሴ ለማዳካም  አንዴ ይቅርታ ተጠየቀ ሌላ ጊዜ ስለ መግባባት ንግግር ተደረገ በማለት ለማወናበድና ዕድሜ ለማስረዘም የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ይጠቅሳሉ። የወያኔ መሪዎች የሰላምና የዕርቅ ብሩን ከዘጉ ዓመታት ማስቆጠራቸውን ገልጸው በአሁኑ ወቅት የተባለው የብሔራዊ መግባባት ንግግር የተደረገው የወያኔ አጃቢና ሻማ ያዥ ፓርቲዎችን ከቀውሱ ጀርባ የቤት ስራ ሊሰጣቸው ታስቦ መሆኑን ሕዝቡ ይገነዘባል በማለት ተጨማሪ አስተያየት ይሰጣሉ።

 

Ø ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከአፍሪካ ወደ አውሮፓ አገሮች ለመሰደድ ሙክራ ሲያደርጉ የነበሩት 600 ስደተኞች በየሊቢያ የወደብ ጠባቂዎች የታገዱ መሆናቸው ታወቀ። ስደተኞቹ ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የመጡ ሲሆን ህጻናትና እርጉዝ ሴቶች እንደሚገኙባችውም ተነግሯል።  መቀመጫው ትሪፖሊ የሆነውና የዓለም አቀፍ እውቅና ባያገኝም ራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው አካል ስር የሚገኘው   የሊቢያ ባህር ኃይል ስደተኞችን ያገተው ከትሪፖሊ ምዕራብ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሳብራታ በምትባለው ወደብ ነው። ሊቢያ ውስጥ ከ800 000 በላይ ስደተኞች እንደሚገኙ ቀደም ብሎ በፈረንሳዩ የመከላከያ ሚኒስትር የተሰጠውን መረጃ  የሊቢያ ባለስልጣኖች የተጋነነ ነው በማለት ውድቅ ቢያደርጉትም ባለፉት ሶስት ዓመታ እስከ 300 000 ስደተኞች ሊቢያ መግባታቸውን አልካዱም። ከአምስት አመት በፊት የጋዳፊ መንግስት ተገርስሶ ሊቢያ ውስጥ ቀውስ ከተፈጠረ ጀምሮ ከፍተኛ ገንዘብ በማስከፈል ስደተኞች ከቦታ ወደ ቦታ የማስተላለፍ ስራ በጣም አትራፊ የሆነ  የንግድ ስራ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ።፡

 

Ø የሩዋንዳ መንግስት ያለፈበትን የሰው እልቂት ወደ ብሩንዲ በመላክ የአገሪቱ ዜጎች እርስ በርስ እንዲጫረሱ በማድረግ ላይ ነው በማለት የብሩንዲ የገዥው ፓርቲ መሪ  ከሰሱ። የፓርቲው ፕሬዚዳንት ፓስካል  ንያቤንዳ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ለተባለው የዜና ወኪል በጽሁፍ በላኩት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት የብሩንዲን ዜጎች በወታደራዊ ትምህርት አሰልጥነው ወንድሞቻቸውን እንዲገድሉ ወደ ብሩንዲ ይልካሉ የሚል ክስ ከሰነዘሩ በኋላ የአውሮፓ አገሮችም መሳሪያና ገንዘብ በመስጠት እየተባበሩ ነው ብለዋል። በቅርቡ በሩዋንዳ እና በብሩንዲ መንግስታት መካከል የእርቅ ውይይት እንዲካሄድ ግፊት ስታደርግ የነበረችው የካቶሊክ ቤተክርሲያን ከወቀሳው ያልዳነች ስትሆን የፓርቲው መሪ አሸባሪዎች የሚሏቸውን የአማጽያንን ዓላማ በማራገብ የሀሰት ዜና ያስፋፋሉ በማለት በውጭ ጋዜጠኞች ላይም የከረረ ሂስ ሰንዝረዋል። በብሩንዲ የፖሊቲካ ቀውስ መከሰት ከጀመረ ወደ አንድ ዓመት ገደማ እየተጠጋ ሲሆን እየተካሄደ ባለው የእርስ በርስ ግጭት  ከ400 ሰዎች በላይ መገደላቸውና ከ250 000 ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሰደዳቸው አይዘነጋም።

 

Ø የጣሊያን ዜጋ የሆነውን ወጣት ገዳዮች ናቸው ተብለው የተጠሩ የቡድን አባሎች በአሰሳ ተገድለዋል በማለት የግብጽ መንግስት መግለጫ መስጠቱ የሚታወቅ ሲሆን በወጣቱ ግድያ ላይ የግብጽ ባለስልጣኖች ያሉበት መሆኑን የሚጠረጥረው የጣሊያን መንግስት የግብጽ ባለስልጣኖችን መግለጫ ያልተቀበለ ከመሆኑም ሌላ በጉዳዩ ላይ የጣሊያን መርማሪዎች በሚገኙበት የምርመራ ቡድን ተመስርቶ ምርመራው እንዲቀጥል የጠየቀ መሆኑ ታውቋል። የግብጽ መንግስት በጣሊያን መንግስት ግፊት ወንጀለኞቹ ተገድለዋል ካለ በኋላ ምርመራው የቀጠለ መሆኑን እንዲሁም ሌሎች ተባባሪዎች መያዛቸውን የሚገልጽ  መግለጫ ቢሰጥም የጣሊያን መርማሪዎች ምርመራ ውስጥ ይሳተፉ ለሚለው ጥያቄ ገና መልስ ያልሰጠ መሆኑ ተነግሯል።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በአይቮሪ ኮስት የወደብ መዝናኚያ ከተማ ለ19 ሰዎች መገደል ምክንያት የሆነው የሽብር ጥቃት ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ ሁለት የእስላማውያን አክራሪ ድርጅት አባላት በማሊ ውስጥ የተያዙ መሆናቸውን የማሊ የስለላና የጸጥታ ክፍል ባለስልጣኖች ገለጸዋል። ከተያዙት መካከል አንደኛው ሾፌር በመሆን  ጥቃቱን ለፈጸሙት ግለሰቦች የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጠ ሲሆን   ሁለተኛው ደግሞ የእርሱ ተባባሪ መሆኑ ተነግሯል። ግንቦት አራት ቀን ግራንድ ባሳም በተባለው የአይቮሪ ኮስት የቱሪስት መዝናኚያ ቦታ ላይ የተካሄደው የሽብር ጥቃት በጥቂት ወራት ውስጥ ከተካሄዱት መካከል ሶስተኛው ሲሆን  በሰሜን አፍሪካ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን መውሰዱ ይታወቃል።  

 

 

መጋቢት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓ.ም.  በግብጽ በሲና ባህረ ሰላጤ አካባቢ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ 60 የታጠቁ ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውን አንድ የመንግስቱ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ገልጿል። የግብጽ መንግስት ወታደራዊ ጸረ ሽብር ቡድን አባላት በሰሜን ሲና ከራፋህ እና ከሼክ ዛይድ ከተሞች በስተደቡብ በሚገኘው ቦታ ላይ ባካሄዱት አሰሳ 60 አማጽያንን ከመግደላቸውና 40 ያህሉን ደግሞ ከማቁሰላቸው በላይ 27 የተላያዩ መኪናዎችን ያቃጠሉ መሆናቸውን ቃል አቀባዩ ጨምሮ ገልጿል። በመንግስቱ ቃል አቀባይ የተሰጠው መግለጫ በሌላ ሶስተኛ ወገን አልተረጋገጠም። በሕዝብ ምርጫ ወደ ስልጣን መጥተው የነበሩት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሞርሲ ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ እስላማውያን አክራሪዎች በሲና አካባቢ ጥቃት ሲሰነዝሩ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን ባለፈው ሳምንት ውስጥ ከአይሲስ ጋር ግኝኑነት ያለው ቡድን  ኤል አሪሽ በተባለው ከተማ በአንድ መፈታሻ ጣቢያ ላይ ባካሄደው ጥቃት 15 ፖሊሶች መግደሉ  ይታወሳል።

 

Ø ቱኒዚያ በሊቢያ ወሰን ሰርጎ ገቦችን ለመከላከል እንዲያስችል  ለመትከል ለታሰበው የስለላና የመቃኚያ የኢሌክቶኒክ መሳሪያ ወጭ  የአሜሪካ ለመክፈል የተስማማ መሆኑ  በቱኒዚያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ገልጿል።  ፕሮጀክቱ የሚፈጀው 24.9 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ቢ.ቲ.ፒ እና አይኮም በሚል ምህጻረ ቃል ለሚጠሩት የአሜሪካ ኩባንያዎች ኮንትራቱ የተሰጠ መሆኑ ተነግሯል። የቱኒዚያ መንግስት በወሰኑ አካባቢ 200 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው የመከላከያ ግምብ የገነባ ሲሆን የኤሌክቶኒክ መሳሪያው የቅኝቱንና የስልላውን ተግባር በማጠናከር ከሊቢያ ወደ ቱኒዚያ የሚደረገውን ዝውውር ከባድ ያደርገዋል ተብሎ  ይገመታል። ባለፉት ወራት ከሊቢያ ወደ ቱኒዚያ ስርገው የገቡ አሸባሪዎች በተደጋጋሚ ጥቃት ሰንዝረው ጉዳት ማድረሳችው ይታወቃል።

 

Ø ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም በኮንጎ የሚገኘው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይልና የኮንጎ መንግስት ወታደራዊ ተቋም በመተባበር   በአገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል  ኤዲ ዔፍ በሚለው የእንግሊዘኛ ምህጻር ቃል የሚጠራው የዩጋንዳ አማጽያን ቡድን ይዞታ ላይ  በሄሊክብተሮች አማካይነት ያካሄዱት ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አንድ የተመድ ባለስልጣን ገልጸዋል። አላይድ ዴሞክራቲ ፎርስስ (ዔዲ አዔፍ) allied democratic forces (ADF) እየተባለ የሚጠራው ቡድን በዩጋንዳው በሙሰቨኒ መንግስት ላይ አምጾ ውጊያ ማካሄድ ከጀመረ ከ20 በላይ ሲሆነው በምስራቅ ኮንጎ በሚኖሩ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሽብር ተግባር ፈጽሟል የሚሉ ተደጋጋሚ ክሶች ሲቀርቡበት እንደቆዩ ይታወቃል። የምስራቅ ኮንጎ አካባቢ የተለያዩ ብሔረሰቦች የሚኖሩበት ከመሆኑም በላይ አካባቢው በንጥረ ነገሮች ሀብታም ስለሆነ ቦታውን ለመቆጣጠር በልዩ ልዩ ክፍሎች ተደጋጋሚ ጦርነቶች ሲካሄዱበት ቆይተዋል። የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል እና የኮንጎ መንግስት የጸጥታ ኃይሎች በአርቡ ዕለት ወታደራዊ ጥቃት ያደረሱት ጉዳት በዝርዝር ባይታወቅም በርካታ የአምጻያን ኃይሎች ቦታውን ለቀው እንደሸሹ ተገልጿል።

 

Ø በየመን ደቡባዊ ከተማ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም በኤደን አይሲስ የተባለው እስላማዊው አሸባሪ ቡድን አባላት በሶስት የተለያዩ ቦታዎች ላይ አጥፍቶ ጠፊ በመሆን ባፈነዷቸው ቦምቦች ከ26 ሰዎች በላይ መሞታቸውና በርከት ያሉት መቁሰላቸው ተነገረ። አንድ ፈንጅ የተጠመደበት አምቡላንስ መኪና በከተማይቱ ሰሜን ምዕራብ አካባቢ የመፈተሻ ጣቢያ ሲደርስ በመፈንዳቱ 14 ወታደሮች የተገደሉ ሲሆን በሌሎች ሁለት የመፈተሻ ጣቢያዎች የፈነዱት ቦምቦችም ጉዳት አድርሰዋል። አይሲስ ኢላማ ያደረገው በሳኡዲ በሚመራው የጥምር ኃይል ወታደሮች ላይ መሆኑ ግልጽ ሲሆን ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል ምን ያህሉ የጥምሩ አካል አባላት  እንደሆኑ አልታወቀም። በሁቲ አማጽያንና በሳኡዲ በሚመራው ጥምር ኃይል መካከል የተደረገው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት በስራ ላይ በመዋሉ ላለፈው አንድ ወር በከተማዋ ጸጥታ ነግሶ የነበረ መሆኑ ሲታወቅ  በአርብ ዕለቱ የአይሲስ ጥቃት ጸጥታው ሊደፈርስ ይችላል የሚል ስጋት ሰፍኗል።   

 

 

መጋቢት 25 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ያነሳውን የማንነትና የመብት ጥያቄ የወያኔ መሪዎች ሚሊሺውንና የፖሊስ ኃይሉን ከትግራይ በማስመጣትና ወታደሩን በማስፈር ምላሽ በመስጠት አስፈራርተውና አሸብረው የታላቋ ትግራይን ህልውና እውን ለማድረግ የጀመሩት ሙከራ አሁንም ከሕዝብ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደገጠመውና ውጥረቱ እየከፋና ግጭቶችም እየበረከቱ መምጣታቸው ከአካባቢው የሚመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። የወያኔ መሪዎች  የሕዝብን ተቃውሞ በኃይል ለማብረድ ባደረጉት ሙከራ የሀገር ሽማግሌዎችንና ቄሶችን በመላክ የተዘጉ መንገዶች ለጊዜው ቢያስከፍቱም ሕዝቡን አሁንም ጥያቄያቸው ካልተመለሰ የታስሩት ካልተፈቱና መድረሻቸው የጠፋው ካልታወቀ ትግሉን የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል እየገለጸ ይገኛል። የወልቃይት ሕዝብ ማንነቱ ሲዘረፉ ልጆቹ ሲገደሉና ሲታስሩ ድምጽ አልባ የነበሩት የሀገር ሽማግሌዎችና የቤተ ክህነት መሪዎች ዛሬ ወያኔ በሕዝባዊ ተቃውሞ ተወጥሮ ሲያዝ ደፋ ቀና ማለታቸው በእርግጥ ሽምግልና ነው ወይንስ የሕዝብን ትግል ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ለማልበስ በማለት የሚጠይቁ በርካታ ናቸው።

 

Ø በምዕራብ ወለጋ በመንዲ ከተማ አንድ የገበያ ማዕከል በእሳት አደጋ እንዲወድም ከተደረገ ወዲህ ሕዝባዊ ተቃውሞ በማገርሸቱ የወያኔ ፖሊሶች የመንዲ ከተማ ተማሪዎችንና መምህራንን አስረው ወደ አልታወቀ ሰፈራ እንደወስዷቸው ታውቋል። በገበያው ቦታ ቃጠሎ የወያኔ ሰላዮች እጁ ሙሉ በሙሉ እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን በገበያ ቦታ ሱቅ የነበራቸው ግለሰቦች ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣን በመደገፋቸው ብቻ በበቀል ርምጃ ሱቃቸው እንዲቃጠል መደረጉን የመንዴ ከተማ ሕዝብ የሚስማማበት ሲሆን ከቃጠሎው ማግሰት ወደ አሰሳ የሚወስደውን መንገድ ላይ አምስት ቦታ ዘግተዋል በማለት አስራ ሰባት ተማሪዎችና ምሁራን በወያኔ ፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው ይታወቅ እንጅ የት እንዳታሰሩ የታወቀ ነገር የለም።

 

Ø በመቀሌ የጀመረው የባጃጁ የሥራ ማቆም አድማ አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን የወያኔ አገዛዝ በርካታ የታጠቁ ፖሊሶቹንና ወታደሮችን በከተማ ውስጥ በማስፈር ሕዝብን እያስፈራራና የባጃጅ ሹፌርና ባለንብረቶችንም እያዋካበ እንደሚገኝ ታውቋል። ከመቀሌ ሳንወጣም መቀሌ ውስጥ ከአሪና ጽ/ቤት የተያዙት የአረና የአሠራር አባልና የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ መፈታታቸው ታውቋል። የታሰሩበት ምክንያት በጽ/ቤታቸው አቅራቢያ ቆሻሻ ወረቀት በማቃጠላቸው መሆኑ ተነግሯቸዋል። ብዙ ወገኖች ግን የወረቀት ቃጠሎ ሰብብ እንዲሆነና እስር ለማወከብና ለማስፈራራት ታቅዶ የነበረ መሆኑን ይስማሙበታል።

 

Ø ከአስር ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በድርቅና በረሃብ አደጋ መጠቃታቸው እየተነገረ ባለበትና ከፍተኛ የሆነ የሰዎች ሞትና ዕልቂት እንዳይከሰት የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ በፊት ርብርብ በሚያደርግበት ሰዓትና በሀገር ውስጥ ያለው የእርዳታ እህል መጠን ከሁለት ወር በላይ አያራምድም በሚባልበት ጊዜ በጂቡቲ ወደብ የእርዳታ ስንዴ ማራገፊያ ማጣቱ ተገለጸ። ብሉምበርግ የዜና ወኪል እንደዘገበው ከሆነ 450ሺ ሜትሪክ ቶን ስንዴ የጫኑ 10 የዕቃ መጫኛ መርከቦች ከወደብ መጨናነቅ የተነሳ የእርዳታ ስንዴውን ማራገፍ እንዳልቻሉ ገልጸዋል። መርከቦቹ ወደብ ቢደርሱ እንኳን ለማራግፍ 40 ቀናት እንደሚፈጅ ታውቋል። የእርዳታ ስንዴውን ለመግዛትና ለማጓጓዝ 120 ቀናት ወይም አራት ወራት እንደሚፈጅ የእንግሊዝ ለጋሽ ድርጅት አስታውቋል። የተመድ የምግብና የእርሻ ድርጅት ከ10 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ የእርዳታ ፈላጊ እንዲሆንና 7.9 ሚሊዮን ደግሞ በሴፍቲ ኔት ፕሮግራም ውስጥ እንዳለ ገልጿል። ከወር በፊት ጂቢቲ ወደብ የደረሱ መርከቦች እስከ አሁን የዕርዳታ እህሉን ማራገፉ እንዳልቻሉ ታውቋል። የወያኔ አገዛዝ የኢትዮጵያን ታሪካዊ የባህር በሮችን ለሻዕቢያ አሳልፎ መስጠት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ደህንነትና ልማት ብቻ ሳይሆን ለአደጋ ጊዜ እንዳልብ ሊጠቀምባት አለመቻል አሳዛኝ የታሪክ ክስተት መሆኑን የሚናገሩ ወገኖች አልጠፉም።

 

Ø በልዩልዮ ሰበብና ምክንያት የሕዝብ ገንዘብ መሰብሰብና መዝረፍ መለያ የሆነው ወያኔ በባለተሽከርካሪዎች ላይ ተጨማሪ የግዳጅ ገንዘብ መሰብሰቢያ ዘዴ ጀምሯል። ገንዘብ የሚሰብሰበው የመንገድ ልማት ፈንድ የሚባል ድርጅትን በማቋቋም ሲሆን ዋና ስራው መኪኖች ዓመታዊ ምርመራ ካካሄዱ በኋላ በመኪናው የፊት መስታዋት ላይ የሚለጠፍ ወረቀት መለጠፉ ሲሆን ከዓመታዊ ምርመራ በተጨማሪ ለመንገድ ልማት ፈንድ የቤት ተሽከርካሪዎች 150 ብር እንዲከፍሉ ሲደረገ ትላልቅ የጭነት መኪናዎች ደግሞ 2500 ብር ይከፍላሉ ተብሏል። ወያኔ በሚጀመረው በዚህ አዲስ አሰራር መሠረት ማንኛውንም ተሽከርካሪ ለመንገድ ልማት ፈንድ የግዳጁ ክፍያውን ካልፈጸመና ከደረሰኝ ጋር የሚኪናው መስተዋት ላይ ካላጠፋ መኪናውን ማሽከርከር እንደማይችል ታውቋል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ፍጹም ስግብግብና የማይጠገብ ዘራፊዎች በመሆናችው ብቻ የተለያዩ ምክንያትና ሰበብ በመፍጠር የሌብነት ድርጅት በማቋቋም ዝርፊያ ማካሄድ የተለመደና የዘወትር ተግባራቸው ሆኗል።

Ø ማኅበረ ቅዱሳን ከመጋቢት 15 ቀን እስከ መጋቢት 21 ቀን 2008 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ በኢግዚብሽን ማዕከል ኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮዋን እንጠንቀቅ ድርሻችንን እንወቅ በመሪ ርዕስ ያዘጋጀውን ዐውደ ርዕዩትን በመጨረሻ ሰዓት ላይ በወያኔ ባለሥላጣናት መከልከሉ ታወቀ። ማኅበሩ ቅዱሳን ለምን በመጨረሻ ሰዓት እንደተከለከለ ባይታወቅም የአዲስ አበባ ከተማ ባለሥልጣናት ግን ከበላይ አካል በመጣ ትዕዛዝ ነው በማለት ተናግረዋል። ማኅበሩ የእግዚብሽን አዳራሹን ጊዜያዊ ቁልፍ ተረክቦ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ እንደነበረ ተገልጿል። አንዳንድ ለማኅበረ ቅዱሳን ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደሚናግሩት የኢግዚቢሽኑንና አዳራሽ በመጨረሻ ሰዓት ላይ የከለከለው የእግዚቢሽኑ አዳራሽ ሥራ አስኪያጅ የተባለው ታምራት የተባለ ግለሰብ ሲሆን ከአዲስ አበባ ከተማ ሰላማዊ ሰልፉና ስብሰባ ፈቃድ መጠየቂያ ቢሮ ፈቃድ ካላመጣችሁ በማለት መከልከሉን ይገልጻሉ። ብዙ ምዕመናን ግን የማህበረ ቅዱሳን ዐውደ ርዕዩ መከልከል ዙሪያ የወያኔ ባለሥልጣናትና የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ፓትርያርክ እንጅ እንዳለበትና ኤግዚብሽኑ የታገደው የፈቃድ ጉዳይ ሳይሆን ፖለቲካዊ ነው ይላሉ።፡

 

Ø በቅርቡ በቤልጀየም ከተማ በብራስልስ የደረሱት የቦምብ ፍንዳታዎች ተከትሎ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች በሽብር ተግባር ላይ ተሰማርተዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች  በፖሊስ መያዛችው ተዘግቧል። ሰባት ሰዎች በብራስለልስ የተያዙ ሲሆን ሁለት በጀርመን እና አንድ በፓሪስ የሚገኙ ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል። ማክሰኞ ብራስልስ ከተማ የደረገው የቦምብ ጥቃት ከፈረንሳዩ ጋር ግንኑነት አለ የተባለ ሲሆን ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይካሄዱ ለመከላከል የፖሊስ የምርመራ ተግባር ተጠናሮ የቀጠለ መሆኑ ተዘግቧል። ዛሬ ረፋዱ ላይ ሻየርቤክ በተባለ አካባቢ የቦምብ ፍንዳታ የተሰማ ሲሆን በአሰሳው ወቅት አንድ ሰው መገደሉን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። 

 

Ø ጣሊያናዊውና በካምፕሪጅ ዩኒቨርሲት የፒ ኤች ዲ ተማሪ የነበረው ጁሊያኒ ሬጂኒ ከወራት በፊት   ስለግብጽ የሠራተኛ ማህበር ጉዳይ በአገሪቱ ውስጥ ጥናት በማድረግ እያለ ባልታወቁ ሰዎች ተጠልፎ ከተወሰደ ከጥቂት ቀናት በኋላ  በስለት የተቆራርጠውና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት አስከሬኑ መገኘቱ ይታወቃል። ረቡዕ መጋቢት 15 ቀን 2008  የግብጽ መንስት በካይሮ በአንድ የአፕርትመንት ክፍል ውስጥ በአንድ አሸባሪ ቡድን ላይ ባካሄደው አሰሳ የሟቹን ቦርሳ ያገኘ መሆኑን ተንናግሯል። ፖሊስ አሰሳ የተካሄደበ ቡድኑ የውጭ ሰዎችን በማፈን ስራ ላይ የተሰማራ መሆኑን ገልጾ ከቡድኑ ጋር በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የቡድኑ አባላት በሙሉ መገደላቸው ጨምሮ አስረድቷል። የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች  ጣሊያናዊው ተማሪ ጥናት ሊያካሄድበት የነበረው የግብጽ የሠራተኛ ማህበር ሁኔታ እና የሠራተኛ መብት ጉዳይ በግብጽ ባለስልጣኖች የሚወደድ አለመሆኑን በመጥቀስ ሟቹን ጠልፈው የገደሉት የግብጽ ባለስልጣኖች ናቸው የሚል ግምት  ሲሰጡ መቆየታቸው አይዘነጋም። በአሁኑ ወቅት የግብጽ መንግስት ሟቹን ገድለዋል የተባሉት  የቡድን አባላት መገደላቸውን ቢያስታውቅም እነዚህ በእርግጥ የሟቹ ገዳዮች መሆናቸውን ማረጋገጫ መስጠት ይኖርበታል የሚሉ ክፍሎች በርካታ ናቸው።

 

Ø በናይጄሪያ በሙስና ወንጀል ውስጥ የተሰማሩ ወደ 300 የሚሆኑ የውጭ እና የአገር ውስጥ ኩባንያዎችን እንዲሁም ከፍተኛ ወታደራዊ መሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ ግለሰቦችን ለፍርድ የምታቀርብ መሆኗን አስታውቃለች። ክስ የቀረበባቸው ኩባንያዎችና ግለሰቦች ለዓመታት ቦኮ ሃራምን ለመዋጋት የሚያገልገል መሳሪያ ለመግዛት ከ241 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግምት ያለው  የውሸት ኮንትራክቶች ተፍራርመው የመንግስት ገንዘብ ዘርፈዋል በሚል ነው። እስካሁን ድረስ በተደረገው ምርመራ 35 ሚሊዮን ዶላር የተገኘ መሆኑ ተነግሯል። ኮንትራቱ የተሰጠው በወታደራዊ ጉዳይ ላይ የአገሪቱ ብሔራዊ አማካሪ ጽሕፈት ቤት ሲሆን ያለፈው መንግስት የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ የሆኑት ሚስተር ሳምቦ ዳሱኪ መከሰሳችው ይታወሳል።

 

 

Ø የቀድሞ የቦዚንያ ሰርብ መሪ የነበረውና በ1984 እስከ 1987 ድረስ በነበረው ጦርነት ከፍተኛ የጦር ወንጀል ፈጽሟል የተባለው ራዶቫን ካራድዚክ ለፈጸመው ወንጀል የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት የአርባ አመት እስራት የፈረደበት መሆኑ ተነግሯል። ከቀረበት 11 ክሶች መካከል በ10 ሩ ጥፋተኛ ነው በማለት ፍርድ ቤት የፈረደበት ሲሆን ግለሰቡ ግን ጥፋተኛ አይደለሁም ብሎ ተከላክሏል። ካራድዚክ ሳብርኒካ በተባለችው ግዛት በጅምላ ለተገደሉት 7000 የሚሆኑ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና በሳራይቮ ለተገደሉት 12 ሺ ሰዎች ተጠያቂ ነው በማለት ፍርድ ቤቱ የበየነውን ውሳኔ በመቃወም የተከላከለ ሲሆን ተፈጸሙ የተባሉት ወንጀሎች በሙሉ በተለያዩ ስነምግባር በሌላቸው ግለሰቦች የተፈጸሙ ናቸው እንጅ እርሱ በሚመራው ወታደራዊ ተቋም የተወሰዱ አለመሆናቸውን በመጥቀስ አስተባብሏል። የፍርዱ ሂደት ከስምንት ዓመት በላይ የፈጀ ሲሆን የካራድዚክ ጠበቃ ይግባኝ እንደሚል አስታውቋል።፡የቦዝኒያ ስርብ መሪ ሚሎራድ ዶዲክ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ያወገዙ ሲሆን የስርብያን ሕዝብ ተጠያቂ የሚያደርጉት የምዕራብ ኃይሎች በሰርቢያ ላይ ላዘነቡት የአየር ጥቃትና ለጨረሱት ሕዝብ ተጠያቂዎች ናቸው ብለዋል።  

በተያያዘ ዜና ከጥቂት ዓመታት በፊት በቲምበክቱ የሚገኘውን ታሪካዊ ቦታዎች በማፍረስ ወንጀል ተከሶ በምርመራ ላይ የነበረው አህመድ አልፋኪ አል ማህዲ የተባለው ግለሰብ ለሰራቸው ወንጀሎች በቂ ማረጋገጫ በመገኘታቸው በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ላይ  ይቀርባል የተባለ ሲሆን ጥፋተኛ መሆኑን ለመግለጽ ፈቃደኛ ነው ተብሏል። ቀደም ብሎ በማስተማር ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የአርባ ዓመቱ አልማህዲ አንሳር ዳይን የሚባለው የአክራሪ ቡድን አባል የነበረ ሲሆን የእስልምናን ህግ በኃይል ተግባራዊ ለማድረግ ከሚንቀሳቀሱ ጥቂት ግለሰቦች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል።  

 

 

 

መጋቢት 15 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø በቅርቡ በሞዛምቢክ ወደብ ተገኝተው ወደ አውስትራሊያ ለምርመራ የተላኩት ሁለት የአውሮፕላን ስብርባሪ አካሎች ከሁለት አመት በፊት በህንድ ውቅያኖስ  በአየር ላይ እንዳለ የጠፋው የማሊዚያ ቦይንግ 777 አውሮፕላን አካል ሳይሆን አይቀርም በማለት  መርማሪዎች ግምታቸውን የሰጡ መሆናቸውን የአውስትራሊያው የትራንስፖርት ሚኒስትር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል። መርማሪዎቹ ባገኙት የምርመራ ውጤት የስብርባሪዎቹ ወርድና ስፋት እንዲሁም የተሰሩበት ንጥረ ነገር እና  የአሰራራቸው ሁኔታ ከጠፋው አውሮፕላን ጋር የሚገጣጠም መሆኑን ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት ከአፍሪካ አጠገብ ከምትገኘው ከሪዩኒየን ደሴት የተገኘ ሌላ የአውሮፕላን አካልስብርባሪ የጠፋው የማሌዚያ  አውሮፕላን አካል ነው ተብሎ መረጋገጡ ይታወሳል። በቅርቡ የተገኙት ስብርባሪዎች ከጠፋው አውሮፕላን ጋር አካል ጋር መመሳሰላቸው አውሮፕላኑ በህንድ ውቅያኖስ ላይ ወድቋል የሚለውን ግምት እውነተኛነት የሚያረጋግጥ ቢሆንም አውሮፕላኑ በምን ምክንያት ወደቀ የሚለውን ጥያቄ ግን ሊመልስ አይችልም ተብሏል።  

 

Ø አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣን ረቡዕ መጋቢት 25 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ሞሮኮ በምዕራብ ሳህራ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎች ከአገሪቱ እንዲወጡ ያስተላለፈችውን ትዕዛዝ ካልቀለበሰች የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል የሚዘጋ መሆኑ አስታውቀዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ የጸጥታው ምክር ቤት አንድ ዓይነት እርምጃ እንዲወስድ ይጠይቃሉም ተብሏል። ሞሮኮ ቀደም ብሎ የተመድ ዋና ጸሐፊ ስለምዕራብ ሳህራ የተናገሩትን በመቃወም 84 የሚሆኑ የዓለም አቀፍ የሲቪል ሰራተኞች ከምዕራብ ሳህራ እንዲወጡ ያዘዘች ስትሆን የራሷንም የወታደራዊ አገኛኝ ቢሮን መዝጋቷ ይታወሳል። ቀደም ብሎ የስፔን ቅኝ ግዛት የነበረችውን ምዕራብ ሳህራን በ1967 ዓም ግዛቴ ነው በማለት ወረራ በማካሄዷ ፖሊሳሪዮ የተባለው ነጻ አውጭ ድርጅት ለረጅም ዓመታት  ውጊያ ማካሄዱና በ1983 ዓም በተመድ አማካይነት ውጊያው ቆሞ የአገሪቱ የወደፊት እድል በውሳኔ ሕዝብ እስኪወሰን ድረስ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል በአገሪቱ ውስጥ መሰየሙ ይታወቃል። በውሳኔ ሕዝቡ ማን መሳተፍ አለበት በሚለው ላይ ስምምነት ባለመደረሱ እስካሁን ድረስ ሊካሄድ አልቻለም። በአሁኑ ወቅት የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ በመከፋፈሉ አንድ ዓይነት ውሳኔ መድረስ ያልቻለ መሆኑ ተነግሯል። እንደፈረንሳይ የመሳሰሉት አገሮች ሞሮኮን ሲደግፉ ሌሎች የተቃወሙ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø ባለፈው እሁድ በሴኒጋል በተካሄደው ምርጫ የቀረበውን የሕገ መንግስት ማሻሻያ መራጮች ያጸደቁት መሆኑ ተገልጿል። የቀረበው ማሻሻያ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆኖ የሚመረጠው ግለስብ የስልጣን ዘመኑ ከሰባት ወደ አምስት ዓመት እንዲቀንስ የሚያደርግ ሲሆን ከመራጩ 62.7 የሚሆነው ስለደገፈው ማሻሻያው በስራ ላይ ይውላል ተብሏል። በእሁድ ዕለት ምርጫ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የሄደው ሰው ቁጥር ድምፅ መስጠት ከሚችለው 38 ከመቶ የሚሆነው ብቻ ነው። አዲሱ የሕገ መንግስት ማሻሻያ በተግባር የሚወለው የአሁኑ ፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን ሲያልቅ ማለትም ከሶስት ዓመት በኋላ መሆኑ ተነግሯል። የአሁኑ ፕሬዚዳንት የህገ መንግስቱን ማሻሻያ በውሳኔ ሕዝብ እንዲጸድቅ ያደረጉት ለሌሎች አፍርካ አገሮች አርአያ ለመሆን ነው በማለት የተናገሩ ከመሆኑም በላይ ጊዜው ከራሳቸው የስልጣን ዘመን እንዲጀመር ያደረጉት ሙከራ የሕገ መንግስቱ ፍርድ ቤት የሻረው መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø ዛሬ መጋቢት 15 ቀን 2008 ዓም ሻርም ኤል ሼክ በተባለው የግብጽ የወደብ የመዝናኚያ ከተማ 27 የሚሆኑ የአረብ እና የአፍሪካ አገሮች የመከላከያ ሚኒስትሮች ስብስባ የተጀመረ መሆኑ ተገልጿል። ስብሰባው ለሁለት ቀናት ያህል የሚቆይስ ሲሆን በጸረሽብረተኛነት እና በወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ትብብር ስለሚደረግበት ጉዳይ ይነጋገራል ተብሎ ይጠበቃል። የሳህልና የሳህራ አገሮች በየጊዜው በሽብረተኛነት ክፉኛ የተጠቁ ሲሆን ግብጽም በአክራሪ ኃይሎች ስትጠቃ ቆይታለች። ስብሰባው ምን ዓይነት ውሳኔ እንደሚያስተልፍ እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።   

 

 

 

መጋቢት 14 ቀን 2005

 

Ø የአዲስ አበባን አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ለመጠቅለል ያወጣውን የማስተር ፕላን እቅድ በመቃወም በመላ ኢትዮጵያ ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ተቀሰቀሰና በዚሁ ምክንያት ከ 300 በላይ ዜጎች ተገድለው በሺህ የሚቆጠሩ ከታሰሩና ከተደበደቡ በኋላ የወያኔ መሪዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው በኩል ይቅርታ ይጠይቁ እንጅ ለሕዝባዊ ተቃውሞ የወያኔው ኦህዴድ መካከለኛ ሹማንትና ካድሬዎች ተጠያቂ መሆናቸውን ኦህዴድ የአምስት ቀን ስብሰባ ከጨረሰ በኋላ ማስታወቁ ይታወቃል። በሰሜን ጎንደር የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ላነሳው የማነነት ጥያቄም ወያኔ ከትግራይ ሚሊሺያውንና ፖሊሱን እንዲሁም የጦር ኃይሉን ወደ አካባቢው በመላክ ትግሉን ለማኮላሸት ያደርገው ሙከራ ስላልተሳካለት ለወልቃይቱ ችግር ተጠያቂው በራሱ አምሳል የፈጠረው የወያኔው ብአዴን ነው በማለት የብአዴን መካከለኛ አመራሮቹንና ከፍተኛ ካድሬዎቹን በትግሪኛ ተናጋሪ የህወሃት አባላት ለመተካት ማቀዱ ታውቋል። የወያኔ መሪዎች ብአዴንን በአማርኛ ተናጋሪ ትግሬዎች በመምራት የታላቋ ትግራይ ህልማቸውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ነው።

 

Ø የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የሚዘገበው ሐራ ተዋህዶ በጎጃም ክፍለ ሀገር በጣና ሐይቅ ላይ በደቀ እስጢፋኖስ ገዳም ላይ የዘረፋ አደጋ እያንጃበበ መሆኑን ጠቁሞ የጉዳዩ አሳሳቢነት ባህር ዳር ለሚገኙ የወያኔ ባለሥልጣናት ቢገለጽም እስከ አሁን የወሰዱት እርምጃ እንደሌለ  ገልጿል። ሐራ ተዋህዶ እንዳብራራው ካለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ ማንነታቸው ያልታወቀ ዘራፊዎች በጀልባ ወደ ገዳሙ መምጣትና መመለሳቸውን ገልጾ ከመጋቢት በ12 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ግን በርካታ ጀልባዎች በዓሳ አጥማጅነት ስም በሚገባ ታጥቀው በአካባቢው እንደሚገኙ አስታውቋል። ከዚህ ቀደም በገዳሙ ያሉ የመነኮሳትን ልብስ በመልበስ ተመሳስለው ወደ ገዳሙ ለመግባት ሙከራ ያደርጉ ዘራፊዎችን የገዳሙ አባቶች እንዳስቆማቸው ይታወሳል። ገንዘብ የማይጠቅማቸው የወያኔ  መሪዎች የኢትዮጵያን ሁሉ ውርስና ቅርስ የሆኑ ታሪካዊ ሀብቶችን ለመሸጥ ለዘረፋ መሰማራታቸው ታውቆ ዜጎች ሁሉ ዘብ እንዲቆሙና ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ይጠይቃሉ።

 

Ø  በወያኔው የፖለቲካ ፍርድ ቤት የሚመላለሰው የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው ወጣት ዮናታን ተስፋዬ በትናንትናው ዕለት ፍርድ ቤት ቢቀርብም የወያኔው አገልጋይ የሆነው የፍርድ ተቋም  ፖሊስ ለምርመራ የ28 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው የጠየቀውን ጥያቄ ተቀብሎ ወደ ወህኒ መልሶታል። ወጣት ዮናታን ተስፋዬ ባለፉት ሶስት ወራት ያለ ምንም ክስና ወንጀል በወያኔ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኝ የታወቀ ሲሆን በናንትናው ዕለት ከወህኒ ቤት የወጣበትን መኪና መስኮት ለመዝጋት ሙከራ ያደረገውን ፖሊስ በመቃወሙ በፖሊስ ድብደባ እንደደረሰብት ታውቋል። በሕግ ጠለላ ስር አለ የተባለ ህጋዊ እስረኛን በሕዝብ ፊት በደበደበው ፖሊስ ላይ   የተወሰደ እርምጃ የለም።

 

 

Ø በምዕራብ ወለጋ በመንዲ ከተማ የሚገኘው የገበያ ቦታ የእሳት አደጋ እንደደረሰበት ታውቋል። የአካባቢው የወያኔ ባለሥልጣኖች የእሳት አደጋውን ማን እንደለኮሰውና በምን ምክንያት እንደሆነ የተሰጠ ዝርዝር መግለጫ ባይኖርም በአካባቢው የተነሳውን ጸረ ወያኔ ሕዝባዊ ተቃውሞ ነጋዴኦዎቹናና ባለሱቆቹ ይደግፋሉ በማለት ብቻ ለበቀል በወያኔ ሰላዮች የተነሳ የእሳት ቃጠሎ መሆኑን ብዙዎቹ ይጠራጠራሉ።

 

Ø የኢትዮጵያ የልማት ባንክ ለወያኔ መሪዎችና የጦር አለቆች በብድር ስም በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ካዘራፈ ወዲህ ለሰፋፊ እርሻዎች ብድር  እንዳይሰጡ ማዘዙን የባንኩ ባለሙያዎች ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በጋምቤላና በኦሞ ሸለቆ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን የተቀራመቱትን የወያኔ መሪዎችና የጦር አለቆች ለልማት ማካሄጃ ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በብድር ይውሰዱ እንጅ አንዳቸውም በመሬቱ ላይ የስሩት ልማት እንደሌላና የተበድሩትን ገንዘብም  እንዳልከፈሉ ታውቋል። ባንኩ በአሁኑ ጊዜ ለልማት የሚያበድረው ገንዘብ ዕጥረት እየገጠመው በመሆኑ ለሰፋፊ እርሻዎች የሚሰጠውን ብድር ያቆመ መሆኑን ቢገልጽም  ከዚህ በፊት ገንዘብ ተበድረው ያልከፈሉትን የወያኔን መሪዎች የጦር አለቆች ለማሰከፈል ስለሚወሰደው እርምጃ የተናገረው ነገር የለም።

በተመሳሳይ ዜናም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ካፒታል እጅግ አነስተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ የወያኔ ፓርላማ የልማት ባንኩን ካፒታል ለማሳደግ ለወያኔ ፕርላማ አዲስ ህግ እንዲቀርብና የባንኩን ካፒታል ለማሳደግ አገዛዙ የመድግመው ገንዘብ ስለሌለው የቦንድ ሽያጭ እንዲያደርግ ወስኗል። ይሁን እንጅ ቦንዱ ለሀገር ውስጥ ለሀገር ውጭ ቁርጥ ያለ አቋም አልወሰደም። 

                                               

Ø በሕዝብ መከራ ስቃይ የግል ደስታና ምኞት ብቻ ሳይሆን ጥቅም መሰብሰብ መለያቸው የሆነው የወያኔ መሪዎች በአነስተኛ የጉሊት የንግድ ስራና በዝቅተኛ የኑሮ ደርጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ከጉሊት ንግድ ማባረሩ ታወቀ። በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ሽሮ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለዓመታት በጉሊት ንግድ ይተዳድሩ የነበሩ ነዋሪዎች ያለ ምንም ካሳና ተለዋጭ ቦታ የጉሊት ንግድ ቦታቸው ለባለ ጊዜ ባለሀብቶች ተሰቶባቸው ተባረዋል። የጉሊት ነጋዴዎቹ ሌላ ቦታ ሄደው መስራት እንደማይችሉ እየታወቀ በግፋና በማን አለብኝነት የጎሊት ገበያቸው ለባለጊዜ ሀብታሞች መሰጠቱ ዬያኔ መሪዎች ገንዘብ ካዩ ደሃ ማየት የማይፈልጉ የሚዘጥ የሚለወጥ ከሆነ ምንም ነገርን ገበያ ከማውጣት የማይመለሱ ሞራል ስነ ምግባር የሌላችው አልጠግባ ባይ ስግብግብ መሆናችውን አሳይተዋል።

 

Ø ትግራይ ውስጥ በመቀሌ ከተማ የባጃጅ ሹፌሮች የትግራይ ገዥዎችና የከተማው ባለሥልጣኖች ያወጡትን አዲስ የባጃጅ ሕግ በመቃወም የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸው ታውቋል። አዲሱ ሕግ ባጃጆች እንደ ታክሲዎች ታፔላ አበጅታችሁ መሰማራት አለባችሁ የሚለውን ሕግ በመቃወም ነው። በዚህ የሥራ ማቆም አድማ በመቀሌ ያሉ 2500 ባጃጆች ተሳታፊ ሆነዋል።

 

 

Ø እስካሁን በተሰጠው የፖሊስ መግለጫ ትናንት መጋቢት 13 ቀን 2008 ዓም በቤልጅየም ዋና ከተማ በብራስልስ በአውሮፕላን ማረፊያውና በከተማው ባቡር ጣቢያ በፈነዱት ቦምቦች በጠቅላላው 34 ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውና ከ250 በላይ የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸው ተገልጿል። በደረሰው አደጋ የሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የሀዘን ቀናት እንዲሆኑ ባለስልጣኖች ያዘዙ ሲሆን በዛሬው ቀንም እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር እኩለ ቀን ላይ በአገሪቱ በሙሉ የአንድ ደቂቃ የጸጥታ ሀዘን ተደርጓል።  ዛፈንተም በተባለው አውሮፕላን ጣቢያ ከሁለት ጓደኞቹ ጋር በመሆን ሊያፈነዳ ያቀደውን ቦምብ በጋሪ ሲጎትት ምስሉ በጣቢያው የጸጥታ ካሜራ የተቀዳውና ቦምቡ ባለመፈንዳቱ አምልጦ የነበረው ግለሰብ ዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2008 ዓም   በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል። ግለሰቡ ዋና የቦምብ ሠራተኛ ነው የተባለ ሲሆን እንዲሁም በፓሪሱ የሽብር ተግባር ላይ ተሳትፏል ተብሎ ይጠረጠራል። አይሲስ የተባለው ድርጅት የትናንቱን የቦምብ ጥቃት በማካሄድ በኩል ኃላፊነቱን ወስዶ ተጨማሪ የቦምብ ጥቃቶች ሊካሄዱ እንደሚችሉ አሳውቋል።  የቤልጅየም ራዲዮና ቴሌቪዥን አገልግሎት በትናንትናው ዕለት ቦምብ በማፈንዳት ራሳቸውን ስላጠፉት የባክሩዊ ወንድማማቾች ምንነት በሰፈው አትቷል። ብራሂም ባክሩዊ የተባለው በአውሮፕላን ጣቢያው በተደረገው ጥቃት ራሱን ሲያጠፋ ካሊድ ባክሩዊ የተባለው ደግሞ በማይልቤክ የባቡር ጣቢያ ቦምቡን አፈንድቶ ራሱን ገድሏል። ሁለቱም በፖሊስ የሚታወቁ የወንጀል ሬከርድ ያለባቸው መሆኑ ተነግሯል። ሶስተኛው ተጠርጣሪ ግን እስካሁን ያልተያዘ መሆኑ ታውቋል። የቤልጅየም የጸጥታ ኃላፊዎች ከማክሰኞ ቦምብ ጋር በተያያዘ የሚጠረጠሩ በርካታ ሰዎች ገና ያልተያዙ መሆናቸውን አስታውቀዋል።  

 

Ø የናይጀር ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፉ በምርጫ  ያሸነፉ መሆናቸውን የአገሪቱ የምርጫ ቦርድ ገለጸ። እሁድ መጋቢት 11 ቀን 2008 ዓም በአገሪቱ በተደረገው ምርጫ ድምጽ ሊሰጥ ከሚችለው የናይጀር ዜጋ መካከል 60 ከመቶ የሚሆነው ድምጹን ሰጥቷል የተባለ ሲሆን  የድምጹን 90 ከመቶ በማግኘት ፕሬዚዳንቱ  አሸንፈዋል ተብሏል። ተቃዋሚ ፓርቲዎች በሙሉ በምርጫው ሂደት ያልተካፈሉ ሲሆን ቀደም ሲል በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት የተቃዋሚ ህብረት መሪ ሃማ አማዶ ለህክምና ወደ ፈረንሳይ መወሰዳቸው አይዘናጋም። ተቃዋሚዎቹ 60 ከመቶ የሚሆነው መራጭ በምርጫው ተሳትፏል የተባለው ሀሰት መሆኑን ገልጸው የምርጫውን እንደማይቀበሉ ገልጸዋል። በድጋሚ ተመረጡ የተባሉት ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፉ በቤተመንግስታቸው ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ የናይጀር ዜጎች ወደ አንድነት እንዲመጡ ተማጽነዋል።

 

Ø እሁድ መጋቢት 11 ቀን በኮንጎ የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ  በተገኘው ከፊል ውጤት ላለፉት 32 ዓመታት በስልጣን ላይ የነበሩት የ72 ዓመቱ ሳሶ እንጉሶ አሸንፈዋል ተብሏል። እስከትናንት ማክሰኞ ድረስ  62 ከመቶ የሚሆነው የመራጩ ድምጽ የተቆጠረ መሆኑንና ከዚሁ 67 ከመቶ በማግኘት ፕሬዚዳንቱ አሸናፊ መሆናቸውን የምርጫው ኮሚሽን አስታውቋል። ፕሬዚዳንቱ በሙስናና በጥቅም ትሥስር እንዲሁም መብቶችን በማፈን በኩል በተደጋጋሚ ክሶች የቀረቡባችው  ሲሆን ከአሁኑ ምርጫ ጋር በተያያዘም ተቃዋሚዎች የምርጫውን ውጤት አስቀድመው እንዳያሳውቁ ለመከላከል በሚል ምክንያት በአገሪቱ ውስጥ ያሉት የስልክና የመገናኝ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጋቸው ይታወቃል።   

 

Ø ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 12 ቀን 2008 ዓም ከብሩንዲው ፕሬዚዳንት ጋር ቅርበት እንዳላቸው የሚታወቁ አንድ የብሩንዲ ከፍተኛ የጦር መኮንን በወታደራዊ ተቋም መሥሪያ ቤት ውስጥ እንዳሉ የተገደሉ መሆናችው ተዘግቧል። መኮንንኑ መስርያ ቤታችው ውስጥ በግድግዳ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ እያነበቡ እያሉ ከጀርባቸው በተተኮስ ጥይት ተመተው የተገደሉ ሲሆን ግለሰቡ በቡጁምቡራ አካባቢ የጸጥታ ኃላፊ የነበሩና በመንግስት ደረጃ ሲካሄዱ የነበሩትን የጅምላ ግድያዎች ትዕዛዝ በመስጠት ሲያስተባበሩ የነብሩ ከመሆናቸው በላይ በርካታ እንዲታሰሩና መዳረሻቸው እንዲጠፋ ያደረጉ መሆናቸው ተዘግቧል። ግለሰቡ በወታደራዊ ተቋም ዋና ጽህፈት ቤት ውስጥ መገደላቸው በብሩንዲ ማንም ግለሰብ ደህንነቱ  ሊጠበቅ የማይችል መሆኑን የሚያረጋግጥ ሲሆን  ይህ አስፈሪ ሁኔታ አገሪቱን ከፍተኛ ቀውስ ሁኔታ ይከታታል ተብሎ ይፈራል።      

 

 

 

 

መጋቢት 13 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወያኔ መሪዎች የትግራይ አዋሳኝ የነበሩ ለም መሬቶችን ከወሎና ከጎንደር ወደ ትግራይ ከቀላቀሉ ወዲህ ነዋሪው የማንነት ጥያቄ ማንሳቱና በአማራነት ለመኖርን መምረጡን ለማፈን የወያኔ አገዛዝ በተለያዩ ጊዜ የዘር ማጽዳት ወንጀልን በስልታዊ መንገድ ሲያካሂድ መቆየቱ ይታወሳል።  ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ያነሳውን ጥያቄ በዘረ ፍጅት ለመመለስ የትግራይ ሚሊሺያዎችንና የአገዛዙን ሠራዊት ወደ አካባቢው የላከ መሆኑ ተነግሯል። ወያኔ ውጥረቱን ለማብረደ ያደረገው ሙከራ ባለመሳካቱ ከሶስት ቀን በፊት  የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ትግል አስከባሪ ከሆኑት መካከል  አንዱ ሲሳይ ብርሃኔ በወያኔ ፖሊሶች ታፍኖ ተወስዶ መዳረሻው በመጥፋቱ ምክንያት ውጥረቱ እየጨመረ መጥቷል። የዳንሻ ከተማ በትግራይ ሚሺያዎችና በወያኔ ጦር ስትወረር ሕዝቡም የመኪና መንግደኦችን በመዝጋት ወደ ጎንደርና ሁመራ የሚወስዱ መንገዶችን የዘጋ ሲሆን የታስሩት የሕዝብ ወኪሎች እንዲፈቱ በመጠየቅ የዳንሻን ፖሊስ ጣቢያ መክበቡ ታውቋል። እሁድ ዕለት የተጀመረው ይህ አዲስ ፍጥጫ የዳንሻ ከተማ አጎራባች የሆኑ ወረዳዎችን ሁሉ ያነቃነቀ ሲሆን የወያኔ መሪዎች የሕዝብን መነቃቃት ለማብረድ ሽምግልና የሚሉት ስልትን በማምጣት ሕዝብን ለማዘናጋት እየሞከሩ መሆናቸው ተገልጿል። በዛሬው ዕለት በሽምግልና ጥረት የጎንደር ዳንሻ መንገድ መከፈቱ ተነግሯል።

 

Ø በደቡብ ኢትዮጵያ ገሙ ጎፋ ውስጥ የኮንሶ ሕዝብ የመብትና የማንነት ጥያቄን የወያኔ ቡድን በአግባብና በበቂ ሁኔታ ባለመመለሱ በሕዝብና በገዥዎች መካከል ያለው ክፍተት ከመጨመሩና  ውጥረቱም ከመናሩ በላይ በየጊዜው የሚገደሉና የሚታስሩ ሰዎችም ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ ይታወቃል። የሕዝቡን የመብትና የማንነት ጥያቄ ወያኔ በኃይልና በሽብር ለመግታት ያደረገው መኩራ እስከ አሁን እንዳልሰራና ሕዝብ ጥያቄው በአግባቡ እስኪመለስ ድረስ ትግሉን እየቀጠለ መሆኑ እየታየ ነው። ወያኔ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሳይቀር አስር ቤት በማድረግ በመቶ የሞቆጠሩትን ይሰር እንጅ አሁንም ውጥረቱ ጋብ እንዳላለና የወያኔ መሪዎች ነፍሰ ገዳይ የሆነውንና  አግአዚ የተባለውን ጦራቸውን ወደ ኮንሶ በመላክ ከተማዋን በወታደራዊ ቁጥጥር ስር አድርገዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ሕዝቡ የሚፈልገው ለጥያቄው ሰላማዊ ምላሽ እንጅ እስር፤ የወታደር ጋጋታ  እና የነፍስ ገዳይ ጦር ክምትት እንዳልሆነ በመግለጽ የወያኔ አፋኝና በጨመረ ቁጥር የሕዝብም የመታገል ቁርጠኛነት ይጨምራል በማለት ይናገራሉ።

 

Ø የአዲስ አበባ ሕዝብ እስከ ዛሬ ወሃ በየቀኑ ያገኘ የሚመስል መግለጫ የወያኔ ባለሥልጣኖች ሰሞኑን ሰጥተዋል። በመግለጫው መሠረት የአዲስ አበባ ሕዝብ ውሃ በፈረቃ የሚሰጠው መሆኑን ማስጠንቀቂያ የቀረበ ሲሆን ውሃውን በፈረቃ ለማደል አስገዳጅ የሆነው  ምክንያት በለገዳዲና በድሬ ግድቦች ላይ ግንባታና ጥገና እየተካሄደ በመሆኑ ነው ተብሏል።  የፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ ከወራቶች በፊት የለገዳዲ ግድብ ውሃ እየቀነሰ መምጣቱን ለሕዝብ ያሳወቀ ሲሆን  የወያኔ ባለሥልጣኖች ለውሃው መቀነስ የመብራት ኃይል መዳከም መሆኑን የሚገልጹት ምክንያት ሀሰት መሆኑን ማጋለጡ  ማጋለጡ ይታወሳል። ለዓመታት ምንም ዓይነት ጥገናና ዕድሳት ያልተደረገለት ሲገነባ አርባ አምስት ሚሊዮን ሜትር ኪዮቢክ ውሃ እንዲይዝ ተድርጎ የተሰራው የለገዳዲ ግድብ ዛሬ ላይ አንድ ሚትር ወይንም 62 ሺ ሜትር ኪዩቢክ ሜትር ውሃ መቀነሱ ታውቋል። የወያኔ ባለሥልጣናት ውሃ በፈረቃ ይሆናል ማለታቸው ወትሮም በፈረቃ የነበረው ውሃ ጭራሽኑ ይጠፋል ማለታቸው ካልሆነ በስተቀር ውሃ በፈረቃ ሌትና ቀን ሳይጠበቅ የመጣበት ጊዜ ተረስቷል የሚሉ ነዋሪዎች ብዙ ናቸው።  

 

Ø በተደጋጋሚ ጊዜያት የሚፈጽማቸውን የጅምላ ግድያዎች መሰረት በማድረግ የወያኔ አገዛዝ የሰብዓዊ መብት ረጋጭነት ብቻ ሳይሆን የወንጀለኛ ጥርቅም ቡድን መሆኑን በማጋለጥ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተመልካች ቡድኖች ሪፕርት ሲያቀርቡ መቆየታችው ይታወቃል። በቅርቡም በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞችና ዩኒቨርስቲዎች የተፈጸሙትን ግድያዎች የጅምላ  እስሮችና ድብደባዎች በሚመልከት ሪፖርቶች እየወጡ ባለበትና አጥፍዎቹ ለሕግ እንዲቀርቡ፣ተጎጅዎቹም አስፈላጊው ካሳ እንዲሰጣቸው ወትወታው በጠነከረበት ሰዓት የወያኔ ቡድን መግደል ብቻ ሳይሆን አሳዛኝ ቀልድም መቀለድ እንደሚችል ለዓለም እያሳየ ነው። ወያኔ ለተፈጸሙ ግድያዎችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚያጣራ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ አካል ስላለን ተፈጸሙ የተባሉ የሰብአዊ ጥሰቶችን ይኸው አካል ሊያጣራ ነው በማለት መረራ ቀልድ ተናግሯል። ወያኔ የአዲስ አበባ አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ በማስተር ፕላን ለመጠቅለል የወጣውን ዕቅድ በመቃወም ለሞቱ ለተንገላቱ ለታሰሩና ለተደበዱ ሰዎች የሰብዓዊ መብታቸው መደፈሩን ለማጣራት አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር የተባለው ካድሬ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪና መርማሪ ብሎታል። አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር በወያኔ የምርጫ ቦር ውስጥ ለሰራው ተንኮልና ደባ ወያኔ በኮሚሽነርንት ማዕረግ የሰብአሰኢ መብት ጥሰትን ትመላች ማድረጉ ይታወቃል።

 

Ø ዝርፊያና ስርቆት ይወያኔ መሪዎች መለያ ከሆን ወዲህ በልዩ ልዩ አጋጣሚ በእጃቸው የገባ የሕዝብና የአገር ሀብት መዝረፍና መሰወር እየተለመደ ከመጣ ወዲህ የወያኔ ባለሥልጣኖች ለይስሙላ ምርመራ ይጀምሩ እንጅ ምርመራዎቹ በእነሱ ትዕዛዝ ተድበስብሶ እንዲቀር መደረጉ ይታወቃል። ሰሞኑን ለትግራይ ክፍለ ሀገር ለመስኖ ስራ በማለት የውሃና የኃይል ሚኒስትር የሰጠው 30 ሚሊዮን ብር መዘሩፉ ታውቋል። ገንዘቡ የትግራይ ክፍለ ሀገር የውሃና የግድብ ቢሮ ኃላፊ ጌታቸው የተባለው የትግራዩ ገዥ የፀጋዬ በርሄ የእህት ልጁ እንዳስረቀው ታውቋል። ጌታቸው ለመስኖ ውሃ በማለት ከወጭ ያስመጣቸው  የፕላስቲክ ቱቦዎችን ጥራታቸው የተጠበቁ አለመሆናቸው ሲነቃበት የጠፋ ሲሆን የትግራይ ባለሥልጣናት አጥፊውን ለማግኘት ምንም ዓይነት ጥረት አለማድረጋቸው ከተሰረቀ 30 ሚሊዮን ብር ጀርባ የትግራይ መሪዎች እጅ እንዳለበት አመላካች ሆኗል። ወያኔን ስርቆት ወያኔና ዝርፊያ የማይለያዩና መሳ ለመሳ የሚሄዱ ክስተቶች ሆነዋል።

Ø ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2008 ዓም በቤልጅየም ዋና ከተማ በብራስልስ የአየር ማረፊያ እና የከተማው የባቡር ጣቢያ ላይ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷቸው ቦምቦች ባጠቃላይ 21 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ሌሎች በርካታ መቁሰላቸው ታውቋል። በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ላይ በብራስልስ አውሮፕላን ማረፊያ በመንገደኞች መውጫ ላይ ሁለት ቦምቦች ፈንድተው 11 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ከአንድ ሰዓት በኋላ በአንድ የከተማው  የባቡር ጣቢያ  ላይ  የፈነዳው ቦምብ ደግሞ  ቢያንስ 10 ሰዎች ሰዎችን መግደሉና በርካታዎችን ማቁሰሉ  ተዘግቧል። በዛሬው ቀን ባለስልጣኖች  ሁሉም ዜጎች  በያለቡት  እንዲቆዩ መመሪያ የሰጡ ሲሆን የትራንስፖስት አገልግሎቶች ዝግ ሆነው ውለዋል። ይህ አደጋ የደረሰው በፓሪሱ የሽብር ጥቃት ላይ ተሳትፏል የተባለው ሳላህ አብዱሰላም በቤልጅየም ፖሊሶች ተያዘ በተባለ በአራተኛው ቀን ሲሆን አሸባሪ የበቀል እርምጃ ሊወሰዱ ይችላሉ ከሚል ግምት ፖሲሶች  ከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ሲያደርጉ መሰንበታቸው ታውቋል። የቤልጀየም መንግስት የጸጥታውን ጥበቃ ሁኔታ ወደ አንደኛ ደረጃ ከፍ በማድረግ ሙሉ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ከ2011 እስከ 2015 ዓም ድረስ  2007 ባሉት የአምስት አመት ጊዜ ውስጥ የናይጀሪያ የነዳጅ አምራች ኩባንያ ለመንግስት ማስገባት የነበረበትን 25 ቢሊዮን ዶላር ያላስተላለፈ መሆኑን ጉዳዩን የሚመርምረው አካል ገልጿል። ከአንድ ሳምንት በፊት የናይጀሪያ ኦዲተር ጄኔራል በፈርንጆቹ ዓመት በ2014 ብቻ 16 ቢሊዮን ዶላር ከነዳጅ የተገኘ ገንዘብ የጠፋ መሆኑን አስታውቆ ነበር። በናይጄሪያ ህግ መሰረት የነዳጅ አምራች ኩባንያው የሚያገኘውን ገንዘብ ለመንግስት ማስረከብ ያለበት ሲሆን ይኽም ገንዘብ ከመንግስቱ በጀት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ይታወቃል። ባሁኑ ወቅት የነዳጅ ዋጋ በጣም በመውረዱ ምክንያት የናይጀሪያ መንግስት ከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዳጋጠመው ይነገራል።

 

Ø በቅርቡ በጊኒ ደበባዊ ክፍል በኢቦላ ቫይረስ የተጠቁ አራት ሰዎች መሞታቸው የሚታወቅ ሲሆን  ከበሽተኞቹ ጋር ግንኙነት አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ ቁጥራቸው ከ800 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በልዩ የምርመራ ጣቢያ ለሶስት ሳምንታት እንዲቆዩ የተደረገ መሆኑን በአገሪቱ በሽታውን ለመቋቋም የተፈጠረው አስተባባሪ አካል ቃል አቀባይ ገልጿል።  በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ በሽታው በሶስት የምእራብ አፍሪካ አገሮች ብቻ ከ11 000 ሰዎች በላይ መግደሉ አይዘነጋም።

 

Ø ትናንት መጋቢት 12 ቀን በአልጄሪያ ደቡብ ምስራቅ በሆነውና ከቱኒዚያ ጋር ወሰን ቅርብ ከሆነው ኡኤድ ሱፍ ከተባለ ከተማ አቅራቢያ የጸጥታ ኃያሎች በአሸባሪነት የጠረጠሯቸውን ስድስት ሰዎችን የገደሉ መሆናቸው ገልጸዋል። በርካታ መሳሪዎች እና ጥይቶች እንዲሁም የተለያዩ ወታደራዊ መኪናዎች መማረካቸውም ተገልጿል።

በተመሳሳይ ዜና በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ውስጥ በሚገኘው የአውሮፓ ህብረት ወታደራዊ  ማሰልጠኛ ተቋም እንደ ዋና መስሪያ ቤት በሚጠቅምበት ሆቴል ውስጥ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመው የነበረ ሲሆን ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ግለሰብ ሲገደል ሌሎች ሶስት ግለሰቦች ያመለጡ መሆናቸው ተዘግቧል።  

 

 

መጋቢት 12 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ያነሳውን የማነንት ጥያቄ አስተባብረሃል መርተሃል በማለት አቶ ሲሳይ ብርሃኔ የተባለ ወጣትና የልጆች አባት በወያኔ የደህንነት ኃይሎች ታፍኖ መወሰዱን ተከትሎ በዳንሻ ከተማ ከፍተኛ ውጥረትና ውዝግብ መነሳቱ ተሰምቷል። ከቀናት በፊት ታፍኖ የታሰረው ወጣት ሲሳይ በወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ እንቅስቃሴ ተሳታፊ በመሆኑ የተረዳው ሕዝብ ወደ ዳንሻ ከተማ በመሄድ ወጣቱ እንዲፈታ ሲጠይቁ የወያኔ ባለሥልጣናት ወደ ከተማው ነፍሰ ገዳይ ጦራቸውን በማስገባታቸው ምክንያት ውጥረቱ እየሰፋ የመጣ ሲሆን ወደ ዳንሻ የሚያስገቡ ሆነ የሚያስወጡ መንገዶች የተዘጉ መሆናቸው ታውቋል። የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ትግልን ለማገዝ ከአርማጭሆ ድረስ በዛ ያሉ ሰዎች መጥተው መቀላቀላቸው ተነግሯል። የዳንሻ ከተማ ኃላፊዎች ፖሊስችንና ሚሊሻዎችን ከትግራይ እያስገቡ መሆናቸውና በአንዳንድ የከተማዋ ክፍሎችም የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር ከአካባቢው የተገኝው ዜና ይገልጻል። የወጣት ሲሳይ ብርሃኔ ታፍኖ መወሰድና የወያኔ ጦር  የትግራይ ፖሊስና ሚሊሺያ ወደ ዳንሻ ከተማ መግባት ወትሮም ተወጥሮ የነበረውን የወልቃይትን ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ይበልጥ እንዳጦዘውና እንዳከረረው ተገልጿል።

 

Ø በኢትዮጵያ በአራቱም ማዕዘናት የተነሱት ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ምንጫቸው ዘረኛነትና አምባገነን አገዛዝ መሆኑ ግልጽ ሆኖ እያለ የወያኔ መሪዎች ምንጩ የመልካም አስተዳደር ችግር ነው በማለት ሕዝብን ለማታለል እየሞከሩ ሲሆን ሰሞኑን ደግም ለጠፋው ህይወትና ንብረት ተጠያቂ ላለመሆን ኃላፊነቱን በኦህዴድ ካድሬዎች ላይ እየጫኑ ይገኛሉ። የኦህዴድ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰሞኑን ተፈጽሞ በርካታ ካድሬዎች ተጠያቂ መሆናቸውን አስታውቋል። የኦሮሞ አካባቢዎችና ከተሞች በሙሉ በደብረጽዮን በሚመሩ የደህንነት ሰዎችና በሳሙራ ዩኒስ በሚታዘዙ ወታደሮች ቁጥጥር ስር መውደቁ የሚታወቅ ሲሆን የኦህዴድ ስብሰባ ላይ በመካከለኛ የሥልጣን እርከን ላይ ያሉ ሹመኞችና ካድሬዎች ተጠያቂ ይሆናሉ ተብሏል። የተባሉት  ባለሥልጣናትና ካድሬዎች በቅርቡ ቅጣታቸውን እንደሚቀበሉም ተገልጿል። የወያኔው ኦህዴድ ጠቅላላ ጉባዔ በቅርብ እንደሚጠራ የተነገረ ሲሆን በሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ለጠፋው ህይወት ለወደመው ንብረት ተጠያቂ የተባሉት ላይ የቅጣት እርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። አንደ አንዳንድ የኦህዴድ ምንጮች ከሆነ ጠቅላላ የኦህዴድ  ጉባዔ ወደ እስር ቤት የሚልካቸው መካከልኛ ስልጣን ላይ ያሉ ኃላፊዎችንን ካድረዎች እንደሚኖሩ በእርግጠኛነት በመናገር የወይኔ መሪዎች ግን ከደሙ ንጹህ ተብለው ላጠፉት ህይወት ላወደሙት ንብረት ሳይጠይቁ የአንድ ዘር አምባገነን አገዛዛቸው ለመቀጠል ማሰባቸውን ይገልጻሉ።

 

Ø የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብትና ንብረት የነበሩትን በሙሉ ለንግድ ሸሪኮቻቸውና ለባዕዳን ቸብችበው ከጨረሱ ወዲህ አሁን በአገዛዛችው አስራ አንደኛ ሰዓት ላይ አራት ግዙፍ ድርጅቶችን በጨረታ ለመሸጥ ማቀዳቸው ታውቋል። እነዚህ አራት ድርጅቶች የብሔራዊ ትንባሆ ድርጅት፤ የኢትዮጵያ ቆርኪና ጣሳ ፋብሪካ፤ የባህር ዳር ጨርቃጨርቅ ፋብሪካና የኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ መሆናቸው ተነግሯል። ድርጅቶቹን ወደ ግል ይዞታ ለማዞር በሀራጁ ገብያ ገዥ ካልተገኘ በድርደር ለመሸጥም መታቀዱ ተገልጿል። እንደ ወያኔ መሪዎችና ባለሥልጣናት አባባል ከሆነ ድርጅቶቹን በጨረታ ለመግዛት ፍላጎት የነበራቸው ስምምነት ላይ መድረስ ስላልተቻለ በድርድር ለመሸጥ ሙከራ እየተደረገ ነው። የወያኔ መሪዎች ስልጣን ከያዙበት ጊዜ ጀምሮ ከ 371 በላይ የሀገርና የሕዝብ ንብረት ቸብችበው ከ 24 ቢሊዮን ብር በላይ ማሰባሰባቸው ሲታወቅ ከተሸጡት ውስጥ 28ቱ ገዥዎች አሁንም ድረስ ዕዳ ያለባቸውና የግዥውን ገንዘብ አለመክፈላቸው ወይንም በከፊል ከፍለው ዕዳ ያልጨረሱ መሆናቸው ተገልጿል።  

 

  

Ø እሁድ መጋቢት 11 ቀን 2008 ዓም ከ2000 በላይ የሆኑ  የእስራኤል ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን በኢየሩሳሌም ከፍተኛ የተቃውሞ ስልፍ ማድጋቸው ታውቋል። ቤተ እስራኢሎችን ያስቆጣውና የተቃውሞ ስልፊ እንዲያካሂዱ ምክንያት የሆናቸው ጉዳይ ቀደም በዚህ ዓመት ህዳር ወር ላይ የእስራዔል መንግስት በኢትዮጵያ የቀሩ ዘመዶቻቸው መምጣት እንዲፈቀድላቸው የወሰነውን ውሳኔ አሁን በመጋቢት ወር የበጀት እጥረትን እንደምክንያት በመስጠት እንዲቀለበስ በማድረጉ ነው። ሰልፈኞቹ “ስቃዩ ይቁም፤ አድልዎ ይቁም፤ ዘረኝነት ይቁም፤ ኢትዮጵያ የሚገኙት ዘመዶቻችን ባስቸኳይ እንዲመጡ ይደረግ” የሚሉ መፈክሮችን ያሰሙ እንደነበር ታውቋል። አንዳንዶቹ ከሃያ ዓመት ጥረት በኋላ እናትና አባታቸው ማስመጣት ያልቻሉ መሆናቸውን ገልጸው ከፈረንሳይ፤ ከአሜሪካ እና ከሩሲያ አለምንም ችግር እንዲመጡ ሲደረግ ከኢትጵያ እንዳይመጡ መከልከሉ ዘረኛነት ምን ያህል ስር የሰደደ መሆኑን ያሳያል በማለት ተናግረዋል። በእስራኤል አገር ከ 135 ሺ በላይ የእስራኤል ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚገኙ ሲሆን አብዛኞቹ ከኢትዮጵያ የተወሰዱት ከ1976 እስከ እስከ 1983 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ ነው።

 

Ø ትናንት መጋቢት 11 ቀን 2008 በቤኒን በተደረገው ብሔራዊ ምርጫ በመጀመሪያ ዙር የተሰበሰቡትን የድምጽ ካርዶች ቁጥር መሰረት በማድረግ  የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዮኔል ዚንሱ መሸነፋቸውን አምነው ለተቀናቃኛቸው የእንኳን ደስ አለህ መልክት በቴሌፎን  የገለጹላቸው መሆኑ ተነግሯል። ሊዮኔል ዚንሱ ፈረንሳይ አገር የተወለዱ የታወቁ የባንክ ኢንቨስተር ሲሆኑ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ የወሰዱት ባለፈው ዓመት ነበር። በትናንቱ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተመረጡት ፓትሪስ ታሎን በንግዱ ዓለም ተሰማር ሲሆን በአገሪቱ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። የቢኒን የምርጫ ኮሚሽን በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት በይፋ አሸናፊውን የሚገልጽ መሆኑ ተነግሯል።  

በተመሳሳይ ዜና ትናንት በተደረገው  በዛንዚባር በተደረገው ምርጫ ሲቪክ ዩናይት ፍሮንት የተባለው የተቃዋሚው ፓርቲ በምርጫ ያልተሳተፈ ቢሆንም  የታንዛኒያ ገዥ ፓርቲ ተወካይ 91 ከመቶ የሚሆነው ድምጽ በማግኘት አሸናፊ ሆኗል ተብሏል። በኬፕ ቨርዴ ደሴትም ከአስራ አምስት በኋላ ተቃዋሚው በምርጫው ያሸነፈ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø ዛሬ መጋቢት 12 ቀን 2008 ዓም ንጋት ላይ በሶማሊያ ከሞጋዲሾ 40 ኪሎሜትር ርቀት በሚገኘው ላንታ ቡሮ በተባለቸው ከተማ በአንድ የመንግስቱ ጦር ሰፈር ላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ወረራ አካሂደው ጉዳት ያደረሱ መሆናቸውን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አልሸባብ በራዲዮ እና በኢንተርኔት ባሰራጨው ዜና በጥቃቱ 73 የመንግስት ወታደሮችን መግደሉንና ወታደራዊ ካሚዮኖች መሳሪያና ጥይቶች  እንዲሁም ሰባት በመኪና ላይ የሚጫኑ ከባድ አውቶማቲ መትረየሶች የማረከ መሆኑን ገልጿል።  የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ ወረራው የተካሄደ መሆኑን ቢያምንም ስለደረሰው ጉዳይ መግለጫ ካለመስጠቱ ሌላ አጥቂዎቹ በርካታ ጉዳት እንደደረሰባቸውና ወደመጡበት እንድያፈገፍጉ መደረጋቸውን ገልጿል። ቀድም ብሎ አልሸባብ በአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል እና በሶማሊያ ወታደሮች ጦር ሰፈሮች ላይ ወራዎች ማካሄዳቸውና ጉዳት ማድረሳችው አይዘነጋም። አልሸባብ የዛሬውን ጥቃት የፈጸመው ትናንት  መጋቢት 11 ቀን 2008 ዓም አንድ  የኬኒያ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ በሳምንቱ መጨረሻ በሶማሊያ ውስጥ በሁለት የተለያዩ ቦታዎች የኬኒያ ወታደሮች የአልሸባብን ጥቃት መመለሳቸውና በርካታ የአልሽብብ ወታደሮችን መግደላቸውን የሚገልጽ መግለጫ ከሰጠ በኋላ ነው።  

 

 

 

መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በአልጠግብ ባይነት በኢትዮጵያ ያሉትን ባለሀብቶች ለማሰር ንብረታቸውን ለመውረስ የማይቆፍሩት ጉድጓድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የሌለ ሲሆን ሰሞኑን ከ15 ዓመት በፊት ወደ ሀገር ውስጥ ሸቀጥ ያስገቡ ነጋዴዎችን በወቅቱ የጉምሩክና የገቢዎች ቀረጥ አልከፈላችሁም በማለት ክስ ለመስረትና ንብረታቸውን ለመውረስ ዝግጅት መጨረሳቸው ታውቋል። በዚህ የስም መዝገብ ውስጥ በዋናነት ወያኔ በሙስና ሽፋን ክስ የመሰረተበትና ከሀገር ኮብልሎ የሚገኘው የጌት አሶ ድርጅት ባለቤት ጌቴ ገለቴ እንዳለበትና በ35 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ክስ እንደሚመሰረትበት የገቢዎችና የጉምሩክ ምንጮች አጋልጠዋል። ባለሀብቱ ጌቱ ገለቴ ከሀገር ሸሽቶ ቢወጣም ከእርሱ ድርጅት ጋር ሰርታችኋል በተባሉ አስራ አራት አስመጭዎች ላይ ተመሳሳይ ክስ ለመመስረት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ታውቋል። የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ውስጥ የፖሊቲካ መሪ፤ የኢኮኖሚ ዘዋሪ፤ ወታደራዊ አዛዥ፤ ሀብታም ነጋዴ፤ የአንድ ዘር የበላይነትን የሚያነግሰውን ዘረኛነትን እንደ ቅኝ ገዥ ፖሊስ ማራመድ መርህ አድርገው መንቀሳቀስ ከጀመሩ ወዲህ  ውዲህ የትግራይ ተወላጅ ካልሆኑ በስተቀር ሌሎች ነጋዴዎች ሱቃቸው ሲወስድ ግብራቸው ሲበዛ እያየን ነው የሚሉ ወገኖች እንደ ዜጋ በሀገር የመስራትና የመነገድ መብትን ለማስከበር እስካልቻልን ድረስ የወያኔ ዘረኛ ተግባር ቀጣይ ነው ይላሉ።

 

Ø የወያኔ ስርቆትና ሌብነት ቅጥ እያጣ ከመጣ ጀምሮ መሪዎቹ ዘረፋን መንግስታዊ መልክ እየሰጡት መምጣታቸው የሚታወቅ ነው። አገዛዙ በቅርቡ የኮንዶሚኒየም ቤት ቆጠራ ይደረግ በማለት በጀመረው ማጣራት በቆጠራው የወያኔ አባል ወይንም የትግራይ ተወላጅ በመሆናቸው የኮንዶሚኒየም ቤት ዕጣ ሳይወጣላቸው በር ሰብረው የገቡና የአገዛዙን ባለስልሥልጣኖች የተማመኑ በብዛት መገኘታቸው ብዙም ሳያጠያይቅ የኮንዶሚኒየም ህንጻ መጥፋት ግን አነጋጋሪ ሆኗል። በወረቀትና በፕላን ላይ ቦታ ተሠራ የተባለ ህንጻ በቦታው ላይ የሌለ ሲሆን ለአጣሪዎቹና ለቆጣሪዎቹ ዱብ ዕዳ ሆኗል። የሌለው ህንጻ ቁጥር የተሰጠው የኮንዶሚንየም ክፍሎቹም ብዛት የተገለጸበት  መረጃ በግልፅ ቢኖርም በመሬቱ ላይ ግን ህንጻው ሊገኝ አልተቻለም። የወይኔ ባለሥልጣኖች ቆጣሪዎችና አጣሪዎች ህንጻ ጠፋ የሚለውን መረጃ እንዲያዳፍኑ መመሪያ እንደተሰጣቸው ታውቋል። የሕንጻው መጥፋት የሚያሳየው ቀድሞው ህንጻው እንደተሰራ ተደርጎ መቅረቡና ለህንጻው ተብሎ የወጣው ወጭ በወያኔ ባለሥልጣናት መዘረፉን ነው። ግንባታውን ታቅዶ ሳይሰራ በቀር ጊዜ መረጃውንና ሰነዱን አለመሰራቱን መግለጽ ሲገባው የወያኔ ባለስልጣናት ህንጻው እነደተስራ አድርገው ገንዘብ እንደበሉት ሲገልጹ ሙስና ሌብነትና ዝርፊያ በዓይን ባወጣ መልኩ የወያኔ አገዛዝ መለያ ሆኗል ተብሏል።

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በሀሰተኛ ክስና በፈጠራ ወንጀል ከሰዋቸው አንድ ዓመት ከሁለት ወር በስቃይ እስር ቤት ውስጥ የነበሩት የመኢአድ ም/ ፕሬዚዳንት  አቶ ዘመነ ምህረቱ ከእስር ቤት ተፈተዋል። አቶ ዘመነ ከሽብርተኛነት ጀምሮ ተራ ወንጀልን ያጠቃለለ ክስ ተመስርቶባቸው ከአስራ ስምንት ጊዜ በላይ ፍርድ ቤት ተመላልሰው ክሳቸው በሽበረተኛነትም ሆነ በሻዕቢያ ተላላኪነት የማያስከስሣቸው ሆኖ በመረጋገጡ በዋስ እንዲወጡ ተወስኖ በዋስትና ከጠባብ እስር ቤት መጥተው ወደ ሰፊው እስር ቤት ተመልሰዋል። ከእርሳቸው ጋር አብረው የታሰሩት የመኢአድ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ መለስ መንገሻና የመኢአድ አባል አቶ ጌትነት ደረሰ አሁንም በእስር ላይ መሆናቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የኦሮሞ ብሔራዊ ኮንግሬስ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ምርመራ አላላቀም በሚል ሰበብ ተጨማሪ ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል። የወያኔ ፖሊስ የምርመራ ጊዜ በማለት ተጨማሪ 8 ቀን በመጠየቁ የወያኔው የፖሊቲካ ፍርድ ቤትም በመፍቀዱ እነ በቀለ ገርባ አሁንም በእስር እንዲቆዩ ተድርጓል። አቶ በቀለ ገርባ በመላ ኢትዮጵያ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ መርተሃል፤ አስተባብረሃል ተብለው መከሰሳቸው የሚታወቅ ሲሆን ጠበቃቸውን እንዳያናግሩ ተከልከልውና በተጨናነቀ እስር ቤት ኢሰብአዊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል።

 

Ø የወያኔ የጡት አባ የሚባሉት የዓለም ባንክና የዓለም የገንዘብ ድርጅት የወያኔ አገዛዝ በፖሊቲካ ቀውስ ሲጦዝና በኢኮኖሚ ምስቅልቅል ሲንገላታ የገንዘብ ካዝናቸውን በመክፈት በብደር ስም ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በኢትዮጵያ ስም ሲያስታቅፉት እንድነበር ይታወሳል። አገዛዙ በቅርቡ የገጠመውን ከፍተኛ የወጭ ምንዛሬ ዕጥረት ለመቅረፍ እንዲችልም ዓርብ መጋቢት ዘጠኝ ቀን 2008 ዓም የ33 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ከዓለም ባንክ ጋር አዲስ አበባ ውስጥ ተፈራርሟል። ስምምነቱ የወያኔ የገዘብና የኢኮኖሚ ኮርፕሬሽን ሚኒስትር አህመድ ሰዒድ ሲፈርመው በዓለም ባንክ በኩል የዓለም ባንክ የአካባቢው ተወካይ ካርላይን ቱርክ ፈርመዋል። እንተለመደው ሁሉ ገንዘቡ ለሕዝብ ጤና፤ የትምህርትና የእርሻ አገልግሎት እንዲሁም ለንፁህ የመጠጥ  ውሃ ልማት ይውላል ይባል እንጅ በርካታው ገንዘብ በየምክንያቱ  በወያኔ ካዝና በኩል ወደ ውጭ ወጥቶ እንደሚቀመጥ ይታወቃል። የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ስም በመቶ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመበደርና በመዝረፍ መጭውን ትውልድ ባለዕዳ በማድረግ የራሳቸውን የሀብት ክምችትና ድሎት እየገነቡ መሆናቸውን በርካታ ዜጎች ያውቁታል።

 

Ø ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓም በቱርክ ኢስታንቡል ከተማ የገበያ ቦታ አካባቢ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፍነዳው ቦምብ ቢያንስ አምስት ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውንና ከሃያ በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለፈው እሁድ በዋና ከተማዋ በአንክራ ታክ በተባለው የኩርድ ታጣቂ ቡድን በተፈጸመው  ተመሳሳይ የቦምብ ጥቃት  37 ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል።  እንዲሁም ባለፈው ወር በአንድ ወታድራዊ ኮንቮይ ላይ የታቃጣው የቦምብ አደጋ 28 ሰዎች መግደሉ አይዘናጋም። ባለፈው ዓመት በቱርክ መንግስት እና ፒኬኬ በተባለው የኩርድ አማጽያን ድርጅት መካከል ተደርጎ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ከፈረሰ በኋላ 340 የሚሆኑ የቱርክ የጸጥታ ኃይል አባሎች ሲገደሉ 300 የሚሆኑ የኩርድ ተዋጊዎችና እንዲሁም 200 የሚሆኑ ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል ተብሏል።

 

Ø ከአራት ውራት በፊት በፓሪስ በተለያዩ ቦታዎች በተሰነዘሩት ጥቃቶች 130 ስለማዊ ሰዎች መገደላቸውና   ከ100 በላይ መቁሰላቸው የሚታወቅ ሲሆን በጥቃቱ ላይ ተሳታፊ የነበረውና በቤልጀምና በፈረንሳይ የጸጥታ ኃይሎች በጥብቅ ሲፈለግ የነበረው ሳላህ አብዱሰላም የተባለው ግለስብ በትናንትናው ዕለት ቤልጂየም ውስጥ በጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት እግሩ ላይ ተመቶ ተይዟል። በጸጥታ ኃይሎች ሲፈለግ የነበረ አንድ ግለሰብ አብሮ የተያዘ ሲሆን ሳላህ አብዱሰላምን አስጠግታችሁ ደብቃችኋል በሚል የተከሰሱ ሶስት የቤተ ሰቡ አባላት አብረው የተያዙ መሆናቸው ተገልጿል።  በላፈው ማክሰኞ በሌላ ቀበሌ የአብዱ ሰላም አሻራ በመገኘቱ በአካባቢው አሰሳ ተካሄዶ የነበረ ሲሆን ግለሰቡ በመሸሽ ላይ እያለ በተደረገው ክትትል ለረጅም ጊዜ ሲኖርበት ከነበረው ቦታ 500 ሚትር ርቀት ላይ በጥይት እግሩ ላይ ቆስሎ ሊያዝ ችሏል። የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ሆላንድ ሳላህ አብዱሰላም በመያዙ  ድል የተገኘ መሆኑን ገልጸው በሽብረተኛነት ላይ የሚካሄደው ውጊያ ግን በዚህ አያበቃም ብለዋል።

 

Ø ባለፉት ሶስት ወራት በብሩንዲ ዜጎችን በገፍ ይዞ ማሰር እየተካሄደ መሆኑንና እንዲሁም የተያዙትን  በምርመራ ማሰቃየት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሃላፊ ገልጸዋል። ኃላፊው ሚስተር ዘኢድ ራአድ አል ሁሴን ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በሰጡት መግለጫ በአገሪቱ ውስጥ ያለው ሽብር ከመጠን በላይ ሆኖ የሚገኝ መሆኑን ባጭሩ ካልተቀጨ ወደ አጠቃላይ ቀውስ ሊያድግ የሚችል መሆኑን አብራርተዋል።  የሰብአዊ መብት መጣስና ወንጀለኞች ለድርጊታቸው ተጠያቂ ሳይሆኑ የሚቀሩበት ሁኔታ እየቀጠለ መሄዱ የብሩንዲ ዜጎች በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ መኖራቸውን ያረጋግጣል ብለዋል።  በአገሪቱ ውስጥ በዜጎች ላይ በርካታ ቶርቾርችና ማጉላላት እየተፈጸሙ መሆናቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች እንደሚደርሷቸው ገልጸው በቅርቡ ወደ አገሪቷ የሄደው የተመድ ልዕክ በአንድ እስር ቤት ውስጥ ካነጋገራቸው መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በመርመራ ከፍተኛ ድብደባና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ነግረዋቸዋል ብለዋል።

 

Ø መጋቢት 9 ቀን   ለ 10 አጥቢያ  ከሌሊቱ 10 ሰዓት  ላይ አንድ ከዱባይ ወደ ደቡብ ሩሲያ ሲበር የነበረ ቦይንግ 737 የመንገደኞች አውሮፕላን በደቡብ ሩሲያ ግዛት ሮስቶቭ ኦን ዶን በተባለችው ከተማ አውሮፕላን ጣቢያ ለማረፍ ሙከራ በሚደርግበት ወቅት ወድቆ በመከስከሱ በውስጡ የነበሩት 55 ተሳፋሪዎችና 7  የአውሮፕላኑ ሰራተኞች በሙሉ መሞታቸው ታውቋል። የአደጋው ምክንያት  ምን እንደሆነ ለጊዜው ባይታወቅም መጥፎ የአየር ሁኔታ ወይም የቲክኒክ ብልሽት ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ተሰጥቷል። ከሞቱት መካከል አራቱ ህጻናት ሲሆኑ አብዛኞቹ የሩሲያ ዜጎች መሆናቸው ተገልጿል። የአውሮፕላኑ የመረጃ ሳጥኖች የተገኙ ሲሆን ምርመራው የሚቀጥል መሆኑን የሩሲያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል።   

 

 

 

 

 

መጋቢት 9 2008 ዓ.ም.

 

Ø ከምዕራብ አፍሪካ ጠፍቷል በሚል ከአለም የጤና ፕሮግራም የምስክርነት ቃል በተሰጠው በሶስት ወር ውስጥ  የኢቦላ በሽታ በጊኒ የተገኘ መሆኑ ተገለጸ። በአሁኑ ወቅት በሽታው የተከሰተው ከአምስት አመት በፊት በሽታው በጀመረበት በአገሪቱ ደቡባዊ ግዛት ኢንዘረኮሬ በተባለው አካባቢ ሲሆን  የአንድ ቤተ ሰብ አባላት የሆኑ ሶስት ሰዎች በበሽታው መሞታቸው ታውቋል። በጊኒ በሲየራ ሊዮን እና በላይቤሪያ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ በሽታው ከ11 300 ሰዎች በላይ መግደሉ የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተከሰተው በሽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሌሎች ቦታዎች እንዳይስፋፋ ከፍተኛ ስጋት አለ።

 

Ø ዛሬ መጋቢት 9 ቀን 2008 ዓም በአልጀሪያ የሚገኙ እስላማውያን አክራሪዎች በአገሪቱ ደቡባዊ ግዛት የሚገኘውን አንድ የጋዝ ኩባንያ በተመዝግዛጊ ሚሳየል ያጠቁ መሆናቸው ከአካባቢው የተገኘው ዜና ይገልጻል። በሮኬቱ ጥቃት የሞተ ወይም የቆሰለ ሰው የሌለ መሆኑንም ተነግሯል። ኩባንያው ሶናትራች በተባለ በአልጄሪያ ኩባንያ በእንግሊዙ ቢፒ እና ስታቶል በተባለ የኖርዌይ ኩባንያ በጋራ የሚንቀሳቀስ ነበር።

 

Ø በናይጀር በሁለት ቦታዎች እስላማውያን ታጣቂዎች ባካሄዷቸው ጥቃቶች አራት ወታድሮች ሲገደሉ ሶስት ሌሎች የቆሰሱ መሆናቸው የናይጀር የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።  አልካይዳ በኢስላሚክ ማግረብ የሚባለው የአልካይዳ ቅርንጫፍ ናይጀርን ከቡርኪና ፋሶ በሚያዋስነው አካባቢ ባለ አንድ የገበያ ቦታ ላይ ባካሄደው ጥቃት ሶስት ፖሊሶችን የገደለና አንድ ፖሊስ ያቆሰለ መሆኑ ተዘግቧል። ለተወሰነ ጊዜ  ከፖሊሶች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ  አጥቂዎቹ መሸሻቸው የታወቀ ቢሆንም ስለደረሰባቸው ጉዳት የተገኘ መረጃ የለም። በናይጀር እና በናይጄሪያ ወሰን ደግሞ አራት አጥፍቶ ጠፊዎች በአንድ ወታደራዊ ኮንቮይ ላይ ባካሄዱት ጥቃት የቡድኑ መሪ መኮንን ሲገደል ሌሎች ሁለት ወታደሮች የቆሰሉ መሆናቸውን ሚኒስትሩ ጨምረው አብራርተዋል። አምስተኛዋ አጥፍቶ ጠፊ የያዘችውን ፈንጅ ከማፈንዳቷ በፊት በቁጥጥር ስር ውላለች ተብሏል። በሚቀጥለው እሁድ በናይጀር ሁለተኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን ተቃዋሚ ኃይሎች በምርጫው እንደማይሳተፉ ገልጸዋል። በመጀመሪያ ዙር ምርጫ በሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ ድምጽ ያመጡትና በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ የሚገኙትን ፕሬዚዳንት ሊያሸንፉ ይችላሉ ተብለው የተገመቱት  ሃማ አማዶ ለተወሰነ ወቅት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸውና ለህክምና ወደ ፈረንሳይ አገር እንዲወጡት የተፈቀደላቸው መሆኑ አይዘነጋም።   

 

Ø በሊቢያ የአንድነት መንግስት እንዳይመሰረት እንቅፋት በሚፈጥሩ ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ ለማድረግ በአውሮፓው ህብረት የወሰነውን ውሳኔ  ፈረንሳይ የምትደግፍ መሆኑን የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ። ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በቱኒዚያ የሁለት ቀናት ጉብኝት ባደረጉበትና የሊቢያን ሁለት ተጻራሪ አስተዳደሮች ይተካል ተብሎ የሚጠበቀውን የአንድነት መንግስት መሪን አግኝተው ባነጋገሩበት ወቅት ነው። የአንድነት መንግስት ተብሎ በተመድ አስተባባሪነት የተቋቋመው መንግስት ያለው ቱኒዚያ ውስጥ ሲሆን እስካሁን ድረስ አገር ውስጥ ካሉት ሁለት ተጻራሪ መንግስታት ያገኘው ሙሉ ድጋፍ የለም። ትሪፖሊ ያለው መንግስት አባላት እና ተባባሪ የሚሊሺያ ተቋም የአንድነት መንግስቱ የውጭ ኃይሎችን ለማገልገል በውጭ ኃይሎች የተቋቋመ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ አድረገውታል። በአገሪቷ ምስራቃዊ ግዛት ውስጥ ባለቸው በቶብሩክ ከተማ ውስጥ መሰረቱን አድርጎ የሚንቀሳቀሰውና ዓለም አቀፍ እውቅናና አግኝቷል የተባለው አካልም እስካሁን ድረስ ለአንድነት መንግስቱ በይፋ  የሰጠው ድጋፍ የለም። አንዳንድ አባላት የሚደግፉት ቢሆንም ሌሎች እንደሚቃወሙት ተነግሯል።

 

Ø ሰሜን ኮሪያ በዛሬው ቀን ሁለት ቦለስቲክ ሚሳየሎች የተኮሰች መሆኑ ተነግሯል። ሚሳየሎቹ 800 ኪሎ ሜትር ያህል የተጓዙ ሲሆን ባህር ውስጥ ወድቀዋል ተብሏል። ሰሜን ኮሪያ ሚሳየሎቹን የተኮሰቸው የአሜሪካ መንግስት በአገሪቱ ላይ ማዕቀብ እንዲደረገ በወሰነ በማግስቱ ነው። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለፕሬዚዳንቱ የተሰጠውን ስልጣን ተጠቅመው ባደረጉት ውሳኔ በአሜሪካ ውስጥ የሚገኘው የሰሜን ኮሪያ መንግስት ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ያደረጉ ከመሆኑ በላይ ወደ ደቡብ ኮሪያ እቃዎች እንዳይላኩና በአገሪቱም ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ የንግድም ሆነ የኢንዱስትሪ ስራ እንዳይካሄድ አውጀዋል። ከሰሜን ኮሪያ ጋር የንግድም ሆነ የጥቅም ግንኙነት የሚያደርግ አሜሪካውም ሆነ የውጭ ዜጋ በወንጀለኛነት ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ሰሜን ኮሪያ የተኮሰቻቸው ሚሳየሎች አሜሪካ ለወሰደችው ማዕቀብ መልስ ቢሆንም በአካባቢ ያሉትን አገሮች አሳስቧል። የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ድርጊቱን ከማውገዛችውም በላይ መንግስታቸው ከአሜሪካ እና ከደቡብ ኮሪያ ጋር በመምከር ማናቸውንም ዓይነት እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል። የአሜሪካን መንግስት ወታደራዊ ቃል አቀባይም ሰሜን ኮሪያ ከድርጊቷ እንድትታቀብ ጥሪ አድርገዋል።

 

Ø በዛሬው ቀን በኬኒያ ዋና ከተማ በናይሮቢ አንድ ከብሄራዊ ፓርክ ያመለጠ አንበሳ በአውራ መንገዶች ላይ በመዘዋውሩ መንገዶች ለትራፊክ ለረጅም ሰዓታት ዝግ ሆነው የቆዩ ሲሆን ባለመኪናዎች በሚነፉት ጥሩንባና በሚያሰሙት ጩኸት እንዲሁም ፎቶ ግራፍ ለማንሳት ሰዎች ባደረጉት መሯሯጥ የተቆጣው አንበሳ አንድ የ63 ዓመት አዛውንትን አጥቅቶ የአካል ጉዳት ያደረሰባቸው መሆኑን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተወሰን ጊዜ በኋላ የፓርኩ ሰራተኞች አንበሳውን  አረጋግተው  ሌላ ጉዳት ሳያደርስ ወደ  ወደ ፓርኩ እንዲመለስ ያደረጉት መሆኑ ተነግሯል።  ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ከፓርክ ያመለጡ አንበሶች በናይሮቢ መንገዶች የታዩ መሆናቸው ይታወቃል።

 

 

መጋቢት 8 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ያለ ይሉኝታ ቆሞ የሚሄድ ውሸት መናገር ተፈጥሯቸው የሆነው የወያኔ መሪዎች ከፍለው በሚያቀርቧቸው ጋዜጠኞችና በኢትዮጵያ ላይ ቀስታቸውን በወጠሩ ግለሰቦች አማካኝነት የሚነዳው የውሸት ፕሮፓጋንዳ የወያኔ መሪዎች በተናገሩ ቁጥር አድማጩ ኢትዮጵያዊ ማፈር ጀምሯል። የወያኔ ቀንደኛ መሪ አርከበ እቁባይ ብሉምበርግ ለተባለው የአሜሪካን የዜና ወኪል በሰጠው ቃለ ምልልስ “በምግብ እህል ራሳችንን ችለናል ከአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው እድገት እያስመዘገብን ነው” በማለት አፉን ሳያዳልጠው ዋሽቷል። የወያኔ አገዛዝ ራሱና የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ከ15 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊ የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ፈላጊ ነው በሚሉበትና ለተጨማሪ ዕርዳታ 1.4 ቢሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ረሃብተኞች ሲማጸኑ እየተሰሙ ባሉበት ወቅት የራሱ ጥጋብ ራሱን ያሳወረው የወያኔ መሪ አርከበ ኢትዮጵያ በምግብ እህል ራሷች ችላለች ብሏል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በሥራ አጥነት ለስደት መከራ እየተጋለጠ እያለ ሕዝብ በኢኮኖሚ ተሻሽሏል ይለናል። ሥራ አጥነት በመላ ኢትዮጵያ መስፋፋቱን፤ ድህነት ቅጥ ማጣቱን፤ የሕዝብ ተስፋ መጥፋቱን፤ ራዕይ ባለመኖሩ ስደት መምረጡን አርከበ  የኢኮኖሚ ዕድገት ውጤት ነው ይለዋል። የወያኔ መሪዎች ዓለም ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን የኢትዮጵያን ሁኔታ በፕሮፓጋንዳ ለመሸፈን የሚናገሩት ንግግርና የሚያቀርቡበት መረጃ ሕዝብን ከመናቅና ከመጥላት የመነጨ መሆኑ በግልጽ የሚታይ ነው።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ የራሱን ኪስ ለማደለብ  በሕዝብ ጤንነት ኪሳራ ላይ መስርቶ መንቀሳቀስ ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ የገንዘብ መሰብሰቢያ ዜዴ ከሆኑለት አንዱ የኤች አይቪ ቫይረስን መከላከል እንደነበር ይታወቃል። አሁን ግን በአዲስ አበባ ከተማ ቫይረሱ በሰውነት ውስጥ መኖሩን ምርመራ ለማድረግ እንኳን አለመቻሉ ታውቋል። ለዚህ የሚሰጠው ምክንያት የኤች አይቪ ቫይረስ ምርመራ ማካሄጃ ወይም ቲስት ኪት በመጥፋቱ ነው። የኤች አይ ቪ ቫይረስ ጉዳይ አሁን ወሬው እየጠፋ ህመሙ ግን እየተስፋፋ እንደሚገኝ ይታወቅ እንጅ የቫይረሱን ስርጭትና መስፋፋትን ለመከታተልና መረጃ ለመሰብሰብ ግን አልተቻለም። አንዳንድ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ ዶክተሮች ወደ ህክምና ተቋማችው የሚመጣ ታካሚ በሚገባ ይመክርና ይመለሳል። ለኤች አይቪ ምርመራና ህክምና ግን አይታሰብም እስከማለት መድረሳችው የችግሩን አሳሳቢነት አሳይተዋል። አንዳንድ የሕክምና ባለሙያዎች የኤች አይ ቪ ቫይረስ በተስፋፋበት ወቅት በርካታ ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ይለግሱ እንደነበረ በማስታወስ ዛሬም ወያኔ በሽታውን ለማስፋፋትና የእርዳታ ገንዘብ ለመሰብሰብ በኅበረተሰብ ጤነንት ላይ ቁማር እየተጫወተ ነው ይላሉ።

 

 

 

Ø የወይኔ ቡድን መሪዎች የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ በግድያ በእስርና በድበድባ ማቆም ባለመቻላቸው ከሕዝብ ጋር ንግግርና ምክክር ማድረግ በሚል አዲስ የማዘናጊያ ዘመቻ ለመጀመር ዝግጁነታቸውን ጨርሰዋል። በዚህ መሠረት ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ በተለያዩ ሠፈሮች ውስጥ ውይይት እንደሚጀመርና እስከ መጋቢ 30 ቀን 2008 ዓም እንደሚዘልቅ ለማወቅ ተችሏል፡፤ ከመጋቢት 8 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ እስከ መጋቢት 30 ቀን 2008 ድረስ በሚቆየው በዚህ ውይይት ምክክር ላይ ከፋብሪካ ሠራተኞች፣ ከምሁራን፤ ከመንግስት መስሪያ ቤቶች ከግል ድርጅቶች፣ ከንግዱ ማኅበረሰብ እና ከመሳሰሉት ተቋማት አባላት ጋር  ምክክር እንደሚደረግና በወያኔ በዋናነት የተቀመጠው አጀንዳም በመልካም አስተዳደር እርምጃዎች ላይ እንደሆነ ተገልጿል። በተለያዩ አካባቢዎች በናሙና መልክ ተመርጠው ለምክክር የሚጠሩት ነዋሪዎች ወደ ሠፈራቸው ሲመለሱ ስለ ማደናገሪያ ስልቱ እንዲያወሩ ለማድረግ መታቀዱ ታውቋል። በቅርብ ከወያኔ መሪዎች ዋነኛው የሆነው ደብረጽዮን የመልካም አስተዳደር ፕሮጀግት ሳይሆን ሂደት ነው በማለት መናገሩና ዛሬ ካድሬዎች ስለ መልካም አስተዳደር ስብሰባና ምክክር በማለት ኅብረተስብን የሚያደናቁሩት የወያኔ አገዛዝ የሚያቃጭል የተቃውሞ እሳት መቀጣጠሉን በሚመለከት መሆኑ ታዛቢዎች ይናገራሉ።

 

Ø የአባይን ግድን አስመልክቶ የግብጽ መንግስት ከወያኔ ጋር ለአራት ዓመታት ያደረገው ውይይትና ድርድር መፍትሄ ባለማምጣቱ ግብፅ የአባይን ግድብ የሚከታተል አዲስ ሳተላይት ወደ ህዋ መላኳን የግብፅ የሳተላይት ባለስልጣናት ገልጸዋል። አዲስ ሳተላይት የውቀድሞውን ሳተላይ የሚተካና ከቀድሞ በተሻለ የአባይን ግድብ የሚከታተል ፎቶ የሚያነሳ ዘመናዊ መሳሪያዎች የተገጠሙለት መሆኑ ተገልጿል። ግብፅ ስለ አባይ ግድብ መረጃ ለማግኘት በማለት በግድብ ላይ ብቻ ያነጣጠረ ሳተላይት መተኮሱ ቢረጋገጥም በእርግጥ ሳተላይቱ ለሰላማዊ ኤንጂኔሪንግ ፕሮጅክት መከታተያ ነው ወይንስ ለወታደራዊ አገልግሎት ዝግጅት ማጣደፊያ በማለት የሚጠይቁ ወገኖች ብዙ ናቸው። የግብጹ አዲስ ሳተላይት ወደ ህዋው መምጠቅ በግብፅ የመገናኚያ ብዙኅን የመነጋገሪያ አጀንዳ ይሁን እንጅ የወያኔ አገዛዝ የሰጠው አስተያይት አልተመዘገበም።

 

 

Ø በሌላ በኩል ደግሞ በግብጽ በሱዳንና በወያኔ መሀል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የአባይ ግድብ ቴክኒካል ጉዳዮች እንዲያጠኑ የተመረጡት ሁለት የፈረንሳይ ኩባንያዎች እስከአሁን ስራ ያልጀመሩ መሆናቸውን የግብፅ ባለሥልጣኖች ገልጸዋል። ጥናቱ የተራዘመው ግብፅና ወያኔ ባለመስማማታችው ስሆን በቅርብ ግን ሥራ እንደሚጀመሩና በበዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ እንደሚያጠናቅቁ የተገለጸ ሲሆን  ለሥራቸው ማካሄጃ ከወያኔ ከሱዳንና ከግብፅ የተውጣጣ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው መሆኑ ተዘግቧል።   

 

Ø የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ሙስና ውስጥ ተዘፍቀዋል፤ የመንግስታቸውን ስራ የሚያካሄዱት በዝምድና በጥቅም ላይ መሰረት በማድረግ ነው በሚል የተጋለጡ  ስለቀረበባችው ክስ በዛሬው ዕለት በደቡብ አፍሪካ ምክር ቤት ቀርበው ጥያቄዎች ይመልሳሉ ተብሏል። በቅርቡ የደቡብ አፍሪካ ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር የሆኑት ግለስብ  ጉብታ የሚባለው የህንድ ሃብታም ቤተሰብ አሎች የዋናውን የገንዘብ ሚኒስትር ቦታ ልናሰጥህ እንችላለን ብለውኛል ብለው በማጋለጣቸው በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የፖሊቲካ ውጥረት ተፈጥሯል። ጉብታ የተባለው መሰረቱ  ህንድ የሆነው ቤተሰብ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከፍተኛ የንግድ እና የኢንዱስትሪ ኩባንያዎች ያሉት ሲሆን የፕሪዚዳንት ዙማ ልጅ የባለቤትነት ድርዳ ያለው  ከመሆኑም በላይ ሶስተኛዋ ሚስታቸው በኩባንያው ውስጥ ሠራተኛ ናቸው ተብሏል። ከፕሬዚዳንቱ ጋር ባላቸው የቅርብ ግንኙነት ምክንያት  ከዚህ በፊት የጉብታ ቤተሰቦች በደቡብ አፍሪካ የፖሊቲካ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ያደርጋሉ የሚል ክስ በተደጋጋሚ የቀረበ ሲሆን አሁን መጨረሻ የቀረበው ክስ ግን ፕሬዚዳንት ዙማ የሚወክሉትን የገዥውን ፓርቲ ኤ ኤን ሲ ጭምር ክፉኛ ያስቆጣ መሆኑ ታውቋል። የኤ ኤን ሲ ዋና ጸሐፊ ሚስ ማንታሼ ጉዳዩ በጣም አሳሳቢ መሆኑን ገልጸው አስፈላጊውን ርምጃ ባስቸኳይ መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል። ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምክር ቤት ውስጥ ዙማን የሚወጥሩ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ያቀርባሉ ተብሎ ይገመታል።

 

Ø ረቡዕ መጋቢት 7 ቀን 2008 ዓም በደቡብ እና በሰሜን ምስራቅ ሱማሊያ በተደረጉ የተለያዩ ጦርነቶች ከ 30 በላይ የሚሆኑ የአልሸባብ አባላት የተገደሉ መሆናቸውን የኬኒያ ወታደራዊ እዝ እና የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። በደቡብ ሱማሊያ በታችኛው ጁባ አካባቢ  የኪኔያ ወታደሮችና ሌሎች የተመድ የአስከባሪ ኃይል በሰፈሩበት ካምፕ ላይ የአልሸባብ ኃይሎች ጨለማን ተገን በማድረግ የወረራ ሙከራ አድርገው የነበረ ሲሆን በተደረገው የመልሶ ማጥቃት ርምጃ  ወረራው ከሽፎ 19 የአልሸባብ አባላት መገደላቸውናመሳሪያዎች እና ጥያቶች መመረካቸው ተነግሯል። አንድ ወታደራዊ መኪና ተቃጥሏል ተብሏል። በሰሜን ምስራቅ ሶማሊያ በተደረገው ጦርነትም 11 የአልሸባብ አባላት መገደላቸውን የአክባቢው ነዋሪዎች ተናገረዋል።

 

Ø በግብጽ የሲና ባህረ ሰላጤ ውስጥ በምትገኘው ራፋህ በተባለች ከተማ የሲሲ መንግስት በመቃወም የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች አንድ የመሳሪያ ማከማቻ መጋዘን ላይ ባካሄዱት ጥቃት ቢያንስ አምስት ወታደሮች ሲገደሉ ከ 10 በላይ የቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል፡፤ ጥቃቱ የተፈጸመው ሐሙስ መጋቢት 8 ቀን 2008 ዓም ጠዋት ላይ ሲሆን አጥቂዎቹ ሞርታር ቦምብ እና አውቶማቲክ መሳሪያዎች የተጠቀሙ መሆናችው ታውቋል። በሲና አካባቢ ታጣቂዎች በየቀኑ በግብጽ ወታድሮች ላይ ጥቃት ሲፈጸሙ መቆየታቸው የታወቀ  ሲሆን  የግብጽ የመከላከያ ኃይል ለመቆጣጠር ከሚችለው በላይ ሆነብታል በማለት ታዛቢዎች ይተቻሉ።

በተያያዘ ዜና የግብጹ ፕሬዚዳንት ሲሲ የምዕራብ አገሮች ሊቢያ ውስጥ ጦራቸውን ማስገባት የለባቸውም በማለት ለአንድ የጣሊያን ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል። ሲሲ የምዕራብ አገሮች ሊቢያ ውስጥ ጦራቸውን ካስገቡ ጦርነቱ እየተባባሰ ሊሄድ እንደሚችል ከአፍጋኒስታንና ከሶማሊያ ሁኔታ ተመክሮ መውሰድ ይገባቸዋል ካሉ በኋላ ማድረግ ያለባቸው በዓለም አቀፉ ህብረተብ እውቅና ያገኘውን ክፍል በወታድራዊ መስክ ማጠናከር ብቻ ነው ብለዋል።

 

Ø በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል በየመን ውስጥ የሚያካሄደው ዋና ዋና  ወታድራዊ ዘመቻ የሚቆም መሆኑን የጥምሩ ኃይል ቃል አቀባይ ካይሮ ላይ ገልጿል። እንደ ቃል አቀባዩ ገለጻ ላለፉት አንድ ዓመት ጥምሩ ኃይሉ ሲያካሄዳቸው የነበሩት የአየር እና የመሬት ላይ ውጊያዎች የሁቲን እንቅስቃሴ ለመግታት መሆኑን ገልጾ  ከዚህ በኋላ ጥምር ኃይሉ ለየመን ኃይሎች የአየር ሽፋን ከመስጠት በስተቀር በእግረኛ ጦር ውስጥ እንደማይሳተፍ ገልጿል። ዋና ከተማውን ጨምሮ በርከት ያሉ ቦታዎች በሁቲ ቁጥትር ስር ባለበት ሁኔታ በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል በመሬት ላይ የሚያደርገውን ወታደራዊ ዘመቻ ለማቆም የተገደደው እስካሁን የተደረገው ጉዳት እንጅ ውጤት አልባ መሆኑን በመረዳቱ ነው  የሚሉ በርካታ ናቸው። በሳዑዲ አረቢያ የሚመራው ጥምር ኃይል በቅርቡ ባካሄደው የአየር ጥቃት 65 ሰላማዊ ሰዎች ሲገደሉ 55 መቁሰላችው ተዘግቧል።

 

 

መጋቢት 7 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የወያኔ አገዛዝና የዓለም አቀፉ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ድርቅና ረሃብ እየከፋ መምጣቱንና ከ 10 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ለአሰፊ የረሃብ አደጋ መጋለጡን በመጥቀስ የ 1.4 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ተማጽነዋል። በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ እርዳታ ፈላጊ ቁጥር ካለፈው ታኅሳስ ወር ጀምሮ በአስደንጋጭ ፍጥነት እየጨመረ መሆኑን የተመድ የሰብአዊ ጉዳይ አስተባባሪ ቢሮ አስታውቋል። የአስተባባሪ ቢሮ ቡድን አባላት የረሃብ የድርቁን አስከፊ ቦታዎች እንደገና እንዲገመገሙና በሶስት ሳምንት ጊዜ ረፖርት እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል። ለኢትዮጵያው ድርቅ ረሃብ የተጠየቀው እርዳታ በእርስ በርስ ጦርነት የሚዳክሩት ከሶሪያና ከየመን ቀጥሎ ትልቁ ዓለም አቀፍ እርዳታ መሆኑ ታውቋል። የተመድ ከጠየቀው 1.4 ቢሊዮን ዶላር ገንዘብ ውስጥ እስከ አሁን የሰበሰብው ግማሽ ያህሉን ብቻ መሆኑ የረሃብና የድርቁን አደጋ እርዳታ ከፍተኛ አደጋ ተደቅኖበታል ተብሏል።  ለመጭው ክረምትም የዘር እህል እርዳታ የጠየቁት ገበሬዎች ቁጥር ከ2.2. ሚሊዮን ወደ 3.3. ሚሊዮን ከፍ ማለቱ ታውቋል። የሰብአዊ እርዳታ ባለሙያዎች ግን የኢትዮጵያው ድርቅ ረሃብ የተፈጥሮ ብቻ ሳይሆን የብልሹ አገዛዝ ውጤት መሆኑንና የወያኔ አገዛዝ ድርቅና ረሃብ የፖሊቲካ መሳሪያ እያደረገውና እርዳታን ለፖለቲካ ታማኞቹና ለተመረጡ ዘሮች ቅድሚያ እየሰጠ መሆኑ ይገልጻሉ።

 

Ø የወያኔ አገልጋይ የሆነውና ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ኃይለማሪም ደሳለኝ በኢትዮጵያ አራቱም ማዕዘናት ለተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ የወያኔ ብልሹ አስተዳደር መሆኑን ለፕሮፓጋንዳም ቢሆን አምኖ ይቅርታ በጠየቀ ማግስት የወያኔ ድህንነት መ/ቤት ባስተላለፈው ሚስጥራዊ ትዕዛዝ ሕዝባዊ ተቃውሞውን ያስተባበሩና የመሩ እንዲሁም የተባበሩትን በሙሉ ታድነው እንዲያዙ ጠይቋል። የታመኑ የደህንነት ምንጮች እንደገለጹት የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ይቅርታን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የተቃውሞ መሪዎችን አዘናግቶ ማጥመድ አንዱ ሴራ ነው ተብሏል። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተጽፎ የተሰጠውን የይቅርታ ደብዳቤ ባነበበ ማግስትም የወያኔው ሎሌ ሬድዋን ሁሴን የፖሊስ ኃይሉ የወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ትዕዛዝ ሳይሆን የግለሰብ ፖሊስ እርምጃ ነው በማለት መናገሩ ወያኔ ለግድያው የራሱን የፖሊ ኃይል አሰልፎ የሰጠ ይሁን እንጅ አንድም ነፍስ ገዳይን ለሕግ አላቀረበም። የወያኔ ፖሊስና ሠራዊት ለተቃውሞ በወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በወያኔ መሪዎች ትዕዛዝ ፍጅት መፈጸማቸው እየታወቀ ሬድዋን ሁሴን ፖሊስና ሠራዊቱ በራሱ አነሳሽነት የወስደው እርምጃ ነው ማለቱ ተራ ቅጥፈት ተብሏል።

 

Ø የወያኔ ሥርዓት ዘረኛና አምባገነኑን አገዛዝ የሕዝብ ድጋፍ አለኝ ለማሰኘትና የራሱን ዘር አባላትንና የድርጅት ካድሬዎችን በአዲስ አበባ ውስጥ በብዛት ማስገባት ከጀመረ ወዲህ አሁንም ይህን የተጠናከረ ዘመቻ ለማስቀጠል በሺ የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆችን ወደ አዲስ አበባ ለማዛወር ተጀምረው ያላላቁ የኮንዶሚንየም ቤቶችን ለባለ ዕጣ ተሰጠ በማለት በር ያልተገጠመለትና፤ ወሃ፤ መብራት፤ መጸዳጃ ቤት የሌለው ቤት ውስጥ እንዲገቡና የሚኖሩበትን የቀበሌ ቤት በአስቸኳይ እንዲያስረክብ መጠየቁ ታውቋል። የቀበሌ ቤቶችንም ለራሱ ዘር አባላት መድቦ መጨረሱ ተገልጿል። የወያኔ ቡድን መሪዎች በአስራ አንደኛው ሰዓት የሥልጣን ዘመናቸው የትግራይን ሕዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ለመለየት የተለይ ጥቅም እየሰጣቸው መሆኑን አውቀው የወያኔን ስውር ደባ እንዲጠነቀቁበት ሕዝብ እየመከረ ነው።

በተመሳሳይ ዜናም በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ያሉ ሱቆችን በሙሉ በትግራይ ተወላጆች ለማስያዝ በጨረታ ስም ሱቆቹን በሙሉ ለትግራይ ተወላጆች እየሰጠ ሲሆን በአውሮፕላኑ ማረፊያ ውስጥ በሁሉም መስኮች ትግራዮች ብቻ እየተቀጠሩና እየሰሩ መሆናቸውን ሲታወቅ አንዳንድ ወገኖች ቦሌ አውዎላፕላን መረፊያ የመጣ መንገደኛ አደዋ የገባ ቢመስለው አይፈረድበትም ይላሉ።

 

Ø ትናንት መጋቢት 6 ቀን 2007 ዓም የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው በአዲስ አበባ ከዩኒቨርስቲ ምሁራን ጋር ስብሰባ ተቀምጦ ስለ ብሔራዊ መግባባት ለምሁራኑ ዲስኩር መስጠቱ ታውቋል። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር አድርግ ተብሎ የተነገረውና ተጽፎ የተሰጠውን ማንበብ ሥራዎ በማድረግ ሕዝብን ለማታለልና ለማዘናጋት አዲስ ጥረት የጀመረ መሆኑ ተወስቷል። በዚህ ስብሰባ ላይ የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ስለ ኢኮኖሚው ፈጣን እድገት፤ በምግብ እህል እራስን ስለመቻል፤ እና ስለሌሎች ጉዳዮች ራሱን ብቻ የሚያታልል ዲስኩር የሰጡ መሆኑ ሲደመጥ ምሁራኑ በብሔራዊ መግባባት ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግሯል። የፖለቲካ ታዛቢዎች ግን የወያኔ መሪዎች ጭንቀት ሲበዛባችው ፍርሃት ሲወጥራቸው ሕዝባዊና ሀገራዊ የሚመስሉ ነገር ግን የራሳቸውን ሥልጣን ጊዜ የሚያራዝሙበት አጀንዳ መቅረጽ የተለመደ ስልታቸው ሲሆን አሁንም ምሁራንን ስብሰባ ስለ ብሔራዊ መግባባት ማውራታቸው ከጭንቀት ለመገላገል መሆኑን አውስተው ብሔራዊ መግባባትና ተቃዋሚዎችን ያሳተፈ አገራዊ አጀንዳ ያለው የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ማስከበርን የሚያጠቃልል እንደሆነ በመግለጽ የወያኔው ስብሰባ ጉንጭ አልፋ ነበር ይሉታል። አንዳንድ ምሁራን ሃይለ ማሪያም ደሳለኝ ፈታኝ የሆኑ የታሪክ የዴሞክራሲና የአሠራር ጥያቄዎችን አቅርበው እንደነበር ታውቋል።

 

Ø ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2008 ዓም በሰሜን ናይጀሪያ ግዛት ከተማ በማይድጉሪ በሚገኝ አንድ መስጊድ ውስጥ ሁለት አጥፍቶ ጠፊ ሴቶች የያዙትን ቦምብ በማፈንዳታቸው 22 ምዕመናን ሲገድሉ ሌሎች 18 ቆስለው ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናቸው ከአካባቢው የመጣው መረጃ ይገልጻል። የመጀመሪያው ቦምብ የፈነዳው መስጊድ ውስጥ በነበሩ ምዕመናን ላይ ሲሆን  ሸሽተው  የሚወጡትን ኢላማ አድርጎ ለመግደል ሁለተኛዋ አጥፍቶ ጠፊ ከመስጊዱ ውጭ የያዘችውን ቦምብ አፈንድታለች።  ቦምቦቹ የፈነዱት ምዕመናኑ የጠዋት ጸሎት ለማድረግ በተሰበሰቡበት ጊዜ ነው። በ2001 ዓም በማይዱጉሪ የተመሰረተው ቦኮ ሃራም የተባለው አክራሪ እስላማዊ ድርጅት  እንቅስቃሴ ወዲህ በሽብር ተግባር ከ200 000 በላይ የናይጄሪያ እና የአካባቢው አገር ዜጎችን መግደሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች እንዲሰደዱ ማድረጉ  ይታወቃል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ ቡድኑ በናይጄሪያ እና በአካባቢው አገሮች የተቀነባበረ ዘመቻ ተዳክሟል ተብሎ የተነገረ ቢሆንም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ከማድረስ ያልተቆጠበ መሆኑ እየታየ ነው።

 

Ø መጋቢት 4 ቀን 2008 ዓም በአይቮሪ ኮስት የወደብ ከተማ የተካሄደውን የአሸባሪዎች ግድያ ተከትሎ የፈረንሳይ መንግስት ለአስቸኳይ ጊዜ የሚደርስ አንድ ወታደራዊ ቡድን ለመላክ ያቀደ መሆኑ ተነገረ። ይህ የገለጹት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጋር  አይቮሪ ኮስትን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የፈረንሳይ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሲሆኑ ፈረንሳይ ሽብርን ለመከላከል ምን ጊዜም ከአይቮሪ ኮስት ጋር ትቆማለች ብለዋል። ፈረንሳይ በሳህል አካባቢ የታጠቁ ቡድኖችን እንቅስቃሴ ለመግታት ከ 3500 በላይ የሆነ ጦር ያሰማራች ስትሆን ባለፉት አመታት በርካታ ወታደራዊ ዘመቻዎችን አድርጋለች። አልካይዳ ኢን ኢስላሚክ ማግሬብ የተባለው ቡድን በአካባቢው የፈረንሳይ ዜጎችንና ንብረቶችን ኢላማ አድርጎ ጥቃት እንደሚፈጽም በተደጋጋሚ የዛተ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኮ ሙን ስለ ምዕራብ ሳህራ ጉዳይ የተናገሩትን በመቃወም የሞሮኮ መንግስት ሚነርሶ (MINURSO) በሚባለው በደብቡ ሳህራ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ያለውን ተሳትፎ እንደሚቀንስና በዓለም ላይ ከሚገኙት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥም ወታሮቹን እንደሚያስወጣ ገልጿል። ከተለያዩ አገሮች የመጡና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው 482 ይድረሳል የተባለው የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል በምዕራብ ሳህራ የተመሰረው በ1983 ዓም በአገሪቱ ውስጥ ውሳኔ ሕዝብ ለማካሄድ አመች ሁኔታ ለመፍጠር ሲሆን ከዚህ ውስጥ 162 የሚሆኑት የሞሮኮ ወታድራዊ መኮንኖች መሆናቸው ይታወቃል። የሞሮኮ መንግስት በመግለጫ ላይ ባንኪ ሙን ስለ አካባቢው ያደረጉት ንግግር ሕዝቡ  ዕድሉን ለመወሰን ያለውን መብት የሚገድብ ነው ብሏል። በሌላ በኩል አንድ የፖሊሳሪዩ ቃል አቀባይ የሞሮኮ መንግስት በአጠቃላይ በፍርሃት ሁኔታ ላይ ያለ መሆኑን ገልጾ በአሁን በመንግስቱ እየተደረጉ ያሉት እንቅስቃሴዎች አለም አቀፉን ህብረተሰብ ለማስፈራራትና ተጽእኖ ለማድረግ ነው ብሏል።

 

Ø ባለፈው ጥር ወር በግብጽ ውስጥ እንዳለ ተሰውሮ ከወር በኋላ አካላቱ በከፍተኛ ደረጃ አስከሬኑ ተግድቶ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ የተገኘውን ጣላናዊ ወጣት አስመልክቶ ገዳዮችን አድኖ ለፍርድ ለማቅረብ መንግስታቸው የሚቻለውን እንደሚያደርግ  የግብጹ ፕሬዚዳንት ሲሲ ገልጸዋል። የካምብሪጅ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበረውና የ28 ዓመት ጎልማሳ የሆነው ጁሊዮ ሬጂኒ  ስለግብጽ ሰራተኛ ማህበር ሁኔታ ጥናት ያደርግ የነበር ሲሆን የሲሲ መንግስትን በመውቀስ በተደጋጋሚ በጋዜጦች ላይ መፃፉ ይታወቃል። ባለፈው ጥር ወር ባልታወቀ ምክንያት ከተሰወረ በኋላ ወር ጊዜ በኋላ በካይሮ አቅራቢያ በሆነ አንድ ጉድጓድ ውስጥ አስከሬኑ ተጥሎ ተገኝቷል። በጁሊዮ አስከሬን ላይ በተደረገው ምርመራ የጎድኑ አጥንቶች የተሰባበሩ መሆናቸውና  በብልቱና በሌሎች አካሎች በኤሌክትርክ የተጠበሱ መሆናችው ታውቋል።   ጁሊያኑ የተያዘውና በምርመራ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰበት በግብጽ የጸጥታ ኃይሎች ነው የሚል ከፍተኛ ጥርጣሬ አለ። የሲሲ መንግስት ወንጀሉን በሌሎች ላይ ለማላከክ ቢሞክርም በጣሊያን መንግስት በኩል ተቀባይነት ስላላገኘ በሁለቱ አገሮች መካክል ያለው ግንኙነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ውጥረት ውስጥ እንደገባ ይሰማል።  

በሌላ በኩል በሲሲ የሚመራውን የግብጽ አምባገነን አገዛዝ የሚቃወሙ ክፍሎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተጠናከሩ መምጣታቸውን ከስፍራው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ። ከዚህ በፊት በሙስሊም ወንድማማቾች ድርጅት የሚመራው የሙርሲ መንግስት በአገሪቱ ውስጥ አለመረጋጋትና ሽብር አምጥቷል በሚል እምነት የመንግስቱን መወገድና  የወታደሩን ወደ ስልጣን መምጣት ይደግፉ የነበሩ የታወቁ የተቃዋሚ ኃይሎችና የብዙሀን ድርጅቶች  መሪዎች እንዲሁም  ባለሙያዎችና ሙሁራን  በጋዜጣ ላይ አስተያየታቸውን በመጻፍም ሆነ በይፋ በመናገር የፕሬዚዳንት ሲሲን አገዛዝ፤ አፋኝነትና ጸረ ዴሞክራሲያዊነት በማጋላጥ ተቃዋሟቸውን ማሰማት መጀመራቸው ተዘግቧል።  

 

 

 

 

የመጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ዛሬ መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ ያሉ የተለያዩ አካባቢዎች በወያኔ ልዩ የፌዴራል ጥበቃ ስር መወደቃቸው ታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ ይህ ዓይነት ጥበቃ የውጭ እንግዶች ሲመጡ ወይንም ወያኔ የራሱን በዓል ሲያከብር ብቻ እንደነበረ የሚናገሩ የዓይን እማኞች የዛሬው ልዩ ጥበቃ በምን ምክንያት እና ለምን ተግባር እንደሆነ የተናገረ ነገር ባይኖርም በተለይ አራት ኪሎ፤ አጼ ሚኒሊክ ቤተ መንግስት አካባቢው ጭምር በአግአዚ ጦር እየተጠበቀ ሲሆን አራት ኪሎ፤ ስድስት ኪሎ፤ አዋሬ፤ ካዛንችስ፤ ቀበና ፤ ሾላ ፒያሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የወያኔ ፌዴራል ፖሊስ ልዩ ኃይል ተሰማርተው እንደነበር ታይተዋል። የወያኔ ቡድን መሪዎች በመላው ኢትዮጵያ የተቀጣጠለባቸው ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ የራሳቸው ጥላ እስኪያስበረግጋቸው ድረስ እያሰጋቸው ሲሆን ይህ ስጋትና ፍርሃታቸው ወደ ሕዝብ ለመመለስ ገዳይ ጦራቸውን በከተሞች ውስጥ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ በማሰማራት አስፈራርቶና አሸብሮ ለመሰንበት የሚጠቀሙበት ዘዴ እንደሆነ ይታወቃል።

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች የሕዝብን ጥያቄና አቤቱታ በአግባብ ማስተናገድ ተፈጥሯቸው ስላልሆነ ሁልጊዜም ምላሻቸው ግድያና እስር መሆኑ ይታወቃል። በደቡብ ኢትዮጵያ ጎሙ ጎፋ ውስጥ የኮንሶ ሕዝብ ያቀረበው አስተዳደራዊ ጥያቄ የወያኔ አገዛዝ ግድያና በእስር ለማቆም ከሳምንታት ጀምሮ በግድያ የሰለጠነው ጦሩን በኮንሶ አስፍሮ ግድያ መፈጸሙ የሚታወቅ ሲሆን ይህ የሕዝብ ጥያቄና ተቃውሞ እንደገና ተቀስቅሶና አገርሽቶ በመነሳቱ የወያኔ መሪዎች የተመደውን የጥይት ምላሽ በመስጠታቸው ሶስት የኮንስ ነዋሪዎች መገዳላቸውና ሌሎቹ ደግሞ መቁሰላችው ተገልጿል። የወያኔ ነፋስ ገዳይ ጦርና የአካባቢዎች ፖሊስ የኮንሶ ከተማን በመክበብና በመውረር ነዋሪውን ጭንቀት ውስጥ እየተከቱትና ወታደራዊ ሽብርን በመላ ኮንሶ ለማድረስ ጥረት እያደረጉ መሆናችው ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ የወያኔ ጦርና የፖሊስ ኃይል የኮንሶ ከተማ ነዋሪን በግዳጅ የድጋፍ ሰልፉ እንዲያደርግ ቀስቀሳ መጀመራችው ታውቋል። በኮኖስና በአጎራባች ከተሞች ውጥረቱ ከፍተኛ ሲሆን የወያኔ ወታደሮች የሕዝብን ንብረት ዘርፈው እየወሰዱ መሆናቸው ተገልጿል። የፖሊትካ ታዛቢዎች የሕዝብን ጥያቄ በአግባብ መመለስ ብቻ የተቃውሞውን ጥያቄ የሚመልስ  ውጥረትን የሚያላላ መሆኑ ታውቆ እስካልተሰራበት ድረስ ወያኔ በኃይልና በግዳጁ ሊፈጽመው የሚችል አንዳች ነገር የለም በማለት አስተያየት ይሰጣሉ።

 

Ø በናዝሬት የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ እንደገና የተቀስቀሰ ሲሆን ወያኔ አግአዚ ጦሩን በመላክ ተማሪዎቹ ን ሲደበድብ የቆየ ከመሆኑ በላይ በጅምላ ያሰራችው መሆኑ ታውቋል። ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓም ወደ አዳማ ዩኒቨርስቲ ዘልቆ የገባው የወያኔ አግአዚ ጦር ተማሪዎችን በማፈስ በናዝሬት ስታዲዮም እንዳሳደራቸው ሲታወቅ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የዩኒቨርስቲው የሠት ተማሪዎች መኝታ ክፍሎች በእሳት መቃጠላችውና ጉዳት እንደደረሰባችው ተገልጿል። በዛሬው ዕለት ተማሪዎቹችን ወደ አልታወቀ ቦታ ይዘዋወራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለተማሪዎቹ ምንም ዓይነት ምግብም ሆን ልብስ እንዳይገባላቸው ተከልክሏል። በአዳም ዩኒቨርስቲ ትምህር ሙሉ በሙሉ የተቋረጠ መሆኑም ከናዝሬት የተገኘው መረጃ ያመልክታል። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስተር ተብየው ለተፈጠረው ችግር ለጠፋው ህይወት ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ብቻ ይቅርታ ይጠይቀ እንጅ በሕዝብ ልጆች ላይ የሚፈጸመው ግድያ እስርና ድብደባ ግን አሁንም እንዳልቆመሁሉ ህዝባዊ ተቃውሞና ቁጣውን በኃይልና በጭካኔ ለማቆም የተደረገው ሙከራ ውጤት አልባ መሆኑ ታይቷል።

 

Ø የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በወያኔ ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው የጅምላ አፈሳና እስር እንደተፈጸመባቸው ከአዋሳ የመጣው መረጃ ያለመክታል። እንደ መረጃው ከሆነ የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መጋቢት 3 ቀን 2008 ዓ.ም. ማምሻውን ተደብደበውና ታስረው ንጋቱ ላይ በከባድ ካሚዮን ተጭነው ወደ አልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን አስረድቷል። ለተማሪዎቹ የጅምላ አፈሳና እስር ምክንያት የሆነው በአዋሳ ስታዲዮም ተዘጋጅቶ በነበረው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ተቃውሞ የቀሰቀሳችሁ እናንት ናችሁ በሚል ሲሆን የወያኔው አግአዚ ጦር በተማሪዎቹ ላይ በመኝታ ክፍሎቻቸው ሳይቀር በመግባት ድብደባ መፈጸሙንና አስሮ መውሰዱን ተብራርቷል። የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የተባለው ዮሴፍ ማሞ የወያኔን ጦር ወደ ዩኒቨርስቲ ግቢ በማስገባትና ተማሪዎችን በማስደብደብ አቢይ ሚና መጫወቱ ተደርሶበታል።

Ø  

Ø በሚቀጥለው እሁድ መጋቢት 11 ቀን  በናይጀር በሚደረገው የሁለተኛ ዙር ምርጫ የአሁኑ ፕሬዚዳንት የቅርብ ተፎካካሪ የነበሩት የተቃዋሚው ክፍል መሪ ሃማ አማዶ ከታሰሩበት እንዲፈቱ የቀረበውን ማመልከቻ አንድ የናይጀር የይግባኝ ፍርድ ቤት ሳይቀበለው ቀርቷል። ሃማ አማዶ ህጻናትን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ አስተላልፈዋል በሚል ማስረጃ በሌለው ክስ ተጠርጥረው  ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ ታስረው የሚገኙ ሲሆን ከእስር ቤት ሆነው ባደረጉት ውድድር በመጀመሪያ ዙር በተደረገው ምርጫ 18 ከመቶ አግኝተው እንደነበር ተገልጿል። በመጀመሪያ ዙር ምርጫ አሁን በስልጣን ያሉት ፕሬዚዳንት ማሃማዱ ኢሱፉ (Mahamadou Issoufou) የምርጫውን 48 ከመቶ ብቻ በማግኘታቸው ምክንያት አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት ያልቻሉ ሲሆን የተቃዋሚ ኃይሎች ምርጫው የተጭበረበረ ነው በማለት ክስ ማቅረባቸው ይታወቃል። በሃማ አማዶ ላይ  የቀረበውን ክስ አስመልቶ ፍርድ ቤት ቤቱ ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 008 ዓም ውሳኔ መስጠት የነበረበት ሆኖ ሳለ የውሳኔውን ቀን ወደ መጋቢት 19 ቀን 2008 ዓም  በማስተላለፉ ምክንያት በውድድሩ ወቅት ሃማ አማዶ በእስር ቤት ሆነው መቆየት ግድ ሆኖባቸዋል። ጠበቆቻቸው በዋስ እንዲፈቱ ያቀረቡትን ማመልከቻ አልቀበልም ማለቱ እና የውሳኔውን ቀን ከምርጫው አንድ ሳምንት በኋላ ማስተላለፉ ፍርድ ቤቱ የአገዛዙ ተባባሪና ደጋፊ መሆኑን አሳይቷል የሚሉ ወገኖች በርካታ ናቸው።  

 

Ø አንድ የናይጄሪያ ፍርድ ቤት የናይጄሪያ የኢኮኖሚና የገንዘብ ወንጀል ለመመርመር የተቋቋመው ኮሚሽንና የወታደሩ ተቋም የሚከተሉት  የአምባገንነ አገዛዝ አሰራር ነው ካለ በኋላ በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ተይዞ ክስ ሳይቀርብበት ከሶስት ወር በላይ በእስር ላይ የሚገኝ አንድ የኮሎኔል ማዕረግ ያለው ግለሰብ ባስቸኳይ እንዲፈታ ጠይቋል። ኮሎኔሉ ቀደም ብሎ 2.9 ሚሊዮን ዶላር በማጉደል በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም አማካሪ የሚስተር ዳሱኪ ረዳት ሲሆን እስካሁን ክስ ያለተመሰረተበት መሆኑ ይታወቃል። ቀደም ብሎ ሚስተር ዳሱኪ ከእስር እንዲፈቱ ሶስት የተለያዩ ፍርድ ቤቶች  ውሳኔ ቢያስተላልፉም የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ግለስቡ በእስር እንዲቆዩ አዘዋል። አንዳንድ የህግ ሰዎች ፕሬዚዳንቱ በሙስና ስም የሚወስዱት እርምጃ የፖለቲካ በቀል ነው ሲሉ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ደግሞ ከመንግስት ባለስልጣኖች በተጨማሪም  ወታደሮቹም ሆኑ ዳኞች በሙስና የተጨማለቁ ናችው በማለት ይከሷቸዋል።

በተያያዘ ዜና የመንግስት ንብረት የሆነውና የናይጀሪ ናሽናል ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን (Nigeria National Petrolium Corporation) የሚባለው የናይጄሪያ ነዳጅ ድርጅት እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2014 የበጀት አመት ወደ መንግስቱ ግምጃ ቤት ማስተላለፍ የነበረበትን 16 ቢሊዮን ዶላር ያላስገባ መሆኑ በምርመራ ተደርሶበታል። የዛሬ ሁለት ዓመት በቀድሞ የናይጄሪያ መንግስት አስተዳድር ወቅት ድርጅቱን ሲመሩ  የነበሩት ግለሰብ 20 ቢሊዮን ዶላር አጉድለዋል ተብለው መከሰሳቸው ይታወሳል። ናይጀሪያ በያመቱ በአማካይ 77 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ነዳጅ የምታመርት ስትሆን በርከት ያለው ገንዘብ በሙስና ይበዘበዛል ይባላል።

 

Ø እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ራባት በሚባለው የሞሮኮ ዋና ከተማ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሆነ ሕዝብ ወደ አደባባይ ወጥቶ በቅርቡ የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ስለምዕራብ ሳህራ ጉዳይ የሰጡትን አስተያየት አውግዟል። ዋና ጸሐፊው ሰኞ ዕለት ኒውዮርክ በሚገኘው በተመድ ጽሕፈት ቤታቸው የሞሮኮን አምባሳደር ጠርተው ባነጋገሩበት ወቅት በእሳቸው ላይ በሞሮኮ ባለስልጣኖች የተሰነዘሩት ስድቦችና ክሶች በጣም ያሳዘናቸውና ያበሳጫቸው መሆኑን ገልጸዋል ተብሏል።  ሕዝብ አደረገ በሚባለው ሰላማዊ ሰልፍ  የመንግስት ባለስልጣኖች መኖራቸውን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል ተብሏል። በማዕድን ሀብቷ የምትታወቀው የምዕራብ ሳህራ ግዛት በ 1967 ዓም ከስፔን ቅኝ ገዥነት ነጻ ስትወጣ ሞሮኮ በኃይል ወደ ግዛቷ በማጠቃለሏ ፖሊ ሳሪዮ በተባለው ድርጅት አማካይነት ለረጅም ዓመታት የትጥቅ ትግል  ሲካሄድ መቆየቱ ይታወቃል። በ1982 ዓም በተመድ አማካይነት በተጻራሪ ወገኖች መካከል ድርድር ተካሄዶ ጉዳዩን በውሳኔ ሕዝብ ለመጨረስ ስምምነት ቢደረግም የታቀደው ውሳኔ ሕዝብ እስካሁን አለመካሄዱ የተመድ ባለስልጣኖችን ሲያሳስብ ቆይቷል። ባለፈው ሳምንት ባንኪ ሙን በአልጀሪያ በካምፕ ውስጥ በስደት ላይ የሚገኙትን የምዕራብ ሳህራ ዜጎች  ሁኔታ አይተው አገርን በሃይል የመያዙ ሁኔታ አብቆቶ በስምምነት ስደተኞቹ ወደ አገራቸው መመለስ አለባችው የሚል ቃል በመናገራቸው የሞሮኮን ባለስልጣኖች ማበሳጨቱ  ይታወሳል።

 

Ø ማይንማር ወይም በቀድሞ ስሟ በርማ የምትባለው አገር ላለፉት 50 ዓመታት በወታደራዊ አምባገነን አገዛዝ ስር ስትማቅቅ ቆይታ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ አዲስ ፕሬዚዳንት አግኝታለች።  ናሽናል ሊግ ፎር ዴሞክራሲ የተባለውን ፓርቲ በመወከል የተወዳደሩት ሂትን ኪያው ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ እሳቸውም የታዋቂዋ የፖሊቲካ እንቅስቃሴ መሪ የኦንግ ሳን ሱ ኪ የቅርብ ረዳት ናቸው ተብሏል። ኮንግ ሳን ሱ ኪ የፓርቲው መሪ ቢሆኑም ከውጭ ዜጋ ወልደዋል በሚል ምክንያት በህገ መንግስቱ እንዳይወዳደሩ ቢከለሉም በፓርቲ መሪነታቸው ከጀርባ ሆነው የመንግስቱን ስራ ሊያካሂዱ እንደሚችሉ ገልጸዋል።      

 

 

 

መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø እሁድ መጋቢት 4 ቀን 2008 .. ግራንድ ባሳም በተባለው የአይቨሪ ኮስት የመዝናኚያ ወደብ ሲዝናኑ በነብሩ ቱሪስቶች ላይ የታጠቁ ሰዎች ተኩስ ከፍተው 16 ሰዎች የገደሉ መሆናቸው ተነገረ። ወደቡ በአገሬውም ሆነ በውጭ ሰዎች የሚዘወተር ሲሆን ከሞቱት መካከል አራቱ የፈረንሳይና የጀርመን ዜጎች መሆናቸው ታውቋል። ገዳዮች በሙሉ መገደላችው ሲነገር በእስላማዊ ማግረብ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የአልቃይዳ ቅርንጫፍ ደግሞ ለድርጊቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። ለረጅም ጊዜ የፖለቲካ መረጋጋት የነበረባት አይቮሪ ኮስት አልፎ አልፎ የአልቃይዳ ጥቃት ሲገጥማት መቆየቱ ይታወቃል።

Ø የግብጽ የፍርድ ሚኒስትር ባለፈው አርብ በተሌቪዥን በባደረጉት ቃለ ምልልስ ውስጥ  ህግን ካፈረሱ ነቢዩ መሀመድን እንኳ አስራለሁ የሚል ቃል ስለተናገሩ  ከስራ የተወገዱ መሆናችው ተገለጸ። የፍርድ ሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም የግብጽ ይግባኝ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩ ሲሆን የሙባረክን መንግስት የገለበጠውን ሕዝባዊ እንቅስቃሴም ሆነ የእስልምና ወንድማማችነት ተብሎ የሚጠራውን ድርጅት በጽኑ ይቃወሙ እንደነበር ይታወቃል። የፍርድ ሚኒስትር ቃሉን ከተናገሩ በኋላ ይቅርታ ቢጠይቁም  የግብጽ መንግስት ባለማመንታት ከኃላፊነታቸው እንዲወገዱ አድርጓል። የዳኖችም ማህበር ግን በእሳቸው ላይ የተወሰነውን ውሳኔ በመቃወም ባወጣው መግለጫ ባፍ ወለምታ በተደረገ ስህተት የተወሰደው ቅጣት አግባብ አይደለም ብሏል።

Ø በተያያዘ ዜና ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ተቋም ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. የእስልምናን ሃይማኖት ሰድባችኋል ተብለው የሶስት ዓመት ጽኑ አስራት የተፈረደባችው ሶስት የክርስትና እምነት ተከታይ የሆኑ ወጣቶች እንዲለቀቁ ጠይቋል። ድርጅቱ ወጣቶቹ በቀልድ መልክ የሰደቡት በእስልምና ስም በአሸባሪ ድርጊቶች ላይ የተሰማሩትን ሃይሎች እንጅ ሃይማኖቱን ባለመሆኑ ምህረት ሊደረግላችው ይገባል ብሏል።

 

Ø አውሮፓው ኅበረት ለብሩንዲ ሲሰጥ የቆየውን ቀጥተኛ እርዳታ ለጊዜው ያቋረጠ መሆኑን አሳታወቀ። የአውሮፓው ህበረት ባወጣው መግለጫ በብሩንዲ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ እየሆነ የቀጠለ በመሆኑ ህብረቱ የጠቋማቸው የሰላም ሀሳቦች  በብሩንዲ መንግስት ተቀባይነት አግኝተው  ተግባራዊ እስኪሆኑ ድረስ እርዳታው ይቋረጣል ብሏል። ለሰብአዊ ጉዳዮች የሚሰጡት እርዳታዎች ግን አይቋረጡም በማለት መግለጫው አክሎ ገልጿል።  በብሩንዲ ከፍተኛ ግምት ያለው የመንግስት ወጭ ይሽፈን የነበረው ከአውሮፓው ህብረት በሚሰጥ እርዳታ ሲሆን የተደረገው ጊዜያዊ ማዕቀብ የመንግስቱን እንቅስቃሴ በጽኑ ሊጎዳው ይችላል የሚል ግምት ተወስዷል።

 

 

Ø በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሪነት  በሊቢያ እንዲቋቋም ታቅዶ የነበረው የአንድነት መንግስት ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2008 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት አካል ምክር ቤት አብዛኞቹ አባሎች የመንግስቱን መቋቋም የደገፉ መሆናቸውን ገልጾ ከዚህ በኋላ የመንግስቱ አካል ስራውን ሊጀምር ይችላል ብሏል። የአውሮፓ ህብረት አገሮችና አሜሪካ መግለጫን ወዲያውኑ የተቀበሉት ሲሆን የአንድነት መንግስቱ በሊቢያ ውስጥ ህጋዊ የሆነና ተቀባይነት ያለው ብቸኛው መንግስት ይሆናል ብለዋል። ከአንዳንድ ክፍሎችና የሚሊሺያ መሪዎች አሁንም ተቃውሞ የሚሰማ በመሆኑ የአንድነት መንግስቱ አካል ተቋቋሞ ስራውን የሚጀምርበት ሁኔታ አሁንም አስተማማኝ አይደለም በማለት ጉዳዩን የሚከታተሉ ሰዎች ይተቻሉ።

 

Ø በማሊ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ የተመደበ አንድ የቻድ ዜግነት ያለው ወታደር ሁለት ባልደረቦችን ገድሎ አንደኛውን ያቆሰለ መሆኑ ተነገረ። ገዳዩ በቁጥጥር ስር የተደረገ ሲሆን ግድያውን ለመፈጽም ያነሳሳው ምክንያት ምን እንደሆን እየተመረመረ ነው ተብሏል። በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወታደሮች ተመሳሳይ አደጋ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያው አለመሆኑ ይታወቃል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኪዳል በሚባለው የቻድ እተማ በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ይሰራ የነበረ ሌላ የቻድ ዜግነት ያለው ግለሰብ አንድ ወታደራዊ ኮማንደርና አንድ የህክምና ዶክተር መግደሉ ይታወሳል። 

 

 

 

 

መጋቢት 3 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

·       የወያኔ ቡድን መሪዎች ለስልጣናቸው  ናቸው ብለው የሚጠረጥሯቸውን  በሙሉ መግደል ማሰርና ማግለል የዘወትር ተግባራቸው ሲሆን በራሳቸው የጦር ኃይል ውስጥም  ጦሩን ያሳምጻሉ ተብለው የጠረጠሩትን  ሁሉ ከስብሰባና ከግምገማ አዳራሽ እየወሰዱ መዳረሻቸውን እየጠፉ መሆኑን ከወያኔ መከላከያ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለከታል። በዚህ መሠረት በወያኔ ሰሜን ዕዝ ውስጥ የከፍተኛ መኮንኖች ግምገማ ላይ ያነሱት ሃሳብ አመጽ ቀስቃሽ ነው፤ አፍራሽ ነው ብሄራቸው ተጠርጣሪ ነው በሚል ሶስት /ሎኔል ሁለት 3ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው መኮንኖች በወያኔ ወታደራዊ ደህንነት ተይዘው ከተወሰዱ በኋላ መድረሻቿው መጥፋቱ ታውቋል። ይህ በሰሜን ዕዝ የተፈጸመው ሁኔታ መረጃዎችና ወታደራዊ አዛዦችችን የበለጠ ስጋት ላይ ጥላችቸው። ተይዘው መዳረሻችው የጠፋ መኮንኖች ማንነትና ብሔራቸው ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን በርካታ የጦር አባላት ግን ሁኔታውን በቅርብ አየተከታተሉት መሆኑ ተገልጿል።

 

·       የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ኃይለለማሪያም ደሳለኝ ለወያኔው ፓርላማ ባደረገው ንግግር የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ከመልካም አስተዳደር የመጣ ችግር ነው በማለት በማለት ጥፋቱን አምኖ በእንቅስቃሴው የተገደሉትን ወገኖች  ይቅርታን ይጠይቅ እንጅ ተቃውሞው ጸረ ሰላም ኃይሎች ያዘጋጁት ነው በማለት የተናገረ ከመሆኑም በላይ ለሞቱ ወገኖች ካሳ ለመክፈል እንዲሁም ገዳዮችን ፍርድ ቤት ለማቅረብ መዘጋጀቱን የሚገልጽ ቃል አለመተንፈሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው የፓርላማ ንግግር ከተራ ፕሮፓጋንዳ ያለፉ አልሆነም ተብሏል።  ተቃውሞ አሰምታችኋል፤ ቁጭታችሁን አደባባይ ገልጻችኋል ተብለው በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች በእስር እየማቀቁማና እየተሰቃዩ ስለ እነርሱ አንዳች ነገር ሳይተነፍስ የመልካም አስተዳደር ጉድለትና ስራ አጥነት የፈጠረው ተቃውሞ ነው ማለት ብቻ ምንም ማለት እንድልሆነ የፖለቲካ ታዛቢዎች ይናገራሉ። ወያኔ የችግሩ እናት መሆኑን ካመነ ችግሩን ተከትሎ ለመጡት ችግሮች ሙሉ ኃላፊነት መወሰድና ማስታካከል ይገባዋል በማለት አስተያየታቸውን አክለው ይገልጻሉ።

 

·       የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያዋን ሙስሊሞች ላይ ያወጀውን ጦርነት በመቃወም በኢትዮጵያ ላይ ያለውን ጭቆዎና እንዲያበቃ የድምጻችን ይሰማ በማለት በመረጡት ጊዜና ቦታ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ የቆዩት የሙስሊሙ ህብረተሰብ አርብ መጋቢት 2 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ  በቢር ኑር መስጊድ ታላቅ ተቃውሞ ማድረጋቸው ታውቋል። የወያኔ ፖሊሶችንና የደህንነት ኃይሎችን በማዘናጋት የተደረገው ተቃውሞ የወያኔ ፖሊሶችን ያስደነገጠ እንድነበር ታውቋል። በዕለቱ ሕዝበ ሙስሊሙ ከያዛቸው መፈክሮች ውስጥ የተቀበረች ፍትህ ቀባሪዋን ትቀብራለች የታሰሩት  ይፈቱ ብሔራዊ ጭቆና ያብቃ መብታችን ይከበራል የሚል ይገኙበታል። ሕዝበ  ሙስሊሙ የተቃውሞ ድምጹን በስለማዊ መንገድ እንዳያሰማ የወያኔ ደህንነትና የፖሊስ ኃይሎች አባላት ጥበቃ ያድርጉ እንደነረ ታውቋል። ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከሳምንታታት በፊት በታላቁ አንዋር መስጊድ ባለፈው ሳምንት በቢኒ መስጊድ ሰላማዊ የሆነ ተቃዋሞ ማድረጋቸው ይታወሳል። \

 

 

·       ከሁለት መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ በሺህ የሚቆጠሩ ሲታስሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲደበደቡ ድምጻቸውን ያላሰሙ የሃይማኖት እንዲሁም ገዳዮችን አሳሪዎችንንና ደብዳበዎችን ሳያወግዙ የቆዩ  የሃይማኖት አባት ተብዮዎች በሻሽመኔ ከተማ ባካሄዱት ስብሰባ በሕዝብ ተቃውሞና ቁጣ ለጠፋው ንብረትና ለተቃጠለው ሀብት እጅጉ አዝነናል ማለታቸው ትዝብት ላይ የጣላቸው ሲሆን የዘረኛውና የአምባገነኑ አገዛዙ ሌላ መሳሪያ መሆናቸውን በግልጽ ለሕህዝብ አስይተል። በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶድክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት ሃይማኖት መሪዎች የተገኙ ሲሆን በወያኔ አገዛዝ የሚጨቆነው ሕዝብ ከተቃውሞና ቁጣ ተቆጥቦ በልማት ስራ ላይ እንዲትተጋ ትምህርት ለምስጠት ቃል ገብቷል። የሃይማኖት መሪዎቹ ሕዝብን በግብረ ገብነት አንጸው ፈሪሃ እግዚእብሔር እንዲኖረው እንዲሁም ለመክራውና ለስቃዩም ድምጽ በመሆን ለተገፋትና ለተጨቆኑ አቤት ባይ መሆን ሲገባቸው ከገዳይና ከአሳሪ ጎን መቆማቸው የወያኔ ጉዳይ ፈጻሚ ካድሬ እንጅ የህዝብ እረኛና ጠባቂ አለመሆናቸውን በግልጽ አሳይተዋል ተብሏል።

 

·       ከሁለት ዓመት በፊት ከኩዋላ ላምፑር ወደ ፔኪንግ ሲጓዝ በረራ ላይ እያለ መዳረሻው ጠፍቶ የቀረውና በበረራው ቁጥር MH370 እየተባለ የሚጠራው  የማሊዢያ አውሮፕላን ስብርባሪ አካል ነው ተብሎ የሚጠረጠር የብረት ቁራጭ በሞዛምቢክ ወደብ የተገኘ መሆኑ ሲገለጽ በቅርቡ ለምርመራ ወደ አውስትራሊያ ይላካል ተብሏል። ይህንን አንድ ሜትር ርዝማኔ ያለውን የብረት ቁራጭ ያገኘው ባለፈው ታኅሳሥ ወር የእረፍት ጊዜውን በሞዛምቢክ የወደብ መናፈሻ ሲዝናና የነበረው የደቡብ አፍሪካ ወጣት ሲሆን ብረቱን ወደ ቤቱ ይዞ ከመጣ በኋላ ለባለስልጣኖች ያስረከበ መሆኑን ገልጿል። የደቡብ አፍሪካ የትራንስፖርት ጉዳይ ባለስልጣኖችም ዕቃውን መረከባቸውን ገልጸው እቃው ሰለጠፋው አውሮፕላን ጉዳይ ኃላፊነት ወደተሰጠው አገር ወደ አውስትራሊያ የሚላክ መሆኑን ገልጸዋል። በካምቤራ የሚገኘው የአውስትራሊያ የትራንስፖርት ሚኒስትርም ሁኔታውን አረጋግጦ ከማሌዢያና ከደቡብ አፍሪካ ባለስልጣኖች ጋር እየመከረ መሆኑን አሳውቋል።  በበረራው ቁጥር  MH370 የሚታወቀው የማሊዢያ አውሮፕላን 239 መንገደኞችን አሳፍሮ ከኩውላ ላምፑር ወደ ፔኪንግ ሲጓዝ በበረራ ላይ እንዳለ ተሰውሮ መጥፋቱ ይታወሳል። ከአየር ላይ ወርዶ ባህር ውስጥ  ሰጥሟል የሚል ግምት ቢሰጥም እስካሁን ድረስ የወደቀበት ቦታም ሆነ የአውሮፕላኑ አብዛኛው ክፍል ያልተገኘ መሆኑ ተነግሯል። ባለፈው ሐምሌ ሪዩኒየን በምትባልና በህንድ ውቅያኖስ ላይ በምትገኝ ደሴት አንድ ለመዝናናት የመጣ  የፈረንሳይ ዜጋ የአውሮፕላኑ ክንፍ አካል የሆነ ስብርባሪ ክፍያ ማግኘቱና በምርመራም የአውሮፕላኑ አካል ሆኖ መረጋገጡ አይዘነጋም።

 

·       የአልጄሪያ የጸጥታ ኃይሎች ሐሙስ ዕለት ጉማር በምትባለው  በአልጀርያና በቱኒዚያ ወሰን  አቅራቢያ በምትገኘው ከተማ ባካሄዱት አሰሳ ሶስት አሸባሪዎችን ገድለው ሶስት ስቲንገር የተባለ የጸረ አውሮፕላን ሚሳየል መተኮሻ መሳሪያ ያገኙ መሆናቸውን ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ከሶስቱ ስቲንገሮች ሌላ 20 የሚሆኑ የካላሽንኮፍ መሳሪያዎች ሌሎች ሶስት የሚሳየል መተኮሻዎችና እንዲሁም ቦምቦችና ጥይቶች ያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል። አልጀሪያ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ እስላማውያን አክራሪዎችን ስትዋጋ የቆየች ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህም አክራሪ አሸባሪዎች በቱኒዚያ የተለያዩ ጥቃት መፈጸማቸው ይታወቃል።

 

·       በሊቢያ እንዲቋቋም የተፈለገው የህብረት መንግስት እውን እንዳይሆን እንቅፋት በሆኑት የሊቢያ ባለስልጣኖች ላይ ማዕቀብ ለማድረግ  የአውሮፓው ህብረት አገሮች እየመከሩ መሆናቸው ተነገረ። የአብዛኛውን የአውሮፓ አገሮች ስምምነት አግኝቷል የሚባላው የማዕቀብ ሀሳብ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በተግባር ይውላል ተብሏል። ማዕቀቡ የሚጣልባቸው ባለስልጣኖች እነማን እንደሆኑ በይፋ ባይነገርም በትሪፖሊ በሚገኘው የመንግስት አካል ውስጥ የፓርላማው መሪ  የሆኑት ኑሪ አቡ ሳህማና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካሊፋ ጉዌል ሊሆኑ እንደሚችሉ አንድ ስማቸውን መግልጽ ያልፈለጉ የአውሮፓው ህብረት ባለስልጣን ጠቁመዋል።  ለረዥም ጊዜ የሊቢያ መሪ ሆነው የቆዩት ጋዳፊ የዛሬ አምስት አመት በሕዝብ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከስልጣን ቢወገዱም በባዕድ ጣልቃ ገብነትና አክራሪ ኃይሎች ባደረጉት እንቅስቃሴ ምክንያት በአገሪቱ  ሁለት ተጻራሪ የሆኑ ራሳቸውን መንግስት የሚሉ አካሎች መቋቋማቸው ይታወሳል።

 

·       በሲየራ ሊዮን ውስጥ በነበረው የእርስ በርስ ጦርነት ከፍተኛ ወንጀል በመፈጽሙ የአስራ አምስት አመት እስራት ተፈርዶበት የነበረውና የእስራት ዘመኑን ሳይጨርስ በምህረት ተለቆ የነበረው የሚሊሺያ መሪ እንድገና መታስሩ ተነገረ። ሞይኒና ፎፋና የተባለው በአገሪቱ የርስ በርስ ጦርነት በተካሄደበት ወቅት በርካታ ሰው በመግደሉና ብዙዎቹንም ከእነ ህይወታቸው እንዲቃጠሉ በማድረጉ በልዩ ፍርድ ቤት የአስራ አምስት ዓመት እስራት ተፈርዶበት ታስሮ የቆየ መሆኑ ይታወቃል።  ሁለት ሶስተኛውን የእስራት ጊዜ በማገባደዱ በምህረት ተፈትቶ የነበረ ቢሆንም ሲፈታ ቃል የገባውን ግዴታ አላከበረም በሚል ምክንያት ትናንት አርብ መጋቢት 2 ቀን 2008  እንደገና በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል።

በተያያዘ ዜና በሲየራ ሊዮን ጽንስን ለማስወረድ የሚፈቅደው ረቂቅ ህግ የአገሪቱ ምክር ቤት ቢወስንም ፕሬዚዳንቱ ህጉን ፈረመው ለማጽደቅ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ ይህንን እርምጃ የወሰዱት በሃይማኖት አባቶች ግፊት ሲሆን ህጉ ሊጸድቅ የሚችለው ሕዝቡ በውሳኔ ህዝብ ድምጽ ሰጥቶ ከደገፈው ብቻ ነው ብለዋል።

 

 

 

 

 

መጋቢት 2 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የኢትዮጵያና ኬኒያ ድንበር አቋርጠው ወደ ኬኒያ የሚገቡ ስደተኞች ጉዳይ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን የኬኒያ ጋዜጣ ዴይሊ ኔሽን  ባለሥልጣኖችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል። ጋዜጣው ድንበር እየሰበሩ ወደ ኬኒያ የሚገቡ የኢትዮጵያ ስደተኞች ለኬኒያ ፀጥታ ስጋት እየሆነ መምጣቱን በመግለጽ ተጨማሪ የድንበር ጥበቃና ቁጥጥር እንዲደረግ እየተጠየቀ መሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያዊ ስደተኞች ኬኒያን እንደመሸጋገሪያ እንደሚጠቀሙባትና አብዛኛዎቹ ወደ ደቡብ አፍሪካ አውሮፓና ዓረብ አገራት እንደሚሻገሩባት ገልጿል። ከኢትዮጵያ ወደ ኬኒያ በአማካይ በየቀኑ 30 ስደተኞች እንደሚገባና አንዳንዶቹ ተይዘው በኬኒያ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጿል። በርካታ የፖሊቲካ ተመልካቾች የወያኔ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ከሀገሩ እየወጣ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገሩ እንዲልክ ምኞትና ፍላጎቱ መሆኑን በመግለጽ ነገር ግን በስደት የሚደርስባቸው የማያንስ በመሆኑ በሀገራቸው የወያኔን ዘረኛ አገዛዝ ለመጣል በቁርጠኝነት ለመታገል ቢሞክሩ ውጤቱ የግልና ሀገራዊ ይሆናል ይላሉ።

 

Ø የ24 ዓመቱ የወይኔ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በሁሉም  የኢትዮጵያ ክፍሎች ሕዝባዊ  ተቃውሞና ቁጣ እየገጠመው ባለበትና በነፍስ ገዳዩ አግአዚ ጦር ግድያ ድብደባና እስር ወያኔ  መልስ እየሰጠ በሚገኝበት ሰዓት ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣው በቡድንና  በድርጅት ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችም በወያኔ ላይ ያላቸውን ጥላቻ በልዩ ልዩ መንገድ እየገለጹ ይገኛሉ። ንብረትነቱ የወያኔ ባለሥልጣናት የሆኑ የሰላም አውቶቡስና የስኳይ አውቶቡሶ ማንነቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሰው መስታወታቸው የተሰበረ መሆኑ ታውቋል።ከአዲስ አበባ መቀሌና ከአዲስ አበባ ወልደያ ይጓዙ የነበሩ አውቶቡሶች ሰንበቴ በተባለ ቦታ በአንድ ግለሰብ የድንጋይ ውራ መስተዋታቸው የተሰባበረ ሲሆን በተመሳሳይ መልክ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጉዳት የደረሰባቸው አውቶቡሶች በርካታ ናቸው። በወያኔ ላይ ያነጣጠረው ጥላቻ የሥርዓቱ ዘረኛና አረመኔ  አገዛዝ ግለሰቦች ቁጣቸውን በወያኔ ከሕዝብ እየተነጠለ መሄዱን በግልጽ የምያሳይ መሆኑ ተመልካቾቹ ይናገራሉ።

 

 

 

Ø ከደቡብ ሱዳን ወታደሮች ጋር ተባባሪ ሆኖ የሚንቀሳቀስ አንድ የሚሊሺያ ቡድን በርካታ ሴቶችን አስገድዶ ደፍሯል በማለት የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ። ባለፈው ዓመት ዩኒቲ ከሚባለውና የነዳጅ አምራች ከሆነው አካባቢ ብቻ ከ 1300 ሴቶች በላይ በመገደድ የተደፈሩ መሆናቸው ተገልጿል። ሴቶችን የመድፈር ሁኔታ በጣም አሰቃቂ መሆኑን ድርጅቱ ገልጾ አንዲት ሴት የአስራ አምስት ዓመት ልጅዋ ከ 10 በበለጡ ሰዎች ስትደፈር በአይኗ ተመልክታለች በማለት የሁኔታውን አሳሳቢት ገልጿል። በተጨማሪም የመንግስት ወታደሮች ከ60 በላይ የሚሆኑ የደቡብ ሱዳን ዜጎች በኮንቴነር ውስጥ አለአየር በሙቀት አፍነው  መግደላቸውንና  አስከሬናቸውንም ሳይቀብሩ  ሜዳ ላይ የበተኑ መሆናቸውን መሆናቸውን አምነስቲ  በሌላ ዘገባ አስፍሯል። የደቡብ ሱዳን መንግስት ድርጊቱ መካሄዱን አስተባብሎ ወታድሮቹ በጦርነት ወቅት የዓለም አቀፍ ሕግን እንዲሚከተሉ አስረድቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ አርብ መጋቢት 2 ቀን 2008 ዓም ለሕዝብ ይፋ የሆነው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ዘገባ በደቡብ ሱዳን ህጻናትና አካለ ስንኩላን ከእነህወይታቸው እንደሚቃጠሉና ለዋጋ ክፍያ ሴቶች እንደሚደፈሩ መረጃ መኖሩን በመጥቀስ ዘግቧል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኃላፊ በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው የሰብአዊ መብት ወንጀል በዓላም ከሚደርሱ ወንጀሎች የከፋ ሆኖ ሳለ የዓለም አቀፉ ህብረተስብ ችላ ማለቱ ያስገረማቸው መሆኑን ገልጸዋል።  አያይዘውም በሱዳን ተጻራሪ ቡድኖች ላይ የመሳሪያ ማዕቀብ እንዲደረግባቸውና እንዲሁም ጥፋተኞቹ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት የሚቀርቡበት ሁኔታ እንዲፈጠር ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ሀሳብ የሚያቀርቡ መሆናቸው አስታውቀዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት በደቡብ ሱዳን በ10 ሺዎች  የሚቆጠሩ ሰዎች መገደላቸውና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ተዘግቧል።

 

Ø የአንጎላው ፕሬዚዳንት ሚስተር ጆሴ ኤዱዋርዶ ዶ ሳንቶስ በ2010 ዓም በሚደረገው የአገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ እንደማይወዳደሩ አስታወቁ። ከ 37 በፊት ወደ ስልጣን የመጡት ዶስ ሳንቶስ በአፍሪካ ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ ከቆየቱ መሪዎች ውስጥ ሁለተኛው ናቸው። አምባገነኑ ዶስ ሳንቶስ በሥልጣን ዘመናቸው በጭካኔ አገዛዝ በማስፈንና ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ረገጣ በማካሄዳቸው ይታወቃሉ። ከዚህ በፊት በ 1993 ዓም በተካሄደው ምርጫ ለውድድር እንደማይቀርቡ   እንደማይቀርቡ ካወጁ በኋላ ሌላ አዲስ ሕግ መንግስት እንዲጸድቅ በማድረግ ውሳኔያቸውን መሻራቸው ይታወሳል። አንጎላ በአልማዝ ማዕድን ሀብታም አገር ስትሆን ለ 27 ዓመታት የእርስ በርስ ጦርነት የተካሄደባት አገር መሆኗ ይታወሳል። የእርስ በርስ ጦርነቱ ካበቃ ከ1994 ዓም ጀምሮ አገሪቱ በኢኮኖሚ አድጋለች የሚል ሪፖርት የቀረበ ቢሆንም ተገኘ የተባለው ሀብት ለጥቂት ባለስልጣናቾ ጥቅም ማደለቢያ ዋለ እንጅ ሕዝቡ አሁንም በድህነት እንደሚኖር የተረጋገጠ ነው።

 

Ø ባለፈው ታኅሳስ ወር ውስጥ በአራት ወታደራዊ ካምፖች ላይ ጥቃት የፈጸሙ  ናቸው በሚል ጥርጣሬ የተገደሉት የብሩንዲ ተቃዋሚዎች መሞታቸው  ለቤተሰቦቻቸው ሳይነገር ተቀበሩ እንጅ በጅምላ ጉድጓድ ውስጥ አልተቀበሩም በማለት የብሩንዲው አቃቤ ህግ ማብራሪያ ሰጥቷል። አቃቤ ህጉ ከሞቱት 87 ሰዎች ውስጥ 58 ቱ በክብር እንዲቀበሩ ተደርገዋል በማለት ቀደም ብሎ በሰብአዊ ድርጅቶች የቀረበውን መረጃ አስተባብሏል። ባለፈው ታኅሳስ ወር አምነትስቲ ኢንተርናሽናል የሚባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ከሳተላይትና ከቪዲዮ የተገኙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ አማጽያኑ በአምስት የተለያዩ ቦታዎች በጅምላ የተቀበሩ መሆናቸውን መግለጹ ይታወሳል። የብሩንዲ የእርስ በርስ ግጭት ከተጀመረ ካለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀምሮ ከ400 በላይ የሆኑ ስዎች ሲገደሉ በ10 ሺ የሚቆጠሩ ቤት ንብረታቸው ጥለው የተሰደዱ መሆናቸው ይታወቃል።

Ø  

 

 

 

 

መጋቢት 01 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø የዴንማርክ መንግስት ከኢትዮጵያ እየተወሰዱ ያሉትን የጉድፈቻ ልጆች ላለመቀበል መወሰኑ ታወቀ። መንግስቱ ይህን አቋም የወሰደው ወደ ዴንማርክ የሚመጡት ህጻናት ወላጅ አልባ ሳይሆኑ ለጥሩ ትምህርትና ኖሮ በወላጆቻቸው ወደ አውሮፓ ይላካሉ እየተባለ መሆኑና ለዚህም ገንዘብ እየተከፈላቸው መሆኑን የዴንማርክ መንግስት የማህበራዊና የስደተኛ ጉዳይ መስሪያ ቤት በማረጋገጡ ነው ተብሏል። የመንግስቱ አካል ዴንማርካውያን ማደጎ ለማግኘት የጀመሩትን እንቅስቃሴ እስኪጨርሱ ብቻ ድጋፉን የሚሰጥ መሆኑ ገልጾ ከዚያ በኋላ ግን ምንም ዓይነት ጉዲፈቻ ከኢትዮጵያ መውሰድ ማቆም ይጀምራል ብሏል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ኢትዮጵያውያንን ህጻናቱን በጉዲፈቻ ስም ከወላጅ እያታለሉ እንደሚሸጡ ለአቅመ ሄዋን እንኳን ያልደረሱ ልጃገርዶችን በቤት ሰራተኛነት ስም ለዘመናዊ ባርነት ወደ አረብ አገር በመላክ ገንዘብ እንደሚሰሰብስቡ ይታወቃል። ዛሬ የወያኔ ባለስልጣኖች ባንድ በኩል ኢትዮጵያውያንን ለስደት እየገፋፉ በሌላ በኩል ደግም ከስደተኛው ከፍተኛ ግምት ያለው የውጭ ምንዛሬ በመሰብሰብ ኪሳቸውን  እያጠረቁት ይገኛሉ።

 

Ø የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ኃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2008 ዓም በወያኔ ፓርላማ ቀርቦ ባደረገው ንግግር የተለመደ የማስመሰያና የማዘናጊያ ቅጥፈቱን ደስኩሯል። በመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን ዘረኛ አገዛዝ በመጥላት ሕዝቡ ዴሞክራሲያ ሥርዓት በመጠየቅ ና የሰብአዊ መብት እንዲከበር ያቀረበውን ጥያቄ የመልካም አስተዳደር ችግር መሆኑንና በመጥቀስ ወያኔ በቂ ምላሽ ሰጥቷል በማለት ዋሽቷል። የወያኔው ጠ/ሚኒስትር  በጭብጨባ ለሚቀበለው የወያኔ ፓርላማ ያቀረበው ዲስኩር በወያኔ መሪዎች ተዘጋጅቶ የተሰጠው መሆኑ ሲታወቅ የሕዝብ ጥያቄና ተቃውሞ መልስ ተሰጥቶበታል  በማለት አልፎታል። በዚህ የሀሰት ዲስኩሩ በሻዕቢያ ታግተው የነበሩትንና በቅርቡ በሱዳን መንግስት አደራዳሪነት ነጻ የተለቀቁትን ኢትዮጵያውያን አስመልክቶ ዜጎቹ የተለቀቁት ሻዕቢያ የሚደርስበትን ስለሚያውቅ  ፈርቶ ነው በማለት ዋሽቷል። የወያኔ መሪዎች የሀሰት ዲስኩርና ዓይንን በጨው ታጥቦ መዋሸት ተፈጥሯቸው ሲሆን እንዲህ ዓይን ባወጣና በገሀድ ዓለም የሚያወቅውን ሐቅ በመገናኛ ብዙሃን መዋሸታቸው የውሸታችው መጠን ጣራ የነካ መሆኑ ያሳያል ተብልውል።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ በግልጽና በይፋ ለተመድ የጸጥታው ም/ቤት ተለዋጭ አባልነት ራሱን ዕጩ አድርጎ የአፍሪካ አገሮችንና የምዕራባውያንን ድጋፍ ለማግኘት በሚሯሯጥበት በአሁኑ ሰዓት በተገላቢጦሽ የተመድ የፀጥታው ምር ቤት ኢ ዴሞክራሲያ ስለሆነ መላወጥ አለበት በማለት ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መምከሩ ታውቋል። የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በተገናኘበት ሰዓት ከሁለተኛ የዓለም ጦርነት በኋላ አሸናፊዎቹ አገሮች ተመድን ሲመሰርቱ የፀጥታው ምክር ቤት ወንበርን ለራሳቸው መውስዳቸውን በማስታወስ ከ70 ዓመት በፊት የተቋቋመው ድርጅት ዛሬ ላይ ግን ለውጥ ማድረግ አለበት ብለዋል። ወያኔ እገዛዋለሁ በሚለው አገር ያሉ ዜጎችን በጭካኔና በአረመኔነት እየገደለ እያሰርና እየደበደበ ለዓለም ሕዝብ አሳቢ በመሆን የተመድን የፀጥታ ምክር ቤት ወንበር መከጀሉ ለስላቅ ዳርጎታል።  99.9 ከመቶ ተመርጥኩ በማለት ምርጫን ያጭበረበረ አምባገነን  የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ኢዴሞክራሲያዊ ነው በማለት የዴሞክራሲ ተሟጋች ለመሆን ማሰቡ ብዙዎችን አስገርሟል።

 

Ø እንደተላኩ መጥፋት፤ እንደወጡ መቅረት እየተለመደባትና እየተዘወተረባት በመጣችው ኢትዮጵያ ኩብለላ አዲስ ነገር መሆኑ በቀረበት በአሁኑ ሰዓት የወያኔ የፕሮፓጋንዳ ወፍጮ የሆነውና በወያኔ መሪዎች መቶ በመቶ ቁጥጥር ስር ያለው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮፕሬሽን ምክትል ስራ አስኪያጅ የነበረው ጨምቤሳ አሜሪካን ከተላከ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ለመመልስ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል የሚል ዜና እየተዘገበ ነው። ምክትል ሥራ አሲያጁ መቼና ለምን ዓይነት ሥራ ወደ አሜሪካ እንደመጣ ባይገለጽም አሜሪካ በሚኒሶታ ግዛት ውስጥ እንደሚገኝና ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ፍላጎት እንደሌለው ተገልጿል።

 

Ø በተመሳሳይ ዜና የአዲስ አበባው የኤፍ ኤም 97.1 ራዲዮ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆነው አቶ አንድነት ለሥራ ጉዳይ ወደ እንግሊዝ አገር እንደተላከ ለንደን ላይ መቅረቱ ተገልጿል። አቶ አንደነት ለምን ጉዳይ ወደ ኢንግሊዝ እንደተላከ የታወቀ ነገር ባይኖርም ኢትዮጵያ ውስጥ የአለውን የአንድ ዘር የበላይነትን ያረጋገጠውን አምባገነን አገዛዝ በመጥላት ሀገር ጥለው የሚኮበልሉት ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ ከፍተኛ የወያኔ ባለሥልጣናት እና አጋሮቻቸው መሆናቸው ሲታወቅ አብዛኛዎቹ በ-ከሚሰምጥ መርከብ እየሸሹ ነው ተብለዋል።

 

 

Ø 23 ዓመት በፊት የደቡብ አፍሪካ ኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ጸሐፊና የአፍሪካ ናሽናል ኮንግሬስ  የትጥቅ ክንፍ ኮማንደር በመሆን የሚታወቀውን እውቁን የነጻነት ታጋይ  ክሪስ ሃኒስን በመግደል  የ እድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት የነበረው የፖላንዱ ዜጋ ጃኑዝ ዋለስ የእስራት ዘመኑን ሳይጨርስ በምህረት እንዲለቀቅ የደቡብ አፍሪካ ፍርድ ቤት ፈርዷል። በስልጣን ላይ ያለው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ባለስልጣኖች የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በፍትሕ ላይ የተፈጸመ አሳዛኝ ወንጀል ነው ካሉ በኋላ ጃኑዝ ከተለቀቀም ወደ አገሩ ወደ ፖላንድ መባረር አለበት እንጅ በደቡብ አፊርካ እንዲቀመጥ ሊፈቀድለት አይገባም ብለዋል። ጃኑዝ የፖላንድ ዜጋ የነበረ ሲሆን በ1973 ዓም ወደ ደቡብ አፍሪካ መጥቶ የደበቡ አፍሪካ ዜግነትን ያገኘ ነው። ግለሰቡ ሃኒን የገደለው በበ1985 ዓም ሲሆን ለአለፉት 23 ዓመት በእስራት ላይ ነበር።  የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ባወጣው መግልጫ ገዳዩ በፈጸመው ድርጊት ሀገሪቱ ትልቅ የነጻነት ታጋይ የነበረውን ውድ ልጇን ተስርቃለች ብሏል። 

 

 

Ø በናይጀሪያ ሪቨር ስቴት በተባለውና የነዳጅ አምራች በሆነው  አካባቢ በነበረ ከፍተኛ ብጥብጥ የተነሳ ባለፈው ዓመት የተደረገው ምርጫ መሰረዙ የሚታወቅ ሲሆን በመጭው መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓም ድጋሚ ምርጫ ለማካሄድ የታቀደ መሆኑ ተገልጿል። አካባቢው የተቃዋሚ ድርጅቶች በጥንክሬ የሚንቀሳቀሱበት  ቦታ ሲሆን በቅርቡ ከምርጫው ጋር በተያያዘ በተከሰተ ግጭት ከ30 በላይ የሚሆኑ የገዥው ፓርቲ አባሎች የተገደሉ መሆናቸውን የፓርቲው ቃል አቀባይ ገልጿል። በ2007 በተደረገው ብሔራዊ ምርጫ ወቅት በነበረው ግጭት ከ100 ሰዎች በላይ መሞታቸውን የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ገልጸዋል።

 

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሰሞኑን በደቡብ አልጀሪያ የሚገኘውን የምዕራብ ሳህራ ስደተኞች ካምፕ ከጎበኙ በኋላ የስደተኞቹ የኑሮ ሁኔታ በጣም አሳዛኝ መሆኑን ገልጸው ምዕራብ አፍሪካን አስመልክቶ እንደገና የሰላም ውይይት ተካሄዶ ስደተኞቹ የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል። በ1965 ዓም ሞሮኮ የምዕራብ ሳህራን ግዛት  ወደ ራሷ ግዛት በመጠቅለሏ   ፖሊዛሪዮ በሚባል ድርጅት አማካይነት ለረጅም ዓመታ የነጻነት ትግል ሲካሄድ መቆየቱ ይታወቃል። የሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የባንኪ ሙኑን ጉዞ በጽኑ መቃወሙን የገለጸ ሲሆን ዋና ጸሐፊው ስልጣናቸው የሚጠይቀውን ገለልተኛነት አድልዎ አልባነትና እውነተኛነትን ከራሳቸው አስወግደዋል በማለት ከሷቸዋል። የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች የካቲት 30 ቀን 2008 ዓም የሞሮኮ መንግስት ላሰማው ክስ በሰጡት መልስ ዋና ጸሐፊው የምዕራብ ሳህራ በቅኝ ግዛት መያዟን የተናገሩት እስካሁን ድረስ በተደረገው ስምምነት መሰረት በአካባቢው ስደተኞች መብታቸውን ሊያስጠብቅ የሚችል አስተዳደር ሊመሰረትና ስደተኞች ወደ አገራችው የሚመለሱበት ዋስትና ባለመፈጠሩ ነው  ብለዋል።  

 

 

Ø የሱማሌ መንግስት ወታደሮች በአሜሪካ አማካሪዎች ታጅበው በደቡብ ሶማሊያ በምትገኘው አውዴግል  በተባለችው  አለሸባብ በሚቆጣራት ከተማ ላይ  በአካሂዱት የሌሊት ከበባና ዘመቻ አስር የአልሸባብ ወታደሮችን የገደሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። አንድ በከፍተኛ ድረጃ የሚፈልግ የአልሸባብ አባል አብሮ የተገደለ መሆኑም ተገልጿል። አጥቂዎቹ በሌሊት ወደ ከተማዋ የሄዱት በአሜሪካ ሄሊኮፕተሮች ሲሆን የአሜሪካን አማካሪዎች በቀጥታ በውጊያው በቀጥታ ባይሳተፉም ወደ ቦታው አብረው እንደሄዱ ተነግሯል።  ወደ አምሳ የሚጠጉ የአሜሪካ አማካሪ ወታድሮች በሱማሊያ ውስጥ መኖራቸው ይታወቃል።  አልሸባብ በራዲያ ባስረጨው ዜና በከተማዋ ላይ የውጭ ዜጋዎች ጥቃት ለመስንዘር የሞከሩ መሆናቸውን ገልጾ በተደረገው የመከላከል ጦርነት በሽንፈት ወደ መጡበት ተመልሰዋል ብሏል። ረቡዕ ጠዋት አካባቢውን በጽጥታ ኃይሎች በማጠር የጸጥታ ቁጥጥር ያደረገ ሲሆን የሱማሊያ መንግስትና የአሜሪካ  ሰላይ ናቸው የተባሉትን ግለስቦች መያዙ ተዘግቧል። በተያያዘ ዜና ረቡዕ የካቲት 30 ቀን 2008 ዓም በዋናው ከተማ በሞቃድሾ በአንድ ቡና ቤት አጠገብ በመኪና ላይ የተቀበረ ፈንጅ በመፈንዳቱ ሶስት ፖሊሶችና አንድ ሰላማዊ ሰው መገደላቸው ታውቋል። ለጥቃቱ ኃላፊነትን የወሰደ ወገን ባይኖርም አልሸባብ መሆኑ ይገመታል።

 

 

 

የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም.

 

Ø በትናንትናው ዕለት የተወሰኑ የአዲስ አበባ ዩነቨርስቲ ተማሪዎች በተለያዩ አካባቢዎች የወያኔ አግአዚው ጦር እያካሄደ የሚገኘውን ጭፍጨፋ በመቃወም የተቃውሞ ስልፎች ማድረጋቸው ታውቋል። ተማሪዎቹ በአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን ፖሊሶችና የወያኔው አግአዚ ጦር በቦታው በመድረስ ተማሪዎችን በድብድባ መበተናቸውና የተወሰኑትንም አስረው መውሰዳቸው ተዘግቧል። በተጨማሪም ከስድስት ኪሎ ዪነቨርስቲ ካምፓስ የተወሰኑ ተማሪዎች ታስረው የተወስዱ መሆናችው ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

 

Ø በተያያዘ ዜና ሰኞ ማታ በወለጋ ዩነቨርስቲ የአግአዚ ጦር በተማሪዎቹ መኖሪያ ክፍሎች በመሰማራት ከፍተኛ ድብደባ ማካሄዱና በዚህም በርካታ ተማሪዎች መጎዳታቸው ተዘግቧል። ደብደባው ጨለማን ተገን ያደረገ እንደነበር ሲታወቅ እስከአሁን በድብደባው ክፉኛ የተጎዱ 49 ተማሪዎች መኖራቸው ሲረጋገጥ በአንዳንድ ተማሪዎች ላይ የደረሰው  ጉዳትም ለህይወት የሚያሰጋ ነው ተብሏል። የፖሊቲካ አክቲቪስቶች የተናጠል ትግል በተናጠል የሚመታ በመሆኑ የተባበረና የተቀነባበረ ትግል ለማካሄድ እንቅስቃሴው መጀመር እንዳለበትና ወያኔን ማዋከብና ማስወገድ እንደሚያስፈልግ አስረግጠው ይናገራሉ። በሌሎች አካባቢዎችም የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ቀጥለዋል።  

 

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በኢትዮጵያውያን ላይ ያወጁትን ጦርነት በከተሞች ውስጥ በመግደልና በጅምላ በማሰር የአገዛዙን ዕድሜ ለማስረዘምና በስግብግብነት ኪሳቸውን ለመሙላት ጥረታቸውን በቀጠሉበት ሰዓት በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ዜጎች ለዘመናት ከሚኖሩበት እያፈናቀሉ መሬታቸውን መቸብቸብ የተለመደ ሲሆን ከመሬታቸውን አንፈናቅልም ያሉትን ከፍጹም ሰብዓዊነት ውጭ ከመቶዎች ዓመታት በፊት አውሮፓውያን  ፈንጋዎች የሚፈጽሙትን ዓይነት የጭካኔ ተግባር በደቡብ ኢትዮጵያ በኦሞ ሸለቆ በሶርማ ነገድ ላይ እየፈጸሙ መሆኑን ሰሞኑን በማኅበራዊ ገጾች ላይ የተለቀቀው ፎቶ አሳይቷል። የወያኔ መሪዎች የሱርማ ነገድ  7000 ሄክታር መሬትን ያለ ምንም ካሳ ከነጠቁ ወዲህ ነዋሪውንና ተወላጁን አረመናዊ በሆነ መንገድ ግድያ ድብደባና እስር እንዳካሄዱባቸው ታውቋል። የሱርማ ነገድ አባላት የራሳቸው የሆነ ጥንታዊ የኑሮ ዘይቤ ያላቸው ሲሆን በፍንገላ መሬታቸው ተወስዶ አረመናዊ ተግባር ሲፈጸምባቸው ድምጽን ማሰማት የሁሉም ዜጋ ብቻ ሳይሆን የማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ግዴታ ነውና ድምጻችንን እናሰማላቸው የሚሉ ወገኖች እየተበራከቱ ይገኛሉ። በተመሳሳይ ዜናም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የኮንሶ ሕዝብ በማንነትና በአከላለል የጀመረውን ጥያቄ  አሁንም እየቀጠለ ሲሆን ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎችን እያደረጉ መንገዶችንም እየዘጉ መሆናችው ይነገራል።

 

Ø በተመሳሳይ ዜና  ባለፈው ቅዳሜ  እንደተጀመረ የሚነገርለት በገለብ ሐመር ባኮ በኩራዝ ወረዳና በአካባቢው ከፍተኛ ፀረ-ወያኔ አመጽ እየተካሄደ መሆኑ ከስፍራው የተገኘ ዜና ያስረዳል፡፡ ሕዝቡ አካባቢውን አቋርጦ የሚሄደውን አውራ ጎና ቆፍሮ የተሸከርካሪ ትራንስፖርትን ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎሉ ታውቋል፡፡  በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከመሀል ሀገር እስከ ዳር አገር ወያኔን ለመደምሰስ እያመጸ መሆኑ የወያኔ ቁንጮዎች ክፉኛ እንደ ተረሸበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይህ ፀረ-ወያኔ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እግር አግሩን እየተከተሉ የሚያጤኑ የፖለቲካ ተንታኞች ይህ ሁኔታ የሚያመለክተው የወያኔ ዘረኛና ግፈኝ አገዛዝ ከመጨረሻው የገመዱ ጫፍ ላይ መድረሱን እንደሆነ አበክረው ያስረዳሉ፡፡

 

Ø የታክሲ ሾፌሮች አድማ አድማሱን በማስፋት  ባለፉት ቀናት በደብረ-ብርሀን፣ በደብረ-ሲና፣ በአጣዬና በካራቆሬ መቀጣጠሉ ታወቋል፡፡ ወደ እነዚህ ከተሞች የሚገባም ሆነ የሚወጣ ምንም ዓይነት የመንገደኛ ተሸከርካሪ እንደሌለ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ይህ የሾፍሮች አመጽ በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞች ሊቀጣጠል እንደሚችል በመረዳት የወያኔ ቁንጮዎች በትግራይ ተወላጆች ብቻ የተሞላውን የአጋዚ ጦር በሁሉም ቦታ እንዲሰፍር ያዘዙ መሆናቸው ይንገራል።

 

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች የአንድ ዘር የበላይነት ያለውን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ዕድሜ ለማስቀጠል ታማኛ አገልጋይ የፖሊስ ኃይል ዋና መሳሪያና ቀኝ እጅ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ታማኝነታችው ያጠራጠረ የፖሊቲካ አመለካከታቸው ያልታወቀ ወይንም ዘራችው ካልተስማማችው ከሥራና ከሠራዊቱ በምክንያት ማባረር የተለመደ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ መሠረት በድሬደዋ  18 መርማሪ የፖሊስ አባላት መባረራቸውና ሃምሳ የሚደርሱ በእነርሱ ምትክ መተካታቸው ታውቋል። ፖሊሶቹ  ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ መንገድ የተወነጀሉ ሲሆን ዋናው ምክንያት ግን ፖሊቲካዊ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ምናልባት ፖሊሶቹ እንቅስቃሴያቸው አመጽ ቀስቃሽ ነው ብሎ ከታመነ ክስ ለመሰረተባችው እንደሚችል ተግልጿል። በፖሊስ መርማሪዎቹ ምትክ 49 የፖሊስ አባላት የምርመራ ስልጠና እንዲሰጣቸው መወሰኑ ታውቋል።

 

Ø አጣዳፊ የተቅማጥና የትውከት በሽታ በአርባ ምንጭ ከተማ ውስጥ መከሰቱ ተሰምቷል። በሽታው በከተማዋ ውስጥ በሰፊው መሰራጨቱ ይሰማ እንጅ በበሽታው ሰብብ ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ የተገለጸ ነገር የለም። የአርባ ምንጭ ከተማ የጤና ባለሙያዎች ግን በሽታው አደገኛና በቀላሉ በወረርሽኝ መልክ የሚስፋፋ በመሆኑ በአስቸኳይ ርብርብ መደረግ አለበት ይላሉ።  

 

 

 

የካቲት 29 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ትናንት የካቲት 28 ቀን 2008 ዓም አንድ ኢትዮጵያዊ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ዕቃ መጫኛ ቦታ ውስጥ ከ10 በላይ ለሆነ የበረራ ጊዜ ተሸሽጎ ስቶክሆልም ስዊድን ሲደርስ የእቃ መጫኛ ሰራተኞች ያገኙት መሆኑን የስዊድን ፖሊሶች ገልጸዋል።ክአካል ድክመት በስተቀር በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ የሚገኘው የ27 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ የፖሊቲካ ጥገኝነት የጠየቀ መሆኑንም ፖሊሶች ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የሆነ ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ መልክ የአውሮፕላኑ የእቃ መጫኛ ክፍል ውስጥ ተደብቆ ስዊድን መድረሱ ይታወሳል።  የወያኔ አፋኝ አገዛዝ አንግፍግፎት ወደ ባዕድ አገር የሚሰደደው ኢትዮጵያዊ ቁጥር በጣም ከፍተኛ ሲሆን ህወይታችውንም አካላቸውን ለአደጋ በማጋለጥ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ውጭ ለመውጣት የሚያደርጉት ጥረት የወያኔ አገዛዝ ምን ያህል ጨካኝ መሆኑን ያሳያል በማለት አስተያየት የሚሰጡ አሉ። 

 

 

Ø በናዝሬት ሲካሄድ የቆየው የወያኔው ኦህዴድ ማዕከላዊ ስብሰባ ማብቃቱና በወያኔ ተዘግጀቶ የተሰጠው የውሳኔ መግለጫ ማውጣቱ ታወቀ። የወያኔው ኦህዴድ በዚሁ መግለጫ ድርጅታዊ አካሄዱን ለማረም ሲባል የማስተካካያ እርምጃ እንዲወሰድና ከመልካም አስተዳደር ጋር በተግናኘም የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽሕፈት ቤት ኃላፊውን ዳባ ደበሌን ከኃላፊነትና ከማዕካላዊ ኮሚቴ አባልነት በማንሳት በድርጅት አባላነት እንዲሰራ እንዲሁም ዘላለም ጀማነህ የተባለው ሌላው የአመራር አባል እስከ መጭው ድርጅታዊ ጉባኤ ድረስ ታግዶ እንዲቆይ ወስኖበታል። የወያኔው ኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ከወያኔ መሪዎች በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ስለ ኦህዴዱ መሪ ተብየው ሙክታር ከድር የተባለ ነገር የሌለ ሲሆን አዲስ ስለ ተሹሙትም ግለሰቦችም  የተተነፈሰ ነገር የለም።

በሌላ በኩል ደግሞ በምዕራብ አርሲ በሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ ጉዳት የደረሰባችውን የአገዛዙ መገልገያ ጽሕፈት ቤቶችን ነዋሪው መልሶ እንዲያቋቁማቸው እየተደረገ መሆኑ ታውቋል። የፈረሱና የተቃጠሉ የቀበሌ ጽሕፈት ቤቶችን መልሶ ለማቋቋም ሕዝብ ገንዘብ እንዲያዋጣ በአካባቢው ያሉ የወይኔ ሹመኞች የግዳጅ ሃሳብ ማቅረባቸው የታወቀ ሲሆን ባለሙያዎችችም በሙያችው እንዲረዱ በነጻ ጉልበት እንዲሰሩ እየተጠየቁ መሆናቸው ተገልጿል።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ የሚያካሄደውን አረመናዊ ግድያና የጭካኔ ድብደባና የጅምላ እስር ከዓለም ለመደብቅ የሚያደርገው ያልተስካ ሙከራን በመቀጠል ስለ ሕዝባዊ ተቃውሞ ቁጣ ለብሉምበርግ የዜና አውታር ይዘግቡ የነበሩትን ዊሊያ ዳቪንሰንና የግል ጋዜጣኛዋን ጄሲ ፎርተን ከነ አስተርጓሚዎቻቸው  ለ24 ሰዓታት አስሮ መፍታቱ ታወቀ። ጋዜጠኞቹ ከአንድ ቀን እስር በኋላ አዋሽ አካባቢ በወያኔ ፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወደ አዲስ አበባ ከተላኩ በኋላ በፖሊስ ጣቢያ አንድ ቀን አድረው ቃል ሳይሰጡና ለምን እንደተያዙ እንኳ ሳይገለጽላቸው ተፈተዋል። ስልኮቻቸውና መታወቂያቸው ግን እንዳልተመለሰላቸው ታውቋል። የብሉምበርግ ጋዜጠኛው ባለፉት አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜያት ተይዞ መለቀቁን ገልጾ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዜጠኛነት ዘገባ መስራት ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል ብሏል። ጋዜጠኞቹ የውጭ አገር ዜጎች በመሆናቸው በአገሮቻቸው ተጽእኖና ግፊት ሲፈቱ የሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች  ግን በወያኔ ፀረ ሽብርተኛ ሕግ ተከሰው ረዥም የእስር ዘመን ይፈረድባቸው እንደነበር የፕሬስ ወዳጆች ይናገራሉ።

 

Ø የወያኔ መከላከያ ሚኒስትር ተብየው ሲራጅ ፈርጌሳ እና የስዳኑ አቻው ካርቱም ላይ ባካሄዱት ውይይት በወሰን አካባቢ የወያኔ እና የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች በአንድነት ጸጥታ ሊያስከብሩ በሚችሉበት ሁኔታ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነግሯል። ከ250 ስኩየር ኪሎሜትር በላይ የሆነውንና ከ600 ሺ ኤከር በላይ ለም የሆነ መሬት ያለውን  የአልፋሻጋ አካባቢን ወያኔ ለሱዳን መስጠቱ በተደጋጋሚ የተነገረ ሲሆን አሁን በጋራ የጸጥታ ኃይል ለማሰማራት የተገደዱበት  የሕዝብን ትጥቃዊ ተቃውሞ ለመከላከል ነው ተብሏል።   

 

 

Ø ባለፈው ቅዳሜ የካቲት 26 ቀን  በሱማሊያ ከሞጋደሾ በስተሜን በሚገኘውና ራስኮ ካምፕ በሚባለው የአልሸባብ የስልጠና ካምፕ ላይ የአሜሪካ ሰው አልባ መንኩራኩርና የጦር አውሮፕላኖች ባካሄዱት የአየር ጥቃት ከ150 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች መገደላቸውን የአሜሪካው የመከላከያ ተቋም ቃል አቀባይ ጠቅሷል። ቃል አቀባዩ አልሸባብ ከፍተኛ የሆነ ጥቃት አቅዶ እንደነበረ ጨምሮ ገልጾ ብዙ ጉዳት ከመድረሱ በፊት የተወሰደ እርምጃ ነው ብሏል። የስልጠናው ቦታ በሶማሊያ መንግስት የጸጥታ ትቋም የተጠቆመ መሆኑ ሲነገር እቅዱ ምን እንደነበር ግን አለተገለጸም። አልሸባብ የአየሩ ጥቃት መደረጉን ቢያምንም ከ150 በላይ ሞተዋል የሚለው በጣም የተጋነነ ነው ብሏል። የአሜሪካ ባለስልጣኖች የተደረገው የአየር ጥቃት እንደ ትልቅ ድል ቢቆጥሩትም  ከ100 በላይ የሆኑ አባላት በአንድ ቦታ ላይ አሰባስቦ ስልጠና ማካሄድ መቻሉ ድርጅቱ ጠንካራ መሆኑን ያሳያል የሚሉ አስተያየት ሰጭዎች አልጠፉም።

 

Ø ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓም  ዕለት በቱኒዚያ እና በሊቢያ ወሰን ቤን ገርዳኔ በተባለው ቦታ ላይ የተደረገው ግጭት በጠቅላላው 55 ሰዎች የሞቱ  መሆናቸውን የቱኒዚያው ጠቅላይ ሚኒስትር ገልጸዋል። ከሞቱት መካከል 36 የሚሆኑት አጥቂዎቹ ሲሆኑ ከወታደሮቹ በኩል 12 መሞታቸውና  ሌሎች 17 መቁሰላቸው ተነግሯል። ለጥቃቱ እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም በድረ ገጽ አማካይነት ከተሰራጨው መረጃ የአይሲስ አባላት የሆኑ ቱኒዚያውያን ሳይሆኑ አይቀርም የሚል ግምት ተሰጥቷል። የቱኒዚያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጥቃቱን ያደረሱ ሰዎች አብዛኞቹ የቱኒዚያ ዜግነት ያላቸው መሆኑን ገልጸው ለጥቃቱ ኢላማ ያደረጉት የፖሊስ ጣቢያውን ነበር ብለዋል። ከአጥቂዎቹ መካከል የተያዙት ግለስቦች የቡድኑን የመሳሪያና የጥይት ክምችት መርተው አሳይተዋል ተብሏል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በአካባቢው ተደጋጋሚ ግጭቶች የደረሱ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በሰኞ ዕለቱ ግጭት ግን በርካታ ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።

 

Ø በአሜሪካ ኦክላሃማ ግዛት ውስጥ የሚገኝ  ፍርድ ቤት በኬኒያ  በህጻናት ላይ  የወሲብ ወንጀል ፈጽሟል በተባለ አንድ ግለሰብ ላይ የአርባ ዓመት እስራት የፈረደ መሆኑ ተገልጿል። እድሜው 21 ዓመት የሆነው ማቲው ሌን ዱርሃም የተባለው ግለሰብ ይህንን አሰቃቂ ድርጊት የፈጸመው በ2006 ዓመተ ምህርት ከሚያዚያ እስከ ሰኔ ባሉት የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ናይሮቢ አጠገብ በሚገኘው የሕጽናት መጠለያ ጣቢያ ሲሆን ከ10 በላይ በሚደረሱ ህጻናት ላይ ወንጀል የጸመ መሆኑና  አንዳንዶቹ ገና አራት ዓመት ያልሞላቸው እንደነበሩ ተገልጿል። 

 

Ø ባምባሪ በተባለቸው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ምስራቃዊ ከተማ ውስጥ በሁለት ተጻራሪ ቡድኖች መካከል በተካሄደ ግጭት ከ10 ሰዎች በላይ መሞታችው ተነገረ። ግጭቱ የተካሄደው በሙስሊም ታጣቂዎችና በክርስቲያን ታጣቂዎች መካከል ሲሆን የካቲት 24 ቀን 2008 ዓም የተገደሉትን ሁለት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች  ለመበቀል የተጀመረ መሆኑ ታውቋል። የማዕድን ከተማ የሆነችው ባምባሪ በርካታ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የሚኖሩባት ከተማ ስትሆን ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሁለቱ ቡድኖች መካከል ተከታታይ ግጭቶች ተደርገውባታል። ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓም የተሰራጨ አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘገባ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እየተካሄደ ያለው ግጭት በርካታ ችግሮችን መፍጠሩን ዘርዝሮ ዘግቧል።  

 

 

የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በአዲስ አበባ የተጀመረውን በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች የተካሄደው የታክሲዎች የሥራ ማቆም አድማ በዛሬው የካቲት 28 2008 ዕለት በጎንደር ውስጥ በጋይንት መደረጉ ታውቋል። የታክሲ ሹፌሮች አድማ በጋይንት ያለውን ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ የገታውና ያቆመው መሆኑ ሲታወቅ እጅግ ብዛት ያለው የወያኔ ፌዴራል ፖሊስ ውስጥ ወደ ዓለም በር በመግባት አካባቢውን የጦር ሠፈር አስመስሎት ይገኛል። የጎንደሩ የወያኔ የጸጥታና የፍትህ ቢሮ በመደናገጥ ከባህር ዳር ተጨማሪ ኃይል በመጠየቁ ዛሬ ማምሻውን ስምንት ከባድ ካሚዮኖች ልዩ የወያኔ የፖሊስ ኃይል ጭነው ዓለም በር እንደገቡ ከጋይንት የመጣው መረጃ አመልክቷል። ከዚህ በተጨማሪ የታክሲ ሾፌሮች የሥራ ማቆም አድማ በሌሎች የጎንደር ከተሞች በክምር ድንጋይና በደብር ታቦርም መደረጉ ተረጋግጧል። የፖሊቲካ ታዛቢዎች በየከተሞቹ የሚደረገው የተጠናጠል የሥራ ማቆም አድማ ወያኔን ጊዜ የሚሰጠውና ነጥሎ ለማጥቃትና ለመምታት የሚያመቸው በመሆኑ አንድ አጠቃላይ የሥራ ማቆም አድማ በማድረግ አገዛዙን ሽባ ማድረግ የማይታለፉ የትግል ስልትና ዘዴ መሆን ይገባዋል ይላሉ።

 

Ø የአዲስ አበባው ሲኖዶስ ያደረገውን ድንገተኛ አስቸኳይ የቋሚ ሲኖዶስ ጉባዔ በዛሬው ዕለት አጠናቅቆ መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል። በቋሚ ሲኖዶስ እና በፓትሪያርኩ መካከል ከፍተኛ የሆነ የአሰራርና የሃሳብ ልዩነት ያለ ሲሆን ቋሚ ሲኖዶሱ አቡነ ማትያስ በማኅበር ቅዱሳን ላይ ያስተላለፏቸው መመርያዎችና የጠሯቸው ስብስባዎች ሁሉ ህገ ወጥ ናቸው በማለት የተቻቸው ሲሆን ከእንግዲህ ወዲህ  የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅር ጠብቀው እንዲሰሩና ኃላፊነታቸው እንዲወጡ አስጠንቅቋቸዋል። አቡነ ማትያስ አቤቱታዎችን ለመመልከት በማለት ራሳችው ብቻቸውን የጠሯቸው ስብሰባዎች ያስለፏቸው ውሳኔዎች የአቋም መግለጫዎች በሙሉ ህገ ወጥና ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪ አቡነ ማትያስ የቋሚ ሲኖዶሱ አባላትን ለማሸማቀቅና ለማስፈራራት ያደረጉት ሙከራና በሠሯቸው ማዕከላዊነት ያልጠበቀ አሰራር አዋረዱን አሳፈሩን ተብለዋል። አቡነ ማትያስ ከልዩ ጽ/ቤታቸው ውስጥ ያለው አሠራርም ቋሚ ሲኖዶሱን እንዳሳስበቸው ገልጸዋል። ፓትርያርኩ ርእሰ መንበር ሆነው አባታዊ ኃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ስፖንሰር ተገኘ በሚል ብቻ ጉዞ እንደሚደረግ ጠቅሰው ስህተቱ እንዲታረም ጠይቀዋል። በመጨረሻም አቡነ ማትያስ ህግ አክብረው ከሲኖዶሱ ጋር መክረውና ተነጋግረው እንዲሰሩ በጥብቅ አሳስበዋቸዋል። በአገሪቷ ላይ ስላለው ሰላም ጉዳይ የመከረ ሲሆን የተቃጠሉ ቤተ ክርስያናትን ጉዳይ የሚያጣራ ልዑክ መድቧል። ድንገተኛው አስቸኳይ ስብሰባ በዛሬው ዕለት መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች ሲካሄዱ የነበሩ ሕዝባዊ ተቃውሞችን ለመግታት ተገቢ ርምጃ አልወሰዳችሁም የተባሉ ሁለት የኦህዴድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከኃላፊነት መነሳታቸው የሚታወስ ሲሆን በወያኔ አስገዳጅነት በሚካሄደው የወያኔ ኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብስባ ሌሎች ተጨማሪ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ሊባረሩ ወይም ሊታሰሩ ይችላሉ የሚል ግምት እየተሰጠ ነው። ወያኔ የኦህዴድ አመራር አባላትን አንገት አስደፍቶ ፍጹም ታዛዥ ለማድረግ የሚያካሄደው ስብሰባ በውጥረትና እርስ በርስ በመጠባበቅ በስጋት እየተካሄደ መሆኑ ታውቋል።

በተመሳሳይ ዜናም የወያኔው ብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በስብሰባና በግምገማ የተወጠሩ ሲሆን ከፍተኛ የብአዴን ካድሬዎች ከሥራና ከኃላፊነት ሊባረሩ ይችላሉ ተብሏል። የወያኔ መሪዎች የብአዴን መሪዎች ወያኔ ራሱ ያቀጣጠለው የቅማንት ማንነት ችግርን የብአዴን መሪዎች በአግባብ አልያዙም በሚል እየወቀሰ ሲሆን የወልቃይት እና የጠገዴ ወረዳዎችን ወደ ጎንደር እንዲቀላቀሉ ብአዴኖች ውስጣዊ ድጋፍ ሰጥተዋል ተብለው እየተወቀሱ መሆናቸው ታውቋል።

 

 

Ø በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት ተወካይ የሆኑት ሚስተር አህማዱ ለሚቀጥለው የመኸር ወቅት መዘጋጃ በርካታ አካባቢዎች ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ገልጹ። የበልግ ዝናም ባለመኖሩ የተጎዱ አካባቢዎች መኖራችውን ጠቅሰው በሚቀጥለው የመኸር ወቅት ዝናም ከመጣ ወደ 7.5 ሚሊዮን የሚሆኑ ቤተሰቦች የዘር እህል ለማግኘትና ከብቶቻቸውን ለመመገብ እርዳታ ያስፈልጋችዋል ብለዋል። ለዚህ እርዳታ የታቀደው 50 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 13 ሚሊዮን የሚሆን በያዝነው ወር ውስጥ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል። ከተፈለገው ገንዘብ እስካሁን አስር ከመቶ እንኳ እንዳልገባ ተጠቅሷል።  

 

Ø የቱኒዚያ የጸጥታ ኃይሎች ከሊቢያ በኩል ወሰን ጥሰው መጥተው ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉ 21 የአይሲስ ታጣቂዎች መግደላቸውን አስታውቀዋል። ታጣቂዎች ጥቃቱን የፈጸሙት ቤን ጎርዳኔ በሚባለው ከተማ ውስጥ ባሉ የወታደራዊ ሰፈር ላይ እና ፖሊስ ጣቢያ ላይ ሲሆን በተኩስ ልውውጥም አራት ሰላማዊ ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ተጠቅሷል። ባለፈው ሳምንት የአሲስ ኃይሎች ተመሳሳይ ጥቃት መፈጸማቸው የሚታወቅ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ  ወዲህ ቡድኑ በተከታታይ እያደረሰ ያለው ጥቃት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የቱኒዚያ የገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ገልጿል። የቱኒዚያ መንግስት በወሰን አካባቢ ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በመቆፈር  የጸጥታ ሁኔታውን ያጠናከረ ሲሆን ወደ ከተማዋ የሚያስገባውን በር በመዝጋትና በከተማዋ የሰዓት እላፊ አዋጅ በማወጅ እርምጃ የወሰደ መሆኑ ተነግሯል ።

በተመሳሳይ ዜና የሞሮኮ የአገር ግዛት ሚኒስትር ቃል አቀባይ ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ህዝብ የሽብር ተግባር ለማካሄድ ሲያቅዱ ነበር ያላቸውን አምስት  የአይሲስ አባላት በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑን ገልጿል። አሸባሪዎቹ ፕሬሸር ኩከር በመጠቀም በገበያ ቦታዎች ፈንጅዎችን ለማፈንዳት ሲዘጋጁ ተይዘዋል ያለው መግለጫ በሊቢያ በአይሲስ አማካይነት ተጨማሪ ወታደራዊ ስልጠና ለመቀበል እቅድ የነበራቸው መሆኑም ተገልጿል።

 

Ø በሱማሊያ በላፕ ቶፕ ኮምፒውተር ላይ የተጠመደ ፈንጅ በአውሮፕላን ማረፊያ ፍተሻ ላይ እንዳለ በመፈንዳቱ ስድስት ሰዎች የቆሰሉ መሆናችው ተነገረ። ይህ የአልሸባብ ድርጊት ነው ተብሎ የሚነገርለት ጥቃት የተፈጸመው በለደወይን በሚባለው የሱማሊያ ከተማ ሲሆን የጸጥታ አባላት በተመሳሳይ ጊዜና ቦታ ሌሎች ሁለት ፈንጅዎችን አምከነዋል ተብሏል። ከቆሰሉት ስድስት ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ፖሊሶች መሆኑ ታውቋል። ባለፈው ወር የአልሸባብ አባላት በላፕቶፕ ላይ ያጠመዱት ቦምብ በበረራ ላይ በነበረ አውሮፕላን  ውስጥ በመፈንዳቱ በአካሉ ላይ የክፍተት አደጋ ተፈጥሮ አውሮፕላኑ በአስቸኳይ ለማረፍ የተገደደ መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø አሌክ ባዴ የሚባሉት የናይጄሪያ የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር ሰኞ የካቲት 28 ቀን አስር በሚሆኑ የሙስና ክሶች ተከሰው በናይጀሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸው ተገልጿል። ባዲህ 19.7 ሚሊዮን ዶላር የሆነ ገንዝብ በማጉደል የተከሰሱ ሲሆን ከክሶች ውስጥ አንደኛው በ2005 ዓም ለአየር ኃይል ከተመደበው በጀት ውስጥ 6.9 ሚሊዮን ዶላር ስርቀው በአቡጃ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ህንጻ አስርተውበታል የሚል ነው። በሚቀጥለው ሀሙስ በዋስ የመለቀቅ ማመልከታቸው እስከሚታይ ድረስ ባዲህ በእስር ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ አዟል። ቀደም ብሎ የአየር ኃይል ሃላፊ የነበሩት ባዴህ የመከላኪያ ሚንትስትር በመሆኑ የተሾሙት በ2006 ዓም በቀደሞ ፕሬዚዳንት ሲሆን  ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የናይጀሪያ ወታደራዊ ተቋም በመሳሪያና በጥይት ችግር ተዳክሞ  በቦኮ ሃራም ተከታታይ የሆኑ ከፍተኛ ጥቃቶች ሲፈጸምበት መቆየቱ   ይነገራል።  

 

 

 

 

 

 

 

 

የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው የታክሲ ሹፌሮች የሥራ ማቆም አድማ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ከተሞች መዛመቱ ታውቋል። በተለይ በወሎ በወልዲያ የተጀመረው የታክሲዎችና የባጃጅ የሥራ ማቆም አድማ በደሴ በኮምቦልቻ በቆቦ በከምሴና በሌሎች የወሎ ከተሞች ዓርብ ዕለት ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል። የታክሲዎችና የባጃጅዎች የሥራ ማቆም አድማ ለማቆም የወያኔ ካድሬዎች ከወያኔ ፖሊስና ወታድሮች ጋር በመተባበር ሹፌሮችንና ባለንብረቶችን ለማስገደድና ለማስፍረራት ያደርጉት ሙከራ ውጤት አልባ በመሆኑ አዲስ የንግግርና የድርድር መንፈስ በተለይ ለታክሲና ለባጃጅ ባለንብረቶች እያቀረበ መሆኑ ታውቋል። ወለጋ ውስጥም የታክሲዎቹ የሥራ ማቆም አድማ የቀጠለ ሲሆን የወያኔ ፀጥታ ኃይሎች ከሥራ ማቆም አድማዎቹ ተከትሎ በከተማዋ ውጥረት እንዲሰፍን አድርገዋል።

 

Ø ትናንት የካቲት 25 ቀን 2008 ዓም ምሽት ላይ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ አንድ ቦይንግ 783 የሆነ አውሮፕላን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ተነስቶ ወደ ሮም ለመብረር ሲዘጋጅ በደረሰብት የፊት ጎማ ጊር ብልሽት በረራውን ለመሰረዝ መገደዱ ታውቋል። የፊት ጎማ ጊር መበላሸት በአውሮፕላኑ ላይ ከበድ ያለ ጉዳት ሲያደርስ በአንድ የአውሮፕላኑ አስተናጋጅ ላይ ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሷል። ስለ አውሮፕላኑ አደጋና ብልሽት የአየር መንገዱ ባለሥልጣኖች ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም። የዓይን ምስክሮች ግን አውሮፕላኑ መንገደኞችን አሳፍሮ ከጨረሰ በኋላ ወደ መንደረደሪያው ቦታ ሲያመራ የፊት ጎማ ጊሩ መሰበሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያን አየር መንገድ የሚከታተሉ ወገኖች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአየር መንገዱ ላይ ትናንሽና ጥቃቅን የሚባሉ ጉዳቶችና አደጋዎች እያደረሱበት መሆኑንም ይህም በአመዛኙ በቴክኒካል ብልሽት መሆኑ ይታወቃል። ችግሩ አየር መንገዱ በዘር ምርጫ መቅጠሩና ችሎታና ብቃትን መመዘኛ ባለማድረጉ የመጣ መሆኑን በመግለጽ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ብቃትና ችሎታ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ ተቀጥረው መስራት እስካልቻሉና ከአንድ ዘርና ከአንድ ድርጅት የመጡ ብቻ የሚቀጠሩበት እስከሆነ ድረስ ውድቀትን ማስከተሉ የማይቀር ነው ይላሉ።

 

Ø በአዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖዶስ ቋሚ አባላት ሳይታሰብ በድንገት ስብሰባ መቀመጣቸው ተገለጸ። ስብሰባው በድንገት የተካሄደው በብጹዕ አቡነ ናትናኤል ዕረፍተ ሞት ምክንያት ሲሆን በፓትርያርኩና በማሀበረ ቅዱሳን መካከል ስላለው ውዝግብ በዋናነት ይነጋገራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ስለ ስለ ሰላም፤ በሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ የተነሳ ስለተቃጠሉ  አብያተ ክርስቲያናት፤ ስለድርቅና ረሃብ፤ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ ስላለው የተዛባና ማዕከላዊነት ስለሌለው አሰራር፤ እንዲሁም ስለ ፓትርያርኩ የውጭ ጉዞ ይነጋገራል ተብሏል። ከቅርብ ጉዜ ወዲህ በፓትርያርኩና በሲኖዶሱ መካከል የሥራ አለመግባባት መፈጠሩ የታወቀ ሲሆን ፓትርያርኩ ያለ ቋሚው ሲኖዶስ ዕውቅና የሚወስዱት እርምጃና መግለጫ የቋሚ ሲኖዶስ አባላትን ያጠያየቀ ሆኗል። ለኢትዮጵያ ተወህዶ ኦሮትዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅርብ ነን የሚሉ ምንጮች ፓትርያርኩ ከመስመር እየወጡ እንደሆነና ከመንፈሳዊ መሪ ይልቅ የወያኔ ካድሬ እየሆኑ መምጣታቸውን ይገልጻሉ። በቅርብ ወደ ቫቲካን ተጉዘው የሮማውን ፓፓ በመካከለኛው ምስራቅ ስለሚገደሉና ስለሚታሰሩ ክርስቲያኖች ይጸለይ ብለው መጠየቃቸውን እንደ አብነት ያነሳሉ።   በኢትዮጵያ በአደባባይ ሰው እየተገደለና ዜጎች በግፍና በጭካኔ እየታሰሩ ድምጽ ፓትሪያርኩ ድምጽ ሳያሰሙ ለመካከለኛ ምስራቅ ክርስትያኖች እንጩህ ማለታቸው በኢትዮጵያ ግድያ እስር በደልና ጭቆና የለም ለማለት ነው በማለት ይተቿቸዋል።፡

 

Ø የሻዕቢያ አገዛዝ አግቷቸው የነበሩትን የማዕድን ፈላጊ ኢትዮጵያውያንን የለቀቀው በሱዳን መንግስት ሽምግልና መሆኑን የሱዳኑ ዕለታዊ ጋዜጣ ሱዳን ትሪቡን ገለጸ። የታገቱት ኢትዮጵያውያን ወርቅ ፈላጊ እንደነበሩና በሻቢያ ታጣቂዎች ታፍነው ወደ ኤርትራ ተሻገረው እንደነበርና ታፍነው የተወሰዱት ቁጥራችው 80 ይደርስ እንደነበረም አብራርቷል። ከታገቱት ወርቅ ፈላጊዎች መሃሉ ሁለቱ ለማምለጥ ሲሞክሩ በሻዕቢያ ወታደሮች የተገደሉ መሆናችው ጨምሮ ዘግቧል። ከወያኔና ከሻዕቢያ ጋር መልካም ወዳጀነትና ሽርክና ያላት ሱዳን ታጋቾቹ በሙሉ በሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ የተሳካ ሽምግልና ማድረጓን ጋዜጣው ይግለጽ እንጅ ወያኔም ሆነ ሻዕቢያ ስለ ሽምግልናውና ስለተለቀቁት ታጋቾች የገለጹት ነገር የለም። ጋዜጣው ግን ሱዳን በሻዕቢያ መሪ በኢስያስ አፈወርቂ ላይ ባላት ተጽእኖና ግፊት ምክንያት ታጋቾቹ መፈታታችው በጋዜጣው ተዘግቧል።

 

Ø አፍቃሪ ወያኔ የሆነውና በወያኔ ቡድን መሪዎች የተደራጀው ሰጎን የተባለው የሻዕቢያ ተቃዋሚ ቡድን ሰሞኑ በማህበራዊ ገጾች ላይ ያሰራጨው ሀሰተኛ ዜና የቡድኑን ማንነትና የወያኔን ተራ ፕሮፓጋንዳ አጋልጧል። ቡድኑ በማህበራዊ ገጾች ላይ እንዳስታወቀው የወያኔ የጦር አውሮፕላኖች ምጽዋ ወደብ አካባቢ የሚገኘውን የሻዕቢያ ጦር ካምፕና ማሰልጠኛ መድብደቡንና ቀይ ባህር ላይም በአንድ መርከብ ላይ ጥቃት መጣሉንና በእሳት እንዲጋይ ማድረጉን የዘገበ ሲሆን በዘገባው ላይ ተቃጠለች የተባለቸው መርከብ ጭስ አውስትራሊያ ውስጥ ከሶስት ዓመት በፊት በእሳት የጋየች መርከብ መሆኗ መረጋገጡ የወያኔ ፍጡር የሆነው ሰጎንና የወያኔ ፕሮፓጋድናሲቶች የፈጠሩትና ያሰራጩት ወሬ ገና ከመነሻው ፉርሽ እንዲሆን ተደርጓል።

 

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪሙን በሊቢያ የአይሲስ ኃይሎች እየተጠናከሩ መምጣቸው በጣም ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸው የምዕራብ አገሮች ጣልቃ በመግባት ሁኔታውን ማባባስ የለባቸውም በማለት ማስጠንቀቂያ መስጠታችው ታወቀ። ባንኪሙን ይህንን የተናገሩት ቅዳሜ የካቲት 26 ቀን 2008 ዓም የሞሪታንያ ጉብኝታችውን ጨርሰው ወደ አልጀሪያ ለመሄድ በሚዘጋጁበት ወቅት ነው። በተያያዘ ዜና ባለፈው ሐሙስ በተደረገ አሰሳ ሁለት ዜጎቹ መገደላቸው በጣም ያስቆጣውና ያሳሰበው የጣሊያን መንግስት ሊቢያን ለሚሰማራው የአለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል እሰከ  አምስት ሽ ወታደሮች ድረስ ለመላክ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል። ወታደሮች በመላክ በኩል ከሌልች ፓርቲዎች ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠመው የጣሊያን መንግስት  ወታደሮቹ የሚላኩት ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኘው የሊቢያ መንግስት ሲፈቅድ ብቻ ነው ብሏል።

በተያያዘ ዜና የዓለም አቀፉ ህብረተሰብን እውቅና ያገኘውና በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት አካል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የመድኃኒት እጥረት ያለ መሆኑን ገልጸው ሊቢያ በውጭ አገር የተያዘባት ገንዘብ እንዲለቀቅላት ጠይቀዋል። አገሪቱ በውጭ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እያላት ዜጎቿ በመድሃኒት እጥረት መሰቃየት የላባቸውም ብለዋል። በቱኒዚያ ባንኮች 290 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን የሊቢያ ገንዘብ የታገተ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸው ይህ ከጠቅላላው አንድ ከመቶ የማይሞላ ገንዘብ ቢለቀቅ እንኳ ትልቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል።

 

 

የናይጄሪያ መንግስት ከጥቂት ጊዜ ወዲህ ቦኮ ሃራም በተባለው አሸባሪ ቡድን ላይ እያካሄደ ያለው ተከታታይ ዘመቻ ውጤት እያስገኘ መሆኑ ይታወቃል። በርካታ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የተገደሉ መሆናቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ መያዛቸውና  እጃቸውን መስጠታቸው እንዲሁም ደግሞ በአሸባሪው ቡድን ቁጥጥር ስር በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ከእስር የተለቀቁ መሆናቸው በየጊዜው ተዘግቧል። ቡድኑን ይበለጥ ለማዳከምና በመጨርሻም ሽንፈት እንዲከናነብ ለማድረግ ስሞኑን በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በሚገኙ ሶስት ከተሞች የገበያ ቦታዎች የቡድኑ የገቢ ምንጭ ነው ተብሎ የተገመተው  የከብት እና የስጋ ንግድ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል። ከቦኮ ሃራም ድርጅት ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የሚጠረጠሩ ግለሰቦች ነጋዴ በመምሰል የቀንድ ከብቶች እያመጡ በገበያ ላይ የሚሸጡ መሆናቸው በመታወቁና ገንዘቡን በሽብር ላይ ለተሰማራው ድርጅት መጠቀሚያ ማድረጋቸው በመረጋገጡ ለተወሰነ ጊዜ ከብቶች እና  ስጋ በገበያ ላይ እንዳይሸጡ በይፋ ተከልክሏል። ማይዱግሪ በሚባለው የክፍለ ሀገር ከተማ የንግድ ፈቃድ ካላቸው በስተቀር  ለሁለት ሳምንታት ማንም ሰው ወደ ከተማው የቀንድ ከብቶች እንዳያስገባ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።

 

የግብጽ የፀጥታ ኃይሎች በሰላማዊ ስዎች ላይ በማካሄድ ላይ የሚገኙት አፈናና በደል መረን እየለቀቀ መምጣቱን የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እየተናገሩ ይገኛሉ። የጸጥታ ኃይሉ አባላት በዜጎች ላይ የሚያካሂዱት ድብደባ፤ እስራትና አለፍርድ ግድያ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ የሄደ ሲሆን ማንነታቸውን በደበቁ የጸጥታ ኃይሎች እየተጠለፉ በድብቅ የሚገደሉ ዜጎች ቁጥርም እየጨመረ መጥቷል ተብሏል። በቅርቡ ቢኒ ሱኤፍ በምትባል በግብጽ ደቡባዊ ክፍል በምትገኝ ከተማ ጭንብል የለበሱ ፖሊሶች  አንድ ስራው መሀንዲስ የሆነ ግለሰብን ከስራው ቦታው ወስደው ከአስራ አምስት ቀን በኋላ በመትረየስ ረሽነው የገደሉት መሆኑ ታውቋል። በተደጋጋሚ በቁጥጥራቸው ስር አለመሆኑን ለቤተሰቡቹ የገለጹት ፖሊሶች  ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ሟቹ የሙስሊም ወንድማማቾች አባል መሆኑና ፖሊሶችን ለመግደል ሙከራ ሲያደርግ የተገደለ መሆኑን በመግለጽ ቤተሰቦቹ ጠርተው አስከሬኑን እንዲወስዱ አድርገዋል።  የሟቹ አባላት “ልጄን ፖሊሶች ከያዙት በኋላ አሰቃይተው ገድለው እንድቀብረው ሰጥተውኛል፤ መንግስትን ለመዋጋት ግን አቅም የለኝም ብለዋል”… በግብጽ ውስጥ የፖሊሶች ስልጣን አደብ እያጣ መምጣቱና  አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በርካታ ሰዎች የሚናገሩ ሲሆን የሕዝብ በደል እየተበራከተ ከመጣ ወደ አመጽ ሊያመራ የሚችበት መንገድ ሰፊ መሆኑን ይጠቅሳሉ። በጭለማ ዜጎችን ከየቤታቸው በማፈንና በቀን ከቤተሰቦች ጋር ፈላጊ ሆኖ መገኘት የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ገና ወደ ስልጣን ሲወጡ የተካኑበት ስልት መሆኑን ብዙዎቹ ያስታውሳሉ።

 

 

የካቲት 25 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በአዲስ አበባ የተጀመረው የታክሲዎች የሥራ ማቆም አድማ የማኅበሩ መሪዎች ከወያኔ ባለሥልጣናት ጋር ባደረጉት ንግግርና ድርድር ለጊዜውም ቢሆን የሥራ ማቆም አድማውን ለመግታትና ወደ ሥራ ለመመለስ ስምምነት ላይ መድረሳቸው በሚነገርበት በአሁኑ ሰዓት በወሎ በወልድያና በደሴ የተጀመረው የታክሲና የባጃጅ የሥራ ማቆም አድማ ለመግታት የወያኔው ብአዴን ካድሬዎች ልዩ ልዮ ማስፈራሪያ ቢያቀርብም ሾፌሮቹ ወደ ሥራ ለመመለስ ጥያቄዎቻቸው ሳይሸራረፍ እንዲመለሱ ጠይቀዋል። የታክሲና የግዳጁ ባለንብረቶችም  ሥራ ካልጀመሩ ታርጋ እንደሚነጠቁ ቢገለጽላቸውም ከታክሲ ሾፌሮች ጋር ያላቸውን አንድነት በመግለጻቸው የወያኔው ብአዴን ካድሬዎች የንግድ ፈቃዳችሁን እንሰርዛለን የሚል ማስፈራሪያ በማቅረባቸው ባለንብረቶቹ ይህን አታስብ የሚል መልስ እንደሰጧቸው ታውቋል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ለ24 ዓመታት ሕዝብን የሚያፍንና የሚያስጨንቅ ሕግ በማውጣትና  ዘወትር ሕዝብ ስለ ዕለት ኑሮው ብቻ እንዲያስብ ለማድረግ የተጠቀሙበት ዜዴ አሁን ላይ ተቀባይነት እያጣ መምጣቱና መብቱን ለማስከበር ተቃውሞን በልዩ ልዩ መንገዶች መግለጽ መጀመሩ የወያኔ መሪዎችን እያሸበረ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ በተመድ የጸጥታ ምክር ቤት ውስጥ የተለዋጭ ቦታ ለማግኘት ይፋ የምረጡኝ ዘመቻ መጀመሩ ታወቀ። የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ድጋፉን እንዲሰጠው በይፋ ጠይቋል። በ1950 ዎቹና በ 1960 ዎቹ የኢትዮጵያ ወታደሮች ለሰላም ማስከበር በኮንጎና ኮርያ የዘመቱ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን  በወያኔ አገዛዝ ግን ከወያኔ ጦር ውስጥ በዘራቸውና በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ የተመረጡ ከስምንት ሺህ በላይ ወታደሮቹን በሰላም አስከባሪነት ስም በሩዋንዳ በብሩንዲ ላይቤሪያ ኮትዲቩዋር ደቡብ ሱዳንና በሶማሊያ ማሰማራቱ ይታወቃል። የወያኔ መሪዎች የውጭ ምንዛሬ ለማግኛና ወታደራዊ አዛዦቻቸውን ለመጥቆም የተስማሩበት የሰላም አስከባሪነት ስራ የወያኔ ባለስልጣኖች ለተመድ የጸጥታ ምክር ቤት ተለዋጭ መቀመጫ ለማግኘት እንደ ጥሩ መንደርደሪያ እያቀረቡት ነው። ብዙ ወገኖች ግን ከ90 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ክልል በሚባል የሕዝብ እስር ቤት ያጎረ የሰብዓዊ መብትን የረገጠ፤ የመጻፍና የመናገር መብትን የከለከለ፤ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን ያሰረ አገዛዝ ለሕዝብ  አብሮ መኖርና ለሰብአዊ ክብር ለቆመ ዓለም አቀፉ ድርጅት ውስጥ በተለዋጭነትም ሆነ  በጊዜያዊነትም ቢሆን ኃላፊነት የማይገባው ዘረኛ አምባገነን ነው ይላሉ።

 

Ø የግብጽ መንግስት በድርቅና በረሃብ ለተጎዱ ኢትዮጵያውያን የሚውል የአንድ ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ በዓለም የምግብ ፕሮግራም በኩል መስጠቷን የዓለም የምግብ ድርጅት ከጣሊያን ሮማ ከተማ አስታውቋል። እንደ ግብጽ የትብብርና የልማት ኤጀንሲ ከሆነ የዕርዳታ ገንዘብ ከ 1700 ሜትሪክ ቶን በላይ ምግብ እንደሚገዛና በረሃብና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖችና ቤተሰቦች የሚከፋፈል ይሆናል ብሏል። የግብጽ መንግስት ለተመድ የዓለም  ፕሮግራም ይህን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ ሲለግስ የመጀመሪያው ሲሆን በዓለም የምግብ ፕሮግራም በኩል ከተዳከመ የዕርዳታ ገንዝብ ጀርባ ግብፅ ሊያስተላልፈው ያልፈለገው መልእክት ወይንም በልዋጭ ያገኘው ነገር ግን አልታወቅም።

 

Ø በተመሳሳይ ዜናም የአሜሪካን መንግስት በኢትዮጵያ ያለፈውን የረሃብና የድርቅ ሁኔታ አጥንቶና ተመክቶ ሪፖርት የሚያቀርብ ልዩ የባለሙያ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መላኩ ታውቋል። እነዚህ አንድ  ደርዘን የሚሆኑና ከአሜሪካ ዓለም አቀፉ የልማት ዕርዳታና የአደጋ ምላሽ ሰጭ ቡድን አዲስ አበባ የገባ ሲሆን የአሜሪካን ዕርዳታ ስለሚቀናበርበት ሁኔታ ያስተባብራሉ ተብሏል። በቅርቡ የተመጠነ ምግብ የውሃ የንፅህና ሃይጅን ባለሙያዎች ወደ አዲስ አበባ ያመራሉ ተብሏል። የተመድ  ለኢትዮጵያው ድርቅና ረሃብ ለ 4 ቢሊዮን ዶላር ዕርዳታ የጠየቀ ሲሆን ይህ ገንዘብ በዓለም ላይ ዕርዳታ ከሚያስፈልጋቸው ከሶርያና ከየመን ቀጥሎ በሶስተኛነት አስቀምጠውታል። አሜሪካ የዝናብ ወቅት በመምጣቱና ገበሬዎች የዘር እህል ስለሌላቸው በ4 ሚሊዮን ዶላር የበቆሎና የስንዴ ዘርም ማቅረቧ ተገልጿል።

 

Ø በሊቢያ በታጣቂዎች ታግተው የነበሩ ሁለት የኢጣሊያ የህንጻ ሠራተኞች መለቀቃቸውን አንድ የአካባቢ ባለስልጣን ገለጸ። ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ውስጥ  ኤኒ የሚባለው የነዳጅ አምራች ኩባንያ ተቀጣሪ ሆነው በምዕራብ ሊቢያ ሲሰሩ የነበሩ አራት ጣሊያናውያን በታጠቁ ኃይሎች መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን ሀሙስ የካቲት 24 ቀን 2008 ዓም የጸጥታ ኃይሎች ባደረጉት አሰሳ ሁለት የተፈቱ መሆናቸው ሲገለጽ የተቀሩት ሁለቱ ሳይሞቱ አይቀሩም ተብሏል። ከአራት ዓመት በፊት የሊቢያ መሪ ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ ሊቢያ ውስጥ ከፍተኛ የፖሊቲካ ቀውስ መፈጠሩና በምስራቅና በምዕራብ የአገሪቱ ክፍሎች  ራሳቸውን መንግስት ብለው የሚጠሩ ሁለት አካሎች መቋቋማቸው ይታወሳል።

 

Ø በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የተሰማሩት የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በሴቶች ላይ የሚፈጽሟቸው አስገድዶ የመድፈርና ሌሎች አስከፊ ተግባሮች እየተባባሱ መሄዳቸውን በቅርቡ የተሰራጨ አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዘገባ ገለጸ። እንደአውሮፓውን ዘመን አቆጣጠር 2014 ላይ በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የተፈጸሙት ወንጀሎች 52 የነበሩ ሲሆን በ2015 ዓመተ ምህረት ይኸው ቁጥር ወደ 69 ከፍ ብሏል። ወንጀል ፈጻሚዎቹ ወታደራዊ መኮንኖች የዓለም አቀፍ የፖሊስ ኃይሎች እና ሌሎች ሰራተኞች እንዲሁም በፈቃደኛነት አለክፍያ የሚሰሩ ሰራተቾች ያሉትበት ሲሆን የመጡትን እንደፈረንሳይ ከመሳሰሉ የአውሮፓ አገሮችና ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ነው።

 

Ø የዚምባብዊየው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ በአገራቸው ውስጥ ያለው ማዕድን  የማውጣት ስራ ከውጭ ኩባንያዎች ተወስዶ በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚደረግ መሆኑን ሐሙስ የካቲት 24 ቀን 2008 ዓም የዚምባብዌ ብሮድካስቲንግ ኮርፔሬሽን ለሚባለው የአገሪቱ የመገናኚያ ብዙሃን በሰጡት ቃል ምልልስ ገልጸዋል። በባዕድ ኩባንያዎች የሚካሄደው የአገሪቱ የአልማዝ ማዕድን  በከፍተኛ ደረጃ እየተዘረፈ በመሆኑ አገራችው  እስካሁን ድረስ ከማዕድን ስራ ያገኘችው ገቢ እንደሌለ ተናግረው የማዕድኑ ስራ በመንግስት ቁጥጥር ስር መዋል አለበት ብለዋል። ባለፈው ወር የዚምባብዌ የማዕድን ሚኒስትር በምስራቃዊ የአገሪቱ ክፍል ያለውን የማዕድን ቦታ የስራ ፈቃዱ ጊዜ ከተጠናቀቀ የባዕድ ኩባንያ ላይ ተወስዶ በመንግስት ቁጥጥር ስር የተደረገ መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል።

በተያያዘ ዜና በአገሪቱ ማራንጅ ተብሎ በሚጠራው የአልማዝ ማዕድን ማውጫ ስፍራ በደረሰው የመሬት መደርመስ ሶስት ህገ ወጥ ማዕድን ቆፋሪዎች መሞታቸውና ሌሎች ሰባት የሚሆኑት እስካሁን  መውጣት ያልቻሉ መሆናቸውን የፖሊስ ምንጮች የካቲት 24 ቀን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።

 

Ø የናይጄሪያ መንግስት በሞኖፖል  በቁጥጥር ስር አድርጎት የቆየውን ግዙፍ  የነዳጅ ኩባንያ ስለሳ በሚሆኑ ትናንሽ ኩባንያዎች የከፋፈለ መሆኑ ተነገረ። ኩባንያውን በትናንሽ ኩባንያ መከፋፈል አስፈላጊ የሆነበት ዋና ምክንያት በገፍ እየተካሄደ ያለውን ሙስና ለማስቀረትና የስራ ቅልጥፍና ለማስፈን ነው ተብሏል። በነዳጅ አምራቹ ኩባንያ ላይ የመዋቅርና የአሰራር እርምት የተጀመረው ከጥቂት ወራት በፊት የቡሃሪ አስተዳድር ነባሩን የኩባንያውን ቦርድ ካፈረሰ በኋላ እና ስራው ተመክሮ ባለው ዲሬክተር እንደመራ ካደረገ በኋላ ነው ። ከዚያን ጊዜ ጀመሮ የኩባንያው ኪሳራ በዓመት ከ160 ቢሊዮን የናይጄሪያ ኒያራ ወደ 3 ቢሊዮን ኒያራ ዝቅ ማለቱ ይነገራል።

በተያያዘ ዜና ሐሙስ የካቲት 24 ቀን 2008 የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የሚገኙትን ሶስት መንደሮች ከቦኮሃራም ቁጥጥር ስር ነጻ ማድረጋቸውንና 63 ሰዎች ማስለቀቃቸውን የተቋሙ ቃል አቀባይ ገልጿል። በዘመቻው አምስት ታጣቂዎች ሲገደሉ በርካታ መሳሪያና ጥይት የተያዘ መሆኑም ተነግሯል። ከዚህ በተጨማሪ አልጋርኖ በተባለው ጫካ ውስጥ የቦኮሃራምን መደበቂያ ቦታዎች ጦሩ በአሰሳ መስክ የደመሰሰ መሆኑና በርካታ ንብረቶች የያዘ መሆኑን ገልጿል።

 

 

የካቲት 24 2008 ዓ.ም.

 

ከሁለት ወር በፊት የአዲስ አበባ ታክሲ ሾፌሮች የጀመሩት የሥራ ማቆም አድማ ወደ ሌሎች ከተማዎችም እየተዛመተ መሆኑ ታውቋል። አምቦ፣ ወሊሶ፣ ናዝሬት፣ ቃሊቲ ሌሎችም ከተሞች በስራ ማቆም አድማው ተሳታፊ ሲሆኑ ወሎ ወልዲያ ውስጥም ዕሮብ የካቲት 23 ቀን ጀምሮ የሥራ ማቆም አድማ ተጀምሯል። ወያኔ ያወጣው የትራንስፖርት ሕግና ደንብ ሀገራዊ አዋጅ በመሆኑ ሁሉንም አሽከርካሪዎች መብት የሚጋፋ ሲሆን የነዳጅ ዋጋም ከፍ ማለት ለሥራ ማቆም አድማው ምክንያት መሆኑ ታውቋል። ወያኔ በተለይም የአዲስ አበባ ታክሲ ሾፌሮች አድማን ተከትሎ ያወጣው ሕግና ደንብ ቢያንስ ለሶስት ወር ተግባራዊ አይሆንም፤ ስለ ሕጉም ተጨማሪ ማብራሪያና ግንዛቤ ማስጨበጫ ይሰጣል ይበል እንጅ አድማው አድማሱን እያሰፋው መሆኑ ታውቋል። የወያኔ አገዛዝ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ  አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ለመጠቅለል ያወጣው ፕላን ተቃውሞና ቁጣን ቀስቅሶ ከ250 በላይ ተገድለው በሺህ የሚቆጠሩ ታስረውና ቆስለው ትግሉ ከሶስት ወር በላይ በቀጠሉበት በጎንደር የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ባነሳበት በጋምቤላ ወታደራዊ ግጭት በተለኮሰበት ሰዓት የሥራ ማቆም አድማው እየተስፋፋ መምጣቱ የወያኔ አገዛዝ በእርግጥ 11 ኛ ሰዓት ላይ ነው የሚሉ ታዛቢዎች ብዙ ናቸው።

 

የወያኔ ብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴው ከዛሬ ከየካቲት 24 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ ስብሰባ እንደሚቀመጥና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚሞክር የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የወያኔ ብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴው በዚሁ ስብሰባው ያለፉትን ስድስት ወሮች የሥራ አፈጻጸም እገመግማለሁ የድርቁን ሁኔታ እመለከታለሁ የተወጠኑትን ልማቶች እዳሣለሁ ይበል እንጅ በዋናነት በመላ አገሪቱ ስለተቀጣጠለው ተቃውሞና ቁጣ፤  ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስለተጀመረው የሥራ ማቆም አድማና በጎንደር የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ስላነሳው የማንነት ጥያቄ እንደሚመክርበት ተናግሯል። የወያኔ መሪዎች ለብአዴን ባለሥልጣኖች በተደጋጋሚ ጊዜ የወልቃይት ሕዝብን ለመሸንገል ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን አካባቢው በትግራይ ስር እንዲሆን ያቀረበላቸውን ምልጃ አንዳልተቀበሉት  ይታወቃል። በርካታ ይወያኔው ብአዴን አባላት ብአዴን ራሱን ችሎ እንደቆመና በሁሉም መስክ የወያኔ የባላይነት ለመግታት መንቀሳቀስ አለበት በማለት ጥያቄ አንሰተዋል። ብአዴን ለወያኔ ዋና ቀኝ እጁና ታማኝ ሎሌ መሆኑን በመቃወም አንዳንድ ካድሬዎች ሳያስፈነግጡ እንዳልቀሩ ይነገራል።

 

የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ የወያኔ ቡድን በግዴታ የትግራይ ማንነት ተሰጥቶኛል በሚል ያነሳውን ተቃውሞ እየቀጠለና ውጥረቱ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የወያኔ መሪዎች 70 ሺ የትግራይ አባወራዎችን በወቃይት ጠገደና በቤንሻንጉል ለማስፈ ማቀዳችው ታውቋል። የሰፈራ ፕሮግራሙ በትግራይ ውስጥ በድርቅና በድኽነት ተጎዱ የተባሉትን አባ ወራዎች ማስፈር ብቻ ሳይሆን ራሳቸውን እንዲከላከሉ ማስታጠቅንም የሚያካትት መሆኑ ለሕዝብ ግጭት ወያኔ ሆን ብሎ እየሠራ መሆኑን አሳይቷል። የትግራይ የሀገር ሽማግሌዎችና ታሪ አዋቂዎች የትግራይ ድንበር እስከ ተከዜ ነው በማለት በግልጽ በመናገር ወያኔ ከወልቃይት ጠገዴና ከሁመራ የትግራይ አገዛዝ እንዲወጣ  ያቀረቡለትን ምክር ችላ በማለት የሠፈራ ፕሮግራም ለመጀመር ማቀዱ በተነሳው የተቃውሞ እንቅስቃሴና  ባለው ውጥረት ላይ ቢንዚን እንደማርከፍከፍ ይቆጠራል የሚሉ ወገኖች አሉ።፡

 

የወያኔ ኦህዴድ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ኃላፊዎቹ ከሥልጣን ተባረው ሹም ሽር ተደረገ ከተባለ ወዲህ የመጀመሪያ የሆነውን ስብሰባ ትናንት የካቲ 23 ቀን 2008 ዓ.ም. በናዘሬት መጀመሩ ተሰምቷል። የስበስባው ዓላማ ተደረገ ስለተባለው ሹም ሽርና ስለቀጥለው ሕዝባዊ ተቃውሞ ቁጣ መሆኑ ሲነገር በወያኔ መሪዎች የተደረገው ሹም ሽር ብዙዎቹ የኦህዴድ ካድሬዎችን ያስቆጣና ያሳዘነ ስለሆነ ይፋ የሆነ ተቃውሞ ይገጥመዋል ተብሎ ይጠበቃል።የወያኔ መሪዎች የአዲስ አበባ አጎራባች ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ለመጠቅለል ያወጡትን ማስተር ፕላን በመቃውም በመላ አገሪቱ ባሉ ከተሞች ከፍተኛ ሕዝባዊ ቁጣ ከቀሰቀሰ ወዲህ ቁጣውን መከላከል አልቻላችሁም ተብለው የወያኔው ኦህዴድ ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዳባ ደበሌ ከሥልጣኑ ሲባረር በእርሱ ምትክ በከር ሻሌ መሾሙ ይታወቃል። እንዲሁም የኦህዴድ የከተሞች ዘርፍ የፖሊቲካ ኃላፊ ሲሳይ ዛዩ ከስልጣኑ ሲነሳ ሳዳ ነሻ ተክቶታል። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ የነበረው በዙ ጭቅቢሳ የጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሆኖ ሲመደብ ሰለሞን ክፑማ የኦህዴድ ፕሬዚዳንት አማካሪ ተብሏል። ወያኔ የሕዝብን ጥያቄ በጥይትና በእስር በድብደባ ለመመልስ እየሞከረ በኦህዴድ ውስጥ ሹም ሽር በማድረግ ሕባዊ ተቃውሞውን ለማብረድ መሞከሩ በሕዝባዊ ቁጣ ላይ የሚያመጣው ምንም ዓይነት ለውጥ እንደማያመጣ ብዙዎቹ ይስማሙበታል።

 

በወያኔ የተደራጁትና በስደት የኑዌር ጎሳ ወጣቶች አንድነት የተባለው ቡድን ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በጻፈው ደብዳቤ በኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኅብረት የደቡብ ሱዳን ልዑክ በመሆን የተሾሙትን ድምስ ሞርጋንን ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀዋል። ቡድኑ ጀምስ ሞርጋንን የአማጺ ቡድን አባልና ደጋፊ ናቸው በማለት ክስ ያቀረበ ሲሆን በኬኒያ ናይሮቢ የደቡብ ሱዳን ምትል አምባሳደር ሆነው ሲሰሩ ለሶስት ዓመታት ያህል ኢትዮጵያውያንን ሲሰልሉ ነበር በማለት ለጋምቤላ አማጽያን መሪ ፖል ፓይ አባላትን ይመለምሉ ነበር ብሏል። በወያኔ የተፈጠረውን የተደራጀው የኑር ወጣቶች አንድነት በአንድ ሀገር ሹመትና የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት ደብዳቤ መጻፉ ብዙዎችን ያሰገረመ ሲሆን የደቡብ ሱዳን መንግስት ለቡድኑ የሰጠው ምላሽ የለም።

 

በኢትዮጵያ የገባው ድርቅና ረሃብ በከፍተኛ ደረጃ እየተባባሰ መሄዱን የዜና ምንጮች እየገለጹ ይገኛሉ። ከጥቂት ወራት በፊት የቢቢሲው ጋዜጣኛ በኮረምና በአላማጣ ተገኝቶ የአጠናከረው ዘገባ አስመልክቶ የወያኔ ባለስልጣኖች ከፍተኛ ተቃውሞ በማሰማታቸው ምክንያት በየመስኩ የሚገኙ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ጋዜጠኞችን ለመጋበዝ ባይፈቅዱም ሰሞኑን በአንዳንድ ቦታዎች ዘልቆ የድርቁን ሁኔታ የተመለከተው የጋርድያን ጋዘጤኛ የችግሩ መጠን አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጿል። በድርቅ ያለቁ ከብቶች በርካታ መሆናቸውን ፤ ህጻናት በምግብ እጥረት እየተሰቃዩ የሞት አፋፍ ላይ መሆናችውን፤ ለድርቅ የሚከፋፈለው እህል ለቤተሰብ የማይበቃ መሆኑንና የሚከፋፈለውም በአድልዎ መሆኑን እንዲሁም እህል ለመግዛት ከሞት የተረፉ  ከብቶቻቸውን እንዲሸጡ ባለስልጣኖች እንደሚያስገድዷቸው ነዋሪዎች መናገራቸውን ዘግቧል። ሁኔታው በዚህ ዓይነት የሚቀጥል ከሆነም ሌላ ዙር እልቂት ሊከተል እንደሚችል አስጠንቅቋል።

 

ተውፊቅ ኦካሻ የሚባሉት የግብጽ ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ የእስራኤሉን አምባሳደር በቤታቸው ጠርተው በመጋበዛቸው እና ከግብጽ የጸጥታ ሁኔታ አንጻር ምስጥራዊ ተብሎ በሚገመት ጉዳይ ላይ ውይይት እና ስምምነት በማድረጋቸው ምክር ቤቱ እንዲባረሩ የወሰነ መሆኑ ተገለጸ። ምክትል አፈጉባዔው አል መስሪ አልዮም ለተባለው ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ ባለፈው ሳምንት ከእስራኤሉ አምባሳደር ጋር መገናኘታቸውንና በኢትዮጵያ የሚሰራውን ግድብ አስመልክቶ እስራኤል ቁልፍ ሚና ሊኖራት እንደሚችል  መስማማታቸውን ገልጸዋል። ተውፊክ ከእስራዔሉ አምባሳደር ጋር ተገናኝተው ስለግድቡ ጉዳይ መነጋገራቸው የምክር ቤት አባላቱን በከፍተኛ ደረጃ ያበሳጨ ከመሆኑም በላይ አንዳንዶቹም በጫማ እስከመድበደብ ደርሰዋል።  የግድቡን ጉዳይ እንደከፍተኛ ብሔራዊ የጸጥታ አደጋ የሚያዩት ከሁለት ሶስተኛ በላይ የሆኑ የግብጽ የምክር ቤት አባላት ተውፊክ መቀመጫቸውን እንዲያጡ ወስነዋል። በተውፊክ ላይ የተወሰደው እርምጃ የእስራኤሉን አምባሳደር በቤታቸው መጋበዛችው ሳይሆን ለአገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ቁልፍ የሆነውን ጉዳይ አንስተው በመነጋገራቸውና ስምምነት በማድረግ የውጭ ጣልቃገብነትን በመጋበዛቸው  ነው ተብሏል። ግብጽ እና እስራኤል በ1971 ዓም የዲፕሎማቲክ ግንኙነት ቢመሰርቱም እስራኤል በፍልስጥየሞች ላይ በምትወስደው ጠንካራ እርምጃ ምክንያት ግንኙነታቸው ቀዝቃዛ ሆኖ ቆይቷል።  

 በተያያዘ ዜና የግብጽ ወታደራዊ ፍርድ ቤት በሚያዚያ 2007 አውቶቡስ በሚጠበቁ ወታደሮች ላይ ቦምብ በማፈንዳት ሁለት ወታደሮች ገድለዋል ተብለው የተከሰሱትን ሰባት ሰዎች የሞት ፍርድ የበየነባችው መሆኑ ተገልጿል። ሞት የተፈረደባቸው ሰዎች ከፊሉ በሲና በረሃ የሚኖሩ ሲሆን ከፊሉ ነዋሪነታቸው ካይሮ ውስጥ መሆኑ ታውቋል ። በሌላ በኩል በአሌክሳንድርያ ከተማ የሚገኝ ፍርድ ቤት ደግሞ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ አምስት ሰዎች በ25 ዓመት እስራት እንዲሁም ሁለት በአስራ አምስት አመትና ሌሎች አራት በሶስት አመት እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

 

አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣን ረቡዕ ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጠቱ መረጃ በደቡብ ሱዳን ግጭቱ ከተጀመረ ከ2006 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ከ50 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ መሆናቸው ገልጸዋል። በባለስልጣኑ የተሰጠው ቁጥር ሌሎች የሰብአዊ እርዳታ ድርጅቶች ከሚያስቀምጡት ግምት በአምስት እጥፍ የላቀ መሆኑ ታውቋል። ባለስልጣኑ ከ.4.2 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ስደተኛ የሆነ በመሆን ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ መሆኑና እንዲሁም በከፍተኛ ደረጃ ህዝቡን ሊጨርስ የሚችል ረሃብ እየተከሰተ መሆኑን ገልጸዋል።

 

ከሊቢያ ወደ ቱኒዚያ የገቡ አምስት የታጠቁ ሰዎች ከጸጥታ ጠባቂዎች ጋር ከአንድ ሰዓት በላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የተገደሉ መሆናቸውን የቱኒዚያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ረቡዕ የካቲት 23 ቀን 2008 ዓም ከሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪም አንድ ሲቪል መሞቱና እንድ የቱኒዚያ ወታደር መቁሰሉ ተነግሯል። ቁጥራቸው ያልታወቀ አሸባሪዎች ከሊቢያ ተነስተው የቱኒዚያን ወሰን ካቋረጡ በኋላ አንድ ቤት ውስጥ መሽገው በተደረገው የተኩስ ልውውጥ መገደላቸው የተነገረ ሲሆን በርካታዎቹ ሸሽተው ማምለጣቸው ተገልጧል። በርካታ የካላሽን ጠመንጃዎችና ጥይቶች እንዲሁም የፒክ አፕ መኪናዎች የተያዙ መሆናቸው ተነግሯል። ከጥቂት ቀናት በፊት ከቱኒዚያ ወሰን አቅራቢያ በምትገኘው የሳብራታ ከተማ ውስጥ ሰፍሮ በሚገኘው የአይሲስ ጦር ላይ አሜሪካ የአየር ጥቃት ማካሄዷ የሚታወስ ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የቱኒዚያ የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ ላይ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። 

 
   
   

yekatit 2

Ø በትናንትናው ዕለት በእስራዔል አገር የሚገኙ በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን  በሀምሌ 2006 ዓም  የሴፍ ሳላምሳ ለተባለው ዜጋ ህይወት መጥፋት ምክንያት ነበር የተባለው የፖሊስ አባል በወንጀል እንዳይከሰስ የእስራኤል ባለስልጣኖች ያደረጉትን ውሳኔ  በመቃወም ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ መሆናቸው ታውቋል።  በሰልፉ ላይ በነበረ ግጭት ከስምንት ሰዎች  በላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተነግሯል። የዛሬ ሁለት ዓመት ዮሴፍ ሳላምሳ ራሱን ለማጥፋት ምክንያት የሆነው ቀደም ብሎ ፖሊስ ዮሴፍን በቁጥጥር ስር ለማድረግ የኤሌክትርክ ንዝረት የሚረጭ መሳሪያን በመጠቀም ራሱን እንዲሰት ስላደረገው ነው የሚል ማስረጃ ቢኖርም አቃቤ ህጉ ፖሊሱ በወንጀል እንዳይከሰስ የወሰነ መሆኑ ታውቋል።፡

በተያያዘ ዜና የዛሬ ሁለት ዓመት ወደ ጋዛ ዘልቆ የነበረ የእስራኤል ዜግነት ያለው  ትውልደ ኢትዮጵያዊ እስካሁን ድረስ መዳረሻው የጠፋ በመሆኑ በሃማስ ቁጥጥር ስር ሳይሆን አይቀርም ተብሎ ተገምቷል። አበራ መንግስቱ  የአይምሮ በሽተኛ የሆነ ትውልደ ኢትዮጵያ ነው የተባለ ሲሆን በ2006 ዓም ወሰን አቋርጦ ወደ ጋዛ ከገባ በኋላ የት እንደደረሰ አልታወቀም። የአበራ መንግስት የቅርብ ዘመዶች ጄኔቫ ድረስ በመዝለቅ ግለሰቡን ለማስለቀቅ የዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ጋዛን በሚያስተዳድረው  በሃማስ ላይ ተጽእኖ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። አያይዘውም አበራ መንግስቱ ወታደር ሆኖ የማያውቅ የአእምሮ በሽተኛ በመሆኑ ሊለቀቅ ይገባል ብለዋል።  አበራ መንግስቱ ጥቁር በመሆኑ የእስራኤል መንግስት እስካሁን ድረስ ጉዳዩን ችላ ብሎታል በማለት በርካታ ወገኖች የሚያቀርቡትን ክስ ዘመዶቹ አስተባብለዋል።

 

Ø ሰኞ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓም በናይጀሪያ ከሌጎስ ከተማ አጠገብ ከሚገኝ አንድ የአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት ውስጥ የታጠቁ ሰዎች ሶስት ልጃገረዶችን ጠልፈው የወሰዱ መሆናቸው ተነግሯል።  ሴት ተማሪዎቹ ተጠልፈው የተወሰዱት ከትምህርት ክፍል ይሁን ከመኝታ ቤት አልታወቀም።  አካባቢው  ጠለፋ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው የተባለ ሲሆን ፖሊሶች ከፍተኛ ፍለጋ እያደረጉ መሆናቸው ታውቋል። በደቡብ ናይጄሪያ ውስጥ አብኛውን ጊዜ ካሳ ከተከፈለ በኋላ ተጠላፊዎቹ የሚለቀቁ ሲሆን እነዚህም በፖሊሶች ካልተገኙ ተመሳሳይ ክፍያ በማድረግ ማስለቀቅ ይቻላል የሚል ግምትና ተስፋ ያላቸው በርካታ ናችው። ከጥቂት ዓመታት በፊት ቺቦክ በሚባለው የሰሜን ናይጄሪያ ከተማ ከ200 በላይ የሚደርሱ በትምህርት ላይ የነበሩ ልጅአገረዶች በቦኮ ሃራም ተጥልፈው መወሰዳቸው ይታወሳል።

በተያያዘ ዜና በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ከምትገኘው ማይዱጉሪ ከተማ አጠገብ ጉዎዛ በተባለው ቦታ ባለፈው ቅዳሜ የካቲት 19 ቀን 2008 ዓም 76 የሚሆኑ ረሃብ ያጠቃቸው የቦኮ ሃራም አባላት እጃቸውን ለባለስልጣኖች የሰጡ መሆናቸውን የወታደራዊ ቃል አቀባይ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 23 ቀን 2008 ዓም ገልጿል። እጃቸውን ከሰጡት መካከል ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት ሲሆን ሁሉም በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። እጃቸውን የሰጡትና የተያዙት ይኖሩበት በነበረው አካባቢ ከፍተኛ የምግብ እጥረት መኖሩን ገልጸው ሌሎች በርካታዎች እጃቸውን ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል። የናይጄሪያ ባለስልጣኖች ባለፉት መስከረምና ጥቅምት ወራት በርካታ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች እጃቸውን መስጠታችውን መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን በፈቃደኛነት እጅ የሚሰጡት ታጣቂዎች ትምህርት ከተሰጣቸው በኋላ ወደ ህብረተሰቡ እንዲመለሱ የሚደረጉ መሆናችው ተገልጿል።

 

Ø ወደ ፊት እንጓዝ (Go forward) በሚል ስም የሚጠራው የዩጋንዳ የተቃዋሚ ፓርቲ በዩጋንዳ የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ ውድቅ መሆን አለበት በማለት በአገሪቱ የበላይ ፍርድ ቤት ላይ ክስ የመሰረተ መሆኑ ታውቋል። ፓርቲውን በመወከል የተወዳደሩት የምርጫው ኮሚሽን አገኙ ካላቸው ድምጽ በላይ ማግኘታቸውን ያረጋገጡ መሆናቸውን በመዘርዘር ውድድሩ ማጭበርበር የተሞላበት የማስመሳያ ምርጫ ነበር በማለት ድርጅቱ ከሷል።  ከድምጹ 35 ከመቶ አግኝተዋል ተብለው በሁለተኛ ደረጃ እንዲቀመጡ የተደረጉት የሌላው ፓርቲ መሪ ሚስተር ቢስጌ አሁንም በቤቱ ውስጥ ታግተው ያሉ ሲሆን በፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ለመንግስቱ የህግ ሽፋን መስጠት ነው በሚል ምክንያት ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ለመውሰድ አንፈልግም ብለዋል። ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ ቼንጅ የተባለው ቢሲጌ የሚመሩት ፓርቲ  በርካታ አባላት ምርጫው የተጭበረበረ መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሰብሰው ለፍርድ ቤት ሊያቀርቡ በሚዘጋጁበት ወቅት በድንገት በኡጋንዳ የጸጥታ ኃይሎች  በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል። በርካታ ታዛቢዎች ምርጫው ማጭበረበር የበዛበት፤ ገለልተኛነት እና ግልጽነት የጎደለው፤ ከፍተኛ ማስፍራራትና የኃይል እርምጃ የነበረበት  በመሆኑ ተአማኒነትና ተቀባይነት አይኖረውም ብለዋል።  

 

 

 

የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ለአራት ወራት የቀጠለውን የሕዝብ ተቃውሞና ቁጣን ለማስታገስ የወያኔ መሪዎች የራሳቸውን ከፍተኛ ካድሬዎች መስዋዕት በማድረግ ከስልጣንና ከኃላፊነት በማባራር ድርጅታዊ ብወዛ መጀመራቸው ታውቋል። በዚህ መሠረት የወያኔው ኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበረው ዳባ ደበሌ ከስልጣኑ ተነስቶ የተባረረ ሲሆን በምትኩ በወያኔው ኦህዴድ ውስጥ ታማኝነቱ አያጠራጥርም የተባለው በከር ሻሌ ተመድቧል። ከዚህ ቀደም በከር ሻሌን በጉምሩክና  ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ውስጥ ይሰራ እንደነበር ታውቋል። በናዝሬት ለተወሰነ ጊዜ ከንቲባ እንደነበረ ተገልጿል። የወያኔው መሪዎች በኦህዴድ ውስጥ ከስራ የማገድ የማባረርና የማዛወር ሥራን በሰፊው ያካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ በዚህ እንዳለ ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም የጤና ድርጅት ሀላፊ በመሆን ለመመረጥ  ፍላጎት እያሳየ ስለሆነ ግለሰቡ ኃላፊነቱን ከለቀቀ  ደቡብ ህብረቱ  ዮናስ ሴፍ እንዲተካ ሀይለማርያም ደሳለኝ እየለመነለት ነው ተብሏል

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በአዲስ አበባ ታክሲ ሹፌሮችና ማህበራት ላይ ያወጡትን ህግን ተከትሎ በትናንትናው ዕለት የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመደረጉ የወያኔ የትራንስፖርት ባለስልጣኖች የህጉን ግንዛቤ ማስጨበጫ ጊዜ ለማራዘም በሚል ህጉ እስከሚቀጥሉት ሶስት ወር ድረስ ተባራዊ እንዳይሆን መወሰናቸው ታውቋል። የወያኔው ትራንስፖርት ባለስልጣኖች ያወጡትን  የህግ መዘግየት መግለጫ ተከትሎ የተወሱን ታክሲዎች በመንገድ ላይ መታየት መጀመራቸው የታወቀ ሲሆን የወያኔ መሪዎች መሰረታዊ የሆነው የታክሲ ሹፌሮችና ማህበራቱን ጥያቄ በአግባብብና በትክክለኛ መንገድ እስካለመለሱ ድረስ ትግሉና አድማው በማናቸው ጊዜና ወቅት ሊቀጥል እንደሚችል ለታክሲ አሽከርካሪዎችና ማህበራት ቅርበት ያላቸው ምንጮች እየገለጹ ነው። ሌሎች ወገኖች ደግሞ የወያኔ ቡድን መሪዎች  ህጉን ለሶስት ወር እንዲዘገይ ያደረጉት በኢትዮጵያ ያለው የፖሊቲካ ትኩሳት እስኪበርድና ትንፋሽ መግዣ ጊዜ ለማግኘት መሆኑን ጠቅሰው የታክሲ ሹፌሮችና ማኅበራት ይህን ታሳቢ በማድረግ በማናቸውም ጊዜና ሁኔታ አድማቸው ለመቀጠልና መብታቸውን ለማስከበር ዝግጁ ሆነው መጠበቅ እንዳለባቸው ይናገራሉ። በተያያዘ ዜና የአዲስ አበባ ታክሲ ሹፌሮች አድማን ተከትሎ በሌሎች ከተሞችና ስፍራዎች የሚገኙ ታክሲዎችና ባጃጆች የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ ሲሆን ይህም ሆለታንና  ሰላሌና አርሲ  እንደሚጨምር ታውቋል ታውቋል። በናዝሬት የወያኔ ኦህዴድ ባለሥልጣኖች የታክሲ ስራ ማቆም አድማ እንዳይዛመት በማለት በማንኛውም መልኩ አድማ ማድረግ አይፈቅድም በማለት መግለጫ አውጥቷል።

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች በሁሉም አቅጣጫ የተነሳባቸውን ተቃውሞ ቁጣ ለማስታገስና የመልካም አስተዳደርና ስራ እየሰራን  ነው ለማለት ከአዲስ አበባ ከተማ በመሬት አስተዳደር ቢሮ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ስልሳ አንድ ሹሞችን ይዞ ማሰሩን ይፋ አድርጓል። አገዛዙ ከትናንንት በስቲያ በድንገተኛ መንገድ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሹሞች ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ መሬት እየሸነሸኑ መሸጣቸው ካርታ እያዘጋጁ በይዞታነት ያረጋግጡ ነበር የሚል ውንጀላ ያለባቸው ሲሆን ከአስሩም ክፍለ ከተማ ውስጥ መያዛቸው ተብራርቷል። በርካታ የሕግ ባለሙያዎች የሹሞቹ መታሰር የዘገየ መሆኑንና አሁንም ከሹሞቹ ጀርባ የጥቅምና ተካፋይነትና አይዞህ ባይ የወያኔ መሪዎችና ባለስልጣኖችን ሳይነካ ሹሞቹን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ ፍትሓዊ አሰራር ሳይሆን የሕዝብ ቁጣን ማስተንፈሻ ነው በማለት ይተቹታል።

 

 

Ø የወያኔ ቡድን መሪዎች ከ 80 በላይ ኢትዮጵያውያን የሆኑ የወርቅ ማዕድን ፈላጊዎች በሻዕቢያ ታግተዋል በማለት በአስቸኳይ እንዲለቀቁና  ካልተለቀቁ  ግን ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን በማለት በኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ በኩል መግለጫ ከሰጠ ወዲህ ታገቱ የተባሉት ኢትዮጵያውያን የወርቅ ማእድን ፈላጊዎች በነጻ መለቀቃቸውን የወያኔ ኮሚኒኬሽን ቦሮ ተናግሯል። ይሁን እንጅ የወያኔው ቢሮ ታጋቾች ስንት እንደሆኑና እንዴት እንደተለቀቁ የገለጸው ነገር የለም። የወያኔ አገዛዝ ከቀናት በፊት ዛቻ አዘል ማስጠንቀቂያና ስለ አጸፋው እርምጃ ይናገር እንጅ ምን ዓይነት የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ አላስታወቅም ነበር። ለዲፕሎማቶች ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደገለጹት ከሆነ የሱዳን መንግስት ታጋቾቹ እንዲለቀቁና በሱንዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ የሽምግልና ጥረት ማድረጉን እየገለጹ ሲሆን የሱዳን መንግስት ግን አደረገው ስለተባለው የሽምግልና ጥረት የእምነትም ሆነ የክህደት ቃሉን አልሰጠም።

 

 

Ø በአዳራሽ ውስጥ የ1500 ሜትር ሩጫ አሸናፊ የነበረችውና ከጥቂት ጊዜ በፊት በጋብቻ ምክንያት የስዊድን ዜግነት ያገኘችው አበባ  አረጋዊ የአካል ጥንካሬን የሚሰጥ ዕጽ መውስዷ በምርመራ ስለተጋለጠ  ከስፖርት ውድድር ታግዳለች ። እስካሁን ድረስ በዚህ  መንገደ የተከሰሰ ከእሷ በ አንድም ኢትዮጵያዊ  አለመኖሩ ታውቋል።

 

Ø የጉጂ  ሕዝብ በ ሼክ አላሙዲ ሚድሮክ የወርቅ ማዕድን ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ሲያደርግ መቆየቱ  በተደጋጋሚ የተገለጠ ሲሆን  ደርባ የሚገኘው የሚድሮክ ሲሚንቶ ፋብሪካው እንዲሁ  ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞታል ። ሕዝቡ በሼኩ ላይ ጠንካራ ተቃውሞውን እየገለጸ ያለው ሼኩ ለአገሪቱ መክፈል ያለበትን  በርካታ ገንዘብ ካለመክፈሉ በላይ ሰራተኞችን  በአነስተኛ ክፍያ እየበዘበዘ ነው በሚል ነው።  ይህ በዚህ እንዳለ ብሔራዊ የዘይት የኢትዮጵያ ኩባንያ የተባለው የሼኩ ተቋም ጅቡቲ ያለውንሊቢያ ኦይል የሚባለውን ድርጅት መግዛቱ ተነገሯል

 

Ø የጅቡቲ አምባገነናዊ አገዛዝ በተቃዋሚዎች ላይ እያካሄደ ያለው አፈና የቀጠለ ከመሆኑ በላይ በታጁራህ ታስረው በተለያይ የማሰቃያ መንገዶች ሲሰቃዩ ከነበሩት መካከል   ሁሙድ እስማኤልና አብዶ አህመድ ሞሚን  ሕይወታቸው ያለፈ መሆኑ ተነግሯል።  ኦቦክ በሚባለው ቦታ ታስረው ከነበሩት መካከል  ኦማን መሀመድ ቦዴ፤አሊ ሁሴን አሊ፤ከድር መሃመድ አይዳሂስ ና መሀመድ አሊ ሃጉስ በከፍተኛ ድብደባ ተሰቃይተው የሞቱ መሆናቸውን የጅቡቲ የሰብዓዊ  መብት ተከላካይ ኮሚቴ ገልጿል ።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት ወያኔ ወደ ሶማሊያ ጦሩ መላኩን መዘገባቸን የሚታወስ ሲሆን ይህ ወደ ሶማሊያ የተላከው ውጋግን ሬጅመንት በመባል የሚታወቀው ጦር በቁጥር 600 መሆኑና የሚመራው በኮሎኔል ታደሰ ወረደ ተስፋዬ በተባለ ግለስበ የሚመራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ጦሩ የሚሰማራው በደቡብ ሶማሊያ ሲሆን  የኪስማዮን ወደብ ለመጠበቅ ነው ተብሏል።  የወያኔ፤የዩጋንዳና ኬንያ ጦሮች ሽብርተኛ የተባለውን አል ሸባብን በማዳከም በኩል ውጤት አግኝተናል ቢሉ  ቡድ ሰሞኑን በሞቃዲስሾ ጥቃት ሰንዝሮ በርካታ ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል

 

Ø ከሰባት  ዓመታት በፊት በደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ላይ ዴሞክራቲ አሊያንስ በሚባለው የተቃዋሚ ቡድን ቀርበው የነበሩት 738 ክሶች በፍርድ ቤት  እንደገና ቀርበው ይታያሉ የሚል ዜና ከሰሞኑ ተሰምቷል።  የፕሬዚዳንቱ ቢሮ ክሱን በጽኑ የሚከላከል  መሆኑን ጠቅሶ በ2001 ዓም በወቅቱ የነበረው አቃቤ ህግ ክሶቹ ወደ ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ማድረጉ ትክክል ነበር የሚል ማብራሪያ ሰጥቷል። ክሱን ያቀረበው ተቃዋሚ ክፍል ያን ጊዜ የነበረው አቃቤ ህግ በፖሊቲካ ምክንያት ክስ እንዳይመሰረት አደረገ እንጅ ክሶቹ ትክክል ነበሩ የሚል መከራከሪያ አቅርቧል። ከተዘረዘሩት ክሶች ውስጥ አንደኛው  በወቅቱ የጸጥታ ኃላፊ የነበሩት የአሁኑ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ በብዙ ቢሊዮን ዶላር በተደረገው የመሳሪያ ግዥ  ከፍተኛ የሆነ የጉቦ ገንዘብ ተቀብለዋል የሚል ነው። ዴሞክራቲክ አሊያንስ የተባለው የተቃዋሚዎች ህብረት የአገሪቱ የታችኛው ምክር ቤት  በፕሬዚዳንቱ ላይ እምነት የሌለው መሆኑን የሚያረጋግጥ ድምጽ እንዲሰጥ የውሳኔ ሀሳብ ያቀረበ መሆኑ ታውቋል። በምክር ቤቱ ከፍተኛ የመቀመጫ ብዛት ያለው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ የተባለው የገዥው ፓርቲ ሲሆን የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ውድቅ ያደርገዋል ተብሎ ይገመታል። 

 

Ø ሰኞ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓም በምስራቅ ኮንጎ  በምትገኝ አንድ መንደር ውስጥ ራሱን “የመከላከያ ኃይል ህብረት”  በሚል መጠሪያ የሚጠራ የታጠቀ ቡድን አባሎች  የመንደሩ ነዋሪ የሆኑትን 12 ሰዎች መግደላቸውን አንድ የሰብአዊ መብት ድርጅት ተቋም ከአካባቢው የአገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ ገልጿል። መቀመጫቸው በኡጋንዳ ወሰን አካባቢ የሆነው ታጣቂዎች ግድያውን የፈጸሙት  በያዙት  ቆንጨራ ሲሆን ምግብና የቤት እንስሳት ዘርፈው የሄዱ መሆናቸው ተነግሯል።

 

 

 

 

የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø ዛሬ በመላዋ አዲስ አበባ የሚገኙ የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ማድርጋቸው ታወቀ። የታክሲ አሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ የመቱት የወያኔ አገዛዝ የአወጀውን የትራንስፖርትና የመንጃ ፈቃድ ህግን በመቃወም መሆኑ ታውቋል። ወያኔ ባወጣው አዲስ ሕግ ማንኛውም ሹፌር ለሃያ አንድ ጊዜ ካጠፋ መንጃ ፈቃዱ እንደሚነጠቅ ይደነግጋል። የክፍለሀገር  ባለ አሽከርካዎችም በሥራ ማቆም አድማ ተሳታፊ መሆናቸው ሲታወቅ አድማውን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት ችግር በአዲስ አበባ ከተማ መታየቱ ታውቋል። የታክሲ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ የከተማው መነጋገርያ መሆኑ ተገልጿል። ብዙ አስተያየት ሰጭዎች የወያኔ አገዛዝ የአዲስ አበባ ታክስ ሹፌሮችንና ባለንብረቶችን ከንግዱ ዓለም ለማባረርና በራሱ ድርጅቶችና ዘር አባላትን ለመተካትና የድህንነት አባላቱን ለማሰማራት በማሰብ ያወጣው ዕቅድ መክሸፉንና የታክሲ ሾፌሮቹ ለሌሎች የኅብረተስብ ክፍል ያስተማሩበት አድማ ነው በማለት አስተያየት ይሰጣሉ።

ወያኔ ሕዝብ መናቅ የባሕርዩ ነውና በቀጥታ የሚመለከታቸውን ባለ ጉዳዮች ሳያማክርና ሕዝብ ሳይመክርበት ህግ ማውጣት ልማድ ብሎ ይዞታል፡፡ የአዲስ አበባ የትንሿ አውቶብስ (የሚኒ ባስ) ባለንብረቶች ማህበር በየጊዜው እየናረ በመሄድ ላይ ያለው የጎማ፣ የዘይት፣ የመለዋወጫ ዋጋ አሁን ካለው ከታክሲ ታሪፍ ጋር የተመዛዘነ ባለመሆኑ የዋጋ ጭማሪ እንዲደረግ ከሚመለከተው የወያኔ አካል ጋር ከስምምነት በድረሳቸው እየተገለጸ ባለበት ሾፌሮች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል የተደረገውን የትራፊክ ህግ በመቃወም ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ሥራ ያቆሙት ባለታክሲዎች ከተማዋን የቀውስ መንደር አስመስለዋት እንደዋሉ በከተማዋ የተለያዩ አቅጣጫዎች ተዘዋውሮ የነበረው ዘግቢያችን መታዘብ ችሏል፡፡ በከተማዋ ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ከሃምሳ ሺ በላይ ታክሲዎች ሙሉ በሙሉ የአድማው ተባባሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በከተማዋ ውስጥ ውር ውር ሲሉ የነበሩ ታከሲዎች በአጠቃላይ ግፋ ቢል አንድ ሺ እንደሚሆኑ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ውስጥ የሚሠሩ ወገኖች ያስረዳሉ፡፡ እነዚሁ ታክሲዎችም ንብረትናታቸው የሙሰኞቹ የወያኔ ሹመኞች እንደሆኑ በአድማው ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሾፌሮች ያስረዳሉ፡፡ አብዛኛው ሠራተኛ ወደ ሥራ ሲሄድ በእግር ለመሄድ ተገዷል፡፡ ሲመለስ ምሽትም ስለሚሆን በእጅጉ ሕዝቡ አዳጋች ችግር ይገጥመዋል፡፡ ይህ አዲስ የወጣ ህግ የተረቀቀው በወያኔ ካድሬዎች ማለትም ድንጋይ ማምረቻ እየተባለ ከሚጠራው ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ በወጡና በሥራው ላይ ከሁለት አመት ያልበለጠ ልምድ ባላቸው በመሆኑና የነሱ የበላይ የሆኑትም በወያኔ ካድሬነት ብልጫ ቢኖራቸው እንጂ በህግ ትምህርት ምንም እውቀት እንደሌላቸው የዚህ ህግ የመረቀቅና የመጽደቅ ሄደትን አጣርተው የሚያውቁ ያስረዳሉ፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ መካከለኛና ከፍተኛ አገር አቋራጭ አውቶብሶችም ሥራ ማቆማቸው ታውቋል፡፡ ወያኔ በአድማው በመደናገጡ የወጣው ህግ እስከ ሦስት ወር በሥራ ላይ እንዳይውል መታገዱን ገልጾ ሾፌሮቹ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ለማባበል ያደረገው ሙከራ ሰሚ አላገኘም ፡፡ ወያኔ እራሱም ሆነ የሚያወጣው ህግ በሕዝብ ላይ የሚጫኑና የተጫኑ በመሆናቸው በኃይል የመወገዳቸው ጀምበር እየቀደደ ለመሆኑ ከዚህ ወያኔን እያራደ ካለው አድማ መረዳት ተችሏል፡፡

 

Ø የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ተከትሎ የቀጠለው ሕዝባዊ አመጽ አራተኛ ወሩን እያስቆጠረ ሲሆን የወያኔ ቡድን መሪዎች አመጹን አቁመናል ንቅናቄውን ገትተናል ይበሉ እንጅ አሁንም ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣው አንደቀጠለ መሆኑን ከየአካባቢው የሚመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። እሁድ ዕለት፤ በሐረርጌ ፤ በወለጋ በአርሲና በሸዋ የሚገኙ ልዩ ልዮ ከተሞች ውስጥ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን የወያኔው ነፍስ ገዳይ አጋዚ ወታደሮችም ወለጋ ውስጥ አንድ ፖሊስ ከሕዝብ ጋር ወግነሃል በማለት የገደሉት መሆናቸው ተዘግቧል። ከዚህም በተጨማሪ በየከተሞቹ ከሕዝባዊ ተቃውሞችና ቁጣ ጀርባ እጃችሁ አለበት በማለት የልማት ሠራተኞች መምህራን ላይ ወከባ እስርና የጭካኔ ተግባር እየተፈጸመባቸው መሆኑ ታውቋል።  በሌላ በኩል ደግሞ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ከዳባት ከተማ ወደ አዲስ አበባና ወደ መቀሌ ሽሬ የሚወስደው መንገድ በተቃውሞ መዘጋቱ ታውቋል። ከወልቃይት ሕዝብ ማንነት ጋር በተያያዘና ከሕግ፤ ከባህልና ከታሪክ ውጭ ወልቃይት ወደ ትግራይ መካለለሉን በመቃወም የወልቃይት ነዋሪና ተወላጆች ተቃውሞ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን ትግሉ ወደ መንገድ መዝጋት ሲሸጋገር ይህ የመጅመሪያው ነው።

 

Ø ከአስር ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ድንበሩ ሰላምና ጦርነት አልባ ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ሰሞኑን የወያኔ ቡድን መሪዎች በወርቅ ማዕድን ፍለጋ ላይ የነበሩ 80 ሰዎች በሻዕቢያ ታግተው ተወስደዋል በሚል የወያኔ መሪዎች የክስ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸው ታውቋል። የወያኔ ቃል አቀባይ ቀደም ሲል በጉዳዩ ላይ ማስጠንቀቂያ አዘል መግለጫ የሰጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በበኩሉ ሻዕቢያ የታገቱትን ሰዎች በአስቸኳይ ካለቀቀ ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን በማለት ዝቷል። የወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የታገቱት ሰዎች ቁጥር 80 መሆናቸውን ይግለጽ እንጅ ቀደም ሲል በወጡት መግለጫዎች የታገሩት ማዕድን ፈላጊዎች ቁጥር 85 ተብሎ መዘገቡ ይታወቃል። ይህንን የተደጋገመ የወያኔን ማስጠንቀቂያና ዛቻ አስመልክቶ ሻዕቢያ የሰጠው ይፋ አስተያየት የለም። የፖሊቲካ ታዛቢዎች ግን የወያኔ ቡድን በሀገር ውስጥ በአራቱም ማዕዘን የተነሳበትን ተቃውሞ ለማዘናጋትና ለማረሳሳት ከሻዕቢያ ጋር እሰጥ አገባ ለመግባትና የጦርነት ከበሮ ለመደብደብ የወሰው የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ትኩሳቱን ለማረሳሳ በማሰብ መሆኑን ይገልጻሉ።

 

 

Ø ከሃያ ዓመት በላይ በእስር በራሱ ጦርነትና በሽብርተኞች ጥቃት የምትታመሰውን ሶማሊያን ለመታደግ የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ስለማ አስከባሪ ተልዕኮ እሁድ ዕለት በጅቡቲ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል። በዚህ ስብሰባ ላይ ለሶማሊያው ሰላም አስከባሪ ተልእኮ ወታደሮቻቸውን ካዋጡት አገሮች በተለይ ኬኒያ ኡጋንዳና ወያኔ በቅርብ የተጀመረው የአልሸባብ ጥቃት እያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። የኬኒያ መንግስት በቅርብ በአልሸባብ ጥቃት 200 የሚደርሱ ወታድሮች ከተገደሉ ወዲህ ለሰላም አስካሪው ተልዕኮ ቀጣይነት ቢገልጽም ተጨማሪ ጦር ማዋጣቱ ግን አጠራጣሪ ሆኗል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ለሱማሊያ ተጨማሪ የሰላምና አስከባብሪ ኃይል ለመላክ ፈቃደኛ መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወቃል። የወያኔ አገዛዝ የአፍሪካ ኅብረት ለሚጠራው የሰላም አስከባሪ ተልእኮ ወታደሮችን በመላክ የውጭ ምንዛሬ መሰብሰቢያ ብቻ ሳይሆን በጦሩ ውስጥ ያሉትን የራሱን አንድ ዘር አዛዥና ወታደሮችንም መጠቀሚያ ማድርጉ ይታወቃል።

ይህ በዚህ እንዳለ ትናንት የካቲት 20 ቀን 2008 ዓም ባዮዳ በሚባለው የሱማሊያ ከተማ ውስጥ ሁለት ቦምቦች ፈንድተው ጉዳት መድረሱን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ በፈነዱት ቦምቦች  ከ 30 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውና ከ 60 በላይ የሚሆኑ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል።  ሰዎች ተሰብስበው የአግር ኳስ ውድድር በሚያዩበት አንድ ሬስቶራንት አጠገብ የፈነዳው መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ሁለተኛው ቦምብ ደግሞ አጥፍቶ ጠፊ በሆነ አንድ ግለሰብ በመንታ መንገድ መገኛኚያ ላይ ፈንድቷል።  ለጥቃቱ አልሸባብ ኃይላፊነቱን ወስዶ መግለጫ ሰጥቷል። ይህ ባለፉት ሁለት ወራት ለአራተኛ ጊዜ በከተማዋ ውስጥ የደረሰው የቦምብ ፍንዳታ  የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተጠናከረ የመጣውን የአልሸብን ኃይል ለመቋቋም ወታደራዊ ብቃቱን ለማጠናከር ቃል በገባ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ነው። ከጥቃቱ በኋላ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ጠርተው መወሰድ ስላለበት እርምጃ ተወያይተዋል ተብሏል።

 

Ø የናይጀሪያ መንግስት ማንነታቸው የማይታወቅና በፈጠራ ስም ሲከፈል የነበረውን ደሞዝ በመሰረዝ በርካታ ገንዘብ ያዳነ መሆኑን አስታወቀ። የቡሃሪ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች ናቸው ተብለው በደሞዝ መክፈያ ሊስት ውስጥ የነበሩት  24 000 የውሸት ስሞችን የሰረዘ ሲሆን ለእኒዚህ ሰዎች ይከፈላል ተብሎ በየወሩ ይበዘበዝ የነበረውን 15.5 ሚሊዮን ዶላር ለማስቀረት የተቻለ መሆኑን ገልጿል። አንዳንድ ሰራተኞች በሌሉ ሰዎች ስም በርካታ ደሞዝ የሚቀበሉ መሆናቸው የተደረሰበት መሆኑና ሌሎች ደግሞ ከሁለት ከሶስት ቦታ ደሞዝ የሚቀብሉ መሆናቸው በምርመራ ተረጋግጧል።  ሙስና በናይጄሪያ ውስጥ በተለያየ መንገድ ስር የሰደደ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ይህንን ለማስቀረት የቡሃሪ መንግስት ከፍተኛ ጥረት የሚያደርግ መሆኑን ገልጿል።

 

ቤልጀየም ነዋሪ የነበረ አንድ አልጀሪያዊ ከጥቂት ወራት በፊት ፓሪስ ከተማ ውስጥ ተካሄዶ በነበረው ት በሚል ጥርጣሬ አክቡ በምትባለው የአልጀሪያ ከተማ በቁጥጥር ስር መደረጉን ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ህዳር 3 ቀን 2008 ዓም በፓሪስ ከተማ በተካሄደው የሽብር ጥቃት 130 የሚሆኑ ስዎችን መግደላቸው የሚታወስ ሲሆን ጥቃቱን ከፈጸሙት መካከል አራቱ በቤልጀየም ነዋሪ መሆናቸው ተደርሶበታል።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ በየአመቱ 600 000 (ስድስት መቶ ሺ) የሚሆኑ መንገደኞችን የሚያስተናግደው በምዕራብ ኬፕ የሚገኘው የጆርጅ አውሮፕላን ጣቢይ ከጸሐይ ብርሃን የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጭ መሳሪያ በመትከል እና ስራውን እንዲጀምር በማድረግ ከአፍሪካ የመጀመሪያ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት አውሮፕላን ጣቢያው ከሚያስፈልገው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ አርባ ከመቶ የሚሆነውን ከዚሁ መሳሪያ የሚያገኝ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ 100 ከመቶ የሚሆነው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ከዚሁ መሳሪያ ይገኛል ተብሏል። ከጸሐይ ብርሃን የኤሌክትርክ ኃይል የሚያመነጨውን መሳሪያ ለመትከል አንድ ሚሊዮን ዶላር የፈጀ ሲሆን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሌሎች አውሮፕላን ጣቢያዎች ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስዱ ይጠበቃል። የኤሌክትርክ ኃይል መሳሪያን በአየር ጣቢያዎች ላይ በመጠቀም ረገድ ቀዳሚዋ ህንድ ስትሆን ባለፈው ዓመት በኮቺን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ላይ በ9.5 ሚሊዮን ዶላር የተተከለው  መሳሪያ በአይነቱ ከዓለም አንደኛ ነው ተብሏል።  

 

 

 

 

 

የካቲት 19 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø ትናንት የካቲት 18 ቀን እና ዛሬ የካቲት 19 ቀን 2008 ዓም በተለያዩ ቦታዎች  ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ቀጥለው የዋሉ ሲሆን በምዕራብ እና በምስራቅ ሃረርጌ እንድሁም ምእራብ ሸዋ እና ቦረና አካባቢዎች ተማርዎቹ እና ሕዝቡ የተቃውሞ ሰልፎች አድርገዋል። በሌላ በኩል እንቅስቃሴዎቹ በሚካሄዱባቸው የወያኔ  በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈና አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በርካታ ዜጎችም የታሰሩ መሆናችው ተዘግቧል። ሶማሊያ የነበረው ልዩ የአግአዚ ኃይል ወደ ምስራቅ ሃሮሚያ ገብቶ በርካታ ዜጎች ማሰሩን አንዳንድ ምንጮች ዘግበዋል። በተያያዘ ዜና የወያኔ አገዛዝ የኦሮሚያ አካባቢን በወታደራዊ አስተዳደር ቁጥጥር ስር ለማድረግ ያደረገው ውሳኔ በአካባቢው ለሚገኙ ከፍተኛ የጦርና የጸጥታው ተቋም መኮንኖች የተነገረ መሆኑ አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል። ውሳኔው የኦሮሚያ አካባቢን በ8 ወታደራዊ ቀጠና ከፍሎ በዚያ የሚገኘውን የጸጥታም ሆነ የአስተዳደር ኃላፊነት በበላይነት መምራት ነው። በአካባቢዎቹ የሚገኙ የሲቪል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ቀጠና እዝ ታዛዥ እንዲሆኑ ተደርጓል ተብሏል። 

 

Ø በተመሳሳይ ዜና በወለጋና አካባቢው ላይ በተካሄዱት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ በርካታ ተማሪዎች  በተለያዩ መንገዶች ቅጣት የተፈጸመቫቸው መሆኑን ከአካባቢው የመጣ ዘገባ ይገልጻል። ተይዘው ክስ የሚመሰረትባቸውና ታስረው የተለቀቁ ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን እንቅስቃሴው ውስጥ ተሳታፊ ነበራችሁ በሚል ሰብ ብቻ ከትምህርታቸው የታገዱ ተማርዎች ቁጥር በርካታ መሆኑን  ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ይገልጻል።  ከበላይ በመጣ ትዕዛዝ መሰረት የወለጋ የሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት ርእሳነ መምህራን ተማሪዎቹ ከትምህርት እንዲታገዱ ውሳኔ ያስተላለፉ ሲሆን ተማሪዎቹ በየትኛውም ትምህርት ቤት እንዳይማሩ የተደረገ መሆኑ ታውቋል።፡ በታዘዙት ድርጅታዊ ትእዛዝ መሰረት መወሰኑን ከነቀምት የተገኘ መረጃ አስረድቷል።

 

Ø አረና በመቀሌ ከተማ የጠራው ሰልፍ የታገደ መሆኑን ከድርጅቱ አካባቢ የተገኘው ዜና ይገልጻል። አረና በኤርትራ ስለጠተለፉት ዜጎች፣ በኦርሚያ አካባቢ እየተካሄደው ስላለው ሕዝባዊ ተቃውሞ እና እየተደረገ ስላለው ግድያ እና አፈና፤ ሰለ ህግ የበላይነት እንዲሁም  ስለድርቅ ጉዳዮች አስመልክቶ ድምጽ ለማሰማትና መልእክት ለማስተላለፍ ለየካቲት 20 ቀን 2008 ዓም በመቀሌ ከተማ ሰልፍ ቢጠራም የወያኔ ባለስልጣኖች የአሁኑ ወቅት የተረጋጋ አይደለም በሚል ምንያት ሰልፉ የከለከሉ መሆናቸው ተነግሯል። ለሚመለከታቸው እስካሳወቅን ድረስ ስልፉን ማካሄድ እንችላለን የሚሉ አባላት ቢኖሩም በእርግጠኛነት ሰልፉ መካሄዱ የሚታወቀው በነገው ዕለት መሆኑ ተነግሯል።

 

Ø ትናንት የካቲት 18 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ የአልሸባብ ታጣቂዎች በሰነዘሩት ጥቃት ቢያንስ 14 ሰዎች መሞታቸው  የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ሞጋዲሾ ውስጥ የሚገኘው  የሱማሊያ ወጣት ሊግ ሆቴል ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለት ሲሆን አጥቂዎቹ ጥቃታቸውን የፈጸሙት በመኪና ላይ የተጠመደ ፈንጅ አጠገቡ በማፈንዳት ነው። ፒስ ጋርደን በሚል ስም የሚጠራ በአካባቢው ያለ ፓርክም እንዲሁ የፈንጅ አደጋ ደርሶበታል። ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ ሊገቡ ጥረት አድርገው የነበሩትን አራት የአልሸባብ ታጣቂዎች ገድለው ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት ሁኔታውን ለመቆጣጠር የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የተሰማሩ ሲሆን በየቦታውም ፍተሻ እያካሄዱ መሆናቸው ታውቋል።  ከሶስት ቀን በፊት የአልሸባብ ኃይሎች የፕሬዚዳንቱ መኖሪያ በሆነው በቤተ መንግስት አካባቢ ጥቃት ፈጽመው ሶስት ሰዎች መግደላቸው ይታወሳል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት በሊቢያ ቤንጋዚ ውስጥ አይሲስ የተባለው አሸባሪ ድርጅት መኪና ላይ የተጠመደ ፈንጅ አፈንድቶ  አምስት የጸጥታ ተቋም አባላትን የገደለ መሆኑ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። አይሲስ በድረ ገጽ አማካይነት ባሰራጨው ዜና ፈንጅው ኢላማ ያደረገው የምስራቅ ሊቢያ መንግስት የጦር ኢታ ማጆር ሹም ላይ ሲሆን በፈንጅው  ከ25 በላይ ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን ገልጿል። በምስራቅ ሊቢያ መቀመጫውን ያደረገውና በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ታዋቂነት በተሰጠው መንግስት  ስር ያሉ የጸጥታ ኃይሎች ባለፈው ማክሰኞች በሚድትራኒያን ባህር ጠረፍ ላይ የምትገኝ አንድ የወደብ ከተማ ከአይሲስ አስለቅቀው በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው ይታወሳል። 

 

Ø ከቦኮሃራም ጋር እየተፋለሙ ያሉትን የናይጄሪያ ወታደሮች እንዲያሰለጥኑ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎች ወደ ናይጄሪያ የሚላኩ መሆናቸው ተነገረ።  ከጥቂት ጊዜ በፊት በናይጄሪያ መንግስት ጥያቄ  አንድ የአሜሪካ ወታደራዊ ቡድን ቅደመ ጥናት ለማድረግ ወደ ናይጀሪያ ተልኮ ምን እንደሚያስፈልግና ምን መደረግ እንዳለበት ጥናት ሲያደርግ መቆየቱ ይፋ የሆነ ሲሆን በጥናቱ መሰረት የተወሰኑ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎችና አሰልጣኞች ወደ ናይጄሪያ እንደሚላኩ ታወቋል። ቀደም ብሎ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎች የናይጄሪያ ወታደሮችን በማሰልጠን ተግባር ላይ ተሰማርተው ሲያሰለጥኑ መቆየታችው የሚታወስ ሲሆን የናይጄሪያ ወታደሮች ወታደራዊ ዲሲፕሊን የማይጠብቁና የሕዝቡን ሰብአዊ መብቶች የማከብሩ ናችው በሚል ምንያት የማሰልጠኑ ተግባር ከሁለት ዓመት በፊት መቋረጡ ይታወቃል። ባለፈው ጥር ወር አሜሪካ ከተቀበሩ ፈንጅዎችና ከደፈጣ ጥቃቶች መከላከል የሚያስችሉ 24 ወታደራዊ መኪናዎችን ለናይጄሪያ መንግስት የሰጠ ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ ያስገኙት ውጤት እና ጥቅም እየተገመገመ ነው ተብሏል።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

የካቲት 18 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በአዲስ አበባ መስፋፋት ስም መሬት የመቀማቱን እቅድ በመቃወም በተጀመሩትና  ወደሶስት ወር ለሚጠጋ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሲካሄዱ በነበሩት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በሻዕቢያ የሚደግፉ ኃይሎች እጃቸው ያለበት መሆኑን የሚያረጋግጥ ተጨባጭ መረጃ የተገኘ መሆኑን በመጥቀስ የወያኔው አፈቀላጤ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎቹ የሕዝብ ብሶትና ብስጭት የወለዳቸው እንቅስቃስዎች መሆናቸው እየታወቀ ወያኔ የችግሩን ምንጭ ወደ ሻዕቢያ ለማዞር የሞከረው በሕዝብ ድጋፍ እንቅስቃሴውን ለማብረድ ይቻላል ከሚል ስልት የተነሳ መሆኑን አንዳንድ ወገኖች ግምታዊ አስተያየት ይሰጣሉ።  ቀደም ሲል በድንበር አካባቢዎች በወርቅ ማዕድን ላይ ሲሰሩ የነበሩና ቁጥራቸው ከ80 የሚበልጡ ዜጎች በሻዕቢያ ወታደሮች ተጠልፈው መወስዳቸውን ተከትሎ  በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች በሚያስተናግዷቸው ድረ ገጾችና በሌሎች መገናኛ ብዙሐን  በሻዕቢያ ላይ እርምጃ መወሰድ አለበት የሚል ጩኸት ሲያሰሙ የቆዩ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን የአሁኑ የወያኔ መግለጫ ይህንን ተከትሎ ለማስፈራራት የተደረገ ነው ነው የሚሉም አልጠፉም።  ቅስቀሳውም ሆነ ማስጠንቀቂያው  መጨረሻ ምን እንደሆነ ግራ ያጋባል ያሉ ክፍሎች ወያኔ ያለበትን መረረ ቀውስ ለማርገብ ጦርነት ሊገባ ወደኋላ የማይል ቢሆንም እንደፈለገው ተነስቶ በሻዕቢያ ላይ ወረራ ሊያካሄድ  አይችልም የሚል ድምዳሜ ይሰጣሉ።

    

Ø በተያያዘ ዜና ባለፈው ሰሞን አንድ የሻዕቢያ ተቃዋሚ የሆነ የታጠቀ ኃይል ወደ ኢርትራ ዘልቆ  ከሻዕቢያ ወታድሮች ጋር ድንገት ተገናኝቶ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ  ከቡዱኑ አባላት መካከል አንዱ መገደሉንና ሌላ አንድ መቁሰሉን እንዲሁም ሶስት አባሎቹ መማረካቸውን አሥታውቋል።  ይህን ዜና ያሰራጨው የኤርትራ ብሔራዊ ካውንስል ሌዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚባለው ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ  በዚህ ዓመት ጠቅላላ ጉባዔ እንደሚያደርግም ድርጅቱን በሚመራው ግለሰብ  ተገልጿል። ካውንስሉ የመጀመሪያውን አሰባሳቢ ጉባኤ ያደረገው ከሁለት ዓመት በፊት በአዋሳ ከተማ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን  ወያኔ የሻዕቢያ ተቃዋሚዎችን በመርዳትና በማጠናከር ሻዕቢያን የማዳከም እቅዱ ተዳክሞ የማያውቅ ቢሆንምና  በሱዳን መንግስት የተያዙትን የጀብሃ መሪዎች አማላጅ ሆኖ በማስለቀቅ ቁልፍ ሚና ቢጫወትም  እስካሁን ድረስ የሻዕቢያ ተቃዋሚ የሆኑ ቡድኖችን ለማጠናከር የወሰደው እርምጃ አጥጋቢ አይደለም  ሲሉ አዲስ አበባ ያሉት የሻዕቢያ ተቃዋሚ ድርጅቶች ሲከሱ ይደመጣሉ። የአሁኑ የወያኔ ማስፈራሪያ ምን መልክ እንደሚይዝ ወደፊት የሚታይ ይሆናል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2008 ዓም ሕዝባዊ ተቃውሞው  በተለያዩ ቦታዎች የቀጠሉ መሆናቸውን ከተለያዩ ምንጮች የሚገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። በምዕራብ ሀረርጌ በአሩሲና በምዕራብ ሸዋ  አካባቢ የተቃውሞው እንቅስቃሴ መቀጠሉ ተነግሯል። በአርሲ በርካታ ሰዎች በወያኔ አግአዚ ጦር የታሰሩ ሲሆን  የወያኔ ወታደሮች የሚገድሏቸውና የሚያቆስሏቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደው ማንነታቸው እንዳይታወቅ በአንዳንድ ቦታዎች በተለይም በምስራቅ ሃርርጌ እና በምዕራብ ወለጋ  በአግአዚ ቁጥጥር የሚሆን  ቁጥጥር የመስክ ሆስፒታሎች እየተሰሩ መሆኑ ተነግሯል። 

 

Ø በማሊ ውስጥ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል የነበረ አንድ የቻድ ወታደር ያለበትን ክፍል አዛዥና አንድ ሌላ ዶክተር የገደለ መሆኑ ተነግሯል። ወታደሩና አዛዡንና ዶክተሩን የገደለበት ምክንያት ለጊዜው ግልጽ ባይሆንም በቁጥጥር ስር የዋለው ወታደር  በተለያዩ ሁኔታዎች ሲበሳጭ የነበረ መሆኑ ተነግሯል ። በማሊ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ስር ያሉ የቻድ ወታደሮች ክፍያቸው እየዘገየ በመምጣቱ በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ የቆዩ ሲሆን የቻድ መንግስትም በማሊ የሚገኙ ወታደሮች ትጥቅና መሳሪያ የተሟላ አይደለም በማለት ቅሬታ ሲያሰማ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ስር ከ9000 በላይ የሆኑ የቻድ ወታድሮች ይገኛሉ።

 

Ø ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የኡጋንዳ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ በጠቃላላው አገሪቱ ውስጥ ከ200 በላይ የሚሆኑ ደጋፊዎቹና አባሎቹ የታሰሩ መሆናቸውን ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ ቼንጅ (Forum for Democratic Change) የሚባለው ዋናው የኡጋንዳ ተቃዋሚ ፓርቲ ገለጸ። በየቦታው የታሰሩት አባላት አብዛኞች የአካባቢው የፓርቲ መዋቅር ባለስልጣኖች ሲሆኑ ምርጫው የተጭበረበረ መሆኑን የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃዎች የያዙ መሆናቸውን የፓርቲው ቃል አቀባይ ገልጿል። የፓርቲው መሪ ቢሲግየ እስካሁን በእስር ላይ መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን አባሎቹ አለአግባብ በመያዛቸው ፓርቲው ክስ ይመሰርታል ተብሎ ይጠበቃል። የኡጋንዳ የፖሊስ ቃል አቀባይ በተለያዩ ቦታዎች በወንጀል ጉዳይ የተያዙ መኖራቸውን አምነው አንድም የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንዳልተያዘ ገልጸዋል።

 

Ø የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ከተማ በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ውስጥ የፈነዳው ቦምብ አራት ፖሊሶችን ሲገድል ከ6 በላይ ሰዎች ያቆሰለ መሆኑ ተነግሯል። ቦምቡ ከቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የተያዘ ሲሆን ተመርምሮ እንዲቀመጥ ለማድረግ ጥረት በሚያድርጉበት ወቅት ሳይታሰብ ፈንድቶ ጉዳት ያደረሰ መሆኑ ታውቋል። የቦካሃራማ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ከተማዋን እንዲሁም ፖሊስ ጣቢያውን ማጥቃታቸው የሚታወቅ ቢሆንም ይህኛው ቦምብ የተጠመደ ወይም የተቀበረ እንዳልሆነ ታውቋል።

 

Ø የአምስት የአፍሪካ አገሮች መሪዎች ትናንት የካቲት 17 ቀን በብሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ መግባታቸው የተነገረ ሲሆን በአገሪቱ ውስጥ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ቆይታ ከአገሪቱ ባለስልጣኖችና ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተገንኝተው እርቅ ስለሚፈጠርበት ሁኔታ ይወያያሉ ተብሏል። በብሩንዲ ታዋቂ የሆኑ የፖሊቲካ የሃይማኖት እና የሲቪክ መሪዎች አገሪቱን ለቀው በውጭ አገር በሚኖሩበት ሁኔታ ትርጉም ያለው ውይይት አካሂዶ እርቅ ማውረድ አስቸጋሪ ነው ተብሏል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ከጥቂት ቀናት በፊት ብሩንዲ ውስጥ ተገኝተው እርቅ እንዲመጣ ጥሪ ቢያደርጉም ግብኝታቸው ያስገኘው ውጤት አነስተኛ ነው የሚሉ በርካታ ናችው። የብሩንዲ የተቃዋሚዎች ህብረት ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ ፕሬዚዳንቱ አክራሪ አምባገነን መሆናችውን ገልጸው ማዕቀብና ግፊት ካልተደረገባችው ለስምምነት ዝግጁ አይደሉም ብለዋል።

 

Ø ትናትን የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ እንደገና አገርሽቶ ቢያንስ ሶስት ዩንቨርስቲዎች የተዘጉ መሆናችው ተነግሯል። ተማሪዎቹ  የተቃውሞ እንቅስቃሴ ያደረጉት ለትምህርት ቤት የሚከፍሉት ገንዘብ ከፍተኛ በመሆኑና በየትምህርት ቤቱ ዘረኛነት በመስፋፋቱ ነው ተብሏል።  ኖርዝ ዌስት ዩኒቨርስቲ በሚባለው ህንጻዎች በእሳት የጋዩ ሲሆን በኬፕ ታውን ዩኒቨርስቲም የመማሪያ ክፍሎችን በሰው ሰገራ በማበላሸት ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። ፖሊሶች የአስለቃሽ ጋዝ በመጠቀም ተማሪዎችን ለመበተን ሞክረዋል። በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎቹ ጥያቄ ለትምህርት የሚከፈለው ዋጋ የበዛ መሆኑን በመጥቀስ ሲሆን በኬፕ ታውን ዩኒቨርስቲ ከትምህርቱ ክፍያ  በተጨማሪ አፍርካንስ የተባለው የነጮቹ ቋንቋ የትምህርት ቋንቋ እንዲሆን መደረጉን በመቃወም ተማሪዎች ተሰልፈዋል። የዩኒቨርስቲዎቹ ሰራተኖች እና አስተማሪዎች የተማሪዎችን ጥያቄ በመደገፍ በተቃውሞ ሰልፉ ተቀላቅለዋል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባንኪ ሙን  ትናንት የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በደበቡ ሱዳን ዋና ከተማ በጁባ ከፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ዋና ጸሐፊው ከተቃዋሚው መሪ ከሪክ ማቻር ጋርም በስልክ የተወያዩ ሲሆን በትናንትናው ዕለት በሰጡት መግለጫ ሁሉም ወገኖች የሰላሙን ስምምነት ተግባራዊ ከማድረግ በስተቀር ሌላ አማራጭ የላችውም ብለዋል። በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉት የደቡብ ሱዳን ዜጎች ከሁለት ሚሊዮን በላይ መሆኑን ገልጸው የደቡን ሱዳን መንግስት ዜጎችን ለመንከባከብ ኃላፊነት አለበት ብለዋል። ተመድ 21 ሚሊዮን ዶላር ለእርዳታ እንደሚሰጥም ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም ዋና ጸሀፊው የደቡብ ሱዳን ባለስልጣኖች  ባለስልጣኖቹ ከፖሊቲካ ይልቅ ሰላምን እንዲያስቀድሙ ፤ ችግሮችን እንዲያስወግዱና በመቻቻል በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ተስማምተው የሽግግርና የአንድነት መንግስት እንዲያቋቁሙ መልእክት ለማስተላለፍ የሚወዱ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ነሐሴ ወር በደቡብ ሱዳን ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የእርቅ ስምምነት መፈረሙ የሚታወስ ሲሆን ከዚያ ወዲህ በየቦታው በተካሄዱ ጦርነቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩም ቤት ንብረታቸውን ጥለው የተሰደዱ  መሆናችው ይታወቃል። በተያያዘ ዜና ደቡብ ሱዳን ነጻ ወጣች ከተባለ ጀምሮ 4 ቢሊዮን ድላር ያህል የእርዳታ ገንዘብ መሰረቁን ያስረዱ ክፍሎች በቅርቡ ደግሞ የፕሮእዚዳንት ሳልቫ ኪር ረዳቶች በተጭበረበሩ ፊርማዎችና ሰነዶች 14 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ  መስረቃእውን አጋልጠዋል።

 

 

 

 

 

የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø ከሁለት ወር በፊት የጀመረው ህዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ትናንት የካቲት 16 ቀን እና ዛሬ የካቲት 17 ቀን በተለያዩ ቦታዎች ቀጥሎ የዋለ መሆኑ ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱት ዜናዎች ይገልጻሉ። ዛሬ በያቤሎ ቦረናና እና በባሌ የተለያዩ አካቢቢዎች እንቅስቃሴዎች መደረጋቸው የተዘገበ ሲሆን በትናንትናው ዕለትም በምዕራብ ሸዋና በወለጋና በቦረና በተካሄዱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በርካታ ሰዎች በአግአዚ ወታደሮች ጥይት መገደላቸው ታውቋል።  ይህ በዚህ እንዳለ በግንጭ እና በአምቦ ጉብኝት ያደረገ የውጭ አገር ጋዜጠኛ ነዋሪዎችን በማነጋገር ካገኝው መረጃ የወያኔ ወታደሮች ከፍተኛ አፈናና በደል እያደረጉ መሆናቸውንና በተለያዩ አካቢቢዎች ፍርሃት የሰፈነ መሆኑን አጋልጠዋል። መትረየሶች የጫኑ መኪናዎች መንግዶችን በመሙላታቸው እና በየቦታው የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች የሚያካሄዱትን ፍተሻ እና ተያይዞም ያለው ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ ሕዝቡ እንደተለመደው በሰላማዊ ኑሮውን ለመግፋት ያልተቻለ  መሆኑን ዘርዝሮ ገልጿል። በጭለማ የሚንቀሳቀስ ወጣት በፖሊሶች እንደሚያዙና እንደሚመረመሩ፤ የእጅ ስልካቾቻቸው ከተቃውሞ ጋር የተያያዙ ፎቶግራፎች ካሏቸው ወዲያውኑ እንደሚታሰሩ አንዳንዳቹም እንደሚገደሉ፤ ወላጆች በየቀኑ  ለልጆቻቸው እየተጨነቁ እንዳሉ ዘግቧል። በአምቦ ውስጥ የወታደሩ ብዛት በጣም ከፍተኛ መሆኑን ከአንዳንድ ቦታዎች በስተቀር የንግድት ተቋሞችና ሆስፒታሎች ዝግ መሆናቸውና ላለፉት ሶስት ወራት ትምህርት የተቋረጠ መሆኑን ተገልጿል። የወያኔ አገዛዝ በስልጣን እስካለ ድረስ አመጹ የሚቀጥል መሆኑ ነዋሪዎች የገለጹለት መሆኑን ተናግሯል።

 

Ø ኦክስፋም የተባለው የዓለም አቀፍ ድርጅት በቅርቡ ባወጣው አዲስ ዘገባ በኢትዮጵያ ውስጥ የገባውን ድርቅና ረሃብ በሚመከት አዳድስ ጥናታዊ መረጃዎች ያቀረበ መሆኑ ታውቋል። ባለፈው ዓመት ከ 12 እስከ 18 ወራት ባሉት ጊዜያት ውስጥ የዝናቡ መጠን የተመጣጠኑ ባለመሆኑ ከ50 እስከ 90 በመቶ ምርት የቀነሰባቸው አካባቢዎች መኖራቸውን፤ በአርብቶ አደሩ አካባቢ ሶስትና አራት በጎች ወይም ፍየሎች ሸጠው ምግብ ይገዙ የነበሩ ቤተሰቦች አሁን አንድ እንኳ ሸጠው እህል ለመግዛት ባለመቻላቸው ህይወታቸው እየተጠበቀ ያለው  ሙሉ በሙሉ  በእርዳታ እህል ላይ መሆኑ ዘግቧል። ከሚያስፈልገው  እርዳታ ውስጥ እስካሁን የተገኘው 58 ከመቶ የሚሆነው ብቻ እንደሆነም ዘገባው ጠቅሶ ባስቸኳይ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት እርዳታ ካልተገኘ ከሚያዚያ በኋላ ከፍተኛ ችግር ሊከተል እንደሚችልም የአለም አቀፉ ድርጅቶችን ዋቢ በማድረግ አሳስቧል።  የሶማሌ ጎሳዎች በሚኖርበት አካባቢ ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ  በረሃብ የተጠቃ መሆኑን ጠቅሶ በአንድ አካባቢ ብቻ 13500 የሚሆኑ ሰዎች የመጠጥ ውሃ የሚያገኙት ለጊዜው ከተቆፈረ የውሃ ጉድጓድ ነው ብሏል። በሌላ በኩል  ድርቅን ለመቋቋም የሚያስችል የመስኖ ልማት ማስፋፋት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ተግባራዊ ማድረግ ሲገባው የወያኔ አገዛዝ ይህን ባለማድረጉ አገሪቷን ለከፍተኛ ረሃብ እንድትጋለጥ አድርጓታል  በማለት አንዳንድ ወገኖች እየተናገሩ ሲሆን ለድርቅ ተጠቂ የማይሆኑ አዝርእትን መጠቀምም ድርቅን ለመቋቋም ይረዳል የሚሉ ሀሳቦችም እየተሰነዘሩ ይገኛል።

 

 

Ø በባህርዳር  ከተማ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ  በተጠራ ስብሰባ ላይ የተገኙት ነዋሪዎች በወያኔ ሹመኞች ላይ ከፍተኛ ቁጣ ማሰማታቸው ከባህር ዳር ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።  ከዚህ በፊት ግምገማ ተብለው በተጠሩ ስብሰባ የደረሰብንን በደል ነቅሰን ተናግረን እናንት እርምጃ ባለመውሰዳችሁ  ጠላት እንድናፈራ አድርጋችሁናል ካሉ በኋላ በእንዲህ ዓይነት ስብሰባ ለመሳተፍ ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸዋል።  ይህ በእንዲህ እንዳለ ለባህርዳር ስፖርተኞች ማጎልመሻ በአስር ሚሊዮን ብር በጀት የሚሰራ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ተቋሙ  የሚገነባበት ቦታ ቀደም ብሎ በተለያዩ አነስተኛ  የንግድ ስራዎች የተሰማሩ ዜጎች  ይጠቀሙበት የነበረ ቦታ ሲሆን  ስፍራውን ለማስለቀቀ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል።   በእንጨት ንግድ፤ በመኪና ጥበቃ፤ በጉልት ችርቻሮ፤ ወዘተ… የንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ጉሮሮ ይሸፍኑ የነበሩትን ዜጎች  ከቦታችው ከማንሳት ይልቅ  የተባለውን ተቋም ወይ ወደ ሌላ ቦታ መውሰድ አሊያም ዜጎቹ ሊነግዱበት የሚችሉበት ተለዋጭ ቦታ መስጠት ሲገባ ከፍተኛ ወከባና እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑን ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል።  

 

 

Ø ባለፈው ወር በሶማሊያ ደቡባዊ ግዛት በአልሸባብ ኃይሎች የተገደሉት የኬኒያ ወታደሮች ቁጥር  180 እስከ 200 ይደርሳል ሲሉ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ከአንድ የሶማሊያ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉ ቃለ ምልልስ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ 180 እስከ 200 የሚደርሱ የኬኒያ ወታደሮች መሞታቸው የተረጋገጠ ነው ካሉ በኋላ በወታደሮቹ የቀብረ ስነስርዓት ላይ መገኘታቸው ትክክል የነበረ መሆኑን ገልጸው  በአንዳንድ የሶማሊያ ዜጎች የተሰነዘረባቸውን ተቃውሞ አጣጥለዋል። የኬኒያ ባለስልጣኖች የሱማሊያው ፕሬዚዳንት የሰጡት አዲስ መግለጫ  ሀሰት ነው በማለት የካዱ ሲሆን የሞቱት የኬኒያ ወታደሮች ምን ያህል መሆናቸውን ለመናገር ሳይደፍሩ ቀርተዋል። አልሸባብ ከ100 በላይ የኬኒያ ወታደሮች መግደሉን የሚገልጽ መግለጫ በወቅቱ መስጠቱ ይታወሳል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም ረፋድ ላይ ዮላ በምትባለዋ  በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በምትገኘው ከተማ ውስጥ በዋናው የፖሊስመስርያ ቤት ውስጥ  ከፍተኛ የሆነ የፈንጅ ድምጽ መሰማቱን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። በፈንጅው ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ እስካሁን መረጃ ባይገኝም የህንጻዎች ግድግዳዎችና መስኮቶቹ የፈራረሱ መሆኑን የአይን እማኞች ይናገራሉ። ቦታው በተደጋጋሚ በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የአሁኑንም ፈንጅ የቦኮ ሃራም ድርጊት ሳይሆን አይቀርም በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚሰጡ በርካታ ናቸው።  

 

ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በጄኔቫ ሲወዘርላንድ ይፋ የሆነው  95 ገጾችን የያዘው የተመድ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ዘገባ ሊቢያ ውስጥ ስለሚገኘው አስከፊ ሁኔታ በሰፊው የዘረዘረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ሊቢያ ውስጥ በተፈጠረው የፖሊቲካ ቀውስ አንገትን በመቁረጥ ጨምሮ በርከት ያሉት ግድያዎች መካሄዳቸውን፤ በርካታ ዜጎች የታሰሩ መሆናቸውን የኤሌክትሪክ ኃይልን ጨመሮ በድብደባ በመሳሰሉት በዜጎች ላይ የማሰቃያ ድርጊቶች መፈጸማቸውን ዘገባው ገልጾ ወንጀለኞች ወንጀለኞቹ አለምንም ጥያቄ በነጻ ተቀምጠዋል ብሏል። ዘገባው መንገድ ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን፤ ለመግደል የተደረጉ ሙከራዎችን ማስፈራዊያዎችንና ማስጠንቀቂያዎችን እንዲሁም ሴቶች ላይ የተፈጸሙ አስከፊ ድርጊቶችን አካትቷል። ዘገባውን ያወጣው የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን አያይዞ በሰጠው መግለጫ ድርጊቱን የፈጸሙት በሊቢያ የሚገኙ ተንቀሳቃሽ አካሎች በሙሉ መሆናቸውን ጠቅሶ አገሪቱ በትናንሽ የጎሳ ቡድኖቹ፤ በአይሲስ ቅርንጫፍ ቡድኖች፤  ትሪፖሊ ላይ መቀመጫ ባደረገውና  ራሱን መንግስት ነኝ ብሎ በሚጠራው ቡድን እና የዓለም አቀፍ እውቅናን ባገኘውና መቀመጫውን በምስራቅ ሊቢያ ባደረገው ቡድን መከፋፈሏ ህግን ለማስከበር አልተቻለም ብሏል። የተመድ የሰብአዊ ኮሚሽን መሪ ሚስተር ዘይድ ራእድ ድርጊቱን የፈጸሙት ሁሉ የጦርነት ወንጀል የፈጸሙ በመሆናቸው ወደ ፍርድ ሊቀርቡ ይገባል ብለዋል። ዘገባው ከመጻፉ በፊት ከ250 በላይ ምስክሮች በላይ መረጃ የሰጡ ሲሆን 900 አቤቶታዎችን ዘገባውን ያወጣው ክፍል የመረመረ መሆኑ ታውቋል።

 

 

 

የካቲት 16 ቀን 2009 ዓ.ም

 

·       በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ የሚገኙት ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008  ቀን 2008 ዓም ቀጥለው መዋላችው ከልዩ ልዩ ምንጮች የሚገኙት ዜናዎች ይጠቁማሉ። በዛሬው ቀን በምስራቅ ሀረርጌ በዳሩ ላቡ አካባቢ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን እንዲሁም ካለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ በመቻራ፤ በሚቻ፤ በጋዱሎ፤ በቢልካየና በሳኩራ አካባቢዎች የሕዝቡ ተቃውሞ የቀጠለ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪም በምዕራብ ወለጋ የተለያዩ ቦታዎችና  እንዲሁም በዚሁ አካባቢ አላሙዲ የወርቅ ማዕድኑን በሚዘርፍበት በዩብዶ ከፍተኛ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተደረገ መሆኑ ተዘግቧል።  በያቤሎ ቦረና አካባቢም ተመሳሳይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ እንደነበር የተለያዩ ምንጮች ገልጸዋል።

 

 

·       እንደገና አገርሽቶ በመቀጣጠል ላይ ባለው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ምክንያት ውጥረት ውስጥ የገባው የወያኔ አገዛዝ በአንድ በኩል “የማያዳግም”  የኃይልና የጭካኔ እርምጃ የአግአዚው ጦር እንዲወስድ ጥብቅ መመሪያ እያስተላለፈ በሌላ በኩል ሰላም ሊያወርዱ ይችላሉ ብሎ የሚገምታቸውን ወገኖች በመቅረብ እንቅስቃሴውን ለማኮላሸት ጥረት እያደረገ ይገኛል። በተለያዩ ቦታዎች ያሉትን አባገዳዎች ጠርቶ ሁኔታውን እንዲያረጋጉ የግዳጅና የማስፈራሪያ ጥያቄ ማድረጉን ውስጠ አዋቂ ምንጮች እየተናገሩ ሲሆን ለሃይማኖት መሪዎችም ተመሳሳይ ጥያቄ ትዕዛዝ አቅርቦ በጉዳዩ ላይ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ተነግሯል።

 

·       የሰማያዊ ፓርቲ የቀድሞው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ትናንት የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም ለሥተኛ ጊዜ አራዳ ፍርድ በዝግ ችሎት የቀረበ መሆኑ የተነገረ ሲሆን አቃቤ ህጉ የምርመራ ጊዜውን ያልጨረሰ መሆኑ ገልጾ ጥያቄ በማቅረቡ  28 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ የተሰጠው መሆኑ ታውቋል። አቶ ዮናታን እስካአሁን ድረስ ለምርመራ ማንም እንዳላናገረው የተናገረ ሲሆን ከታሰረ ጀመሮ ጠበቃውን ማነጋገር ያልቻለ መሆኑንም አስረድቷል። ከጠበቃው ጋር ሳይመካከር ቃሉ መስጠት እንደማይፈልግ ለፍርድ ቤቱ ተናግሮ ጠበቃውን ለማነጋገር እንዲፈቅድለት ጠይቋል ተብሏል።

 

·       የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ሚስተር ብሌዝ ኮምፓዎሬ (Blaise Compawore) የአቮሪ ኮስት ዜግነት የተሰጣቸው መሆኑ ዛሬ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. በይፋ ተነግሯል። ባለቤታቸው የአይቮሪ ኮስት ተወላጅ የሆኑት ሚስተር ኮምፓወሬ ዜግነቱ የተሰጣቸው ከሁለት ዓመት በፊት በአገሪቱ ፕሬዚዳንት በሚስተር ካታራ ሲሆን እስካሁን በሚስጥር ተደብቆ በዛሬው ዕለት በይፋ ተገልጿል።  ሚስተር ካምፓወሬ ከሁለት ዓመት በፊት በሕዝባዊ አመጽ ከስልጣን ተወግደው ወደ አይቮሪ ኮስት የሄዱ ሲሆን ከእሳቸው በፊት የነበሩትን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራን በግፍ አስገድለዋል በሚል ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው አይቮሪ ኮስት እንድታስረክባቸው የቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወቃል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት የአይቮሪ ኮስት ዜግነት ከተሰጣቸው የማስረከቡ ጥያቄ የማይፈጸም መሆኑ ተነግሯል።

 

·       በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለተፈናቀሉ ሰዎች የተሰራውን መጠለያ ጣቢያ ሲጎበኙ  የነበሩት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን በዚህ ዓመት በአለም ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እርዳታ በመቀበል ላይ ያሉ ዜጎች ቁጥር 60 ሚሊዮን መድረሱን ይፋ አድርገዋል። ዋና ጸሐፊው የወቅቱ የስደተኛ ቁጥር ባለፉት 65 ዓመታት ከነበረው ቁጥር ከፍተኛው መሆኑን ገልጸው እርዳታው መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። በሚቀጥለው ግንቦት ወር በሚደረገው የሰብአዊ መብትና እርዳታ ስብሰባ ላይ ጉዳዩ በሚገባ ተነስቶ ውይይት እንደሚካሄድበትም ቃል ገብተዋል። በኮንጎ ሀብታም የሆነውን የማዕድን ቦታ ለመቆጣጠር የተለያዩ የታጠቁ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱ ሲሆን እነዚህ ቡድኖች በሚወስዷቸው የኃይል እርምጃዎች በርካታ ዜጎች ቤት ንብረታቸውን እየጣሉ መሰደዳቸው ይታወቃል።

 

·       በሊቢያ የሚንቀሳቀሰው የአይሲስ ቡድን ሳብራታ (Sabratha) በምትባለው ከተማ ውስጥ የሚገኘውን የመንግስቱን የጸጥታ ክፍል ጽ/ቤት ለጥቂት ጊዜ በቁጥጥር ስር አውሎ 12 ወታደራዊ መኮንኖችን አንገታቸውን በስለት  በመቁረጥ የገደላቸው መሆኑ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ዛሬ ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓም የሊቢያ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ ከከተማው የተባረሩ መሆናቸው ታውቋል። የአይሲስ ቡድን አባላት ወደ ጽ/ቤቱ ሊገቡ የቻሉት በከተማው የሚገኙ ወታደሮች በሌላ ግዳጅ ላይ መሰማራታቸውን እና በስፍራው ላይ የጸጥታ ክፍተት በመከሰቱ ነው  ተብሏል። አሸባሪዎቹ ቦታውን ለሶስት ሰዓታት ያህል ለመቆጣጠር የቻሉት አንገታቸውን የቀሏቸውን ሰዎች አሰከሬን መሬት ላይ በማነጥፍ መንግድ ለመዝጋት በመሞከራቸው ነው በማለት በአአባቢ የነበሩ እማኞች ይናገራሉ። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በሊቢያ የአይሲስ እንቅስቃሴ ጎላ እያለ የመጣ ሲሆን ባለፈው ሳምንት በአሜሪካው የአየር ጥቃት የተወሰኑት መገደላቸው ይታወሳል።

 

 

·       በአፍሪካ ከሚገኙት አምስት ህጻናት መካከል አንደኛው ለተለያዩ በሽታዎች መከላከያ የሆኑ ክትባቶች እንደማይደረግለት የአለም የጤና ድርጅት (WHO) ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ዘገባ አስታወቀ። እንደ ፈርንጆቹ አቆጣጠር ከ2000 ዓም ጀምሮ እስከ 2014 አመተ ምህረት ድረስ ባሉት አመታት ለህጻናት የሚደረገው የክትባት አገልግሎት ከ57 ከመቶ ወደ 80 በመቶ ያደገ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በሌሎች የአለም አገሮች የጠፉ በአፍሪካ ግን በስፋት የሚገኙትን በሽታዎች ለማጥፋት ብዙ ስራ መሰራት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።   

 

 

የካቲት 15 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በአገሪቱ ለገባው ድርቅና ረሃብ ከዓለም አቀፉ ህብረተሰብ እየተሰጠ ያለው እርዳታ በቂ አለመሆኑን በኢትዮጵያ የሚገኙት የተመድ የህጻናት መርጃ ድርጅት ተወካይ ገልጹ። እስከሚቀጥለው ግንቦት ወር ድረስ በቂ እርዳታ የማይገኝ ከሆነ እና እንደወትሮው ዝናም በወቅቱ ካልዘነበ የብዙ  ሰዎች ሕይወት ሊቀጠፍ  እንደሚችል   ስለሁኔታው እውቀት ያላቸው ሰዎች ይናገራሉ።   በአፋር አካባቢ የቀንድ ከብቶች እያለቁ መሆናቸውን የአይን እማኞች በየጊዜው የተናገሩ ሲሆን  እስከ ስኞ 14 ይደርሳል ተብሎ የተጠበቀው  የእርዳታ እህልም እንዳልደረሰ ያካባቢው ነዋሪዎች አጋልጠዋል ። በርካታ ሰዎች    በምግብ እጥረት እንደተጠቁ የታወቀ  ሲሆን በተለይም ህጻናት መሞት የጀመሩ መሆናቸውም ተነግሯል። የወያኔ አገዛዝ ከዚህ በፊት የድርቁን ሁኔታ በራሳችን ገንዘብ እና የሰው ኃይል እንቋቋማዋለን እንጅ ወደ ልመና አንገባም የሚል ዲስኩር ሲያሰማን ቆይቶ በኋላ ባዕዳንን ሲለምን የታየ መሆኑን ያስታወሱት ዜጎች ከድርቅ በኋላ ረሃብ የሚከሰትበት ወቅት አልፏል እያለ በደነፋ በጥቂት ቀናት ውስጥ በድርቁ ምክንያት ሰዎች መሞታቸው እየተዘገበ ነው በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

 

 

Ø በተያላዩ አካባቢዎች የሚደረገው ሕዝባዊ ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በምዕራብ ወለጋ በቤጊና በአይራ የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ጎላ ያሉ እንደነበር ተዘግቧል።  ሰኞ የካቲት 14 በምስራቅ ሀራርጌ በተለያዩ አካባቢዎች ተቃውሞ ቀጥሎ የነበረ ሲሆን  አራሙሪ በተባለው መንደር በተከሰተ ሕዝባዊ ተቃውሞ ከአስር በላይ ሰዎች ሲገደሉ  በመቻራም በእድሜ ለጋ የሆኑትን ጨምሮ በርካታ ስዎች መገደላቸው ታውቋል። በቅርቡ እንደገና በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ተቃውሞ በጠቅላላው ከ43 በላይ ሰዎች በወያኔ አግአዚ ጦር መገደላቸውን አንዳንድ ምንጮች ይጠቁማሉ። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር በዛሬው ዕለት የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን ብሎ መዛቱ የታወቀ ሲሆን ይህም  የወያኔ አግአዚ ጦር ጭፍጨፋን ያጠናክረዋል ተብሏል።

 

Ø በእስራኤል አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የመረረ የዘር መድሎዎ የሚደርስባቸው መሆኑ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የተዘገበ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ ጋብቻቸው ህጋዊ እንዲሆንና የጋብቻ የምስክር ወረቀት እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ወጣቶች እውነተኛ የአይሁድ ሃይማኖት ተከታዮች አይደላችሁም በሚል ምክንያት ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገ መሆኑን የእስራዔል ጋዜጦች አጋልጠዋል። ቤታህ ቲክቫ (Petah Tikva) በተባለችው የእስራዔል ከተማ በቅርቡ ከ30 በላይ የሆኑ አዲስ ትዳር መስራቾች የጋብቻ የምስክር ወረቀት  የተከለከሉ መሆናቸው ሲታወቅ በሌሎች ቦታዎችም ተመሳሳይ ድርጊት የሚፈጸም መሆኑን በርካታ ዜጎች ይናገራሉ። ለመከልከሉ ዋናው ምክንያት የሃይማኖት ጉዳይ ሳይሆን ዓይን ያወጣ ዘረኛነት መሆኑን ብዙዎቹ ይናገራሉ። ከጥቂት ወራት በፊት በእስራኤል የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚደርስባቸውን የዘረኛነት በደል በመቃወም ከፖሊስ ጋር ግጭት ማድረጋቸው ይታወሳል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ከሚመለከታቸው ወገኖች ጋር ንግግር ለማድረግ ትናንት የካቲት 14 ቀን 2008 ዓም ከሰዓት በኋላ ብሩንዲ የገቡ ሲሆን ሌሊቱን  ከ10 በላይ የሚሆኑ ቦንቦች ፈንድተው በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸው እንዲሁም ከቆሰሉት መካከል ወታደሮች እንደሚገኙበት ተነገረ። ቦምቦቹን ያፈነዳው የትኛው ወገን እንደሆን ካለመታወቁ በላይ ፖሊሶች በአገሪቱ ሰላም የለም የሚል መልእክት ለተመድ ዋና ጸሐፊ ለማስተላለፍ ተቃዋሚዎች  ያካሄዱት የሽብር ተግባር ነው በማለት መግለጫ ሰጥተዋል።  የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የመንግስትና የተጻራራሪ ወገኖችን አግኝተው ያነጋገሩ መሆኑን ጠቅሰው ሁለቱም ወገኖች ተገናኝተው ለመወያያትና ላለፉት 10 ወራት በአገሪቱ የሰፈነውን የቀውስ ሁኔታ ለመፍታት መስማማታቸውን ገልጸዋል። በተጻጻሪነት የተሰለፉት የብሩንዲ ተቃዋሚ ኃይሎች የተወሰኑት ከአገር የተሰደዱ ገሚሶቹ በእስር ላይ የሚገኙኑ እና ከፊሎቹ ደግሞ ትጥቅ አንስተው የሚታገሉ ሲሆን በስልጣን ላይ ያለው ክፍል ተቀምጦ ለመነጋገር ፈቃደኛ የሆነው ከየትኞቹ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር መሆኑ በግልጽ አልተነገረም። ይሁን እንጅ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ንክሩንዚዛ ማክሰኞ ዕለት በሰጡት መግለጫ ንግግሩ አገሪቱ ውስጥ በሽብር ተግባር ከተሰለፉት በስተቀር ከሁሉም የብሩንዲ ዜጎች ጋር ሊደረግ ይችላል ማለታቸው ውይይቱ ዋና ዋና ተቃዋሚዎችን ሊያገልል ይችላል የሚል ግምት አሳድሯል። 

 

Ø በሊቢያ ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው መንግስት አካል የሆነው የህግ አውጭው ምክር ቤት ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም ለማካሄድ ያቀደው ስብስባ ምልአተ ጉባዔ ባለማግኘቱ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀርቦ የነበረው የአንድነት መንግስት ምስረታ ረቂቅ ሀሳብ ሊጸድቅ ያልቻለ መሆኑ ተነገረ።  ስብሰባው ምልአተ ጉባዔ አግኝቶ እንዲካሄድ ለማደረግ 89 የምክር ቤት አባላት በስብሰባው ላይ መገኘት የነበረባቸው ሲሆን ይህ ባለመገኘቱ ስብሰባው ሳይጀመር ሊበተን ችሏል። በርከታ የምክር ቤቱ አባላት ወደ ስብሰባው መምጣት ያልቻሉት በቀረበው ረቂቅ ሀሳብ ላይ ልዩነት ስላላቸው ነው ተብሏል። ባለፈው ታኅሳስ ወር በስምምነት የተመሰረተው የፕሬዚዳንት ካውንስል የተባለው አካል 18 የካቢኔ አባላት ያሉበት የአንደነት መንግስት ረቂቅ ሀሳብ ያቀረበ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት ምክር ቤት እስካሁን ሳያጸድቀው ቀርቷል። በሚቀጥለው ሳምንት ሌላ ስብሰባ የሚይጠራ መሆኑም ተነግሯል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም የስፔይንና የሞሮኮ ፖሊሶች አራት የአሸባሪ ቡድኖች አባሎችን የያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። የስፔይን ፖሊሶች ሶስት ሰዎችን በሴሜን አፍሪካ ከምትገኘውና ሴውታ (Ceuta) ተብላ ከምትጠራው ከተማ መያዛቸው ከመነገሩ በተጨማሪ የሞሮኮ ፖሊስች ደግሞ ፋርካና በተባለችው የወሰን ከተማ አንድ የሞሮኮ ዜጋ በቁጥጥር ስር አውለዋል። በሴውታ ከተያዙት መካከል አንደኛው በጓንታናሞ እስር ቤት ታግቶ የነበረ የአልካይዳ አባል የነበረና በወታደራዊ ትምህርቶችና በቦምብ ስራዎች የሰለጠነ መሆኑ  ታውቋል። አራቱም ሰዎች ተባባሪዎች ለመመልመልና በወታደራዊ  ተግባር ላይ ለማሰልጠን ግንኙነት ሲያደርጉ እጅ ከፍንጅ የተያዙ መሆናቸው ተዘግቧል። በሞሮኮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጸጥታ ሁኔታ እየደፈረሰ በመምጣቱ ተጥርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማድረጉ ተግባር በተጠናከረ ሁኔታ ከመምጣቱ በተጨማሪ የስፔይን ፖሊስም ካለፈው ዓመት ወዲህ 100 በላይ ተጥርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑ ይነገራል።   

 



 

 

 

የካቲት 14 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø ባለፉት ሁለት ቀናት በአሩሲ በምስራቅና በምዕራብ ሀረርጌ በምዕራብና በምስራቅ ወለጋ እንዲሁም በሸዋ ሱልልታ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ከየአካባቢዎቹ የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።  በአንዳንድ ቦታዎች የአግአዚ ጦር እንዳይገባ ለመከላከል ተቃዋሚዎቹ  መንገዶችን የተዘጉ ሲሆን በምዕራብ ሀረጌና በምስራቅ ወለጋ የአግአዚ ጦር ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ በሚያሰሙ ንጹህ ዜጎች ላይ በከፈተው ተኩስ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ሞተዋል።  ባለፈው ሳምንት በምዕራብ ሸዋ ተካሂዶ በነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ በንጹሓን ዜጎች ላይ ሲተኩሱ የነበሩና በሕዝቡ በተሰነዘረ ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸው አራት ወታደሮች በአዲስ አበባ የጦር ኃይሎች ሆስፒታል ህክምና እያደረጉ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም ከምዕራብ ሸዋ ከአምቦ ከነቀምት ከነጆ ከጊንጪ ከግንደበረት ታፍነው የመጡ ወጣቶች አዲስ አበባ ማዕከላዊ ምርመራ ተብሎ በሚታወቀው እስር ቤት የተለየ ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን አንዳንድ ምንጮች ይገልጻሉ።

 

 

Ø ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት እሁድ የካቲት 13 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዘገባ በኦሮሚያ አካባቢ የወያኔ አግአዚ ወታደሮች በሰላማዊ ዜጎች ላይ እያካሄዱት የሚገኙት የግፍ ጭፍጨፋ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን ዘግቧል።  የአግአዚ ወታደሮች ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሚያካሂዱ ዜጎች ላይ የእሩምታ ተኩስ በመተኮስ በርካታ ሰዎች መግደላቸውን በሺ የሚቆጠሩትን ደግሞ አፍሰው ማሰራቸውን ዘገባው አጋልጧል። የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን መሰረዙንና  አሁኑ ሁኔታው የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ የወያኔ ባለስልጣኖች  ተደጋጋሚ መግለጫ ቢሰጡም እንቅስቃሴው ተባብሶ መቀጠሉን ዘገባው በዝርዝር ገልጿል። በታኅሣስ እና በጥር ወራት 2008 ዓም ድርጅቱ ያነጋገራቸው ከስድሳ የሚበልጡ ሰዎች የአግአዚ ወታደሮች በተቃውሞ ስልፎች ላይ ባሄዱት ተኩሶችም ሆነ ዜጎችን ከያዙ በኋላ በርካታ ዜጎች መግደላቸውን  በጅምላ ማሰራቸውናና የያዟቸውንም በቶርቸር ሲያሰቃዩ መቆየታቸውን በማረጋገጥ የመሰከሩ መሆናቸውን ዘገባው ገልጿል።   በአንዳንድ ቦታዎች በመንግስት ንብረቶችና በውጭ ባለሃብቶች ላይ የደረሰ የዘረፋ ተግባር ቢኖርም ተቃውሞ በአብዛኛው ሰላማዊ እንደነበሩ ድርጅቱ በዘገባው ዘርዝሯል። በአንዳንድ አካባቢዎች አስተማሪዎች እና ተማሪዎች በአግአዚ ወታደሮች በመታሰራቸው በሌሎች ደግሞ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ባለመሄድ ተቃውሞ በማድረጋቸው በርካታ ትምህርት ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውም ተዘግቧል። በጥር ወር ላይ የአውሮፓው ፓርላማ ወያኔ እያካሄደ ያለውን ጭፍጨፋ ቢያወግዝም ለወያኔ ከፍተኛ እርዳታ የሚያደርጉት እንግሊዝ አና አሜሪካ እንዲሁም ሌሎች መንግስታት ድምጽ አለማሰማታቸው ድርጅቱ የሚያሳስበው መሆኑን ገልጿል።

 

Ø በደቡብ ምዕራብ በኢትዮጵያ ኬኒያንና በደቡብ ሱዳን ወሰን ላይ የሚገኘውን ኤለሚ ትሪያንግል የሚባለው ቦታ ሶስቱም አገሮች የይገባኛል ጥያቄ ያነሱ ሲሆን በቅርቡ በደቡብ ሱዳን እና በኬኒያ እንዲሁም በወያኔ ባለስልጣኖች መካከል ውይይት ለማካሄድ የታቀደ መሆኑ ተነገረ። የኤሌሚ ትሪያንግል የሚባለው ቦታ የተለያዩ ማዕድናት የሚገኙበት ቦታ ሲሆን እንድ አውሮፓ አቆጣጠር ከ1956 ዓም ጀምሮ በኬኒያ ቁጥጥር ስር ሆኖ የቆየ ነው።  በ1907 ዓም ኢትዮጵያ ከእንግሊዝ ጋር በነበራት ውል መሰረት ቦታው ለኢትዮጵያ ተሰጥቶ ነበር የሚል ማስረጃ አለ ተብሏል።  

 

Ø ወያኔ ዘመናዊ ባርነት ወጣት ሴቶችን ለአረቦች በመሸጥ ሚያገኘው ገቢ በጣም በርካታ መሆኑን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂዎች በቅርቡ ደግሞ ሕጻናትን ለጉዲፈቻ በማቅረብ ብቻ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገቢ ያደረገ መሆኑን ይናገራሉ።   ባትና እናት የሞቱባቸውም ሆነ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ ለቀጥታ ሽያጭ የተዘጋጁ ህጻናት ቁጥር በአሁኑ ወቅት  ወደ 5 ሚሊዮን ይጠጋል ሲሉም እነዚሁ ወገኖች አጋልጠዋል ። እናቷ እያለች ወላጆች  የላትም ተብ ለአሜሪካዋ  አንጀሊና ጆሊ የተሸጠቸው ሴት ሕጻን ምስክር ናት ተብሏል ። በከፍተኛ ደረጃ ለጉዲፈቻ  ሕጻናት የሚወሱዱባቸው አገሮች  ኮሪያ፤ካምቦዲያና ሃአይቲ ሲሆኑ በነዚህ ቦታዎች የግዢው ውጋ ውድ ነው ያሉ ውስጠ አዋቂዎች የኢትዮጵያ ልጆች ግን ርካሽ ዋጋ ማግኘት ይቻላል ብለዋል ። ይህ የሕጻናት ንግድ በአብዛኛው የሚካሄደው በወያኔ ወይም ክልል አንድ ተወላጆች እንደሆነም ተጋልጧል ። የኢትዮጵያን ሕጻናት በመግዛት በኩል ቀዳሚ የሆኑት አሪካ፤ካናዳ፤ ፈረንሳይና ስዊድን ናቸው ።

 

Ø የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዋና ተቃዋሚ በመሆናችው ከአርብ ከየካቲት 10 ቀን 2008 ጀምሮ በቤት ውስጥ የቁም እስር ላይ የነበሩት  ሚስተር ቢስግየ ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2008 ዓም ከቤታቸው ለመውጣት ሲሞክሩ በፖሊሶች ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ የተወሰዱ መሆናቸው ተገልጿል። ፓሊስ ሚስተር ቢስግየ በቁጥጥር ስር ለማዋል የተገደደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዳቸው ስለተደረሰበት ነው ብሏል።  ባለፈው ሐሙስ በተደረገው ምርጫ ሙሰቨኒ የድምጹን 60 ከመቶ በማግኘት አሸንፈዋል ቢባልም ምርጫው ግልጽነት የሌለበት፤ በፍርሃት እና በሽብር የተካሄደ መሆኑን አውሮፓው ህብረት  ታዛቢዎችና በሌሎችም ወገኖች ገልጸዋል። ተቃዋሚዎችም ምርጫው መጭበርበሩ ግልጽና ይፋ ስለሆነ ውጤቱን አንቀበልም ብለዋል። ሙሰቨኔ ምርጫው ተጭብርብሯል የሚለውን ክስ ያጣጣሉት ሲሆን በተቃዋሚዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ጸጥታን ለማስከበር ነው በማለት በተደጋጋሚ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በዛሬው ቀን ወደ ብሩንዲ እንደተጓዙ ተግልጿል። ዋና ጸፊው በብሩንዲ ጉዟቸው ከመንግስት እና ከተቃዋሚ ኃይሎች ባለስልጣኖች ጋር ተገናኝተው የሚወያዩ ሲሆን በሁለቱ ተጻራሪ ወገኖች መካከል ተጀምሮ የነበረውና በአሁኑ ወቅት ተንጠልጥሎ የሚገኘው የሰላም ውይይት እንደገና ሊጀመር የሚችልበትን መንገድ ያመቻቻሉ ተብሏል። ማክሰኞ የካቲት 15 ቀን ጠዋት የብሩንዲውን ፕሬዚዳንት በሚያናግሩበት ወቅት የጉዳዩን አሳሳቢነት በማንሳት ከፍተኛ ተጽእኖ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

 

Ø በቱኒዚያ ከወራት በፊት ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፕሬዚዳንቱ  ለሌላ አንድ ወር ጊዜ የተራዘመ መሆኑን የመንግስቱ ቃል አቀባይ ገልጿል።  ባለፈው ህዳር ወር በቱኒዚያ በዋና ከተማ በቱኒስ የአይሲስ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 12 ሰዎች ከተገደሉ ወዲህ በአገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ የሚታወስ ሲሆን አዋጁ ስብሰባንና የተቃውሞ ሰልፍን የሚከለክል እና የጸጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ልዩ ስልጣን የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። የአዋጁ ጊዜ እንዲራዘም የተደረገው ከሁለት ቀን በፊት በሊቢያ በአሜሪካ የአየር ጥቃት የተገደለው የአሸባሪዎች መሪ የቱኒዚያ ተወላጅ መሆኑ ከተነገረ በኋላ ነው። በተያያዘ ዜና በሞሮኮ ዋና ከተማ  በመገበያያ ቦታዎች እና በሆቴሎች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ተዘጋጅቶ የነበረ 10 አባላት ያሉት የሽብረተኞች ቡድን በቁጥጥር  ስር መደረጉን የሞሮኮ ባለስልጣኖች ገልጸዋል።  የ”ሞሮኮ ሞል” በሚል የሚታወቀው በካዛብላንካ የሚገኘው የገበያ ቦታ እና  ሶፊቴል ሆቴል በጥቃቱ ኢላማዎች ውስጥ እንዳሉበት ተነግሯል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሞሮኮ የአይሲስ እንቅስቃሴ እየተስፋፋ መምጣቱ ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል ሲሉ ታዛቢዎች ይናገራሉ።

 

 

 

 

 

 

የካቲት 12 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም ፋሽስት ኢጣሊያ ከ30 ሺ በላይ የሚሆኑ ኢትዮያውያንን በግፍ የጨረሰበት የሰማዕታት ቀን በዓል በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት የዓለም ክፍሎች ተከብሮ ውሏል። በየካቲት 29 ቀን 1929 ዓም ፋሽስቱ ግራዚያኒ አርበኞች በጣሉበት ቦምብ በመቁሰሉ ምክንያት ፋሽስቶቹ በወሰዱት የበቀል እርምጃ በአዲስ አበባ ከተማ ከ30 ሺ የማይንሱ ኢትዮጵያውያንን በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ መፈጀታቸውን በማስታወስ በየአመቱ ኢትዮጵያውያን ቀኑን ሲያከብሩት መቆየታችው የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ ቦታዎች ተከብሯል። በአዲስ አበባ ከተማ አርበኞች እና የከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት በየካቲት 12 አደባባይ ቀኑ የተከበረ ሲሆን በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍልና በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን  በተለያዩ መንገዶች አስበውት ውለዋል።

 

Ø ሰሞኑን አገርሽቶ እንደገና ተጠናክሮ በመቀጠል ላይ ያለው ሕዝባዊ ተቃውሞ በተለያዩ ክፍሎች የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። በዛሬው ዕለት በነገሌ ቦረና የአካባቢው አርሶ አደሮች የተሳተፉበት ከፍተኛ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የተደረገ ሲሆን በግፍ የታሰሩት ባስቸኳይ ይፈቱ፤ የአግአዚ ወታደሮች ከአካባቢው ይውጡ፤ ግድያው ይቁም፤ የአላሙዲ የወርቅ ማዕድን የህዝብ ንብረት ነው የሚሉ መፈክሮችን ሲያሰሙ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪ በትናንትናው ዕለት በ ወለጋ በጊምቢ እና በጋዎ ቅቤ ከተሞች ተመሳሳይ  ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እንደነበሩ ተዘግቧል። ትናንት በአምቦ ከተማ ዋና እስር ቤት በተቃጠለበት ወቅት እሳቱን በመሸሽ ሲያመልጡ የነበሩ ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ  እስረኞች በአግአዚ ወታደሮች ጥይት የተገደሉ መሆናችው አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል።  በጉደር ከተማ የኤልከትሪ ኃይል የተቋረጠ ሲሆን የአግአዚ ጦር ከፍተኛ የሆነ ተኩስ ሲያሰማ መቆየቱ ተነግሯል።

 

Ø በተያያዘ ዜና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ምክትል ኃላፊ አቶ በቀለ ገርባ እና ከሳቸው ጋር የተያዙት የፓርቲው አባላት፤ እንዲሁም የነገረ ኢትዮዮጵያ ዋና አዘጋጅ አቶ ጌታቸው ሽፈራውና የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ ዳንዔል ተስፋየ  አርብ የካቲት 11 ቀን 2008 ዓም ፍርድ ቤት ቀርበው አቃቤ ህጉ ምርመራዬን አልጨረስኩም በማለቱ የ28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ የተፈቀደለት መሆኑ ታውቋል። አቃቤ ህጉ ተጨማሪ ምርመራ ይቀረኛል፤ ምስክር አላዘጋጀሁም ቢልም ከታሳሪዎቹ መካከል አቶ ጌታቸው ሽፈራው አንድም ሰው እንድላነጋገቸው ገልጸዋል። በተጫማሪም የአቶ ጌታቸው ጠበቃ ደንበኛቸውን ለማነጋገር እስካሁን ያልተፈቅደላቸው መሆኑን አስረድተው አቶ ጌታቸውን እንዲያነጋገሩ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

 

Ø ትናንት አርብ የካቲት 11 ቀን 2008 ዓም በታላቁ የአንዋር መስጊድ ሳላት ሲያካሂድ የነበረው የሙስሊሙ ማህበረሰብ የወያኔ አገዛዝ የሚፈጽመውን የግፍ ድርጊት በማውገዝና ፍትህን በመጠየቅ  ከፍተኛ የተቃውሞ ድምጽ ሲያሰማ መዋሉ ታውቋል። በቦታው ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መካከል ኮሚቴው ይፈታ ድምጻችን ይሰማ ብሄራዊ ጭቆና ያብቃ መንግስት የለም ወይ ? ነጻነት እንፈልጋለን የሚሉ ይገኙባቸዋል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም የኡጋንዳ የምርጫ ኮሚሽን  ሀሙስ ዕለት በተካሄደው የአገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት ሙሰቭኒ አሸናፊ ሆነዋል በማለት ይፋ መግለጫ ሰጥቷል። ፕሬዚዳንቱ ከድምጹ 60.75 አግኝተዋል የተባለ ሲሆን የቅርብ ተወዳዳሪያቸው የነበሩት ሚስተር ኪዛ ቢስግየ 35 ከመቶ ያገኙ መሆናቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ኅብረት የተዛቢ ቡድን ምርጫው ማስፈራሪያ እና ግጭት የነበረበት በመሆኑ ታአማኒነት አይኖረውም ሲሉ  ተቃዋሚ ድርጅቶች ደግም ምርጫው ተጭበርሯል በማለት በይፋ ተናግረዋል። ሚስተር ቢስግየ ከአርብ ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ የተያዙት በዋናው ከተማ ዙሪያ  በፖሊሶች አማካይነት እየተካሄዱ የነበሩትን ህገ ወጥ የምርጫ ሁኔታዎች ለማጋለጥ በሚዘጋጁበት ጊዜ መሆኑን ገልጸው ምርጫው ግልጽ ማጭበርበር የነበረበት በመሆኑ ውድቅ መሆን አለበት ብለዋል።  ምርጫው  የገዥው ፓርቲ አፈና በግልጽ የታየበት ሲሆን በየቦታው በጸጥታ ኃይሎች ከተወሰዱት የአፈና እርምጃዎች በተጨማሪ አገዛዙ በርከት ያሉ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግየተው እንዲከፈቱ በማድረግና ግልጽ የሆኑ ማስፈራሪያዎች በማራገብ የተቃዋሚ ደጋፊዎች በተገቢው መንገድ ድምጻቸውን እንዳይሰጡ አድርጓል ተብሏል። በዛሬው ቀን በካምፓላ ከተማ መንገዶች ላይ የጸጥታ ኃይሎች በብዛት መሰማራታቸው ታውቋል።

 

Ø የካቲት 11 ቀን 2008 በሊቢያ የአይሲስ ካምፕ ላይ በአሜሪካ በተደረገው የአየር ድብደባ  ከሶስት ወር በፊት በአይሲስ ተይዘው የነበሩት ሁለት የሰርብያ ዲፕሎማቶች አብረው የተገደሉ መሆናቸውን ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም የሰርብያ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናግረዋል። በሊቢያ የሰርብያ ኤምባሲ የመገኛኚያ ኃላፊ የነበረውና ይጓዝበት የነበረውን ሲያሽከረክር የነበረው ሹፌር የተያዙት አምባሳደሩ የሚገኙበት ቡድን በወታደራዊ አጀብ ታጅቦ በሰሜን ሊቢያ ባህር ዳርቻ ላይ ሲጓዙ ከአጥቂዎች በተሰነዘረ የደፈጣ ውጊያ ነበር። የሰርብያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰዎች በአሜሪካ የአየር ጥቃት መሞታቸውን የሚያረጋግጥ የፎቶግራፍ መረጃ ያገኙ መሆናቸውን ገልጸው ስዎችን ለማስፈታት በንግግር ላይ እንደነበሩ አስረድተዋል።

 

Ø  ቅዳሜ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም በሞሪታኒያ ከዋናው ከተማ አጠገብ ከሚገኝ ትልቅ እስር ቤት ውስጥ 40 የሚሆኑ እስረኞች ጠባቂዎችን በማጥቃት ከአስር ቤት ያመለጡ መሆናቸው ተዘግቧል። እስረኞቹ የጠባቂዎቹን  የመለዋውጫ  አመች ጊዜ ተጠቅመው ጥቃት በማድረስ አምልጠው በተለያዩ አቅጣጫዎች የሸሹ  ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ ታስረው መመለሳቸውና ሌሎት እየተፈለጉ መሆናቸው ተገልጿል። ከአመለጡት እስረኞች መካከል በአሸባሪነት የተያዙ የአክራሪ ቡድን አባሎች የሌሉበት መሆኑ ተነግሯል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው ድርጅት በሞሪታኒያ ግለሰቦች በእስር ቤት የጭካኔ ምርመራ የሚካሄድባቸው መሆኑን  አጋልጦ የእስር ቤቱም ሁኔታ አስከፊ መሆኑ ዘግቧል።  በዛሬው ዕለት እስረኞቹ ያመለጠበት እስር ቤት 400 ሰዎችን ብቻ የሚያስተናግድ ቢሆንም ከ1200 ሰዎች በላይ የታሰሩበት ነው ተብሏል።   

 

 

 

 

የካቲት 11 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

 

Ø በአዲስ አበባ መስፋፋት ስም ታቅዶ በነበረው አይን ያወጣ ዘረፋ ተጀምሮ  በንጹኃን ዜጎች ላይ የተወሰደው የግድያና የእስራት ዘመቻን ይቁም በማለት እየተቀጣጠለ ያለውና የሕዝብ ብሶት የወለደው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ትናንት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓ/ም እና ዛሬም የካቲት 11 ቀን  በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ቀጥሎ መዋሉና ዜጎች መጎዳታቸውን ከየአካባቢው የደረሰን ዘገባ አስረድቷል። ትናንት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦ እና በጉደር ያሉ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸው በታጠቁ የአግአዚ ወታደሮች የተሰበረ ሲሆን ሰላማዊ ዜጎች እየታፈኑ ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች መናገራቸው በዘገባው ተመልክቷል። ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ ለመውሰድ በተደረገው ሙከራ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን ከአግአዚ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል የሚል ዜና አለ። በዛሬው ዕለትም በአምቦ የሚገኘው ዋናው እስር ቤት ተቃጥሏል የሚል አንዳንድ ምንጮች ዘግበዋል።

የካቲት 10 ቀን 2016 ዓም በምዕራብ አርሲ አሳሳ በሚባለው ከተማ የወያኔ ቅልብ ወታደሮች  ሰላማዊ ሰዎችን ዘግናኝ በሆነ መንገድ ሲደበድቡ ነበር በማለት ምንጮች የገለጹ ሲሆን ትምህርት ቤቶችና መስሪያ ቤቶች ስራ አቁመው መዋላቸው ተነግሯል።  በምስራቅ ሀረርጌ የኦህዴድ ጽህፈት ቤት ላይ ጥቃት መድረሱንና በሕዝባዊ ተቃውሞው ማዕበል መመታቱን የሚገልጹ ምንጮች የአህዴድ ሹማምንቶች ጽህፈት ቤቱንና መኖሪያቸውን ጥለው የሸሹ መሆናቸውን አክለው ገልጸዋል። እንዲሁም በዛሬው ዕለት በምዕራብ ሀረርጌ በጭሮ ከተማ አካባቢ መንገድ የተዘጋ መሆኑ አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል። በትናንት የካቲት 10 ቀን የአግአዚ ወታደሮችና በአድማ ብተና ልዩ ስልጠና የተሰጣቸው ናቸው የተባሉ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ምሽቱን ተጉዘው ባሌ መግባታቸውን ለማወቅ ተችሏል። አርጆ ከተማ ላይ መንገድ በመዘጋቱ የጅማ የነቀምት የትራንስፖርት መንገድ አገልግሎት መቋረጡን በትራንስፖርት ስራ ላይ የተሰማሩ አሽከርካሪዎች መናገራቸው ታወቋል

 

 

Ø አንዳንድ የወያኔ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በወገናቸው ላይ እየተካሄደ ያለውን አሰቃቂ የሆነ ጭፍጨፋ መቃወማቸውና ጥያቄ ማቅረባቸው ቀደም ብሎ መዘገቡ የሚታወስ ሲሆን ወያኔ በሰራዊቱ ውስጥ የተፈጠረውን ክፍተት ለማጥበብና ለሰራዊቱ የማዕረግ እድገት ለመስጠት ሴራ ያቀደ መሆኑን ምንጮች አጋልጠዋል። የማዕረግ እድገት ለመስጠት የታሰበው  በያዝነው ወር የሚከበረውን የመከላከያ ሠራዊት ክብረ በዓል  ምክንያት በማድረግ ሲሆን በአብዛኛው ለበታች የሠራዊቱ አባላት እንደሆነ ምንጮች ገልጸዋል። ለህገ መንግስቱ ታማኝ መሆን አለበት የሚባለው ሠራዊት ከድንበር ጥበቃ ይልቅ የመብት ጥያቄ ባነሱ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ቃታ መሳቡ ተገቢ አይደለም በሚል ቅሬታቸውን ለአቆቻቸውና እንዲሁም ለግምገማ በተዘጋጀ መድረክ በአደባባይ ላይ ሲናገሩ የነበሩ  መስመራዊ መኮንኖች በአሉታዊ ከመገምገማቸው አልፎ ትጥቅ እንዲፈቱ ተደርገው የነበሩ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። ተቃውሞውን በሰፊው የሚያነሱትና የሚያባብሱት የበታች ወታደሮች  በመሆናቸው ወያኔ ጥያቄያቸውን ለማቀዝቀዝ የማዕረግ አድገት ሴራ ጠንስሷል ተብሏል።  በዚህ ሳምንት ማብቂያ ላይ በድሬዳዋ የሚገኘው የምስራቅ እዝ የሠራዊቱ የበታች መኮንኖች የመስመራዊ መኮንነት እድገትና ለተራ ወታደሮች ደግሞ   የክንድ ማዕረግ እንደሚሰጥ ታውቋል።

 

Ø ከአመታት በፊት በአዋጅ መልክ ጸድቆ በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ ተደርጎ የነበረው የጸረ ሙስና ህግ በድጋሚ ማስተካከያ ሊደረግለት የታሰበ መሆኑ ታውቋል። ለህጉ መስተካከል በመልካም አስተዳደርና በኪራይ ሰብሳቢነት ለሚያጠፉ አጥፊዎች ክፍተት ይሰጣል የሚል የማታለያ ምክንያት  ከአገዛዙ ይሰጥ እንጂ  እቅዱና የመስተካከሉ ዓላማ ሌላ ነው በማለት የታመኑ ምንጮች ያስረዳሉ።  ሕጉ እንዲስተካከል የተፈለገው የኦሮሚያ ፕሬዚዳንትንም ሆነ ከፍተኛ ባለስልጣኖችን ሊያስከሥስ የሚፈቅድ አንቀጽ የለውም በሚል ምክንያት ሲሆን ዋናው ዓላማ ግን እነሙታር ከድርና ለመወንጀልና ለመቅጣት ነው ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከየኦሮሚያ ምክር ቤት እንዲያጸድቀው ከወያኔ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተሰጠ ሲሆን በተሻሻለው እና በተጨመረው አንቀጽ ላይ የይስሙላ ውይይት ቢሾፍቱ ላይ እንዲደረግ መወሰኑን ከዘገባው ለመረዳት ተችሏል።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ በቅርቡ ተጨማሪ ወታደሮች ወደ ሱማሊያ የላከ መሆኑ ውስጥ አዋቂ ምንጮች አጋልጠዋል። በሱማሊያ ተዳክሟል ሲባልለት የቆየው የአልሸባብ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ምክንያትና እንዲሁም የወያኔ ጦር ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት በመሆኑ ተጨማሪ ጦር መላክ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም ምክንያት ቁጥሩን በውል ለማወቅ ያልተቻለ ጦር ሰሞኑን ባስቸኳይ ወደ ሱማሊያ የተጓዘ መሆኑ ተነግሯል። ከዚህ በተጨማሪ  በሱማሊያ ውስጥ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አሰባሪ ኃይል ወያኔ እና ኬኒያ የጦርና የማመላለሻ ሄሊኮፕተሮች ለመስጠት መስማማታቸውን ለማወቅ ተችሏል።   

 

 

Ø ትናንት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ ብሔራዊ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን እንደተጠበቀው የኡጋንዳ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአሁኑ ፕሬዚዳንት ሙሴቨኒ በምርጫው መሪነቱን የያዙ መሆናቸውን ገልጿል። ዛሬ የካቲት 11 ቀን ቀን በተጻራሪነት በመቆም የፕሬዚዳንቱ ግምባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆኑት  ኪዛ ቢስግየ  በፓርቲያቸው ጽሕፈት ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት በሚዘጋጁበት ወቅት በፖሊሶች ተይዘው የተወሰዱ መሆናቸው ታውቋል። ከፓርቲው ጽ/ቤት ውጭም በደጋፊዎቻችው ላይ የሚያስለቅስ ጋዝ መተኮሱ ተነግሯል። ሚስተር ቢስግየ በፖሊሶች ተይዘው ሲታሰሩ ይህ ሶስተኛ ጊዜያቸው ሲሆን በዛሬው ዕለት በምን ምክንያት እንደተያዙ ፖሊሶች የሰጡት ምክንያት የለም። ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዳልሆነ ብዙዎቹ እየተናገሩ ነው። በትናንትናው ዕለት በርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግየተው የተከፈቱት መራጩ ድምጹን እንዳይሰጥ ተስፋ ለማስቆረጥ የተደረገ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሳየከፈቱ ቀርተው ዛሬ ድምጽ የሚያሰጡ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውንም ለማወቅ ተችሏል። በትናንትናው ዕለት የቲውተርና የፌስ ቡክ እንዲሆም የኢንተርኔት አገልግሎቶች እንዲቋረጡ የተደረጉ መሆናቸውም ይታወቃል። ወገንተኛነቱ ለሙሰቬኒ መሆኑ የሚነገርለት የምርጫ ቦርድ እስካሁን በተቆጠረው ምርጫ ሙሰቨኒ 60 ከመቶ በማግኘት እየመሩ መሆናቸውን ገልጿል።

 

Ø ደቡብ ሱዳን የርስ በርስ ጦርነት ምክንያት ከተሰደዱ  ዜጎች መካከል የሆኑና እና ማላካል ተባለ ሰፈር ተጠልለው የነበሩ ስደተኞች በእርስ በርስ የጎሳ ልዩነት በፈጠሩት ግጭት 18 መሞታቸውናና  ወደ 40 የሚደርሱ መቁሰላቸው ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ድርጊቱን ያወገዘ መሆኑ ተነግሯል።  ዲንካዎችና ሺሉኮች መሀል የተቀሰቀሰው ግጭት ተስፋፍቶ ዲንካዎችን ከኑዌሮችም ጋር አጋጭቷል ። የጎሳ ልዩነት መዘዙ ብዙ ለመሆኑ የደቡብ ሱዳን ምሳሌነት ያለ ነው ። ስምምነት የተፈጠረና ሰላም የወረደ መሆኑ ቢነገርም  ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ተጻራሪያቸውን ሪያክ ማሻርን ሳይጠብ የሽግርና የአንድነት መንግስት ለመመስረት መነሳታቸው ራሱ ቀውሱን እንደገና ቀስቅሶታል ተብሏል። ጣልቃ ገብ የውጭ ሀይሎች የችግሩን ምስረታ ምንጭ በማድረቅ ፈንታ የእራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ በመጣራቸው ችግሩ የቀረፍ አልሆነም ተብሏል።

 

Ø የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች በሊቢያ የሚገኘውን የአይሲስ የማሰልጠኛ ጣቢያን የደበደቡ መሆኑ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። በአየሩ ድብደባ ከ40 በላይ የሆኑና አብዛኞቹ የቱኒዚያ ዜጎች ናቸው የሚባሉ ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ኑረዲን ቹሴን የተባለውም መሪ ሳይገደል አይቀርም የሚል ግምት ተወስዷል። ኑረዲን ቹሴን ባለፈው ዓመት  ለ30 የእንግሊዝ ተወላጆች መገደል ምክንያት የሆነውንና  በቱኒሲያ የተካሄደውን የሽብር ተግባር የመራ ነው ተብሏል። በሊቢያ የሚገኘው የአይሲስ ቡድን መንቀሳቀስ ከጀመረ አንድ ዓመቱን ያስቆጠረ ሲሆን 6000 የሚሆኑ የታጠቁ ተዋጊዎች እንዳሉት ይገመታል። የቀደሞ አምባገነን መሪ ጋዳፊ ከስልጣን ከተወገዱ ካለፉት አራት አመታት ወዲህ ሊቢያ በቀውስ ላይ የምትገኝ ሲሆን ቀውሱ እንዲፈጠርና እንዲባባስ ያደረጉት ምዕራባውያን ናቸው በሚል አስተያየት የሚሰነዝሩ በርካታ ናቸው።

 

Ø ዛሬ የካቲት 11 ቀን 2008 በሰሜን ካሜሩን ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች የመንገድ ላይ ነጋዴዎች መስለው ቦምቦች አፈንድተው ጉዳት ያደረሱ ሲሆን ሌሎች ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ደግሞ በአንድ ትምህርት ቤት ላይ ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመዋል። ከሁለቱም ቦታዎች ከ20 ሰዎች በላይ ሲገደሉ ከ70 በላይ መቁሰላችውና ወደ ሆስፒታል መወሰዳችው ተሰምቷል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በሰሜን ካሜሩን በተደጋጋሚ ጥቃት መፈጸማቸውና ጉዳት ማድረሳቸው በየጊዜው ተዘግቧል።

 

Ø በግብጽ አንድ የፖሊስ አባል የተራንስፖርት መኪና አሽከርካሪ  የትራንስፖርት ዋጋ በዝቷል በማለት  ሹፌሩን መግደሉን ተከትሎ በቁጣ የተነሳሳው ሕዝብ ፖሊሱን ከመደብድቡ በተጫማሪ መንገድ በመዝጋት ተቃውሞውን የገለጸ መሆኑን ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል። የግብጽ መንግስት የፖሊስ አባሉ የታሰረ መሆኑን መግለጫ ቢሰጥም የሕዝቡ አመጽ ያልበረደ መሆኑ ተነግሯል። የግብጽ ሕዝብ ለወታደሩ አገዛዝ ያለውን ጥላቻ እየገለጸ መሆኑ የሚታይ ሲሆን ባለፈው ሳምንት ውስጥም የሆስፒታል ዶክተሮችና ሰራተኞች ፖሊሶች የአስቸኳይ ጊዜ ህክምና ክፍሎችን ማጥቃታቸውን ተከትሎ ተቃውሞ ማሰማታችው ይታወሳል። የግብጽ ፖሊሶችና ወታድሮች ለሰሩት ጥፋት ተጠያቂ አለመሆናቸውና ለፍርድ አለመቅረባቸው ሕዝቡን እያስመረረው ያለ ክስተት  መሆኑን የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ። 

 

 

 

 

የካቲት 10 ቀን 2008 ዓም

Ø በአንዳንድ አካባቢዎች የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በአርሲ ኮፈሌ መንገድ ተዘግቶ በተካሄደ ከፍተኛ ተቃውሞ አራት ሰዎች መገዳላቸውና በርካቶች ለእስር መዳረጋቸው ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።ዛሬ በምዕራብ አርሲ አዶ ከተማ የአግአዚ ወታደሮች ለሊቱን ቤት ለቤት በመግባት ወጣቶችን እያስወጡ ሲደበደቡ ማደራቸውንና   የታፈሱት ወጣቶች  በመሳሪያ ሰደፍ እየተመቱ ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል። ቤተሰቦቻቸውና የአካባቢው ነዋሪዎች ድርጊቱን በመቃወም ከፍተኛ  የሆነ ጩኸት ከማሰማታቸውም በላይ ድንጋይ በመወርወር ለመከላከል መሞክራቸው ከአካባቢው የመጣው ዜና ጨምሮ ይገልጻል። በተመሳሳይ ዜና  በሀረርጌ ግራዋ ወረዳ ኦሮሚቱ ከተማ አህመድ ከማል በተባለው የከተማዋ አስተዳዳሪ ጥሪ ወደ ኦሮሚቱ ዘልቆ በነበረው ነብሰ ገዳይ ወታደር አደም የተባለ የአስራ ዘጠኝ አመት እድሜ ያለው ወጣት መገደሉን የደረሰን መረጃ አሰረድቷል።   በዛሬው ቀን በተጨማሪ በምዕራብ አርሲ ዋቤ ከተማ በምስራቅ ሀረርጌ ግራዋ ዶጉ እና ቆቦ ከተሞች እንቅስቃሴዎቹ የቀጠሉ ሲሆን በአምቦና በጉደር ከተሞች ወደ መንደሮች የሚያስገቡ መንገዶች መዘጋታቸው ተዘግቧል። በተያያዘ ዜና ለጂቡቲው ፕሬዚዳን ለኦማር ገለህ ተሰጥተው የነበሩ የስሮፍታ እና የጎፈር የመንግስት እርሻዎች በተቃዋሚዎቹ በእሳት መቃጠላቸው አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል።

 

 

Ø ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓ/ም በአርሲ በሲንቂሌ ከተማ አካባቢ ቆርኪዎች በሚገኙበት ብሄራዊ ፓርክ ላይ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በእንስሳቱ ላይ ጉዳት ባያደርስም እሳቱ ሙሉ በሙሉ አሁንም አለመጥፋቱን  ከስፍራው የደረሰበ ዘገባ ያስረዳል።ወያኔ ቃጠሎው የተነሳው የጸረ ሰላም ኃይሎች በለኮሱት እሳት ነው በማለት የሞከረ ሲሆን በእሳቱ ምክንያት በእንስሳት ላይ ጉዳት ባይደርስም ዛፎች መቃጠላቸውና ፓርኩ መጎዳቱን የአይን እማኞች ይናገራሉ።   በከሁለት ወራት በፊት አንድ ቆርኪ መገደሉን ተከትሎ ሀምቢቱና ዳዌ በተባሉ ጎሳዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ የነበረ መሆኑና በአባገዳዎች ከፍተኛ ጥረት ግጭቱን በፈጠሩት መካከል እርቅ እንዲሰፍን ለማድረግ ጥረት ተደርጎ እንደነበር የአካባቢው ሰዎች ይናገራሉ። ከታመኑ ምንጮች ለማወቅ እንደተቻለው ዛሬ የካቲት 10 ቀን 2008 ዓም እና ነገ የካቲት 11 ቀን 2008 ዓም ልዩ የአግአዚ ጦር ወደ ስፍራው ተልኮ ካምፕ ሊመሰረት ታቅዷል ተብሏል።

 

Ø በድርቅ ምክንያት የተጎዱ ዜጎች  የምግብ እርዳታ ማግኘት የሚችሉት በሴፍትኔት ከተደራጁ ብቻ መሆኑን ከትግራይ የመጣ ዘገባ ይገልጻል። በረሃብ የተጎዱ ስድስትና ከዚያ በላይ የቤተሰብ አባላትን በኃላፊነት የሚያስተዳደሩ  አባወራዎች እርዳታ የሚሰጣችሁ  ለአምስት የቤተሰብ አባላት ብቻ ነው እየተባሉ የቤተሰቦቻቸው ቁጥር ከስድስት በላይ የሆኑ ቤተሰቦች እርዳታ መከልከቸውን የተገኘው ዘገባ አስረድቷል። የተሰጠን መመሪያ በሴፍቲ ኔት ለተደራጁ አምስት የቤተሰብ አባሎች ብቻ ነው በማለት በግለስብ አ15 ኪሎ ስንዴና በቢራ ጠርሙስ የተሰፈረ ዘይት ብቻ ለአምስት የቤተስ ሰብ አባላት ብቻ ሲሰጥ ከዚያ በላይ ቁጥር ያላቸው ቤተሰቦች እርካታ ተከልለው ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸውን የራያና አዘቦ ነዋሪዎች በምሬት እየገለጹ ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪም በረሃብ የሚሰቃዩት ዜጎች ውሃ ለማግኘት ሩቅ ስፍራ እንደሚጓዙና ከውጭ እርዳታ ተገኝቷል የተባለውን የህጻናት አልሚ ምግብ የሆነ አይተውት እንደማያውቁ ተናግረዋል። በሌሎች የትግራይ ክፍሎችም ድርቁና ረሃቡ በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋቱና ዜጎች ከፍተኛ ችግር  ላይ መሆናቸው እየተነገረ ሲሆን የተቃዋሚ ኃይሎች ደጋፊዎች ናችሁ በሚል የእርዳታ እህል የሚከለከሉ ዜጎች በርካታ መሆናቸውንም ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።

 

Ø ረቡዕ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓም በቱርክ ዋና ከተማ በአንክራ አንድ መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ወታደሮችን ጭኖ ይጓዝ በነበረ አውቶቡስ አጠገብ በመፈንዳቱ 28 ወታድሮች ሲገደሉ ከ61 በላይ የሚሆኑት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተዘግቧል። ዛሬ ሀሙስ የካቲት 10 ቀን ረፋዱ ላይ ደግሞ በደቡብ የቱርክ ግዛት አንድ ወታደራዊ የማመለሻ መኪና በመንገድ ላይ በተቀበረ ፈንጅ  ተመትቶ ቢያንስ ስድስት ወታድሮች መሞታቸውና ሌሎች መቁሰላቸው ተዘግቧል። የአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በአንካራ ከተማ የፈንዳውን ቦምብ ያጠመደው ሳሊህ ኔካር የሚባል የሶሪያ ተወላጅና የሶሪያ የኩርድ ድርጅት አባል መሆኑን ቢናገሩም በሶሪያ እና በቱርክ የሚገኙ የኩርድ ድርጅቶች አመራር አባላት ለቦምቦቹ መፈንዳት እጃቸው የሌለበት መሆኑን ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ምንም እንኳ በሶርያ እና በቱርክ የሚገኙ የኩርድ ድርጅቶች መሪዎች ለቦምቡ መፈንዳት ኃላፊነት መውስደኡን ቢክዱም ቦምቡን ያፈነዱት ድርጅቶቹ መሆናቸውን የሚያስረዱ ተጨባጭ መረጃዎች ስላሉን እርምጃ እንወስዳለን ብለዋል። የቱርክ መንግስት ፒኬኬ በተባለው የቱርክ ኩርድ ድርጅት ላይም ሆነ ዋይ ፒ ጄ በሚባለው የሶሪያ ኩርድ ድርጅት ላይ እወስደዋለሁ  የሚለው እርምጃ  ችግሮችን ከማቀጣጠል ውጭ የሚያመጣው ውጤት የለም በማለት ያቀጣጥላል የፖሊቲካ ታዛቢዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

 

Ø መሀመድ ካራቲ የተባለው የአልሽባብ የኢንተለጀንስ ኃላፊ ከሌሎች 10 የአልሸባብ ወታደራዊ መሪዎች ጋር በመሆን በኬኒያ የአየር ጥቃት የተገደለ መሆኑን የኬኒያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። በየአይር ጥቃቱ የአልሸባብ አባላት የተገደሉት በጥር  30 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ሶማሊያ ውስጥ ሲሆን በጥቃቱ ሌሎች 40 የሚሆኑ የአልሸባብ አባላት ተገድለዋል ተብሏል። ባለፈው ወር ከ100 በላይ ለሆኑት የኬኒያ ወታደሮች ሞት ምክንያት ለሆነውና  በኬኒያ የጦር ሰፈር ላይ ለተወስደው እርምጃ መሀመድ ካራቲ ቁልፍ ሚና የነበረው  መሆኑን የኬኒያ ባለስልጥኖች ገልጸዋል። አልሸባብ መሀመድ ካራቲ አልሞተም በማለት ዜናውን ያስተባበለ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø ዛሬ በዩጋንዳ በተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ላይ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች መከፈት ከነበረባቸው ስድስት እና ሰባት ሰዓት ዘግየተው እንዲከፍቱ በመደረጉ በርከት ያሉ ወገኖች ቅሬታቸውን መግለጻቸው ታውቋል። ጣቢያዎቹ ዘግየተው በመከፈታቸው የምርጫ ታዛቢዎች ሁኔታው አሳሳቢ ነው ያሉ ሲሆን የፕሬዚዳንቱ ተቃውሚዎች ደግሞ መራጮችን ተስፋ አስቆርጦ ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ ለማድረግ በመንግስት በኩል ሆን ተብሎ የተወስደ የተንኮል እርምጃ ነው ብለውታል። በአንዳንድ አካባቢዎች መራጮች የምርጫ ካርዶች እስከመጡ ድረስ ከሰባት ሰዓታት በላይ ተሰልፈው ሲጠብቁ መዋላቸው ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሙሰቬኒን ሊያሸንፉ ይችላሉ ተብለው የተገመቱት ኪዛ ቤሲግየ ሙሰቨኒን በአምባገነንት የከሰሷቸው ሲሆን ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ ለመሆኑ ጥርጣሬ ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል። በ28 ሺ የምርጫ ጣቢያዎች እ 15 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

 

 

 

 

የካቲት 09 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በምዕራብ አሩሲ በተከሰተው ሕዝባዊ አመጽ ሰባት የአግአዚ ወታደሮች መገደላቸውና በርካታ የወያኔ ንብረት መውደሙን በመግለጽ በትናንትናው ዘገባችን መግለጻችን ይታወሳል። ባለፈው አርብ በምዕራብ አሩሲ አጄ በተባለች ከተማ የተቀሰቀሰው አመጽ ወደ ሻላ ሲራሮና ሻሸመኔ ከተሞች ተዛምቶ በርካታ ጉዳት የደረሰ መሆኑ ተዘግቧል። የሕዝቡን እንቅስቃሴ ለማብረድ የወያኔ አግአዚ ጦር በከፈተው ተኩስ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ዜጎች መሞታቸው የተገመተ ቢሆንም በሻሽመኔ ኩየራ ሆስፒታል ህክምና ሲደረግላቸው ከነበሩት መካከል ቢያንስ አምስት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን በሻሸመኔ የሚገኙ የአይን እማኞች ገልጸዋል። ትናንት የካቲት ስምንት ቀን በሀገረ ማርያም ከተማ በእሳት መጋየቱ እና እንዲሁም በአዶላ ከተማ አንድ የወታደር ካምፕ መቃጠሉን ከስፍራው የሚመጡ ያልተረጋገጡ ዜናዎች ይገልጻሉ። ከሻሽመኔ በተለያዩ አቅጣጭዎች የሚሄዱ መንገዶች ዝግ ሆነው መቆየታቸው እየተሰማ ሲሆን ከከተማው አካባቢ በአካባቢው ያሉ እንደ አዶላ የመሳሰሉ ቦታዎችም የአመጽ እንቅስቃሴ ታይቶባቸዋል።  ከኮፈሌ የሚያስወጡት መንገዶች በተቃዋሚዎች መዘጋታቸው ከሚደርሱ ዘገባዎች ለማወቅ የተቻለ ሲሆን የአግአዚ ጦር ወደ ቦታው እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በዛሬው ቀን  በሰሜንና በምስራቅ ሸዋ በምዕራብ ወለጋ  እና በምስራቅ ሀረርጌ አመጹ እየተስፋፋ መሆኑ እየተነገረ ነው።

 

Ø የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) አመራር አባል አቶ ሀብታሙ አያሌውና መምህር አብረሃም ሰለሞን፣ ማክሰኞ የካቲት 8 ቀን 2008 .. ከእስር የተፈቱ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ባለፈው ሐሙስ የካቲት 3 ቀን 2008 ..የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ አቶ አብረሃ ደስታ፣ አቶ የሺዋስ አሰፋና መምህር አብረሃም ሰለሞን ከእስር እንዲፈቱ፣ መወሰኑን ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወሳል። ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ መሰረት የመፍቻ ትዕዛዝ ለማረሚያ ቤት አስተዳደር መድረሱ የተረጋገጠ ቢሆንም፣ ከእስረኞቹ መካከል ሁለቱ ሲፈቱ ሌሎች እስካሁን ያልተፈቱ መሆናቸው ታውቋል።  

 

Ø ከሚዛን ወደ ቴፒ ሃምሳ ስድስት ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው የቴፒ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ መኪና ድልድይ ውስጥ ገብቶ የአስራ አምስት ሰዎች ህይወት ወዲያወኑ ሲያልፍ 30 የሚሆኑ ከባድ በሆነ ሁኔታ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል። ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ለህክምና ወደ ሀዋሳ ሲወሰዱ የተቀሩት አስር ሰዎች መኪናው የተጫናቸውና በውሃ የተወሰዱ መሆናቸውን ዘገባው አመልክቷል።  በሰርቪሱ ውስጥ የነበሩት ሟቾችና ተጎጂዎች አብዛኞቹ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ማኅበረሰብ አባላት ናቸው።

 

Ø የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ፍራንስዋ ሜክሲኮን ሲገበኙ  በዚያች ሀገር በሚኖሩ ውህዳን ብሄረሰቦች ላይ በቤተ ክርስቲያኗ የተደገፈ ፍጅትና በደል መድረሱን አምነው ሕዝቦቹን ይቅርታ መጠየቃቸው ታውቋል። ለጳጳሱ የይቅርታ ጥያቄ ከፍተኛ አድናቆት የሰጡ ክፍሎች  የካቶሊ ክርስቲያን  ከሙሶሊኒን ተባብራ በኢትዮጵያ ላይ ላደረሰችው በደልና ግድያ እስካሁን ይቅርታ አለመጠየቋ የሚያስወቅሳት ነው ብለዋል። ሰሞኑን የሚከበረውን የአድዋ ድል ታሪክ ለመፋቅ ፋሽስቱ ሙሶሊኒ ወራሪ  ጦሩን ወደ ኢትዮጵያ  ሲልክ በወቅቱ የነበሩት ጳጳስና ቤተክርስቲያኗ በአጠቃላይ ዘመቻው "አህዛብ የሆኑትን አረመኔዎች  ለማሰልጠን የተደረገ ዘመቻ ነው በሚል ሙሉ ድጋፍ በይፋ መስጠታቸው የሚታወስ ነው ። ጣሊያን ባደረገው ወራራ ወደ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አልቀዋል ። የካቶሊክ ቤተክርስያን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ ላለፉት 30 ዓመታት ኢሕአፓ  ለቫቲካን ባለስልጣኖች በተደጋጋሚ ጥያቄ ያቀረበ መሆኑንና  ስካሁም መልስ አለማግኘቱን ድርጅቱ ለፍኖተ ዴሞክራሲ  ሰጠው መግለጫ ገልጿል ።

 

Ø በአባይ ጉዳይ የተነሳ ግብጽ ከጥንት ጀምሮ ለኢትዮጵያ ደግ የማትመኝና ተንኮል ስትሰራ የቆየች ሀገር ብትሆንም በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃና በተለይም በአፍሪካ ቀንድ  ሳውዲ አረቢያ ዋናዋ ጸረ ሰላም ሀገር ሆነ ተገኝታለች ሲሉ የፖለቲካ ማሪዎች አሳስበዋል ።  በአሁኑ ወቅት ሳውዲ አረቢያ በካታር እየታገዘች መሆንዋ የሚታወቅ ሲሆን  ሳውዲ ቃታር  ወደ ኢርትራ ገብተው ጦር ሰፈሮችን በማቋቋም  የመንን ለማጥፋት  ዘመቻ ላይ መሆናቸውን  ከዕይታ ማራቅ አያስፈግም ብለዋል ። አይሲል የተባለውን ሆን አልቃይዳን በመርዳት ዋና የሆነችው ሳውዲ አረቢያ ጸረ ኢትዮጵያ ገንጣይ ሀይሎችን --ወያኔን፤ ኦሮሚያ እስላሚያ፤የኦጋዴን ቡድኖችን-- በቀጥታም ሆነ በሱዳን በኩልም ስትረዳ መቅየትዋን ጠቅሰዋል ። ሳውዲ በጦር ሀይል ወደ ኤርትራ መግባቷ ለኢትዮጵያ በቀላሉ የሚታይ አደጋ አይደለም ሲባል  ግብጽን ባሕር ዳር ያስገባና በአዲስ አበባም መሬት ሊሰጥ የተነሳው ከሃዲው የወያኔ ቡድን ይህን በተመለከተ ይህ ነው የሚባል ተቃውሞ እንዳላሰማም ተጋልጧል ።

 

Ø ብሩንዲ በንግድ ላይ የተሰማሩትን የሞተር ቢስክሌት ታክሲ የከለከለች መሆኑ ከስፍራው ከተገኘ ዜና ማወቅ ተችሏል። በሞተር ቢስክሌት ላይ በመሆን አጥቂዎች የሚያካሄዱት ግድያዎች እየበረከቱ በመምጣታቸው የብሩንዲ ባለስልጣኖች የሞተር ቢስክሌት ታክሲን ለመከልከል የተገደዱ  መሆናቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ በሞተር ቢስኪሌት ላይ የተቀመጡ ሰዎች በወረወሯቸው ሶስት የእጅ ቦምቦች አንድ ሰው ሲሞት ሌሎች ቁጥራችው ያልታወቀ ሰዎች መቁሰላችው ተዘግቧል። የሞተር ቢስኪሊት ታክሲ መከልከሉ በብሩንዲ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር የሚያመጣ ሲሆን በመስኩ በተሰማሩ ዜጎች ላይም የኑሮ ችግር እንደሚፈጥር ታውቋል።

 

Ø የቀድሞ የተባብሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ የነበሩት ግብጻዊው ጴጥሮስ ጴጥሮስ ጋሌ በ93 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በ1985 የተባበሩት መንግስታ ዋና ጸሐፊ ሆነው የተሾሙት ጴጥሮስ ጵጥሮስ ጋሌ በሩዋንዳና በቦስኒያ የደረሰውን እልቂት ለማስቆም የወሰዱት ርምጃ ደካማ ነበር ተብለው የተወቀሱ ሲሆን ኢርትራን ከኢትዮጵያ በማስገንጠል በኩል ቁልፍ ሚና ተጫውተዋ ተብለው በኢትዮጵያውያን መከሰሳቸውም አይዘነጋም። የመጀመሪያውን የስልጣን ዘመም ከአምስት በኋላ ሲጨርሱ በአሜሪካ ተጽእኖ ሌላ የስልጣን ዘመን ያልታደሰላቸውና ከስልጣን የተነሱ መሆናችው ይታወቃል። በተመሳሳይ ዜና የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት የጋማል አብደል ናስር አማካሪ የነበሩትና ለ20 አመታት ጊዜ የግብጹ ታዋቂ ጋዜጣ  የአልአህራም አዘጋጅ የነበሩት መሀመድ ሃይከል ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓም በ92 ዓመታቸው መሞታቸው ተነግሯል። አልአህራም ጋዜጣ በአረቡ አለም ተወዳጅ የነበረ ሲሆን ታዋቂነታቸውም ከጋዜጣው ተወዳጅነት ጋር ተያይዞ የመጣ ነው። ሃይከል በፕሬዝዳንት ናስር የስልጣን ዘመን የፕሬዚዳንቱ አማካሪ ከመሆናችው በተጨማሪ ለአጫጭር ጊዜያትም የማስታወቂያ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

 

 

 

የካቲት 08 ቀን 2008 ዓ.ም. 

Ø ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በምእራብ አሩሲ በተካሄደ የሕዝብ ተቃውሞ ከ7 ያላነሱ የአግአዚ ጦር አባላት የተገደሉ መሆኑን ከአካባቢው የመጣው ዜና ያስረዳል። ባለፈው አርብ ወታደሮች በአንድ አውቶቡስ ተጭነው በሚሄዱ ሰልፈኞች ላይ ተኩሰው ጉዳት ካደረሱ በኋላ በአካባቢው የአመጽ እንቅስቃሴ ሲካሄድ መቆየቱን ተያይዞ የመጣው ዜና ያስረዳል።  በዚሁ ዕለት ከሻሸሜኔ ወደ ተለያዩ አቅጣጫ የሚወስደው መንገድ ለትራፊክ ዝግ ሆኖ እንደነበረና በመኪናዎችና በሌሎች ንብረቶች ላይ የቃጠሎ አደጋ መድረሱን ከአካባቢው የመጣው  ዜና  ጨምሮ ገልጿል።

 

Ø በተያያዘ ዜና ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ በተካሄደው የወያኔ የሰሜን እዝ ስብሰባ ላይ የወያኔ ባለስልጣኖች የአግአዚ ጦር በተለያዩ ቦታዎች ሕዝቡን በማግባባት ቅራኔውን ለማብረድ በቅቷል በማለት ውሸት የተሞላበት ንግግር ያሰሙት ለአግአዚ ጦር አባላት የሞራል ድጋፍ ለመስጠት መሆኑ ታውቋል። እንዲያውም ሳሞራ ዩኑስ የተባለው የጦር አለቃ በሰሜን እዝ ውስጥ የወያኔ አባላት ብቻ ለሆኑ ወታደራዊ አዛዦች ባደረገው ንግግር የወያኔ አግአዚ ጦር የወሰደው ትክክለኛ ርምጃ ትክክለኛና የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጾ ወደፊትም አሸባሪዎችን ለመቆጣጠር ተመሳሳይ እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ያሳሰበ መሆኑን ከታመኑ ምንጮች ከተገኘ ዜና ለማወቅ ተችሏል።

 

 

Ø ወያኔ ደደቢት ጫካ የገባበትን አርባ አንደኛ አመት እንዲያከበሩ በአዲስ አበባ አስሩ ክፍለ ከተሞች ውስጥ የሚገኙ የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች መመሪያ የተላለፈላቸው መሆኑ ታውቋል።  በዓሉን በድምቀት ለማክበር እነዚሁ አባላትና ደጋፊዎች ለበአሉ የሚያፈልጉ ወጭዎችን ከኅብረተሰቡ በመውጮ የሚሸፈንበት መንገድ እንዲያመቻቹ የታዘዙ ሲሆን የፎረሞችና የሊግ አባላት ቤት ለቤት በመዞር ገንዝብ እንዲያሰባስቡ ተነግረዋል ተብሏል። በዕቅዱ መሰረት የሚሰበሰበው ገንዘብ ለበዓሉ አከባበር ከሚወጣው ወጭ በጣም ሊልቅ እንደሚችልና በብዙ ሚሊዮን የሚገመተው ትርግ ገንዘብ የወያኔ ካዝና ውስጥ እንዲገባ ታቅዷል። አዲስ አበባ በተለምዶ ሰንጋተራ ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ የሚገኘው የኢህአዴግ የወጣቶች ፎረም ብቻ ለህወሃት በዓል ስድስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር የሚፈጅ ወጪ ለማውጣት የበጀት ማሳመኛ ንድፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ውስጠ አዋቂዎች ገልጸዋል።

 

Ø የወያኔ አገዛዝ ፕራቬታይዜሽን በሚል ፖሊስ የመንግስትን ሀብት የነበሩትን ተቋሞች ለግል ሀብታሞች የሸጠ ቢሆንም እስካሁን ድረስ በርከት ያለ የሽያጭ ገንዘብ ያላሰባሰበ መሆኑ ታወቀ። ለዚህ ጉዳይ ወያኔ ያቋቋመው ተቋም 34 የሚሆኑ የንግድና የማምረቻ ተቋሞችን በ2.15 ቢሊዮን ብር የሸጠ ሲሆን እስካሁን ያስገባው 8.6 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው። የአልአሙዲው ንብረት የሆነው ሜድሮክ ኩባንያ 1.5 ቢሊዮን ብር ያልከፈለው እዳ ያለበት ሲሆን ይኸው ካጠቃላዩ ውስጥ ስድሳ ከመቶ የሚሆነው መሆኑም ተዘግቧል። የመንግስትን ንብረት ለግል ባለሃብቶች መሸጥ በሚል ሽፋን የወያኔ ባለስልጣኖች በርካታ የሕዝብ ሀብት መዝረፋቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው የሚሉ በርካታ ናችው።

 

Ø ባለፈው እሁድ የካቲት 6 ቀን 2008 ዓም  በእስራኤል አገር ዮሴፍ ሳላምሳ የተባለውንና በኋላ ራሱን ያጠፋውን  ትውልደ ኢትዮጵያዊ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በቁጥጥር ስር እንዲውል ያደረጉትን ሁለት ፖሊሶች የእስራኤል የፍርድ ሚኒስትር ነጻ በማድረጉ በእስራኤል አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ክፉኛ ማዘናቸውን የገለጹ ሲሆን ካሪን ኤላሃራር እና አብራሃም ንጉሴ የተባሉ የእስራኤል የምክር ቤት አባላት በውሳኔው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸው ታወቋል።  ካሪን ኤል ሃራር የተባሉት የምክር ቤት አባል በትውልደ ኢትዮያዊ እስራዔላውያን ላይ ፖሊሶች እየወሰዱ ያሉት አሰቃቂ የኃይል እርምጃ ከፍተኛ ችግር እየሆነው ነው በሚል የተናገሩ ሲሆን  አብርሃም ንጉሴ የተባሉትና ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑት  ሌላው የምክር ቤት አባል ደግሞ በፖሊስ ላይ እምነታችንን አጥናል ብለዋል። በእስራኤል አገር የትውልደ ኢትዮጵያውያን ማህበር ኃላፊ የሆኑት ዚፋ መኮንን ደጉ በአሁኑ ወቅት ከእየአንዳንዱ የትውልደ ኢትዮጵያን ቤተሰብ ቢያንስ አንድ ሰው መታሰሩን ወይም በወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን ገልጸዋል። ዮሴፍ ሳላምሳ የዛሬ ሁለት ዓመት  ስለት ያለው ጩቤ ይዞ ወንጀል ሊፈጽም ነው በሚል ጥርጣሬ ፖሊሶች ከፍተኛ የኤሊክትርክ ኃይል በሰውነት ላይ የሚያሰራጨውን ስተን ጋን (stun gun) የተባለውን መሳራያ በመጠቀም በቁጥጥር ስር አውለውት የነበረ ሲሆን  ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ቢለቀቅም የአይምሮ ጭንቀት ስለደረሰበት ራሱን በራሱ ያጠፋ መሆኑ ይታወቃል። ዮሴፍን በቁጥጥር ስር ያዋሉት ፖሊሶች ባለፈው እሁድ የእስራዔል የፍርድ ሚኒስትር ፖሊሶቹ የፈጸሙት የአሰራር ስህተት ቢኖርም ከመከሰስ ነጻ አድርጓቸዋል።

 

Ø የካሜሩን ልዩ የጸጥታ ኃይሎች በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ የምትገኘውንና ጎሺ (Goshi) የተባለችውን ከተማ ወረው  162 የቦኮሃራም አክራሪዎችን የገደሉ መሆናቸውንና በከተማዋ ውስጥ የነበሩትን የቡድኑን የቦምብ ፋብሪካዎችንና መሳሪያዎችን ከጥቅም ውጭ አድርገው ከተማዋን የተቆጣጠሩ መሆናቸው ታውቋል። ከየካቲት 3 እስከ 6 2008 ዓም በተካሄደ ዘመቻ የካሜሩን ልዩ የጸጥታ ኃይሎች ከተማዋን በቁጥትር ስር ካደረጉ በኋላ ለናይጀሪያ መከላከያ ኃይሎች አስረክበዋል ተብሏል። በዚህ በጋራ ኃይሉ ስም በተደረገ ዘመቻ በቦኮሃራም ቁጥጥር ስር የነበሩ ከ100 የበለጡ የናይጄሪያና የካሜሩን ዜጎች የተለቀቁ ሲሆን ሁለት የካሜሩን ወታደራዊ አዛዦች በመንገድ ላይ የተጠመደ ፈንጅ በመኪና ሲሄዱ የተገደሉ መሆናቸውም ተገልጿል።

 

Ø ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ የተቃዋሚ ደጋፊዎችን ለመበተን ፖሊስ በወሰደው ርምጃ አንድ ሰው የተገደለ መሆኑን የኡጋንዳ የፖሊስ ምንጮች የገለጹ ሲሆን በሚቀጥለው ሐሙስ በሚካሄደው ምርጫ የፖሊስ ኃይሎች ሚና አሳሳቢ ነው አሳሳቢ መሆኑ ጉዳዮ የሚከታተሉ ወገኖች እየገለጹ ይገኛሉ።  ለአጭር ጊዜ ተይዘው የተለቀቁትና በተቃዋሚነት የሚወዳደሩት ሚስተር ቢስግየ የሐሙሱ ምርጫ ነጻና ፍትሓዊ እንደማይሆን ገልጸው ደጋፊዎቻቸው ከባለስልጣኖች እየተሰጡ ያሉትን ህጋዊ ያልሆኑ ትእዛዞች እንዳይቀበሉ ጥሪ አድርገዋል።  ህጋዊ ካልሆኑ ትዕዛዞች መካከል አንደኛው መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች ሲሄዱ የሞባይል ስልክ እንዳይዙ የሚከለክለው ሲሆን ይህ ትእዛዝ የተላለፈው በምርጫው ውስጥ የሚከሰቱ የማጭበርበር ተግባሮች እንዳይጋለጡ ለመከላከል ነው ተብሏል። ዋና ተወዳዳሪ የሆኑት ግለሰብ ሕዝቡ ለውጥ እንደሚፈልግ ግልጽ በሆነና በማያሻማ መንገድ ገልጿል በማለት የተናገሩ ሲሆን ከ30 ዓመት በፊት ወታደራዊ ኃይልን ተጠቅመው ወደስልጣን የመጡት ሙሰቨኒ ደግሞ የአገሪቱን ጸጥታ የሚፈታተን ሁሉ የኃይል ርምጃ ይወሰድበታል በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

 

 

የካቲት 07 ቀን 2008 ዓ.ም. 

Ø በአዲስ አበባ ከተማ አለአግባብ እና አለበቂ ክፍያ በሚደረገው የመሬት ንጥቂያ ነዋሪዎች በከፍተኛ ደረጃ እየተጨነቁና እየተመረሩ መሆናቸውን ከየአካቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይጠቁማሉ።  ቁልፍ የሆኑ የከተማ ቦታዎች ከድሃ ነዋሪው ላይ እየተነጠቁ ለወያኔ ሹመኞችና ደጋፊዎች ማደለቢያ ሲሆን መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን ለመንገድ ማስፋፋያና ለመሳሰሉት ሕዝባዊ ተግባሮች ነዋሪዎች በአነስተኛ ክፍያ መሬታቸውን እንዲለቁ ሲገደዱ  መቆየታቸውም ይታወቃል።  ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ከእግዚአብሄር አብ ቤተክርስትያን ታክሲ ማዞረያ ወደ መብራት ኃይል ያገናኛል የተባለውን መንገድ ለመስራት ዳርና ዳር ያሉ ቤቶች እንዲፈርሱ መደረጉን ተከትሎ  ነዋሪዎች ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገቡ መሆናቸው ታውቋል።   ከማፍረሱ ስራ ጋር በተያያዘ  ዓርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ክልል ውስጥ የሚኖር ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት የሆነና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በአብራሪነት ሲያገለግል የቆየ አንድ ፓይለት የመኖሪያ ቤቱ የሚፈርስ መሆኑ ከአገዛዙ ትዕዛዝ ሲደርሰው ራሱን ማጥፋቱን ለማወቅ ተችሏል።  ሟቹ ለሚፈርሰው ባለአንድ ፎቅ መኖሪያ ቤቱ የማይመጣጠን ካሳ እንደሚከፈለው የተነገረው ቢሆንም ለቤቱ ግንባታ የወጣው ወጪና ይሰጣሃል የተባለው የካሳ ክፍያ የማይገናኝ ሆኖ ስላገኘው  በሁኔታው በማዘንና በመበሳጨት ራሱን ለማጥፋት ተገዷል ተብሏል።  የተባለውን መንገድ ለመስራት ወደ ጎን ሁለት ሜትር ከሰማንያ የነዋሪዎች ቤትና ግቢ እንደሚፈርስ በቤቶቹ ግድግዳዎችና አጥሮች ላይ ከተጻፈው ጽሁፍ ማወቅ ተችሏል።  

 

 

Ø ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማና በአካባቢው ባሉ አንዳንድ አካባቢዎች የነብስ ግድያ ወንጀሎች እየተበራከቱ መሆናቸው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ። ግድያውን የሚፈጽሙት እነማን እንደሆኑ በውል ባይታወቅም የጸጥታ ቁጥጥር ከፍተኛ ነው በሚባሉባቸው አካባቢዎች ግድያዎቹ መብዛታቸው ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል ተብሏል።   ባለፈው ሳምንት በየረር ስድስት ወጣቶች በስለት ተወግተው የተገደሉ ሲሆን ከሟቹ ውስጥ ሁለቱ  ተወግተው የተጣሉበት ቦታ ከአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ መቶ ሜትር በማይሞላ ርቀት ላይ እንደነበር የአይን እማኞች ተናግረዋል።  ለግድያዎቹ የፖሊስ ኃይሎች ዝምታን መምረጣቸው በእነሱ ተባባሪነት የተፈጸመ ወንጀል ሳይሆን የሚል ግምት አሳድሯል።

 

Ø የወያኔው አገዛዝና የሱዳን የማዕከላዊ ባንኮች ኃላፊዎች ባለፈው ሳምንት በሱዳን ዋና ከተማ በካርቱም ላይ ተገናኝተው የሱዳን ፓውንድና የኢትዮጵያ ብር በሱዳንና በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ የግንዛቤ ስምምነት ላይ የደረሱ መሆናቸው ታውቋል። ይህ የግንዛቤ ስምምነት ተግባራዊ የሚሆነው በወያኔ አገዛዝና በሱዳን መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣኖች ከጸደቀ በኋላ ነው የተባለ ሲሆን የሱዳን ባለስልጣኖች የሁለቱ አገር ባንኮች ባንድ ላይ የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲመቻች ጥሪ አድርገዋል። ስምምነት ተግባራዊ ቢሆንም እንኳ በአብዛኛው ሊሰራ የሚችለው በወሰን አካባቢ እንጅ በሌሎች ቦታ እንዳልሆነ ታዛቢዎች ይጠቁማሉ።

 

 

Ø ትናንት የካቲት 6 ቀን 2008 ዓም በአሜሪካ በተደረገው የቦስተን ኦሎምፒክ ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊዎች ሆኑ። የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው እውቋ መሰረት ደፋር የ3000 ሺ ሜትር ሩጫ አሸናፊ የሆነች ሲሆን  ለመሮጥ የፈጀባት ጊዜ 8 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ ከ83 ማይክሮ ሰከንድ ሆኖ ከሁለት ዓመት ወዲህ  በአለም ፈጣን ተብሎ ተሰይሟል።በሴቶች የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ሩጫ  ኢትዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም   4 ደቂቃ ከ1 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ  ሰከንድ በመግባት አንደኛ ከመሆኗ በተጨማሪ ከአለም ከፍተኛውን ነጥብ አስቆጥራለች። ደጀን ገብረ መስቀልም 3ሺህ ሜትር ወንዶች ውድድሩን 7 ደቂቃ 42 ሰከንድ 94 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት አንደኛ ሆኗል። መሰረትናና ዳዊትን ደጀንን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።

 

Ø ለኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ቦታ በሚቀጥለው ሀሙስ በሚደረገው ምርጫ ላይ ተውዳዳሪ ሆነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት ሚስተር ቤሲግየ (Besigye) ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በካምፓላ መሀል ከተማ  ለደጋፊዎችቻቸው የምረጡኝ ቅስቀሳ ለማድረግ በሚዘጋጁበት ወቅት በፕሬዚዳንት ሙሰቨኒ መንግስት የጸጥታ ኃይሎች በድንገት ታስረው የተወሰዱ ሲሆን ደጋፊዎቻቸውም በአስለቃሽ ጋዝ እንዲበታተኑ ተደርጓል። ፓሊሶች ስብሰባውን የበተኑት ተወዳዳሪው ለስብሰባ የተከለከሉ የሕዝብ ቦታዎች ስለተጠቀሙ ነው የሚል ምክንያት ሲሰጡ ተቃዋሚዎች ደግሞ መንግስት ምርጫው በሰላም እንዳይካሄድ የሚያካሂደው አፈና ነው ብለውታል። ከ30 ዓመታት በላይ በስልጣን ላይ ያሉትን የኡጋንዳውን ፕሬዚዳንት  ሙሰቨኔን ለማስወገድ ሰባት ተቃዋሚዎች የሚወዳደሩ ሲሆን የፕሬዚዳንቱ የግል ዶክተር የነበሩት ሚስተር ቤሲግየ ሙሰቨኒን ለማሸነፍ እድል አላቸው ይባላል። ባሁኑ ወቅት በኡጋንዳ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ውጥረት ከፍተኛ ሲሆን  በምርጫው ወቅት ወይም በኋላ በአገሪቱ ውስጥ ሁከት ለፈጥር ይችላል የሚለው ግምት ከፍተኛ ነው።

 

Ø ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በብሩንዲ ታጣቂ ኃይሎች የወረውሩት የእጅ ቦምብ ጉዳት ያደረሰ መሆኑ ተነገረ። በሞተር ቢስኪሌት ላይ ከተቀመጡ ሰዎች በዋና ከተማዋ መህል ቦታ ላይ በተወረወሩ ሶስት  የእጅ ቦምቦች አንድ ህጻን ልጅ ሲሞት  ከ30 በላይ የሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ታውቋል።  ጥቃቱን የፈጸሙት ከየትኛው ወገን እንደሆኑ በውል የሚታወቅ ነገር የለም። መንግስት እንዲህ ዓይነቱን የሽብር ተግባር የሚያሂዱት ተቃዋሚዎች ናቸው ብሎ ሲከስስ ተቃዋሚ ኃይሎችና ሌሎች አካሎች የጅምላ ግድያ በማካሄድ የሚታወቀው የገዥው ፓርቲ የወጣት ድርጅትና ሚሊሺያው ነው በማለት የጥቃቱን ኃላፊነት በመንግስት ክፍሎች ላይ ይለጥፋሉ። ወደ ጠቅላላ የእርስ በርስ ግጭት እየሄደ መሆኑ የሚነገርለት የብሩንዲ ችግር የአሁኑ ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ተወዳዳሪ መሆናቸውን በመቃወም የተጀመረ ሲሆን ለአስር ወራት ያህል የተካሄደው የእርስ በርስ ግጭት በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት ማጥፋቱና ከ230 ሺ ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደጎረቤት አገሮች እንዲሰደዱ ያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስተባባሪነት በሊቢያ የአንድነት መንግስት ለማቋቋም በተደረገው  ስምምነት መሰረት የተዘጋጀውን የመንግስቱን የካቢኔ አባላት ስም ዝርዝር በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው መንግስት ሳይቀበለው ውድቅ ያደረገው የሚታወስ ነው። በትናንትናው ዕለት አዲስ ሌላ የስም ዝርዝር ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ዛሬ ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም ለምክር ቤት የሚቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ቀደም ብሎ ቀርቦ የነበረው 32 አባላት የሚገኙበት ካቤኔ አባላቱ በዝተዋል በሚል በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት አካል ምክር ቤት ውድቅ በማድረጉ በአሁኑ ወቅት 18 አባላት የሚገኝበት ካቢኔ እንዲሆን ተደርጓል። ምክር ቤቱ የቀረበለትን ረቂቅ ሀሳብ ማጽደቁና አለማጽደቁ በዛሬው ምሽት ወይም ነገ ጠዋት ይታወቃል ተብሏል።

 

Ø በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ አለሸባብ በሚቆጣጠረው የጌዶ አካባቢ ውስጥ አንድ የአሜሪካ ሰው አልባ መንኮራኩር (ድሮን) የወደቀ መሆኑን በአካባቢ ያሉ የአይን እማኞች ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ ገልጸዋል። አለሸባብም በራዲዮ ጣቢያው ባስተላለፈው ዜና  ስድስት ሚሳይል የጫነውን የሰው አልባ መንኮራኩር በቁጥጥሩ ስር ያደረገ መሆኑን አሳውቋል። ከአሜሪካ መንግስት በኩል እሳካሁን ስለጉዳዩ የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም የአካባቢው ነዋሪዎች መንኮራኩሩን በዓይናቸው እንዳዩት ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜና የሱማሊያ የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት ግለሰብ መኪና ውስጥ በተጠመደ ፈንጅ መገደላችውን የሶማሊያ ፖሊስ ገልጿል። ከቀድሞ ሚንስትር ጋር የነበሩ ሁለት ሰዎችም በጸና ቆስለዋል ተብሏል። ግለሰቡ የዛሬ ስምንት ዓመት የሶማሊያ የሽግግር መንግስት የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።

 

 

 

 

የካቲት 05 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø የግብጽና የሱዳን ፕሬዚዳንቶች እና የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር  በየካቲት ወር መጨረሻ ላይ ሻርም ኤል ሼክ በተባለው በግብጽ የመዝናኚያ ከተማ ተገናኝተው ስለአባይ ግድብ ሁኔታ እንደሚወያዩ ተገለጸ። ሰሞኑን የሶስቱ አገሮች የውሃና የመስኖ ሚንስትሮች ካርቱም ሱዳን ላይ ተገኛኝተው ግድቡ ስለሚያስከትለው ጉዳት እንዲያጠኑ የተመደቡት ሁለቱ የፈረንሳይ የጥናት ተቋሞች ባቀረቧቸው ረቂቅ ሀሳቦች ውይይትና ድርድር ያካሄዱ ቢሆንም ስምምነቱን ለመፈረም ያልተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸው  በያዝነው  ወር መካከል ላይ እንደገና ለመገናኘት ተስማምተዋል። የጥናቱ ሀሳብ  በመጨው ስብሰባ ላይ በሶስቱም አገሮች ጸድቆ ስምምነት ካገኘ ኩባንያዎቹ ከአንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ የጥናታቸውን ውጤት ማስረከብ ይኖርባቸዋል ተብሏል። በሌላ በኩል የወያኔ የውሃ ሀብት ሚኒስትር ለቢቢሲ የአረቢኛ ክፍል በሰጠው መግለጫ የወያኔ አገዛዝ የአባይን ግድብ ስራ እንደማያቆም ተናግሮ የኤሌክትሪክ ሽያጩን አስመልክቶ ሱዳን እና ግብጽ ቅድሚያ እንደሚያገኙ ገልጿል። ግብጽ የግድቡ ስራ  በኮታ ማግኘት አለብኝ የምትለውን  55.5 ሚሊዮን ኩቢክ ውሃ ይቀንሳል በማለት እየተከራከረች ሲሆን ወያኔ ደግሞ ግድቡ የውሃ መቀነስ አያመጣም ባይ ነው።  

 

Ø ትናንት የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦና በዙሪያዋ የሚገኙ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች ዋና እና ምክትል ርእሳነ መምህራን በተጨማሪም ሱፐርቫይዘሮች የተገኙበት ስብሰባ  በአምቦ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ ውስጥ ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን በቅርቡ የተደረገው አመጽ አንዱ የመነጋገሪያ ርዕስ እንደነበር ታውቋል። በስብሰባው ላይ  በምዕራብ ሸዋ አምቦና አካባቢው በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተነስቶ የነበረው የተማሪዎች ተቃውሞ የመጀመሪያው መንፈቅ ትምህርት ሳይጠናቀቅ መሆኑ ተገልጾ በሁለተኛው መንፈቅ የትምህርት ዘመን እንዳይደገም መምህራን የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ግዴታቸው መሆኑ እንደተነገራቸው ለማወቅ ተችሏል።  ስብሰባውን ሲመሩ የነበሩት የኦህዴድ ካድሬዎች በርካታ መምህራን ከተማሪዎች ጋር አብረው ተቃውሞ ያነሱ እንደነበር ገልጸው ችግሩ በድጋሚ እንዳይነሳ ለመከላከል እነዚህን መምህራን ማጋለጥ ያስፈልጋል የሚል የማስፈራሪያ ቃል ሲናገሩ የተሰሙ መሆናቸውን የመጣው ዘገባ ጨምሮ ገልጿል። ከተማሪዎቹ ጋር ተቃውሞ በማሰማት ተባባሪነታቸው የተጠቆመባቸው መምህራንን ከስራ ከመታገድ ጀምሮ እስከ እስራት ድረስ በሚደርስ ቅጣት ሊቀጡ እንደሚችሉም ተገልጿል። በስብሰባው የተካፈሉት የየትምህርቱ ኃላፊዎች  ቢሮ ሃላፊዎችና ርዕሳነ መምህራን ወደ የመጡበት ትምህርት ቤት ሲመለሱ በተቃውሞው ወቅት የባከነውን ግዜ መምህራን በበጎ ፈቃድ በማግባባት ያለምንም የተጨማሪ ሰዓት ክፍያ ተማሪዎችን እንዲያስተምሩ እንዲያደርጉ የተነገራቸው ሲሆን እምቢ ያሉትንም በማስገደድ እንዲያስፈጽሙ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል ተብሏል።  

 

Ø በተመሳሳይ ዜና በቡራዩ ከተማ በድሪባ ኩማ የተመራ ተመሳሳይ መምህራንን የማስገደድና የማሸማቀቅ ስብሰባ ትናንት የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም መጀመሩን ከስፍራው የመጣ ዘገባ አስረድቷል። በቡራዩና አካባቢዋ የሚገኙ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ርዕሳነ መምህራን በተካፈሉበት በዚሁ ስብሰባ መምህራንና ወላጆች ቀጣዩን ሁለተኛ መንፈቅ የትምህርት ዘመን ያለምንም ተቃውሞ የሚካሄድበትን ሁኔታ መምከር እንደሚገባና በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ መተባበር ያልፈለገ ወላጅም ሆነ መምህር ኪራይ ሰብሳቢ እና የጸረ ሰላም ኃይሎች ተባባሪ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል በማለት አስተያየት እየተሰጠ እንደነበር ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።

 

 

Ø እነ ሀብታሙ አያሌው ትናንት የሰበር ሰሚው ፍርድ ቤት በነፃ የለቀቃቸው ቢሆንም ይህ ዘገባ ተጠናቅሮ እስከመጣበት ዛሬ ቅዳሜ የካቲት አምስት ረፋድ ድረስ እንዳልተለቀቁ ታውቋል። በእነ ዘላለም ወርቅ አገኘሁ የክስ ፤ መዝገብ በሽብር ወንጀል ተከሰው የታሰሩት ሀብታሙ አያሌው፤ አብርሃ ደስታ፤ የሺዋስ አሰፋ፤ ዳንኤል ሺበሺ የሚባሉት የሰማያዊ የአረና እና የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት እና መምህር አብርሃም ሰለሞን ከአንድ አመት ተኩል በላይ በእስር እንዲንገላቱ ተደርጎ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው ነሃሴ 14 ቀን 2007 ዓ/ም ከእስር እንዲፈቱ የወሰነውን ውሳኔ ዓቃቤ ህግ ይግባኝ በማለት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርቦ እንደነበር ዘገባው አስታውሷል። ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ ሳይፈቱ የቀሩት ተከሳሾች ባቀረቡት አቤቱታ ጉዳያቸው ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ ትናንት ዓርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በዳኛ ዳኜ መላኩ ትዕዛዝ በነጻ እንዲሰናበቱ መወሰኑ ቢታወቅም የወህኒ ቤት ምንጮች ውሳኔው የተወሰነው አርብ ቀን  በመሆኑና መጪው ቅዳሜና እሁድ ነው በማለት እስር ቤቱ የሰበር ሰሚውን ፍርድ ቤቱ ውሳኔ  በመጣስ እስረኞቹን ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ለማንገላታት ችሏል።

 

Ø አርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓም የሮማው ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ እና የሩሲያው የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያ ፓትሪያርክ በኩባ ዋና ከተማ በሃቫና አውሮፕላን ማረፊያ ለሁለት ሰዓታት ተገናኝተው ባደረጉት ታሪካዊ ስብሰባ በሁለቱ ቤተ ክርስቲያኖች መካከል አንድነት እንዲፈጠር ጥሪ አስተላልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም በተለይ  በመካከለኛው ምስራቅ በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለውን  ግድያ ሁሉም እንዲከላከል  ጥሪ አድርገዋል። ከ1000 ሺ ዓመት በፊት በአስራንደኛው ክፍለ ዘመን የካቶሊክና እና የኦሮቶዶክስ እምነት ተከተያዮች ከተለያዩ በኋላ በሁለቱ ቤተ ክርስቲያኖች መሪዎች መካከል ግንኙነት ተፈጥሮ ውይይት ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው በመሆኑ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ከስብሰባው በኋላ ሁለቱም ወገኖች በሰጡት መግለጫ ስብሰባው በቅንነትና በግልጽ  የተካሄደ የወንዳማማቾች ስብሰባ ነበር ብለውታል።

 

Ø አርብ የካቲት አራት ቀን ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ በብሩንዲ የገዥው ፓርቲ አባላት  የሆኑ ሁለት ሰዎች በታጠቁ ሰዎች መገደላችውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ በአንዲት ከተማ ውስጥ ገብተው ነዋሪዎችን እንዲወጡ ካደረጉ በኋላ ከመካከላቸው በቅርቡ የገዥው ፓርቲ አባል በመሆን የተመደበውንና  አካባቢውን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠውን ግለሰብና  የገዥው ፓርቲ የወጣት ሊግ አባል የሆነውን ግለሰብ መርጠው በማውጣት ረሽነዋቸው የሄዱ መሆናቸው ተሰምቷል። የገዥው ፓርቲ የወጣት ሊግ የተባለው ተቋም እንደሚሊሺያ በመታጠቅ በርካታ ተቃዋሚዎችን የገደለ መሆኑ ይታወቃል። ለተወሰነ ጊዜ ጸጥታ ነግሶበት የነበረችው ብሩንዲ ሁከት እንደገና እያገረሸበት መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ።

 

Ø ትናንት አርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓም በካይሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ዶክተሮች በፖሊሶች የሚካሄደውን የአፈና ተግባር ተቃውመው ድምጻቸውን ያሰሙ መሆናችው ታወቀ። ከአስራ አምስት ቀናት በፊት ማታረያ በሚባለው በሰሜናዊ ካይሮ በሚገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን ሆስፒታል በመውረር ፖሊሶች ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን ሁለት ዶክተሮችንም በጽኑ የደበደቡ መሆናቸው ተነግሯል። የአቃቤ ህጉ ቢሮ ድበደባውን ፈጽመዋል የተባሉትን 9 የፖሊስ አባላት መጀመሪያ አስሯቸው የነበረ ቢሆንም ሐሙስ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም  ካለምንም ማብራሪያ  የለቀቃቸው መሆኑ ተዘግቧል። ስራቸውን በሚገባ እያከናውኑ በነበሩት ዶክተሮች ላይ የጸጥታ ኃይሎች ድብደባ ማካሄዳቸው አግባብ አለመሆኑን በመግለጽና ፖሊሶቹ ታስረው ፍርዳቸውን እንዲቀበሉ በመጠየቅ ዶክተሮቹ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል።

 

 

 

 

የካቲት 04 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በአባይ ግድብ ላይ ለመነጋገር በካርታሙ ሱዳን ተሰብስበው የነበሩት የግብጽ የሱዳንና የወያኔ የውሃና የመስኖ ሚኒስትሮች  ስለ ግድቡ ጥናት  የቴክኒክ ጉዳይና ለጥናቱ ስለሚከፈለው ገንዘብ በሰፊው የተውያዩና እያንዳንዳቸው ያላችውን አቋም የተለዋወጡ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ስምምነት ላይ ባለመድረሳቸው ድርድሩን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ  አዲስ አበባ ላይ ለመቀጠል መስማማታችውን ኢጅፕት ኢንዲፔንደንት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ ከስብሰባው አካባቢ ያገኘውን ዜና ዋቢ አድርጎ ሐሙስ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም ባሰፈረው ዘገባ ገልጿል። በአዲስ አበባው ጉባኤ ድርድሩ  በቴክኒክ ጉዳይና በገንዘብ አከፋፈሉ ድርድሩ የሚቀጥል መሆኑና ስምምነት ከተደረገ  አርተሊያና ቢአር ኤል የተባሉት ሁለቱ የአጥኚ ኩባንያዎች ስራቸውን እንዲጀምሩ ኮርቴል የተባለው የእንግሊዙ ኩባንያ ኮንትራቱን እንዲያዘጋጅ ይነገረዋል ተብሏል።

 

 

Ø በጉጂ አካባቢ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ  አባሎቹና የቅርንጫፍ ቢሮ አመራሮች የታሰሩበት መሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ  አዲስ አበባ ውስጥ ካዛንቺስ ከሚገኘው ቢሮው መግለጫ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። በጉጂ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ቤት ለቤት ታድነው በፖሊስ ከተወሰዱ በኋላ እስካሁን ድረስ ክስ ያልተመሰረተብቸው መሆኑን ፓርቲው ጨምሮ ገልጿል።  በጉጂ የአላሙዲን ወርቅ ቁፋሮ ስራ  እንዲቆም የሚጠይቅ ሕዝባዊ ተቃውሞ አንዱና ዋናው ስለነበር አዲስ አበባ ውስጥ የአላሙዲን ድርጅቶችን በጥምረት የሚመራው የእነ ዶክተር አረጋ  ቡድን ተሰብስቦ የወያኔ ባለስልጣኖች በጉዳዩ ላይ መፍትሄ እንዲሰጡ  ጥያቄ ቢያቀርብም በተፋፋመው ሕዝባዊ ቁጣ ሳቢያ ቁፋሮው ለግዜው መቆሙ ይነገራል። በወያኔ እና በደጋፊዎቹ አማካኝነት እየተወሰደ ያለው የሀብት ዘረፋው ይብቃ የሚለው ጥያቄ የጉጂ ብቻ  ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያዊ መሆኑን በተለያየ ግዜ   ዜጎች አንሰተው የታገሉ መሆናቸው ይታወሳል።      

 

 

Ø በአፋር ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ እየተደረገ ያለው ግምገማ  ባለስልጣኖችን ሊያግባባ ሳይችል በመቅረቱ የወያኔ ሹሙ  ካሳ ተክለ ብርሃን ስብሰባውን እንዲመራ መደረጉን  ከሰመራ የመጣው ዘገባ ገልጧል። የእስማኤል አሊ ሴሮን ወንበር የያዘው ስዩም አወል የተባለው የወያኔ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ስብሰባውን እንዲመራ ታቅዶ የነበረ ቢሆን ባለስልጣኖቹ  እርስ በእርሱ ውዝግብ ውስጥ በመግባታቸው ምክንያት ተግባራዊ ሳይሆን ቀርቷል።በአፋር ባለስልጣኖችን ያወዛገበው የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጩ የእከክልኝ ልከክልህ የሆነ የመዋቅር ችግር በመኖሩ ነው በማለት ዘገባው አስረድቷል።  በአፋር ለተከሰተው ድርቅ ዘላቂ መፍትሄው አርብቶ አደሩን ካለበት አፈናቅሎ ወደሌላ አካባቢ መውሰድ ነው የሚለው እቅድ  የአመለካከት ችግር አለበት ከሚለው ቡድን ጋር መግባባት መግባባት ሊደረስ ባለመቻሉ ስብሰባውን ለማድረግ ሳይቻል ቀርቶ በካሳ ተክለብርሃን በሌሎች የወያኔ ባለስልጣኖች አማካይነት ስብስበው እንዲመራ ተድረጓል።       

 

Ø በሩዋንዳ የሚገኙትንና ከሰባ ሺ በላይ የሚቆጠሩትን የብሩንዲ ስደተኞች ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እቅድ እንዳለ የሩዋንዳ ባለስልጣኖች ገለጹ። ስደተኞች ወዴትኛው አገር እና በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚጓጓዙ በባለስልጣኖቹ ባይገለጽም እቅዱ ባስቸኳይ እንደሚጀመር ተነግሯል። ሩዋንዳ የብሩንዲን መንግስት ተቃዋሚዎች በአገሯ ላይ በወታደራዊ ትምህርት ታሰልጥናለች መሳሪያ ታስታጥቃለች የሚሉ ክሶች የተመድ  የውይይት መድረክ አባላትና እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣኖች መክሰሳቸው ይታወቃል። ከሁለት ቀናት በፊት የሩዋንዳው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስደተኞችን ማባረር አንችልም በማለት የተናገሩት ቃል ተቀልብሶ በአሁኑ ወቅት ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እቅድ ያለ መሆኑ መገለጹ ሩዋንዳ ከተመድ እና ከአሜሪካ ከፍተኛ ተጽእኖ የደረሰባት መሆኑን ያሳያል ሲሉ ታዛባዎች ይተቸሉ። የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ጽሕፈት ቤት እስካሁን ስለጉዳዩ የሰጠው መግለጫ የለም።

 

Ø 12 ከፍተኛ መኮንኖች የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ጥርሬ የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የገንዘብ ወንጀል ኮሚሽን ለሚባለው ጸረ ሙስና ተቋም የተላለፉ መሆናቸውን  የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም አስታወቀ። ከፍተኛ መኮንኖቹ በስም ባይጠቀሱም ስድስቱ የጄኔራል ማዕራግ ያላቸው መሆኑ ታውቋል። ኮሚሽኑ በምርመራ መኮንኖች የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ካረጋገጠ ጉዳያቸው በወታደራዊ ፍርድ ቤት እንደሚታይ ተገልጿል። ባለፈው ዓመት በፕሬዚዳንቱ የተሰየመ አጣሪ ኮሚቴ ባደረገው ምርመራ በተጭበረበረና በሀሰት የመሳሪያ ግዥ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ የአገሪቱ ሀብት መዘረፉን የደረሰበት መሆኑ ተገልጿል። የቀድሞ የፕሬዚዳንት የጸጥታ አማካሪ ሚስተር ዳሱኪ ባለፈው  ታኅሣሥ ወር 2008 ዓም  68 ሚሊዮን ዶላር ዘርፈዋል ተብለው መከሰሳቸው ይታወሳል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሚስተር ጆናታን የቅርብ ረዳቶች የሆኑ በርካታ ስዎች በሙስና ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቅሷል።  

 

Ø በሰሜናዊ ማሊ አንድ መኪና ላይ በተጠመደ ፈንጅ ቢያንስ ሶስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። እስካሁን ድረስ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም የእስላማውያን ታጣቂዎች ናቸው የሚል ጥርጣሬ አለ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከ2004 ዓም ጀምሮ በማሊ የጸጥታ ማስከበር ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል።

 

Ø ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳን ከሳልቫ ኬር የካቲት 3 ቀን 2008 በተላለፈ አዋጅ የተቃዋሚው መሪ ሪክ ማቻር የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው በይፋ ተገልጿል። ሪክ ማቻር የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቦታቸውን እንደገና ለማግኘት የቻሉት ባለፈው ዓመት በተደረገው ስምምነት መሰረት ሲሆን ሐሙስ ዕለት የተላለፈው አዋጅ ስምምነቱን በተግባር ያዋለ በመሆኑ ለሰላም አንድ ተስፋ ነው የሚል አስተያየት ተሰጥቷል። ይሁን እንጅ በተልያዩ ቦታዎች አሁንም ጦርነቱ የቀጠለ መሆኑ ሰላም ለመመጣቱ የሚጠራጠሩ በርካታ ናችው። ሪክ ማቻር ከአዲስ አበባ ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ በአዋጁ የተነገረውን በደስታ የሚቀበሉት መሆናቸውን ገልጸው  ስምምነቱ በስራ እየዋለ መሆኑ ይጠቁማል ብለዋል። ሪካ ማቻር ወደ ጁባ መች እንደሚሄዱና ከመሄዳችው በፊት ምን አይነት አስተማማኝ የጸጥታ ሁኔታ መዘጋጀት እንዳለበት እስካሁን በግልጽ አልተነገረውም ። በየቦታው ጦርነቱ እስከቀጠለ ድረስና የሳልቫ ኬር  መንግስት የስምምነቱ መሰረት የሆነውን የአስተዳድር ክልሎችን መልክ ቀይሮ አዳዲስ የአስተዳደር ክልሎች በመፍጠሩ ጦርነቱ ሊያበርድና ሰላም ሊገኝ አይችልም የሚሉ በርካታ ናቸው።

 

Ø ሐሙስ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም የካሜሩን ወታደሮች ወደ ናይጄሪያ ግዛት ዘልቀው በመግባት ባካሄዱት ወታደራዊ ዘመቻ 27 የቦኮሃራም ታጣቂዎች የገደሉ መሆናቸውን አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን ገልጿል። ጎሺ በምትባለው የናይጄሪያ ግዛት ላይ በተደረገው ዘመቻ አንድ የካሜሩን ወታድር የሞተ ሲሆን ሰባት ወታድሮች የቆሰሉ መሆናችውም ተገልጿል። ባለፈው ረቡዕ የቦኮሃራም አጥፍቶ ጠፊዎች  በሰሜን ካሜሩን ባፈነዱት ቦምብ 10 ሰዎች መገደላቸውና ከ 40 በላይ መቁሰላቸው ይታወሳል። ከታኅሣሥ 2007 ዓም ጀምሮ  ቦኮሃራምና ለማጥቃት የአካባቢው አገሮች ጥምር ኃይል መቋቋሙ የሚታወስ ሲሆን በአክራሪው ኃይል ላይ በርካታ ወታደራዊ ዘመቻዎች መደረጋቸው ይታወሳል። የቦኮሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረ ካለፈው ስድስት ዓመታት ጀመሮ ከ 20 ሺ ሰዎች በላይ የተገደሉ ሲሆን 2.5 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ  መሆኑ ይነገራል።

 

 

የካቲት 3 ቀን 2008 ዓ.ም.

 

Ø በወሎ ክፍለሀገር  የሚገኘው የሎጎ ሃይቅ ቀደም ሲል ከነበረው ይዞታው በአንድ አመት ውስጥ በ36 ሜትር ርዝመት መሸሹና ዙሪያውን ምንነቱ ባልታወቀ አዲስ መጤ አረም የተጠቃ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች እየተናገሩ መሆናቸው ተዘገበ። በእርሻ ላይ ኑሯቸውን የመሰረቱ በአካባቢው የሚኖሩ አርሶ አደሮች የሎጎ ሃይቅን ለመስኖ እርሻ ሲጠቀሙ መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት  ውሃው በከፍተኛ ደረጃ በመጉደሉ በሃይቁ ውስጥ ይገኙ የነበሩት የቆሮሶና የአምባዛ  አሳ ዝርያዎች እየጠፉ መሆናቸው ይመሰክራሉ።  የሎጎ ሃይቅ ዙሪያውን ከ28 ሺህ ስኩዌር በላይ የነበረው ሲሆን በአንድ አመት ወደ 22 ሺህ ስኩዌር ስፋት በመጥበቡ ጉዳዩ አሳሳቢ መሆኑ ታውቋል። ስለአሳ ዝርያ መጥፋት ስለሃይቁ መትነንና በመስኖ  አርሶ አደሮች ውሃው እንዲወጣ ማድረጋቸውን ጨምሮ በሃይቁ ዳርቻ በወረርሽኝ መልክ የተከሰተው አዲስ መጤ አረም አሳሳቢ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለወያኔ ጉዳይ አስፈጸሚዎች ለብአዴን ሹማምንቶች ቢያሳውቁም ጥበቃ ለማድረግም ሆነ መፍትሄ ለመሻት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የሎጎ ሃይቅ ለመድረቅ ግስጋሴ የጀመረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።  

 

 

Ø ከየካቲት 10 ቀን 2008 ዓ/ም አንስቶ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች  ስለይዞታቸው ዳግም ማረጋገጫ እንዲወሰዱ ሊታዘዝ መሆኑን ለድሪባ ኩማ ቢሮ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አጋልጠዋል። ከድሪባ ኩማ ቢሮ በተዘጋጀ ትዕዛዝ በአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተሞች ውስጥ የሚገኙ የመሬት አስተዳደር ኤጀንሲዎች አማካኝነት ነዋሪዎች በአዲስ መልክ የይዞታ ማረጋገጫ እንዲወስዱ ይህን ካላደረጉ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንዲያሳውቁ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል። ቀደም ሲል የይዞታ ማረጋገጫቸውን የወሰዱና ካርታ በእጃቸው ላይ የሚገኝ ነዋሪዎችን ጨምሮ ይህ ዳግም ማረጋገጫ ለምን እንዳስፈለገ ለግዜው የታወቀ ነገር የለም። በአዲስ አበባ ነዋሪዎች እያፈናቀለ ወደ ዳር አገር እንዲሰደዱ በማድረግ መሬታቸውን በሊዝ የሚቸበችበው ወያኔ  ቀደም ሲል ካርታ ያልወሰዱትን ሰባ አምስት ካሬ ብቻ ይዞታቸው እንዲሆን በማድረግ ቀሪውን በካሬ ሜት አራት ሺህ ብር በሚጠጋ ክፍያ በማስከፈል ነዋሪዎችን ለማስለቀስ የራሱን ኪስ በረብጣ ሊሞላ መሰናዳቱን መዘገባችን ይታወሳል።

 

በተያያዘ  ዜና የመሬት ይዞታቸው ተረጋግጦላቸው  የአፈር ግብር እየከፈሉ የነበሩ ዜጎች በድጋሚ ማረጋገጫ  ማግኘት እንዲችሉ የአየር ላይ ካርታ ይነሳል በሚል ነዋሪውን እያመሱት መሆኑን ከባህርዳር የመጣ ዘገባ አስረድቷል።

 

 

Ø ባለፈው ማክሰኞ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በቦርኖ ግዛት ዲክዋ ከሚባለው የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ሁለት የሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 56 ሰዎች መሞታቸውንና ሌሎች መቁሰላቸው ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። አጥፍቶ ጠፊዎቹ ቦምቡን ያፈነዱት በካምፑ ውስጥ የተጠለሉት ስደተኞች ለምግብ ተሰልፈው በነበረበት ወቅት ሲሆን ተጎጅዎቹ በብዛት ሴቶችና ህጽናት መሆናቸው ተገልጿል። ቦምብ ታጥቀው ለማፈንዳት የመጡት ሴቶች ሶስት የነበሩ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንደኛዋ ወላጆቿ በካምፕ ውስጥ መኖራቸውን ስትረዳ ቦምቡን ከማፈንዳት ተቆጥባ እጇን ካምፑን ለሚጠብቁ የጸጥታ አባላት ሰጥታለች። ካምፑ  ከልዩ ልዮ ቦታዎች ተሰደው የመጡ ከ50 ሰዎች በላይ ያሉበት ሲሆን አብዛኞቹ ሴቶችና ሕጻናት መሆናቸው ተረጋግጧል። የናይጄሪያ ባለስልጣኖች የካምፑ የጥበቃ ሁኔታ እንዲጠናከር መመሪያ የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። ድርጊቱን የፈጸመው ቦኮሃራም መሆኑ የተገመተ ሲሆን ቡድኑ ባለፉት ስምንት ዓመታት በካሄዳቸው የሽብር ጥቃቶች ከ20 ሺ ሰዎች በላይ መገደላቸውና ከ2 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ይታወቃል።

በተያያዘ ዜና ለቦኮ ሃራም በርከት ያሉት የጦር መሳሪያና ጥይቶች  ሲያስተላልፉ የነበሩ ሁለት የናይጀሪያ ወታደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ ገልጿል። ሁለቱ ወታደሮች በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ውስጥ ተመድበው በፈንጅ ስራ ላይ ተመድበው ይሰሩ የነበሩ ሲሆን ከመሳሪያ ማስተላለፍ በተጨማሪ የቦኮሃራምን ታጣቂዎች የቦምብ የማምረት ስራ ሲያስተምሯቸው ቆይተዋል የሚል ጥርጣሬ ፈጥሯል። ቦኮ ሃራም የናይጄሪያን ወታደራዊ ተቋም ስርጎ የገባ መሆኑ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ተነግሯል።

 

Ø የተባበሩት መንግስት ድርጅት አንድ የፎረንሲክ ኤክስፕርቶች ቡድን ወደ ብሩንዲ ለመላክ ያቀደ መሆኑን የድርጅቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ረቡዕ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም ባደረጉት መግለጫ ገልጸዋል። ቡድኑ ምርመራ የሚያካሄደው ባለፈው ታኅሣሥ ወር በመንግስት ኃይሎች  በግፍ ተረሽነው ከተገደሉ በኋላ በተለያዩ ቦታዎች በጅምላ ተቀብረዋል  የተባሉትን ከ100 በላይ የሆኑ ሰዎችን አስከሬን ለመመርመርና ማንነታቸውን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት እርዳታ ለመስጠት ነው። የተመድ ባለስልጣን በሰጡት መግለጫ  የብሩንዲ ዜጋ የሆነ አቃቢ ህግ ክስ ለማቅርብ ምርመራ የጀመረ መሆኑ ገልጸው የተመድ ቡድን በቦታው በመገኘት የፎርንሲክ አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።  በተያያዘ ዜና ሩዋንዳ ለብሩንዲ መንግስት ተቃዋሚዎች በስደተኞች ጣቢያ  ወታደራዊ ስልጠና መስጠቷን አስመልክቶ አንዳንድ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ድርጊቱን ማውገዝ መጀመራቸው  ተነግሯል። ሁለት ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣኖች በትንናንትናው ዕለት በአሜሪካው ምክር ቤት ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ላይ ቀርበው በሰጡት የምስክርነት ቃል ሩዋንዳ የብሩንዲን ተቃዋሚዎች ወታደራዊ ስልጠና መስጠቷ ተጨባጭ መረጃ ያላቸው መሆኑ ገልጸው ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባል ብለዋል። የአሜሪካ የቅርብ ወዳጅ የሆነው የካጋሚ መንግስት በባለስልጣኖች በይፋ ሲወቀስ ይህ የመጀመሪያው በመሆኑ ብዙዎችን አስገርሟል። 

 

Ø የቀድሞ የቱኒዚያ ፕሬዚዳንት ቢን አሊ የአገሪቱን ንብረት በመዝረፍ በግል አከማችተውት ከነበረው ንብረት ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና የገባ መሆኑን አንድ የቱኒዚያ ሚኒስትር ረቡዕ የካቲት 03 ቀን 2008 ዓም የተናገሩ መሆኑ ታውቋል። የዛሬ አመስት አመት በቱኒዚያ በተነሳው ሕዝባዊ አመጽ ምክንያት ፕሬዚዳንት ቢን አሊ አገር ጥለው ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሲሰደዱ  የቢን አሊና የተባባሪዎቻቸው ንብረት የሆኑ የንግድ ተቋሞች፤ ህንጻዎች የቅንጦት መኪናዎች ወርቅና አልማዝ እንዲሁም ሌሎች ጌጣጌጦች የተወረሱ መሆናቸው ይታወቃል። ባለፉት አምስት አመታት አብዛኞች ንብረቶች ተሸጠው ከግማሽ ቢሊዮን ዶላር በላይ ወደ መንግስት ካዝና የገባ መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት ያልተሸጡ በርካታ ንብረቶች ያሉ መሆናችውን ሚኒስትሩ ገልጸው  ባጭር ጊዜ ውስጥ ለመሸጥ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።

 

 

 

 

 

የካቲት 2 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚገኘውና ህጻናትን እናድን (ሴቭ ዘ ቺልድረን) የተባለው ተቋም ትናንት የካቲት 1 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት  በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ 245 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ካልተገኘ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የረሃቡ ሁኔታ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ሊወድቅ እንደሚችል  አስታውቋል። በአሁኑ ወቅት በምግብ እጥረት የተጠቁ ከ400 ሺ በላይ የሆኑ ህጻናት  ተጨማሪ አልሚ ምግቦች የሚያስፈልጋቸው መሆኑንና ባጠቃላይ 1.7 ሚሊዮን የሚሆኑ ሴቶችና ህጽናት በከፍተኛ የምግብ  እጥረት ሊጠቁ እንደሚችሉ ገልጿል። የድርጅቱ የኢትዮጵያ ቅርጫፍ ዋና ዲሬክተር በጉዳዩ ላይ ተጫማሪ ማብራሪያ ሲሰጡ ከረጅዎች የተባለው እርዳታ ካልመጣ አሁን ያለው የምግብ ክምችት በሚቀጥለው ሚያዚያ ወር ላይ ሊገባደድ የሚችል መሆኑን ገልጸው ከግንቦት በኋላ ባሉት ወራት ከፍተኛ ችግር ሊከሰት እንደሚችል  ተናግረዋል። እህሉ ከውጭ ተሸምቶ ወደ አገር ውስጥ እስኪገባ ድረስ የሶስትና የአራት ወራት ጊዜ ስለሚያስፈልግ በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት የተጠቀሰውን እርዳታ ማግኘት ወሳኝ ነው ብለዋል።  በደቡብ ኢትዮጵያ ብቻ ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በረሃቡ የተጠቁ መሆናቸውን አንዳንድ ምንጮች የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ አስቸኳይ እርዳታ እየተሰጣችው የሚገኙት ዜጎች ብዛት 10.2 ሚሊዮን ደርሷል ተብሏል። ባጠቃላይ በዚህ ዓመት የድርቁና የረሃቡን ችግር ለመቋቋም 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል የተባለ ሲሆን እስካሁን በእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተሰበበው 680 ዶላር ብቻ መሆኑ ተዘግቧል።

 

Ø ካርቱም ሱዳን ላይ ተሰብሰበው የሚገኙት የግብጽ የሱዳንና የወያኔ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የአባይ ግድብን አስመልክቶ የፈረንሳዩ አጥኝ ኩባንያ ባቀረበው የጥናት ሀሳብ ላይ ያላቸውን አቋሞች ተለዋውጠው ትናንት ማክሰኞ የካቲት 1 ቀን 2008 ዓም ስምምነት ላይ መድረሳችው ታውቋል። አርቲሊያ እና ቢ አር ኤል የተባሉት የፈረንሳይ አጥኝ ተቋሞች ጥናት የሚያተኩረው ግድቡ ወደ ሱዳንና ወደ ግብጽ የሚፈሰውን የውሃ መጠን ሊቀንስ መቻሉንና አለመቻሉን እንዲሁም በግድቡ ምክንያት በአካባቢው የእጽዋት ሁኔታ ለውጥ ሊመጣ የሚችል መሆኑንና አለመሆኑን ነው። በስብሰባው ላይ ኩባንያዎቹ ለስራቸው የሚያስከፍሉትን የገንዘብ መጠን የያዘ ኢንቮሎብ በይፋ በሶስቱም አገሮች መልክተኞች የተከፈተ መሆኑ ተገልጿል። ለጥናቱ የሚደረገውን ወጭ ሶስቱም አገሮች በእኩል ደረጃ እንደሚያዋጡ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም የሶስቱ አገሮች የመስኖና የውሃ ሀብት ሚኒስትሮች በሚገኙበት ስምምነቱ በይፋ ይፈረማል ተብሏል። ግብጽ በግድቡ ምክንያት ወደ አገሯ ከሚፈሰው ውሃ 55፣5 ቢሊዮን ኪውቢክ ሜትር ይቀንሳል የሚል ስጋት የፈጠረባት ሲሆን የወያኔ አገዛዝ ግድቡ ምንም ዓይነት የውሃ መቀነስ እንደማያመጣ ተናግሯል።

 

Ø በኩዌት አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ የአስሪዋ ልጅ የነረችውን የ23 ዓመት ወጣት በስለት ከገደለቻት በኋላ የገዛ ህይወቷን  ራሷን ወግታ በጽኑ ያቆሰለች መሆኑ ታውቋል። ኢትዮጵያውያቷ የቤት ሰራተኛ ይህን ድርጊት ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ያልታወቀ ሲሆን ለጊዜው ወደ ሆስፒታል የተወሰደች መሆኑ ታውቋል። በአረብ አገር ለግርድና እየተሸጡ በሚሄዱ ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ በደልና ጭካኔ የተመላበት ድርጊት በአሰሪዎቻቸው መፈጸሙ በተደጋጋሚ የተነገረ ሲሆን ይህችን ኢትዮጵያዊት ወደ ዚህ ድርጊት ሊገፋፋት የቻለው የተፈጸመባት በደል ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ በርካታ ናቸው። ራሷን ያቆሰለችው በጽኑ በመሆኑ በህይወት ልትተርፍ መቻሏና አለመቻሏ አልተረጋገጠም።

 

 

Ø በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በፍስሃ ገነት ከተማ ውስጥ በሚገኙ ስድስት  የጤና ጣቢያዎች ተቀጥረው በመስራት ላይ የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች የትርፍ ጊዜ ክፍያ አይሰጠንም በሚል ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑ ታወቀ። በዲፕሎም ዘርፍ የትርፍ ግዜ ክፍያ አርባ ስምንት ብር በዲግሪ ዘርፍ የትርፍ ግዜ ክፍያ ስድሳ ሁለት ብር እንዲከፈል በህግ የተቀመጠ ቢሆንም የወረዳ አመራሮች ሊከፍሉን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል በማለት ምሬታቸውን በይፋ ሲገልጹ የተሰሙ መሆኑ ታውቋል።   ለጤና ባለሞያዎች የትርፍ ግዜ ክፍያ እንዲሆን ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ለኮቸሬ ወረዳ የተመደበ ቢሆንም ክፍያው ያልተፈጸመ ከመሆኑ በላይ በጀቱ ተመላሽ ሳይደረግ የገባበት ሳይታወቅ የቀረ መሆኑን ጉዳዩን የሚያውቁት ዜጎች ገልጸዋል።

 

 

Ø በየመን በሁቲ አማጽያን የሚደገፈው የየመን ጦር በሳኡዲ አረቢያ ደቡብ ምዕራብ በአሲር ክፍለ ሀገር ውስጥ ከሳኡዲ ወታደሮች ጋር ከባድ ውጊያ አካሄዶ አልራቦህ የተባለውን የሳኡዲ አረቢያ ከተማ እና በአካባቢው ያሉትን መንደሮች  በቁጥጥሩ ስር ማድረጉን ገለጿል። የሳኡዲ ጦር በአውሮፕላንና በሌሎች ከባድ መሳሪያዎች ቢረዳም በጦርነት ከባድ ጉዳት ደርሶበት  መሳሪውያውን እየጣለ የሸሸ መሆኑን ዘገባው ገልጿል። ዘገባው በሌላ በሶስተኛ ወገን ማረጋገጫ አላገኘም። በሌላ በኩል ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በየመን ዋና ከተማ በሳንአ በሳኡዲ የሚመራው የጥምር ኃይል ባደረገው የአየር ጥቃት የአንድ ቤተ ሰብ አባል የሆኑ አምስት ሰዎች መገደላቸው ታውቋል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በማሊ ሞፕቲ በተባለው ግዛት ሲጓዙበት የነበረው መኪና በመንገድ ላይ በተጠመደ ፈንጅ በመመታቱ ሶስት ወታደሮች መገደላቸውና ሌሎች መቁሰላችው የማሊ የመከላከያ ሚኒስቴር ከሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪም ትናንት የካቲት 1 ቀን 2008 ዓም ደግሞ ከቡርኪና ፋሶ አዋሳኝ ላይ ባለችው ሞንዶሮ በተባለችው ቦታ በፈነዳ ቦምብ ሌሎች ሁለት ወታደሮች መቁሰላቸውን የመከላከያ ሚኒስቴሩ ገልጿል። ለእነዚህ የተለያዩ ጥቃቶች እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም የማሲና  ነጻ አውጭ ድርጅት የሚባለው በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው እስላማዊ አክራሪ ድርጅት ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ተሰጥቷል።

 

Ø ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም  በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ተኩል ላይ በሰሜን ካሜሮን ከናይጄሪያ ወሰን አካባቢ በአንድ መንደር ውስጥ  ሁለት ሴቶች አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷቸው ቦምቦች ስድስት ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸውና  ቁጥራቸው ከ30 እስከ 50 የሚደርስ ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል። ሁለቱ አጥፍቶ ጠፊዎችም አብረው የተገደሉ መሆናቸውንም ተያይዞ የመጣው ዜና ያስረዳል። የመንደሩ ሰዎች የተሰበስቡት ለሀዘን ሲሆን አጥፍቶ ጠፊዎችም ሰዎችን ለመቀላቀል የቻሉት ሀዘናቸውን ለመድረስ የመጡ ዘመዶች መስለው እንደሆነ ተጠቁሟል። ህይወታቸውን ካጡት መካከል የስድስት እና የአስራ አምስት አመት ልጆች የሚገኙበት ሲሆን አንድ የአካባቢው የጸጥታ ኮሚቴ አባል መገደሉም ተገልጿል። ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባችው ለህክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን እስካሁን ባይኖርም የቦኮሃራም ታጣቂዎች ለመሆናችው ከፍተኛ ግምት አለ። ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በአጥፍቶ ጠፊዎች አማካይነት በካሜሩን ከደረሱ የቦካ ሃራም ጥቃቶች  መካከል ይህኛው አምስተኛ ሲሆን አጥቂዎችን ለመቆጣጠር የተወሰደው እርምጃ እስካሁን አጥጋቢ ውጤት አልሰጠም በማለት በርካታ ዜጎች ይተቻሉ።   

 

 

 

 

 

የካቲት 1 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø በጋምቤላ የታጠቀውን ልዩ ኃይል መሳሪያ የማስፈታት ትእዛዝ ከፌዴራል  መሰጠቱን ተከትሎ የተወሰኑ አባላቶችን ትጥቅ ማስፈታት ቢቻልም በርከት ያሉት ከነመሳሪያቸው መሰወራቸውን ምንጮች አጋልጠዋል። በኑዌርና በአኝዋክ ጎሳ አባላት መካክል የተነሳውን የእርስ በእርስ ግጭት ለማብረድ ተችሏል በማለት የወያኔ አገዛዝ ደጋግሞ ቢናገርም በጋምቤላ ያለው እውነታ ግን ከዚህ ተቃራኒ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል። ከጋምቤላ ጸጥታና ደህንነት ቢሮ የሰው ኃይል አስተዳደር መምሪያ የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው የታጠቁ የልዩ ኃይል አባላት ብዛትና  ትጥቅ በማስፈታቱ ዘመቻ ትጥቃቸውን አስረክበዋል የተባሉት አባላት ቁጥር ፍጹም እንደማይገናኝ የታወቀ ሲሆን በርካታ ዜጎች ከእነትጥቃቸው ተሰውረዋል ተብሏል።

 

Ø በጉጂ ሕዝባዊ  በአላሙዲን ንብረት በሆነው ሜደሮከ የሚቆፈረው የወርቅ ቁፋሮ እንዲቆም በመጠየቅ እየተካሄደ ያለው ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የቀጠለ መሆኑን ከአካባቢው የሚደርሱ መረጃዎች እየተጠቆሙ ያሉ ሲሆን ሕዝባዊ ቁጣውም መርታችኋል የተባሉ ሰባት ወጣቶች በፖሊስ ታፍነው ወደ ሀገረ ማርያም መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል።  

በተያያዘ ዜና በሀረር መኤሶ ከተማ አሰቦት ወረዳ ውስጥ የወያኔ አለቅላቂዎችና አድርባዮች ባደረጉት ጥቆማ መሰረት ፖሊሶች ቤት ለቤት በመሄድ ተቃውሞውን መርታችኋ ተሳትፋችኋ የተባሉ ሰላማዊ ስዎችን የያዙ መሆናቸው ታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ  የኦህዴድ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊና የመኢሶ ከተማ አስተዳደር የነበረውን ሹም የነበረው የተያዘ መሆኑ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

 

Ø ትናንት ጥር 30 ቀን 2008 ዓ/ም በአርሲ ጎለልቻ በተባለው አካባቢ አንድ አይሱዙ የህዝብ ትራንስፖርት መኪና ሁለት መቶ ሜትር ጥልቀት ባለው ገደል ገብቶ የተሳፋሪዎች ህይወት ማለፉን ከስፍራው የመጣ ዘገባ ገለጠ:: ተሽከርካሪው 55 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ሲሆን በግሎልቻና በጮሌ ወረዳዎች መካከል የሚገኘውን ዳገት በመውጣት እንዳለ ተንሸራቶ ገደል ውስጥ የገባ መሆኑ ተዘግቧል። በአደጋው 22 ሰዎች መሞታቸው የተነገረ ሲሆን  የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በህይወት የተረፉትን  ከገደል ለማውጣት የተቻለ መሆኑ ታውቋል። 

 

Ø ትናንት ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስርያ ቤት ጀምሮ እስከ አሜሪካው ምክር ቤት ድረስ በርካታ ኢትዮጵያውያን የተገኙበት ታላቅና ደማቅ ሰልፍ ተደርጓል። 21 የሚሆኑ የሃይማኖት የፖሊቲካ የሲቪክ ማህበራት የሴቶች ድርጅቶች በተውጣጣ የጋራ ኮሚቴ የተዘጋጀው ሰልፍ ላይ ከዋሽንግተን፤ ከቦስተን ፤ ከፍሎሪዳ፤ ከአትላንታ፤ ከቺካጎ፤ ከኖርዝ ካሎራይና፤ ከፔንሴልቪኒያ እና ከኒውዮርክ የመጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈው የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል። ወያኔ መሬት ለመንጠቃ ያደረገውን ሙከራ  የተቃወሙትን ሰላማዊ ዜጎች በግፍ መጨፍጨፉን አውግዘዋል፤  በዘርና በሃማኖት የሚያደርገውን ክፍፍልን ተያይዞ የሚያካሄደውን ጭፍጨፋ ኮንነዋል እንዲሁም መሬታችንን ለሱዳን አሳልፎ መስጠቱን በብርቱ ተቃውመዋል። የተላያዩ መፈክሮችም በአማርኛና በኦሮምኛ ተሰምተዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ህጋዊ ሲኖዶስ ጳጳሳትና የኢትዮጵያ ሙስሊም አባቶች ተገኝተዋል።

 

Ø ናንት ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም በኒውዮርክ ከተማ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መስርያ ቤት ፊት ለፊት የዳግ ሃመርሾልድ አደባበይ በሚባለው ቦታ ላይ በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በወያኔ እየተካሄደ ያለውን ጸረ ሕዝብ ድርጊት በማውገዝ የተቃውሞ   ሰልፍ  አድርገዋል። ሰልፉ የተዘጋጀው በኒውዮርክ በኒው ጀርሲ እና በኮኔትኬት ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ሲሆን በሰልፉ ላይ ልዩ ልዩ የወያኔ አገዛዝ ጸረ ሕዝብ ድርጊትን የሚያጋልጡና የሚያወግዙ መፈክሮች ከመሰማታቸውም በላይ የድንበሩን ስምምነት በመቃወም የተሰባሰበው የኢትዮጵያውያን ፊርማ ለተመድ ባለስልጣኖች ተሰጥቷል። በሰልፉ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች ውስጥ - “በወያኔና በሱዳን መካከል የተደረገው የወሰን ስምምነት ህጋዊ አይደለም፤ በየቦታው የሚደረገው ግድያ መቆም አለበት፤ የመሬት ዝርፊያ ይቁም፤ መሬት የሕዝብ እንጅ የማፊያዎች አይደለም፤ ሕዝብን ከቦታ ቦታ ማፈናቀሉ ይቁም፤ አንንደነት ኃይል ነው” የሚሉ ይገኙባቸዋል። 

 

Ø የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የጸጥታ ሁኔታ ለማጠናከር በሚል ሽፋን የገጠር መኖሪያ ቤታቸውን ለማሰራት  23 ሚሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ አልአግባብ አውጥተዋል የሚለውን ክስ ለመመርመር  የደቡብ አፍሪካ ሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ስራውን በጀመረበት ወቅት ፍርድ ቤቱ ጠንከር ያለ እርምጃ እንዲወስድ  በመጠየቅ የደቡብ አፍሪካ የፖሊቲካ  የተቃውሞ ሰልፎች አድረገዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት ገለልተኛ የሆነ ኮሚቴ ባቀረበው ዘገባ ፕሬዚዳንቱ በገጠር መሬታቸው ላይ የመዋኛ ቦታዎችን፤ የቲያትር ቤት፤  የዶሮ እርባታና የቀንድ ከብቶች ማኖሪያ ተቋሞችን የያዘ ግንባታዎች የመንግስት ገንዘብ በማውጣት ያስሩ መሆናቸውን ያረጋገጠ ሲሆን ፕሬዚዳንቱም ከፊሉን ገንዘብ ለመመለስ መስማማታቸው ታውቋል። ይሁን እንጅ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተር ፓርቲ የሚባለውና ዴሞክራቲክ አሊያንስ የሚባለው ድርጅት የሚስተር ዙማ እርምጃ በቂ አይደለም በማለት ጉዳዩ ከሙስና ጋር የተያያዘ መሆኑን በመግለጽና ሚስተር ዙማ ከስልጣን እንዲነሱ በመጠየቅ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።  

 

Ø በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የተደረገለት የሊቢያ መንግስት ንብረት የሆነ አንድ ተዋጊ አውሮፕላን ደርና በተባለችው አይሲስ በተቆጣጠራት ከተማ ላይ ጥቃት ሲፈጽም ወድቆ የተሰባበረ መሆኑ ተገልጿል። አውሮፕላኑ ወርዶ የተከሰከሰው በቴክኒክ ምክንያት ነው የሚል ማብራሪያ ከአንዳንድ ወገኖች ይሰጥ እንጅ በአይሲስ ኃይሎች ተመቶ ሳይሆን አይቀርም የሚለው ግምት የጠንከረ ነው። የአውሮፕላኑ አብራሪ በጃንጥላ ወርዶ ህይወቱ ሊተርፍ ችሏል። ከአንድ ወር በፊት አንድ ሚግ 23 አውሮፕላን በቤንጋዚ አካባቢ ተመሳሳይ ጥቃት  ሲፈጽም የወደቀ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ ባለስልጣኖቹ የቴክኒክ ችግር ነው ቢሉም የአይሲስ ኃይሎች አውሮፕላኑን  መትተው መጣላቸውን ተናግረዋል።

 

Ø የሱዳን መካለካያ ኅያል ላለፉት ሁለት ሳምንታት በዳርፉር ጀበል ማራ በተባለው አካባቢ ባካሄደው ወታደራዊ ጥቃት አካባቢውን ከተቀናቃኝ ኃይሎች ነጻ ያወጣ መሆኑን ገልጾ ነዋሪዎቹ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አድርጓል። የመንግስቱ ተጻራሪ የሆኑት  ታጣቂ ኃይሎች የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች አካባቢውን እንዳልተቆጣጠሩ በመግለጽ ጠንካራ መግለጫ የሰጡ ሲሆን የአለም አቀፉ ህብረተሰብ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቀዋል። ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በሱዳን መንግስት ወታደሮችና በታጣቂ ኃይሎች መካከል በተነሳው ግጭት በ10 ሺ የሚቆጠሩ የጀበል ማራ ነዋሪዎች አካባቢውን ጥለው የተሰደዱ መሆናቸው ይታወቃል። እስካሁን በተደረጉ ጦርነቶች የመንግስት ኃይሎች አካባቢውንና ወደ ቦታው የሚወስዱትን መንገዶች ሁሉ በቁጥጥር ስር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብአዊ መብት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ሁኔታው ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸው ከቤት ንብረታቸው ተፍናቅለው የተሰደዱት ዜጎች እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል። ባለስልጣኖቹ ጨምረው እንደገለጹት የተመድ ስራተኞች በጸጥታው ምክንያት እስካሁን ወደ ቦታው  ሊሄዱ  ያልቻሉ በመሆናቸው በዚያ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ማወቅ አይቻልም ብለዋል። በዳርፉር ግጭት ከተጀመረ ከ 2003 ዓም ጀምሮ ከ300 ሺ ሰዎች በላይ ህይወታቸው የጠፋ መሆኑና እንዲሁም ክ2.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።

Ø ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ ባንኪ ሙን በአፍሪካ በተባበሩ መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የተፈጸመውን አስገድዶ የመድፈር ወንጀል ጉዳይ እንዲያስተባብሩ አሜሪካዊቷን ጄን ሆል ሉት የተባሉትን ሴት የመደቡ መሆናቸው ተገልጿል። ሴትየዋ በአሁኑ ወቅት የኢራቅ ስደተኞችን እንደገና ለማስፈር በሚደረገው ተግባር የባንኪ ሙን የቅርብ አማካሪ ሲሆኑ ከ2003 እስከ 2008 ባሉት ጊዜያት ውስጥ በተለያዩ ኃላፊነት ስርተዋል።





ጥር 30 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ሶስት ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ተብለው በታንዛኒያ ውስጥ የታሰሩ መሆናቸውን አንድ የታንዛኒያ የዜና ምንጭ ከፖሊስ አካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ ገልጿል። የታሰሩት ኢትዮጵያውያን ታሪኩ መንቼ፤ ኢዲሤ ታገሰ፤ ዘውዱ ሸምቦ የሚባሉ ሲሆኑ ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት ኪሊሚንጃሮ ከሚባለው አካባቢ ወደ ዋናዋ ከተማ ወደ ዳሬሰላም በአውቶቡስ  ሲያመሩ መሆኑ ታውቋል። ሰደተኞቹ ይጓዙ የነበረው ወደ ደቡብ አፍሪካ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ያለህግ አገሪቷ ውስጥ በመግባት ወንጀል ተከሰው በዛሬው እለት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተነግሯል።

 

Ø ባለፉት ሁለት ወራት በተለያዩ ቦታዎች ሲደረጉ የነበሩ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች አሁንም ያልበረዱ መሆኑ ይነገራል። በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በምዕራብ ሀረርጌ ግራዋ አካባቢና በጉጂ አካባቢ ተቃውሞ እንደቀጠለ መሆኑና በርከት ያሉ ዜጎች መታሰራቸው ተዘግቧል። በሌሎች አካባቢዎችም አንጻራዊ ሰላም ያለ ቢመስልም ውጥረቱ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል።

በዛሬው ዕለት በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ የፖሊቲካ ድርጅቶች፤ የሲቪክ ማህበራት አባላት የተለያዩ የሃይማኖት ተቋሞችና የተለያዩ ብሄረሰቦች አባላት  የሚገኙበት ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል። ዝርዝሩን እናቀርባለን።

 

 

 

Ø በአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በአነስተኛ ክፍያ ለብዙ ዘመናት ከኖሩበት ከተወለዱበት ቀየ ላይ እያስነሱ መሬትን በሊዝ መሸጥ ተስፋፍቶ የቀጠለ ሲሆን በአራዳ ክፍለከተማ በተለምዶ ቤል ኤር የተባለው አካባቢ በሊዝ መልክ ለባለሃብት ሊሸጥ መሆኑ ታወቋል። በክፍለ ከተማው የግል ይዞታ ያላቸው ዜጎች ለነገ የካቲት አንድ ቀን የተጠሩ ሲሆን ስብሰባው መሬታቸውን ለመሸጥ መታቀዱን ለመግለጽና የቅድሚያ ማግባባት ለማድረግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን ዘገባው ጠቁሟል። የግል ይዞታ ያላቸውን ነዋሪዎች ቤት ለቤት እየዞሩ በመመዝገብ ካርታ ያወጡና ያላወጡትን የመለየት ስራ ትናንት እሁድ ጥር 29 ቀን ሲካሄድ መቆየቱን የገለጹት   ምንጮች  ቤታቸውን ለቀው እንዲሄዱ የሚደረጉት ነዋሪዎች ስለሚከፈላቸው የካሳ ክፍያ እና ስለሚነሱበት ግዜ ቅድመ ማግባባት ለማድረግ በተጠራው ስብሰባ ልይ ይገለጻል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። 

 

Ø በተያያዘ ዜና ለቡ በተባለው አካባቢ በሊዝ ተሰጥተው የነበሩ መሬቶችን ለቀው እንዲወጡ  መመሪያ በተሰጣቸው መሰረት ባለሃብቶቹ የግንባታ ዕቃዎቻቸውን በማንሳት ላይ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። መሬቱን በሊዝ የሸጠላቸው የአዲስ አበባ መስተዳድር ተለዋጭ መሬት የምታገኙበትን መንገድ እንፈልጋለን ከማለት በስተቀር እስካሁን የወሰደው እርምጃ እንደሌለም ታውቋል።

 

Ø እሁድ ጥር 29 ቀን 2008 ዓም ሰሜን ኮሪያ አንድ የጠፈር ተምዘግዛጊ መሳሪያ ማምጠቋ ታውቋል። የሰሜን ኮሪያ ባለስልጣኖች ተመዝግዛጊው መሳሪያ (ሮኬቱ) የተተኮሰው በህዋው ላይ የሳተላይት ጣቢያ ለማስቀመጥ ነው የሚል ምክንያት ቢሰጡም ሌሎች አገሮች ግን  ዋናው ምክንያት ሰሜን ኮሪያ የቦለስቲክ ሚሳየል ተክኖሎጂን ለመሞከር ያደረገቸው ነው እያሉ ነው። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ሮኬት ያመጠቀችው አራተኛውን የኑክሌር ሙከራ ባደረገች በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ነው። ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ እንዲሁም የምዕራብ አገሮች ጉዳዮ በጣም ያሳሰባቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ባስቸኳይ ተሰብስቦ  የሰሜን ኮሪያን ድርጊት ማውገዙና ተጨማሪ የማዕቀብ ርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱ ተገልጿል። ከዚህ በፊት በሰሜን ኮሪያ ላይ በተከታታይ  የተደረጉት ማዕቀቦች በአገሪቱ የኑክለር ፍላግትና ተግባር ላይ ያመጡት ተጽእኖ አነስተኛ ሲሆን ወደፊት የሚወሰደውም ማዕቀብ ምን ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል ግልጽ አይደለም። በተጨማሪም ቻይና የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ቢፈነገል የሚከተለው ቀውስ ወደ አገሯ እንዳይዛመት ስለምተሰጋ ከበድ ያለ ማዕቀብ በሰሜን ኮሪያ ላይ እንዳይወሰድ ታደርጋለች የሚል ግምት አለ።

 

Ø ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከሶማሊያ ዋና ከተማ ወደ ጅቡቲ ይበር በነበረው የዳዓሎ አየር መንገድ ንብረት በሆነው አውሮፕላን ላይ የደረሰው ጉዳት በላፕ ቶፕ ላይ በተጠመደ ፈንጅ ምክንያት መሆኑን የሚያሳይ የቪዲዮ መረጃ ከሲሲቲቪ ላይ ያገኙ መሆናቸውን የሶማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ገልጸዋል። የተገኘው የቪዲዮ መረጃ አንድ ተሳፋሪ ላፕ ቶፕ የሚመስል ዕቃ ከአውሮፕላን ማረፊያው ሰረተኛ ሲቀበል የሚያሳይ ሲሆን ተሳፋሪው አውሮፕላኑ አደጋ ሲደርስበት በተፈጠረው ክፍተት ተስፈንጥሮ ወጥቶ የሞተ መሆኑ ተነግሯል። ቦምቡን ያፈነዳው ተሳፋሪ ቀደም ብሎ ሊሄድ የነበረው በቱርክ አየር መንገድ ሲሆን የቱርክ አውሮፕላን በመሰረዙ ምክንያት የዳአሎ አየር መንገድ ተሳፋሪውን ተቀብሎ ያሳፈረው መሆኑ ታውቋል። በሴራው እጃቸው አለበት በሚል የሱማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ወደ 20 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø ሱማሊያው ውስጥ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ወደ 58 ሺ የሚደረሱ ህጻናት በቂ እርዳታ ካልተሰጣቸው ህይወታቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ የተመድ ባለስልጥኖች ስኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም  ገለጹ። ቢያንስ 305 ሺ የሚሆኑ ህጻናት በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ መሆናቸውን ገልጸው ከእነዚህ ውስጥ58 ሺ የሚደርሱት በሞት አፋፍ ላይ መሆናቸው ተናግረዋል። ለአራት ተከታታይ ዓመታት በሱማሊያ በአንዳንድ ቦታዎች ድርቅ፤ በሌሎች ቦታዎች የጎርፍ አደጋ በመድረሱ  የብዙ ዜጎች ህይወት የተቃወሰ ሲሆን የአገሪቱ አርባ ከመቶ የሚሆነው 4.7 ሚሊዮን ሕዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ ዜና በደቡብ ሱዳን በጦርነት ቀጠና ውስጥ ያሉ ቢያንስ 40 ሰዎች እየተራቡ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በሰጠውም መግለጫ አስታውቋል። የአገሪቱ 25 ከመቶ የሚሆነው 2.8 የሚሊዮን የሚሆነው ሕዝብ እርዳታ የሚፈልግ ሲሆን በግጭቶች በመስፋፋታቸው ምክንያት እርዳታውን ለማድረስ ያልተቻለ መሆኑ ተነግሯል። እርዳታውን በወቅቱ ከሚፈለገው ቦታ ለማድረስ የጸጥታው ሁኔታ አስተማማኝ መሆኑ አስፈላጊ በመሆኑ ጦርነት በሚያካሄዱባቸው ክፍሎች ትብብር ካልተገኘ በርካታ ዜጎች በምግብ እጥረት ሊሞቱ እንደሚችሉ ይኸው የተመደ ዘገባ አስታውቋል።  

 

Ø በቡርኪና ፋሶ ከአልካይዳ ግንኝነት እንዳለው በሚነገርለት ቡድን ታግተው የነበረ አውስትራሊያዊ ባልና ሚስቶች ቡድኑ ሊፈታቸው እንደሚፈልግ ቀደም ብሎ መገለጹ የሚታወቅ ሲሆን ትናንት ጥር 29 ቀን 2008 ዓም  የሰባ ስድስት አመት እድሜ ያላቸው ሚስስ ጆስሊን ኢሊየት ተፈተው በአገሪቱ ዋና ከተማ በዋጋዱጉ የገቡ መሆናችው ታውቋል። ሴትየዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ባለቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈቱ ተስፋ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ከባላቸው ጋር በመሆን ላለፉት 44 አመታት ሲሰጡ የነበረውን አገልግሎት ለመቀጠል ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል። በንግግራቸው የቡርኪና ፋሶን መንግስትና ሌሎች ትብብር ያደረጉላቸውን ወገኖች አመስግነዋል። ሰዎችን ለማስፈታት መንግስት በተዘዋዋሪ ከአጋቾቹ ጋር መነጋገሩ ፍንጭ ያለ ሲሆን ምንም ዓይነት የገንዘብ ክፍያ ያልተከፈለ መሆኑን ግን የመንግስቱ ባለስልጣኖች ተናግረዋል።  የሴትዮዋ ባለቤት መች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚገልጽ መረጃ እስካሁን አልተገኘም።

 

Ø ትናንት እሁድ ጥር 29 ቀን 2008 ዓም በካይሮ ደቡባዊ ክፍል የግብጽ ፖሊሶች አንድ መኖሪያ ቤት ለመፈተሽ ጥረት ባደረጉበት ወቅት በተነሳ  የተኩስ ልውውጥ አራት ሰዎች የተገደሉ መሆናችው ታውቋል። የግብጽ ባለስልጣኖች የተገደሉት ሰዎች አሸባሪዎች ናቸው ብለው የወነጀሏቸው ሲሆን ቤቱም ቀላል ቦምቦች የመስርያ ቦታ እንደነበረ ተናግረዋል። የአሁኑ የግብጽ መንግስት በስልጣን ከተሰየመ ጀምሮ የአስልምና ወንድማማቾች ቡድን በጸጥታ ኃይሎች ላይ የተለያዩ ጥቃቶች ሲፈጽም የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተገደሉት አራት ሰዎች ቀደም ብሎ ሁለት ወታደሮችንና ሁለት ፕሊሲችን የገደሉ አሸባሪዎች መሆናቸውን የግብጽ የጸጥታ ባለስልጣኖች ገልጸዋል።፡

 


ጥር 28 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በጋምቤላ የነበረውን ግጭት በቁጥጥር ስር ለማደረግ የወያኔ አግአዚና የፌዴራል ጦር ወደ ከተማዋ  መግባቱ የተነገረ  ቢሆንም ግጭቱና ውጥረቱ እስካሁን ያልበረደ መሆኑን ከስፍራው የሚደርሱት የተለያዩ  መረጃዎች ይገልጻሉ፡፡ ትናንት ጥር 27 ቀን 2008 ዓም  በደል ደርሶብናል ያሉ  የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት ፒንዩዲ  በተባለ የመጠለያ ጣቢያ ሄደው የኑዌር ተወላጆች ከሆኑ ጠባቂዎች ጋር ባደረጉት ግጭት ሶስት የአኙዋክ ተወላጆችና አንድ የኑዌር ተወላጅ እንደሞተ ተነግሯል። በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ጎጆዎችም በእሳት ተቃጥለዋል ተብሏል። የወያኔ ጦር በከተማ ሆነ በአንዳንድ ወረዳዎች የተሰማራ ቢሆንም በተለይ በአኙዋክ ብሔረሰብ አባላት የተጠላና የማይታመን በመሆኑ ጸጥታውን ሙሉ በሙሉ ለማስከበር ያልቻለ መሆኑ ይነገራል። የእንግሊዝ መንግስትና ሌሎች የምዕራብ አገሮች ዜጎቻቸው ወደ ጋምቤላ እንዳይንቀሳቀሱ መመሪያ ያስተላለፉ መሆናቸው ተያይዞ የመጣው ዜና ያስረዳል።

 

Ø በመቀሌ  ስለመልካም አሰተዳደር ችግሮች ለመወያየት ተሰብሰቦ የነበረው የከተማዋ ነዋሪ  የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በከፍተኛ ደረጃ እያስመረረው መሆኑኑን ገለጸ።  በመቀሌ በአራት ቀን በፈረቃ የመጠጥ ውኃ ለማዳረስ ቢሞከርም ህዝብ የመጠጥ ውሃ ችግሩ እየተባባሰ እንጂ መፍትሄ ሆኖለት እንደማያውቅ ለማወቅ ተችሏል።  የመሰለ ችግር በምታስተናግደው መቀሌ የመልካም አስተዳደር ችግር ዙሪያ ውይይት አድርጉ የተባሉት ነዋሪዎች አብዛኞቹ የሚገኝ መፍትሔ የለም በማለትና  ተስፋ በመቁረጥ በስብሰባው ላይ ለመገኘት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል ተብሏል።

 

 

Ø ዛሬ ጥር 28 ቀን 2007 ዓም ከሌሊቱ አስር ሰዓት አካባቢ በታይዋን ደሴት በሬክተር መለከያ 6.4 ኃይል ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰ መሆኑ ታውቋል። የመሬት መንቀጥቀጡ ቴይናን በተባለችው ከተማ የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሰነጣጠቀና የደረመሰ ሲሆን እስካሁን ድረስ በደረሰው መረጃ 12 ሰዎች መሞታቸውና ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል። 30 ሰዎች በአንድ በፈረሰ ህንጻ ውስጥ  መውጫ ያላገኙ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ከሞቱት መካከል አንደኛው ገና የተወለደ ህጻን መሆኑም ተዘግቧል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ህይወት ለማትረፍ ከፍተኛ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የጦር ኃይል አባላት ለነፍስ አድኑ ሥራ መሰማራታቸውና በየቦታውም የመጠላያ ቦታዎች መሰናዳታቸው ተገልጿል። የ256 ሰዎች መኖሪያ የነበረው ባለ አስራ ሰባት ፎቅ ህንጻ በመሬት መንቀጥቀጡ ኃይል ከላይ እስከታች የፈረሰ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø ትናንት ጥር 27 ቀን 2008 ዓም በአልሸባብ ቁጥጥር ስር ወድቃ የነበረችውንና መርካ የተባለችውን የወደብ ከተማ የሶማሊያ መንግስት የመከላከያ ጦር ከአፍርካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው ታውቋል።  ከአልሸባብ ታጣቂዎች የተደረገው ውጊያ አነስተኛ ቢሆንም በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተዘግቧል። በከተማዋ የነበረው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከከተማው የወጣው ጨርሶ ለመልቀቅ ሳይሆን ከወታደራዊ ታክቲክ አንጻር መሆኑን በትናንትናው ዕለት መግለጹ ይታወሳል።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ በተረደመስ አንድ የማዕድን ጉድጓድ ውስጥ የነበሩ 87 የማእድን ስራተኞች በህይወት ተርፈው ከጉድጓድ ለመውጣት የቻሉ ሲሆን ከሰራተኞቹ ውስጥ ሶስቱ ግን እስካሁን በጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው ይገኛሉ። አደጋው የደረሰው በትናንናው ሌሊት ሲሆን ለሰላሳ ስድስት ሰዓት በተደረገ ፍለጋ  የጠፉትን ሶስት ሰዎች ማግኘት ያልተቻለ መሆኑ ታውቋል። ህይወታቸው የዳነው 87 ሰራተኞች የህክምና ምርመራ ተደርጎላቸው ምንም ዓይነት ጉዳት ያላጋጠማቸው መሆኑ ተነግሯል።

 

Ø ባለፈው ወር አንድ የአውስትርሊያ ዶክተርንና ባለቤታቸውን በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ከሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ ጠልፎ እስካሁን አግቷቸው የቆየው አካል  አል ሙራቢቱን የተባለውና ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያለው ቡድን መሆኑን በድምጽ ካስተላለፈው መልእክት ለመረዳት ተችሏል። ቡድኑ አርብ ዕለት ባስተላለፈው መልእክት የሰዎቹ መታገድ በመንግስት ታስረው የሚገኙትን የቡድኑን አባላት በለውጥ ለማስልቀቅ አላማ አድርጎ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ቡድኑ  የያዛቸውን ሰዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመልቀቅ የወሰነ መሆኑን ገልጿል። የአውስትራሊያው ዶክተርና ባለቤታቸው ከ 1980 ዓም ጀመሮ ጂቦ በምትባለው ከተማ 120 አልጋዎች ያሉት አንድ ክሊኒክ አቋቋመው የአካባቢውን ሰዎች ሲረዱ መቆየታቸው ይታወቃል።   

 

 



ጥር 27 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ወያኔ በሠራዊቱ ውስጥ ድንገተኛ የሆነ የሰው ኃይል ቅነሳ አድርጎ አዲስ በሚመለመሉ ሊተካ መሆኑን የታመኑ የመከላከያ ምንጮች አጋለጡ። ከጥቂት ቀናት በፊት የወያኔ የጦር አለቆች በተከታታይ የአካሄዱትን የግምገማ ስብሰባ ተከትሎ እዝን ባለማክበር በተደጋጋሚ ትእዛዝ እየጣሱ ያሉትንና የተቃዋሚ ደጋፊ ናቸው ተብለው የሚጠረጥሩ የሰራዊት አባላትን በብዛት ለማባረር መወሰኑን የታመኑ ምንጮች ባስተላለፉት መረጃ ለማወቅ ተችሏል። በሰራዊት ህግ መሰረት የፈጸሙት ጥፋታቸው እስራትና ሌሎች ከባድ ቅጣቶች ሊያስከትሉ ቢችሉም በአሁኑ ወቅት ይህንን ተግባራዊ ማድረግ ሌሎችን አስቆጥቶ ተቃውሞ ያስነሳል ከሚል ስጋት ከሰራዊት ማሰናበቱ የተሻለ መፍትሔ ይሆናል በሚል የወሰኑ መሆናቸው ታውቋል።   በተለይ ከሕዝባዊ ተቃዋሞ  ጋር በተያያዘ  ሰላማዊ ሰዎችን በጥይት መገደል የለባቸውም የሚሉ አስተያየቶችን  የሰጡና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ጠይቀው የነበሩ  የሰራዊቱ አባላት ላይ የስንብቱ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚከናወን ከምንጮቹ መረጃ ለመረዳት ተችሏል።  

 

Ø ስዋይን ፍሉ (የአሳማ ጉንፋን) የተባለው አደገኛ የኢንፍሎንዛ በሽታ ኢትዮጵያ ውጥ የገባ መሆኑ ምንጮች አጋለጡ። በዚህ ሳምንት ውስጥ በየካቲት 12፤ በጥቁር አንበሳና በራስ ደስታ ሆስፒታሎች የስዋይን ፍሉ የሚባለው የኢንፍሎንዛ ታማሚዎች መገኝታቸውን ለማወቅ ትችሏል። የወያኔው የጠና ሚንስቴር እንደተለመደው አንዴ ስዋይን ፍሉ አይደለም ሌላ ጊዜ የዚህ በሽታ አደገኛነት አነስተኛ ነው በማለት ያጣጣለው ቢሆንም  በበሽታው አንዳንድ ሰዎች እንደሞቱ ይነገራል። የበሽታው ናሙና ለምርመራ ወደ አሜሪካ የተላከ ስሆን ውጤቱ እየተጠበቀ ነው ተብሏል። ስዋይን ፍሉ የዛሬ ሰባት ዓመት ምንነቱ በምርመራ የተደረሰበት ገዳይ የሆነ ተላላፊ በሽታ ሲሆን እንደማንኛውም የኢንፍሎንዛ በሽታ ከፍተኛ ትኩሳት፤ ደረቅ ሳር ራስ ምታት ያለውና በተለይ በዕድሜ የገፉትንና በሌሎች በሽታዎች የተጠቁትን የሚጎዳ መሆኑ ይታወቃል። 

 

Ø በኢትዮጵያ የገባው ድርቅና ረሃብ በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የተለያዩ ክፍሎች እየገለጹ ይገኛሉ። ሰሞኑን በአፋርና በምስራቅ ትግራይ ተዘዋውሮ ሁኔታዎችን የተመለከተው ጋዜጠኛ የድርቁ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል። በተዘዋወረባቸው ቦታዎች በርካታ የቀንድ ከብቶች መሞታቸውንና የሚበሉት ምግብ የሌላቸውን ዜጎች የተመለከተ መሆኑን ገልጿል። በአንዳንድ ቦታዎች ምርቶች ጨርሶ የወደሙበት ወይም ከ90 ከመቶ በላይ የቀነሱብት እንደሆነ ተጥቁማል። በሚቀጥሉት ወራት ከ15 ሚሊዮን በላይ በድርቁ የተጠቁ ሰዎች  እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ልዩ ልዮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በጣም አስቸኳይ በሆነ መንገድ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥ ከ10 ሚሊዮን በላይ መሆኑ ተጠቁሟል። በድርቅና በረሃብ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመታደግ የሚያስፈልገው እርዳታ ከ 1.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተተመነ ሲሆን እስካሁን ከውጭ በእርዳታ መልክ የተገኘው 169 ሚሊዮ ዶላር ብቻ መሆኑ ሁኔታውን በጣም አሳሳቢ ያደርገዋል ተብሏል። 

 

Ø ዛሬ ጥር 7 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የተባለው  ቡድን ከዋናዋ ከተማ ከሞጋዲሾ 70 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውንና መርካ የተባለችውን የወደብ ከተማ መቆጣጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ለዜና ተቋሞች በሰጡት መረጃ ገልጸዋል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በከተማዋ ሰፍሮ ጸጥታ ሲያስከብር የነበረው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ዛሬ ጥር 27 ቀን 2008 ዓም ከተማዋን ለቆ የወጣ ሲሆን የአልሸባብ ኃይሎች ወደ ከተማዋ የገቡት አለምንም ተኩስ መሆኑ ተረጋግጧል። ከተማዋ በአልሸባብ ቁጥጥር ስር መውደቋ በሰላም አስከባሪው ኃይል አባላት ላይ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት የሚያስከትል ሲሆ በሞጋዲሾ ለሚገኘውም የሱማሊያ መንግስት ከፍተኛ ተጽእኖ ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።  ከሶስት ሳምንት በፊት ኤል አዴ በተባለ ቦታ አልሸባብ ጥቃት ፈጽሞ በዚያ የነበሩትን 100 የኬኒያ ወታደሮች መግደሉን መግለጹና የኬኒያ መንግስት የሞቱትን ወታደሮች ቁጥር ባይገልጽም ጉዳት መድረሱን በመግለጽ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል።

 

Ø ዛሬ ጥር 27 ቀን 2008 ዓም ማሊ ቲምበክቱ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የተመድ ዋና ጽቤት አጠገብ አንድ ቦምብ የፈነዳ መሆኑና በበጸጥታ ኃይሎች እና በአጥቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ የተደረገ መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ገልጿል። አንድ ሰው የአካል ጉዳት ደርሶበት ህክምና ወደሚያገኝበት አካባቢ የተወሰደ ሲሆን የተመድ ተልእኮ ቡድን መቀመጫውን የከተማ አውሮፕላን ጣቢያ ወደሚገኝበት አካባቢ ያዛወረ መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት የተመድ ኃይሎችና የማሊ መንግስት ከአጥቂዎቹ ጋር ጦርነት የገጠሙ  መሆናቸው ታውቋል።  የዛሬ አራት አመት ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የሚጠረጠሩ አማጽያን የሰሜን ማሊን ግዛት ወርረው በቁጥጥር ስር ማድረጋቸውና በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ ከአካባቢ እንዲወጡ የተደረገ መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውይይት ቡድን ላለፉት አራት አመታት ለንደን በሚገኘው የኢኳዶር ኤምባሲ ተጠልለው የሚገኙት የዊኪሊክ መስራች ጁሊያን አሳንጅ ነጻ ናቸው የሚል ውሳኔ የሰጠ መሆኑ ተገለጸ። አሳንጅ የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ኤምባሲዎች ሲያደርጉት የነበሩትን የሚስጥር መልእክቶች ልውውጦች በኢንተርኔት አማካይነት ለሕዝብ ይፋ በማደረግና  በማጋለጥ የታወቁ ሲሆን አሳንጅ አሜሪካ መጥተው ለፍርድ እንዲቀርቡ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል። የስዊድን መንግስት አሳንጅን ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር ወንጀል ተከሷልና ወደ ስዊድን መጥተው ራሳቸውን እንዲከላከሉ የእንግሊዝ መንግስትን የጠየቀው ጥያቄ እሳቸውን ወደ አሜሪካ ለመላክ የተደረገ የሽፋን ሴራ ነው ከሚል ፍራቻ እንግሊዝ አገር በሚገኘው የኢኳደር ኢምባሲ ውስጥ ጥገኝናት ጠይቀው ላለፉት አራት አመታት በኤምባሲ ውስጥ ቆይተዋል። አለአግባብ የሚታሰሩትን ሰዎች ጉዳይ ለመመርመር በተባበሩ መንግስታት ድርጅት የተቋቋመውና አምስት ሰዎች የሚገኙበት  ፓናል የጁሊያን አሳንጅን ጉዳይ መርምሮ በሰጠው ውሳኔ በዓለም አቀፍ ህዝብ መሰረት አሳንጅ የሚያሳስራቸው ምንም ምክንያት የሌለ መሆኑን ገልጾ እንግሊዝና ሲውድን አለአግባብ አስሯቸዋል የሚል ውሳኔ አስተላልፏል። የኮሚቴው ውሳኔ በስራ ላይ የሚውልበት ህጋዊና  መዋቅራዊ መሰረት ባይኖርም አሳንጅና የአሳንጅ ደጋፊዎች የሞራል የበላይነትን አግኝተዋል ተብሏል። የእንግሊዝ መንግስት ባለስልጣኖች አሳንጅ በፈቃዳቸው በኢኳደር ኢምባሲ ገብተው ተደበቁ እንጅ በእንግሊዝ መንግስት በኩል የተወሰደ እርምጃ እንደሌለ ገልጸው ውሳኔው መሰረተ ቢስ ነው ብለውታል። ሚስተር አሳንጅ ቀደም ብለው ባስተላለፉት መልክት የተመድ ፓናል በዚህ መልክ ውሳኔ ከሰጠ ፓስፖርታቸው እንዲመለስላቸውና  በሳቸው ላይ የተጣለው ክስ ውድቅ እንዲሆን ጠይቀዋል።     




ጥር 26 ቀን 2008 ዓ.ም
 

Ø በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ለቡ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአዲስ አበባ መስተዳድር ለኢንቨስትመንት ግልጋሎት ተብሎ በሊዝ መሬት ተሸጦላቸው የነበሩትና  ግንባታ የጀመሩትም ሆነ ባለሀብቶች ግንባታዎችን ባስቸኳይ አፍርሰው መሬቱን እንዲያስክቡ የሚል ድንገተኛ መመሪያ የተሰጣቸው መሆኑን የታመኑ ምንጮች አጋለጡ። ለቡ በተባለው አካባቢ ለኢንቨስትመንት በሊዝ መሬት ከአዲስ አበባ መስተዳድር ገዝተውና ተረክበው የግንባታ ስራዎችን የሚሰሩ በርካታ  የአገር ውስጥና የውጭ አገር ባለሃብቶች ያሉ ሲሆን በተሰጠው መመሪያው ምክንያት ከፍተኛ ኪሳራ ሊደርስባችው እንደሚችል ተገምቷል። መመሪያው የተሰጠው ከኦሮሚያ ክልል ተብየው ባለስልጣኖች  ሲሆን መሬቱ የኦሮሚያ ክልል እንጅ የአዲስ አበባ መስተዳድር ስላልሆነ ባስቸኳይ ካላስረከቡ በኦሮሚያ አፍራሽ ግብረ ኃይል የሚፈርስ መሆኑ ተነግሯቸዋል።  በለቡ የተጀመረው የመሬት ነጠቃ ከቀጠለ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ገላን በተባለው አካባቢ የኢንዱስትሪ ዞን ግንባታ በሚል የድሪባ ኩማ ቢሮ በሊዝ የሸጠላቸው የውጭና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች ከፍተኛ  ስጋት ላይ መሆናቸውን ታዛቢዎች ሳይጠቁሙ አላለፉም።  በለቡ አካባቢ በሊዝ መሬት ከአዲስ አበባ መስተዳድር የገዙ ባለሃብቶች  ማስጠንቀቂያ ሰጡን ያሉዋቸው ከኦሮሚያ ልዩ ዞን አስተዳደር የመጡ የስራ ሃላፊዎች በመሆናቸውና በሁኔታው በመደናገጣቸው ሽያጩን ለፈፀመላቸው የአዲስ አበባ አስተዳደር ሊዝ ቢሮ አቤቱታ ማቅረባችውን ተናገረዋል። አፋጣኝ መፍትሄ ባለማግኘታቸው ከንቲባው ድሪባ ኩማ ዘንድ አቤት ለማለት ቀጠሮ ማስያዛቸውም ተረጋግጧል።

 

 

Ø በኦሮሚያ ባለስልጣናት መካከል እየተደረገ ያለው የውስጥ ግምገማው  ያልተጠናቀቀ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አንዳንድ የኦህዴድ ባለስልጣኖች ለወያኔ ደህንነት ቃላቸውን እንዲሰጡ የተገደዱ መሆናቸው ታውቋል። በባለስልጣኖቹ ቤቶች ዙሪያ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን የሚጠቁመ መረጃው እየመጡ ሲሆን አመጹን ለማብረድና ችግሩን ለመቅረፍ በየካቲት ወር በየዞኑና በየወረዳው ህዝባዊ ስብሰባ ለመጥራት መታቀዱንም ለማወቅ ተችሏል። በተያያዘ ዜና በሕዝባዊ አመጽ ምክንያት በወያኔ አግአዚ ጦር ከየቦታው ተለቅመው የታሰሩ ወጣቶች በየእስር ቤቱ ከፍተኛ ድብደባ እየተደረገባቸው መሆኑ ከየአቅጣጫው የሚደርሱት ዜናዎች ይጠቁማሉ።

 

 

Ø ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ወያኔ ስብሰባ ጠርቶ እያነጋገረ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች የተደረጉት ስብሰባዎች  የጠበቀውን ውጤት ያላስመዘገቡ መሆናቸው ተነግሯል። በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት በሚገኝ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ በተደረገው ስብሰባ ላይ ስብሰባውን የመሩት የወያኔ ባለስልጣኖች የመልካም አስተዳደር ችግር የደረሰባችሁ ነዋሪዎች እየተነሳችሁ ማስረዳት ትችላላችሁ  በማለት ከሕዝብ መረጃ ለማግኘት ቢጥሩም “ህዝቡ በተለያየ አጋጣሚ ሲናገርና ሲያለቅስበት የቆየበትን ችግር አናውቅም እያላችሁ እንዴት እንደ አዲስ ትጠይቁናላችሁ፤ በጉያችሁ ያቀፋችሁትን አሜክላ ታውቁታላችሁና እናንተው እዚያው ጨርሱት” በማለት ነዋሪው መልስ የሰጣቸው መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።  በተጨማሪም በመለስተኛና በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ የንግድ ማህበረሰብ አባላትን ቤት ለቤት እየዞሩ ያነጋገሩት የወያኔ ካድሬዎች መንግስት እንዲኖር ከፈለጋችሁና የንግድ ስራችሁ እንዲስፋፋ ከፈለጋችሁ ተደራጁ፤ ከተደራጃችሁ መንቀሳቀሻ እንዳይቸግራችሁ ገንዘብ በረዥም ግዜ የሚከፈል ብድር እንሰጣችኋለን በማለት ለማግባባት ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር የደረሰን መረጃ ይገልጻል።  

 

 

Ø የአባይን ግድብ አስመልክቶ ለመነጋገር የተመሰረተው የሶስቱ አገሮች የቴክኒካል ኮሚቴ በሚቀጥለው እሁድ ካርቱም ሱዳን ላይ የሚሰበሰብ መሆኑን የግብጽ የመስኖን ሚኒስትር ረቡዕ ዕለት ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።  ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ የግብጹ የቴክኒክ ኮሚቴ የፈረንሳዩ አጥኝ ቡድን ሊያደርግ ስላለስበው ጥናት ጉዳይ ባቀረበው ሪፖርት ላይ የጀመረውን ውይይት በዚህ ሳምንት አጠናቅቆ ወደ ካርቱም ይጓዛል ብለዋል።   በቅርቡ የፈረንሳይ አጥኝ ኩባንያ ስለግድቡ በሰጠው ሀሳብ ላይ የደረሱበትን መደምደሚያዎች ሶስቱም አገሮች በካርቱሙ ስብሰባ ላይ የሚያቀርቡ ሲሆን ስምምነት ከተፈጠረ አጥኘው ኩባንያ ጥናቱን እንዲጀምር መመሪያ የሚሰጠው መሆኑ ታውቋል።

 

Ø በጥብቅ ሚስጥር የተያዘ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ዘገባ የብሩንዲን ፕሬዚዳንት ከስልጣን ለማስወገድ  የሩዋንዳ መንግስት ወደ አገሩ ከተሰደዱት ስደተኖች መልምሎ ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አጋልጧል። በኮንጎ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ እንዲከታተል በተመድ የተመደበው የሙያተኞች ቡድን ባቀረበው ዘገባ የተመለመሉት ስደተኞች በሩዋንዳ የወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል። የሙያተኛው ቡድን ኮንጎ ውስጥ አግኝቶ ያነጋገራቸውና ወታደራዊ ስልጠና የተሰጣቸው 18  የብሩንዲ  ተወላጆች  የሰጡትን ቃል መሰረት በማድረግ ባቀረበው ዘገባ ሩዋንዳ ውስጥ ከሚገኘው ከማህማ ስደተኞች ካምፕ መመልመላቸውንና ለሁለት ወራት ያህል ወታደራዊ ስልጠና በጫካው ስጥ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸዋል። በተመድ የሩዋንዳው ልዮ መልእክተኛ በሙያተኛው ቡድን ዘገባው ላይ የቀረበውን ክስ መሰረተ ቢስ ነው በማለት ያጣጣሉት ሲሆን ቡድኑ  ከተሰጠውው ተልእኮና ኃላፊነት ውጭ እየሰራ ነው ብለዋል። ካለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀምሮ የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ የምርጫ ዘመን ለመወዳደር ያደረጉትን ውሳኔ በመቃወም በተነሳው ግጭት ምክንያት  በመቶ የሚቆጠሩ የብሩንዲ ዜጎች ያሉ የሞቱ ሲሆን በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ደግሞ መሰዳዳቸው ይታወሳል።

 

Ø የአሸባሪው ድርጅት የአይሲስ መሪዎችና አባላት ባለፉት ጥቂት ወራት ከኢራክና ከሶሪያ በመሸሽ ወደ ሊቢያ የገቡ መሆናቸውን የሊቢያ የጸጥታ ኃላፊዎች ገለጸዋል። በሊቢያ የምትገኘው ሰርት የምትባለው ከተማ ባለፈው ዓመት በአይሲስ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መውደቋ የሚታወቅ ሲሆን ከኢራክና ከሶሪያ የሸሸቱ የድርጅቱ መሪዎችና አባላት የገቡት ወደዚች ከተማ ነው ተብሏል።   ባለፈው ማክሰኞች ጥር 24 ቀን 2008 ዓም አሜሪካንና እንግሊዝን ጨምሮ የ23 አገሮች ተወካዮች ሮም ውስጥ አይሲስ በሊቢያ ውስጥ በሚያመጣው አደጋ ላይ ለመወያያት መሰበስባችው የታወቀ ሲሆን በሊቢያ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር አለመቻሉ  እርምጃ ለመውሰድ ያላስቻለ መሆኑ  ተነገሯል።፡

 

 

Ø አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የእርዳታ ሰጭ አገሮች ስብሰባ ላይ የስዊዘርላንድ መንግስት በናይጄሪያ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ያለውን ቦኮ ሃራምን ለመቋቋም ለተደረገው ወታደራዊ ጥቃት የ12 ሚሊዮን ዶላር ሰጥቷል ተብሎ የተሰጠው መረጃ ትክክል አለመሆኑን የስዊዘርላንድ መንግስት አስተባብሏል። የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ ስዊዘርላንድ በተፈጠሩ ግጭቶች ሁሉ ዘወትር የገለልተኛነት ሚናን የምትወስድ መሆኑ እየታወቀ የተሰጠው ገንዘብ ለወታደራዊ ጉዳይ ነው የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ጠቅሶ የተባለው ገንዘብ የተሰጠው በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ዜጎች መርጃ ነው በማለት መረጃው እንዲስተካከል ጠይቋል። አዲስ አበባ ላይ የተሰበሰበው የእርዳታ ሰጭ አገሮች ስብሰባ ቦኮ ሃራምን ለመቋቋም 250 ሚሊዮን ዶላር ለመርዳት ቃል መግባታቸው ታውቋል።፡

 

Ø የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ረቡዕ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም  በሰጡት መግለጫ በሲየራ ሊዮን የኢቦላ በሽታ እንደገና እየተስፋፋ መሄዱን ገልጸው በበሽታው የተለከፉ 48 ሰዎች በመሰዋራቸው ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል። ባጠቃላይ በአሁኑ ወቅት በበሽታው የተለከፉ 70 ሰዎች ተገልለው ህክምና እየተደረገላችው መሆኑን ጠቁመው ከጠፉት መካከል 18 የሚሆኑት የያዛቸው  በሽታ የአደጋ መጠን ከፍተኛ ነው ብለዋል። ተወካዩ በሆስፒታሎችና በመንደሮች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደርግም አሳስበዋል። ባለፉት ሁለት ዓመታት የኢቦላ በሽታ በምዕራብ አፍሪካ በሚገኙ ሶስት አገሮች 11300 ያህል ሰው የጨረሰ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 4000 የሚደርሱት የሲየራሊዮን ዜጎች መሆናቸው ይታወቃል።





ጥር 25 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ሰኞ ተነስቶ በነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ምክንያት የቡታጅራ  ከተማ አሁንም ውጥረት ነግሶ የሚታይበት ሲሆን  ከወልቂጤ ተጠርቶ በመጣው የአግአዚ ጦርና የፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወደ ወልቂጤ ተወስደው የነበሩ አስራ ስድስት የሚሆኑት ሰዎች ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ያልተመለሱ መሆናቸውን  ከስፍራው ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የመሰንቃ ወረዳ አመራረሮችን ለመግደል ሙከራ አድርጋችኋል፤ የታጣቂዎችን መሳሪያ ለመንጠቅ ሞክራችኋል ፖሊሶች ላይ ድብደባ ፈጽማችኋል የሚል ክስ ለማቅረብ ቃላቸውን እንዲሰጡ የተደረገ መሆኑን ጉድዮን የሚያውቁ ምንጮች የገለጹ ሲሆን ሰኞ ለማክሰኞ አጥቢያ ከፍተኛ ድብደባ ሲፈጽምባቸው ያደሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

 

 

Ø ጥር 7 ቀን 2008 ዓም ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ በታንዛኒያ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ  83 ኢትዮጵያውያን ፍርድ ቤት ቀርበው እያንዳንዳቸው የሶስት ዓመት እስራት ወይም የአንድ ሚሊዮን የታንዛኒያ ሽልንግ (460 ዶላር) ካሳ እንዲከፍሉ የተፈረደባቸው  መሆኑ የታንዛኒያ የዜና ምንጮች ገልጸዋል።  ኢትዮጵያውያኑን በአነሰተኛ የጭነት መኪና አመላልሳችኋላ የሚል ክስ የቀረበባቸው ሁለት የታንዛኒያ ዜጎች እያንዳንዳቸው የአምስት አመት እስራት ወይም 1.5 ሚሊዮን የታንዛኒያ ሽልንግ (688 ዶላር) እንዲከፍሉ የተፈረደባቸው መሆኑ ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።  በተመሳሳይ መልኩ ከሁለት ቀን በፊት የዛምቢያ ፍርድ ቤት በ 33 ኢትዮጵያውያን ላይ የእስራት ፍርድ የፈረደ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን እነዚህ አገሮች በሰላማዊ ስደተኞች ላይ ይህን ዓይነት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እየወሰዱ ያሉት በወያኔ አገዛዝ  ግፊት ነው የሚል ግምት አለ። አገር ጥሎ ወደ ውጭ ለመውጣት ከፍተኛ ችግር ያለ ቢሆንም ኑሮው አስመርሮት ወደ ውጭ የሚወጡት ኢትዮጵያውያን በጣም በርካታ መሆናቸው ይታወቃል። በሊቢያ በኩል በአክራሪዎች መታረድና ውቅያኖስ ውስጥ ሰጥሞ መሞት እያለ፤ በአረብ አገሮች በኢትዮጵያውያን ሞትና ከፍተኛ የአካል ጉዳት የሚያስከትሉ ወንጀሎች እየተፈጸሙ፤ እንዲሁም በደቡብ አፍርካ የአደባባይ ግድያ ወደ ዚያም ለመሄድ በመንገድ ላይ መያዝና እስራት እያጋጠማቸው ስደተኞች አገራችውን አሁኑንም አገራቸው እየጣሉ መሰደዳቸው በወያኔ አረመናያዊ አገዛዝ ስር መኖር ምን ያህል አስከፊ መሆኑን ያሳያል ሲሉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ። 

 

Ø በጎንደር ታች ጋይንት የተባለው ቦታ በድርቅ የተጠቃ ሲሆን በአካብቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ከድርቁ በተጨማሪ ተላላፊ በሆነ ቆዳን በሚያሳክክ በሽታ ተጠቅተው እየተሰቃዩ መሆናቸውን  ከስፍራው የመጣ ዘገባ አስረድቷል።  በሽታው በወረርሽኝ መልክ የተከሰተ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት እስከ ትናንት ጥር 24 ቀን ድረስ ከሃያ ስድስት ሺህ በላይ ሰዎች በህመሙ እየተሰቃዩ መሆኑን አካባቢውን የጤና ተቋማት ከተገኘ መረጃ ለመረዳት ተችሏል። የወያኔ አገዛዝ በሽታውን ለመቆጣጠር  የተለየ ትኩረት ባለመስጠቱ በሽታው ሊስፋፋ እንደቻለ የሚናገሩ ወገኖች በርካታ ናቸው።

 

Ø ዛሬ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ሁለት ከፍተኛ ድምጽ ያላቸው ፈንጅዎች መፈንዳታቸው ታውቋል። ቦምቦቹ የፈነዱት በከተማዋ የንግድ እና የቢዝነስ ቀበሌ አካባቢ ሲሆን ቢያንስ አራት ሰዎች የተጎዱ መሆናቸውን የሚግለጹ ዘገባዎች ደርሰዋል። ቦምቡን ያፈነዳው ወገን ማን መሆኑና ለምን እንደፈነዳ ባይታወቅም ካለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀምሮ በብሩንዲ ውስጥ በተጻራሪ ኃይሎች መካከል በተጀመረው የእርስ በርስ ግጭት በርካታ ሰዎች መገዳላቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ መሰደዳቸው ይታወቃል።

 

Ø ዛሬ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም አንድ የሱማሌ የሕዝብ ማመለላሻ አውሮፕላን ተጎድቶ በአንድ አካሉ ላይ ክፍተት (ቀዳዳ) በመፈጠሩ  በረራ ከጀመረ በኋላ በአስቸኳይ እንዲያርፍ ተደርጓል። የዳሎ ኤር ላይንስ (Daallo Airlines) ንብረት የሆነው የመጓጓዣ አውሮፕላን 60 መንገደኞችን ጭኖ ይጓዝ የነበረው ወደ ጅቡቲ ሲሆን ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለቱ ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተዘግቧል። በአውሮፕላኑ አካል ላይ ትልቅ ቀዳዳ እንዲፈጠር ምክንያት የሆነው ምን እንደሆን ባይታወቅም አኮብኩቦ በረራ በጀመረ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ከአንድ አካባቢ እሳት የተያያዘ መሆኑን በውስጡ የነበሩ ተሳፋሪዎች ተናግረዋል። ዳሎ አኤር ላይንስ መሰረቱ ዱባይ ሲሆን ወደ ጂቡቲና ወደ ሶማሊያ የጉዞ አገልግሎት አለው።

በተመሳሳይ ዜና ዛሬ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ከተማ አንድ ቀላል አውሮፕላን ከአየር ላይ ወድቆ በመሰባበሩ በውስጡ የነበሩ ሶስት ስዎች ወዲያውኑ የሞቱ መሆናቸውን በመግለጽ  የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አውሮፕላኑን የጣለው ምክንያት ምን እንደሆን ለጊዜው ባይታወቅም  የአውሮፕላን አደጋ በጣም ዝቅተኛ ነች እየተባለ በሚነገርላት ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ይህ አደጋ መድረሱ ብዙዎችን አስገርሟል።  

 

Ø አንድ የግብጽ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀድም ብሎ ዝቅተኛው ፍርድ ቤት በ149 የእስልምና ወንድማማቾች አባላት ላይ ውስኖት የነበረውን የሞት ፍርድ ገልብጦ ሌላ የፍርድ ሂደት እንዲካሄድ የወሰነ መሆኑ ታወቀ። ተከሳሾቹ የዛሬ ሶስት ዓመት በአንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ጥቃት በማካሄድ አስራ አንድ የፖሊስ መኮንኖችን ገድላችኋል ተብለው የተከሰሱ ናቸው። ነሐሴ 8 ቀን 2005 ዓም በወቅቱ የፕሬዚዳንት ሞርሲን ከስልጣን መወገድና በግፍ መታሰር ተቃውሞ ሲያሰሙ በነበሩ የእስልምና ወንድማማቾች አባላት ላይ የጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ወስደው በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች መግደላችው ይታወቃል። በዚያኑ ቀን ከዴሳና ማንያ በተባሉ ቦታዎች ላይ በሚገኙ ሁለት የፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ተቃዋሚዎች ጥቃት አድርሰው 13 የፖሊስ አባላትን መግደላቸው ይታወሳል። ተከሳሾቹ የተከሰስቱ የፖሊስ ጣቢያዎችን ለማጥቃት በተደረጉ እርምጃዎች ላይ ተሳትፋችኋል የሚል ነበር። ከፍተኛው ፍርድ ቀደም ብሎ በዝቅተኛ ፍርድ ቤት የተሰጠውን ፍርድ ሽሮ በአዲስ መንገድ ይታይ ይበል መች እና በምን ዓይነት ሁኔታ ፍርዱ እንደገና እንደሚታይ አልተገለጸም።  

 

Ø በምዕራብ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያላገኘው ራሱን መንግስት ብሎ የሰየመው አካል የህግ አውጭ ምክር ቤት  በተመድ አማካይነት ሲካሄድ የነበረውን የእርቅ ስምምነት አለፈቃድና ህገወጥ በሆነ መንገድ ፈርመዋል በሚል  10 የሚሆኑ የምክር ቤት አባላቱን የአባረረ መሆኑ ተገልጿል። ባለፈው ታኃሳስ ወር በሞሮኮ በተደረገው የእርቅ ስብሰባ ላይ ያለፈቃደ የሥምምነት ፊርማ በማስቀመጣቸው ከስራ ከተወገዱት አስር አባላት ውስጥ የምክር ቤት ምክትል መሪ እንደሚገኙበት ታውቋል።  

 

 




ጥር 24 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ሰኞ ጥር 23 ቀን 2008 .. ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በቡታጅራ ከተማ የወያኔ ሹመኞች አፍራሽ ግብረ ኃይል ይዘው ሁለት የመኖሪያ ቤቶችን ለማፍራስ ሙከራ ባደረጉበት ወቅት ሕዝቡ ድርጊቱን በመቃወም  በአንድነት ወጥቶ በኃይል እንዳገዳቸው ተረድተናል፡፡ ወዲያው ከመቅጽበት ከአምስት ሕዝብ በላይ የሚገመት ሕዝብ በቁጣ ተምሞ በመውጣት ከተማዋን አጥለቅልቋታል፡፡  የግለሰብ  ትራክተሮችንና መኪናዎን  በመሀል መንገዱ ላይ በማቆም መንዱን ሙሉ በሙሉ የዘጉት ሙሆኑንም ከደረሰን ዜና መረዳት ቸለኛል፡፡ የሕዝብ ማመላለሻ መነሀሪያ ግቢ ውስጥ በመግባት የተቆጣው ሕዝብ በዚያ የሚገኙ ቢሮዎችና መለስተኛና መካከለኛ አውቶብሶች ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በርካታ ሕዝብሌባ፣ ሌባ ወያኔ ላባ!” እያለ መፈክር ያሰማ እንደ ነበር ከሥፍራው የደረሰን መረጃ ያስረዳል፡፡ ከከሰዓት በኋላ ጀምሮ የከተመዋ አራቱም መግቢያና መውጫ በሮች በሕዝቡ ተዘግተዋል፡፡ተቃዉሞዉ በተደረገበት ወቅት  ባንክ ቤቶች፣ቤንዚን ማደያዎች፣ሱቆች ምግብ ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውና ከሆሳእና፣ከአዲስ አበባ እና ከዝዋይ የሚያገናኘዉ ዋና መንገድ ተዘግቶ እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።ማምሻዉን የወያኔ አግአዚ ጦር ከወልቅጤ ከተማ መጥቶ ቡታጅራ የሰፈረ መሆኑ  ተዘግቧል።

 

Ø በአዲስ አበባ አስተዳደር ውስጥ በሙስና እና በአስተዳድር ጉድለት ተጨማልቀዋል የተባሉ ከአንድ ሽህ ስድስት መቶ በላይ የቀበሌና የወረዳ አመራሮች እና ሌሎች ሹማምንቶች ተነስተው በሌሎች የተተኩ መሆናችው የተገለጸ ሲሆን  በምትካቸው በትምህርት ወያም በአገልግሎት ጥራት ሳይሆን አፍቃሪ  ኢሃዴግነታቸው የተረጋገጠላቸው ግለስቦች የተመደቡ መሆናቸው ታውቋል። ስልጣን ሆነው ህዝብን ሲበድሉና ሲያስለቅሱ የነበሩና ተከሰው ፍርዳቸውን ማግኘት የሚገባቸው ሹማምንቶችን ቦታ መቀየር ወይም ከስራ መደብ ዝቅ በማድረግ ችግሩ ለመሸፋፈን የተደረገ መሆኑም ታውቋል።  በተያያዘ ዜና በተግራይ በተመሳሳይ መልኩ የይስሙላ የአስተዳደር እርማት እየተካሄደ ነው የተባለ ሲሆን 253 ግለሰቦች የሚሆኑ በአስተዳደር ጉድለት ክስ ይመሰርትባቸዋል ተብሏል። ብዙዎቹ በ23 ዓመት ጊዜ በርካታ የሕዝብ ሀብት በመስረቅ የከፍተኛ ሕንጻዎች ባለቤቶች መሆናቸው እየታወቀ የሚከሰሱት በሙስና ሳይሆን በአስተዳደር ጉድለት ብቻ መነገሩ የወያኔ ቁንጮ ባለስልጣኖች አገልጋዮቻቸውን ለመከላከል የወሰዱት ርምጃ ነው በማለት ታዛቢዎች ይናገራሉ።  

 

Ø በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገግልጎትን በሙሉ ቁጥጥር ስር ያደረገው ኢትዮ ቴሌኮም የተባለው መስርያ ቤት ሲሆን መስርያ ቤቱ በወያኔ መዳፍ ስር በመውደቁ ለሕዝብ የኢንተርኔት አገልግሎት በመስጠት ደረጃ አገሪቱ ዝቅተኛ ከሆኑት አገሮች መካከል አንዷ ሆና ተመድባለች። በኬኒያ 69.6 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ሲሆን በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት የሚዳረሰው 3.7 ለሆነው ሕዝብ ብቻ መሆኑን ተገለጿል። በጣም ዝቅተኛ የሆነ የመንግስት አገልግሎት የሚሰጥባት እና በጦርነት የተጠመደችው ደቡብ ሱዳን እንኳ ከሕዝቧ 15.9 የሚሆነው የኢንተርኔት አገልግሎት የሚደርሰው መሆኑ ተዘግቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ  በኢሜል እና በሌላ መልክ ግንኙነት የሚያደርጉ ሰዎች ምን ያህል እንደሆኑ ባይታወቅም የወያኔ አገዛዝ ስፓይ ዌር የተባሉትንና  እና ሌሎች የመከታተያ መንገዶችን በመጠቀም ከፍተኛ የስልላ ተግባሮችን የሚያከናውን መሆኑ ተዘግቧል።  \

 

Ø የአባይን ግድብ አስመልክቶ ጥናቶችን ለሚያካሂዱት ተቋሞች የሚከፈለውን የአገልግሎት ገንዘብ ግብጽ ሱዳንና የወያኔ አገዛዝ በጋራ የሚሸፍኑት መሆኑን ለግብጽ  የውሃና የመስኖ ሚኒስትር ከቀረበው ዘገባ ማወቅ የተቻለ መሆኑን ካዮሮ ፖስት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ ጥር 23 ቀን 2008 ዓም ባወጣው እትሙ ገልጿል። ጥናቱ ተገባድዶ ስምምነት እስኪደረግ ድረስ በግድቡ ገንዳ ውስጥ ውሃ የመሙላቱ ተግባር የሚዘገይ መሆኑም በተጨማሪ ተገልጿል።  ጥናቱን  እንዲያካሄዱ ኃላፊነት የተሰጣቸው ቢ አር ዔል እና (BRL) አረተሊያ (ARETELIA) የተባሉ የጥናት ተቋሞች ሲሆኑ በሶስቱ አገሮች ስም ከእነዚህ ተቋሞች ጋር ስምምነት የሚያደርገው የሕግ አካል መቀመጫው እንግሊዝ አገር የሆነውና ኮርቤት እና ኩባንያው የሚባለው የሕግና የጥብቅና ተቋም ነው ተብሏል። ሁለቱ አጥኝ ተቋሞች ከቴክኒክ አንጻር ጥናት ሊካሄድ የሚችላባቸውን መስኮች በመዘረዘር ያቀረቡት ረቂቅ ሀሳብ ለሶስቱም አገሮች የተላለፈ መሆኑ ታውቋል። በቀረበው ሀሳብ በሁሉም በኩል ስምምነት ካለ ተቋሞቹ የሚጠይቁትን የክፍያ መጠን ለየአገሮቹ እንደሚተላለፍ ተገልጿል። ተቋሞቹ ጥናቱን ከአንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አጠናቅቀው የሚያስረክቡ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን እስከዚያው ድረስ ግን በግድቡ ገንዳ የመሉላቱ ተግባር እንደሚዘገይ ታውቋል።

 

Ø በኢትዮጵያ የአንበሳ መንጋ ተገኘ። ቦርን ፍሪ ፋውንዴሽን በሚባል የእርዳታ ስጭ ድርጅት በመታገዝ አንድ የኦክስፎርድ  የእንሣት ተንከባካቢ ቡድን ሰሞኑን በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ አልጣሽ በረሃ  በሚባለው አካባቢ በቁጥር እስከ 200 የሚደርሱ የአንበሳ መንጋ ቡድን ማግኘቱን በአካባቢው ካደረገው ጉዞ በኋላ ባዘጋጀውና ትናንት ጥር 23 2008 ዓም ይፋ ባደረገው  ዘገባ ገልጿል። የአልጣሽ በረሃ የሚገኘው የጎንደርና የጎጃም ክፍለ ሀገርን በሚከፍለው የአይማ ወንዝ አካባቢ እና እስከ ሱዳን ግዛት የሚዘልቅ ሲሆን  አንበሶች በበረሃ ውስጥ መኖራቸው ቀደም ብሎ በአካባቢው ነዋሪ እንደሚታወቅ ግልጽ ነው። ባለፉት 20 ዓመታት በአፍሪካ የሚገኘው የአንበሶች ቁጥር በ42 ከመቶ የቀነሰ በመሆኑ በዚህ አካባቢ ከ200 በላይ የሚሆኑ አንበሶች በቡድኑ መገኘታቸው  ተስፋ የሚሰጥ ዜና ነው ተብሏል። አንበሶችን ለመታደግና ለመንከባከብ ከወያኔ አገዛዝ ከሱዳን ባለስልጣኖች ጋር በርካታ ስራዎች መስረት እንደሚያስፈልግ ድርጅቱ አሳስቧል።  

 

Ø ባለፈው እሁድ ጥር 22 ቀን በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የተደረጉት የቀድሞ የኡጋንዳ የጸጥታ ኃላፊ ጄኔራል ሰጁሳ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸው ተገለጸ። ጄኔራሉ የሙሰቪኒን ፖሊስ በመቃወም የሚታወቁ ሲሆን ከዋናው አዛዥ መመሪያ ውጭ በፖለቲካ ስብስባዎች ላይ ተገኝተዋል፤ ያለፈቃድ ከስራቸው ላይ ቀርተዋል፤ በፓርቲ ፖሊቲካ ውስጥ ተሳትፈዋል የሚሉ ክሶች ተሰንዝረውባቸዋል። ከሶስት አመት በፊት ጄኔራሉ የሙሰቭን አገዛዝ በመቃወም ወደ እንግሊዝ አገር መሰደዳቸው የሚታወቅ ሲሆን ከ18 ወራት ቆይታ በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰው ነበር።ከሰላሳ አመት በላይ በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚዳንት ሙሰቨኒ የሚወዳደሩበት ብሔራዊ ምርጫ  በሚቀጥለው ወር ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሰባት ተወዳዳሪዎች በተቀዋሚነት ተሰልፈዋል። ጄኔራሉ ፕሬዚዳንቱን የሚቃወሙና ተቃዋሚዎችን የሚደግፉ ነበሩ።

 

Ø የናይጄሪያ ጸረ ሙስና ተቋም አባላት የቀድሞ የናይጀሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት የሚስተር ናማዲ ሳምቦን ቤት ሰብረው በመግባት ፍተሻ ያካሄዱ መሆናቸው ታውቋል። የቀድሞ የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሳሪያ ግዥ ሰበብ ከፍተኛ ጉቦ በልተዋል ተብለው የሚጠረጠሩ ሲሆን ቤታቸው በተበረበርት ወቅት አገር ውስጥ ያልነበሩ መሆናቸው ተዘግቧል። በቀድሞ አስተዳደር ወቅት ከናይጄሪያ 2 ቢሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ መዘረፉ የታወቀ ሲሆን ባለፈው ታኅሳስ ወር የቀድሞ የናይጄሪያ የጸጥታ አማካሪ 68 ሚሊዮን ዶላር በመዝረፍ መከሰሳቸው ይታወሳል። ሚስተር ናማዲ ስለጉዳዩ እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።     

 


ጥር 23 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø  እሁድ ጥር 23 ቀን 2008 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ዓም ከአፊሪካ ህብረት ስብሰባ ጎን ለጎን እየተካሄደ በነበረው የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ አገሮች ተወካዮች ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባሰሙት ንግግር የዓለም አቀፉ ህብረተሰብ በችግር ጊዜ ከኢትዮጵያ ጎን መቆም አለበት ካሉ በኋላ በአገሪቱ ውስጥ የገባውን ድርቅ ለመቋቋም እርዳታ ሰጭ አገሮች የሚሰጡትን የእርዳታ መጠን ከፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። ዋና ጸሐፊው ንግግራቸውን በመቀጠል በአሁኑ ወቅት በጦርነትና በሌላም መልክ እርዳታ የሚጠይቀው ሕዝብ ቁጥር  ከፍተኛና ችግሩም ረጅም ጊዜ ሊቆይ የሚችል መሆኑን ገልጸው በኢትዮጵያ የገባው ድርቅ በአሁኑ ወቅት ከባድ ቢሆንም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሊያልፍ እንደሚችል ተናግረዋል። ችግሩ እስኪያልፍ ድረስ ግን የበርካታ ወገኖችን ህይወት ሊያጠፋ ስለሚችል አሁኑኑ በእርዳታው ላይ መረባረብ ያስፈልጋል  ብለዋል።  በዚያኑ ዕለት ዋና ጸሐፊው ድርቅ ወደ አጠቃው ወደ ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ  ሄደው በዚያ የሚገኘውን የጤና ጣቢያ፤ የውሃ ጉድጓድና የእርዳታ ስርጭት ጣቢያን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአለም ባንክ ከአካባቢው ኃላፊዎች ጋር በመተባበር እያከናወኑ ያሉትን ተግባር እንዲሁም ሕዝቡ ኑሮውን ለመቋቋም እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል። ችግሩ የሚያልፍ መሆኑን ጠቁመው  ድርቁን ለመቋቋም ተመድ የተቻለውን ያህል እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።  እስካሁን ድረስ ተመድ 25 ሚሊዮን ዶላር የሰጠ ቢሆንም ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። የአሜሪካ የዩስ ኤድ ተወካይ በትናንትናው ዕለት አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ አሜሪካ 97 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ለመስጠት ቃል መግባቷን አስታውቀዋል። ድርቁን ለመቋቋም የተገመተው ገንዘብ 1.4 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን እስካሁን የተሰጠው አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø  በዛምቢያ መንግስት ታስረው የነበሩ 33 ኢትዮጵያውያን የአስራ አምስት አመት እስራትና እንዲቀጡና ከባድ ስራዎች እንዲሰሩ የተፈረደባችው መሆኑን ዛምቢያ ታይምስ የተባለው ጋዜጣ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2008 ዓም ባወጣው እትሙ ገልጿል። ከኢትዮጵያውያኑ  ጋር አንድ የዛምቢያና  አንድ የዚምባውየ ዘጎች በህገ ወጥ መንገድ ሰዎችን ለማስተላለፍ አስተባባሪ ሆናችኋል በሚል ወንጀል ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ኢትዮጵያውያኑ ወደ ዛምቢያ የገቡት ከህዳር 18 ቀን 2007 ዓም እስከ ህዳር 25 ቀን 2007 ዓም መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን ህገ ወጥ ዝውውርን የሚከለከለውን ህግ በመተላለፍ እና ራሳቸው የዝውውሩ አካል ለማድረገ ፈቃደኛ መሆኑ በሚል ወንጀል ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ከ33 ቱ ኢትዮጵያውያን መካከል ሁለት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ህጻናት እንደሚገኙበት ታውቋል። ለዜጎቹ ደህንነት ደንታ የሌለው የወያኔ አገዛዝ አለአግባብ ፍርድ ለተፈረደባችው ኢትዮጵያውያን ድምጹን ያላሰማ ሲሆን ምናልባትም ዜጎቻችን በዚህ ዓይነት የግፍ ፍርድ እንዲቀጡ ሳይገፋፋ አይቀርም የሚለው ግምት ከፍተኛ ነው።

 

 

Ø  በአቃቂ ክፍለ ከተማ ገላን በተባለ ቦታ 34 ሚሊዮን በላይ ብዛት ያላቸው የኮብል ስቶን ድንጋዮችን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ኃላፊዎች በገረጋንቲ መልክ በሚስጥር ሊሸጡ መሆናቸው ተደረሰበት። በገንዘብ ሲተመን  ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣል ተብሎ የሚገመተው የከብልስቶን ድንጋይ ክምችት  ደረጃውን ያልጠበቀ ነው በሚል   ከሁለት አመት በላይ ያለ አገልግሎት ተቀምጠው እነደነበር ታወቋል። ይህን አጋጣሚ በመጠቀም የመስሪያ ቤታቸው መዋቅር ሳያውቅና ስውር በሆነ መንግድ ይህንኑ የተከማቸ ኮብልስቶን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሹማምንቶች  በገረጋንቲ መልክ ለኮንስትራክሽን ድርጅቶች አየር በአየር ሊሸጡ መሆናቸውንና የታወቀ ሲሆን  ከወዲሁ ገዥ በሚያመጡና ፊትለፊት ቆመው በሚያስጭኑት መካከል የአንበሳው ድርሻ ይገባኛል በሚለው ላይ ንትርክ የያዙ መሆናቸውን ለማረገገጥ ተችሏል።

 

 

Ø  የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ትናንት እሁድ ጥር 22 2008 ዓም የተጠናቀቀ ሲሆን የቻዱ ፕሬዚዳን ኢድሪስ ዴቢ እና የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ካጋሜ ለቀጣዩ ዘመን የአፍርካ ህብረት ፕሬዛዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ታውቋል። ለሁለት ቀን የቆየው የመሪዎች ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተነጋገረ ሲሆን ከዚህ በፊት የአፍሪካ ህበረት 5000 የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትን ወደ ብሩንዲ ለመላክ ያደረገውን ውሳኔ ሽሮ በምትኩ በተጻራሪ ወገኖች መካከል የእርቁ ውይይት የሚካሄድበትን ሁኔታ እንደሚያጠናክር ወስኗል። የአፍሪካ አገሮች ከዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት እንደወጡ በኬኒያው ፕሬዚዳንት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በርከት ያሉት የደገፉት ቢሆንም እያንዳንዱ አገር የመሰለውን ርምጃ ይውሰድ የሚል ስምምነት ደርሷል።

 

Ø  የደቡብ ሱዳን መንግስት ውታደሮች በቁጥጥር ስር የነበሩ ቁጥራቸው 50 የሚደርስ የደቡብ ሱዳን ዜጎችን በእቃ ማጓጓዥ በርሚል ኮንቴነር ውስጥ በሙቀት አፍነው የገደሏቸው መሆኑን የተኩስ አቁም ስምምነቱን የሚታዘበውና የሚከታተለው ቡድን ለአፍሪካ ህበረት ስብሰባ ባቀረበው ዘገባ አጋልጧል። የጋራ ክትትልና ግምገማ ኮሚሽን ተብሎ የተሰየመውና ከተለያዩ አገሮች የተውጣጣው ቡድን እሁድ ጥር 22 ቀን 2008 ዓም ለአፍሪካ ህበረት ስብሰባ ባቀረበው ዘገባ ድርጊቱ የተፈጸመው ባለፈው ጥቅምት ወር መሆኑን ገልጾ በመንግስት ወታደሮች የተወሰደ የበቀል እርምጃ ነው ብሏል።  የደቡብ ሱዳን ወታደሮች የብረት ኮንቴነሮች እንደእስር ቤት የሚጠቀሙበት መሆኑንና የአየሩ ሙቀት 40 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በሚደርስበት ሁኔታ እስረኞች ከፍተኛ ስቃይ የሚደርስባቸው መሆኑ ተጠቁሟል። ዘገባው በመንግስት ወታደሮች የተፈጸሙትን የግድያ፤ አስገድዶ የመድፈር እና የዝርፊያ ወንጀሎችን በዝርዝር አቅርቧል። ከደቡብ ሱዳን መንግስት ለዘገባው የተሰጠ መልስ ባይኖርም የመንግስቱ ቃል አቀባዮች ቀደም ብሎ የቀረቡትን ተመሳሳይ ክሶች ሳይቀበሉ መቆየታቸው አይዘነጋም።

 

Ø  በአሁኑ ወቅት የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በዓለም ገባያ በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሱ ናይጀሪያ የ 11 ቢሊዮን ዶላር የበጀት እጥረት የሚያጋጥማት መሆኑን ገልጻ ዓለም ባንክ ርዳታ እንዲያደርግላት የቅድሚያ ውይይት ለማካሄድ ማሰቧን ገልጻለች። የአለም ባንክ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጥ የተጠየቀ መሆኑን የድርጅቱ ባለስልጣኖች የገለጹ ሲሆን  ከአፍሪካ ልማት ባንክ ደግሞ አንድ ቢሊዮን ዶላር መጠየቁ ታውቋል።

በተያያዘ ዜና የናይጄሪያ መንግስት ከዚህ በፊት በጦርነት ላይ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ተከሰው በጡረታ ተገልለው የነበሩትን ሜጀር ጄኔራል አህማዱ ሙሐመድ እንደገና ወደ ስራቸው እንዲመለሱ በማድረጉ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለውና ሌሎች የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸው ተዘግቧል። ከሁለት ዓመት በፊት ለቦኮ ሃራም ጥቃት የአጸፋ መልስ ለመመልስ ጄኔራሉ 640 የሚሆኑ የታሰሩ ሰዎችን  ከአስር ቤት አውጥተው ያለፍርድ ገድለዋል የሚል ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታወሳል። ባለፈው ዓመት የተመረጡት የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ጄኔራሉ በተከሰሱባችው ጉዳዮች ላይ ምርመራና ማጣራት  እንደሚደረግ ቃል የገቡ ቢሆንም ጄኔራሉ  ወደ ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ ማድረጋቸው ብዙዎችን አስገርሟል።    




ጥር 21 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ጥር 19 ቀን ማምሻውንና በነጋታው ጥር 20 ቀን 2008 ዓም  የወያኔ አግአዚ ጦር በወለጋ ዩኒቨርስቲ ቀን  በሴቶች መኖሪያ በመግባት ክፉኛ ድብደባ መፈጸሙን ከስፍራው የተገኘው መረጃ ገልጧል። በድብደባው በርካታ ተማሪዎች የተጎዱ ሲሆን ሌሎችም ከአደጋው ለማምለጥ ወደ አካባቢው ጫካዎች መግባታቸው ተሰምቷል። አመጹ ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አልፎ ወደ ከተማው ሕዝብም የገባ መሆኑን አንዳንድ ዜናዎች ይጠቁማሉ። በትናነትናው ዕለት በወለጋ የተለያዩ ቦታዎችና በሸዋ ኦቦቴ ተማሪዎች ተቃውሞ ሲያደርጉ የዋሉ መሆናቸው ከተለያዩ ቦታዎች የተገኙት ተጨማሪ ዜናዎች ይጠቁማሉ።

 

 

Ø ከጋምቤላ አካባቢ በተከታታይ  ከሚደርሱ ዜናዎች ማግኘት እንደተቻለው  ካለፈው ሐሙስ ጥር 19 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የዘለቀው የኑዌርና የአኝዋክ ጎሳዎች ግጭት የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ግጭቱ ተጀመረ የተባለው የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት ቀደም ብሎ በነዌር ብሔረ ሰብ አባል ለተገደለው ዜጋ የበቀል እርምጃ ሲወስዱ ነው ቢባልም ሆን ተብሎ በወያኔ የተጠነሰሰ ሴራ ነው የሚለው  ጥርጣሬ ሰፊ ነው። ሐሙስ ጥር 19 ቀን 2008 ዓም   የኑዌር ብሔረሰብ አባል የሆነውና በጋምቤላ የገጠር መንገዶቸ ቢሮ ምክትል ኃላፊ የነበረው ሰው የተገደለ ሲሆን አርብ ጥር 20 ቀንም በአካባቢው ኮሌጅ ውስጥ በተጣለ ቦምብ የኑዌር ብሔረሰብ አባላት መጎዳታቸው ታውቋል። እስር ቤት ተሰብሮ ከሃያ በላይ የሚጠጉ እስረኞች የተገደሉ መሆናችውና በእርስ በርስ ግጭቱ በርካታ ሰዎች መሞታቸው ከአካብቢው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የኑዌር ብሔረሰብ አባላት ከወያኔ የአግአዚ ጦር ጋር በመደባለቅ በወሰዱት እርምጃ መላው የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት የጋምቤላን ከተማ ለቀው መሰደዳቸው ተነግሯል። ከሞቱት ሌላ በጥይት የቆሰሉና ህክምና ያላገኙ ዜጎች በየመንገዱ ዳር ወድቀው መገኘታቸውን ዘገባው አመላክቷል። በጋምቤላ ሰፍሮ የሚገኘው የወያኔ አግአዚ ጦር  ከጥር 20 ቀን 2008 ዓ/ም እኩለ ቀን በኋላ ጀምሮ በከተማዋ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰማርቶ ቁጥጥር ማድረግ የጀመረ ሲሆም ከዚያን ወቅት ጀምሮ ጋምቤላ በወያኔው የፌዴደራል ቁጥጥር ስር ወድቃ በቀጥታ ከአዲስ አበባ መመሪያ እየሰጠባት ትገኛለች። ወያኔ የአኝዋክ ብሄረሰብ ነጥሎ ለመምታት ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት የጎሳ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ተንኮል ሲፈጥር የነበረ መሆኑ የተዘገበ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ ይኽም ግጭት እንዲጀመር የወያኔ እጅ አለበት የሚሉ በርካታ ናቸው።

 

 

Ø የአባይ ውሃ ተፋሰስን ሁኔታ እንዲያጠኑ ኃላፊነት ተሰጥቷቸው የነበሩ ቢአር ኤል እና አረተሊያ(BRL and Artelia)  የተባሉ ሁለት የፈረንሳይ አጥኝ ተቋሞች ከቴክኒክ አንጻር ጥናታቸው ሊያካትት የሚችለውን ጉዳዮች አስመልክቶ ሁለት ሃሳቦች ያቀረቡ መሆናቸውን የግብጽ የመስኖ ጉዳይ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሳን ሞጋዚ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ጨምረው እንዳስረዱት በጥናት ተቋሞቹ ከቀረቡት ሀሳቦች መካከል አንደኛው ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳንና ግብጽ የሚፈሰው ውሃ ላይ ግድቡ ሊያደርስ ስለሚችለው ችግር ማጥናት መሆኑንና  ሁለተኛው በአጠቃላይ በአካባቢው የአየር ሁኔታ እና እጸዋት ላይ ስለሚመለከተው ጥናት ጉዳይ  መሆኑን ጠቅሰው የግብጹ የቴክኒካል ኮሚቴ ጉዳይ በቅድሚያ ከተነጋገረበት በኋላ   ለሶስቱ አገሮች ኮሚቴዎች ቀርቦ ውይይት የሚደረግበት መሆኑን ተናግረዋል።   ቀደም ብሎ በተሰጠው መግለጫ መሰረት ጥናቱ በሚቀጥለው የካቲት ወር ተጀምሮ ለአስራ አንድ ወራት እንደሚቆይ መጠቀሱ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በማያያዝ በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሰደር የሆኑት አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ  እስካሁን ድረስ ህግ ተላልልፏል የሚል ሀሳብ ግብጽ የሌላት በመሆኑ በወያኔ አገዛዝ ላይ ጥቃት ታነሳለች የሚለው ወሬ መሰረት ቢስ መሆኑን ገልጸው ግብጽ በአለም አቀፍ ደረጃ ጉዳዩን ለማቅረብና ለመታገል ግን ሙሉ መብት አላት ብለዋል።

 

Ø በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ዛሬ ቅዳሜ ጥር 21 ቀን 2008 ዓም የጀመረ ሲሆን ህብረቱ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ስብሰባ ላይ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ስምምነት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው ከሚነጋግርባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሩንዲ ጉዳይ ሲሆን ከዚህ በፊት 5000 የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ ለመላክ ወስዶት የነበረውን አቋም ሊለውጥ እንደሚችል የሚጠቁሙ ጉዳዮች አሉ ተብሏል። የህብረቱ የሰላምና የጸጥታ ካውንስል ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት የታንዛኒያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለጉዳዩ ከጋዜጠኖች በተነሳ ጥያቄ ላይ መልስ ሲሰጡ አሁኑ ጉዳዩ ወደ ብሩንዲ ጦር መላክና አለመላክ ሳይሆን ተጻራሪ ኃይሎች ሊታረቁ የሚችሉበትን ሁኔታ መፍጠር ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በስብሰባው ለመገኘት አዲስ አበባ የተገኙት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን በዛሬው ዕለት ባደረጉት ንግግር በብሩንዲ የሚካሄደው ግድያ መቆም ያለበት መሆኑን ጠቅሰው  ግድያውን ለማስቆም የሰላም አስከባሪ ኃይል መላክ ያስፈልጋል ብለዋል። የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የህብረት አባሎችን ሁለት ሶስተኛ ድምጽ ማግኘት አስፈላጊ ሲሆን ይህ ድምጽ መገኘቱም ሆነ  አለመገኘቱ እንዲሁም ለሰላም አስከባሪው ኃይል  ወታደሮችን ለመላክ የትኞቹ አገሮች ፈቃደኞች እንደሚሆኑ አልታወቀም።  በተጨማሪም የአፍሪካ ህበረት ስብሰባ ይነጋግርበታል የተባለው የደቡብ ሱዳን ሁኔታን ሲሆን ተሰብሳቢዎች ምን ዓይነት ቁርጥ አቋም እንደሚወስዱ አልታወቀም። የብሩንዲው ፕሬዚዳንት እንኩርንዚዛም ሆነ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በስበሰባው አልተገኙም።  በደቡብ ሱዳን፤ በብሩንዲ፤ በሳህል፤ በሊቢያ፤ በቻድ ባህር  ወዘተ… አካባቢ ያለቱን የጸጥታ ሁኔታዎች ስብሰባው ሊቃኝ የሚችል የተለያዩ ምንጮች የጠቆሙ ሲሆን በቅርቡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች የተነሱትን ሕዝባዊ አመጾች ለመቋቋም በወያኔ አግአዚ ወታደሮች በግፍና የተገደሉትን ዜጎች ጉዳይ ግን ስብሰባው የሚያነሳው አይመስልም።

 

Ø ሰሞኑን በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የተሰማሩ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ህጻናትን አስገድደው ደፍረዋል የሚል አዲስ መረጃ መገኙትን የተመድ ኃይላፊዎች ሰሞኑን የገለጹ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን ይህንን ተከትሎ የፈረንሳይ መንግስት ከፍተኛ ምርመራ እንዲደረ መመሪያ መስጠቱን  አስታውቋል። ከዚህ በፊት ክስ የቀረረባቸው የፈረሳይ ወታደሮች ጉዳይ  ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን በቅርቡ የተሰነዘሩት ክሶችንም አስመልክቶ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል። በተመሳሳይ መንገድ የጆርጂያ መንግስትም ተመሳሳይ ምርመራ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።  

 

Ø በሶርያ ዋና የተቃዋሚ ክፍል ነው የሚባለው ቡድን ቅዳሜ ጥር 21 ቀን በጄኔቫ ለመካሄድ ታቅዶ በነበረው ስበሰባ እንደማይገኝ ቀደም ብሎ ማስታወቁ የሚታወቅ ሲሆን ተወካዮቹ አርብ ዕለት በሰጡት መግለጫ በሰብአዊ እርዳታ ሁኔታ ላይ የቀረቡት  ጥያቄዎች  መመለስና አለመመለሳቸውን ለማረጋገጥ ወደ ጄኔቫ የሚሄዱ መሆናቸው ገልጸዋል። አስራ ሰባት አባላት የሚገኙበትና በሳኡዲ አረቢያ የሚደገፈውና የሚረዳው ቡድን አባላት በዛሬው ዕለት ጄነቫ እንደሚገቡ ይጠበቃል። የቡዱኑ መሪ ፋራህ አታሲ አርብ ጥር 20 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ስብሰባው ላይ ለመገኘት ቡድኑ ቀደም ብሎ የሶሪያ መንግስት እያካሄደ ያለውን  የአየር ድብደባ እንዲያቆም፤ የስብአዊ እርዳታዎች ለሕዝብ እንዲደርሱ የሚሉት ቅድመ ሁኔታዎች አሁንም ያሉ መሆናቸውን ገልጸው  ወደ ጄኔቫ የሚሄዱት  ለድርድር ሳይሆን ከተመድ ባለስልጣኖች ጋር ስለሁኔታው ለመነጋገር ነው ብለዋል። በስብሰባው አካባቢ የሚገኙት የሩሲያ መልክተኛ  በአሁኑ ወቅት ቀጥታኛ ድርድር የማይደረግ መሆኑን እና  ተጻራሪ ኃይሎች የሚነጋገሩት በተዘዋዋሪ በሶስተኛ ወገን አማካይነት መሆኑን ገልጸው ለውይይቱ ምንም ዓይነት ቅደመ ሁኔታ አልተደረገም ብለዋል።     

 

 

  

 




ጥር 20 ቀን 2008 ዓ.ም
 

Ø ትናንት ጥር 19 ቀን 2008 ዓ/ም በደብረ ጽጌ ከተማ ሕዝባዊ ቁጣ ተቀስቅሶ በተፈጠረው ግጭት ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ ሰላማዊ ዜጎች በወያኔ ፖሊስ ታፍሰው መወሰዳቸው ከስፍራው የመጣ ዘገባ ገልጧል። ተማሪዎችና የከተማው ሕዝብ በከተማው የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ “ወገኖቻችንን  በግፍ የገደሉት ለፍርድ ይቅረቡ”፣ “የጅምላ እስራት ይቁም”፣ “ያለሃጢአታቸው የታሰሩ በአስቸኳይ ይፈቱ” የሚሉትን መፈክሮች ሲያሰሙ የነብረ ሲሆን  የወያኔ የአግአዚ ወታደሮች ሰልፉን ለመበተን የእሩምታ ተኩስ መክፈታቸውና  ቁጥራቸው ከሃምሳ በላይ የሚገግመት ሰልፈኞችን አፍነው  ወዳልታወቀ ስፍራ የወሰዷቸው መሆኑ ታውቋል። በተያያዘ መረጃ በምዕራብ ሀረርጌና በምስራቅ ሀረርጌ ሕዝባዊ ቁጣው ተጋግሎ ከትናንት በስቲያ ረቡዕ እና ትናንት ሀሙስ የቀጠለ መሆኑን መረጃዎች እየደረሱ ሲሆን  እንደተለመደው የወያኔ የአግአዚ ወታደሮች  በሰለማዊ መንገድ ጥያቄዎች  ያቀረቡ ወገኖችን ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዳቸውን  የአይን እማኞች ተናግረዋል።

 

Ø በናዝሬት እየተካሄደ ያለው የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ በከፍተኛ ውዝግብ እና አለመግባባት ላይ መሆኑን ከስብሰባው አካባቢ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የስበሰባው ዋና አጀንዳ የኦህዴድ ከፍተኛ ሹማምንቶችን መገምገም  የነበረ ሲሆን የድርጅቱ የጽህፈት ቤተ ኃላፊ ዳባ ደበሌ እና የክልሉ ፕሬዚዳንት ሙክታር ከድር ህዝባዊ ተቃውሞውን ለማስቆም ሲወሰድ በነበረው እርምጃ ላይ የነቃ ተሳትፎ አላደረጉም በሚል ተወንጅለው እየተገመገሙ መሆናቸው የተገኘው ዜና ይገልጻል። አመጹን የቀሰቀሱትና  እርምጃም እንዲወሰድ ያደረጉት ራሳቸው የኦህዴድ ባለስልጣኖች ናቸው በማለት ተጠያቂነቱን በኦህዴድ  ላይ ለማላከክ የወያኔ ባለስልጣኖች የኦሮሞ ተወላጆችን ለማሳመን ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ቀደም ብሎ የተዘገበ መሆኑ ይታወሳል። በስብሰባው ላይ ወያኔ የኦህዴድን ባለስልጣኖች እርስ በርስ በማጋጨት ቀደም ሲል የጀመረውን ተንኮል በተግባር እያዋለ ነው የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው።  በአዳማ/ናዝሬት ቀንና ሌሊት እየተካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባውን ማስተር ፕላን መሰረዝ አስመልክቶ ሙክታር ከድር በአመራር ብቃት ማነስና አቋምን በጽናት ተግባራዊ ለማድረግ አለመቻል በሚል ግምገማ ተጠያቂና ጥፋተኛ ነኝ የሚል ግለሂስ እንዲያቀርብ የሚገደድ መሆንና ምናልባት ከኃላፊነት ሳይነሳ አይቀርም የሚለው ግምት እየተሰራጨ ይገኛል።  ከበስተጀርባ አባይ ጸሃዬን ጨምሮ ከፍተኛ የወያኔ ባለስልጣኖች ግምገማውን እየተከታተሉት እንደሆኑ  የደህንነት ምንጮች አክለው ገልጸዋል።  

 

Ø በጎንደር …. በደሴ  … በጎጃም …. በደቡብ ወሎና …. ሰሜን ወሎ ቀደም ብለው የነበራቸውን የትምህርት ደረጃ አሻሽለው ለደረጃ እድገት ያመለከቱ መምህራን ጥያቄያችው ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከፍተኛ ምሬትና ብስጭት ውስጥ መሆናችው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የደሞዝ ጭማሪ ለማግኘትና ህይወታቸውን ለማሻሻል በራሳቸው ወጪ ተምረው የትምህርት ደረጃቸውን ከሰርተፊኬት ወደ ዲፕሎም፤ ከዲፕሎም ወደ ዲግሪ ለማሳደግ የቻሉ መምህራን የደረጃ መሻሻል እንዲደረግላቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም የበጀት እጥረት ስላለ የተሻሻለ የትምህርት መረጃችሁን ተቀብለን ደረጃችሁን አናሳድግም የሚል መልስ የተሰጣቸው መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል።

 

Ø ጥር 15 ቀን 2008 ዓም ምሽትና በማግስቱ ጥር 16 ቀን 2008 ዓ/ም በሬክተር ስሌት 4 ነጥብ 3 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሳ ከተማ ከደረሰ በኋላ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ተማሪዎች በህክምና ሲረዱ ቆይተው ህይወታቸው ማለፉና ዩኒቨርስቲው ለተከታታይ አምስት ቀናት ትምህርት ያቆሙ መሆናቸውን ከስፍራው የመጣ ዘገባ ገልጧል። የመሬት መንቀጥቀጡ በደረሰ የመጀመሪያው ቀን ከኤሌክትሪክ የተነሳ የእሳት አደጋ በዩኒቨርስቲው ግቢ ሲከሰት ከቃጠሎው ራሷን ለማትረፍ ከሶስተኛ ፎቅ ላይ በመዝለል ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባት የነበረችውን ተማሪ ጨምሮ በቤተ መጻህፍት ውስጥ ሳለ ጣራው ተንዶ በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት ደርሶበት የነበረው ተማሪ በህክምና ሲረዱ ቢሰነብቱም የሁለቱም ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ከአገኘነው ዘገባ ማወቅ ተችሏል። ትናንት ጥር 19 ቀን 2008 ዓ/ም አሁንም የመሬት መንቀጥቀጥ ድምጽ እየተሰማ ነው በማለት በይፋ ትምህርት እንዲቆምና ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ ጥያቄ ለማቅረብ ተሰባስበው በነበሩ ተማሪዎች ላይ ፖሊስ ጥይት መተኮሱና ከተኩሱ ለማምለጥ  በተፈጠረው ግፊያ በተማሪዎቹ ላይ መጠነኛ ጉዳት ሳይደርስ እንዳልቀረ  ታዛቢዎች ይናገራሉ።

በተያያዘ ዜና በህክምና ሲረዳ የነበረውና ህይወቱ ያለፈው የአንደኛው ተማሪ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራው ጋምቤላ አሸኛኘት ለማድረግ ተማሪዎች እና መምህራን የትራንስፖርት ገንዘብ ሲያሰባስቡ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።      

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው መግለጫ በምዕራብ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ህጻናትን አስገደደው መድፈራቸውን የሚመለከት አዲስ ክስ የቀረበባቸው መሆኑን ገለጹ። ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 16 የሚደርሱ ልጅ አገረዶች የአውሮፓ አገሮችን በመወከል በሰላም አስከባሪ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ የጂኦርጂያ ወታደሮች አስገድደው እንደደፈሯቸው ሰሞኑን የተመድ ባለስልጣኖች ባካሄዱት ምርመራ ለማወቅ የቻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የሰባት ዓመት ሴት ልጅና የዘጠኝ አመት ወንድ ልጅ በፈረንሳይ ወታደሮች ተደፍረናል በማለት ክስ አቅርበዋል ተብሏል። የተባሉት ወንጀሎች የተፈጸሙት በ2006 ዓም ሲሆን በዋናዋ ከተማ በባንጉዊ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢው የሰፈሩትን ተፈናቃዮች በሚጠብቁ ወታደሮች ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አልሁሴን  ዘገባውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ሁኔታው ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ታኅሣሥ ወር አንድ ገለልተኛ የሆነ አጣሪ ቡድን የ ሰላም አስከባሪ አባላት  በመካከለኛው አፍሪካ ሪፕብሊክ ዜጎች ላይ ስለፈጸሙት ወንጀል ተመድ ምንም የወሰደው ርምጃ አለመኖሩን በመጥቀስ ወቀሳ ማቅረቡ ይታወሳል።

 

Ø አምነስቲ የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ዛሬ ጥር 20 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በብሩንዲ በመንግስት ወታደሮች ተገድለው በአንድ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ የተቀበሩበትን ቦታ የሚያሳይ የሳተላይት ምስል ማረጋገጫ አግኝቻለሁ የሚል መግለጫ ሰጥቷል። ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ ከዚህ በፊት በመንግስት ወታደሮች የተገደሉ ዜጎች ቡሪንጋ በሚባለው በዋናው ከተማ ዳርቻ በአምስት የተለያዩ ቦታዎች  በጅምላ ተቀብረዋል በማለት የአይን እማኞች የሰጡትን ምስክርነት በታኅሣሥ ወር ለተከታታይ ቀናት በሳተላይት ከተነሱ ፎቶግራፎች የተገኘው መረጃ ያረጋግጣል ብለዋል።  በታኅሣስ ወር ውስጥ በመንግስት ወታደሮች ተገድለው በአንድ ጉድጓድ ውስጥ የተጣሉት ሰዎች ቁጥር 87 ይደርሳል ተብሎ የተገመተ ሲሆን ከሳተላይቱ የፍቶግራፍ ምስል የተገኘው መረጃ ባለስልጣኖቹ የወንጀሉ ሚስጥር እንዳይወጣ ለመደበቅ ያደረጉትን ጥረት ያጋልጣል ተብሏል። የብሩንዲ የውስጥ ችግር ከጀመረ ከአለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀመሮ 439 ዜጎች መገደላቸውና ከ240 ሺ በላይ የሚሆኑት አገር ጥለው የተሰደዱ መሆናቸው ተዘግቧል።

በተያያዘ ዜና ብሩንዲ ውስጥ  አንድ የፈረንሳይ ዜጋ የሆነ የለሞንድ ጋዘጠኛና አንድ  እንግሊዛዊ ፎቶግራፍ አንሺ ለታጠቁ ወንጀለኞች ተባባሪ ሆናችኋል በሚል ክስ ከሌሎች አስራ ሰባት የአገሪቱ ዜጎች ጋር  የታሰሩ መሆናችወን ዛሬ ጥር 20 ቀን 2008 ዓም የብሩንዲ ባለስልጣኖች ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።  የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዛሬው ቀን በሰጡት መግለጫ  የተያዙት ጋዜጠኞች ለረጅም ጊዜ ስለአገሪቱ ሁኔታ በገለልተኛነት ሲዘግቡ የቆዩ መሆናቸውን ገልጸው  ባስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።

 

 

 

 



ጥር 19 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የአለም የምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ሚስተር አይሊየፍ ትናንት ጥር 18 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋምና እስከ ሚያዚያ ወር ድረስ ያሉትን የእርዳታ ፕሮግራሞች ለመሸፈን  በሚቀጥለው ወር ተሰብስቦ ማለቅ ያለበት የ500 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ባስቸኳይ የሚያስፈልግ መሆኑን ገልጸዋል። ዳይሬክተሩ ጥያቄው ለእርዳታ ሰጭዎች ዱብ ዕዳ መሆኑን እንደሚገነዘቡ   የገለጹ ሲሆን እናት በምግብ እጥረት ምክንያት ልጆቿን ስታጣ ማየት ደግሞ የበለጠ ዱብ ዕዳ ነው በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት ሊያስረዱ ሞክረዋል። በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት 1.4 ቢሊዮን ዶላር የሚያፈልግ መሆኑ በየገዜው ይገለጥ እንጅ በድርቁ ይጎዳሉ የተባሉ ወገኖች ግምት ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ በመሄዱ  ከተገመተው  የሚያስፈልገው የእርዳታ መጠን ከተገመተው በላይ ይሆናል የሚሉ በርካታ ናችው። በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለተጎዱ ዜጎች ከፍተኛ እርዳታ በሚጠይቅበት ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ የሚቸረው የእርዳታ መጠን በጊዜው ላይደርስ ይችላል የሚለው ስጋት ሰፊ መሆኑ ይነገራል።

 

Ø በድርቁ ምክንያት በግድቦች የሚጠራቀመው ውሃ በማነሱ በጠቅላላው ከ500 ሚጋዋት በላይ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ቀንሷል የሚለው ሰሞኑን ከወያኔ ባለስልጣኖች አካባቢ እየተሰራጨ ያለው ዜና አነጋጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዜጎች እየገለጹ ይገኛሉ። በተከዜ፣ ቆቃ፣ ፊንጫ አመርቲነሽና ጊቤ የሚገኙት ግድቦች የውሃ መጠናቸው የቀነሰ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ይህም  የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን እንዲቀንስ አድርጎ   ፋብሪካዎችን አንዳንድ የስራ ቦታዎች በቀን ለስድስት ሰዓታት ብቻ ኢሌክትሪክ የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል ተብሏል። ሪፖርተር የተባለው ጋዜጣ በቅርቡ ከወያኔ ባለስልጣኖች አገኘሁት ባለው ዜና መሰረት በርካታ የኤሌክትሪክ ኃይልን ማመንጨት ይችላል ተብሎ የተገመተውና በአካባቢው ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል ተብሎ የሚጠበቀው የግልግል ሶስት ስራ ለማፋጠን እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ገልጿል። የኢሌክትሪክ አገልግሎት መቀነስ ለአመታት የተከሰተ መሆኑን ታዛቢዎች ገልጸው ድርቁ ለሽፋን የቀረበ ምክንያት እንጅ እውነተኛው ምክንያት አይደለም በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።  ወያኔ ከአራት አመት በፊት ለጂቡቲ፤ ለሱዳን፤ ለኬኒያና ለሱማሌላንድ በከፍተኛ ደረጃ ኤሌክትሪክ ሲሸጥ መቆየቱና በአሁኑም ወቅት አጠናክሮና አስፋፍቶ የቀጠለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን 400 ሚጋዋት የኤሌክትሪክ አገግልግሎት ለታንዛኒያ ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ሁለቱ አገሮች ስምምነት እንደሚፈራረሙ  ስታር አፍሪካ የተባለው ተቋም ረቡዕ ጥር 19 ቀን 2008 ዓም በድረገጹ ካሰፈረው ዘገባ ማወቅ ተችሏል። በአገሪቱ የኤሌክትሪክ አቀርቦት የቀንሰው በአንድ በኩል ደረጃቸውን ያልጠበቁ ግድቦች በስራ ላይ በመዋላቸውና በመሳሪውያዎች ብልሸት ሲሆን በሌላ በኩል  የወያኔ ባለስልጣኖችን ኪስ ለማደለብ የኤሌክትሪኩ አቅርቦት ወደ ጎረቤት  አገሮች በገፍ  በመሸጡ መሆኑ ይታወቃል።

በተያያዘ ዜና በሰሜን ጎነደር ደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች በመብራት እጦት ሁለት አመት ያለፋቸው መሆኑና አሁንም ቢሆን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።  በአንድ መንደር የሚኖሩ ከአንድ መቶ ሰላሳ በላይ አባወራዎች መብራት ለማግኘት ክፈሉ ተባሉትን አምስት መቶ ሃያ ሶስት ሺህ አምስት መቶ አርባ አራት ብር ከከፈሉ በኋላ እጣ ይወጣላችኋል ጠብቁ የሚል መልስ ተሰጥቷቸው እየጠበቁ መሆናቸውን ከስፍራው የመጣው ዜና ያስረዳል።  

 

 

Ø ከ2003 ዓ/ም እስከ   ዓ/ም ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ምዝበራ ተካሄዶባቸውል ተብለው የሚጠረጠሩትን መስሪያ ቤቶች ለማጋለጥ የኦዲት ግኝት በሚል ስም አንድ ጥናት እየተዘጋጀ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ጥናቱን የሚመራው የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በአዲስ አበባ ያለጨረታ ግዢ የፈጸሙ፤ ያለደረሰኝ ሂሳብ ያወራረዱ፤ ዓመታዊ በጀታቸውን እንደፈለጉ ያባከኑ፤ ስለወጪያቸው ምንም መረጃ የሌላቸው ተብለው ከተፈረጁት መካከል የአዲስ አበባ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፤ የህጻናትና ሴቶች ጉዳይ፤ የመንገዶች ባለስልጣን፤  ግንባር ቀደም መሆናቸውን የዋና ኦዲተር ጥናት አጋልጧል። ዋና ኦዲተር አጠናሁት  በጥናቱ መስሪያ ቤቶችን ያጋልጥ እንጂ የተጠቀሱት መስርያ ቤቶች በወያኔ አባላት የሚመሩና ማንም ጠያቂ የሌላቸው መሆኑ የታወቀ ስለሆነ የሚወሰድ እርምጃ አይኖርም በማለት ብዙዎች ይደመድማሉ።

 

Ø የቀድሞ የአይቮሪ ኮስት ፕሬዚዳንት ሎረንት ጋብጎ ረቡዕ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም በኒዘርላን ሄግ በሚገኘው የዓለም ፍርድ ቤት ላይ መቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን የተለያዩ ክሶች የቀረቡባቸው መሆኑ ታውቋል። በ2003 በአገሪቱ ተካሄዶ የነበረውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ እሳቸውና የቀድሞ የሚሊሺያ መሪ ሚስተር ቻርልስ ጉዴ ግድያ በማካሄድ፤ ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር፤ የግድያ ሙከራ በማድረግና ዜጎችን በአልሆነ መንገድ በማሰቃየት ክስ የቀረበባቸው ሲሆን ተከሳሹ በክሱ ላይ የተዘረዘሩትን ወንጀሎች ያልፈጸሙ መሆናቸውን ክደዋል። ሚስተር ጋብጎ በ2003 ዓም በተደረገው ምርጫ በተወዳዳሪያቸው ተሸንፈዋል ቢባሉም ስልጣን ለማስረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በተወዳዳሪው በሚስተር ኳታራና በእሳቸው ደጋፊዎች መካከል ለአምስት ወራት ያህል በዘለቁ ግጭቶች የብዙ ሰዎች ህይወትን እንደጠፋና ብዙዎቹም አከለ ስንኩላን እንደሆኑ ይታወቃል። በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ የሚስተር ጋብጎ ደጋፊዎች ከተሸነፉ በኋላ የቀድሞ ፕሬዚዳንት  በቁጥጥር ስር ውለው ወደ ሄግ ሊወሰዱ ችለዋል።  ሂደቱ ከሶስት እስከ አራት ዓመት ይወስዳል ተብሎ በተገመተው ክስ ሚስተር ጋብጎ ትክክለኛ ፍርድ ያገኛሉ የሚለው አጠራጣሪ ነው የሚሉ ብዙ ናቸው።  የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ዘረኛነትና አድሎ የበዛበት ነው የሚለው ክስ በብዙ የአፍሪካ አገሮች የሚቀርብ ሲሆን ፍርድ ቤቱ በአፍሪካውያን ላይ ብቻ ያተኮረ እንጅ  በተለያዩ  የአለም ክፍሎች በተለይም በምዕራብ አገሮች  የሚደረጉትን ወንጀል ለማየት ያልደፈረና ያልቻለ ወገንተኛ አካል አድርገው ይመድቡታል።   

 

Ø ትናንት ረቡዕ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ በምትገኘው በቺቦክ ከተማ በርከት ያሉ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷቸው ቦምቦች 15 ሰላማዊ ሰዎችና አንድ ወታደር የተገደሉ መሆናቸውን እንዲሁም ቁጥራቸው ከፍ ያሉ ዜጎች የአካል ጉዳት የደረሰባችው መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የአካል ጉዳት ከደረሰባችው መካከል የተወሰኑት በጽኑ የቆሰሉ ሲሆን ለህይወታቸው አስጊ መሆኑን የሆስፒታል ምንጮች ጠቁመዋል። ቦኮ ሃራም ከሁለት ዓመት በፊት 300 የሚሆኑ የትምህርት ቤት ህጻናትን ጠልፎ የወሰደው ከዚችው ከተማ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የረቡዕ ዕለቱን አደጋ ያደረሱት አጥፍቶ ጠፊዎች የቦኮ ሃራም አባላት እንደሆኑ ተገምቷል።

Ø በተያያዘ ዜና ዛሬ ሐሙስ ጥር 19 ቀን 2008 ኬራዋ በተባለችው የሰሜን ካሜሩን ግዛት ከተማ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ያፈነዱት ቦምብ አራት ሰዎችን የገደለ መሆኑ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ራስን ለመከላከል የተቋቋመው የአካባቢ ጥበቃ አካል አባላት የሆኑ ግለሰቦች ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ  በጾታቸው ሴቶች የሆኑ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ከአንድ ትምህርት ቤት አጠገብ በሚገኝ መጠለያ ጣቢያ ላይ ጥቃቱን እንደፈጸሙ ተናገግረዋል። አካባቢው በመስከረም ወር ተመሳሳይ ጥቃት ተፈጽሞበት ወደ 20 የሚጠጉ ሰዎች የሞቱ ሲሆን ባለፈው ሰኞ ዕለትም በሌላ ከተማ በደረሰ ተመሳሳይ ጥቃት 37 ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል።

 

Ø በግብጽ የሳይናይ ባህረሰላጤ  ኤል አሪሽ  ከተማ የአሲስ ቅርንጫፍ ነኝ የሚለው አሸባሪ ቡድን በግብጽ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጥቃት ፈጽሞ አንድ ኮሎኔል እና ሶስት ወታደሮችን የገደለ መሆኑን ገልጿል። አሸባሪው ቡድን የቀበረው ቦምብ ኢላማ ያደረገው ወታድሮቹ ይጓዙባቸው የነበሩባቸውን መኪናዎች ሲሆን በፍንዳታው ሌሎች 12 ወታድሮች መቁሰላችወ ተጠቁሟል። አሸባሪው ቡድን ይህን ጥቃት የፈጸመው  የሲሲ መንግስት በሙርሲ ደጋፊዎች ላይ እየወሰደ ላለለው እርምጃ አጸፋውን ለመመለስ ጠቅሶ ተመሳሳይ ጥቃቶች እንደሚከተሉ አስጠንቋል። የግብጽ መንግስት ባለስልጣኖች በመቶ የሚቆጠሩ የፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳይናይ ሰሜናዊ ክፍል በአሸባሪ ቡድኖቹ ጥቃት የተገድሉባችውና የቆሰሉባቸው መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።      

 

  

 

 

 

ጥር 18 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአዲስ አበባ የተጀመረውን የአፍርካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባን ተከትሎ ለደህንነት ጥበቃ ሲባል የመኪና አከራይ ድርጅቶች መኪናቸውን ለማን እንዳከራዩ የሚያበራራ የተሟላ መረጃ እንዲኖራቸው መመሪያ የተላለፈ ሲሆን መረጃቸውን ያላሟሉ አከራዮች ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድባቸው መሆኑ የተገኘው መረጃ ይገልጻል።  ሰሞኑን የደህንነት ኃላፊዎች  የመኪና አከራይ ድርጅቶችን ባለቤቶች ጠርተው  ኮድ ሁለት  የሆነ  የግል ሰሌዳ የለጠፉ ተሽከርካሪዎች ብቻ ለኪራይ እንደሚውሉ መመሪያ የሰጡ ሲሆን የመከና አከራዮች ባለቤቶችም መረጃዎቹን በማሟላት ፖሊስን ማገዝ እንደሚኖርባቸው ተገልጾላቸዋል። 

 

 

Ø በደቡብ ክልል በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ችግር ፈጥረዋል፤ በሙስና ውስጥ ተዘፍቀዋል የተባሉትን ሹማምቶች ለመጠቆምና ለማሰር እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እስካሁን ድረስ እንቅስቃሴው ኢላማ ያደረገው የበታች ሹማንቶችን እንጅ የአገር ሃብትና ንብረት የዘረፉትን እነ መኩሪያ ሃይሌን እንዳልነካና ውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቅሰዋል።  ከሚያገኘው ደሞዝ የማይመጣጠን ሃብት ያካበተው መኩሪያ ሃይሌ በደቡብ ግሎባል ባንክ የሃያ አምስት በመቶ አክስዮን ድርሻ እንዳለው የሚያጋልጥ መረጃ ያለ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ወያኔ ለማስመስልና ህዝቡን ለመደለል የመልካም አስተዳድር እያለ ይጩህ እንጅ አገልጋይ የሆኑትን ወንጀለኞች እንደማያጋልጥና እንዲያውም ከፍተኛ ሹመት በመስጠት ወንጀላችውን ሲሸፍን የቆየ መሆኑ በተግባር የታየ ነው ተብሏል። በአገራችን በወያኔ ባለስልጣኖች የሚካሄደው ሙስና ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መሄዱ በጉልህ እየታየ ሲሆን ሲሆን ሰሞኑን ይፋ የተደረገው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም ዘገባ በዓለም ከፍተኛ ሙስና ከሚካሄድባቸው አገሮች መካከል ኢትዮጵያያን አንዷ አድርጎ እንደመደባት ታውቋል። 

 

 

Ø የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የግል ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ለመውሰድ በካሬ ሜትር አራት ሺህ ብር የሚጠጋ ገንዘብ እንዲከፍሉ ሊጠየቁ መሆናቸው ከውስጥ አዋቂዎች ከተገኘው መረጃ ማወቅ ተችሏል። በነዋሪነት ድርሻ ይዞታ የሚባለው ሰባ ሁለት ካሬ ሜትር ብቻ ሲሆን በይዞታነት ተከልሎ የአፈር ግብር ሲከፈልበት የቆየ ድርሻቸውን ለማስከበር እና የግል ለማድረግ ቀሪው ስፍራ ተለክቶ ለእያንዳንዱ ካሬ ሜትር ሶስት ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ብር እንዲከፍሉና በሊዝ እንዲያዛውሩ ለመጠየቅ የታቀደ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ ቀደም የመሬት ባለቤት የሆነ ሰው የይዞታ ማረጋገጫ ለማግኘት የሚከፍለው  አምስት ሺህ ብር የነበረ ሲሆን አሰራሩን በመቀየር በካሬ ሜትር በሊዝ ድረጃ ተጨማሪ ገንዘብ በማስከፈል ወያኔ ከፍተኛ ዝርፊያ ለማካሄድ ያቀደ መሆኑ ጉዳዩ የሚያውቁት ሰዎች ይናገራሉ።

 

Ø የስፔን ባለስልጣኖች በአፍሪካ፤ በመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁ በሩቅ ምስራቅ ስደተኞችን በማመለስ ስራ ላይ ተሰማርተው ከፍተኛ ሀብት የሚያካብቱትን ቡድኖች የግንኙነት መስመር የደረሰብት መሆኑን ገልጸው መረጃውን ለመሚለከታቸው አገሮች ያስተላለፉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ወደ አውሮፓ የተለያዩ ክፍልች ስደተኞችን ለማጓጓዝ ከሚጠቅሙባቸው መካከል የእንግሊዝ አውሮፕላን ጣቢያዎች የሚገኙበት መሆኑም ተጠቁማውውል። አስተላላልፊዎቹ በአፍሪካ በሰሜን አሜሪካ በአውሮፓና በመከካለኛው ምስራቅ በከፍተኛ ደረጃ ስራቸውን በማካሄድ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች ያስተላለፉ መሆናቸውንና እንዲሁም ብዙ ወጣት ሴቶችን ምርጫ በማሳጣት ሴትኛ አዳሪ ለማድረግ ያስገደዷቸው መሆኑ ተረጋግጧል።

 

Ø በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልኡክ የሆኑት ሚስተር ማርቲን ኮብለር ዛሬ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ቀደም የአንድነት መንግስት ለመመስረት ስምምነት የተደረገባችው አንቀጾች ሊለወጡና ሊስተካከሉ እንደሚችሉ ገለጹ። ከሁለት ቀናት በፊት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው ምክር ቤት በተመድ አደራዳሪነት የቀረበውን የስምምነት ሰነድ ያልተቀበለው መሆኑ ይታወቃል። ምክር ቤቱ ሰነዱ ላይ የቀረበው የአንድነት መንግስት ካቤኔ  አባላት ቁጥር የበዛ መሆኑን ጠቅሶ የካቢኔው አባላት ቁጥር እንዲቀነስ የጠየቀ ሲሆን በአንቀጹ ውስጥ የስፈረውንና  የአገሪቷን ከፍተኛ የጸጥታና ወታደራዊ ሹሞች የአንድነት መንግስቱ ይሾማል የሚለውን የስምምነት አንቀጽ ያልተቀበለው መሆኑ ይታወቃል።  ሚስተር ኮብለር ከዚህ ቀደም የስምምነቱን አንቀጾች መለወጥ ስምምነቱን ውድቅ ስለሚያደርገው አንቀበለውም ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ቀደም ብሎ የያዙትን አቋም መለወጣችው የምክር ቤቱ ውሳኔ ከፍተኛ ተጽእኖ በማሳደሩ ነው የሚል ግምት ተወስዷል። የአውሮፓው ህብረት በሊቢያ ስምምነቱን ለማደናቀፍ እየተሯሯጡ ናቸው በሚሉት ግለስቦች ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተሰናዳ መሆኑን ገልጾ በአስር ቀናት ውስጥ ስምምነቱ ተግባራዊ ካልተደረገ ማዕቀቡ የሚጀመር መሆኑን ግልጽ አድርጓል። በሊቢያ በአዲስ መልክ ስምምነት መኖሩና አለመኖሩ ወደፊት የሚታይ ሲሆን የስምምነቱ ተግባራዊነት እየተራዘመ ሲሄድ በአገሪቱ የሚገኙ አክራሪና አሸባሪ ኃይሎች የሚጠናከሩበት ሁኔታ ይመቻቻል የሚሉ በርካታ ናቸው።

 

Ø በሰሜን ካሜሩን በአጥፍቶ ጠፊዎች ለተወሰደው ጥቃት የአጸፋ መልስ ለማድረግ ባለፈው ሰኞ ማታ የካሜሩን ወታደሮች የናይጄሪያ ወሰን ጥሰው በመግባት በወሰን አካባቢ የሚገኙ 40 የናይጀሪያ ዜጎችን የገደሉ መሆናችውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የካሜሩን ባለስልጣኖች ወታደራዊ እንቅስቃሴው የተደረገው በጋራው ኃይል ስር መሆኑን ገልጸው ወታደራዊ እንቅስቃሴው የተደረገው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎችንና የጦርነት ደንቦችን በመከተል ነው በማለት በነዋሪዎቹ የቀረበውን ክስ አስተባብለዋል።  የናይጄሪያ ባለስልጣኖች ስለሆኔታው እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።

 

Ø በትናንትናው ዕለት በደቡብ ሶማሊያ የጦር ሰፈሩን ለቅቆ ከወጣው የኬኒያ ወታደራዊ ኃይል መካከል  በአንድ ማመለለሻ ላይ የተጫኑ ወታደሮች በተጠመደ ፈንጅ ተጠቅተው ቢያንስ አምስት ወታደሮች የሞቱ መሆናቸውን  የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ዛሬ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም  አንድ የኬኒያ ከፍተኛ የፖሊስ አዛዥ የኬኒያ ወታድሮች በተጠመደ ፈንጅ  መገደላቸውን አምነው ምን ያህል እንደሞቱ ግን መርጃ ሳይሰጡ የቀሩ ሲሆን አንድ ሌላ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ከፍተኛ የፖሊስ መኮንን አምስት ወታደራዊ መኮንኖች በቦምቡ ፍንዳታ መሞታቸውን አረጋግጠዋል። በዛሬው ቀን ቀደም ብለው በአልሸባብ በተገደሉት የኬኒያ ወታደሮች የቀብር ስነስርዓት ላይ የኪኒያ ፕሬዚዳንት አገሪቱን በመጎብኘት ላይ ካሉት የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ጋር የሚገኙ ሲሆን ፕሬዚዳንቱ ኬኒያ በአልሸባብ ላይ ተገቢውን የአጸፋ እርምጃ ትወስዳለች ብለዋል። ኬኒያ በደቡብ ሶማሊያ ካሉት ጦር ሰፈሮች ወታደሮቿን ያስወጣችው ለወታደራዊ እንቅስቃሴ ነው እንጅ ከሶማሊያ ጠቅልሎ ለመውጣት አይደለም የሚል መግልጫ መሰጠቷም ይታወሳል።

 

Ø በሰሜን አፍሪካ የሚንቀሳቀሰው የአልካይዳ ቡድን ቲምበክቱ ከምትባለዋ የማሊ ከተማ ቢያትሪስ ስቶክሊ የተባሉ  አንዲት የስዊድን ተወላጅ ጠልፎ የወሰደ መሆኑን በድረ ገጹ ላይ ባስተላለፈው ዜና ገልጿል። ራሱን የአልካይዳ የሳህራው ክንፍ በሚል ስም የሚጠራው ቡድን  ሴትየዋን ያገተ መሆኑን ገልጾ በማሊ የታሰረው መሪውና እንዲሁም በናይጀር የታሰረ ሌላ የድርጅቱ አባል ካልተፈቱ ሴትየዋ የማይለቀቁ መሆናቸውን ግልጽ አድርጓል። የስዊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴትየዋ አለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የጠየቀ ሲሆን ከማሊ መንግስትም ሆነ ከተጠላፊዋ ቤተሰቦች ጋር ግንኙነት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።  

   

 

 

 

ጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ባለፉት ሁለት ወራት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በተለያዩ ከተሞች በተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በወያኔ አግአዚ ጦር የተገደሉ ዜጎች ቁጥር ከ 140 በላይ መሆኑ፤ በአንዳንዶች ግምትም እስከ ሁለት መቶ ደርሷል ተብሎ መነገሩ የሚታወስ ሲሆን ከእነዚህ መካከል 17 የሚሆኑት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ መሆናቸውን የሚያረጋግጡ መረጃዎ አግኝቻለሁ በማለት ግሎባል ቮይስ የተባለው ተቋም ትናንት ጥር 16 ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ከ17ቱ ህጻናት መካከል አብዛኞች ከ12 ዓመት እስከ 17 ዕድሜ ያላቸው መሆናቸውን ተቋሙ ጠቁሞ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ህጽናትም የአካል ጉዳት እንደደረሰባችውና ታስረው እንደተወሰዱም አጋልጧል። በኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚገኑኙ ከ60 ሺ  በላይ ከሆኑ የፖሊቲካ እስረኞች መካከል 20 ሺ የሚሆኑት ኦሮሚኛ ተናገሪዎች መሆናቸውን ገልጾ ወያኔ በዜጎች ላይ በተለይ በኦሮሚኛ ተናጋሪዎች  ዜጎች ላይ የሚፈጽመውን በደል አውግዟል።

በተያያዘ ዜና በዛሬው ዕለት በነቀምት ከተማ በወያኔ አገዛዝ ላይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ  መደረጉ የተዘገበ ሲሆን የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ በዜጎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አልተቻለም። በሀረርጌም ጭሮ ከተማ ተማሪዎች ትምህርት አቁመው የቆሰሉ ጓደኞቻቸውን ለማየት ወደ ሆስፒታል የሄዱ መሆናቸው ተዘግቧል።  ትናንት ጥቅምት 16 ቀን 2008 ዓም   በእስራዔልና በሲወዝርላንድ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች የወያኔ አግአዚ ጦር  በኦሮሚኛ ተናጋሪ ወንድሞቻችንና በሌሎች ዜጎች  ላይ እየፈጸመ ያለውን ወንጀል በማውገዝ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል።

 

Ø ከአገራቸው ተሰደው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ በታንዛንያ በኩል ሲያቆራርጡ የያዟቸውን በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ለወያኔ አሳልፈው ለመስጠት  የታንዛንያ ባለስልጣኖች የወሰኑ መሆናቸውን አንድ የታንዛኒያ ጋዜጣ በዛሬው ዕለት አጋልጧል። የታንዛኒያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጡት መግለጫ በቁጥጥር ስር ያሉት ኢትዮጵያውያንና የሌላ አገር ዜጎች ፍርድ ቤት የሚቀርቡ መሆናችውንና  ከአገር የሚያባረሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ጊዜያት ወደ ደቡብ አፍሪካ በመጓዝ ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ታንዛንያ ውስጥ ተይዘው የታሰሩ ሲሆን ባለፈው ወር ላይ 40 የሚሆኑ ተጥልለውባቸው ከነበሩት ቤቶች ተለቅመው የታሰሩ መሆናቸው ተዘግቧል። ለአስተላላፊዎች ስደተኞቹ የሚከፍሉት ገንዘብ ከ አንድ ሺ እስከ ሁለት ሺ ዶላር የሚደርስ ሲሆን በጉዟቸውም ላይ ከፍተኛ ችግር እንደሚደርስባቸው ታውቋል።

 

 

Ø በፍቼ ከተማ ከዋና መንገድ ወደ ውስጥ የሚገቡና ሁለተኛ ደረጃ ተብለው የተመደቡ የከተማ መሬቶችን በሊዝ ለመሸጥ የወጣው ጨረታ ዛሬ ጥር 17 ቀን 2008 ዓ/ም መጠናቀቁ ታውቋል። በካሬ ሜትር የተሸጠበት ዋጋና ምን ያህል ካሬ መሬት እንደተሸጠ ለጊዜው ማጣራት ባይቻልም የገዙት ሰዎች የኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ዘመዶች መሆናቸውን የአይን እማኞችን ተናግረዋል።

 

Ø በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት የስላም አስከባሪ ኃይል ስር በሁለት ከተሞች ውስጥ ተሰማርተው የነበሩ የኬኒያ ወታድሮች ከተሞችን እየለቀቁ የወጡ መሆናቸው ታውቋል። ከሁለቱ ጦር ሰፈሮች መካከል አንደኛው ኤል አዴ በተባለውና ባለፈው ሳምንት አልሸባብ ጥቃት አድርሶ 100 የኪኒያ ወታደሮች ገደልኩ ባለባት ከተማ የነበረው ጦር ሰፈር ሲሆን ሁለተኛዋ ባድሃዴ በተባለው ከተማ ውስጥ የነበረው ጦር ሰፈር ነው። የኬኒያ ወታደሮች የባድሃዴን ከተማ ለቀው እንደወጡ በከተማዋ ዙሪያ የአልሸባብ ወታደሮች መታየታችውን የአይን እማኞች ገልጸዋል። የኬኒያ ባለስልጣኖች በኤል አዴ ከተማ በተካሄደው የአልሸባብ ጥቃት  የፈነዳው ቦምብ ከ18 ዓመታት በፊት በናይሮቢ በአሜሪካ ኤምባሲ ላይ ከተጣለው የቦምብ ፍንዳታ ሶስት ጊዜ እጥፍ የሚበልጥ መሆኑን ከመናገርና በፈንጅው የሞቱትን ሰዎች ዲ ኤን ኤ በመርመር ለማጣራት እየሞከሩ መሆናቸውን ከመግለጻቸው  በስተቀር ምን ያህል ወታደሮች እንደሞቱ እስካሁን የገለጹት ቁጥር የለም።  የአልሸባብ መግለጫ እውነት ከሆነ ድርጅቱ በአፍሪካ ኅበረት ወታደሮች ላይ ካደረሳቸው ጉዳቶችን የጎላ ያለ ነው የሚሉ ወገኖች በርካታ ናችው።  የኬኒያ ባለስልጣኖች የተደረገው ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንጅ አንደኛውን ከጦር ሰፈሮች ጠቅልሎ ለመውጣት አይደለም የሚል መግለጫ የሰጡ ሲሆን በኬኒያ ወታደሮች በተደጋጋሚ የደረሰባቸው ወከባ ያስመረራቸው መሆኑን የገለጹት  የኤል አዴ ነዋሪዎች  ወታደሮቹ ጦር ሰፈራችውን ጥለው መውጣታቸው ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸዋል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት ቦዶ በምትባል የሰሜን ካሜሩን ከተማ  በአንድ የገባያ ቦታ በፈነዱ ቦምቦች ቢያንስ 32 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውና 86 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ታወቀ። በገበያ ላይ አራት አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ ወጣት ሴቶች የያዝቱን ቦምብ አፈንድተው ከራሳቸው ጋር ገበያተኞችን የገደሉ ሲሆን አጥፍቶ ጠፊዎቹ የቦኮ ሃራም አባሎች ናቸው የሚል ግምት ተወስዷል። አካባቢው በተደጋጋሚ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች  የጥቃት ሰለባ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባለፈው ወር በቦዶ ከተማ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች የያዙትን ቦምብ አፈንድተው ጉዳት ማድረሳችው ይታወሳል። ካሜሩን ቦኮሃራምን ለማዳከምና ለማጥፋት ከናይጄሪያ፤ ከናይጀር፤ ከቤኒን እና ከቻድ ጋር የጋራ ኃይል በመመስረቷ በቦኮ ሃራም ተደጋጋሚ የአጸፋ ጥቃት ደርሶባታል።  

 

Ø በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት ክፍል ፓርላማ ትናንት ጥር 16 ቀን 2008 ዓም ባደረገው ስብሰባ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስተባባሪነት አዲስ የአንድነት መንግስት ለመመስረት የቀረበውን ሀሳብ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ታውቋል። ከ104 ተሰባስባዎች መካከል 89 የሚሆኑት የአዲሱን የአንድነት መንግስት አመሰራረት በመቃወም ድምጽ የሰጡ ሲሆን የተሰጠው ምክንያት የካቢኔ አባላቱ ቁጥር ከሚገባው በላይ ብዙ ነው የሚል ነው። አነስተኛ የካቢኔ ቁጥር ያለው መንግስት በአስር ቀን ውስጥ እንዲቋቋም መመሪያ የሰጠ መሆኑን የምክር ቤቱ ቃል አቀባይ ገልጸዋል። ይመስረታል የተባለው አዲስ መንግስት ከፍተኛ የሆኑትን የጸጥታ ተቋምና የወታደሩን ክፍልን መሪዎች ለመሾም ስልጣን አለው በሚል በስምምነቱ ረቂቅ ላይ የቀረበው የህግ አንቀጽ በምክር ቤቱ አባላት ዘንድ ክርክር የከፈተ  ሲሆን ምክር ቤቱ በዚህ ላይ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 17 ቀን 2007 ዓም ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህ አንቀጽ መሰረት በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ተወዳጅነትንና ተቀባይነት ያገኙት ጄኔራል ካሊፋ ሃፍታር ከስራቸው ላይ ሊነሱ ይችላሉ ከሚል ስጋት ስላደረባችው የምክር ቤት አባላት ይህ አንቀጽ እንዲለውጥ ይጠይቃሉ የሚል ግምት ተፈጥሯል።

 

 

Ø በተያያዘ ዜና የሊቢያ የነዳጅ ኩባንያ ኃላፊ ለንደን ውስጥ በሰጡት መግለጫ በሊቢያ ውስጥ ስምምነት ከጠፋ ሊቢያ ወደ ባሰ ቀውስ የምትሄድ መሆኑንና ከነዳጅ የምታገኘውን ከፍተኛ ገቢ ልታጣ እንደምትችል አስታውቀዋል። ሊቢያ እስካሁን ከነዳጅ ዘይት ማግኘት የነበረባትን 68 ሚሊዮን ዶላር ያጣች መሆኑን ገልጸው የአንድነት መንግስት ካልተቋቋመ ጸጥታ ሆነ መረጋጋት አይፈጠርም ብለዋል። አክለውም አሸባሪና አክራሪ ኃይሎች ቀዳዳውን በመጠቀም ራሳቸውን ሊያደራጁና ከፍተኛ እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ በማለት ያላችውን ስጋት ገልጸል።      

 

 

 

 

 

 

 

ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተቀጣጠለው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በተለያዩ ቦታዎች የቀጠለ ሲሆን ወያኔ እየወሰደ ያለውን አስከፊ እርምጃ በመቃወም አንዳንድ ክፍሎች  ድምጻቸውን እያሰሙ ነው ። ሰሞኑን በወለጋ ዩኒቨርስቲ የአግአዚ ወታደሮች በየተማሪዎቹ መኝታ ቤት ገብተው ባካሄዱት ቢያንስ 15 ተማሪዎች የአካል ጉዳት ደርሶባችው ወደ ለቀምት ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናችው ታውቋል።  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጽጥታው ምክር ቤት የልኡክ አባል በመሆን ወደ ብሩንዲ ሄደው የነበሩትና ስለብሩንዲ ጉዳይ ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር ለመነጋገር አዲስ አበባ የተገኙት የአሜሪካው የተመድ ተወካይ ሳማንታ ፓወር በቲወተር ባስተላለፉት መልክት ከወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከቴዎድሮስ አድሃኖም ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን ገልጸው በወያኔ የተወሰደውን እርምጃ እንደማይደግፉና ችግሮችን በውይይት መፍታት እንዳለባችው የሚገልጹ መልእክቶች ማስተላለፋቸውን  ገልጸዋል።

 

Ø በተያያዘ ዜና በወያኔና በኦህድዴ መካከል ያለው ውጥረት እየሰፋ መሆኑን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱት ዘገባዎች ይጠቁማሉ። ስሞኑን ለወያኔ አባላት ብቻ የወረደው የውስጥ ማስታወሻ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያሉ የወያኔ አባላት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያሳስብ መሆኑ ታውቋል። ማስታወሻው ሰሞኑን የጸጥታ ሁኔታን ለመቋቋም የተወስደው እርምጃ በወያኔ ድርጅት ብቻ እንደተቀነባበረና እንደተካሄደ መሆኑን በመግለጽ በተለያዩ የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የኦህዴድ አባላት   በወያኔ አባላት ርምጃ ውሰዱ በማለት ወጣቶችን በመቀስቀስ ላይ ስለሆኑ ራሳችሁንና ድርጅታችሁን ጠብቁ የሚል መልእክት በመያዙ ከፍተኛ ውጥረት የፈጠረ መሆኑን  የተገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ።  

 

 

Ø ትናንት ምሽት በአዋሳ ከተማ አጠገብ የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰ መሆኑ ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። በደቂቃዎች ልዩነት ለሁለት ጊዜ ያህል የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ የንዝረቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ በትክክል ባይታወቅም በሬክተር ስኬል እስከ 4 የሚደርስ ነው ተብሎ ተግምቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ በሰው ላይ የሕይወት አደጋ ባያደርስም አንዳንድ ወገኖች በሁኔታ በመደናገጥ ከአደጋው ለማምለጥ ሲሮጡና ከፎቅ ላይ ሲዚሉ የአካል ጉዳት የደረሰባችውና ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናቸው ተነግሯል።  በአንዳንድ ህንጻዎች ላይ የመሰነጣጠቅ ጉዳት ያደረስ ሲሆን ነዋሪዎች ድንኳን ዘርገተው ሌሊቱን ማሳለፋችው ታውቋል። በተለይ ሲገነቡ ጥራታቸውን ያልተበቁና አስተማማኝ ያልሆኑ ፎቅ ቤቶች በመሬት መንቀጥቀጡ ሊፈርሱ ይችላሉ ከሚል ስጋት ብዙዎቹ ቤታቸውን እየተዉ አድረዋል።

 

Ø እሁድ ጥር 15 ቀን 2008 ሌሊት ለሰኞ አጥቢያ በአዲስ አበባ የተለያዩ ስፍራዎችና አደባባዮች የተለያዩ የቅስቀሳ ጹሁፎች በደማቅ ቀለሞች በትላልቁ ተጸፈው ያደሩ መሆናቸው ታውቋል። ተጽፈው ካደሩት መፈክሮች እና መልእክቶች መካከል “ድምጻችን ይሰማ፤ “ግድያው ይቁም”፤ “በቃ”፤ “አምባገነናዊ ፍርድ አንቀበልም”፣ “ ብሔራዊ ጭቆና ይብቃ” የሚሉ ሲሆኑ  ለሃይማኖት መብት የሚታገሉት የሙስሊሙ ወገኖቻችን የድምጻችን ይሰማ አባላት መልእክቶች መሆናቸው  ግልጽ ነው። የወያኔን ጨቋኝና የአፈና አገዛዝ በመቃወም እየተደረጉ ያሉ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች አገዛዙ ፋታ በመንሳት ላይ መሆናቸው እየታየ ነው።

 

 

Ø የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ሰሞኑን አዲስ አበባ ላይ ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን ከመሪዎቹ ስብሰባ ቀደም ብሎ የሚካሄደው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በመቀሌ ከተማ እንዲካሄድ በመደረጉ ከተማዋ በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ስር የወደቀች መሆኗ ታውቋል። በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ከፍተኛ ሆቴሎች ማንም አዲስ እንግዳ እንዳያስተናግዱ ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን አልጋ የሚያከራዩ ዝቅተኛ ሆቴሎችና ቡና ቤቶች ለፖሊስ ሳያሳውቁ ማንኛውንም ጸጉረ ልውጥ ሰው እንዳያስተናግዱ ጥብቅ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ታውቋል።ከትግራይ ፖሊስ በተጨማሪ የደህነነትና ልዩ ኃይል አባላት በተለያዩ የመቀሌ ከተማ መግቢያዎች ላይ ሲቪል ልብስ በመልበስ የነቃ ጥበቃ እንዲያደርጉ ምደባ የተሰጣቸው ከመሆኑም በላይ የድርጅትና የፎረም አባላት በአንድ ለአምስትእድር ጃጀት ተጠቅመው ማንኛውንም መረጃ ሪፖርት እንዲያደርጉ  መመሪያ የተሰጠ መሆኑን ተያይዞ የደረሰን መረጃ አስረድቷል።

 

 

Ø በግብጽ በዛሬው ቀን አምስተኛ አመቱ የሚያከበረውና የአምባገነኑን የሙባረክን መንግስት ያስወገደው የግብጽ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሌላ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እንዳይቀሰቅስ በመስጋት የግብጽ ወታደራዊ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ ጥበቃ ማድረጉ ታውቋል። በአሁኑ የግብጹ ፕሬዚዳንት ሲሲ ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ተዘጋጅተዋል ተብለው የተጠረጠሩ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች መኖሪያ ቤቶች የተፈተሹና የተበረበሩ ሲሆን አድማ ያስነሳሉ ተብለው የተገመቱ በርካታ ግብጻውያን መታስራቸውንም ለማወቅ ተችሏል።  በዛሬውም ዕለትም በካይሮ ዋና ዋና መንገዶችና  ታህሪር በሚባለው አደባባይ ዙሪያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶችና ወታደሮች የተሰማሩ ሲሆን ተቃውሞ ሊያሰሙ የሚችሉ ይሰባሰቡበታል የተባሉ ሻይ ቤቶችና ቡና ቤቶች እንዲዘጉ የተደረገ መሆኑና በየፖሊስ ጣቢያዎች  ጥበቃው የተጠናከረ መሆኑም የተገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ።  አምባገነን አገዛቸውን አጥብቀው የሚገኙት ሲሲ ስልጣን ከያዙ ጀምሮ የሰብአዊ መብት ረገጣው በከፍተኛ ደረጃ መባባሱ የተገለጸ ሲሆን ስልጣን ላይ ባለው ቡድን ከ1000 ሰዎች በላይ የተገደሉ መሆናቸውና ከ40 ሺ በላይ የሚገመቱ ሰዎች የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ጠባቂ የነበረውና በይፋ የፈረሰው ወታደራዊ ተቋም አባላት ናቸው የተባሉ አምስት ወታደሮች በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸውን የቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለፈው አርብ ጥር 13 ቀን 2008 ዓም  ንጋት ላይ በዋናዋ ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ከሚገኝ አንድ የመሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ በመግባት የተወሰኑ መሳሪውያዎችንና የጸረ ታንክ ሮኬት መተኮሻዎችን የዘረፉትን ሰዎች ማደኑ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ቀድም ሲል ከተያዙት ጋር ተዳምሮ በአሁኑ ወቅት አስር ወታደሮችና አንድ ሲቪል በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በጋና ወስን አካባቢ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሌላ የቀድሞ ወታደር ተገድሏል። መሳሪያው መዘረፉ የአገሪቱን የጸጥታ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ያደረሰ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የሚጠርጠሩ ሌላ ሰባት ወታደሮች እየተፈለጉ መሆናቸው ታውቋል። የቀደሞ ፕሬዚዳንት ጠባቂ ወታደራዊ ተቋም 1300 የሚሆኑ አባላት የነበሩበት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ተቋሙን ይመሩ የነበሩት ጄኔራሎች በዚህ ዓመት መስከረም ወር ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ካደረጉ በኋላ ተቋሙ በይፋ እንዲፈርስ የተደረገ መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø መቀመጫውን በምስራቅ ሊቢያ ያደረገውና  ዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው የሊቢያ ፓርላማ  በቅርቡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት የቀረበውን የአንድነት መንግስት የስምምንት ረቂቅ ለማጸድቅም ሆነ ለመጣል ይሰብሰባል ዛሬ ጥር 16 ቀን 2008 ዓም ተብሎ ተጠብቋል።  የምክር ቤቱ አባላት ቁጥር 177 ሲሆን ስብሰባውን ለመጀመርም ሆነ ውሳኔውን ለማጸደቅ 89 አባላት መገኘታቸውን የሚጠይቀው ምልአተ ጉባዔ መሟላት አለበት ተብሏል። በሊቢያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ሁለት ተጻራሪ መንግስታት ያሉ ሲሆን አንደኛው በምዕራብ ሊቢያ ትሪፖሊ ውስጥ መቀመጫውን ያደረገው በሚሊሺያዎች የተቋቋመው መንግስት ነው። በምስራቅ ሊቢያ በሚገኘው ምክር ቤት ውስጥ ስድሳ የሚሆኑ የምክር ቤቱ አባላት የተመድን የእርቅ ሀሳብ የሚቃወሙ ሲሆን ረቂቅ የስምምነቱ ሀሳብ የአብዛኛውን ድምጽ ማግኘቱና አለማግኘቱ እስካሁን አልታወቀም።   

  

 

 

 

ጥር 14 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም ከተለያዩ ቦታዎች በወያኔ አግአዚ ጦር ተይዘው የታሰሩት ዜጎች ቁጥር በአንዳንድ ወገኖች ግምት አምስት ሺ ይባል እንጅ ቁጥሩ ከዚያ በላይ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ቀደም ብሎ ከነበሩት ጋር ተዳምሮ የእስረኞቹ ቁጥር በጣም በመብዛቱ የወያኔ ባለስልጣኖች የደርግ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በወረሳቸውና አሁን  የመንግስት ቤቶች ናቸው በሚባሉት ውስጥ እስረኞችን እያጎሩ መሆኑ ታወቀ።   በተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙ የተወረሱ ቤቶች፤ በአስኮ መንገድ ቀደም ሲል የወያኔ ባለስልጣናት ይኖሩበት በነበሩ ቤቶች ውስጥ እስረኞች  መታሰራቸው ታውቋል። በአበባ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ፤ አጠገቡ ከሚገኘው ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ፤ ኮተቤ ደህንነት መስሪያ ቤት፤  ቦሌ ወሎ ሰፈር በሚገኝ የደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ከቤተሰቦቻቸው ተሰውረው የታሰሩ እስረኞች ቁጥር ከፍተኛ  መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን ቀድም ብሎ ወደ መቀሌና ወደ ሌሎች ቦታዎች ተወስደው የታሰሩ እስረኞች  ቁጥርም እጅግ ብዙ እንደሆነ ጉዳዩን የተከታተሉ ወገኖች ይናገራሉ።

 

Ø በአገራችን በገባው ድርቅና ረሃብ ምክንያት የመኖሪያ ቀዬያቸውን እየለቀቁ ወደ አዲስ አበባ እየፈለሱ የሚመጡ ዜጎች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሄዱ ታወቀ። ሰሞኑኑ ዘጋቢያችን በመርካቶ ራጉኤል ቤተክርስትያን  አካባቢ ያነጋገራቸው ወገኖች  ከትግራይና ከወሎ ቦረና የመጡ መሆናቸውን የገለጸሉት ሲሆ   የእርዳታ ስንዴ እንሰጣችኋለን ከሚል ተስፋ በስተቀር የተሰፈረልን እህል ባለመኖሩ ልጆቻችን ሲሞቱ ከማየታችን በፊት በራችንን ዘግተን መምጣቱን መርጠናል ብለውታትል። በአሁኑ ወቅት በረሃብ ምክንያት ከመኖሪያቸው ፈልሰው አዲስ አበባ የገቡት ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እየታየ ሲሆን በእጃቸው ለሚጎትቷቸውና በጀርባቸው ላዘሉዋቸው ሕጻናት የሚበላና የቀመስ ለማግኘት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ቤት በማንኳኳት እየለመኑ መሆናቸው ይታያል።

በተያያዘ ዜና  ሕጻናትን አድን (Save the Childeren) የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ አለም አቀፍ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሚስስ ካሎሪን ማይልስ (Carolyn Miles) በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የድርቁን አካባቢዎች የጎበኙ መሆናቸውን ገልጸው በአሁኑ ወቅት በምግብ እጥረት 10.2 ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚሰቃይ አስረድተዋል። የችግሩ መጠን በጣም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው የወያኔ አገዛዝ ችግሩን ሊቋቋመው እንደማይችል ተናግረዋል። ለሚቀጥሉት 18 ወራት በኢትዮጵያ በድርቁ እየተሰቃዩ ላሉት  ሕጻናት መርጃ  ድርጅታችው 144 ሚሊዮን ዶላር የተመነ ቢሆንም እስካሁን ድረስ የተገኘው ከ30 ሚሊዮን ዶላር ያልዘለለ መሆኑን አስረድተዋል። በረሃብ ከተጠቁት ዜጎች መካከል 5.8 ሚሊዮን የሚሆኑት ሕጻናት መሆናቸውንም ሚስስ ማይልስ ተናግረዋል። ቀደም ብሎ የተባበሩት መንግስታት የአለም የምግብ ድርጅት በእርዳታ አሰባሰብ በኩል ተመሳሳይ ችግር ያለበት መሆኑን መግለጹና ከሚያስፈልገው 685 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ ያገኘው 86 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መሆኑ መናገሩ ይታወሳል።

 

በደቡብ ሱዳን ከሁለቱም ተጻራሪ ወገኖች በተውጣጡ ወኪሎች እንዲመሰረት ስምምነት ተደርሶበት የነበረው ጊዜያዊ የአንድነት መንግስት በተግባር እንዲውል የተሰጠውን ቀነ ቀጠሮ ያሳለፈ መሆኑ ተገለጸ። የአንድነት መንግስቱ እንዳይመሰረት እንቅፋት ከሆኑት አቢይ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የስልቫኬር መንግስት ከስምምነት ውጭ የአካባቢ አስተዳደሮችን ከ10 ወደ 28 ከፍ ማደረጉንና 28 አስተዳዳሪዎች መሾሙን  በሪክ ማቻር የሚመራው የአማጽያን ኃይል በመቃወሙና ባለመቀበሉ  መሆኑ ታውቋል። በዕቅዱ መሰረት ከሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች የተውጣጣ የአንድነት መንግስት ከጥር 13 ቀን 2008 ዓም በፊት መመስረት ነበረበት። ለስምምነቱ መፍረስ ሁለቱም ወገኖች እርስ በርሳቸው የተወነጃጀሉ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ ሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች ጦርነቱን በማስፋፋት እንዲሁም  በጦር ሜዳዎች የጅምላ ርሸና በማካሄድ፤ የያዟቸውን ዜጎች ዱካ በማጥፋት፤ በቡድን ሴቶችን በመድፈር፤ ለወሲብ አገልግሎት ሴቶች አግቶ በመያዝ ፤ አስገድዶ ጽንስን በማስወረድና የመሳሰሉ  ወንጀሎችን በመፈጸም በኩል ሁለቱም ወገኖች ተጠያቂዎች ናቸው ብሏል።

 

Ø የቱኒዚያ ፕሬዚዳንት በአገሪቱ የተቀጣጠለውን ሕዝባው አመጽ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እየተባባሰ የመጣው ስራ አጥነት ዜጎችን ማስቆጣቱ የሚጠበቅ መሆኑን ጠቅሰው መንግስታቸው ስራ አጥነትን ለመቀነስ የተቻለውን ጥረት እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። ትናንት አርብ ጥር 13 ቀን በራዲዮና በቴለቪዥን ባስተላለፉት መልእክት በስራ አጥነት ምክንያት የሚበላውን ያጣውንና ኑሮውን መግፋት ያልቻለውን ሰው ትእግስት አድርግ ማለት አይቻልም ካሉ በኋላ እንደ አይሲስ ዓይነቱ አክራሪና አሸባሪ ቡድኖች ሁኔታውን ተጠቅመው ትርምስ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ መንግስት 6000 ስዎች ባስቸኳይ ስራ የሚያገኙበት ሁኔታ ያመቻቸ መሆኑን ገልጸው ስራ በመስጠት በኩል ያለውን የሙስና አስራር እንደሚመርምሩ ተናግረዋል። በተቃውሞ ስም የሕዝብና የግል ንብረቶች በመውደማቸው ሰዓት እላፊ አዋጅ በዋና ከተማዋ የታወጀ መሆኑን የአገር ግዛት ሚኒስቴር አስታውቋል። የፈረንሳይ መንግስት በሚቀጥሉት አምስት አመታት 1.1 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ለቱኒዚያ ለመስጠት ቃል የገባ መሆኑም ተዘግቧል።   

 

Ø ሰሞኑን የብሩንዲን ባለስልጣኖች ሲያነጋግሩ የሰነበቱት የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ልኡካን በአዲስ አበባ ተገኝተው ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር መነጋገራቸው ታውቋል። የቡርንዲ ባለስልጣኖች  ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ውይይትና ድርድር እንዲያደርጉ የሚለውንና የአፍሪካ ኅበረት የሰለም አስከባሪ ኃይል በብሩንዲ ተገኝቶ ሰላም እንዲያስከብር የሚሉትን ሀሳቦች በጥብቅ የሚቃወሙ መሆናቸውን የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ለተመድ ሉኡክን በስብሰባ ላይ   ገልጸዋል። የልኡኩ አባል የሆኑት የአሜሪካው የጸጥታው ምክር ቤት ተወካይ የተመዱ የልኡክ ቡድን በብሩንዲ ለማከናወን  ያቀደው ተግባር ፍሬ ያልሰጠ መሆኑን  ጠቅሰው በአገሪቱ ውስጥ  እየተካሄደ ያለውን ግድያ ለማስቆም የውጭ እርዳታ የሚጠይቁ ወገኖች በርካታ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቀድሞ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ጃን ባፕቲስት ባጋዛ እና ሌሎች የቀድሞ የብሩንዲ ባለስልጣኖች ተመድ በአገሪቱ ውስጣ አሉ የተባሉ የጅምላ መቃብሮችን እንዲያጣራና ግድያውን ለማስቆም ጥረት እንዲያደረግ ጥያቄ ያቀረበ መሆኑ ተነግሯል። የተመድ የልኡካን ቡድን በአዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር ምን እንደመከረ ባይገለጽም በብሩንዲ ላይ ጠንከር ያሉ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ስምምነት ያለ መሆኑ ይታወቃል።

 

 

ጥር 13 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት ጥር 12 ቀን 2008 ዓ/ም በአዲስ አበባ ተከብሮ በዋለው የቃና ዘገለሊላ በዓል ላይ የበዓሉ ታዳሚ በነበሩት ምዕመናንና በፖሊስ መካከል ግጭት ተነስቶ ለግዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በአካላቸው ላይ ጉዳት እንደደረሰባቸውና በፖሊስ ታፍነው እንደተወሰዱ ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አስረድቷል። በተለምዶ ሾላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘውን የየካ ቅዱስ ሚካኤል ታቦትን በማጀብ ወደ መንበሩ ለማስገባት ተሰባስበው የነበሩ ምዕመናን ባህላዊ ዘፈኖችና ጭፈራዎች እያደረጉ በሚጓዙበት ወቅት  ለጭፈራ ማድመቂያ የያዙትን  ዱላ በተለያዩ ስፍራዎች ቆሞ ይጠብቅ የነበረው የወያኔ የፖሊስ ኃይል ለመንጠቅ ሞከራ ሲያደረግ ከፍተኛ ግብግብ መከሰቱ ታውቋል።  ዱላቸውን የተቀሙት ወጣቶች እንደጀመራችሁ ጨርሱን በማለት ፖሊሶችን ማጥቃት ስለጀመሩ በተነሳው ግጭት በርካታዎች የመፈንከት አደጋ የደረሰባቸው መሆኑና አንዳንዶቹ ከአደጋው ለማምለጥ ሲሮጡ የእግር ወለምታ አጋጥሟቸው ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ከስፍራው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ብዙዎች ታስረው በመኪና ተጭነው ወደ አልታወቀ ቦታ የተወሰዱ ሲሆን ከፖሊስ አባላት መካከልም ጉዳት የደረሰባችው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል። 

 

Ø ከዚህ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም መነሻ አድርጎ በተለያዩ ቦታዎች ተቀጣጥሎ የነበረው ሕዝባዊ አመጽ አሁንም ያልበረደ መሆኑ ይነገራል። በምስራቅ ወለጋ በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞዎች የነበሩ ሲሆን እንዲሁም በአሩሲ ዪኒቨርስቲ  ሁለት ተማሪዎች መታጠቢያ ቤታቸው ውስጥ በስለት ተወግተው ጉዳት እንደደረሰባችው ተዘግቧል። በተማሪዎቹ ላይ ጉዳት ያደረሱት እነማን መሆናቸው ለጊዜው ባይታወቅም የወያኔ ሰላዩች ሳይሆኑ አይቀሩም የሚል ጥርጣሬ አለ።

 

Ø በጋምቤላ በአኙዋክና በነዌር ብሐረሰብ መካከል ግጭት ተቀስቅሶ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ መሆኑ እየተነገረ ነው። በግጭቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባችው በሆስፒታል እየታከሙ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ወደ ዋና ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት የተቋረጠ መሆኑም ተዘግቧል። የወያኔ ባለስልጣኖች በከተማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ተጨማሪ የጸጥታ ኃይሎች በማሰማራት  ፍተሻ እያካሂዱ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø በቱኒዚያ ያለው ስራ አጥነት ጣራ በመንካቱ ምክንያት ሌላ የአመጽ እንቅስቃሴ የተቀሰቀሰ መሆኑ ተነገረ። በቱኒዚያ ሰሜናው ግዛት ባለፈው ሳምንት አንድ ወጣት ለመንግስት ስራ ያቀረበው ማመልከቻ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከኤሌክትሪክ ማስራጫ ምሰሶ ላይ ወጥቶ በኤሌክትሪክ ራሱን መግደሉን ተከትሎ የተጀመረው የተቃውሞ ስልፍ ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም በቱኒዚያ የተለያዩ ከተሞች ተቀጣጥሎ የቀለጠለ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ፌሪያና በተባለችው ከተማ የተቃውሞ ስልፈኞቹ አንድ የፖሊስ መኪና አነቃንቀው በመገልበጣቸው በውስጧ የነበረው አንድ ፖሊስ ህይወቱ ያለፈ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። የዛሬ አምስት ዓመት ሞሃመድ ቦአዚዝ የተባለው ጎልማሳ ራሱን ማቃጠሉን ተከትሎ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ በወቅቱ የነበረውን የቢን አሊን አገዛዝ ያስወገደ ቢሆንም ባለፉት አምስት አመታት የስራ አጡ ቁጥር እየጨመረ እንጅ እየቀነሰ አለመሄዱ ታውቋል። ባሁኑ ወቅት  ከተላለዩ የትምህርት ተቋሞች ተመርቀው ከሚወጡ ምሩቃን መካከል 62 ከመቶ የሚሆኑት ስራ የሌላቸው መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ባለፉት አምስት አመታት ሌሎች የኢኮኖሚና የሶሻል ሁኔታዎች ያልተሻሻሉ መሆናቸውም ይነገራል። በትናንትናው የተቃውሞ ሰልፍ ጉየበሊ በምትባለዋ ከተማ አንድ የፖሊስ ጣቢያ የተቃጠለ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ከ40 በላይ የሚሆኑ ሰዎችና 59 ፖሊሶች ጉዳት የደረሰባችው መሆኑ ተዘግቧል።

 

Ø በትናንትናው ምሽት በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ ታጣቂዎች በአንድ የምግብ ቤት ውስጥ ባካሄዱት ተኩስ 20 የሚሆኑ ሰዎችን የገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ታጣቂዎቹ ወደ ምግብ ቤቱ የገቡት በአካባቢው  በመኪና ላይ የተጠመዱ ሁለት ፈንጅዎችን ባፈነዱበት ወቅት ሲሆን የምግብ ቤቱን አካባቢ ለሰዓታት ያህል ተቆጣጥረው እንደነበር ተዘግቧል። የሶማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር የተኩስ ልውውጥ በማድረግ አካባቢውን የተቆጣጠሩ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባለስልጣኖች የታጣቂዎቹ መሪ በቁጥጥር ስር ተደርጓል የሚል መግለጫ ሰጥተዋል። አልሸባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል።

 

 

Ø በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት አርብ አልሸባብ በደቡብ ሱማሊያ በኬኒያ የሰለም አስከባሪ ኃይል አባላት ላይ ጥቃት ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን ይህ ጥቃት ከመድረሱ ከ45 ቀናት በፊት ጥቃት በአካባቢው ጥቃት ሊሰነዘር እንደሚችል በመግለጽ ለኪኒያ ወታደሮች ማስጠንቀቂያ የተሰጣችውም መሆኑን በጌዶ አካባቢ የሶማሊያ መንግስት መከላከያ ኃይል መሪ ጄኔራል ጉሬ ለዜና ምንጮች ገልጸዋል።  አልሸባብ ያሉትን በርካታ አባላት ከሁሉም አካባቢዎች  ወደ ጌዶ ግዛት እንደሚያመጣና የሚመጡትም ጠንካራ ተዋጊዎች እንደሆኑ የሚገልጽ መረጃ አግኝተን ይህንን ለኬኒያውያን ወንድሞቻችን አስተላልፈናል ብለዋል። አልሸባብ 100 የኬኒያ ወታደሮች ገድያለሁ ያለ ሲሆን የኬኒያ ባለስልጣኖች ምንም እንኳ በሶማሊያ ውስጥ የኬኒያ ወታደራዊ ተልእኮ ይቀጥላል የሚል መግለጫ ቢሰጡም  ምን ያህል ወታደሮች እንደተገደሉባችው እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።

 

Ø በካይሮ ፖሊሶች አሸባሪዎች ተደብቀውበታል ብለው የሚጠርጥሩትን በአንድ ሕንጻ ውስጥ የሚገኝ የመኖሪያ ክፍልን ለመፈተሽ ጥረት እያደረጉ እያሉ አንድ ቦምብ ፈንድቶ  ስድስት ፖሊሶችንና ሶስት ሰላማዊ ሰዎች የገደለ መሆኑንና የፖሊስ ኃላፊውን ጨሞር ሌሎች 13 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ  ከቦታው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የግብጽ መንግስት ባለስልጣኖች አደጋውን ያደረሱት የእስላም ወንድድማቾች ድርጅት አባሎች መሆናቸውን ገልጸዋል። አደጋው የደረሰው የፒራሚድስ ሀውልቶች ካለበት አጠገብ ከሚገኘው ጊዛ ከተባለው አካባቢ ነው።  ሰሞኑን የግብጽ መንግስት ለፕሬዝዳንት ሙባረክን ከስልጣን መወገድ ምክንያት የሆነው የግብጽ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የጀመረበት አምስተኛ አመት መከበሩን ተከትሎ ችግር እንዳይነሳ የጸጥታ ሁኔታውን ማጥበቁ የሚታወስ ሲሆን በተባለው ህንጻ ላይ ፖሊሶች ፍተሻ ያካሄዱት አሸባሪዎች አደጋ ሊያደርሱ እየተዘጋጁ ነው የሚል ጥቆማ ስለደረሳቸው መሆኑ ታውቋል።

 

Ø ዛሬ ጥር 13 ቀን 2008 ዓም ከቱርክ ወደ ግርክ ስደተኞችን ጭና ስትጓዝ የነበረች አንዲት ጀልባ በባህር ውስጥ በመስጠሟ ተጭነው ከነበሩት መካከል ቢያንስ 44 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። ። የግሪክ የጠረፍ ጠባቂዎች ቢያንስ 74 ሰዎች ያዳኑ መሆናችውን የተናገሩ ሲሆን ሞተው አስከሬናቸው ከተገኘው 44 ሰዎች መካከል 20 ህጻናት 17 ሴቶችና 10 ወንዶች  መሆናቸው ታውቋል። ስደተኞቹ አብዛኞቹ የሶሪያ ዜጎች ሲሆኑ ይጓዙበት የነበረው ጀልባ አስተማማኝ ያልነበረ መሆኑን ብዙዎቹ ይናገራሉ። ባለፉት 22 ቀናት ብቻ 113 ስደተኞች ባህሩ ውስጥ ስምጠው የሞቱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ህጻናትን ጨምሮ 12 ስደተኞች መሞታቸው ተዘግቧል።

 

Ø ወደ ብሩንዲ የተጓዙት የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የልኡካን ቡድን አባላት ዛሬ አርብ ጥር 13 ቀን 2008 ዓም ከብሩንዲ የተለያዩ ባለስልጣኖች ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸው ተዘግቧል። የብሩንዲ ባለስልጣኖች ከተቃዋሚ አባላት ጋር ተገናኝተው እንዲወያዩና ስምምነት እንዲያደርጉ እንዲሁም በአፍሪካ አድነት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል የሚገባበትን መንገድ እንዲያመቻቹ የልዑኩ ቡድን አባላት ግፊት የሚያደርጉ መሆናቸው ታውቋል።  ቡድኑ በቅድሚያ የአገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት አግኝቶ ማነጋገሩ የታወቀ ሲሆን በስበስባው ወቅት ምክትል ፕሬዚዳንቱ በአገር ውስጥ ችግር መኖሩን አምነው ችግሩን ለመቅረፍ የብሩንዲ መንግስት የተቻለውን እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የልኡካኑ ቡድን በፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት ከፕሬዚዳንቱ ጋር ንግግር ያደርጋለ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ አገሪቱ ስለሚገባበት ሁኔታ ፕሬዚዳንቱን ለማሳመን ከፍተኛ ግፊትት ያደርጋል ተብሎ ይገመታል። ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በዋናዋ ከተማ በደረሰ ግጭት አንድ ሰው መሞቱና አንድ ሌላ ሰው የአካል ጉዳት የደረሰበት መሆኑ ታውቋል።

 

 

 

 

 

 

 

 




ጥር 12 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት ጥር 11 ቀን 2008 ዓም በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ የጥምቀት በዓል በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የአዲስ አበባ በዓል አከባበር ላይ  በወያኔ የደኅኔት ኃይሎች ተጥለቅሎ እንደንበር ከስፍራው የመጣው ዘገባ ገልጿል። ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነና የሲቪል ልብስ የለበሱ  የወያኔ የደህንነት ተቀጣሪዎች አስተናባሪ የሚል ባጅ ደረታቸው ላይ ለጥፈው ታቦቱን አጅቦ ወደ መንበሩ ለማስገባት ከሚንቀሳቀሰው ሕዝበ ክርስትያን ጋር በመቀላቀል ሲያስፈራሩ የነብሩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።  በአዲስ አበባ እና በአካባቢዎ ባሉ አንዳንድ ቦታዎች ተቃውሞ የሚያሰሙ ወጣቶች የተደበደቡና ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው የታወቀ  ሲሆን በተለያዩ ከተሞችም የጥምቀት በዓሉን አስታኮ በወያኔ አገዛዝ ላይ ተቃውሞ ሲሰማ መዋሉ ተነግሯል።  

 

Ø ካሪታስ ኢንተርናሽና የተባለው የካቶሊክ የአርዳታ ሰጭ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሚስተር ማይክል ሮይ ከቫቲካን ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ አስፈላጊው እርዳታ ካልተደረገ በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ ከፍተኛ የሆነ እልቂት ሊከተል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ምርት ከ90 ከመቶ በላይ መቀነሱና በዚህም 10.5 ሚሊዮን ሕዝብ በድርቁ እንደተጠቃና የ50 ዶላር እርዳታ የሚያስፈልግ መሆኑን በማስታወስ ሚስተር ሮይ የችግሩን አስከፊነት ገልጸዋል። አያይዘውም ካሁኑ ጀምሮ በእርዳታው ላይ መረባረብ ካልተቻለ የዛሬ ሰላሳ አመት ተፈጥሮ የነበረው ዓይነት የእልቂት ሁኔታ ሊደገም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

በተያያዘ ዜና ሞጆ አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በተራቡ ዜጎች ስም ለእርዳታ የመጣ ስንዴ በበርካታ ጋሪዎች ተጭኖ ለጥቁር ገበያ ሲወጣ የተደረሰበት መሆኑ ከስፍራው ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ችለናል። በመቂ ከተማና በሞጆ ከተማ መካከል በሚገኝ የህብረት ስራ ማህበር መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የነበረ ከእርዳታ የተገኘ ስንዴ ጥር 10 ቀን 2008 ዓ/ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ገደማ ላይ አስራ አምስት በሚሆኑ በበቅሎ በሚጎተቱ ጋሪዎች ተጭኖ  ወደ ጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሲወጣ የተመለከቱ የአይን እማኞች የስንዴው ብዛት ሁለት ሺህ ኩንታል ሊጠጋ እንደሚችል የገለጹ ሲሆን ጉዳዩን ለአካባቢው ባለስልጣኖች ቢያቀርቡም እርምጃ አለመወሰዱን አስታወቀዋል። 

 

Ø የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚ እና ተለጣፊ የሆነው የአፋር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የበላይና የበታች አመራር አባላት በአፋር ሰመራ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲካሂዱት በነበረው ስብሰባ ላይ መግባባት ሳይቻል ቀርቶ ስብሰባው መበተኑን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አስረድቷል።  የስብሰባው ዋና ርዕስ በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ለመወያየት ቢሆንም በመካከላቸው ከፍተኛ የሆነ መወነጃጀል ስለተከሰተ ስብስባው የታቀደለት ጊዜ ሳያበቃ በድንገት የተበተነ መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። በስብሰባው ወቅት ስራችሁን አልሰራችሁም፤ በህገ ወጥ ንግድ ላይ ተሰማርታችሁ የግል ጥቅም አጋብሳችኋል፤ በሙዚቃ በመስማትና ጫት በመቃም ጊዜያችሁን ከማሳለፍ ውጭ ለአፋር ነዋሪ ያደረጋችሁት አንዳችም ነገር የለም በማለት ባለስልጣኖቹ በበታች አመራር አባላት ስድብ አዘል  ውንጀላ ያወረዱባቸው ሲሆን ሌሎቹ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ በማንሳተቸው ስብሰባው ተበጥብጦ  እንዲቋረጥ የተደረገ መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።

 

Ø የኢቦላ በሽታ ጠፍቷል የሚል አዋጅ በተነገረ በሳምንት ጊዜ ውስጥ በምዕራብ አፍሪካ በሲየራ ሊዮን አዲስ የኢቦላ በሽተኛ መገኘቱን የዓለም የጠና ድርጅት ዛሬ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም አስታወቀ። በኢቦላ በሽታ የታመመችውና አሁን ህክምና እየተደረገላት የምትገኘው የ38 ዓመት ሴት ቀደም ብሎ በጥር 3 ቀን 2008 ዓም በኢቦላ የሞተችውንና አክስት የምታሆናትን የ22 ዓመት ወጣት ሴት ስታስታምም የነበረችና በኋላም  ልጅቷ ስትሞት የሃማኖት ግዳጇን ለመወጣት ገላዋን ያጠበቻት መሆኑ ተነግሯል። የበሽተኛው ህመም የታወቀው ትናንት ጥር 11 ቀን ሲሆን ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ በመታከም ላይ መሆኗ ተጠቅሷል። የሲየራ ሊዮን ባለስልጣኖች ወደፊትም ተመሳሳይ ህመምተኞች ሊታወቁ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸው ሕዝቡ በዚህ ምክንያት እንዳይደናገጥ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

 

Ø የግብጽ የመከላከያ ሚኒስትር ዛሬ ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ  በሲና ባህረ ሰላጤ የአይሲስ ታጣቂዎች በአንድ መፈተሻ ቦታ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አምስት የግብጽ ወታደሮች የተገደሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ወታደሮቹ የሞቱት ረቡዕ ጥር 11 ቀን ምሽት ላይ በአንድ መፈተሻ ጣቢያ ላይ የታጠቁ ሰዎች በጠባቂ ወታደሮቹ ላይ ጥቃት ሰንዝረው በተካሄደው የተኩስ ልውውጥ ሲሆን አጥቂዎቹ እየተፈለጉ መሆናቸው ተገልጿል። አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን በዌብ ሳይት ባሰራጨው ዜና ሶስት የአይሲስ ወታደሮች ኤል አሪሽ በሚባለው ስፍራ በግብጽ ወታደሮች ላይ ጥቃት ፈጽመው ጉዳት ማድረሳቸውን ገልጿል። የረቡዕ ግድያ  የሙባረክን አገዛዝ ያወረደው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ አምስተኛ ዓመቱን ከሚከበርበት ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ የተካሄደ ሲሆን ሰሞኑን  ተመሳሳይ ጥቃቶች ይሰነዘራሉ በሚል የግብጽ የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።  

 

Ø የጅቡቲ መንግስት ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ስምምነት የተፈራረመ መሆኑ ተገለጸ። በትናንትናው ዕለት ቻይና የንግድ ዞኖችን በጂቡቲ ውስጥ ስለምታቋቁምበት ሁኔታና የቻይና ባንኮች በጂቡቲ ለመንቀሳቀስ የሚያስችላቸውን ህጋዊ ሁኔታ አስመልክቶ ስምምነት የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ከጥቂት ጊዜ በፊት  ቻይና በጂቡቲ ውስጥ የባህር ኃይል የጦር ሰፈር እንድታቋቁም የጂቡቲ ባለስልጣኖች መፍቀዳቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ቀድም ብሎ በጂቡቲ ውስጥ የጦር ሰፈር ያላቸውን ፈረንሳይንና አሜሪካንን ማስከፋቱ ይታወሳል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት መልእክተኞች ዛሬ ጥር 12 ቀን 2008 ምሽት ላይ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ እንደሚገኙ ታወቀ። የመልእክተኞቹ ቁጥር 30 ሲሆን ከመካከላቸው ውስጥ የጸጥታው ምክር ቤት አባላት፣ ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች የሚገኙበት መሆኑ ታውቋል። በብሩንዲ መንግስት ባለስልጣኖች ላይ የሰላ ሂስ ሲያስተላልፉ የነበሩት የአሜሪካ የጸጥታ ምክር ቤት ተወካይ ሳማንታ ፖወር ከመልእክተኞች ውስጥ አንዷ ሲሆኑ አቋማቸው  የብሩንዲን ባለስልጣኖች ሲያስቆጣ መቆየቱ ይታወቃል።  

Ø የኬኒያ መንግስት ማሊንዲ በሚባለው የባህር ዳርቻ ከተማ  የእስላም አክራሪዎች ናቸው የሚላቸውን አራት ግለሰቦች የገደለ መሆኑን አስታውቋል። አራቱ ሰዎች የተገደሉት በጸጥታ አባላት ላይ ተኩስ በመክፈትና ቦምብ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሲሞክሩ መሆኑን ፖሊስ ገልጾ ከተገደሉት መካከል ባለፈው ታኅሣሥ ወር ግድያ አካሂደው ሲፈለጉ የነበሩ አሸባሪዎች እንደሚገኙበት ገልጿል።

በተያያዘ ዜና ኬኒያ ወታደራዊ ተቋም ቺፍ ኦፍ ስታፍ የሆኑት ጄኔራል ባለፈው አርብ ሶማሊያ ውስጥ የአልሸባብ ኃይሎች በፈጸሙት ጥቃት የኬኒያ ወታደሮች መገደላቸውን አምነዋል። ምን ያህል ወታደሮች እንደሞቱ ባይገልጹም አልሸባብ በካምፑ ላይ ያፈነዱት ቦምብ ከአስራ ስምንት ዓመት በፊት ናይሮቢ አሜሪካን ኤምባሲ ውስጥ ከፈነዳው ቦምብ ሶስት እጥፍ የሚሆን ኃይል የነበረው መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው አርብ በተደረገው ጥቃት አልሸባብ ከመቶ በላይ የሆኑ የኬኒያ ወታደሮችን ገድያለሁ መግለጹ ይታወሳል።  

 




ጥር 11 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ባለፈው ሳምንት በአዋሳ ከተማ በሚገኛው የመኪና መናኻሪያ ውስጥ ወደ ሆሳዕናና ወደ ተለያዩ ከተማዎች በሚሄዱ መኪናዎች መቀመጫዎች ላይ ሞት ለወያኔ ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚል ርዕስ የያዛ ፅሁፍ መበተኑን ከስፍራው ዘግየቶ ያገኘነው ዜና ይገልጻል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት በዲላ ዩኒቫርሲቲ ውስጥ በሚማሩ ተማሪዎች የወያኔ አጋዚ ጦር ቦምብ ወርውሮ ሁለት ተማሪዎችን መግደሉና በሌሎች ላይ የመቁሰል አደጋ ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን  በትናነትናው ዜናችን እንደገለጽነው ቁጥሩ ከተማሪዎቹ ጋር እኩል ለኩል የሆነው የአግአዚ ጦር አሁንም ተማሪዎችን እየጨፈጨፈ፤ ሴቶችን እየደፈረና ንብረት በተለይም የተማሪዎችን የእጅ ስልክ በመቀማት ከፍተኛ ግፍ እየፈጸመ መሆኑን ከስፍራው የሚደርሰን ዜና ይገልጻል። 

 

Ø በትናንትናው ዕለት በሀዲያ ዞን ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት በዛሬው ቀን በአንዳንድ አካባቢዎች የጀመረ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። የትራንስፖርት አገልግሎቱ ሊጀመር የቻለው የወያኔ ባለስልጣኖች በሹፌሮችና በባለንብረቶች ላይ ያወጡትን የቅጣት  መመሪያ አንስተናል በማለታቸው አድማ መቸዎቹ በመስማማታቸው ሲሆን ውጥረቱና አለመተማመኑ ግን አሁንም ያለ መሆኑ ይታያል ተብሏል።  ከዋቸሞ ዩነቨርስቲ ተወስደው የደረሱበት ያልታወቁት ተማሪዎች ቁጥር በትናንት ዘገባቸን እንዳቀረብነው አራት ሳይሆን ስምንት ተማሪዎች መሆናቸውን በመግለጽ በዚህ አጋጣሚ ለማረም እንወዳለን።  

 

 

Ø ትናንት ጥር 10 ቀን 2008 ዓም የአውሮፓው ህብረት ምክር ቤት (ፓርላማ)  ሰሞኑን በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የሕዝብ አመጽ አንተርሶ ባለ አስራምስት ነጥብ ጠንካራ ውሳኔዎች ማስተላለፉ ተገለጸ። የአውሮፓው ሕብረት ምክር ቤት (ፓርላማ) ውሳኔዎቹ ላይ ለመድረስ ያበቁትን በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን አሳዛኝ ጉዳዮች  በዝርዝር ገልጧል። ባለፉት ሁለት ወራት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም በኦሮሚያ የተካሄዱትን አመጾች ለመግታት ወታደሮች  ከ140 ሰዎች በላይ መግደላቸውን፤ የአዲስ አበባ መስፋፋት ብዙ አርሶ አደሮችን ያፈናቀለ መሆኑን፣ በአካባቢው የሰብአዊ መብት ጥሰት መኖሩን፤ የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች  አሸባሪዎች ናቸው በሚል  በርካታ ሰልፈኞችን ማሰሩን፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ የኦፌኮ መሪን አቶ በቀለ ገርባን የሚዲያ ሰዎችን እንደ አቶ ጌታቸው ሽፈራው፣ ዮናታን ተረሣ፣ ፈቃዱ ሚርካና የመሳሰሉት መታሰራቸውን ግንዛቤ የወሰደ መሆኑን ገልጿል። እንዲሁም ወያኔ ከዚህ በፊት በርካታ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ ተቃውሞ የሚካሂዱ ስልፈኞች፣ ተማሪዎችና እና ሌሎችን አስሮ በሽብረተኛ አንቀጽ ክስ በመመስረት እስር ቤት እያንገላታ መሆኑን   የእነ እስክንድር ነጋን፣ ተመስገን ደሳለኝን፣ ሰሎሞን ከበደን ዩሱፍ ጌታቸው፣ ውብሸት ታየን፣ ሳለህ ኢድሪስንና ተስፋለደት ኪዳኔን ስም በመጥራት ዘገባ ሁኔታውን የተረዳ መሆኑን ገልጿል። የወያኔ አገዛዝ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌንም ከየመን አፍኖ መውሰዱን የወያኔ ጦር በኦጋዴን ላይ የሚካሄደውን ጦርነትና ጭፍጨፋ አስከፊ መሆኑን እንዲሁም ባለፈው ግንቦት የተካሄደው ምርጫ በማስፈራራትና በማፈን መሆኑን በተጨማሪም ወያኔ በየአመቱ 3ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ከምዕራብ አገሮች የሚያገኝ አገዛዝ መሆኑ፤ አርሶ አደሮች ለም ከሆነው መሬታቸው እየተነቀሉ መሬታቸው ለባዕዳን ከበርቴዎች የሚሰጥ መሆኑን በመጥቀስ   ምክር ቤቱ አጠቃላይ  ግንዛቤ ያለው መሆኑን ገልጾ ውሳኔዎች ያስተላለፈ መሆኑን አሳውቋል።  በውሳኔውም በኦሮሚያና በሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች የወያኔ ወታደሮች የሚያደርሱትን ገደብ የለሽ ግድያ፤ የሰብአዊ መብት ረገጣ፤ ህገ ወጥ እስራትንና ሰቆቃዊ ድርጊትቶችን፤ የመናገርና የመጻፍ መብትን ማገድን እንዲሁም ወንጀለኞች ለፍርድ ሳይቀርቡ በነጻ መለቀቃቸውን አውግዟል። በመንግስት የጸጥታ ወታደሮች እየተደረጉ ያሉት የአፍናና የግድያ ተግባሮች ባስቸኳይ እንዲቆሙና መብታቸውን በመጠቀም በማሰማታቸው ብቻ የታሰሩ  ተማሪዎች፤ አርሶ አደሮች የፖለቲካ ተቃዋሚዎች፣ ምሁራን ጋዜጠኞችና ጦማራውያን በሙሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። በተደረጉት ግድያዎች ላይ ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ ምርመራና ማጣራት እንዲካሄድና ጥፋተኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጥሪ አስተላልፏል። ወያኔ የዓለም አቀፉንና የአፍርካ ህብረትን  የሰብአዊ መብት ቻርተርና ድንጋጌን ማክበር ያለበት መሆኑን ገልጾ በሚዲያ ላይ እያካሄደ ያለን የሞገድ አፈናና እንዲያነሳና ነጻ የሆኑ ሚዲያዎች ስራቸውን በነጻ የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቋል። እየተካሄደ ያለው ያለ አግባብ የሆነ የሰፈራ ፕሮግራም ምክር ቤቱን ያሳሰበው መሆኑን የገለጸ ሲሆን በአካባቢው የሚደረገው የልማት ስራ ከአካባቢው ሕዝብ ጋር ተመካክሮ መሆን እንደሚገባው አሳስቧል። የአውሮፓ አገሮች ለልማት ስራዎች ለወያኔ የሚሰጡት እርዳታና ብድር ከአገሪቱ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ጋር መመጣጠን መሆኑን ገልጾ የአውሮፓው ኅባረትና አባል አገሮች በንጹሐን ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለውን ርምጃ ኮንነው ድርጊቱን ለማስቆም አስፈላጊውን ተጽእኖ እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስርያ ቤት ቃል አቀባይ ሚስተር አድርያን ኤድዋርድስ ትናንት ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በየመን ከፍተኛ የሆነ የእርስ በርስ ጦርነት እየተካሄደ መሆኑ የሚታወቅ  ቢሆንም ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ከኢትዮጵያና ከሶማሊያ እየፈለሱ ወደ አገሪቷ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር 92 446 , መድረሱን ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ 82,268 ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል። ወደ የመን የተሰደዱት ዜጎች ቁጥር በየገዜው እየጨመረ የሄደው በዚያ ያለውን ሁኔታ ካለማወቅ የተነሳ መሆኑን ገልጸው በአሁኑ ወቅት የስደተኞቹ ህይወት በከፍተኛ ደረጃ አደጋ ላይ መሆኑን ዘርዝረው አስረድተዋል። ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም 106 ስደተኞችን የጫነች አንድ አነስተኛ ጀልባ ባህሩ መሀል ላይ በመስጠሟ  36 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ተገልጿል። ከተረፉት ሰባዎች መካከል አንዱ ብቻ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ታውቋል። ቃል አቀባዩ ይህን አደገኛ የስደተኞች ጉዞ የሚያደራጁት ገንዘባቸውን ብቻ የሚያሳድዱትና ለሰው ህይወት ደንታ የሌላቸው አስተላላፊዎች መሆናቸውን ገልጸው በየመን ስላለው አደገኛ ሁኔታና ለባህር ትራንስፖርት ብቃት በሌላቸው ጀልባዎች ላይ መሳፈር አደገኛ ስለመሆኑ ጉዳይ ስደተኞቹ ሊያዉቁ የሚችሉበት ሁኔታ መፈለግ አለበት ብለዋል።

 

 

Ø ራሷን ሶማሌላንድ ብላ የምትጠራው የሶማሌ ግዛት ባለስልጣኖች ትናንት ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ሕገ ወጥ ስደተኞች የሚሏቸውንና በዋናዋ ከተማ በሀርጌሳ የሚገኙትን 300 ኢትዮጵያውያንና ለወያኔ አገዛዝ ባለስልጣኖች የሚያስረክቡ መሆናቸው ገልጸዋል። ከስደተኞቹ መካከል አብዛኞቹ የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላት መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ሰደተኞቹን ባስቸኳይ ለመመለስ ዝግጅቱ የተጠናቀቀ መሆኑን ባለስልጣኖቹ ገልጸዋል። ሱማሌላንድ በ1982 ዓም ራሷን አገር በማለት ያወጀች ሲሆን እስካሁን ድረስ በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ እውቅናን አላገኘችም።  

 

 

Ø ዛሬ ጥር 11 ቀን 2008 ዓም በምዕራብ ፓኪስታን በቻርሳዳ ከተማ በሚገኘው ባቻ ከሃን ዩንቨርስቲ ላይ ታጣቂዎች ባካሄዱት የቦምብ ጥቃት 19 ሰዎች መገደላቸውና ከ50 በላይ መቁሰላችወን የፓኪስታን ፖሊስ ገልጿል። አጥቂዎቹ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተኩል ሲሆን የዩኒቨርስቲውን የጀርባ አጥር በመዝለል ጥቃቱን መሳሪያ በመተኮስና ቦምብ በማፈንዳት መፈጸማቸው የተገለጸ ሲሆን ከዩኒቨርስቲው የጸጥታ አባላት ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል።  አንድ የታሊባን ወታደራዊ ኮማንደር ጥቃቱ የተወሰደው በታሊባን መሆኑን ጠቅሶ እርምጃውም በቅርቡ የፓኪስታን ወትደራዊ ኃይል ለወሰደው ጥቃት የአጸፋ እርምጃ ነው ብሏል። በሌላ በኩል የታሊባን ቃል አቀባይ የሆነው ለቢቢሲ የዜና ወኪል በሰጠው ቃል ድርጊቱን ታሊባን እንዳልፈጸመው ገልጾ ርምጃው ከሙስሊም ሃይማኖት ትእዛዝ ውጭ የተደረገ የሚወገዝ ድርጊት ነው ብሏል። ስለሆነም ድርጊቱን ማን እንደፈጸመው እስካሁን በትክክል የተገኘ መረጃ የለም። ከዚህ በፊት ከተማዋ በታሊባን ተደጋጋሚ ጥቃት የተፈጸመባት መሆኗና በርካታ ዜጎችም እንደሞቱ ይታወቃል።

 

 

Ø የሱዳኑ ፕሬዚዳንት አልበሽር ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም ባደረጉት ንግግር በግብጽ ቁጥጥር ስር ያለውና ሃላየብ ትሪያንግል በሚል ስም የሚጠራው ቦታ የሱዳን ስለሆነ መንግስታቸው ቦታው ለሱዳን እንዲመለስ ከመታገል ወደኋላ የማይል  መሆኑን ገልጸዋል። በሱዳንና በግብጽ መካከል ያለው የወንድማማችነት ግንኙነት የጠነከረ ቢሆንም ከ1982 ጀምሮ በግብጽ አስተዳድር ስር ያለው የሃላየብ ትሪያንግል በታሪክ የሱዳን መሬት በመሆኑ አገሪቱ ቦታው እንዲመልስላት ትፈልጋለች ብለዋል። ቀደም ብሎ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉዳዩን በየዓመቱ በተመድ ስብሰባ ላይ የሚያነሱት መሆኑን ጠቅሰው በሰላማዊ መልክ እንዲያልቅ ማናቸውንም እርዳታ ለማድረግ ጥረት የሚያደርጉ መሆኑን ገልጸዋል።    

በሌላ በኩል የሱዳን የጸጥታና የኢንተለጀንስ ኃላፊ ሚስተር ሙሀመድ አባስ የአየሲስ (ዳሽ) አሸባሪዎች ወደ ሱዳን ገብተው ጉዳት እንዳይደርሱ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃ እየወሰዱ መሆናችውን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት አስቸኳይ የእርዳታ ሰጭ የሚበለው ጸረ ሽብር ግብረ ኃይል አባላት ምረቃ በተካሄድበት ወቅት መሆኑ ታውቋል። የሱዳን ወጣቶች በብዛት ወደ ሊቢያ እየሄዱ አይሲስ የተባለውን ድርጅት ተቀላቅለው እየተዋጉ ነው የሚል መረጃ አለ። ባለፈው ዓመት በሱዳን የግል ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች ወደ ቱርክና ሶሪያ በመሄድ አይሲስን ተቀላቀለው ሲዋጉ መቆየታቸው በተደጋጋሚ ከተገኘ ዜና ማወቅ ተችሏል። ማረጋገጫ ባያቀርቡም የሱዳን የጸጥታ ኃላፊ በዳርፉር እየተዋጉ ያሉት አማጽያን አባላትም ሊቢያ ሄደው ከአይሲስ ጋር ተቀላቅለው እየተዋጉ ነው የሚል መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት በዳርፉር የመንግስት ወታደሮች ከጥቂት ቀናት በፊት ያካሄዱትን ዘመቻ ለመደገፍ ነው ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ታዛቢዎች ወስደዋል።

በተያያዘ ዜና ባለፉት ጥቂት ቀናት በዳርፉር በመንግስት ኃይሎችና በአማጽያኑ መካከል ጦርነት ተጠናክሮ እየተካሄደ ሲሆን በአካባቢው ያሉ  ሰላማዊ ሰዎች በከፍተኛ ችግር ውስጥ ሊወድቁ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣኖች ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በይፋ አስታውቀዋል። በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ሰዎች ቤት ንብረታችውን ለቅቀው ሊሰደዱ እንደሚችሉ ባለስልጣኖቹ ገልጸው በተለይ ሴቶች እና ህጻናት ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ሊወድቁ ይችላሉ ብለዋል። በዳርፉ የሚገኘው የተመድ እና የአፍሪካ ኅበረት የሰላም አስከባሪ ኃይል በዚሁ ቀን ባሰራጨው ዘገባ በማእከላዊ ዳርፉር አሁንም ጦርነቶች እየተካሄዱ መሆናቸውንና  ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ስዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ቤቶች መቃጠላቸውን የሚገልጹ ዘባዎች የደረሰው መሆኑን ገልጿል።

 

 

ጥር 10 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሐዲያ ወደ ሆሳዕና እና ወደ ተለያዩ ከተሞች የሚደረጉ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ዝግ ሆነው መዋላቸውን ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። የትራንስፖርት አገልግሎት ያልነበረው በቅርቡ የተለለፈውን  መመሪያ የተቃወሙ  የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችና ታክሲዎች ባደረጉት አድማ ምክንያት ሲሆን መመሪያው እስካልተነሳ ድረስ አድማው የሚቀጥል መሆኑ ከአካባቢው የሚገኘው ዜና ይገልጻል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቀደም ብለው ከወቻሞ ዩኒቨርስቲ ተይዘው የተወሰዱት አራት ተማሪዎች የት እንደታሰሩ ባለመታወቁ ቤተሰቦቻቸው ከፍተኛ ሀሳብና ጭንቀት  ላይ መውደቃቸውን ለማወቅ ተችሏል። በዲላም በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተማሪዎችና የአግአዚ ጦር አባላት ቁጥር እኩል ለእኩል መሆኑ የታወቀ ሲሆን ተማሪዎቹ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው መሆኑና የእጅ ስልኮቻቸውንም የተቀሙ መሆናቸው ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።

Ø ትናንት ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሀረርጌ መኤሶ  ከተማ የአግአዚ ወታደሮች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ሲተኩሱ የዋሉ ሲሆን ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ሰዎችን አስረው በከባድ ካሚዎን ወደ  ጂጂጋ የወሰዷቸው መሆኑን  ከአይን እማኞች የተገኘው መረጃ ይገልጻል።  ታስረው ወደ ጂጅጋ የተወሰዱት   ሰላማዊ ሰዎች ያለፈቃድ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥታችኋል በማለት እንደሚወነጀሉ የተነገራቸው መሆኑንም ለማወቅ የተቻለ ሲሆን  ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘው ወደ ጂግጂጋ የተዛወሩ እስረኞች ቁጥር አንድ መቶ ሃያ እንደሚሆኑ የአይን እማኞች አስረድተዋል  ። የአዲስ አበባ ማስተር በመቃወም በየቦታው ተነስቶ በነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ በአሁኑ ወቅት “የወገኖችን ህይወት በግፍ ያጠፉ ገዳዮቹ ለፍርድ ይቅረቡ”፤ “ታስረው የሚሰቃዩት ባስቸኳይ ይለቀቁ” ወደሚሉ ሕዝባዊ ጥያቄዎች እየተሸጋገሩ መምጣታቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን ዘገባዎች የሚጠቁሙ ሲሆን ሰሞኑን በአሰቦት ምዕራብ ሐረርጌ ፤ በሊሞ ምዕራብ ሸዋ እንዲሁም በጊዳ ምስራቅ ወለጋ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።  

 

Ø ከሀሮማያ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመልጣችኋል ወይም ደብቃችኋል በሚል በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰው የግፍ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ከአካባቢው የሚደርሰው ዜና ይገልጻል። በትናንትናው ዕለት በርከት ያሉ ሰዎች ከየቤታቸው የተወሰዱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ለጊዜው ስሙ እንዳይገለጽ የተጠየቀ በንግድ ስራ ይተዳደር የነበረው እድሜው ከአርባ እስከ አርባ አምስት ድረስ የሚገመተው ጎልማሳ በአግአዚ ወታደሮች እየተደበደበ ከመኖሪያ ቤቱ ታፍኖ ሲወሰድ በርካታ ዜጎችን አስቆጥቶ ተቃውሞ ያስነሳ ከአካባቢው የመጣ ዜና ይገልጻል።  በተያያዘ ዜና ከአዳማው የደህንነት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት የሶስት ቀን ስብሰባ በኋላ በድንገት ተይዘው የታሰሩት የደህንነት አባሎች ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓ/ም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለምዶ እንግሊዝ ኤምባሲ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ የደህንነት ቢሮ ውስጥ የተወሰዱ መሆናቸውና ከፍተኛ ምርመራ እንደተደረገባቸው መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።  ሕዝብን ለማሳመጽ  ቅስቀሳ አድረገናል በዚህም  ይህ የክህደት ወንጀል ፈጽመናል ብላችሁ እመኑ በማለት ተጽእኖ እየተደረገባቸው መሆኑን ጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አረጋግጠዋል።

 

Ø የናይጄሪያ የማስታወቂያ ሚኒስትር ትናንት ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሰባት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ የናይጄሪያ አገረ ገዠዎች፤ ሚንስትሮች የንግድ ተቋም ባለቤቶች ፤ የባንክ እና የመንግስት ባለሥልጣኖች 9 ቢሊዮን ዶላር የአገሪቷን ገንዘብ አለአግባብ የዘረፉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የተሰረቀው ገንዘብ 1.35 ትሪሊዮን የናይጄሪያ ናይራ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸው ይህም 36 ሆስፒታሎች ለመስራት ወይም 4000 ተማሪዎችን እስከዩነቨርስቲ ድረስ ለማስተማር የሚያስችል ገንዘብ እንደነበር ገልጸዋል። ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸው ባሁኑ ወቅት አስፈላጊው ርምጃ መወሰድ አለበት ብለዋል። ሚኒስትሩ የተዘረፈውን ገንዘብ ዝርዝር መረጃም አቅርበዋል።  ገንዘቡ ተዘርፏል የተባለው እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2013 በአብዛኛው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሲሆን የቀድሞ የጸጥታ አማካሪ የነበሩት ሚስተር ዳሱኪ 2 ቢሊዮን ዶላር ዘርፈዋል ተብለው መወንጀላቸው ይታወሳል። በአሁኑ ወቅት የናይጄሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው ፒፕልስ ዴሞክራቲ ፓርቲ የአሁኑ እርምጃ  የፓርቲውን አባላት ለማጥቃት ሆን ተብሎ በስልጣን ላይ ባለው  ኦል ፕሮግሬሲቭ ኮንግሬስ በተባለው ፓርቲ  የተጠነሰሰ ሴራ የሚል ውንጀላ ሲያቀርብ ባለስልጣኖቹ ደግሞ የአገሪቱን ገንዘብ የሰረቀ የማንኛውም ፓርቲ አባል ለፍርድ ይቀርባል ብለዋል።

 

Ø የናይጀር መንግስት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጋራ በመሆን በናይጄሪያና በናይጀር ወሰን አካባቢ የሚገኙትን እና ለቦኮ ሃራም ጥቃት የተጋለጡትን 99 ትምህርት ቤቶች የጸጥታ ሁኔታቸው ወደተሻለ አካባቢዎች ለማዛወር ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተመድ ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓም ገልጿል። በናይጄሪያ እና በናይጀር ወሰን በሆኑ አካባቢዎች 12600 የሚሆኑ ተማሪዎችን ያስተናግዱ የነበሩ 166 ትምህርት ቤቶች የተዘጉ ሲሆን ባለፉት ሁለት ወራት የጸጥታ ሁኔታቸው ደህና ነው በሚባልላቸው አካባቢዎች የመማሪያ ክፍሎችን በመስራት 6000 ተማሪዎች እንዲዛወሩ የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø ከትቂት ጊዜ በፊት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በሊቢያ የአንድነት መንግስት ለመመስረት  ስምምነት ላይ የተደረሰ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም 32 አባሎች የሚገኙበት የዚህ የአንድነት መንግስት ባለስልጣኖች ስም ይፋ ተደርጓል።  ስምምነት ተደርሶበታል ለተባለው የአንድነት  መንግስት ከሁለቱም ተጻራራሪ መንግስታት ምክር ቤት አባሎች ድጋፋቸውን የሰጡ ከግምሽ በታች መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን  ዛሬ ይፋ የተደረገውን የ32   ሚኒስትሮችና የከፍተኛ ባለስልጣኖች የስም ዝርዝር ምን ያህሉ የተጻራሪ ቡድኖች  ምክር ቤቶች አባላት እንደሚደግፏቸው ግልጽ አይደለም።  የምዕራብና የሌሎች አገሮች መንግስታት እንዲሆም  ዋና ዋና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ተጻራሪ ወገኖች ስምምነት የተደረሰበትን የሊቢያን የአንድነት መንግስት እንዲቀበሉ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ የቆዩ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን የተጠቀሱትን ባለስልጣኖች  እንዲቀበሉ ግፊት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከአራት ዓመት በፊት የሊቢያ መሪ ሙአመር ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ ሊቢያ ቀውስ የገባች ሲሆን በምስራቅና በምዕራብ ሊቢያ ሁለት ተጻራሪ መንግስታት መቋቋማቸውና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችም  የአይሲስ እና የአልቃይዳ አሸባሪዎች እንቅስቃሴ እየተጠናከረ መምጣቱ ይታወቃል።

 

 

ጥር 9 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃውም የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ በተለያዩ ከተሞች  የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። በትናንትናው ዕለት በአምቦ ዪኒቨርስቲ የወንዶች ተማሪዎች መኝታ ክፍል የተቃጠለ ሲሆን የቃጠሎው መነሻና ማን እንዳቃጠለው ለጊዜው አልታወቀም። በሀረር በሃሮማያ ከተማ ከአግአዚ ጦር ተኩስ ያመለጡትን ወጣቶች ሸሽጋችኋል በማለት የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰዎችን ከቤት እያስወጡ ከፍተኛ ድብደባ ያካሄዱባቸው መሆኑ ታውቋል። በመኢሶም  ከፍተኛ የሕዝብ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን የአግአዚው ጦር በወሰደው ርምጃ ሰላማዊ ስዎች መገደላቸውና መቁሰላቸው ተዘግቧል።  

 

Ø በአዳማ/ናዝሬት ከተማ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የወያኔ የደህንነት አባላትና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ስብሰባ የተጠናቀቀ ሲሆን በስብሰባው መጨረሻ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ሁለት የደህንነት አባላት መታሰራቸውን ከስብሰባው አካባቢ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ግለሰቦቹ የታሰሩት በስብሰባው ወቅት አመጽ በተካሄደባቸው አካባቢዎች በአግአዚ ጦር የተወሰደው እርምጃ አግባብ አይደለም በማለት አስተያየት በመስጠታቸውና በጥብቅ በመከራከራቸው ነው ተብሏል።

 

 

Ø ወይኔ እና ሱዳን ቀደም ብሎ አቋቁመውት  የጋራ የወሰን አካላይ ቴክኒካል ኮሚቴ በዚህ ዓመት ስራውን አጋባድዶ ወሰኑን ሊያካልል እንደሚችል የሱዳኑ የቴክኒካል ኮሚቴ ኃላፊ ሚስተር አብደላ አል ሳዲክ  የሱዳን ሚዲያ ሴንተር ለተባለ የሚዲያ ተቋም መግለጻቸው ታወቀ። የሱዳኑ ባለስልጣን የሚካለለው ወሰን ርዝመት 725 ኪሎሜትር መሆንኑና ከዚሁ ውስጥ በሁለቱም አገሮች አርሶ አደሮች ያለመግባባት የፈጠረው በደቡብ ምስራቅ የገዳሪፍ አውራጃ  የሚገኘው አል ፋሻጋ የተባለው 125 ኪሎሜትር ርዝመትና  ስድስት መቶ ሺ ኤከር ስፋት ያለው ለም የሆነ የእርሻ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ቅዳሜ ጥር 7 ቀን 2008 ዓም የሱዳኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለአልጄዚራ የቴሌሊቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ የአልፋሻጋ አካባቢ የሱዳን መሬት መሆኑን ወያኔ አምኖልናል ካሉ በኋላ እስካሁን የኢትዮጵያ አርሶ አደሮችን መሬቱን እንዲያርሱ የፈቀድነው ለትብብር ካለን ፍላጎት ብቻ ነው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። የሱዳን ባለስልጣኖች በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የሰጡት መረጃ የወያኔን ቅጥፈትና ውሸት አጋልጧል ተብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ነኝ ባዩን ጨምሮ የወያኔ ባለስልጣኖች በተለያዩ ወቅቶች ከሱዳን ጋር የተደረገ ስምምነት የለም በማለት ሲዋሹ  መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን ከዚህ ተጻራሪ በሆነ መንገድ የሱዳን ባለስልጣኖች የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ወያኔ የተስማማ መሆኑና የወሰን ማካለሉም ስራ በዚህ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቀ ተናገረዋል።  

 

Ø የታንዛኒያ ፖሊሶች 83 ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን ሕገ ወጥ ናቸው በሚል ያሰሩ መሆኑን ሲትዝን የተባለው የታንዛኒያ ጋዜጣ ዘግቧል። የፖሊሱ መረጃ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በአንድ ጭነት መኪና ተጭነው ወደ ማላዊ ያመሩ እንደነበር ጠቁሞ የመኪናው ሹፌርና ወጣቶቹ ያረፉበት   ቤት ባለቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል። ኢትዮጵያውያኑ በተያዙበት ወቅት በረሃብና በመንገድ ብዛት ደክመውና ተጎሳቁለው እንደነበር ተነግሯል። ከዚህ በፊት ታንዛኒያ ውስጥ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተደጋጋሚ ተይዘው ለፍርድ የቀረቡ መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø የአለም የኢኮኖሚክ መድረክ የሚባለው አመታዊ ስብስባ ዳቮስ በተባለችው የስዊዘርላንድ ከተማ ነገ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ኦክስፋም የተባለው የእርዳታ ድርጅት ባሰራጨው ዘገባ በሃብታቸው የመጠን ከፍተኛውን ደረጃ የያዙት አንድ ከመቶ የሚሆኑ ሃብታሞች ከተቀረው የዓለም ሕዝብ የበለጠ ሀብት እንዳላቸው ገልጿል። ዘገባው  በዓለም በሃብታቸው መጠን ከፍተኛ የሆኑት 62 ግለሰቦች የያዙት ሀብት የዓለምን ግማሽ ሕዝብ ሃብት ድምር መሆኑን የሚገልጽ መረጃ አካትቷል። የአንድ ከመቶ ኢኮኖሚ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይኸው የኦክስፋም ዘገባ በየአገሮቹ ካለው ሀብት ውስጥ የሰራተኞች ገቢ ድርሻ በየጊዜው እየቀነሰ መምጣቱን ገልጾ ከዚሁ ውስጥ የሴቶች ድርሻ ደግሞ በአሳሳቢ ደረጃ ዝቅ ያለ መሆኑን አጋልጧል።  ማክሰኛ ጥር 10 ቀን በሚጀመረው የአለም የኢኮኖሚክ መድረክ ላይ 40 የሚሆኑ የአገር መሪዎች የሚገኙበት ሲሆን 2500 የሚሆኑ ተለያዩ የንግድና የብዙሃን ድርጅቶች መሪዎች ይሳተፉብታል ተብሎ ይጠበቃል።

 

 

Ø በሱዳን ዳርፉር የተሰማራው የተመድ እና የአፍሪካ ህብረት ጥምር የሰላም አስከባሪ ኃይል ቃል አቀባይ ትናንት እሁድ ጥር 8 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ባለፉት ጥቂት ቀናት በመንግስት ኃይሎችና በአማጽያን መካከል ጀበል ማራ በተባለው ቦታ እየተካሄደ ያለው ጦርነት ያሳሰበው መሆኑን ገልጿል። ጦሩ በሰፈረባት ነርቲቲ በተባለቸው ከተማ ውስጥ አምስት ቦምቦች የፈነዱ መሆናቸውና የቦምቡ ፍንዳታ በካምፑ ውስጥ በደንብ ሊታወቅ የቻለ መሆኑን አብራርቷል። የተመዱ ቃል አቀባይ ስለጦርነቱ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም ካለፈው አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ የመንግስት ወታደሮች ዳርፉር ውስጥ በሚገኙ በተለያዩ የአማጽያን ይዞታዎች ላይ ጥቃት የፈጸሙ መሆናቸውን የሱዳን የዜና አውታሮች  ገልጸዋል። የመንግስት ወታደሮች 10 የሚሆኑ ወታደራዊ አውሮፕላኖችን በመጠቀምና በርካታ ወታደሮችን በማሰለፍ በመፈጸሙት ጥቃት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መንደሮች ተቃጥለው ወደ አመድ መቀየራችውና በሺ የሚቆጠሩ ዜጎች አካባቢያቸውን በመጣል መስደዳቸውን የዜና ምንጮቹ ዘግበዋል። ጦርነቱ እየተካሄደ በመሆኑ ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱም ለማወቅ አልተቻለም ብለዋል። ከዚህ በፊት የሱዳኑ ፕሬዚዳንት አል በሽር በመንግስት ወታደሮችና በአማጽያኑ መካከል የተደረገው የተኩስ ማቆም ስምምነት የሚቀጥል መሆኑን በተደጋጋሚ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የመንግስቱ ወታደሮች ጥቃት ለመውሰድ ያስገደዳቸው አማፅያኑ በቅድሚያ ጦርነት በመክፈታቸው ነው ተብሏል።  

 

Ø ዛሬ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሰሜናው ካሜሩን ግዛት በአንድ መስጊድ ውስጥ በአንድ አጥፍቶ ጠፊ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች መሞታቸውንና ሁለት ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን የካሜሩን የጸጥታ ኃላፊዎች ለዜና ምንጮች  ገልጸዋል። ቦምቡ የፈነዳው እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ በመስጊድ ውስጥ የነበረው የጸሎት ስነስርዓት እያለቀ በነበረበት ጊዜ ነው። ከዚህ በፊት አካባቢው በቦካሃራም ታጣቂዎች ጥቃት ሲደርስበት የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከአምስት ቀን በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በፈነዳ ቦምብ 12 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።

 

 

 

 

ጥር 7 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት በሚቀጥሉት ወራት ከፍተኛ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የእህል እጥረት ሊያጋጥም እንደሚችል ገልጾ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም የ50 ሚሊዮን ዶላር አሰቸኳይ ርዳታ እንደሚያስፈልግ ገልጿል።  በሚቀጥሉት ሁለት ወራት በከፍተኛ ደረጃ እየተባባሰ ይሄዳል የተባለው ድርቅ በአሁኑ ወቅት በርካታ ወገኖቻችንን ያስራበ መሆኑኑና የቤት እንሣዎችንና የቀንድ ከብቶችን በብዛት እየጨረሰ መሆኑ ተነግሯል። የተመድ የምግብና የርሻ ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑ ሚስተር አማዶ አላሁሪ በሰጡት መግለጫ በመጭው የፈረንጆቹ ዓመት የድርቁ ሁኔታ በጣም እየተባባሰ ሊሄድ የሚችል መሆኑን ጠቅሰው የእህል ዋጋ በጣም ሊጨምር እንደሚችልና ሳር እና መኖም ስለማይኖር  የቤት እንስሳሳትና የቀንድ ከብቶች  በከፍተኛ ደርጃ ጉዳት ሊደርስባቸው እንደሚችል ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በርካታ ሕዝብ እየተራበ ሲሆን በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ሕጻናትም ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ድርጅቱ በቅርቡ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ገንዘብ መስጠት እንደሚጀመርና 100 000 ሺ በጎችንና ፍየሎችን  ማደል ለመጀመር እቅድ እንዳለው ገልጸዋል። በርክታ አካባቢዎች በድርቅ የተጎዱ ሲሆን አንዳንድ ቦታዎች የምርቱ ውጤት  ከ 50  እስከ 90 እጅ የቀነሰ መሆኑ ይታወቃል። ዜጎች አካባቢያቸውን ጥለው ወደ ተለያዩ ቦታዎች መሰዳድቸውም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ተዘግቧል።

 

Ø ትናንት ዓርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ በአንዋር መስጊድና በቤኒን መስጊድ የጁምዓ ጸሎት ሊያደርሱ በስፍራው በተገኙ አማኞች ላይ ጥብቅ ፍተሻ ሲደረግ እንደነበር ከስፍራው ከመጣ ዜና ለማወቅ ተችሏል። ከሳምንታት በፊት በታላቁ አንዋር መስጊድ ወያኔ ተላላኪዎቹን በማሰማራት የቦንብ ፍንዳታ እንዲካሄድ ካደረገ ጀምሮ የስግደት ስነርዓታቸውን ለመፈጸም ወደ መስጊድ የሚሂዱ ሙስሊሞችን በፍተሻ አሳቦ ማዋከብ ማንገላታትና ማሰቃየትን ስራዬ ብሎ ተያይዞት የነበረ መሆኑ ይታወቃል ። በትናንትናው ቀን  ለሳምንታዊው የጁምዓ የስግደት ጸሎት በታላቁ አንዋር መስጊድና በቤኒን መስጊድ የተገኙትን አማኞች ብዛት ያላቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት በፍተሻ ስም በከፍተኛ ደረጃ  ሲያንገላቱዋቸውና የስግደት ሰዓት እንዲያልፍባቸው ሲያደርጉ እንደነበር በሁለቱም መስጊዶች ተገኝተው የነበሩ ዘጋቢዎቻችን ከላኩት ዘገባ ለመረዳት ተችሏል።

 

 

Ø በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞቸ የህብረተሰቡን የስኳር ፍጆታ ለማሟላት  ከነበሩት ተቋሞች በተጨማሪ ሰባት አዳዲስ  የስኳር ፋብሪካዎች ከፍተናል በማለት ሲደሰኩር የነበረው የወያኔ አገዛዝ ከውጭ አገር ስኳር ሲያስገባ መቆየቱ ይታወቃል።  ተቋቋሙ የተባሉት አዳዲስ ፋብሪካዎች የተገጠመላቸው መሳሪያዎች ከጥቅም ውጭ በመሆናቸውና ቀደም ብለው የነበሩትም በእድሳት ምክንያት ስራ በማቆማቸው ስኳር ከውጭ ለመግዛት ተገዶ የነበረ መሆኑን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ይናገራሉ። በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ባለው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ስኳሩን ከውጭ ለማስመጣት ችግር በመፈጥሩ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ  ለነጋዴዎች በኪሎ አስራ አምስት ብር ሲሸጥ የነበረው የስኳር ዋጋ አስራ ስምንት ብር ለመሸጥ የታቀደ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።  በጥቁር ገበያ የሚሸጠው ስኳር በኪሎ 22 የሚደርስ መሆኑ ሲገመት ከአዲስ አበባ ራቅ ባሉ እንደጋምቤላ አካባቢዎች የአንድ ኪሎ ስኳር ዋጋ ከእጥፍ በላይ ጨምሮ እስከ አርባ ሁለት  ብር  ሊደርስ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø ነገ እሁድ ጥር 8 ቀን 2008 ዓ/ም ከማለዳው 2 ሰዓት ተኩል አንስቶ በቻግኒ ከተማ ነዋሪዎች ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ከስፍራው የደረሰን ዜና ይገልጻል። ስብሰባውን የጠሩት የወያኔ ተላላኪዎች በመባል የሚታወቁት የብአዴን ባለስልጣኖች ሲሆኑ ስብሰባው ይመራዋል የተባለው የብአዴን መገኛኚያ ብዙሐን ነው ተብሏል። የከተማ ነዋሪ ሕዝብ ከፍተኛ በደል እየደረሰበት ያለ መሆኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች የገለጸ ሲሆን በወቅታዊ ጉዳዮችና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ውይይት ይካሄዳል በተባለለት ስብስባም በከፍተኛ ደረጃ ብሶቱን ይገልጻል ተብሎ ይገመታል። ሕዝቡ ተቆጥቶ እርምጃ ሳይወስድብን እናለሳልሰው በሚል ስሜት ሰሞኑን አንዳንድ እርምጃዎች በመውሰደ ላይ ያሉት የብዓእዴን ባለስልጣኖች ዝቅተኛ የአካባቢ ኃላፊዎችን ከቦታቸው ያነሷቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። ብአዴንም ሆነ ወያኔ እያካሄድን ነው የሚሉት  የጥገና ለውጥ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ የማይመልስ በመሆኑ በሕዝብ ቁጣ ከስልጣናቸው ተራርገው ከመወገድ እንደማይድኑ  ብዙዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

 

Ø ትናንት ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ማታ በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ አንድ በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆቴል እና በአካባቢው ባለው ቡና ቤት ውስጥ  የታጠቁ ኃይሎ ጥቃት ሰንስዘረው በርካታ ሰዎች አግተው እንደነበር ተዘግቧል። ሰዎችን ለማስፈታት በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የ18 የተለያዩ አገሮች ዜጎች የሆኑ 23 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ከሞቱቱ ውስጥ አራቱ ታጣቂዎቹ መሆናቸው ታውቋል።  በእስላማዊ ማግረብ የአልቃይዳ ክንፍ እየተባለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። በቅርቡ የተመረጡት የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ቅዳሜ ጠዋት በቦታው ተገኝተው በሰጡት መግለጫ 150 የሚሆኑ ታጋቾችን ከታጣቂዎች ነጻ ለማድረግ የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የቡርኪና የጸጥታ ኃይሎችን በመርዳት በአካባቢው የሚገኙ የፈረንሳይ ወታደሮች የተሳተፉ ሲሆን የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት አሸባሪዎቹ የወሰዱትን እርምጃ ኮንነዋል። ከሁለት ወር በፊት በማሊ ዋና ከተማ በማኮ ተመሳሳይ ጥቃት ተፈጽሞ 19 ቱሪስቶች መገደላችው ይታወሳል። በሌላ ዜና ዛሬ ሌሊቱን በበቡርኪና ፋሶ እና በማሊ ወሰን አካባቢ በሚገኝ ቦታ ላይ የኦስትሪያ ዜጎች የሆኑ አንድ ዶክተርና ባለቤቱ ተጠልፈው የተወሰዱ መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል። አጋቾቹ እነማን እንደሆኑና ወዴት እንደወሰዷቸው የተገኘ መረጃ የለም።

 

Ø በታይዋን ፕሬዚዳንቱን ለመምረጥ በተደረገ ብሔራዊ ምርጫ ዴሞክራቲክ ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ የተባለው ድርጅት መሪ የሆኑት ሚስስ ሳዪ ከፍተኛ ድምጽ አግኝተው በመመረጣቸው ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሴት ፕሬዚዳንት ሆነዋል። ዴሞክራቲክ ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ የተባለው ድርጅት አንድ ቻይና የሚለውን የሚቀበልና ነጻነትን የሚደግፍ በመሆኑ በቻይናና በታይዋን መካከል የሚኖረው ግንኙነት ውጥረት የሞላበት ሊሆን እንደሚችል ብዙዎች ይገምታሉ። የቻይና ባለስልጣኖች ታይዋን የቻይና ግዛት ናት በማለት የሚከራከሩ ሲሆን  ታይዋንን ወደ ቻይና ክልል ለማስገባት ኃይልም ጭምር ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።

 

Ø ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በብሩንዲ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድረገዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የሚገኙ ከፍተኛና ዝቀተኛ መኮንኖች በ30 ዓመት እስራት እንዲቀጡ አንድ የብሩንዲ ፍርድ ቤት ትናንት አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ፍርድ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። የመፈንቅለ መንግስት ሙከራው መሪ ሳይያዙ ያመለጡ መሆናቸው የሚታወስ  ሲሆን ቅጣቱ የተበየነው የእሳቸው ምክትል በሆኑ በሶስት የጦር ጄኔራሎችና በአንድ የፖሊስ ጄኔራል ላይ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ዘጠኝ የበታች ሹማንቶች በተመሳሳይ መልክ የ30 ዓመት እስራት ተበይኖባቸዋል። በተከሳሾቹ ላይ የቀረቡት ክሶች  የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርጋችኋል፤ ወታደሮችን ፖሊሶችንና የሲቪል ሰዎችን ገድላችኋል ንብረቶችን አውድማችኋል  የሚሉ ሲሆን በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ተብለዋል። ተከሳሾቹ ከእስራቱ በተጨማሪ ለ 10 አመት ያህል የመንግስት ስራ ላይ በኃላፊነት እንዳይቀመጡ የታገዱ ሲሆን ሌሎች ዘጠኝ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የበታች ሹሞች በአምስት የእስራት ዘመን እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።   

 

 

 

ጥር 6 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ከትናንት ከጥር 5 ቀን 2008 ዓም ማምሻ ጀምሮ በአምቦ ከተማ ሰላማዊ ዜጎች በታጠቁ ኃይሎች እየታፈሱ ወደ እስር ሲጋዙ እንደነበር የተመለከቱ  የአይን እማኞቸ ዛሬ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም  ረፋድ ላይ የአግአዚ ወታደር በሰላማዊ ሰዎች ላይ ሲተኩስ የነበረ መሆኑን ገልጸዋል።  የተኩሱ መንስዔ በፖሊስ ጥይት ጭንቅላቱን ተመቶ በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምና ሲደረግለት የቆየውና መዳን ባለመቻሉ ህይወቱ ያለፈውን አብደታ ኦላንሳ የተባለውን ወጣት አስከሬን ለመቅበር በተሰባሰቡ ሰዎች ሳቢያ የተሰባሰቡ ሰዎችን ለመበተን የተደረገ መሆኑን የአይን እማኞቹ ጨምረው ገልጸዋል።   በከተማ ነዋሪዎች መከካል በተለይ በጨለማ የሚደረገውን ግንኙነት ለማቋረጥ  በዛሬው ቀን በአምቦ ከተማ መብራት ሙሉ በሙሉ የጠፋ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በነበረውም ተኩስ ሁለት ሰዎች ሳይቆስሉ እንዳልቀሩ ተገልጿል። በትናንትናው ዕለት በባሌ፤ በሐረር በሻሽመኔና እንቅስቃሴዎች የነበሩ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ተዘግተው ውለዋል።

 

 

 

Ø በአዲስ አበባ ከተማ የመብራት መጥፋት በተደጋጋሚ ሲከሰት መቆየቱ የታወቀ ቢሆንም ከቅርብ ቀናት ወዲህ ግን በእጅጉ የተባባሰ መሆኑንና ከወትሮው በተለየ ሁናቴ በአንድ ሰፈር ውስጥ ከቤት ቤት እየነጠሉ ማጥፋት የተጀመረ መሆኑ ታውቋል።  ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስልክና የውሃ አገልግሎቶች  አብረው የሚጠፉበት ሁኔታ  እየተለመደ በመምጣቱ በተለይ በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ስራቸውን ለማካሄድ በእጅጉ መቸገራቸውን ለማወቅ ተችሏል።  አካባቢዎችን በዞን በመክፈል ወይም ከመንገድ በታች እና ከመንገድ በላይ በማለት የፈረቃ ፕሮግራም ወጥቶ በቅድሚያ ቢነገረን ቁርጡን ማወቅ እንችል ነበር የሚሉት ነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት  ከግዜ ወደ ግዜ መሻሻል ሳያሳይ መቆየቱ አንሶ የአሁኑ የተለየና የባሰበት በመሆኑ ተስፋ አስቆራጭ የሆነበት ደረጃ ላይ አድርሶናል ሲሉ ተሰምተዋል።

 

Ø በደቡብ ሶማሊያ ኤል አዲ በምትባለው ከተማ ውስጥ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ጦር ሰፈር ላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰው የጦር ሰፈሩን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት መሆናችውን የቡድኑ ቃል አቀባይ ገልጿልዋል። ቃል አቀባይ  በተጨማሪ በሰጠው መግለጫ በጦር ሰፍሩ የነበሩት ከ60 በላይ የሚሆኑ የኬኒያ ወታደሮችም የተገደሉ መሆናችውን አስረድቷል። የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢብሲ የዜና ወኪል በሰጡት መረጃ የአልሸባብ ወታደሮች በከተማዋ ውስጥ ሰንደቅ ዓላማቸውን ያውለበለቡ መሆናቸውንና የሞቱ ወታደሮችን አስከሬን እያዞሩ ሲያሳዩ እንደንበር ገልጸዋል። የኬኒያ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ዜናውን አስተባብሎ ጥቃቱ የተፈጸመው በኬኒያ ወታደሮች ላይ ሳይሆን በአካባቢው በነበሩ በሶማሊያ መንግስት ወታደሮች መሆኑንና ከሁለቱም በኩል ምን ያህል ሰው እንደሞተ ያልታወቀ እንደሆነ ገልጿል። በከተማው ነዋሪ የሆኑ የአይን እማኞች እንደገለጹት ከንጋቱ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ላይ በካምፕ አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የፈንጅ የመሳሪያ ድምጽ መስማታቸውንና  በርካታ ወታደራዊ መኪናዎች ሲቃጠሉ ማየታቸውን ገልጸዋል።

 

Ø የአለም የጤና ድርጅት ሐሙስ ጥር 5 ቀን 2008 ዓ.ም  ላይቤሪያ ከኢቦላ ነጻ መሆኗን አረጋግጦ የምዕራብ አፍርካ አገሮች ከኢቦላ ነጻ ናቸው በማለት የማረጋገጫ ምስክርነት ቢሰጥም ድርጅቱ መግለጫውን በሰጠ በሰዓታት ጊዜ ውስጥ አንድ የሲየራ ሊዮን ዜግነነት ያለው ግለሰብ በኢቦላ በሽታ መሞቱን የአገሪቱ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ግለሰቡ የሞተው በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ቢሆንም በሟቹ አስከሬን ላይ በተካሄድው ምርመራ የሞተው በኢቦላ በሽታ መሆኑ ተረጋግጧል። ሲየራ ሊዮን ከሁለት ወር በፊት ከኢቦላ ነጻ ናት ተብላ ማረጋገጫ የተሰጣት የሚታወስ ሲሆን የምርመራው ውጤት የኢቦላ በሽታ ከአካባቢው ገና ያልጠፋ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኃላፊ ሚስተር ዘይድ ራአድ አልሁሴን ዛሬ አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ በብሩንዲ በንጹሃን ሰዎች ላይ እየደረሰ የሚገኘው ግፍና በደል በጣም ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በርካታ ሴቶች በወታደሮች መደፈራቸውን፤ በጎሳ ልዩነት ሰዎች መገደላቸውንና ብዙዎች በወታደሮች ተጠልፈው የደረሱበት የማይታወቅ መሆኑን እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች የጅምላ መቃብሮች የተገኙ መሆናችውን የሚጠቁሙ መረጃዎች እንደደረሳችው ገልጸዋል።  በታኅሣሥ  ቀን 2008 ዓም በሶስት ወታደራዊ ካምፖች ላይ በተደረገው ጥቃት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 130 መድረሱ የተገለጸ ሲሆን ይህንን ጥቃት አስመልክቶ ተመድ የሳይትላይት ስዕሎችን በመመልከትና ሁኔታውን የተመለክቱትን የዓይን እማኞች በመጠየቅ ምርመራ የሚያካሂድ መሆኑን ገልጿል። ለዚህ ጥቃት የአጸፋ ምላሽ በሚል  የመንግስት ወታደሮች በዜጎች ላይ እያደረሱ ያሉት አሰቃቂ ድርጊቶች ግን በጣም አሳስቢ  መሆኑን የድርጅቱ ኃላፊ ገልጸዋል። ፖሊሲች እና ወታድሮች በየቤቱ በመግባት ሴቶችን ከቤተሰቦቻቸው በመለየት አስገድደው እንደሚደፍሩና እንዲሁም ወጣት ወንዶች እየመረጡ  የማሰቃየት ምርመራ እንደሚያካሄዱባቸውና ሌሎችን እንደሚገድሉ መረጃ የደረሳቸው መሆኑን አስረድተዋል። በደል እየደረሰባችው ያሉት የቱሲ ጎሳዎች መሆናችውን ገልጸው ሁኔታው ከተባባሰ በሁቲ እና በቱሲው መካከል ከፍተኛ እልቂት ሊያስከትል የሚችል ግጭቶች ሊጀመሩ እንደሚችሉ በመግለጽ ስጋታቸውን ተናግረዋል።

 

 

Ø በትናንትናው ዕለት በኢንዶኔዥያ ዋና ከተማ ጃካርታ ውስጥ በአንድ አካባቢ አሸባሪዎች ያደረሱትን ጥቃት ያቀነባረው ባህሩን ናይም የተባለው ግለሰብ መሆኑና ከዚህ ጋር በተያያዘ ሶስት ሰዎች መያዛቸውን ፖሊሶች ገልጸዋል። ከተያዙት ሰዎች ውስጥ አንደኛው ቦምብ በመስራት የሰለጠነ ሲሆን ሁለተኛው የመሳሪያ እውቀት ያለው ሶስተኛው ደግሞ የሃይማኖት አስተማሪ መሆኑ ታውቋል። ባህሩን ናይም ከአራት ዓመት በፊት ያልተፈቀደ መሳሪያ በመያዝ ለአንድ ዓመት ታስሮ የተለቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከአይሲስ በሚደርሰው ገንዘብ በደብብ ምስራቅ እሲያ የአሲስ ደጋፊ የሚሆኑትን ለማሰባሰብ ጥረት እያደረገ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። በጃቫ ባህረ ሰላጤም ከሐሙሱ ጥቃት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገልጿል። በትናንትናው ዕለት በደረሰው አደጋ ሰባት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ከ20 በላይ መቁሰላችው ሲገለጸ ከሞቱት መካከል አምስቱ አሸባሪዎች ሲሆኑ አንድ የካናዳ ዜግነት ያለው ግለሰብና አንድ የኢንዶኔዚያ ዜጋ በፍንዳታው ሞተዋል።

     

 

ጥር 5 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የወያኔ ባለሟልና አገልጋይ የሆነው ኦህዴድ የአዲስ አበባው ማስተር ፕላን እቅድ የተሰረዘ መሆኑን ቢናገርም  ወደ 200 የሚጠጉ ዜጎች ሳይሞቱ አይቀሩም የሚባልለትና  ከአምስት ሺህ በላይ የሚሆኑት ለእስራት የተዳረጉበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መልኩን ለውጦ እየተካሄደ መሆኑን  ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱት ዘገባዎች   ያስረዳሉ:: በሀሮማያ፤ በምዕራብ ሀረርጌ፤ በድሬዳዋ፤ በጅማ፤ በአርሲ የተለያዩ ቦታዎች፤ በአምቦ እና በሌሎች ቦታዎች በተማሪዎች ፊት አውራሪነት ተጠናክሮ የቀጠለው ሕዝባዊ ተቃውሞ በግፍ የታሰሩት ባስቸኳይ እንዲፈቱ እና በአግአዚ ጥይት ተመትተው የተገደሉት ወገኖች ገዳዮች  ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።  ትናንት ጥር 4 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦ በተማሪዎች በተካሄደ የተቃውሞ ስልፍ ላይ የአግአዚ ወታደሮች በተኮሱት ተኩስ አንዷ ተማሪ ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ ሌላዋ  በጽኑ መቁሰሏን መረጃው ያመለክታል።  በሀሮማያ ህዝባዊ ተቃውሞ ተጠናክሮ የቀጠለና ተማሪዎች ትምህርት አቁመው የቆዩ ሲሆን ሲቪል በለበሱ የደህንነት ኃይሎች ወጣቶች እየታፈኑ  ወደ እስር ቤት ሲጋዙ መዋላቸውን  የአይን እማኞች ያስረዳሉ።  በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ አመጽ አነሳስተው ተሰውረዋል የተባሉ ወጣቶችን ለመከታተል የደህንነት ኃይሎች ገንደ ቆሬ በተባለው ሰፈር ቤት ለቤት አሰሳ ለማድረግ ወደ ስፍራው መንቀሳቀሳቸውን ዛሬ ማለዳ ከስፍራው የመጣ ዘገባ አጋልጧል። በአርሲ ኮፈሌ ከተማ ሁለት ሰዎች በአግአዚ ወታደሮች ድብደባ ክፉኛ ተጎድተው ለህክምና ተወሰዱ ቢባልም ወደየትኛው የህክምና ተቋምና ከእነማን ጋር እንደሄዱ አለመታወቁን የአይን እማኞች የተናገሩ መሆናቸው ታውቋል።   

Ø በተያያዘ ዜና በሕዝባዊ ተቃውሞው ከአግአዚ ቅልብ ወታደሮች በተተኮሰ ጥይት የቆሰሉና ለህክምና አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተኝተው ከነበሩ ቁስለኛ ተማሪዎች መካከል ሁለቱ እግራቸው እንዲቆረጥ በተወሱኑ ሀኪሞች ሀሳብ የቀረበ መሆኑና በሀሳቡ ላይ ሀኪሞቹ መለያየታቸውን  የሆስፒታል ምንጮች ተናግረዋል።  ከአምቦ ዩኒቨርስቲ እንደመጡ የሚነገርላቸው በጥይት የቆሰሉ ሁለት ተማሪዎች በእግራቸው ላይ በደረሰው የከፋ ጉዳት ምክንያት እግራቸው ካልተቆረጠ በህክምና ሊመለስ የሚችል አይደለም የሚል ሀሳብ በአንዳንድ ሀኪሞች ቢገፋም በሌሎች ሀኪሞች በኩል ከፍተኛ ህክምና ለማድረግ አንድ እድል ይሰጥ የሚል ሀሳብ ስለተገፋ ምናልባት እግራቸው ሳይቆረጥ በረዥም ጊዜ ህክምና በከፊል ሊድኑ ይችሉ ይሆናል የሚለው  ግምትና ተስፋ በቤተሰቦቻቸው ላይ የተፈጠረ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø የወያኔው ሌላ ተልላኪና አገልጋይ የሆነው ብአዴን ለሶስት ተከታታይ  ቀናት ባህርዳር ላይ ባደረገው ስብሰባ የእርዳታ እህል እየሸጡ ለራሳቸው ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ እና ሌሎች በደል አድርሰዋል የተባሉ የድርጅቱ አባላት የሆኑ የቀበሌ የወረዳና የዞን ሹማምንት እንዲታሰሩ መወሰኑና ውሳኔውም ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ታወቀ። በሙስናና በመልካም አስተዳደር ችግር ተወንጅለው  እስካሁን ድረስ የታሰሩት በቀበሌ፤ በወረዳና በዞን የተሰማሩ  የብአዴን ሹማምንቶች ቁጥር እስከ መቶ ሰማንያ አምስት የሚደርስ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። የወያኔ አገልጋይ በመሆኑ የአገርና የሕዝብ ሕዝብ ሀብት ሲያዘርፉ የቆዩትና ራሳቸውም በከፍተኛ ዝርፊያ ውስጥ የተሰማሩት የብአዴን ባለስልጣኖች አንድ ቀን በሕዝብ አመጽ ማዕበል ተጠራርገው መቀመቅ መግባታቸው የማቀር መሆኑ ግልጽ ሲሆን በአሁኑ በትናንሾቹ ላይ ይህን እርምጃ የተወሰደው የሕዝብን ቁጣ አቀዝቅዞ ከማዕበሉ ለመዳን ነው የሚል አስተያየት የሚሰነዝሩ በርካታ ናቸው።  

 

 

Ø ሰሞኑን ሲካሄድ የነበረውና  ነገ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም   ይጠናቀቃል የተባለው በአዳማ/ናዝሬት ከተማ የተጀመረው የደህንነት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ስብሰባ በከፍተኛ ጥበቃ ስር እየተካሄደ መሆኑ ታውቋል።  የስብሰባው አጀንዳ ሆኖ ውይይት ከሚካሄዱባቸው ጉዳዮች መካከል በተማሪዎች ግንባር ቀደምትነት የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ በተመለከተ መመከትና መከላከል ስለሚቻልበት እና  እንዲሁም ከበስተጀርባ ያሉትን ኃይሎች አድኖ ለመያዝ መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ላይ ሲሆን  በስብሰባው መጀመሪያ ላይ በተደረገው ውይይት  ለመከላከል የተወሰደው እርምጃ ከመጠን ያለፈ የበዛ በመሆኑ መቆም ይኖርበታል የሚለው አስተያየት በመሰንዘሩና ድጋፍ በማግኘቱ ከመሰብሰቢያው አዳራሽ ውጭ ተራ አባላት በተለየ ጥበቃና ክትትል እንዲቆዩ መደረጉን ከቦታው የተገኘ መረጃ ይገልጻል። ስለ ስብሰባው ዝርዝር ሁኔታ እንደደረሰን እናቀርባለን።  

 

Ø አለበቂ ጥናትና ዝግጅት ወያኔ በአባይ ላይ የሚገነባውን ግድብ አስመልክቶ በወያኔ በሱዳንና በግብጽ መካከል ውይይቶች ሲካሄዱ የነበሩ ሲሆን በቅርቡም ካርቱም ላይ መሰብሰባቸው ይታወቃል። ወደ ግብጽ የሚፈሰው የአባይ ውሃ እንዳይቀንስ ውሃውን ከግድቡ የሚያስወጡ ተጨማሪ ግድቦች እንዲሰሩ ግብጽ የጠየቀችውን  ጥያቄ  የወያኔ አገዛዝ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ታውቋል። የወያኔ ባለስልጣኖች ግድቡ መጀመሪያም ሲሰራ በቂ ውሃ ከግድቡ እንዲወጣ ታስቦ  በመሆኑ ተጨማሪ የውሃ ማስወጫ ቱቦዎች መስራት አያስፈልግም በማለት የግብጽን ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።  የግብጽ ባለስልጣኖች ወያኔ የሚሰራው ግድብ ወደ ግብጽ የሚሄደውን ውሃ በከፍተኛ ደርጃ ይቀንሳል የሚል ጽኑ እምነት ያላቸው መሆኑ የታወቀ ሲሆን ለጥያቄያቸው በወያኔ በተሰጠው የእምቢተኛነት መልስ ምክንያት ምን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ አልታወቀም።

 

Ø የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ መንግስት ስደተኞች ተጠልለው የነበሩበትን ካምፕ በሃይል በማፍረሱና ሴቶችንና ህጻናትን ጨምሮ በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን  ከቦታው ማባረሩን አስመልክቶ በባልስልጣኖቹ የተወሰደው ርምጃ ሰብአዊነት የጎደለውና ተቀባይነት የሌለው የሚወገዝ ድርጊት ነው በማለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ጉዳይ አስተባባሪ ኃላፊ ኮንነውታል። በካምፕ ውስጥ የነበሩት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች በገፍ እንዲባረሩና ወደ ካምፑ እንዳይደርሱ መደረጋቸው  የጅምላ ቅጣት ተብይኖባቸዋል በማለት ወቀሳቸውን አሰምተዋል። የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ባለስልጣኖች የስደተኞችን ማረፊያ ሰፈር ዘግተው ሰዎችን ያባረሩት በካምፑ ውስጥ መሳሪያዎች ተገኝተዋል በሚል ምክንያት  ሲሆን ተመድ ስደተኞቹ ወደ ሌላ ካምፕ እስኪዛወሩ ድረስ ጊዜ እንዲሰጠው ያቀረበውን ጥያቄ ባለስልጣኖቹ ሳይቀበሉት ቀርተዋል።  

 

Ø በዚምባብዌ መንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኘው ሄራልድ የሚባለው ጋዜጣ ዛሬ ጥር 5 ቀን 2008 ዓም  ባወጣው እትሙ ለረጅም ጊዜ በስልጣን ላይ የቆየቱ የአገሪቱ  ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ሲንጋፖር ውስጥ በህክምና ላይ ሳሉ አርፈዋል በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰት ነው በማለት በይፋ ያስተባበለ መሆኑ ታወቀ። በየአመቱ የፈረንጆቹ አዲስ አመት በመጣ ቁጥር የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት አርፈዋል የሚለው ዜና የሰለቸ ውሸት መሆኑን የመንግስቱ ጋዜጣ ጠቅሶ ባሁኑ ወቅት ፕሬዚዳንቱ  በህይወት  መኖራቸውንና  በሩቅ ምስራቅ የእረፍት ጊዜያቸውን እያሳለፉ መሆናቸውን ገልጿል። የ91 ዓመቱ ሮበርት ሙጋቤ ከ1972 ዓም ጀምሮ በስልጣን ላይ የሚገኙ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በወሰዷቸው አቋሞችና እርምጃዎች ምክንያት በርካታ የምዕራብ አገሮች በጠላትነት የሚመለከቷቸው መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም   በኢንዶኔዢያ ዋና ከተማ ጃካርታ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የቦምብ ፍንዳታና የተኩስ ጥቃቶች  ተካሂደው ሰባት ሰዎች መገደላቸውንና ከሃያ በላይ መቁሰላችውን የኢንዶኔዢያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ከተገደሉት መካከል አምስቱ ጥቃቱን ያደረሱ ግለሰቦች መሆናችው ሲታወቅ ለጥቃቱ አይሲስ የተባለው ቡድን ኃላፊነትን ወስዷል ተብሏል። የኢንዶኒኒዢያ ባለስልጣኖች ጨምረው በገለጹት መረጃ መሰረት የዛሬው የሽብር እቅድ የተቀነባበረው የአይሲስ አባል ሆኖ በአገሪቱ ውስጥ የሽብር ተግባሮችን ሲያካሂድ በነበረውና አሁን ሶሪያ ውስጥ በሚገኘው ባህሩን ናይም በተባለው ግለሰብ አማካይነት መሆኑን ገልጸዋል። ጥቃቱ ኢላማ ያደረገው የጸጥታ እና የፖሊስ ኃይል አባላት ላይ ሲሆን በፍንዳታው የፖሊስ መኪናዎች መጎዳታቸው ታይቷል። እስካሁን ከተገኘው መረጃ የተጎጅዎች ቁጥር በትክክል ያልታወቀ ሲሆን ምን አልባትም ከተሰጠው ቁጥር ከፍ ያለ ሊሆን እንደሚችል ብዙዎቹ ይገምታሉ።  በፍንዳታው ምክንያት 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች የሚገኙባት የጃካርታ ከተማ ስትሸበር የዋለች መሆኑ ተነግሯል።፡

 

 

 

 

 

 

ጥር 4 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የሕዝቡ አመጽና እንቅስቃሴ እየተቀጣጠለ መሆኑን በማየትና  እየተጠናከረ ከሄደ ለስልጣኑ አስጊ መሆኑን በመረዳት  ስጋት ላይ የወደቀው የወያኔ አገዛዝ በአገልጋዩ በኦህዴድ አማካነይነት በዜና ማሰራጫዎች  ባሰራጨው መግለጫ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሙሉ በሙሉ የተሰረዘ መሆኑን ገልጿል። የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በአዳማ/ናዝሬት ባካሄደው የሶስት ቀን ስብሰባ ሰፊ ውይይት አካሂዶ የማስተር ፕላኑ እቅድ እንዲስረዝ ውሳኔ አስተላልፏል በማለት የወያኔ መገኛኒያ ብዙሃን ዘግቧል። ቀደም ብሎ  ወያኔ የሕዝቡን አመጽ ለማቀዝቀዝ የሚችል መስሎት ማስተር ፕላኑ ሕዝቡ ሳይስማመበት በስራ ላይ አይወልም የሚል ተማጽኖ በተደጋጋሚ ሲያሰማ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የወያኔ ውሸት የሕዝቡን አመኔታ ባለማግኘቱ አመጹ ተጠናክሮ ሲያካሄድ ቆይቷል። ከ200 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በወያኔ አግአዚ ጦር የተጨፈፉበትም አመጽ  መነሻ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም ይሁን እንጅ ሕዝቡ እየተገደለም እየቆሰለም እየታሰረም  በምሬት አመጹን የቀጠለው የወያኔን አስከፊ አገዛዝ  በመቃወም በመሆኑ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተሰርዟል የሚለው የወያኔ መግለጫ የሕዝቡን ብሶትና አመጽ አይቀንሰውም የሚሉ በርካታ ናቸው። የወያኔ አገዛዝ ሳይወገድ በቀላሉ ሊበርድ የሚችልበት ሁኔታ በአሁኑ ወቅት የማይታይ ሲሆን  እንዲያውም አድማሱ ሰፍቶና ወደሌሎች ስፍራዎች ተዛምቶ ሊቀጥል ይችላል የሚል ግምት አለ።    

 

 

Ø በኢትዮጵያ የገባው ረሃብ ከፍተኛ እልቂትን ሊፈጥር የሚችል መሆኑን የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ያሳሰቡ መሆናቸውን ክርሲያቲያን ሳይንስ ሞኒተር የሚባለው ጋዜጣ በአምዱ ላይ አስፍሮ አውጥቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ  በአለም የምግብ ፕሮግራም መሰረት  በኢትዮጵያ ከገባው ድርቅና ረሃብ ጋር ተያይዞ ርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች በሶስት እጥፍ የጨመረ መሆኑን ገልጸው  እስካሁን ለእርዳታ ይውላል የተባለው ገንዘብ  ከሚያስፈልገው አምስት ከመቶ ብቻ ነው ብለዋል። ክርሲያን ኤድ የተባለው አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት  ኃላፊ በበኩላችው በሰጡት መግለጫ ደግሞ በሁለት ተከታታይ የመከር ወቅቶች በደረሰው የዝናም እጥረግ ምክንያት  በርካታ አርሶ አደሮች ምርት ለማምረት ያልቻሉ መሆናቸውን ገልጸው በተዘዋወሩበት ቦታዎች ከ10 ሺ በላይ የሚሆኑ ከብቶችና የቤት እንሳስዎች መሞታቸውን የተመለከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከ250 እስከ 700 የሚደርሱ ወረዳዎች በድርቁ ተጎድተዋል ካሉ በኋላ ባሁኑ ወቅት እርዳታው ካልደረሰ ከፍተኛ የሆነ  እልቂት ሊከተል ይችላል በማለት ፍራቻቸውን ገልጸዋል።

 

Ø በጎንደር ክፍለ ሀገር በአዲስ ዘመን ከተማ ከ34 አመት በፊት ተሰርቶ የነበረውን ንጹህ የመጠጥ ውሃ ማስረጫን በዘመናዊ መልክ ለማስፋፋት  በሚል ሽፋን 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበት የተሰራውና   በሃምሌ ወር 2007 ተመርቆ የነበረው የውሃ ማሰራጪያ ተበላሽቶ ስራውን ያቆመ መሆኑን ከአካብቢው የደረሰን ዘና ይገልጻል። ከከተማው አካባቢ በሚደርሰው መረጃ  በከተማዋ የመጠጥ ውሃ ባለመኖሩ ነዋሪዎች በባጃጅ ተጉዘው ውሃ እየገዙ ለመጠጣት የተገደዱ መሆኑ ታውቋል። ለውሃ ማሰራጫው ወጣ ከተባለው አርባ ሚሊዮን ብር ውስጥ አብዛኛው በባእዴን ባለስልጣኖች የተመዘበረ መሆኑን ውስጠ አዋቂ ምንጮች ይናገራሉ።  

 

Ø በየአመቱ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ሕዝቡ በተለይም ወጣቶች የሚደርስባቸውን በደል በመዘርዘር አገዛዙን በተደጋጋሚ ሲያወግዙ መቆየታቸው ይታወሳል። የጥምቀት በዓል በመጣ ቁጥር ለወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ራስ ምታት ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ዘንድሮ በሚደረገው የጥምቀት በዓል ዜጎች ከፍተኛ ተቃውሞ ሊያሰሙ ይችላሉ የሚል ስጋት በጸጥታ ኃይሎች አካባቢ የተፈጠረ መሆኑና ይህንንም ለመቋቋም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከጸጥታ ሃይልች አካባቢ ከተገኘው ዜና መረዳት ተችሏል።  በበዓሉ ላይ ወጣቶች ምን አይነት ቀለም ያለው ካናቴራ እያዘጋጁ እንደሆነ በካናቴራዎቹ ላይ የሚያጻፉት ጥቅሶች  ምን እንድሆኑ ለማወቅ ፖሊሲች ጥረት እያደረጉ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።

 

Ø ባለፈው ጥቅምት ወር በእስራኤል አገር በጸጥታ ኃይሎች በጥይት ከተመታ በኋላ ወድቆ በድብደባ ህይወቱ ያለፈውን ኢርትራዊውን ሃብቶም ዘርኦምን የገደሉ አራት እስራዕላውያን ትናንት ማክሰኞ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑ ተነገረ። በክሱ መሰረት የጸጥታ ኃይሎች ተሳስተው ሃብቶምን የመቱት መሆኑንና ተመቶ በወደቀበት ጊዜም በአካባቢው የነበሩ አንድ ወታደርና ሁለት ሲቪሎች  በጣውላ ደብደው የገደሉት መሆናቸው ተጠቅሷል። ሃብቶም ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ህክምና እየተደረገለት ህይወቱ ያለፈ መሆኑ ይታወሳል። በእስራኤል ውስጥ 34 ሺ ኤርትራውያን  ስደተኞች የሚገኙ ሲሆን እስካሁን ድረስ የእስራኤል መንግስት ለስደተኞች ጥገኝነት ከልክሎ ቆይቷል።

 

Ø ዛሬ ጥር 4 ቀን 2008 ዓም በካሜሩንና በናይጄሪያ ድንበር አካባቢ በምትገኝ ኮሎፋታ በተባለችው ከተማ በአንድ መስጊድ ውስጥ ሁለት ሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ መስጊድ ውስጥ በመስገድ ላይ የነበሩ 10 ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውና ከ12 ሰዎች በላይ የቆሰሉ መሆናችውን የአካባቢው አሰተዳዳሪ ለዜና ምንጮች በሰጠት መረጃ ገልጸዋል። ቦምቡን በማፈንዳት ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም አፈንጅዎቹ  ቦኮሃራም  የተባለው አሸባሪ ድርጅት አባል ሳይሆኑ አይቀሩም የሚል ግምት ተወስዷል። ከተማዋ በቦኮ ሃራም አሸባሪዎች በተደጋጋሚ የተጠቃች ከመሆኗ በላይ በመስከረም ወር ዘጠኝ  ሰዎች በ ታኅሳስ ወር ደግሞ ሰባት ሰዎች በቦምብ ጥቃቶች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።

 

Ø ለሁለት አመታት ያህል በምዕራብ አፍሪካ አገሮች የበርካታ ሰዎችን ህይወት ያጠፋው  የኢቦላ በሽታ ባጠቃላይ የተወገደ መሆኑ በመግለጽ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር ያለው የአለም የጤና ድርጅት ሀሙስ ጥር 5 ቀን ይፋ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። በታኅሣሥ 2006 ዓም በምዕራብ አፍሪካ በምትገኘው የደቡብ ጊኒ መንደር ውስጥ የፈነዳው የኢቦላ በሽታ ባጭር ጊዜ የተቀረውን የጊኒ ግዛት፤ ላይቤሪያንን ሲየራ ሊዮንን አዳርሶ ከ11 ሺ ሰው በላይ ገድሏል። በሽታውን ለመቆጣጠር ከፍ ያለ የገንዘብ ወጭ የተደረገበት ከመሆኑ ባሻገር በርካታ የዓለም ድርጅቶችንና መንግስታትን የጋራ ጥረት ጠይቋል። በሐሙሱ መግለጫ የኢቦላ በሽታ በላይቤሪያ በመጨርሻ ከታየ 42 ቀን ያስቆጠረ መሆኑን በመግለጽ ባሁኑ ወቅት የኢቦላ በሽታ የተወገደ መሆኑ ይገልጻል ተብሏል። በሌላ በኩል ቀደም ብሎ በሽታው ተወግዷል የሚል መግለጫ ከተሰጠ በኋላ እንደገና መመለሱን በማስታወስ አሁንም ቢሆን  ዜጎች ራሳቸውን ለመጠበቅ  የሚገባቸውን ጥንቃቄ እንዲወስዱ ምክር የሚሰጥ መሆኑን የላይቤሪያ የጤና ኃላፊ ገልጸዋል።   

 

 

ጥር 3 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ሰኞ  ጥር 2 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ የቤንዚን እጥረት ተከስቶ  በርካታ ማደያዎች በመኪኖች ሰልፍ ተጨናንቀው መዋላቸው ታወቋል። ትናንት ተከስቶ የነበረው የቤንዚን እጥረት ምክንያቱ ምን እንደሆን ለጊዜው ባይታወቅም ከማመላለሻ እጥረት ጋር ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ብዙዎቹ ይሰጣሉ። የነዳጅ እጥረቱ በትናንትናው እለት የዋጋ ጭማሪ ያላስከተለ ሲሆን እጥረቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን ሽያጩ ወደ ጥቁር ገበያ የሚሄድ ከመሆኑም ሌላ ዋጋው በበኣጭር ጊዜ ውስጥ በእጥፍ ወይም ከዚያ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተገምቷል።

 

Ø ትናንት ጥር 2 ቀን 2008  ረፋድ ላይ ሀረርጌ ውስጥ የምትገኘው የሀሮማያ ከተማ በከፈተኛ ተከስ ስትናወጥ መዋለዋ ከቦታው የተገኘው መረጃ ይገልጻል ወደ ስፍራው ገባው የወያኔ አግአዚ ወታደር በሰላማዊ ሰዎች ላይ በከፈተው ተኩስ የተወሰኑ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውና እንዲሁም በርካቶች  ታፍነው መወሰዳቸውን ዜናው ያስረዳል። በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ በሐረርጌ አብዛኛው ቦታ ውጥረት የነገሰ ሲሆን ከድሬደዋ ወደ አወዳይ የሚወስደው መንግድም ተዘግቶ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ባሌንና ከፋን ጨምሮ በሌሎች ቦታዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ መቀጠሉን ዘገባዎች ይገልጻሉ።

 

Ø በወያኔ መከላካያ ውስጥ ኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ  ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችን ለማሰር ሴራ እየተጠነሰሰ መሆኑን ውስጠ አዋቂ ምንጮች አጋለጡ።  በየቦታዊ እየተካሄደ በሚገኘው ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እየተወሰደ ያለው የሃይል እርምጃ መጠንና ከገደብ ያለፈ ነው በማለት ጥያቄ ያነሱ በርከት ያሉ  መኮንኖች  እንዳሉ ሲታወቅ ከእነዚህ መኮንኖች ውስጥ አንዳንዶቹን ቃሊቲ ከሚገኘው ሎጅስቲክ መምሪያ ናዝሬት ወደ ሚገኘው  ሎጂስቲክ መምሪያ እንዲዛወሩ የተደረገ መሆኑ ታውቋል።  ከመከላከያ ውስጥ በተገኘው መረጃ መሰረት በቀጣይ  ግምገማ  ጠንካራ ተቃዋሚዎች የሆኑት እየተለቀሙ ከማእረግ መግፈፍ እሰከማሰር  ድረስ በሚዘልቅ  እርምጃ በመውሰድ ለመቅጣት የታቀደ መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል  ደግሞ ወያኔ አመጹን በማፈን በኩል ከፍተኛ ሚና ለነበራቸውና ወደ ሌሎች ቦታዎች ቢዛመት ተገቢ መካለክል ሊያደርጉ ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው መኮንኖች ከፍተኛ የማዕረግ እድገት ሊሰጥ የተዘጋጀ መሆኑ ተዘግቧል።

 

Ø በዛሬው ዕለት በቱርክ ዋና ከተማ በኢስታንቡል ቱሪስቶች በሚያዞትሩበት ቀበሌ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ 10 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ሌሎች 15 ሰዎች መቁሰላችው ታውቋል። ከሞቱት መካከል ስምንቱ የጀርመን ዜጎች ሲሆኑ ከቆሰሉት መካከል ደግሞ ሁለቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል። ቦምቡን ያፈነዳው አጥፍቶ ጠፊ በ1980  ዓም የተወለደ የሶሪያ ተወላጅ መሆኑን ጉዳዩን የሚመርምሩት የቱርክ የጸጥታ ኃላፊዎች የገለጹ ሲሆን አይሲስ በሚባለው አሸባሪ ቡድን የተላከ መሆኑ ተነግሯል። በተያያዘ ዜና ሰኞ ዕለት ዕለት በኢራክ ዋና ከታማ በባግዳድ በተለያዩ ቦታዎች በተካሄዱ ተኩሶችና የቦምብ ፍንዳታዎች ባጠቃላይ 51 ሰዎች የሞቱ መሆናችውንና በርካታዎች መቁሰላችውን በመጥቀስ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ባለፈው ሳምንት የኢራክ መንግስት አይሲስ የሚባለውን አሸባሪ ቡድን ከራማዲ  ከተማ አባርሬያለሁ ብሎ መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ሲሆን ትናንት በባግዳድ ላይ በተከታታይ የደረሱት ጥቃቶች የአይሲስ የአጸፋ እርምጃ ሳይሆን አይቀርም ተብሏል። በአደጋው የቆሰሉት ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ባለስልጣኖች ተናግረዋል።

 

Ø በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለአመታት በተካሄደው የእርስ በርስ ጦርነትና ችግር 7.5 ሚሊዮን የሚጠጉ የአገሪቱ ዜጎች እርዳታ የሚያስፈግልጋቸው መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ሰኞ ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ላለፉት 20 አመታት በአገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል የሚገኘውን የማእድን ስፍራ ለመቆጣጠር የተለያዩ ቡድኖች ያካሂዱት የእርስ በርስ ግጭትና ውጊያ የብዙ ዜጎችን ህይወት ያጠፋ ሲሆን በርካታዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከአንዱ ስፍራ ወደሌላው ለመሰደድ ተገደዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ ባስከተለው ቀውስ ምክንያት ነዋሪው በምግብ እጥረት በተላላፊ በሽታና በድኽነት እየተሰቃየ እንደሚገኝ መግለጫው አብራርቷል። ከአገሪቷ ሕዝብ ዘጠኝ ከመቶ የሚሆነው እና ወደ 7.5 ሚሊዮን የሚገመተው ሕዝብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው የተነገረ ሲሆን  ቢያንስ አምስት ሚሊዮን የሚሆነው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያጋጠመው ነው ተብሏል። ከአገሪቱ ህጽናት መካከል በቁጥር ግማሽ የሚሆኑት ደግሞ በከፍተኛ የምግብ እጥረት በሽታ እየተሰቃዩ መሆናቸውን ገልጿል። በኮንጎ ዴሞክራቲክ ረፕብሊክ ለሚገኙ ተረጅዎች ተገቢውን እርዳታ ለማድረስ በተያዘው አመት 690 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ባለስልጣኖቹ ገልጸዋል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሕጻናት ጉዳይ መስርያ ቤት ዛሬ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ከስድስት እስከ 15 ዓመት እድሜ ካላቸው የደቡብ ሱዳን ህጻናት ውስጥ  51 ከመቶ የሚሆኑት የትምህርት እደል የተነፈጋቸው መሆኑን ገልጿል። በደቡብ ሱዳን በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት ከ800 በላይ የሆኑ ትምህርት ቤቶች የወደሙ ሲሆን 400 ሺ የሚሆኑ ተማሪዎች ከየክፍላቸው እንዲወጡ ተገደዋል። 51 ከመቶ ለሚሆኑት ሕጻናት የትምህርት እድል በመንፈግ በኩል ሱዳን ከአለም አገሮች አንደኛ ስትሆን 47 ከመቶ የሚሆኑት ህጻናት የትምህርት እድል የማያገኙባት ናይጀር ደግሞ ተከታይዋ ሆናለች።

 

Ø የአይሲስ አሸባሪዎች ዙየቲና የተባለችውን የሊቢያን የነዳጅ ማከማቻና መላኪያ  ከተማ  ከባህር ላይ ሆነው ለማጥቃት ያደረጉት ሙከራ ከተማውን በሚጠብቁ ወታደሮች ሊከሽፍ የቻለ መሆኑን ከአካባቢው የተገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። ባለፈው ሳምንት ከተማዋን ለመቆጣጠር የአይሲስ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ሁለት ቦምብ 56 ስዎች የሞቱ ሲሆን ባለፈው እሁድ ጥር 1 ቀን 2008 ዓም ከባህር ላይ ሶስት ጀልባዎች ከተማዋን ለማጥቃት ሲጠጉ በከተማው ጠባቂዎች በተደረገ የአጸፋ ተኩስ አንደኛው ጀልባ ሲመታ ሌሎች ሊያመልጡ የቻሉ መሆናቸው ተገልጿል። በሊቢያ ውስጥ የአይሲስ እንቅስቃሴ እየተጠናከረ የመጣ ሲሆን የሊቢያን የነዳጅ ክምችት ቦታዎችን ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ ጥረት ማድረጉ ይታወሳል።    

 

 

 

 

 

 

ር 2 ቀን 2008 ዓም

 

Ø ግሎባል ቮይስ ኦን ላይን የተባለው ድርጅት በቅርቡ በወያኔ አግአዚ ወታደሮች የተገደሉት ዜጎች ቁጥር  ከ140 በላይ መሆኑን ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለውን ድርጅት ዋቢ በማድረግ ጠቅሶ ከእነዚህ ውስጥ ቢያንስ 10 የሚሆኑት በእስር ቤት በስየል ምርመራ (ቶርቸር) የሞቱ መሆናቸውን  የሚገልጽ መረጃ ያገኘ መሆኑን ዘግቧል።  ከሞቱት ውስጥ  የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፤ ሴቶች አርሶ አደሮች እና መምህራን የሚገኙበት መሆኑን ዘግቦ 70 ከመቶ የሚሆኑት ወንዶች መሆናቸውን ጠቅሷል። አንዲት የሰባት ወር እርጉዝ ሴት ከእህቷ ጋር ከአደጋው ለማምለጥ ሲሸሹ መገደላቸው መረጃ የደረሰው መሆኑን በመግለጽ  ድርጅቱ ባወጣው ዘገባው ላይ ዘርዝሯል። በተያያዘ ዜና በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ ያሉት አመጾች የቀጠሉ መሆናችው ታውቋል። በጅማ በሃረርጌ ክፍል ሃገር እና በሌሎች ቦታዎች ተማሪዎች የሚያካሂዱትን የተቃውሞ እንቅስቃሴ አጠናክረው መቀጠላችው የሚደርሱን ዘገባዎች ይገልጻሉ።

 

Ø በሞጆ ከተማ ዙሪያና አካባቢ  የሚገኙ አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ካሉበት ቦታ በቅርብ ግዜ ውስጥ የሚፈናቀሉ መሆናቸውን ሁነታውን በቅርብ የሚያዉቁ ዜጎች አጋልጠዋል።   ነዋሪዎቹም ሆነ አርሶ አደሮቹ ለሚፈናቀሉበት ምክንያት በይፋ የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም  ለባህር ትራንስፖርት ቅርበት ያላቸው የታመኑ ምንጮች አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በጀት የተያዘለት የደረቅ ወደብ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በቅርቡ በተጠቀሰው አካባቢ የሚጀመር መሆኑን ተናግረዋል።   ከሞጆ እስከ ናዝሬት ያለውን መንገድ ተከትሎ ከመንገዱ በሁለቱም ጎን ያሉ ነዋሪዎችና አርሶ አደሮች  በፕሮጀክቱ ስራ ምክንያት እንደሚፈናቀሉ ይታወቅ እንጅ ለተነሺዎቹ ወይም ለተፈናቃዮቹ የተመጣጠነ የካሳ ክፍያ የሚደረግ መሆኑ አልታወቀም። በዚህም ምክንያት እንደ አዲስ አበባው ማስተር ፕላን ይህም ከፍተኛ ተቃውሞ ሊቀሰቅስ ይችላል በማለት ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ወገኖች አስተያየታት ሲሰጡ ይሰማሉ።

 

Ø በመልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ ለመወያየት በሚል ምክንያት ዛሬ ጥር 2 ቀን 2008 በመቀሌ ከተማ ሲካሄድ የነበረው ሕዝባዊ ስብሰባ በተስብሳቢው  መካከል  ጭቅጭቅና አለመግባባት በመፈጠሩ ለጥር 3 ቀን 2008 ዓም መተላለፉ ታወቋል። በስብሰባው ከተገኙት ወደ ሁለት ሺህ ከሚጠጉ ተሰብሳቢዎች መካከል  አንድ ሺህ አምስት መቶ የሚሆት  ከመላው ትግራይ እስከ ቀበሌ ድረስ የተሰገሰጉ የወያኔ አባላት ሲሆኑ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ በርካታዎቹ ተሰብሳቢዎች  በመልካም አስተዳደር እጦት ዜጎች እየተንገላቱ መሆናቸውንና  በድርቁ ምክንያትም የሚከፋፈውለው እርዳታ ፍትሃዊ ባልሆነ መንገድ እየተፈጸመ መሆኑን በመገልጽ ጠንካራ ስሜታችውን መግለጽ በመጀመራቸው መድረኩን ይመሩ  ካደሬዎች  ስብሰባውን በድንገት አቋርጠው ለሚቀጥለው ቀን ለማስተላለፍ ተገደዋል።

 

Ø ለወያኔ ባለስልጣኖች ጠርቀም ያለ ጉቦ በመክፈል ከ100ሽ ሄክታር በላይ የጋምቤላ ለም መሬት ተሰጥቶት የነበረውና በቅርቡ ኮንትራቱ ተሰርዟል የተባለው የካራቱሪ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ለጋዜጠኖች በሰጠው መግለጫ በዓለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ ያገኘ መሆንና ጉዳዩን በአለም አቀፍ አደራዳሪዎች አማካይነት በስምምነት እንዲወሰን የጠየቀ መሆኑን ገልጿል።  በወያኔ አገዛዝ በኩባንያው ላይ የተወሰደው እርምጃ ስምምነቱን የሚጥስ እና  ህጋዊ ያልሆነ ውርስና ዘረፋ ስራ መሆኑን ስራ አሲኪያጁ ጠቅሶ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲያልቅ የሚታገል መሆኑን ተናግሯል። በወያኔ አገዛዝ የተዘረዘሩት ክሶች ከእውነት የራቁ ናቸው ካለ በኋላ ኩባንያው ስራውን በተገቢው መንገድ ለማካሄድ ያልቻለው ወያኔ ተግባራዊ ባደረጋቸው ማዕቀቦች ምክንያት  መሆኑን ተናግሯል። የወያኔ ባለስልጣኖች የኩባንያው ምርት ወደ ውጭ እንዳይላክ በመከልከላቸው 180 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ኪሳራ ያደረሰበት መሆኑና እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት ከሱዳን ነዳጅ እንዳይገባ በመከልከሉ ኩባንያው የሚፈለገውን ያህል ሊሰራ አለመቻሉን ገልጿል። 100 ሺ ሂክታር መሬት በጉቦ የተሰጠው ካራቱሪ ለተወሰደብት መሬት ካሳ እንዲከፈለው ጠይቋል።  ወያኔ 3.3. ሚሊዮን ሂክታር  የኢትዮጵያን ለም ቦታዎች በአነስተኛ ገንዘብ ለባዕዳን ባለሃብቶች ለመቸብቸብ አዘጋጅቶ በርከት ያለውን ለባዕዳን ባለሃብቶች የሰጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለባእዳን ከተሰጡት መካከል ለአገሪቱ ውጤት ያስገኘ አለመኖሩም ተረጋግጧል።

 

Ø የሳኡዲ አረቢያ መንግስት እሁድ ዕለት ያኒት ዳምጤ ፋሪድ የተባለቸውን ኢትዮጵያዊት አንገቷን በመቅላት የግድያ ቅጣት የፈጸመባት መሆኑ ታውቋል። ኢትዮጵያዊቷ አሰሪዋን የሳኡዲ ተወላጅ በመጥረቢያ ገድላለች፤ ገንዘብና ወርቅ ሰርቃለች ተብላ የተከሰሰች ሲሆን ያኒት እርምጃውን መውሰዷን ማመንና አለማመኗን እንዲሁም ስለፍርዱ ሂደትና ማረጋገጫ የተሰጠ ዝርዝር መረጃ የለም። በሳኡዲ ውስጥ የሚኖሩት ስደተኞች ከፍተኛ ኢሰብአዊ የሆነ በደል እንደሚደርስባቸው በየጊዜው የተገለጸ ሲሆን  እርምጃውን ወስዳ ከሆነም ይህ ለማድረግ ያስገደዳት የደረሰባት ከፍተኛ በደል ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ታዛቢዎች አሉ።  የሳኡዲው ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ባለፈው የፈረንጆቹ  ዓመት ብቻ ከ155 በላይ የሆኑ ሰዎችን አንገት በመቅላት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ቅጣት የፈጸመ ሲሆን በዚህም የአለምን ክብረ ወስን ይዟል በማለት የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ዘግበዋል።

 

Ø ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በሶማሊላንድ ወደብ አካባቢ በቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በሰጠመው ጀልባ ውስጥ  የነበሩ 119 ስደተኞች መሞታችው የተረጋገጠ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደሚገኙበት ታውቋል። የወደብ ሰራተኞች የ ሰባ አምስት ሰዎችን ህይወት ያዳኑ ሲሆን የአካባቢው ሰዎች ወደ ወደቡ ተጥርገው የመጡ  የ 119 ሰዎች  አስከሬኖች አግኝተዋል። ከሞቱትም ሆነ ተርፈው እየታከሙ ከሚገኙት መካከል ኢትዮጵያውን እንዳሉበት የተረጋገጠ ሲሆን እነማን መሆናችውና ከየት እንደመጡ ለጊዜው የተገኘ መረጃ የለም።

 

Ø በሱዳን በምዕራብ ዳርፉር ዋና ከተማ ቤትና ንብረታቸው በጎሳ ሚሊያሺያዎች የወደመባቸው ዜጎች ከመንግስት መስሪያ ቤት ፊት ለፊት በመሆኑ የተቃውሞ ድምጽ እያሰሙ በነበሩበት ሁኔታ የጸጥታ ኃይሎች ሰልፉን ለመበተን ባካሄዱት የእሩምታ ተኩስ አራት ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውን ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል። የመንግስቱ ባለስልጣኖች የተባለቱ አራት ሰዎች መገደላቸውን አስተባብለው ሰልፉን ለመበተን ያስገደዳቸው ሰልፈኞቹ ሶስት መኪናዎችን በማቃጠላቸው ነው ብለዋል። ከአስራ ሁለት አመት በፊት በዳርፉር በተካሄደው የእርስ በርስ ጦርነት ከ300 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን 2.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።

 

Ø የናይጄሪያ ፕሬዚዳንቱ የሚስተር ቡሃሪ የቅርብ ረዳትና ተባባሪ እንዲሁም የገዥው ፓርቲ አመራር አባል የሆኑት ሚስተር ላዋል ጃፋሩ ኢሳ በእስር ላይ ከሚገኙት ከቀድሞ የብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ የተቀበሉትን 500 ሺ ዶላር የሙስና ገንዘብ ያስረከቡ መሆናቸው ተገልጿል። ሚስተር ኢሳ ባለፈው ሳምንት 850 ሺ ዶላር ወስደዋል በሚል ክስ መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን  ከባለስልጣኖች ጋር በተደረገው ንግግር ስምምነት መሰረት ከወሰዱት ገንዘብ ውስጥ  500 ሺ ውን ብር መልሰው 380 ሺውን ወደፊት ለመስጠት ቃል በመግባት በዋስ የተፈቱ መሆናቸው የአካባቢ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ለቀድሞ የናይጄሪያ ብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ ለሆኑት ለሚስተር ዱሱኪ ቤት ለመግዛት ገንዘቡን መቀበላቸውን አምነው ገንዘቡን በወሰዱበት ወቅት ከመንግስት ካዝና የወጣ የሙስና ገንዘብ መሆኑን የማያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

 

Contact us: eramharic@googlegroups.com

 

ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 ዓም

Ø አርብ ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም በግብጽ ኸርጋታ በምትባለው ቀይ ባህር ላይ በምትገኝ የወደብ ከተማ  ከአይሲስ ጋር ግንኙነት አላቸው የሚባሉ ሁለት ሰዎች  ቤላ ቪስት በሚባለው ሆቴል ውስጥ የነበሩ ሶስት ቱሪስቶችን በጩቤ ወግተው ማቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ መረጃ ይገልጻል። ከቆሰሉት ቱሪስቶች መካከል ሁለቱ የአውስትራሊያ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ አንደኛው የስዊድን ዜጋ ነው። ፖሊሶች አንዱ አሸባሪ የተገደለ መሆኑና  ሁለተኛው መቁሰሉን አስታውቀው ሌሎች መኖርና አለመኖራቸውን ለማወቅ  ከፍተኛ ምርመራ እያካሄዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። አሸባሪዎች የአይሲስን ባንዲራ ያውለበለቡ ሲሆን ዓላማቸው ቱሪስቶችን ጠልፎ ወስዶ ለማገት  እንደነበር ታውቋል። የግብጽ መንግስት የሚያደርስባቸውን ተጽእኖ ለመቋቋም ጂሃዲስቶች እየወስዷቸው ካሉ እርምጅዎች መካከል አንዱ ቱሪስቶችን ማጥቃትና አገሪቷ ከቱሪስት እንቅስቃሴ የምታገኘውን ገንዘብ ማስቀረት ሲሆን ባለፈው ሐሙስም በጊዛ ፒራሚድ አጠገብ በአንድ የቱሪስት አውቶቡስ ላይ ጉዳት ባያደርሱም ጥቃት መሰንዘራቸው ይታወሳል።  

 

Ø በሰሜን ምስራቅ ኬኒያ በሚገኘውና ከ350 ሺ በላይ የሶማሌ ስደተኞችን በሚያስተናግደው ዳዳብ ከሚባለው ካምፕ ውስጥ የኮሌራ በሽታ ተዛምቶ ከ1000 በላይ የሆኑ ሰዎች በበሽታው መታመማቸውንና  እስካሁን አስር ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን የተመድ ባለስልጣኖች ቅዳሜ ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 በይፋ ገልጸዋል። በሽታው በመጀመሪያ የተከሰተው ከሁለት ወር በፊት መሆኑን ገልጸው  ከካምፕ ውስጥ ክሎሪን በመርጨትና ሳሙናዎችን በማከፋፈል በሽታውን ለማጥፋት ጥረት የተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በሽታው በተበከለ የመጠጥ ውሃ አማካይነት የሚተላለፍ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ባለፉት ሳምንታት በከፍተኛ ደረጃ የዘነበው ዝናብ በሽታውን ሊያስፋፈው እንደቻለ ተናግረዋል። የዳዳብ የስደተኛ ሰፈር ውስጥ ከዛሬ 25 ዓመት በፊት ጦርነትና ረሃብ በመሸሸ የመጡ የሱማሌ ስደተኞች የሚኖሩበት መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በሰላም አሰከባሪ ተግባር ላይ ተሰልፈው የሚገኙ የኮንጎ ወታደሮች ባስቸኳይ እንዲወጡ የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትን የጠየቀ መሆኑን አንድ የድርጅቱ ቃል አቀባይ አርብ ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም አስታውቋል። ተመድ ለወሰደው እርምጃ ምክንያት የሆኑት ጉዳዮች ቃል አቀባዩ ሲዘነዝር የኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች በመሳሪያ ጥራት እና ወታደሮችን በጥንቃቄ በመመልመልና በማዘጋጀት በኩል ተመድ የሚፈልገውን ደረጃ የማይመጥኑ ሆነው በመገኘታቸው እንዲወጡ ተወስኗል ብሏል። ባለፈው ነሐሴ ወር ሶስት የኮንጎ ዴሞክራቲክ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ሶስት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ልጃገረዶችን አስገደደው ደፍረዋል ተብለው መከሰሳቸው ይታወሳል። ባሁኑ ወቅት በማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ ከተሰማሩት 10 ሺ  የተመድ  የሰላም አስከባሪ ኃይል መካከል 807 የሚሆኑት የኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት መሆናቸውም ይታወቃል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ቅዳሜ ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ከሞላ ጎደል ሰላማዊ በነበሩ የደቡብ ሱዳን ግዛቶች ውስጥ ጦርነት በመፋፋሙ ዜጎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው እየተሰደዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ታኅሣሥ ወር ብቻ የምዕራብ ኢኳቶሪያል ከሚባለው ግዛት ውስጥ ጦርነቱን በመሸሽ ከ 23 ሺ ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደ ሌሎች ቦታዎች የሄዱና በየጫካው የተሸሸጉ  ሲሆን ከእኒዚህ ውስጥ ስምንት ሺ ያህሉ ወደ ጎረቤት አገሮች የተሰደዱ መሆናቸው ታውቋል። በደቡብ ሱዳን ላለፉት ሶስት ዓመታት ጦርነቱ ሲካሄድ የነበረው በአገሪቱ ሰሜን ምስራቅ አካባቢ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በምዕራብ ኢኳቶሪያል ግዛት የተለይዩ ሚሊሺያ ኃይሎች ተመስርተው ከመንግስት ወታደሮች ጋር ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ።

 

Ø በሊቢያ 60 የፖሊስ ምልምሎች በተገደሉ ማግስት የአውሮፓው ኅብረት ስምምነት ለተደረሰበት አዲስ መንግስት የ100 ሚሊዮን ዩሮ ( 109 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ የሚሰጥ መሆኑን ገለጸ። ይህ በይፋ የተገለጸው የአውሮፓው ኅብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ የሆኑት ሚስስ ፌዴሪካ ሞገሪኒ ከሊቢያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በቱኒስ ከተማ በሰጡት የጋራ ጋዜጣዊ መገለጫ ላይ ሲሆን ኃላፊዋ ባሁኑ ወቅት በሊቢያ የሚገኘው የጸጥታ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ መሆኑን ጠቅሰው አሸባሪዎችን ለመዋጋት  የአውሮፓው ኅብረት የመሳሪያና የቲክኒክ እርዳታ ያደርጋል ብለዋል።

 

Ø በሚቀጥለው ወር በኡጋንዳ የሚካሄደውን አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ከፍተኛ የሆነ ብጥብጥ ሊነሳ ይችላል በማለት በምርጫው ተወዳዳሪ የሆኑ  የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አስጠነቀቁ። ፖሊሶች ደጋፊዎቻችንን እየደበደቡ ነው በማለት ተቃዋሚዎች ሲከሱ የመንግስት ክፍሎች ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሚሊሺያዎችን እያደራጁ ነው የሚል ክስ እያሰሙ ይገኛሉ። ላለፉት ሰላሳ አመታት በስልጣን ተሰይመው የቆዩትን ፕሬዚዳንት ዩወሬ ሙሰቨኒን ከስልጣን ለማስወገድ ሰባት የፖሊቲካ ድርጅቶች መሪዎች እየተወዳደሩ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ፕሬዚዳንቱን ሊያሰጉ ይችላሉ የተባሉት ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ ቼንጅ (Forum for Democratic Change) የተባለው ድርጅት መሪ ሚስተር አማማ እምባባዚ ናቸው። እስካሁን ሲደረጉ በነበሩ የተቃዋሚ ኃይሎች ስብሰባዎች ላይ ፖሊሶች ደጋፊዎቻችንን ደብድበዋል አጉላልተዋል ብለው የድርጅቶቹ መሪዎች  የከሰሱ ሲሆን ምርጫው ሰላማዊ ካልሆነ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሊነሳ እንደሚችል ተንብየዋል። የመንግስቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሰጡት መግለጫ ደግሞ የግል ሚሊሺያዎችን ያቋቋሙ ኃይሎች መኖራችውን ገልጸው እነዚህ ኃይሎች በምርጫ ከተሸነፉ በአገሪቱ ላይ ጦርነት ለመክፈት የተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኡጋንዳ የፖሊስ ኃላፊ ግጭትን የሚከላከሉ ቁጥራቸው ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጥ ሰላማዊ ዜጎች የመለመሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሁሉም ተወዳዳሪዎች በጥር 4 ቀን 2008 የቴሌቪዥን ክርክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም

 

Ø የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ላለፉት ሁለት ወራት ሲካሄድ በቆየው  ሕዝባዊ እንቅስቃሴ  ቢያንስ 140 ሰላማዊ ዜጎች በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች መገደላችውን መቀመጫው አሜሪካ የሆነው የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዎች ትናንት ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ድርጅቱ በግድያው የወያኔ አገዛዝን አውግዞ በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። የ54 ዓመቱ አቶ በቀለ ገርባ ታኅሣሥ 13 ቀን 2008 ዓም በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበት ወቅት ታመው ለጥቂት ጊዜ ህክምና ሲደረግላቸው ከመታየታቸው ሌላ በአሁኑ ወቅት ያሉበት ቦታ እንደማይታወቅ  ዘገባው ገልጿል።

 

Ø ባለፈው ሳምንት ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በተካሄደው ምርጫ የፕርዚዳንቱን የስልጣን ቦታ ለመያዝ በግልጽ አሸናፊ የሆነ ተወዳዳሪ ባለመኖሩ ሁለተኛ ዙር ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ ተገለጸ። ለምርጫው የሚቀርቡት ሁለቱ ተወዳዳሪዎች የድምጹን 24 ከመቶ ያገኙት ሚስተር ዶሎጉወሌና የድምጹን 19 ከመቶ ያገኙት ሚስተር ቱዋዴራ ናቸው። ሁለቱም ሰዎች ከዚህ በፊት በተለያዩ ወቅቶች ያገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል። ሁለተኛው ዙር ምርጫ ጥር 22 ቀን 2008 ዓም የሚካሄድ መሆኑ የምርጫ ኮሚሽኑ አስታውቋል።  

 

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በመንግስት ራዲዮ በሰጡት መግለጫ ቀደም ብለው በተደረገው ስምምነት መሰረት 50 የሚሆኑ የምክር ቤት መቀመጫዎችና የተለያዩ የሚኒስትር ስልጣኖች ለአማጽያኑ ክፍሎች የሚሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሁለቱን ወገኖች ለማስታረቅ የተቋቋመው ኮሚሽን ኃላፊ የሆኑት የቀድሞ የቦትስዋና ፕሬዚዳንት ፌስተስ ሞጌ በሰጡት ማብራሪያ  የመከላከያ፤ የብሔራዊ ጸጥታ፤ የገንዘብ እና የፍርድ ሚኒስትርን ጨምሮ 16 የሚኒስትር ቦታዎች ለሳልቫኬር መንግስት የሚሰጡ መሆናችውንና  10 የሚኒስትር ቦታዎች ደግሞ ለአማጽያኑ ቡድን የሚሰጡ መሆናቸውን  ተናግረዋል። ለአማጽያኑ ቡድን ከተሰጡት የሚኒስትር ቦታዎች መካከል የነዳጅ ዘይት እና የሰብአዊ እርዳታ ሚኒስትሮች ይገኙበታል።  ቀደም ብለው ተይዘው ለተለቀቁ የፖሊቲካ ሰዎች  የውጭ ጉዳዩ እና የትራንስፖር ሚኒስቴር ቦታዎች የተሰጡ መሆናቸውና የካብኔ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የእርሻ ሚኒስቴር የስልጣን ቦታዎች ደግሞ ለሌሎች  ፓርቲዎች ተወካዮች የተደለደሉ መሆናቸው ተነግሯል። በስምምነቱ መሰረት የአማጽያኑ መሪ ሪክ ማቻር የዛሬ ሶስት ዓመት የተባረሩበትን የምክትል ፕሬዚዳንቱን ቦታ መልሰው የሚይዙ ሲሆን በምን ቀን ወደ ዋናው ከተማ መጥተው ስራቸውን እንደሚጀምሩ አልታወቀም።  በደቡብ ሱዳን ከሶስት ዓመት በፊት በተጀመረው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በ10 ሺ የሚቆጠሩ ስዎች ህይወታቸውን ያጡ ከመሆናችውም በላይ 2.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ከቤት ንብረታቸው የተሰደዱ  4.6 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø የብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎችን ለማስታረቅ አደራዳሪ የሆኑት  የኡጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር  ትናንትን በሰጡት መግለጫ የእርቁ ድርድር ሁሉን ያካተተ ሆኖ ጉዳዩ የሚመለካታቸው ክፍሎች በሙሉ መገኘት አለባቸው ብለዋል። በዚህ ሳምንት መጀምሪያ ላይ የብሩንዲ መንግስት ተወካዮች መፈንቅለ መንግስት ያካሄዱ ሰዎች መገኘት አይኖርባቸው በማለት ውይይቱን ማቋረጣቸው ይታወሳል። የኡጋንዳው መከለከያ ሚኒስትር ከብሩንዲ መንግስት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቁመው ለዘላቂ ሰላም ማንም ኃይል ከውይይቱ መወገደ የለበትም ብለዋል። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ የሚወዳደሩ መሆናቸውን በይፋ መግለጻቸውን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ እና የእርስ በርስ ግጭት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መሰደዳቸው ይታወሳል። በግንቦት ወር ተሞክሮ የነበረው መፈንቅለ መንግስት ቢከሽፍም በየመንገዱ እየተካሄደ ያለው ግጭት እስካሁን ያልበረደ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በቅርቡ የሺያ እምነት ተከታይ የሆኑትን ሼክ መገደላቸውን ተከትሎ በሳኡዲ አረቢያ መንግስት እና በኢራን መካከል የተካረረ ጠብ መፈጠሩና ሁለቱ አገሮች በመካከላቸው የዲፕሎማቲክ ግንኙነት ማቋረጣቸው ይታወቃል። ከሳኡዲ ቀጥሎ ባህሬንና ሱዳን ከኢራን ጋር የነበራቸውን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያቋረጡ  ሲሆን ትናንት ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ደግሞ የሱማሊያ መንግስት ከኢራን ጋር ያለውን የዲፕሎማቲክ ግንኙት ማቋረጡን ገልጾ የኢራን ዲፕሎማቶች በ72 ሰአት ጊዜ ውስጥ ከአገሩ እንዲወጡ አዟል። የሱማሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ እንደጠቀሰው ርምጃው የተወሰደው ኢራን በተከታታይ በሱማሊያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባቷ ምክንያት ነው ብሏል። ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይህ ለምክንያት የተሰጠ እንጅ ሱማሊያ ሱዳንና ባህሬን ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲያ ግንኙነት ለማቋረጥ የወሰዱት እርምጃ ከሳኡዲ የገንዘብ ማባብያና ተጽእኖ ጋር የተያያዘ ነው በማለት ይተቻሉ።  

 

 

 

ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø በኢትዮጵያ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም ከአንድ ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚያስፈልግ መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ ባለሙያዎች እየተናገሩት ይገኛሉ። የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው ዜጎች ቁጥር ከ18 ሚሊዮን በላይ ሊሆን እንደሚችሉ ገልጸው በአሁኑ ወቅት በርካታ እንስሳት እየሞቱ እንደሚገኙና 400 ሺ ህጻናት በምግብ እጥረት እንደተጠቁ ይገልጻሉ። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ሁኔታው ሊባባስ የሚችል መሆኑን ጠቁመው እርዳታው ካልደርሰ አገሪቷ በጣም አስጊ ሁኔታ ውስጥ ልትገባ እንደምትችል ተንብየዋል።  የአሁኑ የድርቅና የረሃብ ሁኔታ ከዛሬ 25 በፊት ከነበረው በጣም አይሎ የሚከስት ሲሆን እርዳታ በአሁኑ ወቅት  ቅድሚያ የሚሰጣቸው እንደሶርያ ደቡብ ሱዳንና የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ዓይነቶቹ ቦታዎች በመኖራቸው  ችግሩ የዓለምን ትኩረት ስቦ ተፈላጊውን እርዳታ ለመሰብሰብ የማይቻል ይሆናል የሚል ስጋት የሚገልጹ አሉ።

 

Ø ባለፈው ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም   ሰሜን ኮሪያ ለሙከራ ሃይድሮጅን ቦምብ አፈንድቻለሁ በማለት መግለጫ መስጠቷ የሚታወስ ሲሆን የምዕራብ አገሮች ሙያተኞች የፈነዳው ቦምብ ኃይል የሃድሮጅን ቦምብ ያህል ጥንካሬ የለውም በማለት የሰሜን ኮሪያን መግለጫ ያጣጣሉ መሆናችው ታውቋል። ይሁን እንጅ እነዚሁ የምዕራብ አገሮች መንግስታት  ማክሰኞ ዕለት የፈነዳው ቦምብ  ሰሜን ኮሪያ ከዚህ በፊት ካፈነዳቻቸው የኑክሊየር ቦምቦች ሁሉ በኃይልና በመጠን የላቀ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን አውግዘው የአጸፋ ርምጃ እንደሚወስዱ ዝተዋል። ጃፓን ደቡብ ኮሪያና አሜሪካ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ በሰሜን ኮሪያ ላይ ሊወስድ የሚችለው እርምጃ በጋራ ለማስተባበር የተስማሙ ሲሆን የተባበሩት መንግስታትም አዲስ ማዕቀብ የሚጥል መሆኑን ፍንጭ ሰጥቷል።  ደቡብ ኮሪያ የሰሜን ኮሪያ ድርጊት ከዚህ በፊት ሁለት አገሮች ያደረጉንን ስምምነት የሚጥስ መሆኑን ገልጻ   አቋርጣ የነበረውን የፕሮፓጋንዳ ራዲዮ ስርጭት ከነገ አርብ ከታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም  ጀምሮ የምትቀጥል መሆኗን አስታውቃለች።  ደቡብ ኮሪያ በሁለቱ አገሮች ወሰን አካባቢ ምስጥራዊ ቦታዎች ላይ በተተከሉ 40 ግዙፍ የድምጽ ማጉያዎች አማካይነት የውጭ አገር ዜናዎችንና ቅስቀሳዎችን ለሰሜን ኮሪያ ወታደሮችና ለአገሪቱ ዜጎች ስታስተላልፍ መቆየቷ የሚታወስ ሲሆን ይህም የሰሜን ኮሪያን ባለስልጣኖች ክፉኛ በማስደንገጡና በማስቆጣቱ ሁለቱን ወደ ጦርነት አፋፍ አድርሷቸው  እንደነበር ይታወሳል። በተከታታይ ንግግሮች በተደረሰ ስምምነት መሰረት የፕሮፕጋንዳው ቅስቀሳ መቋረጡ ይታወቃል። 

 

 

Ø ሐሙስ ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም በሳኡዲ የሚመራው ጦር በየመንን ዋና ከተማ በሰንአ ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ በርካታ ሰዎች የሞቱ  መሆናቸውን ለዜና ምንጮች የገለጹ ሲሆን የኢራን መንግስትም በከተማው የሚገኘው ኤምባሲው ተጠቅቶ ጉዳት ደርሶበታል በማለት  ድርጊቱን አውግዟል።  በየመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረና በዋናው ከተማ ሰንአ ላይ ወታደራዊ ጥቃቶች ከተጠናከሩ በኋላ በርካታ አገሮች ኤምባሲያቸውን ዘግተው ወደ ሌላ ቦታ ያዛወሩ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን የኢራን ኤምባሲ ሙሉ በሙሉ የሚሰራ መሆኑና አለመሆኑ አልታወቀም። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በአየር ጥቃቱ ኢምባሲው የፈረሰ መሆኑን እና በውስጡ የነበሩ   በኢምባሲው ሰራተኞች መጎዳታቸውን ይግለጽ እንጅ የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት እንዳልደረሰ መስክረዋል ተብሏል። የሺያ እምነት ተከታይ መሪ በሳኡዲ አረቢያ ባለስልጣኖች ከተገደሉ ወዲህ በኢራን እና በሳኡዲ መካከል ያለው አለመግባባት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ሁለቱ አገሮች  ዲፕሎማቶቻቸውና ከየአገሮቻቸው ከማስወጣታቸው በተጨማሪ ኢራን ከሳዑድ የሚመጡ ሸቀጦች ወደ አገሯ እንዳይገቡ አግዳለች።

 

Ø ከትሪፖሊ 170 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዝሊተን በምትባለው የሊቢያ ከተማ ውስጥ በአንድ የፖሊስ ማሰልጠኛ ጣቢያ ላይ በጭነት መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ  ቢያንስ 50 ሰዎችን የገደለ መሆኑና ከ127 በላይ ሰዎች ያቆሰለ መሆኑ ለዜና ምንጮች የደረሰው መረጃ ይገልጻል። በሞአመር ጋዳፊ ዘመነ መንግስት ወታደራዊ ጦር ሰፈር የነበረው ቦታ አሁን የፖሊስ ማሰልጣኛ በመሆን እያገለገለ ሲሆን  አደጋው በደረሰበት ወቅት 300 ያህል ምልምሎች በመሰልጠን ላይ የነበሩ  መሆናቸው ታውቋል። ባለፉት አራት ዓመታ ሁለት ራሳቸውን መንግስት ብለው የሰየሙ ተጻራሪ ቡድኖች ሊቢያን እያስተዳደሯት ሲሆን  በርካታ የታጠቁ ኃይሎች በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀሳቸው ምክንያት በአገሪቱ ውስጥ አለመረጋጋት ሰፍኖ ይገኛል። እየተጠናከር መምጣቱ የሚነገርለት አይስስ የተባለው ቡድን ከዚህ በፊት ተመሳሳይ የአጥፍቶ ጠፊ ቦምቦችን ማፈንዳቱ የሚታወቅ ሲሆን በፖሊስ ማሰልጠኛ ላይ የደረሰው አደጋ የአይሲስ ስራ ሳይሆን አይቀርም የሚል ጠንካራ ግምት አለ። በአደጋው የተጎዱት ወደ ሆስፒታል ተወስደው እየታከሙ መሆናቸው ተነግሯል። በቅርቡ በተመድ አስተባባሪነት ሁለቱ ተጻራሪ መንግስታት የእርቅ ስምምነት ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን በሊቢያ የተመድ ልዕክ ማርቲን ኮብለር ድርጊቱን አውግዘው የሊቢያ ዜጎች ህብረታቸውን እንዲያጠናክሩ ተማጽነዋል።

 

 

ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም ሰሜን ኮሪያ የሰራቸውን የሃድሮጅን ቦምብ ለሙከራ ያፈነዳች መሆኑን ገልጻለች። የሰሜን ኮሪያ ባለስልጣኖች በሰጡት መግለጫ ሰሜን ኮሪያን በማጥቃት ላይ የሚገኙትን እንደ አሜሪካ ዓይነት ኃይሎችን ለመቋቋም የኑክሊየር ኃይል ያስፈልጋታል ብለዋል። የሰሜን ኮሪያን ድርጊት ቻይና፤ ደቡብ ኮሪያ፤ ጃፓን ራሺያና የአውሮፓው ኅብረት ያወገዙት ሲሆን አሜሪካም ድርጊቱን አውግዛ አስቸኳይ ርምጃ እንወስዳለን ብላለች። የቦምቡ ፍንዳታ በአካባቢው 5-1 የሆነ የመሬት ንቅናቄ ግፊት ማምጣቱ በተለያዩ የመሬት መንቀጥቀጥ መከታተያ ጣቢያዎች የተመዘገበ ሲሆን ቀደም ብሎ  በርከት ያሉት  ቢጠራጠሩትም አንዳንድ ክፍሎች   የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ሰጥተው ነበር። ሰሜን ኮሪያ ለሙከራ የኑክሊየር ቦምብ ስታፈነዳ ይህ አራተኛ ጊዜዋ ነው።

 

Ø የቀድሞ የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር ሚስተር ቤሎ ሃሊሩ መሀመድ እና  ልጃቸው  1.5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆን የመንግስት ገንዘብ ወስደዋል ተብለው መከሰሳቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ገንዘቡ የተወሰደው ቦኮሃራምን ሊቋቋም የሚችል ወታደራዊ ኃይል ለማጠናከር ለሚያስፈልገው የመሳሪያ ግዥ ከተመደበው ገንዘብ ውስጥ መሆኑ ስለተረጋገጠ ሁለቱ ሰዎች ክስ ተመስሮትባቸዋል። ሁለቱም ጥፋተኛ አይደለንም በማለት ቃላቸውን ሰጥተዋል።  የናጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ለመሳሪያ ገዥ በሚል በተፈረሙ የሀሰት ኮንትራቶች ሽፋን ከቢሊዩን የአሜሪካ ብር በላይ የሆነ የመንግስት ገንዘብ ተዘርፏል የሚለውን ክስ ለማጣራት አንድ መርማሪ ኮሚሽን ያቋቋሙ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን በቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትሩና በልጃቸው ላይ የተመሰረተው ክስ የመሪማሪ ኮሚሽኑ የስራ ውጤት መሆኑ ታውቋል። ባለፈው ወር ይኸው ኮሚሽን የቀድሞ የአገሪቱ ብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ በነበሩት በሚስተር ሳምቡ ዳሱኪ ላይ 19 የወንጀል ዓይነቶችን በመዘርዘር ክስ የመሰረተባቸው መሆኑ ተዘግቧል። ሚስተር ቤሎ የቀድሞ መንግስት መከላከያ ሚኒስትር ሆነው የሰሩ ሲሆን ባሁኑ ወቅትም ሕዝባዊ ዴሞክራሲያ ፓርቲ እየተባለ በሚጠራው የተቃዋሚ ድርጅት ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን አላቸው።

በተያያዘ ዜና ናይጄሪያን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ኃላፊ ሚስስ ክርስቲን ላጋርድ ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም  ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ድርጅታቸው ከናይጄሪያ መንግስት የተሰረቀውን ገንዘብ በማፈላለግና ወደፊትም ተመሳሳይ ዝርፊያዎችን ለመከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ለፕሬዚዳንት ቡሃሪ የገለጹ መሆኑን ተናግረዋል። አያይዘውም ናይጄሪያ ያለባትን የኢኮኖሚ ችግር ለመቋቋም በቂ ገንዘብ ስላላት ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ገንዘብ መበደር የለባትም ብለዋል።

Ø በአልጄሪያ አምስት አመት የሚቆየው የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን በሁለት የምርጫ ዘመን የሚወስን የህገ መንግስት ረቂቂ በመንግስት በኩል የተነገረ መሆኑ ታውቋል።  በተጨማሪም በርበር የተባሉት ውህዳን ብሔረሰቦች ቋንቋም እውቅና እንዲሰጠው ረቂቅ ህገ መንግስቱ ያውጃል። ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም በይፋ በዜና ማሰራጫዎች የተነገረው ይህ ረቂቅ ህገ መንግስት የምክር ቤት አባላትን ድጋፍ አግኝቶ ከጸደቀ ለውሳኔ ሕዝብ እንደሚቀርብ ይቀርባል ተብሏል። የአሁኑ ፕሬዚዳንት ቡተፍሊካ በከፍተኛ ህመም ውስጥ በነበሩበት ሁኔታ  የዛሬ ሁለት አመት ለአራተኛ ጊዜ ተመርጠው በስልጣን ያሉ መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ለአቅመ ሄዋን ያልደረሱ ልጆችን አስገድደው ደፍረዋል በማለት አዲስ ክስ የቀረበ መሆኑን በመግለጽ ሁኔታውን እየመረመሩት መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣኖች ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 2008 ዓም ተናገረዋል። ምርመራው ምን ያህል የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት እንዳሉበትና የየትኞቹ አገሮች አባላት እንደሆኑ እንደሚዳስስና  የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትና በአገሪቷ ላይ ያሰማሩ   አገሮች በራሳቸው ምርመራ እንዲያካሄዱ መመሪያ የተሰጠ መሆኑን ተናገረዋል። በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ የተሰማሩ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ድርጊት በተደጋጋሚ መወንጀላቸው የሚታወስ ሲሆን ባለፈው ወርም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቂ ርምጃ አልወሰደም የሚል ወቀሳ ይህንን ጉዳይ ለማጣራት ተሰይሞ ከነበረው ገለልተኛ ኮሚቴ  የተሰጠ መሆኑ ይታወሳል። 

 

Ø በደቡብ ሱዳን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በመሸሽ ዜጎች በየአቅጣጫው አገራቸውን እየተው መውጣታቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ 7000 የሚሆኑ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በመግባት በስደተኛነት መመዝገባቸውን ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ገልጿል። ስደተኞቹ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኮንጎ የገቡት ባለፈው ወር ውስጥ ሲሆን  በአገሪቱ ሰሜን ምስራቅ በሚገኘው የመመዝገቢያ ጣቢያ የተመዘገቡ መሆኑ ተገልጿል።  የደቡብ ሱዳን ችግር ከተጀመረ ከታኅሣሥ 2006 ዓም ጀምሮ በአስር ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 2.2 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ውስጥ በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ስምምነት ተፈርሟል ቢባልም ጦርነቱና ግድያው መቀጠሉን የዜና ምንጮች እየዘገቡት ይገኛሉ።   

 

 

 

ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የቀድሞ የብሩንዲ መከላከያ ሚኒስትር የነበሩት ሳይሪል ዳዩሩኪየ እና ሌሎች አራት ተባባሪዎቻቸው ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ተሞክሮ የነበረውንና ሳይሳካ የቀረውን መፈንቅለ መንግስት በማደራጀትና  በማስተባበር  በተከሰሱበት የወንጀል ክስ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኞች ናቸው በማለት ብይን መስጠቱን  ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ገለጸ። የመከላከያ ሚኒስትሩ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት የመከላከያ ቃል “ሰላማዊ ሕዝብ በገፍ በአውራ ጎዳናዎች ላይ በፖሊሶች ሲገድሉና የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የተባሉት በሰው ደግሞ ሕዝብ እየሞተ  ኳስ ሲጫወቱ እያየሁ፤ እጄን አጣጥፌ ለመቀመጥ አልችልም ብለዋል። ተባባሪዎች በመባል የተከሰሱት አራት ግለስቦች  ሁለት የሰራዊቱ ጄኔራሎችና ሁለት የፖሊስ ኮሚሽነሮች ናቸው። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ውስጥ የብሩንዲ ፕሬዚዳንቱ ህገ መንግስቱን ተላልፈው ለሶስተኛ ጊዜ የሚወዳደሩ መሆናቸውን በይፋ ባወጁበት ወቅት በተነሳው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በርካታ ሰዎች መገዳላቸውና መሰደዳቸው ተከትሎ  በግንቦት ወር ውስጥ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉ ይታወቃል። የመፈንቅለ መንግስቱ ቀንደኛ መሪ ናቸው ተብለው የተፈረጁት ጄኔራል እና  ሌሎች ከፍተኛ መኮንኖኖች እስካሁን ሳይዙ ቆይተዋል። ፍርድ ቤቱ መፈንቅለ መንግስት በማካሄድ ክስ የተከሰሱትን የ28 ሰዎች ጉዳይ ከታኅሣሥ 4 2008 ዓም ጀምሮ እያየ ሲሆን በሌሎች ተከሳሾች ላይም በቅርቡ ብይን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø በማዕከላዊ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው አገራዊ ምርጫ 30 ሰዎች ለፕሬዚዳንት ቦታ የተወዳደሩ ሲሆን ከተወዳዳሪዎቹ ውስጥ 20 የሚሆኑት ምርጫው በርካታ እንከኖች ያሉበት በመሆኑ መሰረዝ አለበት የሚል ጥያቄ አቅርበዋል። ሰኞ ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓም ባወጡት የጋራ መግለጫ በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ አሰጣጡ ስነስርዓትን ያልተከተለ መሆኑንና በመራጮች ላይ  በርካታ ማስፈራሪያዎች  የተደረጉ መሆናችውን ገልጸው  ይህ በምርጫ ስም የተሸፈነ ማጭበርበር ስለሆን ምርጫው መሰረዝ አለበት ብለዋል። በታኅሣሥ 20  ቀን 2008 ዓም በተካሄደው ምርጫ ከተሰጠው ድምጽ አንድ አራተኛ የተቆጠረ ሲሆን እስካሁን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ፎስተን ቱአዴራ የድምጹን 23 ከመቶ በማግኘት እየመሩ መሆናችው ተነግሯል። አሸናፊ ሊሆን የሚችለው ተወዳዳሪ የድምጹን 50 ከመቶ ካላገኘ ሁለተኛ ዙር ምርጫ በጥር 24 ቀን 2008 ዓም ይካሄዳል ተብሏል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በእርስ በርስ ግጭት እየታመሰች ላለቸው የማአከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ይህ ምርጫ መረጋጋትን ያስገኛል የሚል ተስፋ የነበረ ሲሆን በተካሄደው ምርጫ ላይ ተቃውሞ መነሳቱ ብዙዎችን ስጋት ላይ ጥሏል።

 

Ø የዩጋንዳ ፖሊስ ሰኞ ዕለት በሰጠው መግለጫ ከ2004 እስከ 2006 ዓም ባሉት ጊዜዎች ውስጥ ከዋናው አውሮፕላን ጣቢያ በየጊዜው ተይዘው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከነበሩት  አደንዛዥ እጾች  ውስጥ 80 ኪሎ የሚመዝንና  4 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ  እጽ መሰወሩን እና  በከፍተኛ ደረጃ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል። ጉዳዩን የሚያውቁ ሰዎች ለዜና ምንጮች እንደገለጹት 80 ኪሎ የሚመዝን እጽ በከፍተኛ ደረጃ ጥበቃ ከሚደረግለት መጋዘን ተወስዶ በምትኩ የስንዴና የካሳቫ ዱቄት የተቀመጠ መሆኑን ጠቁመዋል። እጹ መሰረቁን ለማወቅ የተቻለው የመንግስት ተቆጣጣሪዎች ባለፈው ዓመት ከመጋዘኑ ለናሙና የወሰዱት ሲመረመር ከተገኘ መረጃ ነው የተባለ ሲሆን በወንጀሉ የከፍተኛ ባለስልጣኖች እጅ ሳይኖርበት አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ አሉ።

 

Ø በደቡብ ሱዳን ካሉት አቢይ በሽታዎች መካከል አንዱ የወባ በሽታ መሆኑ የታወቀ ቢሆንም በዚህ ዓመት  በበሽታው የተለከፉት ሰዎች ብዛት ከዚህ በፊት ባልነበረ ደረጃ መጨመሩ ተገለጸ። የወባ በሽታ ወቅት ነው በሚባሉት ከመስከረም እስከ ታኅሣሥ ባሉት ወሮች  1.6 በሽተኞች በወባ በሽታ የተለከፉ መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች የበሽተኞቹ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲወዳደር  በእጥፍና ከዚያም በላይ የጨመረ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የድንበር የለሽ ሃኪሞች ከመንግስት ተቋሞች ጋር በመተባበር የጠና አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ ቢሆንም በመድኅኒት እጥረት ምክንያት የተሟላ አገልግሎት ሊሰጥ ባለመቻሉ  በርካታ ሰዎች ለሞት አደጋ የታጋለጡ መሆናቸውና አገልግሎቱን እየሰጡ ያሉ ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።       

 

 

 

ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የሳኡዲ አረቢያ መንግስት የታወቁትን የሺያ እምነት ተከታዮች መሪ ሼክ ኒምር ከሌሎች 47 ሰዎች ጋር ባለፈው አርብ በሞት ከቀጣ ጀምሮ በመካከለኛው ምስራቅና በሌሎች ቦታዎች ከፍተኛ የሆኑ የተቃውሞ ስልፎች ተደርገዋል። አልአዋሚያ በሚባለው የእምነቱ ተከታዮች በብዛት በሚኖሩበት የሳኡዲ ግዛት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ከሼክ ኒምር ቤት እስከ ከተማው መካከል ተሰልፈው ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን “ሕዝቡ የሳኡዲ መንግስት እንዲወገድ ይፈልጋል” “ሞት ስልጣን ላይ ላለው የሳኡድ ቤተሰብ” የሚሉ መፈክሮች ሲያሰሙ የነበሩ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።  ባለፈው ቅዳሜ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ውስጥ የሼኩን መገደል የተቃወሙ ዜጎች በሳኡዲ ኤምባሲላይ እሳት በመለኮስ ንብረት ያወደሙ ሲሆን ኢራን 40 ሰዎችን በቁጥጥር ማድረጓን ገልጻለች።  ይህንን ተከትሎ ሳኡዲ አረቢያ ከኢራን ጋር ያላት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በማቋረጥ የኢራን ዲፕሎማቶች በ48 ሰዓት እንዲወጡ ስታደረግ ኢራንም ተመሳሳይ እርምጃ ወስዳለች። በባህሬን ተከታታይ የተቃውሞ ስልፎች የተደረጉ ሲሆን  በሁለት የሱኒ ተከታዮች መስጊዶች ላይ በተጣሉ ቦምቦች   አንድ አሚር የሞቱ መሆናቸውና በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑ ተዘግቧል። ባህሬንም ከኢራን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋርጣለች።  የሼኩ መገደል በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች፤ በእንግሊዝ፤ በፓኪስታን፤ እና በቱርክ ተቃውሞ አስነስቷል። የቀድሞ የኢራክ ጠቅላይ ሚኒስትር አል ማሊኪ የኢራክ ሕዝብ ድርጊቱን እንደሚያወግዝ ገልጸው ይህ አሰቃቂ የሆነ ግድያ ለሳኡዲ ገዥዎች ከስልጣን መወገድ ምክንያት ይሆናል ብለዋል።  የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም ድርጊቱን አውግዘው እርምጃው የተወሰደው በፖለቲካ ምክንያት ነው ብለዋል።

 

Ø በኬኒያ ሰሜን ምስራቅ የሚገኘው የጋሪሳ ዩኒቨርስቲ ለ150 ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት በሆነው በአልሸባብ ጥቃት ምክንያት ላለፉት ዘጠኝ ወራት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ  የተከፈተ መሆኑ ተነግሯል። የዩኒቨርስቲው አስተዳዳሪዎችና መምህራን ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓም ስራ የሚጀምሩ ሲሆን ተማሪዎች ደግሞ ከህዳር 2 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ ትምህርት እንደሚጀምሩ ታውቋል። የተማሪዎችን ደህንነት የሚጠበቅ የፖሊስ ጣቢያ በዩነቨርሲት ውስጥ የተቋቋመ መሆኑም ተነግሯል።

 

Ø በሊቢያ ሲድራ ከሚባለው የነዳጅ ማውጫ ወደብ አጠገብ ራሱን የእስላማዊ መንግስት ብሎ ከሚጠራው አይሲስ ጋር ግንኙነት ያላቸው ኃይሎች ከወታደሮች ጋር እየተፋለሙ መሆናችው ታውቋል። በአሁኑ ወቅት ጦርነት በምን ያህል ርቀት ላይ እየተካሄደ መሆኑ ባይታወቅም እይሲስን የሚደግፉት ኃይሎች ቀደም ብለው ከቦታው 30 ኪሎሜትር የሆነውን ቦታ የተቆጣጠሩት መሆኑን ከአካባቢው የሚመጡ ዘገባዎች ገልጸዋል። ሁለት መኪና ላይ የተጫኑ ቦምቦች ፈንድተውም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብሏል። ይኸው ቡድን ከሁለት ወር በፊት ተመሳሳይ ጥቃት አድሮጎ የነዳጅ ማውጫውን ለመቆጣጠር የሞከረ ሲሆን ብርቱ ተቃውሞ ስለገጠመው ሙከራው መክሸፉ ይታወሳል። ሲድራ የተባለውችው ቦታ በምዕራብ ሊቢያ ራሱን በመንግስትነት ባወጀው ኃይል ስር እንዳለች ይታወቃል።

 

Ø የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ካጋሚ ለሶስተኛ ጊዜ ለመመረጥ እንዲችሉ ህገ መንግስት ማስቀየራቸውንና እሳቸውም ለምርጫው ዝግጁ ነኝ በማለት ይፋ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ መንግስታቸው ድርጊቱን በጽኑ የኮነነ መሆኑን ገልጸዋል። ቃል አቀባዩ ህገ መንግስቱን ተጠቅሞ የስልጣን ዝውውር ማድረግ ለዴሞክራሲያ አሰራር ቁልፍ መሆኑን መንግስታቸው የሚያምንበት መሆኑን ገልጸው የስልጣን እድሜን ለማራዘም ብቻ ያለውን ህግና ደንም መሻርና መለወጥ የሚወገዝ ነው ብለዋል። በተለይም አንድን ግለሰብ ስልጣን ላይ ለማቆየት የሚደረገው አግባብ ያልሆነ የህግ ለውጥ ያሳስበናል ብለዋል። ፖል ካጋሚ የአሜሪካ ለረጅም ጊዜ የአሜሪካ አገልጋይና  ወዳጅ ሆነው የቆዩ መሆናችው የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ መንግስት በካጋሚ ላይ ይህን የመሰለ ውግዘት ማሰማቱ  ብዙዎችን አስገርሟል።

 

Ø የጣሊያኑ ግዙፍ ኩባንያ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ ለጊቤ አራት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግንባታ የሚሆን ፋይናንስ ማግኘቱን ማረጋገጫ አቅርቦ ወደ ድርድር ቢገባም፣ ሦስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፕሮጀክቱ እንዲሰጣቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አዲስ ጥያቄ ማቅረባቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡
ሳሊኒ ቀደም ሲል ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለፕሮጀክቱ የሚሆን ፋይናንስ እንደሚያገኝ ቢገልጽም፣ ከሳምንት በፊት ከጣሊያን ኤግዜም ባንክ 1.5 ቢሊዮን ዩሮ ብድር እንደሚያመጣ መተማመኛ ማቅረቡ ታውቋል፡፡
በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ያሉበት ቡድን፣ ከሳሊኒ ጋር በፋይናንስና በቴክኒክ ጉዳዮች ላይ ድርድር መጀመራቸው ተገልጿል፡፡
ነገር ግን ይህ ድርድር እየተካሄደ ባለበት ወቅት የቱርክ ኩባንያ አዝሚር፣ የብራዚል ኩባንያ ፔሮዝና የቻይና ኩባንያ ሲኖ ኃይድሮ የጊቤ አራት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እንዲሰጣቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥያቄ ማቅረባቸው ታውቋል፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንዳረጋገጡት እነዚህ ኩባንያዎች ለግንባታ የሚሆን ፋይናንስ እንደሚያመጡና ለአገር በቀል ኩባንያዎችም ሥራ እንደሚሰጡ በመግለጽ፣ መንግሥት ውስን ጨረታ አውጥቶ አሸናፊ ለሚሆነው ኩባንያ ሥራውን እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

 

 

 

ታኅሣሥ 23 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø በተለያዩ ቦታዎች በወያኔ አገዛዝ ላይ የሚደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የቀጠሉ ሲሆን ሐሙስ ማታ በዲላ ዩነቨርሲቲ ሰፍሮ የሚገኘው የአግአዚ ጦር እንዲወጣ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባደረጉበት ወቅት  በተወረወረ ቦምብ ሁለት ተማሪዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ ስድስት በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው መሆኑ  ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የወያኔ አገዛዝ ቦምቡ የተወረው ባሸባሪዎች ነው ይበል እንጅ በአግአዚ ወታደሮች ለመሆኑ ጥርጣሬያቸውን የሚገልጹ በርካታ ናቸው።  በህይወት የተረፉት ተማሪዎች ግቢውን ለቅቀው  ለመውጣት ሲሞክሩ በወያኔ ወታደሮች ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ከመሆኑም በላይ በርከታዎቹ ታስረው የተወሰዱ መሆናቸውን  የአይን እማኞች ይናገራሉ።  ከተጎዱት መካከል አራቱ በጽኑ የቆሰሉ ሲሆን በቦምቡ  ለህክምና ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናቸውም ታውቋል።

 

Ø አዲስ አበባ በሚገኘው የወያኔ የማዕከለካዊ ወንጀል ምርመራ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰሞኑን ከአራት መቶ በላይ እስረኞች መታሰራቸውንና ለምርመራ በየቀኑ ከፍተኛ ድብደባ  እየተካሄደባቸው መሆኑን ምንጮች  ገለጸዋል። በእስር ቤቱ የጓሮ አቅጣጫ በሚገኙት ሶስት ክፍሎች ውስጥ ከመቶ ሰማንያ በላይ የሚሆኑ እስረኞች ሲገኙ ከፎቁ ምድር ቤት ውስጥ ባሉ ሌሎች ክፍሎች ውስጥ ደግሞ ሁለት መቶ ሰማንያ በላይ ታፍገው እንዲታሰሩ መደረጉን የሚናገሩት እነዚሁ ምንጮች ከታሰሩበት ክፍል ሲወሰዱ በሚገባ እየተራመዱ የሚሄዱ እስረኞች ከምርመራው በኋላ  በወሳንሳ ተይዘው እንደሚመለሱ ይናገራሉ።  

 

Ø በደቡብ ሶማሊያ በምትገኘው እና ከወታደራዊ አንጻር ቁልፍ ቦታ በያዘችው በኪስማዮ ከተማ ውስጥ የሲየራ ሊዮንን ወታደሮችን በመተካት 250 የወያኔ ወታደሮች ተመድበው የተሰማሩ መሆናቸው ተነግሯል። ሲየራ ሊዮን በሱማሊያ ውስጥ ከተሰማራው ከአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወታደሯቿን ያስወጣችው ባለፈው ዓመት የኢቦላ በሽታ አገሪቱን በከፍተኛ ደረጃ ባጠቃበትና የሶማሊያ መንግስት ወታደሮቹ ኢቦላ ሊያስተላልፉ ይችላሉ የሚል ስጋት በገለጸበት ወቅት ነው። የአልሸባብ እንቅስቃሴ በተዳከመ ሁኔታም ቢሆን ጥቃት መሰንዘሩን በመቀጠሉ የወያኔ ወታደሮች በተጨማሪ እንዲመደቡ ተደርጓል። ለጊዜው 250 ወታደሮች ይሰማሩ እንጅ ሌላ 800 የሚሆኑ ተጨማሪ ወታደሮች በቅርቡ የሚመደቡ መሆናቸውን ምንጮች ይገልጻሉ።  ሶማሊያ ውስጥ በአልሸባብ በደረሰ ጥቃት በርካታ ወያኔን በማገልገል ላይ ያሉ ወታደሮች እየሞቱ መሆናቸው በየጊዜው የተዘገበ ሲሆን የአካል ጉዳተኛ የሆኑትም በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች ውስጥ  ሲታከሙ መቆየታቸውን የሚገልጹ ተከታታይ ዘገባዎች እንደነበሩ ይታወሳል።  

በተያያዘ ዜና ዛሬ ታኅሣሥ 23 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ በሚገኝ የምግብ ቤት ውስጥ የአልሸባብ አባል ነው ተብሎ የሚጠረጠር አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ ራሱን ከማጥፋቱ ሌላ አንድ ሰላማዊ ሰው የገደለ መሆኑና ሶስት ሰዎች ያቆሰለ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ቦምቡ በፈነዳበት ወቅት በርከታ ጋዜጠኞች በምግብ ቤት ውስጥ የነበሩ በመሆናቸው የአጥፍቶ ጠፊው ኢላማ  ጋዜጠኖችን ለመግደል ነበር የሚል ግምት ተሰጥቷል።   

 

Ø የሳኡዲ አሪቢያ መንግስት ከአራት አመት በፊት በቁጥጥር ስር ባደረጋቸውና  የወንጀል ክስ መስርቶ ባስፈረደባቸው 47 ሰዎች ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎ የሞት ቅጣት እንዲፈጸም አድርጓል። የሞት ቅጣቱ ከተፈጸመባቸው መካከል የታወቁት የሺያ ሃይማኖት ተከታዮች መሪ ሼክ ኒሚር አል ኒሚር  አንዱ በመሆናቸው በሳኡዲ ውስጥ የሚገኙት የሺያ እምነት ተከታዮች አመጽ ሊያነሱ ይችላሉ የሚል ፍራቻ ተፈጥሯል። የዛሬ አራት አመት በአገሪቱ ምስራቅ የሚኖሩ የሺያ እምነት ተከታዮች የሚደርስባችውን በደል በመቃወም ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ሲታወቅ የሳኡዲ ባለስልጣኖች እንቅስቃሴውን ለማፈን ሃይልን ከመጠቀማቸው ሌላ ሼክ ኒሚርንና ተከታዮቻቸውን ይዘው ማሰራቸውና ለፍርድ ማቅረባቸው ይታወሳል። ሼኩ በተያዙበት ወቅት በተነሳው ብጥብጥ ሶስት ሰዎች መሞታቸውም ይታወቃል። ሳኡዲ አረቢያ በሼኩ ላይ የሞት ቅጣት መፈጸሟ ልትቋቋመው የማትችለው  ከፍተኛ ውርደት ይደርስበታል በማለት የኢራን መንግስት ያስጠነቀቀ ሲሆን የሺያ እምነት ተከታዮች በሚኖሩበት በምስራቅ ሳኡዲ አረቢያ የሚገኙት   የሺያ እምነት ተከታዮች ከፍተኛ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ የሚል ስጋት አለ። የሳኡዲ መንግስት የሺያ እምነት ተከታዮች በደል አልደረሰባችውም በማለት በተከታታይ መግለጫ የሰጠ ሲሆን ከተገደሉት 47 ሰዎች መካከል ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸው የሱኒ እምነት ተከታዮችም ያሉበት መሆኑን ገልጿል።  ባለፈው የፈረጆቹ ዓመት ሳኡዲ አረቢያ ከ150 በላይ በሆኑ ሰዎች ላይ የሞት ቅጣት የፈጸመች መሆኑ ሲታወቅ ባለፉት 20 አመታት ከተፈጸሙ የሞት ቅጣቶች የአለፈው አመቱ ከፍተኛ ነው በማለት የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ።

 

Ø በሌላ በኩል የመን ውስጥ ከሁቲ አማጽያንና ከቀደሞ የመን ፕሬዚዳንት ከሳላህ አብዱላህ ሳላህ ተከታዮች ጋር እየተዋጋ ያለው በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል ከጥቂት ሳምንታት በፊት ተፈርሞ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ከዛሬ ከታኅሣሥ 23 ቀን ጀምሮ የፈረሰ መሆኑን ገልጿል። በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም በተደጋጋሚ የተጣሰ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ጥምር ኃይሉ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው አርብ ዕለት በሁቲ አማጽያን ወደ ሳኡዲ ግዛት የተተኮሰ ቦልስቲክ ሚሳየል ጠልፈው መያዛቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል። የሳኡዲ መንግስት ፔቲሪየት የተባለው የሚሳየል መጥለፊያ መሳሪያ በመጠቀም በየጊዜው ከየመን የተተከሱ በርካታ ሚሳየሎችን መጥለፋቸው የሚታወቅ ሲሆን ከ80 በላይ የሚደርሱ የሳኡዲ ወታደሮችና የወሰን ጠባቂዎች ከየመን በተተኮሱ ሚሳየሎችና በወሰን አካባቢ በነበሩ ወታደራዊ ግጭቶች መሞታቸው ይታወሳል።

 

Ø አልጄሪያን ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻ ለማድረግ በግምባር ቀደምትነት ከተዋጉት መካከል አንዱ የሆኑትና የነጻነት ጀግና ተብለው የሚጠሩት ሆሲን አይት አህመድ በሰማንያ ዘጠኝ አመታቸው ባለፈው ረቡዕ በስደት በሚኖሩበት በስዊዘርላንድ የሞቱ ሲሆን አስከሬናቸው ወደ አልጄሪያ መጥቶ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሀዘንተኞች በተገኙበት በከፍተኛ ክብር የተቀበረ መሆኑ ታውቋል። በመንግስት ደረጃ ቀብሩ ተዘጋጅቶ የነበረ ቢሆንም የሟቹ ቤተሰቦች አስከሬኑ በተወለዱበት ስፍራ እንዲቀበር በመጠየቃቸው ወደ ዚያው ተወስዶ አርብ ዕለት የቀብሩ ስነስርዓት ተፈጽሟል። ሟቹ በ1954 ዓም አልጀሪያ ከፈረንሳይ ነጻ ስትወጣ የተመሰረተውን ወታደራዊ አስተዳደር በመቃወምና በሕዝብ የተመረጠ መንግስት እንዲሰየም በመጠይቅ በኩል ግምባር ቀደም ሚና የተጫወቱ ሲሆን በነበራቸው የፖሊቲካ አስተሳሰብ ወደ ውጭ ተሰደው የኖሩ መሆናቸው ይታወቃል። ሆሲን አህመድ የመሰረቱ የሶሻሊስት ኃይሎች ግምባር የሚባለው ፓርቲ ተቃዋሚ ፓርቲ ሲሆን የፓርቲው አባላት በቀብሩ ወቅት “ነጻና ዴሞክራሲያዊ አልጀሪያ” የሚል መፈክር ያሰሙ እንደነበር ተዘግቧል።  

 



ታኅሣሥ 22ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ዘጋቢዎቻችን አዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ የገበያ ስፍራዎች  ተዘዋውረው ባጠናቀሩት ዘገባ መሰረት  የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በርከት ያሉ ዕቃዎች የገበያ ዋጋ  ጭማሪ ያሳዩ  መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። የመቶ ኪሎ ጤፍ  ዋጋ ካለፈው በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር ሁለት ሺህ ሶስት መቶ ብር የገባ ሲሆን በዚህም ምክንያት እንጀራ እየጋገሩ የሚሸጡ ባልትና ቤቶች አንዱን እንጀራ ቀደም ሲል ሲሸጡበት ከነበረው ሶስት ብር ከሃምሳ ላይ ጭማሪ አድርገው አራት ብር መሸጥ መጀመራቸውና  አራት ብር ሲሸጡ የነበሩት ደግሞ አራት ብር ከሃምሳ ሳንቲም በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ለመገንዘብ ተችሏል።  አንድ በሬ አስራ ሶስት ሺህ አምስት መቶ እና ከዚያ በላይ በሆነ ዋጋ በአዲሱ ገበያ እየተሸጠ ሲሆን ጠቦት በግ ሁለት ሺህ ብር የፍየል ሙክት አራት ሺህ ስምንት መቶ ብር በመሸጥ ላይ ናቸው።  የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ሃያ ሁለት ብር እንዲሁም የአንድ ኪሎ ቅቤ ዋጋ መቶ ሰማንያ ብር  የደረሰ ሲሆን   የስጋን ዋጋ ወሰደ የተባለው ምስር ክክ ደግሞ አንዱ ኪሎ ሃምሳ ስድስት ብር እየተሸጠ መሆኑ ዘጋቢያችን ደርሶበታል።  ቀደም ብሎ ፈረሱላው እስከ አንድ ሺህ  ሰባት መቶ ብር ሲሸጥ የሰነበተው በርበሬ  ወደ ሁለት ሺህ አርባ ብር ማሻቀቡ ታውቋል።   ቲማቲም አንዱ ኪሎ ሃያ ብር፤ ቃሪያ አንዱ ኪሎ አስራ ስምንት ብር ሎሚ በኪሎ ሃያ አምስት ብር፤ ብርቱካን በኪሎ ሰላሳ ሁለት ብር በመሸጥ ላይ ያሉ ሲሆን የአንዱ ማደባሪያ ከሰል ዋጋ ደግሞ ሶስት መቶ ሰማንያ ብር ገብቷል።  የምግብ ዕቃዋዎች ዋጋ ከአብዛኛው ሰው አቅም በላይ ሆነው ለረጅም ጊዜ መቆየታቸው የታወቀ ቢሆንም ዘንድሮ ደግሞ ገና ዓመት ባሉ ቀናት ሲቀሩት በጣም መጨመሩ ሕዝቡን ከፈተኛ ስጋት ውስጥ ከትቶታል። ምን ዓይነት ዘመን መጣ በማለት የመረረ ንግግር በይፋ እየተናገረ መሆኑ ይሰማል።

 

 

Ø ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በሆሮ ጉዱሩ ዞን ጃርገዳ በሚባለው ወረዳ የአሊቦ ሁለተኛ ደረጃ መምህር የነበረውና የኦህዴዱ ከፍተኛ ባለስልጣን ወንድም  መምህር አዱኛ በትምህርት ቤቱ ውስጥ በአግአዚ ጦር ጥይት ተመትቶ ለከፍተኛ ህክምና በአዲስ አበባው ሚኒሊክ ሆስፒታል ሲታከም ቆይቶ ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀ ረፋድ ላይ የሞተ መሆኑ ታውቋል። የሟቹ ወንድም ድጉማ አሬሶ የሙክታር ከድር አማካሪና የኦርሚያ ክልል ተብየው የልማት ተቋማት ቢሮ ኃላፊ በመሆኑ  አስከሬኑን ለመረከብ በርካታ የኦህዴድ ባለስልጣንት በሚኒሊክ ሆስፒታል ተገኝተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በአሊቦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የወያኔው የአግዓዚ ጦር ከስፍራው በመገኘት ባካሄደው ጭፍጨፋ አንድ ተማሪና ሁለት መምህራን መገደላቸውና ለጊዜው ቁጥራቸው ያለታወቀ ተማሪዎችም ማቁሰላቸው ሲታወቅ የትምህርት ቤቱ ምክትል ዳይሬክተርና መምህር የሆነው አዱኛ ከቢሮ በማስወጣት በተኮሱት ጥይት ያቆሰሉት መሆኑ ታውቋል። ወያኔ በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለፈው ጭፍጨፋ አገልጋዩ እና አሽከሩ የሆነውን ኦህዴድንም እየለበለበ በመሆኑ የአገዛዙ ማክተሚያ ሊሆን ይችላሉ የሚል አስተያየት የሚሰጡ አልጠፉም።     

በተያያዘ ዜና በተለያዩ ቦታዎች ሲካሄዱ የነበሩት ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እንደገና ተቀስቅሰው እየተካሄዱ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በምዕራብ ወለጋና በምዕራብ ሸዋ እንዲሁም በባሌ የተለያዩ ከተሞች በሁለተኛ ደረጃ በዩነቨርስቲ ተማሪዎች አማካይነት የሚካሄደው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

 

 

Ø የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀን 2008 ዓም አዲሱን የፈርንጆች አዲስ ዓመት አስመልክቶ በራዲዩና በቴሌቪዥን ለሕዝባችው ባደረጉት ንግግር  በቅርቡ በተካሄደው የውሳኔ ሕዝብ ድምፅ አብዛኛው ዜጋ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ፍላጎት ያሳየ መሆኑን ጠቅሰው የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት  ለሶስተኛ ጊዜ በሚቀጥለው ምርጫ የሚወዳደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የተደረገው የሕግ መንግስት ማሻሻያ ወቅቱን የጠበቀና አንደነትን አጠናክሮ በማስቀጠል በኩል ከፍተኛ አስተዋጾ ሊያደርግ የሚችል ነው ብለዋል። ሚስተር ካጋሚ በሚቀጥለው ምርጫ ተወዳደረው አሁን ባለው ሕግ መንግስት መሰረት ለሌላ ሰባት ዓመት ያህል በስልጣን ላይ ሊቆዩ የሚችሉ ሲሆን ከዚያ በኋላ በአዲሱ ህገ መንግስት መሰረት ለሌላ እያንዳንዳቸው አመስት አመት ለሆኑ የስልጣን ዘመን ሊወዳደሩ የሚችሉ መሆናችው ታውቋል። ወደፊት በሚደረጉት  ምርጫዎች ሁሉ ካሸነፉ በጠቅላላው ከእንግዲህ ወዲያ ለአስራ ሰባት ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆዩ እንደሚችሉ ይገመታል። ካጋሚ በምርጫ ወደ ስልጣን የመጡት በ1995 ሲሆን እስካሁን ለአስራ ሶስት አመታት ያህል በስልጣን ላይ ቆይተዋል። እድሜ ከሰጣቸውና የሚቀጥሉትን ምርጫዎች ካሸነፉ በጠቅላላው ለሰላሳ አመታት በስልጣን ይቆያሉ ተብሏል። በቅርቡ በርካታ የሆኑ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች የስልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም ሕግ መንግስቱን ማሻሻላቸው ይታወቃል።

 

Ø ጎረቤት በሆነችው ብሩንዲ ውስጥም ፕሬዚዳንቱ ከሕግ ውጭ ለሶስተኛ ጊዜ በስልጣን ላይ ለመቆየቱ ያደረጉት ሙከራ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶ አገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየወሰዳት ይገኛል። ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀን 2008 ዓም በዋና ከተማዋ በቡጁምቡራ በተላያዩ ቦታዎች በፈነዱ ቦምቦች አንድ ሰው ሲሞት በርካታ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል። በአንድ የገዥው ፓርቲ አባላት ያዘወትሩበታል በተባለው ቡና ቤት ላይ የተጣለው ቦምብ አንድ ሰው መግደሉና በርካታዎችን ማቁሰሉ የታወቀ ሲሆን ሌሎች ሶስት የፖሊስ አባላት በሌሎች ቦታዎች ላይ በተጣሉ ቦምቦች የቆሰሉ መሆናችውን ለማወቅ ተችሏል።

 

Ø አዲስ የተመረጡት ከሁለት ወራት በፊት የተመረጡት የአይቮሪ ኮስት ፕሬዚዳንት አላሳኔ ኩዋታራ በፈረጆቹ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ባደረጉት ንግግር ለሶስት ሺ አንድ መቶ (3100) እሥረኞች የእስራት ቅናሽ ያደረጉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት የሚፈቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከአምስት ዓመት በፊት በአገሪቱ ውስጥ የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ ለወራት በዘለቀው ብጥብጥ ሶስት ሺ የሚሆኑ ዜጎች የተገደሉ እና በርካታዎቹ የተጎዱ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል እና በፈረንሳይ ወታደሮች አማካይነት መረጋጋት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል። ከግጭቱ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች መያዛቸው የሚታወስ ሲሆን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጋብጎም በቁጥጥር ስር ውለው ፍርዳቸውን ከአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት እየተባበቁ ናቸው።

 

Ø በቅርቡ በሁለቱ የሊቢያ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የተፈረመው እርቅ በተለይ በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘው የሊቢያ መንግስት ምክር ቤት አባላት ተቃውሞ እንደገጠመው የሚታወቅ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት የእርቁን ሀሳብ እንዲቀበሉ ግፊት ለማደረግ አንድ የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣን ወደ ምስራቅ ሊቢያ የሄዱ መሆናቸውን ከስፍራው ከተገኘ ዜና መረዳት ተችሏል። ማርቲን ኮብለር የተባሉት የተመድ ልኡክ ሸሃት በተባለች ከተማ ተገኘተው ከመንግስት ባለስልጣኖችና ከምክር ቤቱ መሪ ጋር ተገናኝተው የተወያዩ መሆናቸው ታውቋል።  የተመድ የእርቅ ሀሳብ ከሁሉም በኩል የተውጣጣ 17 አባላት የሚገኙበት የመንግስት አካል እንዲቋቋም የሚጠይቅ ሲሆን ከሁለቱም ተጻራሪ ኃሎች በኩል ያሉ ባለስልጣኖች  የፈረሙት ቢሆንም  የማይናቅ ቁጥር ያላቸው የምክር ቤት አባላት የተቃወሙት መሆናችው ይታወቃል። የልዑኩ ጥረት ምን ያህሉን ሊያሳምን እንደሚችል እስካሁን ግልጽ አይደለም።

 

Ø በግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ የነበረ አንድ የሕዝብ ማመለሻ ጀልባ ወንዝ ውስጥ በመስመጡ ሁሉም ተሳፋሪዎቹ ህይወታቸውን ሳያጡ አይቀርም የሚል ስጋት ተፈጥሯል። የአደጋ መከላከያ ሰራተኞች እስካሁን ድረስ የአስራ አራት ሰዎች አስከሬን ከውሃ ውስጥ፡አግኝተው ያወጡ ሲሆን ፍለጋው የቀጠለ መሆኑን የግብጽ የመንግስት ራዲዮ ገልጿል። ጀልባዋ ከተገለበጠች በኋላ ህይወት የማትረፉ ስራ ውዲያውኑ ባለመጀመሩ በርካታ ህዝብ በቦታው በመገኝት ተቃውሞውን የገለጸ ሲሆን ፖሊስ አመጹ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይሆን እርምጃ ወስዷል ተብሏ። የግብጽ መንግስት የሞት አደጋ ለደረሰባችው ቤተሰቦች የ1300 ዶላር ካሳ ለመክፈል ቃል የገባ ሲሆን የአካል ጉዳት ለደረሰበት ደግሞ 255 ዶላር የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል። የአደጋው መነሻም ሆነ በጀልባዋ ላይ ምን ያህል ሰዎች እንደነበሩ እስካሁን የተሰጠ መረጃ የለም።

 

 

 

 

 



ታኅሣሥ 21 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአሜሪካው ኋይት ሃውስ ስር የሚገኘው የብሔራዊ ጸጥታ ካውንስል (National Security Council) ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ (Ned Price) ረቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ የወያኔ መንግስት ስመ ጥፉውን የጸረ ሽብር አዋጅ በመጠቀም ጋዜጠኞች ማሰሩን እንዲያቆም ጠይቀው የተያዙት እስረኞች ባስቸኳይ መፈታት አለባቸው ብለዋል። ቃል አቀባዩ የታሰሩትን ጋዜጠኞች በስም ባይጠቅሱም በተለያዩ ቦታዎች አመጽ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ከወትሮ በተለየና ጠንከር ባለ ቋንቋ የአሜሪካንን ተቃውሞ ማሰማታቸው ተጽእኖ ለማሳደር ነው የሚል ግምት የወሰዱ አሉ። ቃል አቀባዩ በቅርቡ በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው ርምጃ የአሜሪካንን መንግስት ያሳሰበ መሆኑን ገልጸው የወያኔ መንግስት ባስቸኳይ ጋዜጠኞችንም ሆነ ሌሎች መብታቸውን ተጠቅመው ሀሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ የተያዙ እስረኞች ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ይህ የአሜሪካ አቋም እንደሁልጊዜም ከመግለጫ ያለፈ እርባና እንደማይኖረው በመግለጽ ብዙ ሰዎች ግምታቸውን ይሰጣሉ።፡

 

Ø የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሀማዱ ቡሃሪ  ረቡዕ ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ከሁለት ዓመት በፊት ቦኮሃራም በተባለው አሸባሪ ድርጅት ተጠልፈው የተወስዱት ወደ 200 የሚደርሱ የሴት ተማሪዎችን ሁኔታ የማያውቁ መሆናቸውን ገልጸው ልጃአገረዶቹን ለማስፈታት ከአሸባሪው ድርጅት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆናችውን ተናግረዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት 276 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ቤታቸው ተጠልፈው የተወሰዱ መሆናቸውና 76 የሚሆኑት ወዲያውኑ አምልጠው ሲመለሱ ወደ 200 የሚጠጉት  እስካሁን የትእንዳሉ ሳይታወቅ መቆየቱ ይታወሳል። ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ ልጆቹ የት እና በምን ዓይነት የጤንነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚያሳውቅ ምንም ዓይነት መረጃ ያልደረሳቸው መሆኑን ገልጸው የታሰሩትን ለማስፈታት ከእውነተኞቹ የቦኮ ሃራም ድርጅት መሪዎች ጋር መደራደር የሚፈልጉ መሆኑን ገልጸዋል። ድርድሩን ለመጀመር ግን በቅድሚያ እውነተኛ የድርጅቱ መሪዎች መሆናቸው መረጋገጥ አለበት ብለዋል። ቦኮሃራም ከቴክኒክ አንጻር ተሸንፏል በማለት ባለፈው ሳምንት ሚስተር ቡሃሪ መግለጫ የሰጡ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ከዚያ ወዲህ  ታጣቂዎቹ ያካሄዷቸው ተከታታይ ጥቃቶችና ያደረሱት ጉዳት የፕሬዚዳንቱን መግለጫ ተአማኒነት አጠራጣሪ አድርጎታል።   

 

 

Ø በደቡብ አፍሪካ የአካባቢው ንጉስና የኔልሰን ማንዴላ የቅርብ ዘመድ የሆኑት  ቡየለካያ ዳሊንዴይቦ ዘጎችን ጠልፎ በመውሰድና መኖሪያ ቤቶችን በማቃጠል ወንጀል ከተከሰሱ በኋላ ለሰሩት ወንጀል 12 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው ወደ እስር ቤት የገቡ መሆናቸው ተነግሯል። ንጉሱ ወደ እስር ቤት የተላኩት ቀደም ብሎ የተፈረደባቸውን ፍርድ ይግባኝ በማለት ያደረጉት ክርክር ውድቅ በመደረጉ ነው። የክሱ መነሻ ከ20 ዓመታት በፊት ከተከታዮቻቸው ጋር በነበራቸው ግጭት ሲሆን የሰዎችን መኖሪያ ቤት በማቃጠል ሶስት ወጣቶችን በማስደብደብና የአንድ ተቃዋሚ የነበረ ግለስብ ሚስትና ልጆችን በመጥለፍ ወንጀል ተከሰው ነበር። የአምሳ አንድ ዓመት ዕድሜ ያላቸው ንጉስ  በአካባቢው የቆየ ባህል መሰረት ንጉስ ተብለው የተሰየሙት በ1982 ዓም ሲሆን 700 ሺ የሚሆኑት የደቡብ አፍሪካ ዜጎች ንጉስነታቸውን ተቀብለው በስራቸው የሚተዳድሩ መሆኑ ታውቋል። በደቡብ አፊሪካ  10 የሚሆኑ በይፋ እና በሕግ የታወቁ የአካባቢ ንጉሶች ይገኛሉ።

 

Ø 20 ዓመት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ በተፈጸመው ከፍተኛ የሆነ የህዝብ እልቂት ላይ ተሳትፈው ነበር የሚባሉ አንድ የፔንቴኮስታል ቄስ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት  የእድሜ ልክ እስራት የፈረደባቸው መሆኑ ተነገረ። ቄሱ ከአምስት ዓመት በፊት ኡጋንዳ  ውስጥ በጥርጣሬ ተይዘው ታንዛኒያ ውስጥ ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታውቋል። በታንዛኒያ  በሩዋንዳው እልቂት ጉዳይ ብያኔ ለመስጠት የተቋቋመው ኮሚቴ በዚህ ወር መጀመሪያ ስራውን አብቅቶ ሲዘጋ ቄሱ ወደሩዋንዳ እንዲዛወሩ ተደርጎ ነበር።  በቱሲዎች የሚመራው የሩዋንዳ መንግስት ጉዳዩን ለማየት አይችሉም የሚል መከራከሪያ ቢያቀርቡም ወደ ሩዋንዳ ተዛውረው ክሳቸው ሊቀጥል ችሏል።  በክሱ መሰረት በ1987 ዓም ከዋና ከተማ ከኪጋሊ ዳርቻ ባለና ቄሱ በሚያስተዳድሩት አንድ ቤት ክርስቲያን ዙሪያ የ2000 የሩዋንዳ ዜጎች ሬሳ መገኘቱና ለግድያ ቀሱ ተባባሪ እንደነበሩ በመረጋጡ በአስራ ሁለት አመት እስራት እንዲቀጡ ፍርዱ ቤቱ የወሰነ ሲሆን ጠበቃቸው ብይኑን ይግባኝ እንደሚል ገልጿል። በሩዋንዳው እልቂት ተሳታፊ ነበር የተባለ ሌላ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ባለፈው ወር በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መያዙ ይታወሳል።

 

Ø ቅርቡ በቡርኪና ፋሶ በተደረገው ምርጫ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የካምፒወሪ ቀኝ እጅ የነበሩት ሚስተር ሳሊፍ ዲያሎ የብሄራዊ ምክር ቤት መሪ ሆነው መመረጣቸው ተነገረ። ከአንድ ቀን በፊት ሚስተር ክርሲያን ካቦሬ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል። ሁለቱ ሰዎች የቀድሞ ፕሬዚዳንት አገልጋዮችና ባለስልጣኖች የነበሩ ቢሆንም ከሁለት አመት በፊት ከገዥው ፓርቲ ራሳቸውን በማግለል የሕዝብ እድገት እንቅስቃሴ (Movemen of People Progress) የተባለ አዲስ ፓርቲ አቋቁመው በተቃዋሚነት መንቀሳቀሳቸው ይታወቃል።  ሚስተር ዲያሎ ለምክር ቤቱ መሪ ሆነው የተመረጡት 127 መቀመጫ ካለው ምክር ቤት ውስጥ 78 ድምጽ በማግኘት ሲሆን ከተመረጡ በኋላ ባደረጉት ንግግር የምክር ቤት አባሎች ሙስናንና የዝምድና አሰራርን እንዲዋጉ ጥሪ አድርገዋል። በአሁኑ ወቅት  የሁለቱ ሰዎች በከፍተኛ ስልጣን ላይ መቀመጥ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ደጋፊዎችንም ሆነ ተቃዋሚዎችን በማቀራረብ በአገሪቱ ውስጥ ምቹ የፖሊቲካ ሁኔታ ሊፈጥር ይችላል የሚል አስተያየት የሚሰጡ አሉ።






ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለህግ አውጭው ምክር ቤትና ለፕሬዚዳንቱ የስልጣን ቦታ ብሔራዊ ምርጫ መደረጉን ከአካቢብው የተገኝው መረጃ ይገልጻል። ለፕሬዚዳንትነት ስልጣን የሚወዳደሩት ሰላሳ ሰዎች ሲሆኑ ከእኒዚህ ውስጥ ሶስቱ ቀዳሚ ቦታ እንዳላቸው ታውቋል። የተባበሩት መንግስታት የሰላም አሰባሪ ኃይል አባሎች በየምርጫ ጣቢውያውና በአውራጎዳናዎች ተሰማርተው ጸጥታውን ሲያስከብሩ የቆዩ ሲሆን በአንዳንድ  ቦታዎች መዘግየት ቢኖርም ብዙዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች በታቀደላቸው ጊዜ ተከፍተው መራጩን ሲያስተናግዱ ውለዋል። ከአምስት ሚሊዮን ሕዝብ መካከል ለምርጫ የተመዘገበው 1.8 ሚሊዮን ነው የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ፡ድምጹን የሰጠው ሰው ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ እስከ አሁን አልታወቀም። ለፕሬዚዳንትነት ቦታ ከሚወዳደሩት መካከል አሸናፊ የሚሆነው ከድምጹ ከአምሳ ከመቶ በላይ ያገኘ ብቻ ነው። ባሁኑ ምርጫ ቀዳሚ ሆነው ከሚወዳደሩት መካከል ሊያሸንፍ ይችላል የሚለው ግምት የመነመነ በመሆኑ ምናልባት ሁለተኛ ዙር ምርጫ ሳይካሄድ አይቀርም የሚሉ በርካታ ናቸው።  የምዕራብ አፍሪካ ሪፐብሊክ በክርስቲያን እና በእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል በተካሄዱ ግጭቶች በርካታ ሰዎች የሞቱ እና የተጎዱ ሲሆን  ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎችም ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሰደዳቸው ይታወቃል።

 

Ø ባለፈው ሰኞ ታኅሣሥ 18 ቀን በዩጋንዳ የሰላም ውይይት ሲያደርጉ የነበሩ የብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎች አለምንም ውጤት ስብሰባውን ያጠናቀቁ ሲሆን ቀጣዩን ስብሰባ ለማድረግ በመጨው ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓም በታንዛኒያ ከተማ አሩሻ ውስጥ  ለማድረግ  የታቀደ መሆኑን አደራዳሪዎቹ የዩጋንዳ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። የብሩንዲ መንግስት ተወካዮች በስበሰባው ወቅት ከመፈንቅለ መንግስት አድራጊዎች ጋር ውይይት ለማካሄድ የሚያስቸግራችው መሆኑን መግለጻቸው የተጠቆመ ሲሆን የሚቀጥለው ስብሰባው መች ሊደረግ እንደሚችል ስምምነት ላይ አለተደረሰም በማለት መግለጫ ሰጥተዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መሪ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ በሚቀጥለው ስብሰባ ላይ ያልተገኘ ወገን በአፍሪካ ኅበርት አገሮች ማዕቀብ የሚጣልበት መሆኑን  ተናግረዋል። የድርጅቱ ኮሚሽን መሪ ሚስስ ዙማ በሰጠቱ መግለጫ የሚጣለው ማዕቀቡ ምን ሊሆን እንደሚችል ባይገልጹም በብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የሚደረገውን ድርድር የሚያደናቅፍ፤ በታጣቂ ኃይሎች አማ]ካይነት ወታደራዊ ጥቃቶችን በመንግስት ንብረቶች ላይ የሚፈጽም እና እንዲሁም ወደ እርቅ ጠረጴዛ ላይ ለመምጣት ፈቃደኛ የማይሆን ወገን በሙሉ ማዕቀብ የሚጣልበት መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ኅብረት  5000 የሰላም አሰባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ መወሰኑና በማናቸውም መንገድ ለመላክ የቆረጠ መሆኑን  በተደጋጋሚ መግለጹና ይህንን የብሩንዲ መንግስት መቃወሙ ይታወሳል:: ዛሬ ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም  ደግሞ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት እንክሩንዚዛ ለብሩንዲ ሕዝብ በራዲዮና በቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ አገራቸው የሚላክ ከሆነ የአገሪቱን ሉዓላዊነት እንደደፈረ ወራሪ ኃይል ተቆጥሮ ውጊያ ሊገጥመው እንደሚችል ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው በብሩንዲ ህገ መንግስት መሰረት የውጭ ኃይል ወደ አገሪቷ ሊገባ የሚችለው በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ተዋጊ ኃይሎች ሲጠይቁ ወይም በአግሪቷ ላይ በሕዝብ የተመረጠና ተቀባይነት ያለው መንግስት ከሌለ ብቻ ነው። ህጋዊ መንግስት ባለበት ሁኔታ ወደ አግሪቱ የሚገባ ኃይል ሁሉ በጠላትነት የሚታይ ስለሆነ እንዋጋዋለን ብለዋል።     

 

Ø ባለፈው የፈረንጆች ዓመት በዓለም የተለያዩ ቦታዎች 110 ጋዜጠኞች የተገደሉ መሆናቸውን ድንበር የለሽ ጋዜጠኞች የተባለው ድርጅት ማክሰኞ ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም ባወጣው አመታዊ  ዘገባ ገልጿል። 67 የሚሆኑ ጋዜጠኞች በስራ ላይ በነበሩበት ወቅት መገደላቸውን ድርጅቱ በዘገባው ላይ የገለጸ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 11 በኢራክ 10 በሶርያ እንዲሁም ደግሞ በፈረንሳይ አገር በቻርሊ አብዱ መጽሔት አዘጋጆች ላይ በደረሰው ጥቃት ሳቢያ 8 ጋዜጠኞች  መገደላቸውን ዘግቧል። 43 የሚሆኑ ጋዜጠኞች አገዳደላቸው ግልጽ ባልሆኑ ምክንያት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሞቱ መሆናችውን ድርጅቱ ባወጣው ዘገባ ገልጿል። የተገደሉት ጋዜጠኞች ቁጥር ከሌሎች ጊዜዎች ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ መሆኑ የሚያመለክተው ጋዘጠኖች በአደጋ ሳይሆን ሆን ተብሎ እንደተገደሉ የሚያመልክት የድርጅቱ ዘገባ የጠቀሰው ሲሆን የአብዛኞቹ ገዳዮች  ደግሞ መንግስታዊ ያልሆኑ የታጠቁ ክፍሎች መሆናችው በዘገባው ተካቷል።  ድርጅቱ  የጋዘጠኞችን ህይወት ለመጠበቅ በዓለም አቀፍ ደረጃ አስፈላጊው እርምጃ መወሰድ እንዳለበትም አሳስቧል።   



ታኅሣሥ 19 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የጋዜጠኞችን ደህንነት ለመንከባከብ የተቋቋመው ሲፒጄ የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ትናንት ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም. ባወጣው መግለጫ  በቅርቡ በወያኔ አገዛዘ የተያዙት ሁለት ጋዜጠኞች ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም በወያኔ አገዛዝ ቁጥጥር ስር የዋለው የኦሮሞ ራዲዮና ቴሌቪዥን ስርጭት ዜና አንባቢ የሆነው አቶ ፊቃዱ ሚርካና እና አርብ ታኅሣሥ 15 ቀን የተያዘው የነገረ ኢትዮጵያ አዘጋጅ አቶ ጌታቸው ሽፈራው በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው የታሰሩት በቅርቡ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ስለተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ ዜና ዘግባችኋል በሚል ክስ ሲሆን የጋዜጠኖች ተንከባካቢ ድርጅቱ ባስቸኳይ እንዲለቀቁ በመግለጨው ጠይቋል። መግለጫው አክሎ መሰረታዊ ሕዝብ መረጃ የማግኘት መብቱና ሌሎችም መሰረታዊ የሆኑት ሰብአዊ መብቶች ሳይከበሩ ስለ እድገት ማውራት ብዙ ትርጉም የሌለው መሆኑ በመግለጽ በወይኔ አገዛዝ ላይ ወቀሳ አቅርቧል። በተጨማሪ ድርጅቱ በመግለጫው ከሁለት ወራት በፊት በፍርድ ቤት ነጻ የሆኑት አራቱ የዞን 9 ጦማርያን በአቃቤ ህጉ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት እንደገና ፍርድ ቤት መቅረባቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፉ የጤና ድርጅት  ደብሊው ኤች ኦ (WHO) ጊኒ ከኢቦላ በሽታ ነጻ መሆኗን የሚያረጋግጥ ምስክርነት የሰጠ መሆኑ ተረጋገጠ። ለሁለት አመት ጊዜ በበሽታው ሲሰቃይ የነበረውና በግንኙነትና በኢኮኖሚ በኩል ከፍተኛ ችግር የገጠመው የጊኒ ሕዝብ ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከበሽታው ነጻ መሆኑን ማረጋገጫ በማግኘቱ በርችትና በዘፈን ደስታውን ደስታውን ይገልጻል በሚል እየተጠበውቀ  ነው። ባጠቃላይ 2ሺ 5 መቶ የሚሆኑ የጊኒ ዜጎች በበሽታው ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በሲየራ ሊዮንና በላይቤሪያ 9 ሺ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።  ሲየራ ሊዮን ባለፈው ወር ከኢቦላ ነጻ መሆኗን የሚያበስር ማረጋገጫ ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ያገኘች መሆኗ የሚታወስ ሲሆን ባለፈው መስከረም ወር ነጻ መሆኗ ማረጋገጫ በተሰጣት በላይቤሪ ግን አዳዲስ የኢቦላ በሽተኞች መገኝታቸው ታውቋል።

 

Ø ባለፈው መስከረም ወር በቡርኪና ፋሶ የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ታስረው የሚገኙትን ጄኔራል ዲየንዴሬን እና ጓደኞቻቸውን ለማስፈታት ጥረት አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ 20 ወታደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታወቀ። ወታደሮቹ ሰኞ ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም ጄኔራሉንና ሌሎች በመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ የተያዙትን እስረኞች በእስር ቤቱ ላይ ወረራ በማካሄድ ያቀዱት ሴራ ተጋልጦ ወደ 20 የሚጠጉ ወታደሮች  በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆናችው ታውቋል። በቅርቡ የአገሪቷ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ሚስተር ካቦሬ ስለወታደሮቹ መያዝ ባደረጉት ንግግር ቀደም ብለው በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሁሉ ፍርዳቸውን ያገኛሉ። እንዲህ ዓይነት የወንጀል ሙከራ እቅዱ ገና ተግባር ሳይውል ሊጋለጥ እንደሚችል ሁሉም ሊገባው ይገባል ብለዋል። በጥቅምት ወር ተሞክሮ በነበረው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በጠቅላላው 57 ሰዎች የተከሰሱ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ ጄኔራሉን ጨምሮ 20 ዎቹ  የቀድሞ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደራዊ ተቋም አባላት መሆኗቸው ታውቋል።

 

Ø ሰኞ ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ግዛት በማዳጋሊ በሚባለው ከተማ ሁለት የሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 25 ሰዎች መግደላቸው ታወቀ። በተጨማሪ አዋሳኝ በሆነው የቦርኖ ግዛት  የአሸባሪው ቡድን አባላት  ባካሄዱት የተለያዩ ጥቃቶች 30 ሰዎች መሞታችውና ከ100 በላይ የሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ከቦታው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ባለፈው ሳምንት የናይጄሪው ፕርዚዳንት  ከቴክኒክ አንጻር ቦኮ ሃራም ተደምስሷል የሚል መግለጫ መስጥታቸው የሚታወስ ሲሆን የሰሞኑ የአሸባሪው ድርጅት ተከታታይ  ጥቃቶች  ድርጅቱ አሁኑም ህልውና እንዳለው  የሚገልጽ መልእክት ለማስተላለፍ ነው ተብሏል።

 

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 19 ቀን 2008 ዓም ከ21 አመት በፊት በሩዋንዳ ውስጥ የአንድ ከተማ ከንቲባ የነበረ ግለሰብ  በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብሰበው የነበሩ ከ400 በላይ የሆኑ የቱሲ ተወላጆችን  ማስገደሉ በመረጋገጡ የጀርመኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት ፈርዶበታል። የዛሬ ሁለት አመት ግለስቡ በሰራው ወንጀል በዝቅተኛ ፍርድ ቤት የአስራ አራት አመት እስራት ፈርዶበት የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም የፌዴራል አቃቤ ህጉ ቅጣቱ ከሰራው ወንጀል ጋር ተመጣጣኝ አይደለም በሚል ምክንያት ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበው ይግባኝ ግለሰቡ የእድሜ ልክ እስራት ሊፈረድበት ችሏል።     




ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎች ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፕላ ውስጥ የእርቅ ድርድር ለማድረግ መሰብሰባቸው ተገለጸ። የብሩንዲው መንግስት ተወካዮች የሚመራው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሲሆን የተቃዋሚው ክፍል የህብረት ድርጅት መሪዎች ተቃዋሚውን ክፍል እንደሚወክሉ ታውቋል። የሲቪክ ማህበረ ሰብ አባላትና የሃይማኖት ድርጅት መሪዎችም በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል። ስብሰባውን የሚመሩት የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮወሪ ሙሰቨኒ ሲሆኑ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ባሰሙት ንግግር ሁለቱ ወገኖች ግልጽ ውይይት አድርገው እንዲስማሙና ሕዝባቸውን ከእልቂት እንዲያድኑ ተማጽነዋል። ተቃዋሚውን በመወከል በስብሰባው ላይ የተገኙት ተደራዳሪዎች ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ እንዲካሄድ ብሩንዲ ውስጥ በመንግስት ወታድሮች የሚደረገው ግድያ መቆም ያለበት መሆኑን ገልጸው ሕዝብ እየሞተ ድርድር ማካሄድ አይቻልም ብለዋል። እስካሁን ድረስ የብሩንዲ መንግስት ተቃዋሚውን አሸባሪ ናቸው ብሎ በመሰየም ድርድር ለማካሄድ ፈቃደኛ እንዳልነበር ይታወቃል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 5 ሺ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነውን ውሳኔ የብሩንዲ መንግስት ወራሪ ኃይል ነው በማለት የማይቀበለው መሆኑን ቢገልጽም የአፍሪካ ህብረት በማናቸውም መንገድ የሚልክ መሆኑን አስታውቋል።

 

Ø እሁድ ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ምሽት ላይ በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ ካለችው ከማይዱጉሪ ከተማ አጠገብ በምትገኝ አንዲት መንደር ውስጥ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ባካሄዱት ጥቃት 21 ሰዎች መግደላቸውንና 91 ሰዎች ማቁሰላቸውን የአካባቢው ባለስልጣኖች ለዜና ምንጮች ከሰጡት መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ታጣቂዎች በሶስት ከባድ መኪናዎች ላይ ተጭነው ወደ መንደሯ በመግባት በእሩምታ ተኩስ ባደረሱት ጥቃት በርካታ ሰዎች ሊሞትና ሊቆስሉ ችለዋል። በአካባቢ የነበረው የመንግስት ወታደሮች ባደረጉት የአጸፋ ተኩስ 10 ታጣቂዎች የገደሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።  ሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን ጠዋት አንዲት አጥፍቶ ጠፊ ወደ መስጊድ ለመግባት የሚካሄድውን ፍተሻ ለማለፍ ሰልፍ ተሰልፋ እንዳለች   ባፈነዳችው ቦምብ አንደ ሰው ገድላ ሌሎች ስድስት ሰዎች ያቆሰለች መሆኗን በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦኮሃራም ከቴክኒክ አንጻር ተደምስሷል ይበሉ እንጅ አሸባሪው ቡድን አሁንም ጉዳቶችን እያደረሰ መሆኑ ይታያል።  

 

Ø በሰሜን ምስራቅ ኬኒያ ትናንት እሁድ ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓም የታጠቁ ሰዎች በሰነዘሩት ጥቃት ሁለት ፖሊሶች የተገደሉ መሆናቸውንና ሌሎች ሁለት ፖሊሶች መቁሰላቸውን የኬኒያ የቀይ መስቀል ድርጅት ከአካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም በአካባቢው በተደጋጋሚ ጉዳት ያደረሰው አልሸባብ እንደሆነ ይጠረጠራል። ባለፈው ሳምንት ላይ የኬኒያ ፖሲሶች አልሸባብ በአልካይዳና በአይሲስ ደጋፊነት እየተከፋፈለ መሆኑን ገልጸው አክራሪዎቹ በኬኒያ ላይ አዲስ የጥቃት ዘመቻ ሊከፍቱ የሚችሉ መሆናቸውን ማስጠንቀቃቸው  ይታወሳል። የአይሲስ ደጋፊ የሆኑት በኬኒያ ሰሜን ምስራቅ በማንዴራ ግዛት ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ የደረሱበት መሆናቸውን ገልጸዋል።

 

Ø ባለፈው ቅዳሜ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም የቢኒንን ጠቅላይ ሚኒስትር ይዛ የነበረች አንዲት ሄሊኮፕተር ተከስክሳ  የወደቀች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አለምንም ጉዳት ከአደጋው ሊድኑ የቻሉ መሆናቸው ታውቋል። አውሮፕላኑ ለምን እንደወደቀ እየተመረመረ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አባትን ጨምሮ በሂሊኮፕተሩ ውስጥ የነበሩት ሰዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ቀርተዋል። የቤኒንና የፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው የቤኒኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የቀድሞ የባንክ ሰራተኛ ሲሆኑ በሚቀጥለው የካቲት በሚደረገው የአገሪቱ ምርጫ ለፕሬዚዳንትነት ይወዳደራሉ ይባላል።



ታኅሣሥ 16 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በሱዳን በአልጋዳሪፍ የክልል አስተዳድር የአንድ አካባቢ የምክር ቤት ተወካይ የሆኑ ሰው ለሱዳን ዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ ባለፈው ወር ብቻ በድንበር አካባቢ 45 ሱዳናውያን በታጠቁ ኢትዮጵያውያን ተግድለዋል ብለዋል። በርካታ የሱዳን ዜጎች ታፍነው የተወሰዱ መሆኑን ገልጸው የሱዳን ገበሬዎችን መግደል፤ ማሰርና፤ ከእርሻ ቦታቸው ላይ ማስነሳት የተለመደ ነው በማለት ተናግረዋል።  ባለፈው ወር የሱዳን ባለስልጣኖች ኢትዮጵያውያንን አባርረን  100 ሄክታር የሱዳን መሬት መልሰን ተቆጣጥረናል በማለት ያስራጩት ዜና ሀሰት ነው በማለት አስተባብለዋል። “ከ2 ሚሊዮን ኤከር በላይ የሚሆነውን የሱዳን የእርሻ መሬት ተወስዶ የእኛ መንግስት አንቀላፍቷል” በማለት ቅስቀሳ አዘል ንግግር አድርገዋል። በወሰን አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በወያኔ ወታደሮች ጥቃትና ተጽእኖ የሚደርስባቸውን ተጽእኖ ተቋቁመው መሬታችውን ለማስመለስ የሞትና የሸረት ትግል እያካሄዱ መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን በርካታ መስዋእትነትም እንደከፈሉ ይታወቃል። የወያኔ አገዛዝ የሱዳን መንግስት የጠየቀውን ሰፊ የኢትዮጵያ  መሬት ለማስርከብ መስማማቱ ቀደም ብሎ የተገለጸ ሲሆን አንድ የወያኔ ከፍተኛ የመልክተኞች ቡድን  ሐሙስ ታኃሣስ 13 ቀን 2008 ዓም ማታ ብሉል ናይል በሚባለው የሱዳን የአስተዳደር ክልል የገባ መሆኑ ከአካባቢው ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ወያኔ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለማስረከብ ያቀደውን እቅድ በመቃወም በርካታ ወገኖች ተቃውሞ ያሰሙ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን ኢሕአፓና ሌሎች የፖሊቲካና የሲቪክ ድርጅቶ ለተመድ ዋና ጸሐፊ የተቃውሞ ደብዳቤ መጻፋቸው ይታወሳል። 

 

Ø የአፍሪካ ኅብረት ወደ ብሩንዲ የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የወሰነው ውሳኔ የብሩንዲ መንግስት እንዲቀበል በድጋሚ ደብዳቤ የጻፈ መሆኑ የድርጅቱ ጽህፈት ቤት በትናንትናው ዕለት በይፋ ገልጿል። ድርጅቱ 5000 የሚሆኑ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነው አገሪቱ ወደ አጠቃላይ የእርስ በርስ ጦርነት እንዳትገባ ለመከላከልና  የሕዝቡን ደህንነት  ለመጠበቅ እንጅ ለሌላ ድብቅ ለሆነ ዓላማ እንዳልሆነ የድርጅቱ ባለስልጣኖች ተናግረዋል። የብሩንዲ መንግስት የአፍሪካ ኅብረት ለመላክ ያሰበውን የሰላም አስከባሪ ኃይል ወራሪ ኃይል ነው በማለት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ውሳኔን ውድቅ ማድረጉ ይታወቃል። በብሩንዲ ውስጥ ችግር ከተፈጠረ ካላፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ወዲህ በእርስ በርስ ግጭት  ከ400 በላይ ሰላማዊ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውና  በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ለስደት መዳረጋቸው የሚታወቅ ሲሆን። በቅርቡ ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀስ አንድ የታጠቀ የአማጽያን ቡድን ህልውናውን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

 

Ø የደቡብ ሱዳን መንግስት ያሉትን አስር የአስተዳደር ክልሎች ወደ 28 የአስተዳድር ክልሎች ለመለወጥ የወሰነው ውሳኔ በርካታ ተቃውሞ እየደረሰበት መሆኑ ተገለጸ።  የአስተዳድር ክልሎችን ለመለወጥ ስልጣን ያለው አካል የህግ አውጭ ምክር ቤቱ እንጂ አስተዳደሩን የያዘው መንግስት ስላልሆነ የሳልቫኬር መንግስት የወሰነው ውሳኔ ህገ መንግስቱን ይጥሳል ተብሏል። ቀደም ብሎ በአፍሪካ ህብረት አማካይነት በደቡብ ሱዳን መንግስትና በአማጽያኑ መካከል የተደረገው ስምምነት መሰረት ያደረገው አስር የአስተዳደር ክልሎችን በመሆኑ የአሁኑ የመንግስቱ ውሳኔ ስምምነቱን ሊያፈርስ ይችላል የሚል አስተያየትም እየተሰጠ ነው። የአማጽያኑ የአመራር አካሎች በተናጠል የመንግስቱን ውሳኔ የተቃወሙት ሲሆን ምን ዓይነት እርምጃ እንደሚወስዱ እየተመካከሩ ነው ተብሏል። ስምምነቱን በተግባር ለማስፈጸም ባለፈው ሰኞ በ150 የአማጽያን ተወካዮች የሚገኙበት ቀዳሚ  ቡድን ጁባ የገባ መሆኑ ይታወሳል። በተያያዘ ዜና በደቡብ ሱዳን 3.1 ሚሊዮን ሕዝብ በከፍተኛ የምግብ ችግር ላይ መሆኑን የተመድ አካል የሆኑት  የምግብና የእርሻ ድርጅት (FAO) የሕጽናት ተንከባካቢ ድርጅት (UNICEF) እና የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል። ባሁኑ ወቅት ቢያንስ 30 ሺ የሚሆኑት በምግብ እጥረት ምክንያት የሞት አደጋ ሊያጋጥማችው የሚችል ሲሆን ባጠቃላይ 3.1 ሚሊዮን የሚሆኑት በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተጠቁሟል።




ታኅሣሥ 15 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በናይጄሪያ ደቡብ ምስራቅ በምትገኘው ኒዊ በምትባለው ከተማ አንድ ቡታ ጋዝ የጫነ ቦቴ በጋዝ ማከፋፊያ ፋብሪካ አጠገብ በመፈንዳቱ ምክንያት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መጎዳታቸው ተገለጸ። ከሞቱት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ የጋዝ ዕቃቸውን ለማስሞላት የተሰለፉ ሲሆን ሰራተኞችና በአካባቢው የሚኖሩ ነዋሪዎች ይገኙበታል። አንዳንድ ዘገባዎች የሞቿቹን ቁጥር ከ35 በላይ የሚል መረጃ ሲያቀርቡ ሌሎቹ ከ100 በላይ እንደሆኑ ይገልጻሉ።  በአካባቢው የሚገኙ የዓይን እማኞች ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ እሳቱ ሊያያዝ የቻለው የቦቴው ሞተር ገና ሳይበርድ ጋዙን ለማራገፍ በመሞከሩ ነው ይላሉ። በአደጋው ጉዳት የደረሰባችው ሰዎች ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆኑ የሟቹ ቁጥር ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት አለ። በገና በዓል ምክንያት በርካታ ሰዎች ጋዝ ለማስሞላት በቦታው ተገኝተው እንደነበር ታውቋል።

 

Ø የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳን ሳልቫ ኬር ተጨማሪ የአስተዳደር ክልሎችን በመፍጠራቸውና  ገዥዎችን በመሰየማቸው ከጥቂት ወራት በፊት ከተጻራሪው ቡድን ጋር የተፈረመው ስምምነት አደጋ ሊደርስበት ይችላል ተብሏል። ቀደም ብሎ የነበረውን 10 የአውራጃ አስተዳደር ወደ 28 የአስተደድር ክልሎች ከፍ በማለታቸውና ለእየአንዳንዳቸው አስተዳዳሪ በመሾሙ ስምምነቱ መሰረት ያደረገበትን የክልል ክፍፍል ዋና መርህ ያፈርሳል ተብሎ ይገመታል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በስምምነቱ መሰረት የሽግግሩን ሂደት ለማመቻቸት በሚደረገው ንግግር ላይ ለመሳተፍ በተቃዋሚ ኃይል የተላከው ቀዳሚ ተደራዳሪ ቡድን ጁባ የገባ መሆኑ የተገለጸ ቢሆንም አሁን የሳልቫ ኬር መንግስት እየወሰደ ያለው እርምጃ ንግግሩን ዋጋ ያሳጣዋል የሚሉ በርካታ ናቸው። የተጻራሪ ቡድን ሪክ ማቻር ሐሙስ ዕለት በሰጡት መግለጫ በደቡብ ሱዳን ጦርነት መቆሙን የገለጹ ሲሆን ለተቀናቃኛቸው ለሳልቫ ኬር መልካም የገና በዓልን በማንተራስ የመልካም ምኞት መልእክት  አስተላልፈዋል። ይሁኑ እንጅ ረቡዕ ዕለት በላይኛው የናይል ግዛት ውጊያ እንደነበር ሁለቱም ወገኖች ገልጸዋል። በአማጽያኑም ሆነ በመንግስት ኃይሎች ቁጥጥር ስር ያልሆኑ በርካታ የሆኑ ታጣቂ ኃይሎች በመኖራቸው ስምምነቱን በስራ ላይ ለማዋል አስቸጋሪ ነው በማለት አስተያየት የሚሰጡ ብዙ ናችው። ተደረገ በተባለው ስምምነት ከመነሻው እምነት ያልነበረው የሳልቫ ኬር መንግስትም ስምምነቱ ሊፈርስ ይችላል ከሚል ግምት ለጠቅላላ ጦርነት እየተዘጋጀ ነው የሚል መረጃ ከየአቅጣጫው እየተሰማ ነው።

 

Ø በሚቀጥለው እሁድ ታኅሣሥ 17 ቀን 2008 ዓም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው ብሔራዊ ምርጫ ለታኅሣሥ 20 ቀን እንዲተላለፍ የአገሪቱ የሽግግር መንግስት ባለስልጣኖች ሀሳብ ያቀረቡ መሆናቸው ታወቀ። በመጭው እሁዱ ታቅዶ በነበረው ምርጫ ለሚቀጥለው የምርጫ ዘመን የሚያገለግሉ የአገሪቱ ፕሬዚዳንትና የምክር ቤት አባላት ለመመረጥ የተቃደ እንደነበር ተገልጿል። ባለስልጣኖቹ ምርጫው ከእሁድ ወደ ረቡዕ እንዲተላለፍ የጠየቁበት ዋናው ምክንያት የምርጫውን ሂደት ለማዘጋጀትና የምርጫ አስፈጻሚዎችን ለማሰልጠን በቂ  ጊዜ ለማግኘት ነው ተብሏል። በአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ምርጫዎች መካሄድ ያለባቸው በእሁድ ቀኖች በመሆኑ ምርጫው ረቡዕ ዕለት እንዲካሄድ የአገሪቱ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት ልዩ ሁኔታ ነው ብሎ መፍቀድ ይኖርበታል። ምርጫው ለሶስት ቀን እንዲራዘም መጠየቀኡ ችግርን የሚያመላክት አይደለም በማለት የተመድ ባለስልጣኖች የተናገሩ ሲሆን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኘው ያልተረጋጋ ሁኔታ ምክንያት ምርጫው በተቻለ መጠን በጥንቃቄ መካሄድ አለበት ብለዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት ሕገ መንግስቱን ለማጸደቅ በተካሄደው ምርጫ 93 ከመቶ የሚሆነው መራጭ ሕገ መንግስቱን ደግፎ ማጽደቁ ሕዝቡ ለሰላምና ለተረጋጋ ሁኔታ ያለውን ፍላጎት ያሳያል ተብሏል።

 

Ø በብሩንዲ አዲስ የአማጽያን ድርጅት ተፈጥሯል ተብሎ መነገሩ አገሪቱን  ወደ አጠቃላይ የእርስ በርስ ጦርነት እየወሰዳት ነው የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው። በአንድ የቀድሞ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን የሚመራ የብሩንዲ ሪፐብሊካን ኃይሎች (The Republican Forces of Burundi) የተባለ የአማጽያን ድርጅት የተቋቋመ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። የድርጅቱ ዋና ዓላማና ተልእኮ መብታቸውን ተጠቅመው ተቃውሟቸውን ያሰሙ ዜጎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች የሚደርስባቸውን ጥቃት ለመቋቋምና የፕሬዚዳንት ኩርንዚዛን መንግስት ማስወገድ ነው ተብሏል። የድርጅቱ መሪ ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ ከጥቂት ቀናት በፊት በብሩንዲ ዋና ከተማ በሶስት ወታደራዊ የጦር ሰፈሮች ላይ የተደረጉት የጥቃት ወረራዎች በዚህ ድርጅት አማካይነት የተደረጉ መሆናቸውን ገልጸው በርካታ ወታደሮችና ዜጎች ድርጅቱን ተቀላቅለው እየተዋጉ መሆናቸውን አስረድተዋል። 





ታኅሣሥ 14 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የናይጄሪው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ቦኮ ሃራምን ለመደምሰስ ለአገሪቱ የመከላከያ ኃይል የሰጡት ቀነ ቀጠሮ ጥቂት ቀናት የቀሩት መሆኑ የታወቀ ሲሆን  ከቢቢሲ ጋዘጠኛ ጋር ፕሬዚዳንቱ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከቴክኒክ አንጻር ቦኮ ሃራም ተሸንፏል በማለት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ ገለጻቸውን በመቀጠል “ቦኮ ሃራም ቦምቦችን በማፈንዳት አንዳንድ ጥቃት እያደረሰ ቢሆንም በመደበኛ የውጊያ ስልት የመዋጋት አቅሙ በከፍተኛ ደረጃ ተሰብሯል” ብለዋል። ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ከተመረጡ ወዲህ ቦኮሃራም ከበርካታ ቦታዎች እንዲወጣ የተደረገ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በአጥፍቶ ጠፊዎች በሚፈነዱ ቦምቦች  ጥቃት እየፈጸመ መሆኑና እና አንዳንድ የልማት ስራዎችን የማውደም ስራውን የቀጠለ መሆኑ ይታወቃል።  በቅርቡ የተባብሩት መንግስታት የህጻናት ተንከባካቢ ድርጅት ዩኒሴፍ በቦኮ ሃራም ጥቃት ብቻ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የናጄሪያ ህጻናት ከትምህርት አለም የተገለሉ መሆናቸውን ገልጿል።  

 

Ø በቡርኪና ፋሲ አንድ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደራዊ ጠባቂ ተቋም የቀድሞ መሪ የነበሩት ሚስተር ካፋንዶ ከ28 ዓመት በፊት የቀድሞውን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራን ገድለዋል የሚል ክስ ያቀረበባቸው ከመሆኑ በላይ ግለስቡ ባስቸኳይ ተይዘው እንዲታሰሩ ትእዛዝ ያስተላለፈ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ በሕዝባዊ አመጽ ከስልጣን የተወገዱትና  አሁን በአይቮሪ ኮስት በስደት ላይ የሚገኙት ካምፕዌሬም ሚስተር ሳንካራን በማስገደል በኩል ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል በሚል የተከሰሱ ሲሆን ግለሰቡን አስሮ ወደ ቡርኪና ፋሶ እንዲመልሳቸው የአይቮሪ ኮስት መንግስት የተጠየቀ መሆኑ ታውቋል።   

 

Ø በማሊ መንግስቱን የሚደግፍ አንድ የታጣቂ ቡድን አራት የሚሆኑ አባላቱ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በፈረንሳይ ወታደሮች የተገደሉ መሆናቸውን ገለጸ። ባለፉት ቀናት በማሊ የሚገኘው የፈረንሳይ ወታደራዊ ኃይል 10 ጂሃዲስቶችን መግደሉ ማስታወቁ የሚታወቅ ሲሆን የመንግስት ደጋፊ የሆነው ታጣቂ ቡድን  አራት የሚሆኑ  አባላቱ በፈረንሳይ ወታደሮች መገደላቸውን በመጥቀስ የወነጀለ መሆኑ ታውቋል። ቡድኑ በወገን ላይ በስሀተት የተደረገ እርምጃ ነው በማለት የሚናገሩት የፈረንሳይ ወታደሮች በአካባቢው ተገኝተን ጂሃዲስቶችን እንዳንዋጋ ከልክለውናል ብሏል። የፈረንሳይ ወታደራዊ ቃል አቀባይ የታጣቂ ቡድኑን ክስ ያስተባበለ መሆኑን ኤኤፍፒ የተባለው የፈረንሳይ የዜና ምንጭ ገልጿል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማሊ የሚገኘውን የሰላም ማስከበር ተልኦኮ እንዲመሩ የቀድሞውን የቻድ የውጭ ጉድይ ሚኒስትር ሚስተር አናዲፍን መሾሙን አስታውቋል።  ሚስተር አናዲፍ ቀደም ብለው በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በናይጀርና በሱዳን የሰላም ማስከበር ተልእኮን በመምራት ያገለገሉ ሲሆን በሱማሊያ ለሚገኘው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ዋና ሹም በመሆን የሰሩ መሆናቸው ታውቋል። ሚስተር አናዲፍ የሚተኳቸው የቱኒዚያው ዜጋ የሆኑት ሚስተር ሃማዲ ማሊ ውስጥ በቱዋረግ ሚሊሺያዎች እና በመንግስቱ መካከል የእርቅ ስምምነት እንዲፈረም በማድረግ በኩል ቁልፍ ሚና ቢጫወቱም  እርቅን ለማምጣት መከናውን ያለባቸውን የመሸጋገሪያ ስራዎች በተገቢው መንገድ በስራ ላይ እንዲውሉ ባለማድረጋቸው የቱዋረግ አማጽያን እንደገና ጥቃት መፈጸም የጀመሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በማሊ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ የቻድ ወታደሮች  ቁጥር  ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትናንት ረቡዕ ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓም. ባደረገው ስብሰባ በቅርቡ ሞሮኮ ውስጥ ሁሉቱ የሊቢያ ተጻራሪ መንግስታት የፈረሙትን  ስምምነት የደገፈ መሆኑ ታወቀ። ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡ የቀረበው በእንግሊዙ የተመድ አምባሳደር ሲሆን 15 ቱም የተመድ የጸጥታ ምክር ቤት አባላት ደግፈውታል። የእንግሊዙ አምባሳደር የውሳኔው ሀሳብ ከጸደቀ በኋላ ባደረጉት ንግግር ስምምነቱ ሊቢያን ወደ ሰላምና የብልጽግና ጎዳና የሚወስዳት ሲሆን በአገር ውስጥ እየተስፋፋ የሄደውን የዳኤሽ እንቅስቃሴ ለመግታትና የስደተኞችንም በር ለመዝጋት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል። በሊቢያው የእርቅ ስምምነት ላይ ፊርማቸውን ያላኖሩት ወገኖችም ሁኔታውን ተረድተው ባስቸኳይ ፊርማቸውን እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል።



ታኅሣሥ 13 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የሶማሊያ መንግስት የፈረንጆ ገናን በዓልን አስመልክቶ ይፋ የሆኑ ፓርቲዎችና ድግሶች እንዳይደረጉ  ያዘዘ መሆኑ ታወቀ። የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጠው መግለጫ የገናን በዓል ለማክበር የሚደረጉት ድግሶችና ፓሪቲዎች ከእስልምና ጋር የተያያዙ ባለመሆናቸው በሆቴል ውስጥም ሆነ በሌሎች ሕዝብ በብዛት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች መደረግ የማይችሉ መሆኑን ገልጿል። የሶማሌ የጸጥታ አባላት የገናን በዓል ለማክበር የሚሞከሩ ስብስቦችን ለመበተን ትእዛዝ የተሰጣቸው መሆኑም አስታውቋል። የውጭ ዜጎች በየቤታቸው በዓሉን ለማክበር የተፈቀደላቸው ሲሆን የሰላም አሰባሪ ኃይል አባሎችም በየጦር ሰፈሮቻቸው እንዲያከብሩ ትእዛዝ ተሰጥቷል። በገና በዓል ጊዜ በውጭ አገር የተወለዱ እና በውጭ አገር ያደጉ የሱማሊያ ዜጎች ለእረፍት በብዛት ወደ አገራቸውን የሚመጡ ስለሆነ ባደጉትበት ባህል የገና በዓል ፓርቲና ድግስ ያካሄዳሉ የሚል ፍራቻ አለ። የሶማሊያ መንግስት ይህንን መግለጫ ሲሰጥ የእስልምና ሃይምኖትን እንደምክንያት ይጠቀም እንጅ  አልሸባብ በዓሉን ለማክበር በሚደረገ ስብሰባዎች ላይ የጥቃት እርምጃ ይወስዳል የሚስል ስጋት  ዋናው ምክንያት መሆኑን የሚናገሩ በርካታ ናቸው።

 

Ø የፈረንሳይ የመከላከያ ሚኒስቴር ከፓሪስ በሰጠው መግለጫ ባለፈው ቅዳሜ ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም. በማሊ የሚገኙት የፈረንሳይ ወታደሮች በአገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ከምትገኘው ከሜናካ ከምትባለው ከተማ አጠገብ ወታደራዊ ጥቃት ፈጽመው 10 የእስላማውያን ታጣቂዎች ቡድን አባላትን የገደሉ መሆናቸውን አስታውቋል። ሙራቡቲን (Murabutin) የሚባለው ይህ ጽንፈኛ ድርጅት በማሊ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃት ሲፈጽም የቆየ መሆኑ ሲታወቅ ባለፈው ወር በዋናው ከተማ ባማኮ በራዲሰን ሆቴል ላይ ባካሄደው ጥቃት 22 ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል። በማሊ ውስጥ ያለው የጸጥታ ስጋት እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት  ባለፈው ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓም የማሊ መንግስት ለአስር ቀናት የሚቆይ የተጠንቀቅ አዋጅ ያወጀ መሆኑ ተነግሯል።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በናይጀሪያ ወታደሮች  የተገደሉት ከ300 በላይ የሚሆኑ የሺያ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ሁኔታ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው የተገኙ  መሆናቸውን ሂውማን ራይትስ ዎች የሚባለው የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ ድርጅት አጋለጠ። የወታደሩ ክፍል በሺያ እምነት ተከታዮች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ያስገደደው ምክንያት አማኞቹ መንገድ በመዝጋት የወታድሩን መሪ ጄኔራል ለመግደል ሙከራ በማድረጋቸው ነው የሚል ምክንያት የሰጠ ቢሆንም ቁጥራቸው ከ300 በላይ የሆኑትን የሺያ እምነት ተከታዮች ለመግደል ይህ ምክንያት ሊሆን እንደማይችል የሰብአዊ መብት ድርጅቱ ኃላፊ አቶ ዳንኤል በቀለ ገልጸዋል። አቶ ዳንኤል በመግለጫቸው ላይ እንዳስረዱት  መንገድ መዝጋት ብቻ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመግደል አሳማኝ ምክንያት ሊሆን እንድማይችል ገልጸው ወታደሩ ይህንን እርምጃ የወሰደው ወይ ከሚገባው በላይ ለሁኔታ የአጸፋ መልስ በመመለሱ  ነው አለበለዚያም ሆን ተብሎ የሺያ ሙስሊም እምነት ተከታዮችን ለመግደል የተደረገ እቅድ ነው በማለት አብራርተዋል። የናይጄሪያ መንግስትም ባስቸኳይ ገለልተኛ የሆኑ አጣሪ አካል አቋቁሞ ጥፋተኞችን በሕግ እንዲቀጣ ድርጅቱ ጥያቄ አቅርቧል።

 

Ø በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በምትገኘው የቦርኖ ግዛት በአንድ መንደር ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ የካሜሪን ወታደሮች ጥቃት ፈጽመው ከ70 በላይ እንደገደሉ ከአካባቢው የተገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ባለፈው እሁድ ታኅሣሥ 10 ቀን 2008 ዓም ማታ  የቦኮ ሃራም ታጣቂዎችን ያሳድዱ የነበሩት የካሜሩን ወታደሮች ወደ መንደሯ በመግባት በነዋሪው ላይ የእሩምታ ተኩስ ከፍተዎ  ብዙዎቹን ነዋሪዎች አደናግጠው እንዲወጡ ያደረጉ ሲሆን ሰኞ ጠዋት ወደ መንደራቸው የተመለሱት ነዋሪዎች ከ70 በላይ የሆኑ ሰዎች በጥይት ተመተው ያገኙ መሆናችውን  ገልጸዋል። የካሜሩን መንግስት ወታድሮቹ የሰብአዊ መብትን ለመጠበቅ የሰለጠኑ መሆናቸውን ገልጾ ግድያውን መፈጸሙን ቢክድም የናይጄሪያ  የቦርኖ አካባቢ  ባለስልጣኖች ነዋሪዎች መገደላቸውን አረጋግጠዋል።  






ታኅሣሥ 12 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ቦኮ ሃራም በተባለው አሸባሪ ቡድን እንቅስቅሴ ምክንያት አንድ ሚሊዩን የሚሆኑ የናይጄሪያ ህጻናት ከትምህርት ቤት ውጭ እንዲሆኑ የተገደዱ መሆናችውን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት ተንከባካቢ ድርጅት ዩኒሴፍ አስታወቀ። ከስድስት ዓመት በፊት እንቅስቃሴ የጀመረውና ቦኮ ሃራም  ትክክለኛ ትርጉሙ “ዘመናዊ ትምህርት ኃጢያት” ነው በሚል ስያሜ የሚጠራው ድርጅት ባደረገው የሽብር እንቅስቃሴ በናይጄሪያ ውስጥ ከ2000 ትምህርት ቤቶች በላይ እንዲዘጉ ከማድረጉ በላይ ከእነዚህ ውስጥ  በመቶ የሚቆጠሩትን አቃጥሎ አውድሟል፤ ንብረቶቻቸውን ዘርፏል። ባለፉት ስድስት ዓመታት በዚሁ አሸባሪ ድርጅት ከ 17 ሺ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ለመሰደድ ተገደዋል። የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት በዚህ ወር መጨረሻ ላይ ቡድኑ እንዲደመሰስ ለመከላከያው ተቋም መመሪያ ቢያስተላልፉም የቦኮሃራም የሽብር እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

 

Ø ትናንት ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓም. ጂቡቲ ውስጥ  በሕዝቡና በጸጥታ አባላት መካከል በተነሳ ግጭት በርከት ያሉ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። ከዋናው ከተማ አጠገብ በሚገኘው ቡልድሆኮ በሚባለው አካባቢ በጸሎት ላይ የነበሩ ሰዎችን የጸጥታ ኃይሎች ከነብሩበት ቦታ አስነስተው ወደ ሌላ ቦታ ለመውስድ በሚጥሩበት ወቅት በተነሳ ግጭት ሰባት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና  በርካታዎቹ  መቁሰላቸው በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተገልጿል። ዪኒየን ፎር ናሽናል ሳልቬሽን የሚባለው ተቃዋሚ ፓርቲ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 19 መሆኑና ከቆሰሉትም መካከል የድርጅቱ መሪ እንደሚገኙበት ገልጿል። ግጭቱ የተጀመረው የተሰበሰበው ሕዝብ ወደሌላ አንሄድም ብሎ እምቢተኛነቱን በገለጸበት ጊዜ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቱ ገልጸው  ከተሰብሳቢው መካከልም  ጩቢ ገጀራና ቆንጨራ የያዙ እንዲሁም ቢያንስ ሁለቱ ደግሞ ካላሽን ኮፍ የታጠቁ ሰዎች  እንደነበሩበት ተናግረዋል። ግጭቱን ተከትሎ በርካታ ሰዎች የተያዙ ሲሆን ቢያንስ 23 ሰላማዊ ሰዎች እና 50 ፖሊሶች መቁሰላቸው ተዘግቧል።  በጂቡት በርካታ አገሮች የጦር ሰፈር ያላቸው መሆኑ  ሲታወቅ የጂቡቱ ወታደሮችም ሱማሊያ ውስጥ የአፍሪካ ኅበረት ሰላም አሰባሪ ኃይል ውስጥ ተሰልፈው እየተዋጉ ናቸው።

 

Ø የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ እንዲላክ የአፍሪካ ኅብረት የወሰነውን ውሳኔ እንደተጠበቀው የአገሪቱ ምክር ቤት የተቃወመው መሆኑ ታውቋል። ምክር ቤቱ በውሳኔው  የአፍሪካ ኅብረትን ውሳኔ ካወገዘ በኋላ የብሩንዲ መንግስት የሀገሪቷን ህልውና ለውጭ ኃይል አሳልፎ መስጠት የለበትም ብሏል። የምክር ቤት ሊቀ መንበር ብሩንዲ ውስጥ አንዳንድ ችግሮች ቢኖሩም ባጠቃላይ ሰላም ሰፍኗል፤ ችግሮችም ቢሆኑ በጥንቃቄ እየተወገዱ ነው ብለዋል። ሌሎች ህገ አውጭዎች በአገሪቱ ሽብር እየተካሄደ ነው የሚለው መሰረት የሌለውና መገናኚያ ብዙሀን የሚያወራው ወሬ ካሉ በኋላ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በምንም ዓይነት አንቀበልም ብለዋል። ባለፈው አርብ የአፍሪካ ህብረት 5000 ሺ ጦር ወደ ብሩንዲ እንዲላክ በወሰነበት ወቅት የብሩንዲ መንግስት ቢቃወምም ጦር በግድ ወደ አገሪቱ ይላካል የሚል ውሳኔም አብሮ ማሳለፉ የሚታወስ ሲሆን የብሩንዲ መንግስት ተቃውሞ ካደረገ በኋላ ድርጅቱ የሚወስደው ርምጃ እየተጠበቀ ነው።  

 

Ø የዓለም አቀፉ የስደተኛ ድርጅት ዛሬ ታኅሣሥ 12 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዓመታዊ ዘገባ በዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከአፍሪካ እና ከእስያ በስደተኛነት ወደ አውሮፓ የተሻገሩ መሆናቸውን ገልጿል። ከቱርክ በግሪክ በኩል  ወደ አውሮፓ የተሻገረው ስደተኛ ቁጥር 820 ሺ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 455 ሺው ከሶሪያ 186 ሺው ደግሞ ከአፍጋኒስታን መሆኑ ተዘግቧል። የተቀረው ከአፍሪካ መሆኑ ይታወቃል። 3700 የሚሆኑ ሰዎች የሚዲትራኒያን ባህር ሲያቋርጡ የሞቱ መሆናቸውም ድርጅቱ ዘግቧል። ከሁለተኛ ዓለም ጦርነት ወዲህ በአውሮፓ ውስጥ ከታዩት የስደተኛ ችግር የአሁኑ ከፍተኛው ሲሆን ስደተኞችን በመቀበል በኩል በርካታ የአውሮፓ አገሮች ቸልተኛነትን አሳይተዋል። ስደተኞችን በብዛት ለማስተናገድ ፍላጎታቸውን ያሳዩት ጀርመንና ስዊድን ሲሆኑ ብዙዎቹ ግን ስደተኞች እንዳይገቡ ለመከላከል ወሰኖቻቸውን በአጥር የከለሉ መሆኑ ይታያል።

 

Ø በየመን ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ሲካሄድ የነበረው የእርቅ ድርድር ባለፈው እሁድ ታኅሣሥ 10 ቀን 2008 ዓም. ያለውጤት መጠናቀቁ ታውቋል።  የተኩስ አቁሙ ስምምነት ለአንድ ተጫማሪ ሳምንት እንዲራዘም ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 በሁለቱም በኩል ስምምነት የተደረገ ቢሆንም ግጭት እና ጦርነቱ የቀጠለ መሆኑ ተነግሯል። ሰኞ ዕለት በየመን ደቡባዊ ግዛቶች ሁኔታው የተረጋጋ ቢመስልም በሰሜናዊ ክፍሉ በአንዳንድ ቦታዎች ጦርነቶቹ ቀጥለዋል።  የየመን መንግስት ደጋፊዎች ከዋናው ከተማ 40 ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የሚገኘውንና  ኒህም የተባለውና በሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር የሚገኘውን ቦታ አጥቅተው 10 የሁቲ አማጽያን መግደላቸውን ገልጸዋል። እንዲሁም በሳኡዲ ወሰን አካባቢ ያለውን የሁቲዎችን ይዞታ ለማስለቅቅ ወደ ቦታው እያመሩ መሆናቸውም ተገልጿል። በሌላ በኩል ደግሞ የሁቲ አማጽያን ለአራተኛ ጊዜ ጃዛን ወደ ምትባለው የሳኡዲ የወሰን ከተማ የተኮሱትን የቦለስቲክ ሚሳየል በአየር ላይ እንዳለ ያመከኑት መሆናቸውን  የሳዑዲ ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል። ሚሳየሉ የተተኮሰበትንም መሳሪያ በአየር ጥቃት ከጥቅም ውጭ አድርገነዋል ብለዋል። የሁቲ አማጽያን ሚሳየሉን መተኮስ ካላቆሙ ከፍተኛ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በመግለጽ የሳኡዲ መንግስት ባለስልጣኖች ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።       




ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአዲስ አበባ በመንግስት ሆስፒታሎች ውስጥ በበሽተኞች የተያዙ አልጋዎች ባስቸኳይ  እንዲለቀቁ ከጤና ጥበቃ ሚንስቴር  ለየሆስፒታሎቹ አስተዳዳሪዎች ጥብቅ ትእዛዝ የተላለፈ መሆኑን ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። በጠና ከታመሙት በስተቀር በበሽተኞች የተያዙ አልጋዎች እንዲለቀቁና ሆስፒታሎቹ  ምንም ዓይነት አዲስ በሽተኛ እንዳይቀበሉ  የሚያዘው መመሪያ በየዎርዱ ለበሽተኞች ጥቅም እንዲውል የተመደቡ መድኃንቶችም በአስቸካይ እንዲሰበሰቡ የሚል ትዕዛዝ ያካተተ መሆኑ ታውቋል።   በአሁኑ ወቅት አልጋዎችን ማስለቀቅ  ያስፈለገበት ምክንያት በመመሪያው ያልተገለጸ ሲሆን ቀውሱ ወደጦርነት ሊያመራ ይችላል ከሚል ግምት የቅድሚያ ዝግጅት ለማድረግ ነው የሚል አስተያየት  ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ሰዎች ይሰጣሉ።    ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሰሞኑ ሕዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ ከሚኒልክ ሆስፒታል 3 ሀኪሞች፣ ከጥቁር አንበሳ 3 ተማሪዎች በወያኔ አፋኝ ቡድኖች ተይዘው የተወሰዱ ሲሆን  እስካሁን የት እንደታሰሩ የሚጠቁም ምንም ዓይነት መረጃ አልተገኘም ፡፡ 

 

Ø ሰሞኑን በሀገሪቱ  የተለያዩ ክፍሎች የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ አዲስ አበባ ውስጥም ሊከሰት ይችላል ከሚል ስጋት የወያኔ ካድሬዎች ያደረጉት ሰብሰባ በአስደንጋጭ ሁኔታ ያለምንም ውጤት የተበተነ መሆኑ ታወቀ፡፡ የስብሰባው መሪዎች የወያኔ ቁንጮዎች ሲሆኑ የበታች ካድሬዎች ላይ እየደነፉ ቢናገሩም የበታች ካድሬዎች ምንም አይነት ሀሳብ ባለመሰንዘራቸው ሰብሳቢዎቹ እንደተደናገጡ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የወያኔ ባለስልጣኖች በየቦታው የቤት እመቤቶችንና ሽማግሌ አባችቶችን ሰብስበው በየአካባቢዎቻቸው  አዲስና እንግዳ ሁኔታዎች ካስተዋሉና   ፀጉረ ልውጥ የሆኑ ሰዎች  ካዩ  በአስቸኳይ ለፖሊስ እንዲጠቁሙ ከማስጠንቀቂያ ጋር መመሪያ እንደሰጧቸው  መረዳት ተችሏል፡፡ በሌላ በኩል  አባ ዱላና ሙክታር አህመድ ሰብሳቢነት በተደረገው  የኦሮሞ ሊሂቃንን ሰብስባ ላይ በርካታው ተሰብሳቢ ንዴትና ቁጣ በተሞላበት ሁኔታ ስሜቱን የገለጸ ሲሆን  ሰብሳቢዎችም ውርደታቸውን ተከናንበው ስብሰባው ሳያልቅ አዳራሹን ለቀው እንደወጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

Ø ሰሞኑን  በሚያስገርም ሁኔታ ወደ አገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚደረገ የአውሮፕላን በረራዎች እየታጠፉ ወደ መቀሌ እንዲበሩ የተደረጉ መሆናቸውን ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ችለናል። ወደ መቀሌ የዞሩት በረራዎች አንዴም በቀን ሁለት ጊዜ የተደረጉ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን  የወያኔ ድርጅቶችና የወያኔ ሸሪክ የሆኑ ነጋዴዎች  የሚያስገቧቸው ሸቀጦች በብዛት በሚያስደነግጥ ሁኔታ ወደ መቀሌ እንዲጓጓዙ ተደርጓል፡፡ የጉምሩክ ኃላፊዎች ወደ መቀሌ የሚጓዙዙትን አውሮፕላኖች እንዳይፈትሹ ያደረጉ ሲሆን   በድብቅ ወደ መቀሌ እንዲጓጓዙ ከተደረጉት  ሸቀጦች  መካከል የጦር መሣሪያዎች ሊሆኑ ይችላሉ የሚል ግምት ያለ መሆኑን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ካሉ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ይገልጻል።

 

Ø ከቀኖና ውጪ በወያኔ ለሁለተኛ ጊዜ የተሸሙት ፓትርያርክ በጽኑ የታመሙት በቤተ ክህነት ውስጥ የተኮለኮሉት የወያኔ ካድሬዎች ባሳደሩባቸው ተጽእኖዎች ምክንያት ከአእምሮ ጭንቀት  የተነሳ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ቤተ ክርስቲያኗ ለዓባይ ግድብ ከፍተኛ መዋጮ መክፈል እንዳለባት የሚያስገደድ  መመሪያ በማስተላለፋቸው በብዙ  ሚሊዮን  የሚቆጠር ገንዘብ በእነዓባይ ፀሀይ እየተበዘበዘ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች በቁጭት እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ በቤተክስቲያኗ ውስጥ በእጅጉ ከተንሰራፋው ሙስና ጎን ለጎን ዘረኝነትና ኢሰብአዊነት ወደር የለሽ እንደሆኑ እየተነገረ ነው፡፡

 

Ø በሀዲያ ዞን ከተማ የሚ ገኛው የዋቸሞ  ዩኒቫርሲቲ ተማሪዎች ባለፈው ዓርብ ታሕሣሥ 8 ቀን  2008 ዓም የወያኔ አገዛዝ ን በመቃወም እንቅስቃሴ አድ ርገዋል። አጋዝ ጦር ባዳረገው የአፈና ሁኔታ እንቃቃሴው ገብ ብሏል። እስካሁ ን  ድረስ ት / ቤቱ በወያኔ ቅልብ የአጋዝ ጦር ተከቦ ይገኛል። የህዝብን መብት ረግጦ በመሳሪያ ኃይል እገዛለሁ ማለት ዘበት ስለሆነ ይህን ጨካኝ ፣ ሆዳምና የዘራፊዎች መንጋ ሥ ርዓት ለማስወገድ የ ሚደረገው ትግል በሁሉም ቦታ መቀጠል አለበት። ሌሎች የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ፣ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃና የአንደኛ ደረጃ  ት / ቤት መምህራን ና ተማሪዎች እንዲሁም ሕዝቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ፈለግ መከተል ይኖርባቸዋል። ባሪነት እስከመቼ ? ሐንቄቦ ከቦታው አስተላልፈዋል።

እንዲሁም በዚያው ዞን በሆሳዕና ከተማ ከሚገኛው እስር ቤት ለመምለጥ የሞከረ እስረኛ ተገድሏል። ግ ለሰቡ የታሰረበት ምክንያትና ስሙ አል ታወቀም።  ቅርብ ጊዜ በዚሁ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች ከፌዴራልና ከክልል የመጡ የወያኔ / ኢህአዴግ ባለሥልጣናት ሕዝብ ሰብስበው የነበረ ቢሆንም ሕዝቡ ከእናንተ የሚገኛው ምንም ነገር የለም የምንፈል ገው ለውጥ ነው በማለት አሳፍሮ መልሷል።

 

ዘንድሮ በዞኑ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ገበሬው የዘረው እህል በዋግ ተመቷል። የ ገበሬው እ ህል በዋግ መመታቱን እያየ ጨካኙ የወያኔ ስርዓት የማዳበሪያ ዋጋ ክፈሉ በማለት ገበሬውን በማስቸገር ላይ ቢገኝም ሕዝቡ የምንከፍለው ገንዘብ የለም እህሉ በዋግ ተመቷል በማለት ተቃውሞ በማሰማት ላይ ይገኛል።

 

 

Ø ትናንት ታኅሣሥ 10 ቀን 2008 ዓም ንብረትነቱ የኤር ፍራንስ የሆነ ቦይንግ 777 አውሮፕላን 459 መንገደኞችን ይዞ ከሞሪሺየስ ወደ ፓሪስ ሲያመራ በአውሮፕላን መታጠቢያ ቤት የታየወ አጠራጣሪ ዕቃ   የተጠመደ ቦምብ ሊሆን ይችላል ከሚል ፍራቻ ባስቸኳይ ሞባሳ አውሮፕላን ማረፊያ እንዲያርፍ የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ከካርቶ የተሰራውና ውስጡ የወጥ ቤት ሰዓት መቆጣጠሪያ የነበረው ይህ ለየት ያለ እቃ የጠመደ ፈንጅ አለመሆኑን የፈንጅ አዋቂዎችና ፖሊሶች በማረጋገጣቸው አውሮፕላኑ ጉዞውን ወደ ፓሪስ የቀጠለ መሆኑም ተነግሯል። ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓም የፈረንሳይ ፖሊሶች አውሮፕላኑ ፓሪስ ላይ እንዳረፈ ሁለት የሪዩኒየን ዜጎች የሆኑ  ባልና ሚስት በቁጥጥር ስር ያደርጉ መሆናቸው ተዘግቧል።

 

Ø የናይጄሪያ መከላከያ ኃይል በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በቦርኖ ግዛት ውስጥ በሶስት የተለያዩ ቦታዎች ጥቃት በመፈጸም 12 የቦኮ ሃራም ታጣቂዎችን መግደሉን የወታደሩ ቃል አቀባይ ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ገልጿል። ከተገደሉት መካከል በአካባቢው አሚር ወይም መሪ የሆነ ግለስብ የተገደለ መሆኑን መግለጫው ገልጾ በርካታ መሳሪያና ጥይት የተያዘ መሆኑንም አብራርቷል። የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ የናይጄሪያ መከላከያ ኃይል እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ቦኮሃራምን ለማጥፋት የጊዜ ገደብ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን አሸባሪው ቡድን አሁንም ጥቃት ከመሰንዘር ያላቆመ መሆኑ ታውቋል። እንዲያውም በትናንትናው ምሽት በዚያው በቦርኖ ግዛት ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ፈንጅ 6 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ተነግሯል።  

 

Ø የብሩንዲ መንግስት የአፍሪካ ኅብረት የወሰነውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ምንም ዓይነት የውጭ ጦር ወደ አገሩ እንዲገባ የማይፈቅድ መሆኑን ገልጿል። ይህን መግለጫ የሰጡት የብሩንዲ መንግስት ምክትል ቃል አቀባይ ሚስተር ካሬርዋ ሲሆኑ የአፍሪካ ኅብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ካለ ፈቃድ ወደ ብሩንዲ የሚገባ ከሆነ እንደ ወራሪ ጦር የሚቆጠር መሆኑንና  የብሩንዲ መካለክያ ኃይሎች አስፈላጊውን የመከላከል ርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱ መሆናችውን ገልጸዋል። ግለሰቡ በተጨማሪ በሰጡት መግለጫ አፍሪካ ኅብረት ጦሩን ለመላክ የወሰነው ውሳኔ  በተባበሩት መንግስታ ድርጅት መጸደቅ ነበረበት የሚል ሀሳብ አቅርበዋል። ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የአፍሪካ ኅብረት ቁጥራቸው 5000 ሺ የሚሆኑ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነ መሆኑንና የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ ባካሄደው ስብስበስባ ሁሉም ወገን ወእርቅ ጠረጴዛ እንዲመጣ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።  ሁለቱ  የብሩንዲ ምክር ቤቶች በጉዳዮ ላይ በዛሬው ቀን ይመክራሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የአገሪቱ መንግስት ከሰጠው የተለየ ውሳኔ እንደማይሰጡ   ተገምቷል።  ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ኅበረትም ሆነ የተባብሩ መንግስታት ድርጅት በጉድዩ ላይ የሚወስዱት እርምጃ ምን ሊሆን  እንደሚችል ግልጽ ባይሆንም የአፍሪካ ህብረት ጦሩን ለመላክ የወሰነው ውሳኔ ከብሩንዲ ተቃውሞ ከገጠመው በማናቸውም መንገድ ተግባራዊ ይሆናል ማለቱ ይታወሳል።

 

ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓ.ም
 

Ø ትናንት ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም የአሜሪካ መንግስት በድርቅ ለተጠቁት ወገኖች መርጃ 88 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የምግብ እርዳታ መስጠቱን አስታውቋል። ይህ እርዳታ  በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት  የአሜሪካ መንግስት ለድርቅ የሰጠውን እርዳታ ወደ 435 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ያደረገው መሆኑም ተገልጿል። ወያኔ "ረሃብ የለም፤ ያለውን የድርቅ ችግር እኛ እንቋቋመዋለን በማለት ሲያሰራጨው የነበረውን ፕሮፓጋንዳ ለውጦ በድንገት 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል ማለቱ የሚታወስ ሲሆን ከውጭ ለጋሾች ከሚጠበቀው እርዳታ ውስጥ እስካሁን ድረስ ምን ያህሉ እንደገባ አልታወቀም። በትናንትናው ዕለት በይፋ የተነገረው የአሜሪካ እርዳታ 116 ሺ ቶን የምግብ እርዳታ ሲሆን በ74 ወረዳዎች ለሚኖሩ 2.6 ሚሊዮን ለሚሆኑ ወገኖች ይደርሳል ተብሏል። የረሃብተኛው ቁጥር በቅርቡ ከ20 ሚሊዮን ያልፋል የሚል ግምት እየተሰጠ ሲሆን  እርዳታው በወቅቱ ካልደረሰ እልቂት ሊከተል እንደሚችል ብዙዎቹ ስጋታቸውን ይገልጻሉ።

 

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 19 ቀን 2008 ዓም በሱማሊያ ዋና ከተማ ሞጋዲሾ ውስጥ በርካታ መንገደኞችን በሚያስተናግድ አውራ መንገድ ላይ በተጣለ ቦምብ የተወሰኑ ሰዎች መሞታቸውንና  መቁሰላቸውን ከስፍራው የመጣ ዜና ይገልጻል። የሬውተር የዜና ምንጭ ሶስት ሰዎች እንደሞቱ ሲዘግብ የሟቾቹ ቁጥር ከዚህ ሊበልጥ እንደሚችል በቦታው የነበሩ የዓይን እማኞች ይናገራሉ። ቦምቡን በማፈንዳት በኩል እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም አልሸባብ የሚባለው ቡድን መሆኑን ብዙዎች ይጠረጥራሉ።

Ø በሩዋንዳ የውሳኔ ሕዝብ ድምጽ እንዲሰጥበት የተደረገው የሕገ መንግስት ማሻሸያ የጸደቀ መሆኑ ተነገረ። ሰባ ከመቶ በሆኑት የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ የተገባደደ ሲሆን እስካሁን 98.1 ከመቶ የሆነው መራጭ ማሻሻያውን ደግፎታል ተብሏል። በሕገ መንግሥቱ ማሻሻያ መሰረት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ካጋሜ ለሚቀጥሉት 17 ዓመት በስልጣን ላይ ሊቆዩ የሚችሉበት ሁኔታ የተመቻቸላቸው መሆኑ ተገልጿል። በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ ድርጅቶች ከመነሻው ማሻሻያውን የተቃወሙት ሲሆን በቂ ጊዜ ተሰጥቶት ሕዝብ እንዲወያይበት ያልተደረገ መሆኑን በመጥቅስ የምርጫውን ሂደት አውግዘው ትግላቸው የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የአንድን ግለሰብ የሥልጣን እድሜን ለማራዘም የተደረገው የሕገ መንግስት ማሻሻያ የዴሞክራሲን ይዞታ ይጎዳል በማለት የምዕራብ አገሮች ሂደቱን መቃወማቸው ይታወሳል።  

Ø የአፍሪካ ኅብረት 5 ሺ የሚሆኑ ወታድሮችና የፖሊስ አባላት ባስቸኳይ ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነ መሆኑ ተነገረ። በአራት ቀናት ውስጥ መልስ እንዲሰጥ የብሩንዲው መንግሥት በይፋ የተጠየቀ ሲሆን የእምቢታ መልስ ቢመጣ እንኳ በውሳኔው መሰረት የሰላም አስከባሪው ኃይል አባላት ባስቸኳይ የሚላኩ መሆኑ ተገልጿል።  የብሩንዲ መንግስት ባለስልጣኖች በተለያዩ ጊዜያት የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል በአገራቸው ውስጥ የመግባቱን ሁኔታ እንደማይቀበሉ መግለጻቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅዳሜው የድርጅቱ ውሳኔ ላይ ያላቸው አቋም ግን እስካሁን አልታወቀም። የሚላከው 5 ሺ ጦር የሚውጣጣው ከየት ከየት አገሮች እንደሆነ ባይገለጸም ጦሩ በሰላም አስከባሪው ሥራ ላይ የሚሰማራው ቢያንስ ለስድስት ወር መሆኑና ቁጥሩም እንደአስፈላጊነቱ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል። የጦሩ ተልዕኮ የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት መጠበቅና ተጻራሪ ኃይሎች የእርቅ ውይይት ሊያደርጉ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት ነው ተብሏል። በሌላ በኩል የብሩንዲ ተጻራሪ ክፍሎች በመጭው ታኅሣሥ 18 ቀን በዩጋንዳ ዋና ከተማ በካምፓላ የእርቅ ውይይት ለማካሄድ የተስማሙ መሆናቸው ታውቋል። በውይይቱ ላይ የመንግሥቱ ክፍልን ጨምሮ አስራ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማህበረሰቡ ተወካዮች በውይይቱ የሚካፈሉ ሲሆን ስብሰባውን የሚመሩት የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ናቸው ተብሏል።

        በተያያዘ ዜና የአሜሪካ መንግስት በብሩንዲ እየተካሄደ ላለው ግድያ ተጠያቂ ናቸው ባላቸው ሶስት ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ያደረገ መሆኑን አርብ ዕለት ገለጸ። ሶስቱ ማዕቀብ የተጣለባቸው     ግለሰቦች፡ የብሩንዲ የጸጥታ ሚኒስቴር ቺፍ ኦፍ ስታፍ፤ ከዚህ በፊት በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ተሳታፊ የነበሩ አንድ የቀድሞ ጄኔራል እና መንግሥትን ደጋፊ የሆኑ ሚሊሺያዎችን  በማስተባበር በኩል ጉልህ ሚና የነበራቸው አንድ ሌላ ግለሰብ ናቸው።  

Ø ቢየን በሚባለው የስዊስ ከተማ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታራቂነት የእርቅ ውይይት እያካሄዱ ያሉት የየመን ተጻራሪ ኃይላት ተወካዮች ለአንድ ሳምንት ታቅዶ የነበረውን  የተኩስ አቁም ስምምነት የሚከታተልና ተግባራዊነቱን የሚያረጋግጥ አንድ ኮሚቴ ለማቋቋም ዛሬ ቅዳሜ ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም. የተስማሙ መሆናቸው ተገለጸ። ኮሚቴው በአንድ የሊባኖስ ጄኔራል የሚመራ ሲሆን በሳኡዲ ከሚመራው የጋራ ጦር ፤ ከፕሬዚዳንት ሃዲ ደጋፊዎች ፤  ከቀድሞው ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳላህ ደጋፊዎችና ከሁቲ አማጽያን የተውጣጡ ወኪሎች እንደሚኖሩት ታውቋል። ባለፉት ጥቂት ቀናት በተለያዩ ቦታዎች በተካሄዱ ግጭቶች ምክንያት የተደረገው የተኩስ አቁም ስምምነት ይፈርሳል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ የፈጠረ መሆኑ ይታወቃል። ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ በስዊስ የሚካሄድው ውይይት ተቋርጦ የነበረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ስብሰባው የተቋረጠው  ታስረው  የሚገኙት  የፕሬዚዳንቱ  ሃዲ ወንድም እና ሌሎች የየመን ከፍተኛ ባለስልጣኖች በእስረኞች  ልውውጥ እንዲፈቱ የተጠየቀውን ጥያቄ የሁቲ አማጽያን ውድቅ በማድረጋቸው ነው ተብሏል። የሁቲ አማጽያን ተወካዮች እስረኞቹን በእስር ለማቆየት ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸው ሊፈቱ የሚችሉት ግን አጠቃላይ ስምምነት ላይ ሲደረስ ብቻ ነው ብለዋል። ስበሰባው በዛሬው ዕለት የቀጠለ ሲሆን ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ያልተቻለ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ።



ታኅሣሥ 8 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø በምስራቅ ያለውን የሊቢያ የአስተዳድር ክፍል ለመርዳት ወደ ሊቢያ ተልከው የነበሩ 20 የአሜሪካ ወታደሮች ከሌላው ክፍል በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ አገሪቱን ለቀው የወጡ መሆናቸው ታውቋል። በምስራቅ ሊቢያ የተመሰረተውና የዓለም አቀፍ እውቅና አለው የተባለውን መንግስት ነኝ የሚለውን ክፍል ለመርዳት ማዕከል  ከፍተኛና ዘመናዊ መሳሪያዎችን ታጥቀው የተላኩት  የአሜሪካ ወታድሮች በምዕራብ ሊቢያ በሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ ሊቢያ የገቡት ባለፈው ሰኞ ሲሆን  የወጡት ተጻራሪው ክፍል ባቀረበው ጠንካራ ጥያቄና ማስፈራሪያ መሆኑ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።  የአሜሪካ የአፍሪካ ወታደራዊ ኮማንድ ለዜና ምንጮች በሰጠው መግለጫ ወታደሮቹ ሊቢያን ለቀው እንዲወጡ የተደረገው ግጭቶችን ላለመፍጠር ነው ብሏል። በተያያዘ ዜና በትናንትናው ዕለት የሁለቱ ተጻራሪ አስተዳደር ተወካዮች ሞሮኮ ውስጥ በእርቅ  ስምምነት ሰነዱ ፈርመዋል የተባለ ቢሆንም  የሁለቱ ተጻራሪ ምክር ቤቶች መሪዎች በውስጣቸው ባለው አለመግባባት ምክንያት በቦታው ተገኝተው አለመፈረማቸው የስምምነቱን ውጤት አጠራጣሪ ያደርገዋል ተብሏል።

 

Ø ዛሬ ታኅሳስ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. የሩዋንዳ ዜጎች በአገሪቱ ህገ መንግስት ላይ የተደረገውን ማሻሻያ ለማጽደቅ ድምጽ የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። በዛሬው ዕለት 6.4 ሚሊዮን የሚሆኑ የሩዋንዳ ዜጎች ድምጽ ይሰጣሉ ተብለው የሚጠበቁ ሲሆን 34 ሺ ለሚሆኑ በውጭ ለሚኖሩ ዜጎች ደግሞ በትናንትናው ዕለት ድምጽ የመስጠት እድል ተሰጥቷቸዋል።  የተሻሻለው ህገ መንግስት የሩዋንዳውን መሪ የስልጣን ዘመን ለአምስት ዓመት እንዲሆን ቢወስንም ህጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀመረው  በ2016 ዓም. በመሆኑ የአሁኑ ፕሬዚዳንት እድሜ ከሰጣቸው ስልጣናቸውን እስከ 2026 ዓም ድረስ ሊያራዝሙ የሚችሉበት እድል ከፍተኛ መሆኑን ይነገራል። በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችና አንዳንድ የውጭ ኃይሎች የሕገ መንግስቱ ለውጥ ካጋሜን በስልጣን ላይ ለ34 ዓመት ለማቆየት ሆን ብሎ የታቀደ ነው በማለት ቅሬታቸውን ቢያሰሙም ካጋሜና ጓደኞቻቸው የውጭ ኃይሎች በሩዋንዳ የውስጥ ጉዳይ ምን አያገባቸውም በማለት ነቀፌታቸውን አጣጥለውታል።  

 

Ø የአፍሪካ ህብረት  የሰላምና የጸጥታና ኮሚቴ ትናንት ሀሙስ ታኃሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም ባደረገው ስብሰባ ወደ ብሩንዲ የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የተስማማ መሆኑ ተገለጸ። ቁጥሩ ምን ያህል እንደሆነ ባይገለጸም ወደ ብሩንዲ የሚላከው የሰላም አስከባሪ ኃይል በምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ጦር ስር እንደሚሰማራ ታውቋል። ጦሩ ወደ ብሩንዲ የሚላከው የብሩንዲው መንግስት ሲስማማ ወይም የአፍሪካ ህብረት አባል አገር መሪዎች አብዛኛዎቹ መላኩን በድምጽ ሲደግፉት ነው ተብሏል። በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባንኪ ሙን በተጻራሪ ኃይሎች በኩል ውይይት ሊያካሄድ የሚችል ተወካይ ወደ ቡሩንዲ የሚልኩ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ሐሙስ ዕለት ደግሞ የተመድ የሰብዕዊ መብት ሹም በአገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግድያናና አፈና እንዲመረምር አንድ ገለልተኛ የሆነ ቡድን ወደ ብሩንዲ ለመላክ የታቀደ መሆኑን ተናገረዋል።

 

Ø ናይጀር መንግስት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያከሸፈ መሆኑን  መሆኑን ትናንት ሐሙስ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም ፕሬዚዳንቱ ለሕዝባቸው በራዲዩና በቴለቪዥን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው አየር ኃይሉን በመጠቀም ሴራ ጠንሰሰው የነበሩት በሙሉ መያዛቸውን ገልጸው  ሁኔታው በቁጥጥር ሰር መዋሉንም አብራርተዋል።  መፈንቅለ መንግስቱን ለማካሄድ አሲረዋል ተብለው የተጠረጠሩ አራት ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመግለጽ ቀደም ብሎ አንዳንድ የአገሪቱ መገናኚያ ብዙሀን ተናገረው የነበረ መሆኑ ታውቋል።  በሚቀጥለው የካቲት ወር በናይጀር ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን የ63 ዓመቱ አዛውንት ፕሬዚዳንት ኢሱፉ የሚወዳደሩ መሆናቸውም ተነግሯል። የመፈንቅለ መንግስት ጠንሳሾቹ ዓላማ ምን እንደሆን እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን ተቃዋሚ ኃይሎችም የሰጡት መግለጫ የለም። ላለፉት ሁለት ዓመታት ተቃዋሚ ኃይሎች ሊካሄድ የታቀደው ምርጫ ብዙ ጉድለቶች ስላሉት ፍትሃዊ ሊሆን አይችልም በማለት የአገሪቱን የምርጫ ቦርድ ሲከሱ መቆየታቸው ይታወቃል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት በዘንድሮ የፈረንጆቹ ዓመት በዓለም ላይ ቤትና ንብረቱን ጥሎ የተሰደደው ሕዝብ ቁጥር 60 ሚሊዮን መድረሱን  አርብ ታኅሣሥ 8 ቀን 2008 ዓም. ባወጣው ዓመታዊ ዘገባ ገልጿል።  በስደተኛነት፤ ጥገኛነት በመጠይቀና እንዲሁም በአገሩ ውስጥ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ የተሰደደው ሰው ቁጥር አምና 59.5 ሚሊዮን የነበረ ሲሆን የዚህ ዓመቱ ቁጥር  500 ሺ የሚሆኑ ተጨማሪ ሰዎች መሰደዳቸውን  ይጠቁማል።  በአሁኑ ወቅት ከ122 በዓለም ላይ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ  ስደተኛ የሆነ ሲሆን በአማካይ በየቀኑ 4600 ሰዎች ቤት ንብረታችውን ጥለው እንደሚሰደዱ ዘገባው ገልጿል።    




ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የአፍሪካ ኅብረት ስለ ብሩንዲ ሁኔታ በሰፊው ከተነጋገረ በኋላ በሰጠው መግለጫ ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት አገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለው የርስ በርስ ግጭት በጣም ያሳሰበው መሆኑን ገልጾ ሌላ አገሪቱ ውስጥ እልቂት ሲካሄድ አይኑን ጨፍኖ እንደማይቀመጥ ይፋ አድርጓል።  የኅብረቱ  የሰላምና የጸጥታ ካውንስል የስላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ ስለሚላክበት ሁኔታ እየተነጋገረ መሆኑንም ተገልጿል። በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በአፍሪካ ህብረት የተመደቡ አጣሪዎች በብሩንዲ ያለውን ሁኔታ ለተወስኑ ቀናት ካጣሩ በኋላ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን መዘገባቸው የሚታወስ ሲሆን ህብረቱ እዚህ አቋም ላይ የደረሰው የአጣሪ ቡድኑን ዘገባ መሰረት በማድረግ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ብሩንዲ ውስጥ በአሁኑ ወቅት እየታየ ያለው በዘር ላይ የተሰመረተ የጥላቻ  ግጭት የዛሬ 20 አመት ከተከሰተው ጋር ተመሳሳይነት ስላለው አገሪቱ ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላላ የእልቂት ሁኔታ ውስጥ ልትገባ ትችላለች የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልጸዋል። በ 1982 ዓም በሁቱ እና በቱሲ ጎሳዎች መካከል በተነሳው ግጭት ምክንያት ከ300 ሺ ሰው በላይ ማለቁ ይታወሳል።  

 

Ø በሊቢያ ተጻራሪ መንግስትን ያቋቋሙት ወገኖች ተወካዮች ዛሬ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም.  በሞሮኮ ዋና ከተማ ራባት ላይ ተገኝተው ቀደም ብሎ  የጋራ መንግስት ለማቋቋም ደርሰውበታል የተባለውን  ስምምነት በይፋ  ለመፈረም መዘጋጀታቸው የተገለጸ ሲሆን ፈራሚዎቹ ግን በየበኩላቸው መንግስት ነን ያሉትን አስተዳደሮች  አይወክሉም ተብሏል። በትሪፖሊ የሚገኘው አስተዳደር መሪ  አቡሳህማን ቀደም ብለው ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ የሚፈረመው ስምምነት የአብዛኛውን የምክር ቤት አባላት ድጋፍ ያላገኘ በመሆኑ ህጋዊነት አይኖረውም ብለዋል። በራሳቸው በኩል ስምምነቱን እንደማይቃወሙት ገልጸው ሌሎች አባላትን ለማሳመን ግን ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። በሌላ በኩል በምስራቅ የሚገኘው መንግስታዊ አስተዳድር ወታደራዊ መሪ የሆኑ አንድ ጄኔራል የስምምነቱን ሀሳብ የሚቃወሙት መሆኑን ገልጸዋል። ጄኔራሉ ስምምነቱን የተቃወሙት በስምምነቱ ረቂቅ  ውስጥ የአገሪቱን የመከላከያ ኃይል በመሪነት እንዲመራ ስሙ የቀረበ ግለሰብ ተጻራሪው አካል በ10 ቀን ውስጥ ስምምነቱን ገልጾ ካላጸደቀው  የቀረበው ተሽሮ በሌላ ይተካል የሚል አንቀጽ ስለያዘ ነው ተብሏል።  ስለሆነም የዛሬው የይፋ የስምምነት ፊርማ ለይስሙላ እንጅ ተግባራዊነቱ አጠራጣሪ ነው ተብሏል።

 

Ø ጆርዳን በአገሪቱ ውስጥ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ገብተዋል ያለቻቸውን 800 የሚሆኑ የሱዳን ዜጎች ወደ አገራቸው ለመመለስ የተዘጋጀች ሲሆን  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኛ ጉዳይ ኮሚሽን ስዎቹ ወደ አገራቸው ቢመለሱ እጣቸው እስርና ግድያ መሆኑን ገልጾ ጆርዳን ሱዳናውያኑን እንዳታስወጣ ተማጽኗል። ጆርዳን ውስጥ ይገኛሉ ከሚባሉ 3500 ሱዳናውያን መካከል አብዛኞቹ የዳርፉር ተወላጆች በመሆናቸው ወደ አገራቸው ቢመለሱ ችግር ይድርስባቸዋል የሚል ከፍተኛ ግምት አለ። ትናንት ታኅሳስ 6 ቀን 2008 ዓም  የጆርዳን የጸጥታ አባላት ስደተኞቹ የሰፈሩበትን ስፍራ ወርረውና  የሸራ ድንኳናቸው ቀዳድደው በቁጥጥር ስር ካደረጓቸው በኋላ አገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ያጓጓዟቸው መሆኑ ይታወሳል። ስደተኞች አውሮፕላን ማረፊያ አጠገብ ቢያድሩም እስካሁን ያልተጓጓዙ መሆናቸው ከስፍራው ከተገኘ  ዜና ማወቅ ተችሏል።    

 

Ø በየመን ጎራ ለይተው በሚፋለሙት ወገኖች መካከል ስምምነት የተደረሰበት የእስረኞች ልውውጥ በታቀደው መሰረት በስራ ላይ የዋለ ሲሆን ለአንድ ሳምንት እንዲቆይ የታሰበው የተኩስ አቁም ስምምነት ግን እየተጣሰ መሆኑ ከአየቅጣጫው የሚደረሱ መርጃዎች ይጠቁማሉ። የተክሱ አቁም ስምምነቱን በመጣስ ረገድ ሁለቱም ወገኖች በመወነጃጀል ላይ ናቸው። የአረብ የጋራ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን የሁቲ አማጽያን ከ150 በላይ የሆኑ ግጭቶችን በመተንኮስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን መጣሳቸውን ገልጸው የጋራው ኃይሉን ራሱን ለመካለክል እርምጃ ወስዷል ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ሁቲዎችን የማይስታግሱ ከሆኑ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ተግባራዊ ማድረግ ይከብደናል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል። ከሁቲ አማጽያን ጋር አብሮ እየተንቀሳቀሰ ያለው የቀድሞ ፕሬዚዳንት የአሊ አብዱላህ ሳላህ ቃል አቀባይ በበኩሉ በሰጠውም መግለጫ የጋራው ኃይል በመሬት በአየርና በባህር የተቀነባበረ ጥቃት ሰንስዝሮብናል በማለት ክስ አቅርቦ ለዚህ ጥቃት ከፍተኛ የሆኑ ምላሽ እንሰጣለን ብሎ ዝቷል። ለአንድ ሳምንት ይቆያል የተባለው የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈርስ ይችላል የሚል ስጋት ያለ ሲሆን በስዊዝ የሚካሄደውም የእርቅ ውይይት ብዙ ተስፋ የሚጣልበት እንዳልሆነ ታዛቢዎች ይገልጽሉ። በትናንትናው ዕለት የተካሂደው የእስርኞች ልውውጥ መልካም እርምጃ ቢሆንም የተሳሩ ባለስልጣኖችን በማካተት የቀረበው ሁለተኛ ዙር የእስረኞች ልውውጥ ሀሳብን የሁቲ አማጽያን ያልተቀብሉት መሆኑ ተግልጿል።  




ታኅሣሥ 6 ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታራቂነት  በየመን የሚገኙ ተጻራሪ ቡድኖች ጄኔቫ ላይ የሰላም ድርድር መጀመራቸውና ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ያደረጉ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ማክሰኞ ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም.  የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ መስማማታቸው ታውቋል። በስምምነቱ  መሰረት 360 የሁቲ አማጽያን አባላትና 260 የሚሆኑ የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ተፋላሚዎች ከአጋቾቻቸው ተለቀው ወየቤታቸው ይሄዳሉ ተብሏል። ይህ የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት እንዲደረግ ግፊት ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታራቂዎች ሲሆኑ ዛሬ ታኅሣሥ 6 ቀን 2008 ዓ.ም.  ላህጅ በተባለው የደቡብ ግዛት ውስጥ ከሁለቱም በኩል እስርኞች የተፈቱ መሆኑ ታውቋል። የደቡብ የመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረ ጀምሮ 5800 የሚሆኑ የመናውያን ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ለስደት ተዳርገዋል። ባሁኑ ወቅትም 21 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች የምግብና ሌላም እርዳታ የሚፈልጉ ናቸው ተብሏል።

 

Ø በሊቢያ በየራሳቸው መንግስት ነን በማለት የአስተዳደር አካል ያቋቁመት መሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በማልታ መገናኘታቸው ተገለጸ። በምስራቃዊ ሊቢያን ማዕከል ያደረገው  መንግስት መሪ አጂላ ሳላህ እና  በትሪፖሊ የሚገኘው የሊቢያ ብሔራዊ ኮንግሬስ መሪ ኑሪ አቡሳህማን ማልታ ላይ ተገናኝተው ውይይት ያደረጉ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ከውይይት ያለፈ ስምምነት ለማድረግ ያልቻሉ መሆናቸው ታውቋል። በሳምንቱ መጨረሽ ሮም ላይ የተገናኙት የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ተወካዮች የአሜሪካውና የአውሮፓው ኅብረት ባለስልጣኖች ባሉበት ውይይት ማድረጋቸው የተነገረ ሲሆን የስምምነቱ ፊርማ ስነስርዓት ወደ ሐሙስ መተላለፉ ይታወሳል። በተጻራራነት በቆሙ ሁለቱ ምክር ቤቶች ውስጥ በተባለው ረቂቅ ስምምነት ላይ ጠንካራ ተቃውሞ ያሰሙ በመኖራቸው ሐሙስ ዕለት ፊርማው ለመደረጉ የሚጠራጠሩ በርካታ ናቸው። ሞአመር ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ በአግሪቱ በተፈጠረው ውጥንቅጥ  ወደ አውሮፓ ለሚጓዙ ስደተኞች አስተላላፊዎች ምቹ ቦታ መሆኗና  የአይሲስ እና የአልካይዳ ቅርንጫፎችም እየተጠናከሩ መምጣቸው የሊቢያ ሁኔታ የምዕራብ አገሮች ሲያሳስብ የቆየ መሆኑ ግልጽ ነው።

 

Ø ዛሬ ታኅሣሥ 6 ቀን 2008 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ በኬፕ ታውን እና በፕሪቶሪያ ከተሞች በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ ጠየቁ። በቅርቡ ፕሬዚዳንት ዙማ ሁለት ጊዜ የገንዘብ ሚኒስትራቸውን መለወጣቸው በአገሪቱ ውስጥ ተስፋፍቶ ከሚታየው የሙስና ወንጀል ጋር ተዳምሮ በመንግስታቸው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ለማስነሳት ምክንያቶ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል። በአውስትራሊያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር የሆኑት ግለሰብ ከዚህ በፊት የትራንስፖስፖርት ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት 665 ሺ ዶላር ጉቦ ተቀብለዋል በሚል ክስ ፍርድ ቤት መቅረባቸው የሙስናውን መጠንና ደረጃ ያሳይል የሚሉ በርካታ ናቸው። የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ  ፓርቲ ከ986 ዓም. ጀምሮ በስልጣን የነበረ ሲሆን በ2009 ዓም. በሚደረገው ብሔራዊ ምርጫ ስልጣኑን ሊያጣ ይችላል ተብሎ ተገምቷል።  በዛሬው ዕለት በየከተሞቹ በፕሬዚዳንት ዙማ ላይ ተቃውሞ ያሰሙት ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን ተቃውሞ እያደገ እንደሚሄድ ብዙዎቹ ይገምታሉ።  

 

Ø በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሳኡዲ አረቢያ ለግብጽ ስምንት ቢሊዮን ዶላር የሚገመት መዋዕለ ንዋይ ለማፈሰስ እና እርዳታ ለመስጠት ያቀደች መሆኗን ገለጸች ። የሳዑዲ አረቢያ ንጉስ ሳልማን መዋዕለ ንዋዩና እርዳታው እንዲደረግና የግብጽን የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት እርዳታ እንዲሰጥ ማዘዛቸውን በመግለጽ የሳኡዲ  ጋዜጦች በዛሬው ቀን እትማቸው አስፍረዋል። የሳኡዲ መንግስት ለግብጽ እርዳታ ለመስጠት ቃል የገባው በነዳጅ ዋጋ መውደቅ ምክንያት ዘጠና ከመቶ የሚሆነውን ገቢ ባጣበት ወቅት ነው። ግብጽ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጅምሮ በየመን ውስጥ በሳኡዲ ከሚመራው ኃይል ጋር ተሰልፋ የሁቲ አማጽያንን እየወጋች ሲሆን ባለፈው ሰኞ የተቋቋመውም የአረብ አገሮች የጸረ ሽብር ህብረት አባል ናት። ባለፈው መጋቢት የተባበሩት አረብ ኢምሬትና ኩዊት እያንዳንዳቸው 4 ቢሊዮን ዶላር ለግብጽ በርዳታ መልክ መስጠታቸው ይታወሳል።

 

Ø በአፍሪካ ህብረት የሚደገፈው የአፍሪካ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አጥኝ ቡድን ከህዳር 27 ቀን እስከ ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም. በብሩንዲ ተገኝቶ ሁኔታዎችን ከመረመረ በኋላ በሰጠው መግለጫ በአገሪቱ ውስጥ እየተካሂዱ ያሉት ግጭቶችና የሽብር ድርግቶች በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። መርማሪ ቡድኑ በአገሪቱ ውስጥ ባደረገው ቆይታ በርካታ ያለፍርድ የሚገደሉ ያለ ህግ የሚያዙና፤ ሰቆቃዊ ድርጊት የሚፈጽምባቸው መኖራቸውን ገልጾ  ባልታወቁ ሰዎች የሚገደሉ፤ ንብረታቸው የሚወድም እና ያለፍላጎታቸው የሚሰደደዱ  ሰዎች በብዛት  መኖራቸውን ለማወቅ የቻለ መሆኑን በመጥቀስ ሁኔታው ወደ አጠቃላይ የርስ በርስ ጦርነት እያመራ ነው ብሏል። ጉዳዩ መፍትሄ ሊያገኝ የሚችለው በውይይትና በንግግር እንጅ በኃይል እንዳልሆነም የቡድኑ አባላት ጫና ሰጥተው ተናገረዋል።







ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የግብጽ መርማሪዎች የሩሲያ አውሮፕላን በፈንጅ መውደቁን  የሚያረጋግጥ ምንም መረጃ አላገኘንም ማለታቸው ታወቀ። ከሁለት ወር በፊት የሩሲያ አውሮፕላን በግብጽ ሳይናይ ባህረ ሰላጤ ከአየር ላይ ወድቆ በመከስከሱ 224 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል። አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን ፈንጅ በመቅበር አውሮፕላኑ ከአየር እንዲወርድ ያደረገ መሆኑን የገለጸ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሩሲያም ተበታትኖ ከወደቀው የአውሮፕላኑ አካል ላይ የፈንጅ ንጥረ ነገር ያገኘ መሆኑን በመግለጸ  በአይሲስ ላይ የተጠናከረ የአየር ጥቃት በማካሄድ ላይ ይገኛል። የግብጽ የመርማሪዎች ቡድን  በታህሣሥ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ባወጣው  መግለጫ  እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወይም ህገወጥ በሆነ መንገድ መውደቁን የሚያሳይ ምንም ዓይነት መረጃ አላገኘም ብለዋል። ቡድኑ የአውሮፕላኑኑ 38 ኮምፒውተሮችና ሁለት ከሞተር ጋር የተያያዙ የቴክኖሎጂ መሳርያዎችን የመረመረ መሆኑን ለ15 ጊዜ ያህል ወደ አውሮፕላኑ ወደ ወደቀበት ቦታ በመጓዝ ምርመራ ያካሄደ መሆኑን ገልጿል፡፤ እስካሁን ድረስ ባደረገው ምርመራ  አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወድቆ ለመከስከሱ ፍንጭ የሚሆን ምንም ዓይነት መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል።

 

Ø የቀድሞ የብሩንዲ የመከላከያ ሚንስትር እንዲሁም  ሌሎች 27 የጦር እና  የፖሊስ ጄኔራሎች ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆኑ ታውቋል።  ግለሰቦቹ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ የፕሬዚዳንት እንኩርንዚናን መንግስት ለመገልበጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሞክራችኋል፤ ሰዎችን በማነሳሳት ግድያ እንዲፈጽምና  በንበረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርጋችኋል    የሚሉ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን የእምነት ክህደት ቃላቸው ሳይሰጡ የቀሩ መሆናችው ታውቋል። የመከላከያ ሚኒስትሩን ጨምሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት አብዛኞቹ ተከሳሾች  ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ በሆነና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በተገለለ ቦታ መታሰራቸውን እንዲሁም ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ  በባልዲ ውስጥ  እንዲጸዳዱ የተገደዱ መሆናቸውን ገልጸው የእስር ቤቱ ሁኔታ እስካልተሻሻለ ድረስ ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ እንደማይሆኑ አስረድተዋል። በተያያዘ ዜና  የአገሪቱ የእርስ በርስ ግጭት እየተባባሰ በመሄዱና የጸጥታው ሁኔታ አስጊ እየሆነ በመምጣቱ ምክንያት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለስራ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ብሩንዲ የሚገኙ  የአሜሪካ ዜጎች ወደ ብሩንዲ እንዳይሄዱና የሄዱት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ለዜጎቹ ማሳሰቢያ አስተላፏል።  

 

Ø ትናንት እሁድ ታኅሣሥ 3 ቀን 2008 ዓም. በናይጄሪያ   ሰሜናዊ ግዛት ዛሪያ በተባለው ከተማ የመንግስት ወታደሮች  የሺያ እስልምና ተከታይ በሆኑ ዜጎች ላይ ባካሄዱት ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ የተገደሉ መሆናቸውንና መስጊዱ መደምሰሱን የሺያ ሙስሊም እንቅስቃሴ የሚባለለው ድርጅት ገልጿል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል የየእምነቱ መሪ የሆኑት የሼክ ኢብራሂም ዛግራኪ ባለቤትና ሁለት ልጆቻቸው የሚገኙበት ሲሆን  ሼኩ ተይዘው  እንደደረሱ ያልታወቀ መሆኑ ተነግሯል።  በትናንትናው ቀን የናይጄሪያ ወታደሮች ወደቦታው ሲገቡ የእምነቱ ተከታዮች የላሲቲክ ጎማ  በማቃጥል መንገድ  መዝጋታቸው የተዘገበ ሲሆን የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር ይጓዙበት በነበረ መኪና ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሞክረው እንደነበረም የአይን እማኞች ገልጸዋል። ጄኔራሉን ለመግደል ሙከራ ተድርጓል በሚል ምክንያት የናይጄሪያ ወታደሮች በወሰዱት የበቀል እርምጃ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል። በሰሜን ናይጄሪ የእስላምና ኃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን አብዛኞቹ የሱኒ እምነት ተከታዮች መሆናቸውም ይታወቃል። 

 

Ø ትናንት እሁድ ታኃሣሥ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በጊዜያዊ መንግስቱ የቀረበውን ረቂቅ ሕገ መንግስት ለማጽደቅ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን በዋናው ከተማዋ በባንጉ እና በሌሎች ቦታዎች ምርጫውን ለማስቆም የተለያዩ ኃይሎች በፈጠሩት ግጭት አምስት ሰዎች መሞታቸውና ከ20 ሰዎች በላይ መቁሰላቸው ታውቋል። የቀረበው ረቂቅ ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የስልጣን እድሜ በሁለት የስልጣን ዘመኖች የሚገድብ ሲሆን ፤ ሙስናና የሚቆጣጠርና የሚሊሺያዎችን ህልውና የሚገድቡ አንቀጾች ያሉት መሆኑም ተነግሯል።

 

Ø የመን ተጻራሪ ኃይሎች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በጄኔቫ የሰላም ውይይት ስብሰባ  ከሚጀመሩበት ከዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 4 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸው ተገለጸ።  የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን የየየመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያረጋገጡ ሲሆን የሁቲ አማጽያን ቡድንም ስምምነቱን በማረጋገጥ መግለጫ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ ታይዚዝ በተባለችው የየመን ከተማ አንድ የሳኡዲ ኮሎኔል እና የዩናይትድ አራብ ኤምራቲ ዜጋ ወታደራዊ መኮንን በርቀት በተተኮስ ሮኬት ህይወታቸው ያለፈው መሆኑ ተነግሯል። የየመን የርስ በርስ ግጭት ከተጀመረ ጀምሮ ከ6 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አባዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።


ታኅሣሥ4 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የግብጽ መርማሪዎች የሩሲያ አውሮፕላን በፈንጅ መውደቁን  የሚያረጋግጥ ምንም መረጃ አላገኘንም ማለታቸው ታወቀ። ከሁለት ወር በፊት የሩሲያ አውሮፕላን በግብጽ ሳይናይ ባህረ ሰላጤ ከአየር ላይ ወድቆ በመከስከሱ 224 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል። አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን ፈንጅ በመቅበር አውሮፕላኑ ከአየር እንዲወርድ ያደረገ መሆኑን የገለጸ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሩሲያም ተበታትኖ ከወደቀው የአውሮፕላኑ አካል ላይ የፈንጅ ንጥረ ነገር ያገኘ መሆኑን በመግለጸ  በአይሲስ ላይ የተጠናከረ የአየር ጥቃት በማካሄድ ላይ ይገኛል። የግብጽ የመርማሪዎች ቡድን  በታህሣሥ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ባወጣው  መግለጫ  እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወይም ህገወጥ በሆነ መንገድ መውደቁን የሚያሳይ ምንም ዓይነት መረጃ አላገኘም ብለዋል። ቡድኑ የአውሮፕላኑኑ 38 ኮምፒውተሮችና ሁለት ከሞተር ጋር የተያያዙ የቴክኖሎጂ መሳርያዎችን የመረመረ መሆኑን ለ15 ጊዜ ያህል ወደ አውሮፕላኑ ወደ ወደቀበት ቦታ በመጓዝ ምርመራ ያካሄደ መሆኑን ገልጿል፡፤ እስካሁን ድረስ ባደረገው ምርመራ  አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወድቆ ለመከስከሱ ፍንጭ የሚሆን ምንም ዓይነት መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል።

 

Ø የቀድሞ የብሩንዲ የመከላከያ ሚንስትር እንዲሁም  ሌሎች 27 የጦር እና  የፖሊስ ጄኔራሎች ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆኑ ታውቋል።  ግለሰቦቹ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ የፕሬዚዳንት እንኩርንዚናን መንግስት ለመገልበጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሞክራችኋል፤ ሰዎችን በማነሳሳት ግድያ እንዲፈጽምና  በንበረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርጋችኋል    የሚሉ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን የእምነት ክህደት ቃላቸው ሳይሰጡ የቀሩ መሆናችው ታውቋል። የመከላከያ ሚኒስትሩን ጨምሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት አብዛኞቹ ተከሳሾች  ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ በሆነና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በተገለለ ቦታ መታሰራቸውን እንዲሁም ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ  በባልዲ ውስጥ  እንዲጸዳዱ የተገደዱ መሆናቸውን ገልጸው የእስር ቤቱ ሁኔታ እስካልተሻሻለ ድረስ ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ እንደማይሆኑ አስረድተዋል። በተያያዘ ዜና  የአገሪቱ የእርስ በርስ ግጭት እየተባባሰ በመሄዱና የጸጥታው ሁኔታ አስጊ እየሆነ በመምጣቱ ምክንያት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለስራ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ብሩንዲ የሚገኙ  የአሜሪካ ዜጎች ወደ ብሩንዲ እንዳይሄዱና የሄዱት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ለዜጎቹ ማሳሰቢያ አስተላፏል።  

 

Ø ትናንት እሁድ ታኅሣሥ 3 ቀን 2008 ዓም. በናይጄሪያ   ሰሜናዊ ግዛት ዛሪያ በተባለው ከተማ የመንግስት ወታደሮች  የሺያ እስልምና ተከታይ በሆኑ ዜጎች ላይ ባካሄዱት ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ የተገደሉ መሆናቸውንና መስጊዱ መደምሰሱን የሺያ ሙስሊም እንቅስቃሴ የሚባለለው ድርጅት ገልጿል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል የየእምነቱ መሪ የሆኑት የሼክ ኢብራሂም ዛግራኪ ባለቤትና ሁለት ልጆቻቸው የሚገኙበት ሲሆን  ሼኩ ተይዘው  እንደደረሱ ያልታወቀ መሆኑ ተነግሯል።  በትናንትናው ቀን የናይጄሪያ ወታደሮች ወደቦታው ሲገቡ የእምነቱ ተከታዮች የላሲቲክ ጎማ  በማቃጥል መንገድ  መዝጋታቸው የተዘገበ ሲሆን የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር ይጓዙበት በነበረ መኪና ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሞክረው እንደነበረም የአይን እማኞች ገልጸዋል። ጄኔራሉን ለመግደል ሙከራ ተድርጓል በሚል ምክንያት የናይጄሪያ ወታደሮች በወሰዱት የበቀል እርምጃ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል። በሰሜን ናይጄሪ የእስላምና ኃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን አብዛኞቹ የሱኒ እምነት ተከታዮች መሆናቸውም ይታወቃል። 

 

Ø ትናንት እሁድ ታኃሣሥ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በጊዜያዊ መንግስቱ የቀረበውን ረቂቅ ሕገ መንግስት ለማጽደቅ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን በዋናው ከተማዋ በባንጉ እና በሌሎች ቦታዎች ምርጫውን ለማስቆም የተለያዩ ኃይሎች በፈጠሩት ግጭት አምስት ሰዎች መሞታቸውና ከ20 ሰዎች በላይ መቁሰላቸው ታውቋል። የቀረበው ረቂቅ ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የስልጣን እድሜ በሁለት የስልጣን ዘመኖች የሚገድብ ሲሆን ፤ ሙስናና የሚቆጣጠርና የሚሊሺያዎችን ህልውና የሚገድቡ አንቀጾች ያሉት መሆኑም ተነግሯል።

 

Ø የመን ተጻራሪ ኃይሎች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በጄኔቫ የሰላም ውይይት ስብሰባ  ከሚጀመሩበት ከዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 4 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸው ተገለጸ።  የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን የየየመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያረጋገጡ ሲሆን የሁቲ አማጽያን ቡድንም ስምምነቱን በማረጋገጥ መግለጫ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ ታይዚዝ በተባለችው የየመን ከተማ አንድ የሳኡዲ ኮሎኔል እና የዩናይትድ አራብ ኤምራቲ ዜጋ ወታደራዊ መኮንን በርቀት በተተኮስ ሮኬት ህይወታቸው ያለፈው መሆኑ ተነግሯል። የየመን የርስ በርስ ግጭት ከተጀመረ ጀምሮ ከ6 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አባዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።



ታኅሣሥ 2 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በምዕራብ አፍሪካ የምትገኘው ጋምቢያ እስልማዊ ሪፐብሊክ መሆኗን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ያያ ጃሜህ በተሌቪዥን ባሰሙት ንግግር አስታውቀዋል። ጃሜህ በሰጡት መግለጫ አብዛኛው የአገሪቱ ህዝብ የእስልምና ተከታይ ስለሆነ አብዛኛው ከሚከተለው እምነት ጋር ለማጣጣም  የቅኝ ገዥዎች የጣሉብንን የባህልና የእምነት ጫናን አስወግደን አገራችንን እስላማዊ ሪፐብሊክ እንድትሆን መርጠናል ብለዋል። ዜጎች አለባበሳቸውን እንዲቀይሩ የማይገደዱ ሲሆን የሌላ እምነቶች ተከታዮችም በነጻ መንቀሳቀስ ይችላሉ ተብለዋል። ፕሬዚዳንቱ በስልጣን ላይ ከ21 ዓመታት በላይ የቆዩ ሲሆን መንግስታቸው በቅርቡ በአገሪቱ ውስጥ ባለው የሰብአዊ መብት ረገጣ ምክንያት ከምዕራብ አገሮች አገር አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል። በእስያ አህጉር  ፓኪስታንና ኢራን በአፍሪካ ደግሞ ሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ መንግስታትን የመሰረቱ መሆኗቸው ይታወቃል።

Ø በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ውስጥ ዛሬ ታኅሣሥ 2 ቀን 2008 ዓ.ም. የ21 ሰዎች አስከሬን መሬት ላይ ተዘርሮ የተገኘ መሆኑ የዜና ምንጮች ገለጹ። ተገድለው ከተጣሉት መካከል ብዙዎቹ ወጣቶች ሲሆኑ እጃቸውን ወደ ኋላ ታስረው በጥይት የተገደሉ መሆናቸውንም ለማየት ተችሏል። ይህ ግድያ የተፈጸመው የአማጽያን ኃይሎች በሁለት ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ ወረራ አካሄደው ጉዳት ባደረሱ ከአንድ ቀን በኋላ ነው። የተባበሩት መንግስታት፣ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የመንግስት ባለስልጣናት በብሩንዲ ያለው ችግር በውይይትና በእርቅ ካልተፈታ ወደ አጠቃላይ የእርስ በርስ እልቂት ሊያመራ የሚችል መሆኑን በተደጋጋሚ ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም።

በተያያዘ ዜና በአሜሪካ አሳሳቢነት የተባብሩት መንግታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ካውንስል በሚቀጥለው ሳምንት ሐሙስ የብሩንዲው ጉዳይን አስመልክቶ አስቸኳይ ስብሰባ ጄኔቫ ላይ  የጠራ መሆኑ ታውቋል። ካውንስሉ የሚወስነው ውሳኔ ዝርዝር ባይታወቅም በቡርንዲ ያንዣበበውን አስጊ ሁኔታ ለማስወግድ ይችላሉ በሚባሉ መፍትሄዎች ላይ ውስጥ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።  

Ø ላለፉት ሁለት ቀናት በቱኒዚያ ከተማ በቱኒስ ሲወያዩ የቆዩት የሁለቱ የሊቢያ ተጻራሪ አስተዳደር ወኪሎች  በሚቀጥለው ሳምንት በሮማ ከተማ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ የሚቀርበውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርቅ ሀሳብ ለመቀበልና ፊርማቸውን ለማኖር የተስማሙ መሆናቸው ተገለጸ። ስምምነቱ አንድ ብሔራዊ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር ሲሆን ዝርዝሩ ምን ሊሆን እንደሚችል አልተገለጸም። በቱኒስ የተደረገውን ስምምነት የእያንዳንዱ አስተዳደር ምክር ቤት ገና ያላጸደቀው ቢሆንም በሁለቱም በኩል ያሉት አብዛኞቹ አባላት ስምምነቱን ይደግፉታል በማለት ተወካዮቹ ተናግረዋል።  

Ø ናይጄሪያ በቦካ ሃራም እንቅስቃሴ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተስደዱትን 2.3 ሚሊዮን ዜጓቿን ከሚቀጥለው የፈረንጆቹ ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ የምታደርግ መሆኗን ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ገለጹ። ስደተኞቹ የተፈናቀሉባቸው ከተሞችና መንደሮች አብዛኞቹን የመንግስቱ ወታደሮች ከቦኮሃራም ታጣቂዎች ነጻ ያደረጓቸው ሲሆን ቦኮሃራምን ለማዳከምና ለመደምሰስ እየተወሰደ ያለው ወታደራዊ ርምጃ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ሰደተኛው ለማጓጓዝም ሆነ መልሶ ለማቋቋም በርካታ ገንዘብ የሚያስፈልግ ሲሆን ብዙዎቹ ስደተኞቹ ቤቶቻቸው የፈረሱባቸው በመሆኑ በርካታ የግንባታ ስራ የሚያስፈልግ መሆኑ ተገልጿል።





ታኅሣሥ 1 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአባይ ግድብ ግንባታ ምክንያት ግብጽና ወያኔ ያልተስማሙ መሆኑ በተደጋጋሚ የተነገረ  ሲሆን ችግሩ ወደ ሌላ ደረጃ ከመዘዋወሩ በፊት የተባበሩት አረብ ኤምሬትን አስታራቂነት ግብጽ የጠየቀች መሆኑን ሚድል ኢስት ሞኒተር የተባለ ጋዜጣ ገልጿል። እንደጋዜጣው መረጃ ባለፉት ሁለት ሳምንታት የአቡዳቢው አልጋ ወራሽና የኤምሬት የመከለካያ ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት ሼክ መሀመድ ቢን ዜይድ ከሱዳኑ በሽርና ከወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ከኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር አቡዳቢ ውስጥ የተነጋገሩ መሆኑን ገልጾ አልጋወራሹ  በቅርቡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከወያኔ ባለስልጣኖች ጋር ንግግር ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሄዱ በመረጃ መልክ አቅርቧል። ሁለት ጊዜ አቡዳቢን የጎበኙት የሱዳኑ በሽርም ግብጽና ወያኔ ባላቸው ልዩነት ሱዳን ወያኔን ደግፋ እንደማትቆም ተናግረዋል  ብሏል። የግብጹ ረዳት የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ለጋዜጣው በሰጠው ቃል ግብጽ የተባበሩት አረብ ኤምሬትን አማላጅነት የጠየቀችው ከሁለት ዓመት በፊት መሆኑን ገልጾ አገሪቷ በኢትዮጵያ ውስጥ በእርሻ እና በኢንዱትስትሪ መስክ ከፍተኛ መዋእለ ንዋይ ያፈሰሰች ስለሆነ ተጽእኖ ሊኖራት ይችላል ከሚል ግምት ነው ብሏል

 

Ø ኬኒያ ኡጋንዳ ሩዋንዳና ደበቡ ሱዳን በጋራ በፈጠሩት ኖርዘርን ኮሪዶር ኢንተግሬሽን ፕሮጀክት (NCIP) በሚባለውና የተለያዩ የልማት ስራዎች በጋራና በተቀናጀ መልክ ለመስራትና ለማስተባበር በተቋቋመው አካል ውስጥ አባል ለመሆን ወያኔ በይፋ የጠየቀ መሆኑ ታወቀ። ኪጋሊ ሩዋንዳ በተደረገው ስብሰባ ላይ ጥያቄውን በይፋ ያቀረበው የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሲሆን እስከዛሬ ደረስ በታዛቢነት ሲካፈሉ የቆዩ መሆናቸውን ገልጾ ከእንግዲህ ወዲያ በአባልነት ለመስራት የሚፈልጉ መሆናቸውን ተናግሯል። የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝም በሚቀጥለው የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንደሚገኝ አስረድቷል።

Ø በብሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ ውስጥ፡አማጽያን በሁለት ወታደራዊ ጦር ሰፈሮች ላይ በሰነዘሯቸው ጥቃቶች ስምንት ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ሲታወቅ ከሞቱት መካከል ጥቂቶቹ ጥቃቱን  የሰነዘሩት መሆናቸው ታውቋል። አማጽያኑ ከሌሊቱ አስር ሰዓት ላይ ጥቃቱን የጀመሩት ጋጋራ በተባለው ከተማው ሰሜን በሆነው አካባቢ እና ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያ በሆነውና ሙሳጋ በሚባለው በከተማዋ ደቡብ በሚገኘው ቦታ ላይ ሲሆን ከሁለት ሰዓቶች ውጊያዎች በኋላ አጥቂዎቹ ያፈገፈጉ መሆናቸውን የብሩንዲ ወታድራዊ ቃል አቀባዮች ገልጸዋል።  ተኩሱ ከፍተኛ ስለነበር ነዋሪዎች ወደ ስራቸው ለመሄድም ሆነ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ፈርተው በቤት ውስጥ የዋሉ መሆናቸውን የሚደርሱት ዘገባዎች ይገልጻሉ። አካባቢዎቹ የቡርንዲን ፕሬዚዳንት የሚቃወሙት የአማጽያን ቡድን ጠንካራ ድጋፍ ያለባቸው ሲሆን ዛሬ በወታደራዊ ካሞቹ ላይ የተካሂዱት ጥቃቶች ካለፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ወዲህ በወታደራዊ ተቋም ላይ ይህን የመሰለ ጥቃት ሲደርስ የመጀመሪያው ነው ተብሏል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በወታደራዊና የጸጥታ ኃይሎች አባላት ላይ አማጽያኑ የሚያደርጉት  ደፈጣና ጥቃት እየጨመረ መሆኑ የሚነገር ሲሆን በዛሬው ቀን የተካሄዱትም ጥቃቶች  የታሰሩ እስረኞችን ለማስፈታት የተደረገ ነው የሚል መረጃ አለ። የመንግስት ወታደሮች አማጽያኑን ያባረሩ መሆኑን ቢገልጹም በከተማዋ አንዳንድ ቦታዎች ለረጅም ሰዓታት ተኩስ ሲሰማ ቆይቷል። የካቢኒ ሚኒስትሮች አስቸኳይ ስብሰባ ያደረጉ መሆናቸው ሲታወቅ ምናልባት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊታወጅ ይችላል የሚል ዜናም አለ።  የአገሪቱ ፕሬዚዳንት እንኩሩንዚዛ ህገ ወጥ በሆነ ምክንያት ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ውድድር መቅረባቸውን በመቃወም በተነሳ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ቢያንስ 240 ሰዎች መገደላቸውና ከ200 ሺ ሰዎች በላይ መሰደዳቸው ይታወሳል።  

 

Ø የሊቢያ ተጻራሪ ኃይሎች በቱኒዚያ ከተማ በቱኒስ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መገናኛታቸው ታወቀ። ስብሰባው ቀደም ብሎ በተመድ በቀረበውና ሁለቱም ወገኖች በተቃወሙት ሀሳብ ላይ በይበልጥ ተወያይቶ መግባባት ላይ በመድረስ በመጭው እሁድ በጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ላይ ለሚካሄደው ስብሰባ ሁኔታውን ለማመቻቸት ነው ተብሏል። በቱኒሱ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሊቢያ ጉዳይ ተወካይና የውጭ አገር መንግስት ዲፕሎማቶች በስበስባው ላይ መገኘታው ተነገሯል። የተመድ ተወካይ የሀሙሱ ስብሰባ ፍሬያማ ነበር በማለት እሁድ በእሁዱ ስብሰባ ለሚጠናቀቀው ለመጨረሻው ስምምነት ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል። ስብሰባው በዛሬውም ዕለት ይቀጥላል ተብሏል።  እሁድ ዕለት በሮም ከተማ የሚደረገውን ስብሰባ በሊቀ መንበርነት የሚመሩት የአሜሪካው እና የጣሊያኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሲሆኑ የሩሲያ የእንግሊዝ የቻይናና የፈረንሳይ ተወካዮች የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል። ከጋዳፊ ውድቀት በኋላ በምዕራብና በምስራቅ ሊቢያ ሁለት ተጻራሪ መንግስታት ተቋቋመው የሚንቀሳቀሱ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በፊት በተመድ ቀርቦ የነበረውን የእርቅ ሀሳብ በምስራቅ የሚገኘውና መንግስት ነኝ የሚለው አካል ሳይቀብል መቆየቱ ይታወሳል። ባለፈው ሳምንት ሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ቱኒስ ውስጥ ባደረጉት የመጀመሪያ ዙር ውይይት በአገሪቱ ውስጥ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር በመርህ ደረጃ ስምምነት ያደረጉ መሆናቸው ተነግሯል።



ህዳር 30 ቀን 2008 ዓ.ም

 

·       የተማሪዎችና የሕዝብ የተቃውሞ እንቅስቅሴ ቀጥሏል

·       በዋሽንግተን የተቃውሞ ስልፍ ተደረገ

·       ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች የባህል ቀን በጋምቤላ እያከበርኩ ነኝ ይላል፤ የሱዳኑ መሪ በበዓሉ ላይ ተገኝተዋል

·       ናይሮቢ ውስጥ 54 ኢትዮጵያውን ህገ-ወጥ ናችሁ ተብለው ታሰሩ

·       ብሩንዲ ውስጥ ፖሊስ አምስት ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ረሸነ

·       ወደ አፍርካ ቀንድና የገልፍ አገሮች የተሰደዱ የመናውያን ቁጥር 170 ሺ ደረሰ ተባለ

·       አራቱ የቱኒዚያ ሲቪል ማህበራት ተወካዮች ኦስሎ ውስጥ የኖቤል ሽልማታቸውን ተቀበሉ

·       በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ የሩዋንዳው እልቂት ወንጀለኛ ተያዘ

 

Ø ትናንት ረቡዕ ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. 54 በናይሮቢ ኬኒያ ውስጥ ፖሊስ 54 ኢትዮጵያውያንን ህገ ወጥ ናችሁ በማለት ይዞ ያሰረ መሆኑን የናይሮቢ ፖሊስ አዛዥ ለአንድ የኬኒያ ጋዜጣ ከሰጡት መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት በነዋሪዎች ጥቆማ ያድሩበት ከነበሩት ሶስት የመኝታ ክፍሎች ሲሆን በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተገልጿል። ኬኒያን እንደመሸጋገሪያ አድርገው ወደ ታንዛኒያና ኬኒያ የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር የጨመረ የመጣ መሆኑና በሞያሌ እና በሌሎች ቦታዎች ከ20 በላይ የሚሆኑ መፈተሻ ጣቢያዎች ቢኖሩም የስደተኞቹ ቁጥር ሊቀንስ ያልቻለ መሆኑ ተገልጿል። ለስደተኞቹ መተኛ ክፍሎችን ሰጥተዋል የተባሉ ሶስት ኬኒያውያንም አብረው የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø ማክሰኞ ህዳር 28 ቀን 2008 ዓም ማታ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ማንነቱ አማጽያን ናቸው ተብለው ከሚጠረጠሩ ግለሰቦች የተወረወሩ ቦምቦች ፈንድተው አንድ ፖሊስና እንድ ሰላማዊ ሰው የገደሉ ሲሆን አጸፋውን ለመመለስ በማግስቱ ረቡዕ ህዳር 29 ቀን 2008 ዓም. ፖሊሶች በወሰዱት ርምጃ ቦምቦቹን ወርውረዋል ብለው የጠረጠሯቸውን  አምስት ሰዎች ግምባራቸውንና ጀርባቸውን በመምታት የረሸኗቸው መሆኑን የአይን እማኞች መስክረዋል። ፖሊስ በሰጠው መረጃ ሶስተኛ ቦምብ ሲወረወር ፖሊሶች በወሰዱት የመከላከል ርምጃ ነው ያለ ቢሆንም የዓይን እማኞቹ ግን ሰዎቹ ከተያዙና በቁጥጥር ስር ከተደረጉ በኋላ በቅርብ ርቀት ላይ ግምባራቸውና ጀርባቸው ተመቶ የተረሸኑ መሆናቸውን ይገልጻሉ። የዚህ ዓይነት የጅምላ ርሸና ብሩንዲ ውስጥ እየተለመደ መምጣቱ አገሪቷ ወደ አጠቃላይ የርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው የሚለውን ግምት ያጠናከረ መሆኑ ታውቋል። በዚህ ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ችግሮቹ  በውይይት ካልተፈቱ አገሪቷ እየገባችበት ያለው የእርስ በርስ ጦርነት ከፍተኛ እልቂት ሊያስከተል እንደሚችል ያላቸውን ስጋት መግለጻቸው ይታወሳል።

 

Ø በየመን እየተካሄደ ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት 170 ሺ የሚሆኑ የመናውያን ጦርነቱን በመሸሽ ወደ አፍሪካ ቀንድ አገሮችና የገልፍ የአረብ አገሮች የተሰደዱ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽንና አይ ኦ ኤም የሚባለው የዓለም አቀፍ የስደተኛ ድርጅት ገልጸዋል። ድርጅቶቹ ይህንን መግለጫ የሰጡት ኬኒያ ውስጥ  ስለእርዳታ ጉዳይ ከተደረገው ስብሰባ ማጠናቀቂያ በኋላ ሲሆን  ስደተኞች ወደ ጂቡቲ፤ ኢትዮጵያ፤ ሶማሊያ ሱዳን እና ወደ ገልፍ አገሮች መሄዳቸውን ገልጸው ከ94 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ  እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።  የየመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ በርካታ ሰዎች በጦርነት የሞቱና አካላቸው የጎደለ  ሲሆን 2.3 ሚሊዮን የሚሆኑት ቤትና ንብረታቸውን ጥለው ለመሰደድ ተገደዋል። ከአገሪቱ 80 ከመቶ የሚሆነው ህዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑም ተነግሯል።

 

Ø ዛሬ ህዳር 30 ቀን 2008 ዓም አራቱ የቱኒዝያ የብሔራዊ የውይይት መድረክ የሚባሉት ማህበራት  ተወካዮች በአገራቸው ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ያገኙትን የኖቤል ሽልማት ኖርዌይ ኦስሎ በተካሄደ የሽልማት አሰጣጥ ስነስርዓት ላይ ተቀብለዋል። የኖርዌጂያኑ ኖቤል ኮሚቴ ተወካይ በስነስርዓቱ ላይ ባሰሙት ንግግር  በአገሪቱ ውስጥ አምባገነን ሥርዓት ከተወገደ በኋላ  አራቱ የህብረተሰብ ማህበሮች ዴሞክራሲያው ስርዓት በአገሪቱ እንዲሰፍን ቆራጥና ከፍተኛ አስተዋጾ በማድረጋቸው ሽልማቱ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ሽልማቱን ያገኙት አራቱ ድርጅቶች-  የቱኒዚያ ጠቅላላ የሰራተኞች ማህበር፤ የቱኒዚያ የኢንደስትሪ፣ የንግድና የእጅ ስራ ኮንፌዴሬሽን፤ የቱኒዚያ የሰብአዊ መብት ሊግ፤ የቱኒዚያ የህግ ባለሙያዎች ማህበር ተወካዮች ናቸው።

 

 

Ø ኒያኪዙ የተባለችው የሩዋንዳ ከተማ ከንቲባ የነበረውና በ1987 ዓም 800 ሺ ህዝብ በጨረሸው የሰው ዘር ማጥፋት እልቂት በወንጀል ሲፈለገ የነበረው ላዲስላስ እንታጋንዝዋ የተባለው የ53 ዓመቱ  ወንጀለኛ ባለፈው ሰኞ ኮንጎ ውስጥ መያዙን ባለስልጣኖች በዛሬው ዕለት ገልጸዋል። ባለፉት 20 ዓመታት ግለሰቡ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ ሲሆን   ወንጀለኛውን ይዞ ላስረከበ ወይም ለገደለ የ አምስት ሚሊዮን ዶላር ካሳ የሚከፈል መሆኑ ተገልጾ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ግለሰቡ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖ በሰራበት ወቅት በርካታ ቱሲዎችንና ሰላማዊ ሁቲዎችን ጨርሷል ተብሎ የተወነጀለ ሲሆን እየተፈለጉ ከነበሩት ዘጠኝ ቀንደኛ ገዳዮችና አስገዳዮች መካከል አንደኛው እንደነበር ይታወሳል።

 




ህዳር 29 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ከህዳር 26 እስከ ህዳር 27 ቀን ካርቱም ሱዳን ውስጥ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የግብጽ የሱዳንና የወያኔ ባለስልጣኖች ስብሰባ በወያኔ ጠያቂነት ለታህሳስ 1 እና 2፣ 2008 ዓ.ም. እንዲተላለፍ  መደረጉን ተከትሎ  የግብጽ የመስኖ ልማት አማካሪ በወያኔ ላይ ክስ የሰነዘሩ መሆኑን ሱዳን ታይምስ የተባለው የሱዳን ጋዜጣ በትናንትናው ዕትሙ ላይ አውጥቶታል። ባለስልጣኑ ሲጀመር በአንድ ወር ውስጥ ያልቃል ተብሎ የነበረው ውይይት ከስድስት ወር በላይ ሊፈጅ የቻለው በወያኔ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው የአነው ሁኑን ስብስባውም ያራዘመው ግድቡ ሊፈርስ የማይችልበት ደረጃ እንዲደረስ ለግንባታው ስራ ጊዜ ለመግዛት ብለዋል። የ የወያኔ ቡድን ስብሰባው እንዲዘገይ የጠየቀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኬኒያ ጋር በወሰን አካባቢ በተደረገው ስነስርዓት ላይ መገኘት ስላለበት ነው ብሏል። የግብጽ መንግስት ባለስልጣኖች ግድቡ ወደ አጌራቸው የሚሄደውን የአባይ ውሃ መጠን ይቀንሳል የሚል እምነት ያላቸው ሲሆን ባንድ ወቅት ግድቡን ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ አስበው እንደነበር ይታወሳል። ባለስልጣኑ ግብጽ ውሃው የሚቀንስ መሆኑን ካረጋገጠች የግድቡ ስራ እንዲቆም በይፋ ትጠይቃለች ካሉ በኋላ ወያኔ ሌላ ዓላማ ካለውም ጉዳያችንን ለአለም አቀፉ ተቋሞች እናቀርባለን የሚል መግለጫም ሰጥተዋል።

 

Ø አሁን በስደት ላይ የሚገኙት የቀድሞ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ፕሬዚዳንት  ፍራንስዋ ቦዚዜ  በታህሳስ 17 ቀን 2008 ዓም ሊደረግ በታቀደው ምርጫ ላይ እንዳይወዳደሩ ምርጫውን የሚያካሄደው የህገ መንግስት ፍርድ ቤት  በማገዱ ምክንያት ትናንት ህዳር 29 ቀን 2008 ዓም በዋና ከተማዋ ተቃዋሚዎች አንዳንድ መንግዶችን በመዝጋት ትራፊክ ዘግተው መዋላቸውና በተለያዩ ቦታዎች የተኩስ ድምጽ ሲሰማ የዋለ መሆኑን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፖሊስ እና የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ጸጥታውን ለመቆጣጠር በወሰዱት እርምጃ ምሽቱ ላይ ሁኔታው ሊረጋጋ። የህገ መንግስቱ ምክር ቤት ጠለቅ ያለ ማጣራት ካደረገ በኋላ መመዘኛውን ያሟላሉ ብሎ  በምርጫው እንዲወዳደሩ የፈቀደላቸው ግለስቦች 30 ሰዎች ሲሆኑ  የቀድሞው ፕሬዚዳንት እና የክርሲያኑ ሚሊሺያ መሪ በምርጫ ውድድር ውስጥ እንዳይገቡ አድርጓል። የአገሪቱን መሪ እና 141 የፓርላማ አባሎችን ለመምረጥ በሚከናወነው የምርጫ ሂደት ላይ ድምጹን ለመስጠት ሁለት ሚሊዮን የሚሆነው የአገሪቱ ዜጋ የተመዘገበ መሆኑም ተገልጿል። በመጀመሪያ ዙር ከተወዳዳሪዎቹ መካከል በቂ ድምጽ በማግኘት በግልጽ አሸናፊ የሆነ ከሌለ በጥር 6 ቀን 2008 ዓም  ሁለተኛ ዙር ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል። ምርጫው በተለያዩ ጊዜያት ሲተላለፍ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የእስልምና ተካታይ በሆኑ አማጽያን ቁጥጥር ስር በመዋሉ ምርጫውን ለማደራጀትና ለማዘጋጀት አስቸጋሪ የነበረ መሆኑ ተዘግቧል።

 

Ø ሰው ዘር ማጥፋት ሳቢያ ህይወታቸው የጠፋውን ወገኖች ለማስታወስ በየአመቱ በሚደረገው ዓለም አቀፍ በዓልን አስመልክቶ አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣን በሰጡት ገለጻ የብሩንዲው ችግር በውይይትና በድርድር ፖሊቲካዊ መፍትሄ ካላገኘ በአገሪቱ ውስጥ የዘር ማጥፋት የሚከሰትበት  ሁኔታ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።  በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስው ዘር ማጥፋትን ለመካለል የተቋቋመው ተቋም አማካሪ የሆኑት ሚስተር አዳማ ዲየንግ በሰጡት በዚህ መግለጫ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ኃይሎች በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በሁቲና በቱሲ መካከል የዘር ልዩነቱ ተካሮ ወደ እርስ በርስ ግጭትና የዘር ማጥፋት ሁኔታ አግሪቷን እየከተቷት መሆኑን ተናግረዋል። ችግሩ በወታደራዊ ኃይል መፍትሄ ሊያገኝ የማይችል መሆኑን ከገለጹ በኋላ በሩዋንዳ የነበረውን ተመሳሳይ ሁኔታ አስታውሰው ውይይት ተካሄዶ መፍትሄ ካልተገኘ በብሩንዲም ተመሳሳይ ሁኔታ ይፈጠራል በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

 

 

Ø በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በሚቀጥለው ዓመት አጠቃላይ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት የፕሬዚዳንት ካቢላ መንግስት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን የሲቪክ ማህበራት አባላትንና ሌሎች ተቃዋሚ ግለሰቦችን በገፍ በማሰርና በማስፈራራት ተግባር ላይ መሰማራቱ ያሳሰበው መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ዘገባው የሚስተር ካቢላ መንግስት ከምርጫ ጋር ተያይዞ 143 የሰብአዊ መብት ጥሰት ያደረገ መሆኑና ያለምክንያት የሚታሰሩት ሰዎች ቁጥር 649 መድርሱን አስፍሯል። መንግስቱ አፈናውንና እስራቱን ያስፋፋባቸው  ቦታዎች ተቃዋሚዎች ጠንካራ ናችው የሚባሉባቸው እንደ ኪንሻሳ ሰሜንና ደቡብ ኪቩ እንዲሁም ምስራቃዊ ካሳይ አውራጃዎች ናቸው ተብሏል። መንግስት እያካሄደ ያለው  አፈና የዴሞክራሲውን መድርክ ከማጥበቡ ሌላ ምርጫውን ተዓማኒና ተቀባይነት እንዳይኖረው ያደርጋል በማለት በዘገባው ገልጿል። ፕሬዚዳንት ካቢላ ከ1994 ዓም ጀምሮ በስልጣን የነበሩ ሲሆን በህገ መንግስቱ መሰረት ባሁኑ ምርጫ ለመወዳደር የማይችሉ መሆናቸው ይታወቃል። ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ወር  የእርቅና የውይይት ስብሰባ ለመጥራት ያስተላለፉትን ሀሳብ ተቃዋሚዎች ካቢላ የስልጣናቸውን እድሜ ለማራዘም ያቀዱት ተንኮል ነው በማለት ውድቅ አድርገውታል።  

 

Ø በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ የካሜሩን ወታደሮች በአንድ መንደር ላይ ወረራ አካሂደው አንድ መቶ አምሳ የመንደሩን ነዋሪዎች መግደላቸውን እንዲሁም ከብቶች መዝረፋቸውንና ቤቶች ማቃጠላቸውን አንድ የመንደሩ ነዋሪ ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። የመንደሩ ነዋሪዎች አደጋውን በመሸሽ ለስደት የተዳረጉ መሆናቸውም ተገልጿል።  የካሜሩን ባለስልጣኖች ድርጊቱን አልፈጸምንም በማለት ክሱን ያስተባበሉ ቢሆንም ሁኔታው በናይጄሪያ እና በካሜሩን መካከል ውጥረት ሳይፈጥር አላለፈም ተብሏል። ግድያውና ዘረፋው የተካሄደው ባለፈው ወር ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓም. ሲሆን 643 የሚሆኑ የመንደሩ ነዋሪዎች አዳማዋ ፉፉሬ ከሚባለው የመጠለያ ጣቢያ የደረሱ መሆናችው ታውቋል። ናይጄሪያ በቻድ ሃይቅ አካባቢ ዘይት ልታወጣ እንዳቀደች በመግለጽ የናይጄሪያ የነዳጅ ሚኒስትር በቅርቡ ያደረጉት ንግግር በአካባቢው ውጥረት  ለመፈጠሩ ተጨማሪ ምክንያት ነው ተብሏል። ማክሰኞ ዕለት የናይጄሪያ የሰሜን ምስራቅ አውራጃ አስተዳዳሪ የካሜሩን ባለስልጣኖች ዜጎቻቸውን በድብቅ ወደ ናይጄሪያ ያስገባሉ የሚል ክስ የሰነዘሩ ሲሆን የካሜሩን ባለስልጣኖች ደግሞ ቦኮሃራም ላይ እርምጃ ለመውሰድ ከናይጄሪያ ጋር የጋራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸው ወታደሮቻቸው  የሰው ልጅ መብት እንዲያከበሩ ስልጠና የተሰጣቸው በመሆኑ የቀረበባቸውን ክስ አንቀበልም ብለዋል።





ህዳር 28 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø  በሚቀጥለው ወር እስከ 15 ሚሊዮን ይድርሳል ተብሎ የሚገመተው የረሃብተኛው ወገናችን ቁጥር በአሁኑ ወቅት 10 ሚሊዮን የደረሰ መሆኑን የወያኔ ባለስልጣኖች አምነዋል። ከጥቂት ጊዜ በፊት በራሳችን መንገድ እንቆጣጠረዋለን ብለው ሲመጻደቁ የነበሩት ባለስልጣኖች ለድርቁ 1.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው እርዳታ መለመን ጀምረዋል። የድርቁ ሁኔታ በጣም እየተስፋፋ ከመሄዱም በላይ በመጠኑም ቢሆን ሊሻሻል የሚችለው የሚቀጥለው የመከር ወቅት በቂ ዝናም ከተገኘ ብቻ ነው በሚል አዋቂዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።  የረሃብ ሁኔታን በቅድሚያ ለማሳወቅ የተቋቋመውና በአሜሪካ የሚደገፈው (The Famine Early Warning System Network (FEWS NET), የሚባለው ተቋም የምስራቅ ኢትዮጵያን አካባቢ የአስቸኳይ ጊዜ ቦታ ብሎ ሰይሞታል። ቀደም ብሎ የወያኔ አገዛዝ ኢኮኖሚውን በጥምር አሃዝ እያሳደገ ነው፣ ድኽነትንም በግማሽ ቀንሶታል እያሉ ሲያዳንቁት የነበሩት የምዕራብ ተቋሞች በአሁኑ ወቅት አገራችንን በዓለም አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ከማይገኝባቸው አገሮች መካከል ዋነኛ አድርገው ሲመድቧት በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ህይወቱን ለማትረፍ በቂ ምግብ የሌለው እንዲሁም ለምግብ እጥረትና ለበሽታ የተጋለጠ ነው ያላሉ።

 

Ø  በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ በሰላም አስከባሪ ግዳጅ ላይ በነበሩበት ወቅት ህጻናትን አስገደደው ደፍረዋል የተባሉ አራት የፈረንሳይ ወታደሮች በፓሪስ ለጥያቄ የቀረቡ መሆናቸው ተነገረ። በጠቅላላ የተከሰሱት ወታደሮች ቁጥር አስራ አራት ሲሆን አሁን ለጥያቄ የቀረቡት አራቱ ክሱ ስለሚመለከታቸው የራሳቸውን ሁኔታ ለማስረዳት ይሁን ወይም  በሌሎች ላይ የምስክርነት  ቃል ለመስጠት መሆኑ አልታወቀም። ከጥር 2006 እስከ ሰኔ 2006 ቀን ተፈጸመ የተባለው ወንጀል ለረጅም ጊዜ ተደብቆ ቆይቶ ዘ ጋርዲያን የተባለው የእንግሊዝ ጋዜጣ ካጋለጠው በኋላ የፈረንሳይ መንግስት ጥፋተኞችን ለመቅጣት ቃል መግባቱ ይታወሳል። ፈረንሳይና የተባበሩት መንግስታት ጉዳዩን ደብቀዋል በሚል ከበርካታ ክፍሎች የተሰነዘሩትን ክሶች ማስተባበላቸው  ይታወሳል።

 

Ø  አብዱራሂም ሳንድሂሬ የተባለው የአልሸባብ ከፍተኛ መሪ እና ሌሎች ሁለት የድርጅቱ አባላት በአሜሪካው የሰው አልባ መንኮራኩር ተመተው የተገደሉ መሆናቸውን  የአሜሪካው የመከላከያ ተቋም ቃል አቀባይ ሰኞ ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም  በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ኡካሽ በሚል የቅጽል ስም የሚጠራው አብዱራሂም ሳንድሬ የተገደለው ከስድስት ቀን በፊት መሆኑን ገልጸው የግለሰቡ መገደል ለአልሸባብ ከፍተኛ ክስረት የሚያመጣ መሆኑን ቃል አቀባዩ ጨምረው ተናግረዋል። አልሸባብ በከፍተኛ ደረጃ ተመቷል እየተባለ ቢነገርም አሁንም ቢሆን በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት እየሰነዘረ ጉዳት ማድረሱን አላቆመም። በቅርቡም በድርጅቱ ውስጥ አይስስ የተባለውን አሸባሪ ድርጅት በሚደግፉና በሚቃወሙ መካከል ልዩነት ተፈጥሯል የሚል ወሬ እየተወራ ሲሆን በልዩነቱ ምክንያት የተፈጠረውን ግጭት ያመለጠ አንድ የአልሸባብ አባል በደቡብ ሱማሊያ ባራዊ በሚባለው ቦታ እጁን ለሰላም አስከባሪው ኃይል ሰጥቷል የሚል ዜና ተሰምቷል።  

 

Ø  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ምክትል ጸሀፊ ሰኞ ህዳር 27 ቀን 2008 ዓም. ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ብሩንዲ ውስጥ እየተባባሰ የሄደውን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጅምላ ግድያ ለማስቆም በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ የተወሰደው እርምጃ በቂ አለመሆኑን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን የሰየሟቸው ልዩ አማካሪ ወደ ብሩንዲ ሄደው በሁለቱ ተጻራሪ መካከል እርቅ እንዲፈጥሩ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ የሚደገፍ መሆኑን ገልጸው እርምጃው በዚህ ብቻ የሚያበቃ ከሆነ ግን ችግሩ የሚባባስ እንጅ የማይፈታ መሆኑን አስረድተዋል። የሰብአዊ መብት ምክትል ጸሐፊው  ወደፊት ብሩንዲ ውስጥ ከፍተኛ እልቂት ሊከተል የሚችል መሆኑን በማጤን የአለም አቀፉ ህብረተሰብ ተመጣጣኝ የሆነ እርምጃ መውሰድ ይገባዋል ብለዋል። እርምጃዎቹ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ አልጠቀሱም።

 

Ø  በጋና በሙስና ተበክለዋል የተባሉ 20 ዳኞች ከስልጣናቸው የተወገዱ መሆናቸው ተገለጸ። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ውስጥ አንድ ጋዘጠኛ በድብቅ የጋና ዳኞች ለሚሰጡት ፍርድ ገንዘብና ዝሙት ሲጠይቁ ያነሳው ፊልም ለሕዝብ መታየቱና በፍርድ ተቋሙ ላይ በርካታ ተቃውሞ ማስነሳቱ ይታወሳል። ከዚያን ጊዜ ጅመሮ የጋና የፍርድ ተቋም ባደረገው ጥልቅ ምርመራና ከፍተኛ ክትትል በሙስና ተጨማልቀዋል ያላቸውን 20 ዳኞች ከስልጣናቸው ያነሳ መሆኑን ተገልጿል። በሌላ በኩል ሌሎች 12 የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ጉዳይ እየተጣራ መሆኑና ምርመራው ሲጠናቅቅ ብይን የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል።  

Ø   







ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በሰሜን ሸዋ እንሳሮና ሚዳሮሞ በተባሉ ከተሞች ውስጥ የሚኖሩ 300 ቀበሌ ነዋሪዎች በመጠጥ ውሃ እጦት ምክንያት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ከስፍራው የመጣ ዘገባ ገልጧል:: የመጠጡ ውሃ እጥረት የተከሰተው ከድርቁ ጋር በተያያዘ ሲሆን ችግሩ ከወራት በፊት የጀመሩ መሆኑን  ዘገባው ጨምሮ አስረድቷል። የከተማው ነዋሪዎች አዋሳኝ ከሆነው ከደራ ከተማ ውሃ በግዢ ለመጠቀም የቻሉ ቢሆንም አሁንም ቢሆን ችግሩ ከበድ ያለ መሆኑን ይገልጻሉ።

 

Ø በኬኒያና በኢትዮጵያ ወሰን አካባቢ የሚገኘውን የጸጥታ ውጥረት ለመቀነስና በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና አንዳንድ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያቀዱት  ፕሮግራም ሞያሌ ከተማ ውስጥ የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኬኒያው ፕሬዚዳንት  በሚገኙበት  በዛሬው ቀን የተጀመረ መሆኑ ተገለጸ።   በሁለቱ አገሮች ወሰን አካባቢ በሚኖሩ የተለያዩ ጎሳዎች መካከል በየጊዜው በተከሰቱ ግጭቶች  በርካታ ሰዎች መሞታቸው ለስደት መዳረጋቸውና በሁለቱ አገሮች ውስጥ ያሉ የጸጥታ ኃይሎች በሚወስዱት የኃይል ርምጃዎች ምክንያት አካባቢው የጸጥታ ውጥረት ነግሶበት እንደነበር የሚታወቅ ነው።  ባለፈው ወር  የወያኔ ወታደሮች አሸባሪዎችን ለመያዝ በሚል ምክንያት ወሰን ጥሰው ሶስት የኪኒያ የጸጥታ ኃይል አባላትን መግደላቸውን ተከትሎ ብዛት ያላቸው የኬኒያ ወታደሮች ወደ ወሰን አካባቢዎች እንዲሰማሩ በመደረጉ  የጸጥታው  ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ  እንደነበር የሚታወስ ነው። ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ ቦረና አካባቢና በኬኒያ መርሳቤት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችን እንዲያቀራርብ የታቀደ ሲሆን በንግድ በኢኮኖሚና በጸጥታ የሚኖረውን ግንኙነት ያካትታል ተብሏል። ፕሮግራሙ በኢትዮጵያና በኪኒያ ባሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወኪሎች በወሰን አካባቢ ባሉ አስተዳደሮችና በሌሎች ዓልም አቀፍና አካባቢ ድርጅቶች ጠንሳሽነት የተጀመረ ሲሆን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ምክክር የተደረገ መሆኑም ተገልጿል።

 

Ø ባለፈው መስከረም ወር በቡርኪና ፋሶ የተጨናገፈውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ የአገሩቱን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራን በማስገደል ተባብረዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑ ታወቀ። የቀደሞ ፕሬዚዳንት በተወሰኑ ወታድሮች በጥይት መገደላቸው ከሞቱ በኋላ በተደረገው የአስከሬን ምርመራ ሊረጋገጥ የቻለ ቢሆንም በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሞቱና ማን እንደገደላቸው እስካሁን ሚስጥር ሆኖ ቆይቷል። ፕሬዚዳንት ሳንካራን የተኩት ሚስተር ካሞፒዎሬ የቀደሞ ፕሬዚዳንት የተገደለሉበት ሁኔታ እንዲያጣራ መርማሪ አካል ቢያቋቁሙም ምርመራው ያላመጣ መሆኑ የሚታወቅ  ከመሆኑም በላይ  የፕሬዚዳንት ሳንካራ የቅርብ ጓደኛ የነበሩትና በኋላም ሚስተር ካምፒዎሬ የጸጥታ ሹም የነበሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ በግድያው የሚጠረጠሩ አልነበረም። ሚስተር ካምፒዎሬ ከስልጣን ከተነሱ በኋላ የተቋቋመው የሽግግር መንግስት ቀድሞውን ፕሬዚዳንት የአሟሟት  ሁኔታ እንዲመረመር አድርጎ በግድያው ተጠርጣሪ አድርጎ በ 10 ሰዎች ላይ ክስ የመሰረተ  ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ጄኔራል ዲየንዴሬ ናቸው ተብሏል። ጄኔራሉ መፈንቅለ መንግስቱ ከከሸፈ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋላቸውና መንግስት ለመገልበጥ አሲረዋል  በሚል ክስም መወንጀላቸው ታውቋል።

 

Ø በሊቢያ ምዕራብ እና ምስራቅ በየራሳቸው መንግስት የመሰረቱት  ተጻራሪ ክፍሎች የጋራ መንግስት ለማቋቋም ጊዜያዊ ስምምነት ያደረጉ መሆኑ ተገለጸ። በቱኒሲያ ዋና ከተማ በቱኒስ ላይ የሁለቱ ተጻራሪ ክፍሎች ተወካዮች ያደረጉት ስምምነት በአገሪቱ ውስጥ አንድ አገራዊ መንግስት ለመመስረትና በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ አጠቃላይ ምርጫ ለማካሄድ መስማማታቸው ተነግሯል። በተደረገው ስምምነት መሰረት እስከ ምርጫው ድረስ የሚያገለግለውን ጠቅላይ ሚኒስቱር የሚሰይም ከሁለቱም ክፍሎች የተውጣጣ አንድ ኮሚቴ እንዲሁም  ህገ መንግስቱን የሚመረምር ሌላ ኮሚቴ ለማቋቋም ተስማምተዋል። ይህ ስምምነት የተባበሩት መንግስታት በአስተባባሪነት ከሚካሄደው ጥረት ጋር የተያያዘ ባይሆንም በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ተወካይ ማርቲን ኮብለር ጥሩ ጅምር ነው ብለውታል። በሚቀጥለው ሳምንት በተመድ አስተባባሪነት የሚደረገው የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች የድርድር ስብሰባ ሮም ላይ የሚካሄድ መሆኑ ተነግሯል።

በተያያዘ ዜና ከስልጣናቸው በህዝባዊ  እንቅስቃሴና በምዕራብ አገሮች ጣልቃ ገብነት ከስልጣናቸው የተወገዱት የሞአመር ጋዳፊ ልጅ ትናንት እሁድ ህዳር 26 ቀን 2008 ዓም ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታውቋል። ሳዲ ገዳፊ የተባሉት የ42 ዓመት ጎልማሳ የተከተሰሱባቸው ክሶች በ1998 ዓ.ም. አንድ የእግር ኳስ አሰልጣኝ አስገድለዋል የሚል እና አባታቸው ከስልጣን በተነሱ ጊዜ በርካታ ዜጎችን በማስገደል የሽብር ተግባር ፈጸመዋል የሚል ነው።

 

Ø በቻድ ሃይቅ ላይ በምትገኝ አንድ ደሴት ውስጥ ሶስት አጥፍቶ ጠፊ ሴቶች በሰነዘሩት ጥቃት 27 ሰዎች መገደላቸውንና ከ80 በላይ መቁሰላቸውን የቻድ የጸጥታ ኃላፊዎች ገልጸዋል። ቦምቦቹ የፈነዱት በገበያ ቦታ በመሆኑ ከሞቱት ውስጥ በርካታዎቹ ገበያተኞች መሆናቸው ይታወቃል። ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ኃይል ባይኖርም የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ለመሆናቸው ከፍተኛ ግምት አለ። ቻድ ቦኮ ሃራም የሚባለው አሸባሪ ድርጅትን ለማጥፋት በተቋቋመው የጋራ ኃይል ውስጥ ተሰታፊ መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን በዚህም ምክንያት ከቡድኑ ተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰባት መሆኑ ይታወቃል።   

 

 

Ø የከባቢ አየር ብክለትን ለመቋቋም በፓሪስ ከተማ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ደኖችን ለመንከባከብና ለመጠበቅ እንዲሁም የተመናመኑትንም ወደ ነበሩበት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት የሚያደርጉ መሆናቸውን በመግለጽ ቃል የገቡ መሆናቸው ተነገረ። እስካሁን ባለው የዓለም  እድሜ  ከግማሽ በላይ የሚሆነው ደን የጠፋ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የትሮፒካል  ጫካዎች መመንመን ከባቢው አየር የካርቦንን ብክለው እንዳይቋቋም በማድረግ በኩል ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል ተብሏል።  በመጭው 2023 ዓም. 100 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነውን ምድረበዳ መሬት መልሶ በደን ለመሸፈን የአፍሪካ አገሮች ቃል የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። የከባቢ አየርን በመበከል በኩል የአፍሪካ አገሮች ተጠያቂ ባይሆኑም ይህንን ግዙፍ ስራ ለመሸከም ግን ዝግጁ ነን ብለዋል።





ህዳር 25 ቀን 2008 ዓ.ም 

Ø አዲስ አበባ ከሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ የጸጥታና ፍትህ ማስከበር ዳይሬክቶሬት በተገኘው መረጃ መሰረት ተጨማሪ የሆኑ የፌዴራል ፖሊስ  ልዩ ኃይል አባላት ተማሪዎች አመጽ ወዳነሱባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ባስቸኳይ እንዲሄዱ መታዘዛቸው ታወቋል። በትዕዛዙ መስረት   ዛሬ ዕለት ኅዳር 25 ቀን 2005 / ከሰዓት በኋላ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የልዩ ሃይል አባላት ወደ ቦረና፤ ወለጋ እና ባሌ አካባቢዎች የተሰማሩ ሲሆን ሌላ የፌዴራል ደኅንነት ቡድን ደግሞ ነገ እሁድ ኅዳር 26 ቀን ወደ ጎንደር እንዲሰማራ መመሪያ የተሰጠው መሆኑን ለመገንዘብ ተችሏል። በተለያዩ ከተሞች የኦሮሞ ተማሪዎች እያካሄዱት ያሉት የተቃውሞ እንቅስቃሴ አሁንም ያልበረደ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በምስራቅ ሀረርጌ በድሬደዋ በደምቢ ዶሎና በአዲስ አበባ አዋሳኝ ቦታዎች ተቃውሞዎች ቀጥለው መዋላቸው ታውቋል። የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከተደረገባቸው አካባቢዎች ተማሪዎች ከየቤታቸው እየተለቀሙ የሚታሰሩ  በእስር ላይ የሚገኙትም ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው መሆኑን ከየቦታው የሚደርሱ ዘገባዎች ይገልጻሉ። ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለውና መቀመጫው አሜሪካ የሆነው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት በዛሬው ዕለት የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በኦሮሞ ተማሪዎች እያካሄዱ ያሉትን ጭፍጨፋ በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል።  

በተያያዘ ዜና በአዲስ አበባም ተማሪዎች አመጽ ሊያስነሱ ይችላሉ ከሚል ፍራቻ ፖሊሶችና የጸጥታ ኃይሎች ጥበቃውና ክትትሉ እንዲቀጥል መመሪያ የተሰጣቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

 

Ø በአገራችን የገባው ከፍተኛ ድርቅና ረሃብ በህጻናትና በደካሞች ላይ ከፍተኛ የጤና መታወክ ሊያስከትል የሚችል በመሆኑ ይህንን ለመቆጣጠር የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጤና ተቋም (WHO) አንድ የጤና ቡድን ወደ ኢትዮጵያ የላከ መሆኑን አስታወቀ። አንድ የድርጅቱ ባለስልጣን ባሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ የሚገኘው የተረጅው ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅሰው ከዚህ በፊት ተስፋፍተው ከሚገኙ በሽታዎች በተጨማሪ በምግብ እጥረት ምክንያት በተለያዩ በሽታዎች በከፍተኛ ደረጃ የተጠቁ ዜጎች መኖራቸውን አስረድተዋል። ካለፈው ዓመት ጥር ወር ጀምሮ በየወሩ በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ህጻናት ቁጥር እየጨመረ የሄደ ከመሆኑም በላይ በያዝነው ዓመት መጨረሻ ላይ በአገሪቷ ውስጥ ወደ 400 ሺ የሚደርሱ ህጻናትና ወደ 700 ሺ የሚደርሱ እናቶች በምግብ እጥረቱ ሊጠቁ የሚችሉ መሆናቸው ተገምቷል። ኤል ኒኖ ባመጣው ድርቅ የተጠቁ አካባቢዎች እንደወባ፤ የተቅማጥ በሽታ፤ ኮሌራና የመሳሰሉት በሽታዎች ተስፋፍተው በዜጎች ጠና ላይ ከፍተኛ ችግር ሊያመጡ ይችላሉ ከሚል ግምት ድርጅቱ መድሃኒቶችን፤ የህክምና መሳሪያዎችንና ባለሙያዎችን ወደ ቦታዎቹ እያንቀሳቀሰ መሆኑ እኝሁ የድርጅቱ  ተናግረዋል። ድርቁ የሚያስከትለው የጤና መዛባትን ለመከላከል በተጨማሪ ወደ 8 ሚሊዮን ዶላር የሚያስፈልግ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

 

Ø ትናንት አርብ ህዳር 24 ቀን 2008 ዓም.በናይጄሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ በሚገኘው የቦርኖ ግዛት ውስጥ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ ቢያንስ ሶስት ሰዎች መገደላቸውና ሌሎች ስድስት ሰዎች መቁሰላቸው ታወቀ። ሁለት ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉትና አራቱ የቆሰሉት ሳቦን ጋሪ በተባለቸው መንደር መግቢያ ላይ ባለ የፍተሻ ቦታ ላይ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ ሲሆን አንደኛው አጥፎት ጠፊ ኪምባ በተባለው መንደር ያፈነዳው ቦምብ አንድ ሰው ለመግደልና ሁለት ሰዎችን ለማቁሰል ችሏል። ጥቃቱን ያደረሱት አጥፍቶ ጠፊዎች የቦኮሃራም አባላት እንደሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በምእራብ አፍሪካ ሪፐብሊክ የእስልምና ሃይማኖትን የሚከተሉና ራሳቸውን የቀድሞ ሰለካ አማጽያን ብለው የሚጠሩ ግለስቦች ሀሙስ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም ምሽቱ ላይ በአንድ የመጠልያ ጣቢያ ላይ ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች መግደላቸውንና ከሞቱት ውስጥ አምስቱ የአማጽያኑ አባላት መሆናቸውን አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ቃል አቀባይ አስታወቀ። ከሰላማዊ ሰዎች በኩል በርካታ ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን ሁለት  ከአማጽያኑ በኩል እንደቆሰሉም ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ሀሙስ ዕለት የክርቲያን አማጽያን የሆኑ የሌላ ቡድን አባላት ደግሞ ባንጉዊ ከተባለው የአገሪቷ ዋና ከተማ  ተነስቶ ባምባሪ ወደ ተባለ ከተማ ይጓዝ የነበረውን የጭነት መኪናዎች ኮንቮይ በማጥቃት ከመኪናዎቹ ንብረቶችን የዘረፉ መሆናቸው ታውቋል። የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ባስቸኳይ በቦታው ደርሰው አማጽያኑን ያባረሩ ከመሆኑ ባሻገር የአጥቂውን ቡድን መሪ በቁጥጥር ስር ያደረጉት መሆኑን ገልጸዋል። በሚቀጥለው ታህሳስ 3 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሪቱ ረቂቅ ህገ መንግስት ላይ ህዝቡ ድምጽ እንዲሰጥበት የሚደረገ ሲሆን   በታህሳስ 17   ቀን 2008 ዓም ደግሞ ጠቅላላ ምርጫ እንዲካሄድ ታቅዷል። በቅርቡ የሮማው ጳጳስ በአገሪቱ አጭር ጉብኝት በማድረግ እርቅ እንዲፈጠር መልእክት ያስተላለፉ ቢሆንም የእርስ በርስ ግጭቱ ያልቀነሰ መሆኑ ይነገራል።፡

 

Ø ከሊቢያ የሚመጡ የህዝብ ማመለላሻ አውሮፕላኖች በቱኒሲያ ዋና ከተማ በቱኒስ በሚገኘው የቱኒዚያ ካርቴጅ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንዳያርፉ የተከለከሉ መሆናቸውን የአገሪቱ የመገናኛ ሚኒስትር ገለጹ።  ሚኒስትሩ የሊቢያ አውሮፕላኖች ማረፍ የሚፈቀድላቸው ከከተማዋ 270 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ስፋክስ በሚባለው አውሮፕላን ማረፊያ ብቻ መሆኑን ገልጸው ይህ ርምጃ የተወሰደው የአገሪቷን የጸጥታ ሁኔታ ለማጠናከር ነው ብለዋል። የቱኒዚያ አየር መንገድ ባለፈው ነሐሴ ወር ወደሊቢያ የሚያደርገውን በረራ ያቋረጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን  ከአንድ ወር በፊትም ቱኒዚያ ከሊቢያ ጋር ያለውን ወሰን የዘጋች መሆኑም አይዘንጋም። በተያያዘ ዜናም በትናንትናው ዕለት በዋና ከተማዋ እምብርት በሚባለው የሃቢብ ቡርጊባ ጎዳና ላይ ቦምብ ሊያፈነዱ አስበዋል የተባሉ ሁለት ተጥርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የተደረጉ መሆናቸው ታውቋል።      




ህዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ  ተማሪዎች እያድረጉ ያሉት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉን  ከየቦታው የሚመጡ መረጃዎች ይገልጻሉ።  ሰሞኑን በሀሮማያ፤ በአምቦ፤ በመደወላቡ ዩኒቨርስቲዎች በተካሄዱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የተወሰኑ ተማሪዎች በወያኔ ፖሊሶች ከመገደላቸውም በላይ በርካታ ተማሪዎች በፖሊሶች የተደበደቡ መሆናቸውና መታሰራቸው ይታወቃል። በሃሮሚያ በፖሊስ ታፍነው ወደ አልታወቀ ቦታ የተወሰዱት ተማሪዎች ቁጥር ከአምሳ በላይ ሲሆን በወደላቡ ከመቶ በላይ ተማሪዎች ተወስደው ታስረዋል። አሁንም ቢሆን በእነዚህ ዩኒቨርስቲዎች አካባቢ ውጥረቱ ያልበረደ ሲሆን ሌላ ዙር እንቅስቃሴ ይደረጋል ብሎ በመፍራት ወያኔ የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ደረጃ አሰማርቶ ይገኛል። ሰሞኑን በባህታ እስር ቤት ላይ ከደረሰው የእሳት አደጋ ጋር ተያይዞ ወያኔ ያካሄደውን ግድያና ጭፍጨፋ በመቃወም የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባደረጉበት ወቅት ፖሊስ ወደ ግቢው በመግባት በርካታ ተማሪዎችን የደበደበ መሆኑና በርካታዎችንም አስሮ መውሰዱን ከአካባቢው የደረሰን ዜና ይገልጻል።

 

Ø በጎንደር ከተማ  በባህታው የእስር ቤት ቃጠሎ ወቅት ከፖሊስ ግድያ የተረፉትና ማምለጥ ያልቻሉት እስረኞች ከተማው ውጭ በአንገረብ ወንዝ ግድ አቅራቢያ ወደ አለው አዲስ እስር ቤት መዛወራቸው የሚታወስ ሲሆን ለተከታታይ ቀናት ያለምግብና ያለውሃ እንዲቀመጡ የተደረጉትና ከዘመድ ጥየቃ የታገዱት እስረኞች  ያካሄዱትን አመጽ ለማቆም የወያኔ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ የተወሰኑ እስረኞች መገደላቸውና በርካታዎችም መቁሰላቸው ታውቋል። ያመለጡም እስረኞች እንዳሉ ይነገራል። ከተወሰነ ጊዜ በኋላም እስር ቤት በእሳት የተቃጠለ መሆኑን አንዳንድ የአይን እማኞች ይናገራሉ።  በጎንደር ከተማ የወያኔ ወታደሮች በብዛት ተሰማርተው የቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ሕዝቡን እያመሱት ሲሆን በበርካታ አካባቢዎችም የጥይት ድምጽ እየተሰማ መሆኑ ይነገራል።

 

Ø ሰሞኑን በጎንደርና በአንዳንድ የአሮሞ ክልል ከተሞች እየተደረገ ያለው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሌሎች ቦታዎችም እየተዛመተ መሆኑ እየተነገረ ነው። በባህር ዳር በአንዳንድ ቦታዎች የወያኔ አገዛዝ ይወገዱ የሚል መልክትን ያዘሉ በራሪ ወረቀቶች ተብትነው ማደራቸውና በከተማው ውስጥ ውጥረት መኖሩን የሚጠቁሙ ዘገባዎች እየደረሱ ይገኛሉ።

 

 

Ø በግብጽ ካይሮ ከተማ በአንድ ሬስቶራንት ውስጥ ሞልቶቭ ኮክቴል የተባለው የእሳት ቦምብ ተወርውሮ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ 16 ሰዎች መሞታቸውና በርካታ መቁሰላቸው ከዜና ምንጮች የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ስዎቹ የሞቱት በእሳቱ ቃጠሎና በጭስ በመታፈናቸው ሲሆን የሬስቶራንቱ ልዩ ልዩ ክፍሎችም በተነሳው እሳት ጋይተዋል። እሳቱን ያነሳሱት ሶስት ፊታቸውን በማስክ የሸፈኑ ሰዎች መሆናቸው ከአካባቢው የሚደርሰው ዜና የሚገልጽ ሲሆን ሰዎቹ የእሳቱን ቦምብ ከጣሉ በኋላ ማምለጣቸውም ተገልጿል። የእስላማውያን አማጺዎች ከዚህ በፊት በካይሮና በሌሎች ቦታዎች ተመሳሳይ ጥቃት መፈጸማቸው የሚታወቅ ሲሆን ሬስቶራንቱን ያቃጠሉት የዚሁ የአማጽያን ቡድን አባላት ይሆናሉ የሚል ግምት ተሰጥቷል።

 

Ø ከሊቢያ ወደ አውሮፓ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩትን ሁለት ሺ የሚሆኑ ስደተኞች አስራ አንድ ተከታታይ የነፍስ ማዳን እንቅስቃሴዎች በማድረግ ከመስጠም ያዳኗቸው መሆኑን የኢጣሊያ ጠረፍ ጠባቂዎች ሐሙስ ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።  የጣሊያን ጠረፍ ጥበቃ፤ የባህር ኃይል፤ የድንበር የለሽ ሀኪሞች መርከቦችና እንዲሁም ሁለት የአውሮፓ ህብረት መርከቦች የተሳተፉበት ይህ የነፍስ ማዳን ተግባር የተጀመረው  ስደተኞቹ በመስጠም አፋፍ ላይ መሆኖቸውን የሚገልጽ የስልክ መልክት ከደረሳቸው በኋላ መሆኑንና በወሰዱት ተከታታይ እርምጃዎች ስደተኞችን ከስምንት ትናንሽ የላስቲካ ጀልባዎች አውጥቶ ወደ ትላልቅ መርከቦች ማዛወር የተቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

 

Ø አንድ ለመንግስት ሚዲያ ትሰራ የነበረች  የሱማሊያ ጋዜጠኛ በዛሬው ዕለት በመኪናዋ ውስጥ በተቀበረ ፈንጅ የሞተች መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። ሂንዳ ሃጂ መሀመድ የተባለችው ጋዜጠኛ ለመንግስት የዜና ማሰራጫ ተቋም በፕሮግራም አቅራቢነትና በዘጋቢነት ስትስራ የቆየች ሲሆን ባለቤቷም ከሶስት ዓመት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ ሞጋዲሾ ውስጥ መገደሉ ይታወቃል። ጋዜጠኛዋ በፈንጅው የተመታችው በመኪናዋ መቀመጫ ስር የተቀበረው ፈንጅ ከርቀት መቆጣጠሪያ በፈነዳበት ጊዜ ሲሆን ወዲያውኑ ወደ  ሆስፒታል ተወስዳ በህክምና ርዳታ ሊደረግላት ቢሞከርም ከተወስነ ጊዜ በኋላ መሞቷ ተገልጿል። ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ በሱማሊያ ከሃያ አምስት ጋዜጠኞች በላይ በአልሸባብ ታጣቂዎች የተገደሉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ጥቃቱን የፈጸመው ይኽው ቡድን እንደሆነ ይገመታል።

 

Ø የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ መወዳደር እንዲችሉ ህገ መንግስቱን ለማሻሻል የሩዋንዳ ምክር ቤት  የወሰነው ውሳኔ  የዴሞክራሲ መርህን ይጎዳል በማለት የአውሮፓው ህብረት ተቃውሞ ያሰማ መሆኑ ታወቀ። የሩዋንዳ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባሳለፈው ውሳኔ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን ከሰባት ወደ አምስት አመት ዝቅ እንዲልና አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት የስልጣን ዘመን በላይ እንዳይወዳደር ቢደነግግም ህጉ ተግባራዊ የሚሆነው የአሁኑ ፕሬዚዳንት ካጋሜ ከሁለት ዓመት በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ተወዳድረው የስልጣን ዘመናቸውን ከጨረሹ በኋላ ነው የሚል ውሳኔ አስተላልፏል። ምክር ቤቱ ያደረገው የህገ መንግስት ማሻሻያ ለውሳኔ ህዝብ ይቀርባል የተባለ ቢሆንም ሕዝቡ ያጸድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል። የአውሮፓው ህብረት አንድን ግለስብ ለመጥቀም ሲባል በዚህ መንገድ የተደረገ  የህገ መንግስት ማሻሻያ ህጋዊነትን ካለመላበሱ በላይ ተቀባይነት አይኖረውም በማለት የሩዋንዳው ምክር ቤት ያስተላለፈውን ውሳኔ አውግዟል። ባለፈው ማክሰኞ በተባበሩት መንግስታት  የአሜሪካው አምባሳደር  ካጋሜ ለአፍሪካ ምሳሌ መሆን ያለባቸው በመሆኑ በኋላ ከሁለት ዓመት በኋላ በህጉ መሰረት ከስልጣናቸው  መውረድ ይገባቸዋል የሚል ንግግር አሰምተዋል። ካጋሚ የሩዋንዳው እልቂት ከተጠናቀቀበት ከ1987 ዓም ጀመሮ ለ21 ዓመታት በስልጣን ላይ የቆዩ ሲሆን በ 1986 እና በ 2003 ዓም በተደረጉ ምርጫዎች አሸናፊ ሆነው ስልጣን በመያዛቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ጊዜ በላይ መወዳደር አይቻልም በሚለው የአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት  ከሁለት ዓመት በኋላ ተሰናባች ነበሩ።     

 

Ø በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካና በቻይና መሪዎች መካከል በተካሄደው ስብሰባ ላይ ቻይና ለአፍሪካ 60 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ርዳታና ብድር ለመስጠት ቃል መግባቷ ታወቀ። የሚሰጠው ብድር በአብዛኛው በልማት ስራዎች ላይ የሚውል ሲሆን ለተማሪዎች የነጻ እድል ትምህርት መስጠትና ስራተኞችን የማሰልጠን ተግባርን ይጨምራል ተብሏል። ስብሰባውን የመሩት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ዙማ ቻይና ትልቋ የአፍሪካ የንግድ ሸሪክ መሆኗን ገልጸው ከአፍሪካ ከፍተኛ መጠን ያለው ጥሬ ዕቃ የምትገዛ መሆኗንና በአፍሪካ ውስጥ ከፍተኛ ግምት ያለው መዋእለ ንዋይ በማፍሰስ ላይ የምትገኝ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን እንደታየው ቻይና በአፍሪካ አገሮች የምታደርገው የንግድና የመውዕለ ንዋይ እንቅስቃሴ ቻይናና በስልጣን ላይ ያሉትን ጥቂት ግለሰቦችን እንጅ ሰፊውን ሕዝብ ሲጠቅም አልታየም የሚሉ በርካታ ናቸው።   

   

 






ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም 

Ø በአባይ ላይ የሚሰራው ግድ መሰረታዊ ስራ ከተቋረ ስድስት ያለፈው መሆኑን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል ወያኔ ባለስልጣኖች ስራው አለምንም እክል ይጠናቀቃል እያሉ በየጊዜው የሚያሰሙት ጩኸት ውሸት ከመሆኑ ሌላ ለስራው መደናቀፍ ዋና ምክንያት ነው ተብሎ የሚከሰሰው ግለሰብ ሜቲክ በሚል ስም የሚጠራውን የወያኔ ድርጅት በአዛዥት የሚመራውና  ጉቦኛነቱ ወደር የለውም የሚባለው ጄኔራል ክንፈ የተባለው ግለስበ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል  ግዙፍ ነው ተብሎ ለሚነገርለት ግድብ አስፈላጊውን ቱቦዎችንና ሌሎች ቁሳቁሶሽን ሜቲክ ሊያቀርብ ይችላል በማለት የግንባታ ስራው እንዲቆም ካስደረገ ስድስት ወር ያለፈው መሆኑን ያጋለጡ ክፍሎች በመጪው ዓመት ስራው ይጠናቀቃል የተባለው ቢያንስ ለሁለት ዓመት ሊዘገይ የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።  የስራው መዘግየት የግድቡን ስራ ወጭ በስምንት ሚሊዮን ዶላር እንዲጨምር የሚያደርግ ሲሆን ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ ለመክፈል በቦንድ ሽያጭ በመዋጮ መልክ ሕዝብ ላይ የሚጫን መሆኑ መሆኑ ግልጽ ነው።  የወያኔው ጄኔራል ክንፈ ዙሪያውን በችሎታ አልባ ወያኔ አባላት ተከቦ የሚገኝ ሲሆን  እጁን በሁሉም የግንባታ ዕቅዶች ለማስገባት የሚያደርገው ሩጫ ባጠቃላይ የአገሪቷን የግንብታ ስራ እየጎዳ ነው ሲሉ  አንዳንድ የወያኔ ባለስልጣኖች ቅሬታ ሰማት ጀምረዋል ። ክንፈ ከቻይናዎች ጋር በጉቦና ጥቅም ተሳስሮ ያለ አጥፊ ወያኔ ነው የሚሉ በርካታ ናቸው።  የፈረንሳይ ኩባንያዎችና እንዲሁም ሌሎች በርካታ ድርጅቶች  ሜቴክ የተባለው ድርጅት ያከሰራቸውና የጎዳቸው መሆኑን በመግለጽ  ክንፈን እየወነጀሉ ነው ተብሏል ።

Ø በተያያዘ ዜና በአባይ ግድብ ላይ የግብጽ የወያኔና የሱዳን ተወካዮች እያካሄዱት ያለው ስብሰባ መቋረጡ ከዚህ በፊት የተገለጸ ሲሆን ስብሰባው እንደገና እንዲጀመር ከሱዳኑ አቻቸው ጋር እየመከሩ መሆኑን የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬው ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም፣ካይሮ ውስጥ አስታውቀዋል። ሱዳን ስብሰባው በሚቀጥለው ሳምንት እንዲደረግ ሀሳብ ያቀረበች ሲሆን ግብጽ በሀሳቡ መስማማቷን ገልጻለች። በአሁኑ ወቅት ግብጽ የሚገኘው የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትርም በጉዳዩ ላይ ከግብጽ ባለስልጣኖች ጋር ይነጋገራል ተብሏል።

 

Ø ኅዳር 22 ቀን 2008 / ከሰዓት በኋላ  በጫንጮ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማሩ ወደ ሁለት መቶ የሚደርሱ ተማሪዎች  ምንነቱ ባልታወቀ ህመም ተጠቅተው በመማሪያ ክፍላቸው በድንገት የወደቁ መሆናቸውና  ትንፋሽ ሲያጥራቸው ወደ ጳውሎስ ሆስፒታል ተወስደው ህክምና የተደረገላችው መሆኑ ታውቋል። ተማሪዎች ከታከሙ በኋላ ወደ ቤታቸው የተመለሱ ቢሆንም በዛሬው ዕለት  ኅዳር 23 ቀን 2008 / በተመሳሳይ መልክ በህመሙ ተጠቅተው  በድጋሚ ወደ ሆስፒታሉ የተወሰዱ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል።  ይህ ምንነቱና መነሻው ያልታወቀ በሽታ የህክምና ባለሙያዎች ግራ ያጋባ ሲሆን  ህመሙ የተጠቁት ወጣቶች  የትንፋሽ እጥረትና የልብ ምት መፋጠን ታይቶባቸዋል።   

 

Ø በጎንደር ወህኒ ቤት  ከተነሳው የእሳት ቃጠሎ አደጋ ነብሳቸውን ለማዳን ሲወጡ የነበሩ እስረኞች ላይ ፖሊስ በወሰደው ጥቃት የተገደሉት ቁጥር ከሰላሳ  በላይ መሆኑን ምንጮች እየገለጹ ይገኛሉ። ኅዳር 21 ቀን 2008 / ለሊት በወህኒ ቤቱ የደረሰውን ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ በመከላከልና በማጥፋት ፈንታ እስረኞቹ ላይ የጥይት እሩምታ የከፈተው ፖሊስ ከእስረኞቹ በተጨማሪ በአካባቢው ለእርዳታ ሲጯጯሁ የነበሩ ንጹኃን ዜጎች በጥይት የገደለ መሆኑ ታውቋል።   ከፖሊስ ጥይት ተርፈው በዱላ  እጅና እግራቸው ከተሰበረው   በተጨማሪ በእሳቱ የመለብለብ አደጋ የደረሰባቸው በርካታ ዜጎች  በጎንደር ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ ተኝተው ህክምና የተደረገላቸው መሆኑን ከአካባቢው የመጣው ዘገባ የሚያመለክት ሲሆን ሆስፒታሉ ብዛት ባላቸው ፖሊሶች እየተጠበቀ መሆኑ ተገልጿል።  በዛሬው ዕለት ከሞቱት ውስጥ የአንዳንዶቹ የቀብር ስነስርዓት ተፈጽሟል።

 

Ø ትናንት ህዳር 22 ቀን በዩናይትድ ስቴትስ ካሊፎርኒያ ግዛት ሳንበርናርዲኖ በተባለ ከተማ በአንድ የድኩማን መገልገያ ማዕከል ውስጥ ሶስት ሰዎች ተኩስ ከፍተው አስራ አራት ሰዎች መግደላቸውንና 17 ሰዎች  ማቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል። ግድያውን ፈጽመዋል ተብለው ከሚጠርጠሩ መካከል ሁለት ወታደራዊ ዩንፎርም የለበሱ ሰዎች በአንድ ኤስ ዩ ቪ መኪና ሲያመልጡ የተገደሉ ሲሆን  በመኪናቸውም  ውስጥ አውቶማቲክና ግማሽ አውቶማቲክ የሆኑ መሳሪያዎች ተገኝተዋል። የተገደሉት ሰዎች ባልና ሚስት መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን ስማቸው ሰይፍ ሪዝዋን ፋሩክ እና ታሽፊን ማሊክ እንደሚባሉ ተነግሯል።   ሶስተኛው  ተጠርጣሪ ማንነቱ ባይገለጽም በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል።  ስለግድያው ምርመራ በማካሄድ ላይ የሚገኙት የፖሊስና የጸጥታ አባላት እስካሁን በተደረገው ምርመራ የግድያውን ትክክለኛ ምክንያት ማወቅ ያልተቻለ መሆኑን ገልጸው  የሽብር ተግባር ሳይሆን አቀርም የሚል ጥርጣሬ ያላቸውም መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በኮሎራዶ ግዛት አንድ ግለሰብ ፕላንድ  ፓርንት ሁድ በሚባል የሚታወቀውና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ለሴቶች የጤና  በሚሰጠው ተቋም ውስጥ አንድ ግለስብ ባካሄደው ግድያ ሶስት ሰዎች መሞታቸውና ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸው  ሲታወቅ በአሜሪካ በትናንቱ ዕለት የተገደሉት ሰዎች ብዛት በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው ነው ተብሏል። ከጥቂት ሳምንት በፊት ፓሪስ ላይ የአይሲስ አሸባሪዎች ያካሄዱት ጥቃት በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥም ይካሄዳል የሚል ፍራቻ በብዙዎች ዘንድ ያለ መሆኑም ይታወቃል።

 

Ø የሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩብዕ ሐሙስ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም ለሩሲያ ህግ አውጭዎች ባደረጉት ንግግር ቱርክ  የሩሲያ አውሮፕላን መትታ በመጣል ለፈጸመችው  አስከፊ  ተግባር ሩሲያ የአጸፋ ርምጃ አጠናክራ እንደምትወስድ አስታውቀው ወደፊት በወሰደችው ርምጃ እንደምትጸጸት ተናግረዋል። ለሩሲያ ሕዝብ በቀጥታ በራዲዮና በቴለቪዥን በተላለፈው ንግግራቸው ፑቲን ሩሲያ በቱርክ ላይ የምታደርገው የአጸፋ መልስ በንግድ ማዕቀብ ላይ ብቻ የሚወሰን አለመሆኑን  ገልጸዋል። አክለውም በኃላፊነቱ የሚጠየቀው የቱርክ አመራር እንጅ የቱርክ ሕዝብ እንዳልሆነ ገልጸው የቱርክ አመራር ከአሸባሪው ከአይሲስ ቡድን ጋር ጥብቅ ግንኙነት ስላለው አይሲስን እየረዳ ነው ብለዋል።  ሩሲያ  ከአንድ ሺ ዓመት በላይ የቆየ፤ ወታደራዊ ጥንካሬ ያላትና በራሷ የምትተማመን ኩሩ አገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። የቱርክ ባለስልጣኖች የሩሲያ አውሮፕላን በቱርክ የአየር ክልል መመታቱን በድጋሚ አስታውቀው ከአይሲስ ጋር የንግድ ግንኙነት አለ የተባለውን ክስ ክደዋል።  

 

Ø በተባበሩት መንግስታት ድርጅት  የደቡብ ሱዳን አምባሳደር በመሆን የተሰየሙት በአገራቸው በተመድ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሰፈሩት 180 ሺ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ የቤታቸው እንዲሄዱ መደረግ አለባቸው በማለት ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑ ታወቀ። አምባሳደሩ  በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ እየተካሄዱ ያሉ ወንጀሎችና ግድያዎች እንዲሁም በሰፋሪው ላይ የሚታየው አሳዛኝ የኑሮ ሁኔታ ያሳሰባቸው መሆኑን ጠቅሰው የተኩስ አቁም ስምምነቱ በስራ ላይ እየዋለ በመሆኑ ሰፋሪዎቹ ወደ የቤታቸው እንዲሂዱ ማበረታትና መግፋት ያስፈልጋል ብለዋል። በደቡብ ሰዳን የሚገኘውን የተመድ የሰላም ኃይል ይዞታን ለማጠናከር 500 ተጫማሪ ወታደሮች 600 ተጨማሪ ፖሊሶች ተጨማሪ ሄሊኮፕተሮችና ድሮኖች እንዲሚደቡ የተመድ ዋና ጸሐፊ የጸጥታውን ምክር ቤት መጠየቃቸው ተገልጿል።






  ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም.

Ø ከአንድ ዓመት ከስምንት  ወር በፊት በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ ተይዘውና በወያኔ ቁጥጥር ስር ተደረገው እስካሁን በእስር ላይ የሚገኙት የቀደሞ የወያኔ የጋምቤላ ክልል አስተዳዳሪ አቶ ኦኬሎ አኳይ ኦቻላ በሽብር ወንጀል ተከሰው ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታውቋል። አቶ ኦኬሎ አኳይ ኦቻላ በተያዙ ጊዜ በሽብረተኛነት መከሰሳቸው የሚታወቅ ከክሶቹም ውስጥ ከፊሎቹ “የክልሉን ሕዝብ ለአመጽ ካነሳሱ በኋላ ኃላፊነታቸውን ጥለው ከአገር በመውጣት በአሸባሪ ድርጅት ውስጥ ተሳትፈዋል”፤ በጸረ ሽብር ኃይሎች መገናኚያ ብዙሃን አማካይነት የክልሉን ህዝብ ለአመጽ አነሳስተዋል የሚሉት ነበሩ። አቶ ኦኬሎ ለፍርዱ ቤቱ በሰጡት ቃል በክልሉ ከአስር ዓመት በፊት ለደረሰው የዜጎች ግድያና ጭፍጨፋ በዋናነት ተጠያቂ የሚሆኑት መለሰ ዜናዊ፤ አዲሱ ለገሰና በረከት ስምኦን መሆናቸውን ገልጸው እነሱ በፈጸሙት ወንጀል እሳቸው ተጠያቂ መሆን የሌለባቸው መሆኑን በመግለጽ ተከራክረዋል።፡ የቀድሞ የፌዴራል ጉዳዮች ሹም የነበረው ዶክተር ገብረአብ ባርናባስም ግድያውን በማስፈጸም በኩል ቀዳሚ ሚና እንደተጫወተም አጋልጠውል።   በወቅቱ በወያኔ ወታደሮች የተገደሉት ዜጎች ቁጥር ከ400 በላይ ሆኖ ሳለ 60 ብቻ ነው የሞተው ብለህ ተናገር ተብለው በወያኔ ባለስልጣኖች መታዘዛቸውን ገልጸው ትእዛዙን ሳያከብሩ መቅረታቸውን አስረድተዋል።

 

Ø በጎንደር በተለምዶ ባህታ ተብሎ የሚታወቀው እስር ቤት በትናንትናው ዕለት በእሳት የጋየ መሆኑን ታውቋል። ቃጠሎ የተነሳበት ምክንያት ያልታወቀ ሲሆን ከእስር ቤቱ በርካታ እስረኞች ማምለጣቸው በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። እስረኞች ሲያመልጡ በወያኔ  ወታደሮች በተተኮሰ የእሩምታ ጥይት  ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን የሞቱት ከ40 በላይ መሆናቸውም እየተነገረ ነው። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎችም በወያኔ የጸጥታ ስራተኞች ታፍነው ወደ አልታወቀ ስፍራ የተወሰዱ መሆናቸውንም የአይን እማኞች ተናገረዋል።    

Ø የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በተለያዩ ቦታዎች የሚደረገው የተቃውሞ እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት በነቀምት ከተማ የወለጋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ነዋሪው ሕዝብ ከፍተኛ ተቃውሞ በማድረጉ የወያኔ አግዓዚ ሰራዊት በተከተማዋ የተሰማራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ። መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ከመደረጋቸውም በላይ የንግድ ሱቆች መስሪያ ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውና መብራትም እንደጠፋ ተሰምቷል።  በተያያዘ ዜና በአምቦ አመጽ አስነስታችኋል ተብለው የተያዙ ዜጎች ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ምርመራ መወሰዳቸውን  ከአካባቢው ከመጣ መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቀንደኛነት አመጹን አስተባብራችኋል  ከተባሉት መካከል አበበ ቃበታ እና ሳሙዔል ነገዎች የሚባሉ ዜጎች የሚገኙበት ሲሆን ሌሎችም ስማቸውን ለጊዜው ማወቅ ያልታቻለ በርካታ ሰዎች እንደተወሰዱ ታውቋል። በልዩ ልዩ ቦታዎች ዩነቨርስቲዎችና ትምህርት ቤቶች እየተዘጉ መሆናችውም እየተነገረ ነው።

 

Ø የወያኔ የመከላከያ ደህንነት አባል በሆነ ግለስብ አለአግባብ እንዲደበደብ መመሪያ ሰጥቷል፤  በሚል ክስ የተወነጀለው  በሐረር የወያኔው የፈዴራል ፖሊስ ሹም በጥብቅ እየተፈለገ መሆኑ ታወቀ። በድብደባ ተጎዳ የተባለው የወያኔ ሰራዊት አባል ለህክምና ወደ አዲስ አበባ የጦር ኃይሎች ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን የፌዴራል ፖሊስ ሹሙን ለመፈለግ የወያኔ ወታደሮች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የነዋሪዎችን መኖሪያ ቤቶ እየፈተሹና ህዝቡን እያሸበሩ መሆናቸው ታውቋል። በተለይ ከራስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኙ መኖሪያ ሰፈሮችና ወደ ቢራ ፋብሪካ በሚወስደው መንገድ አቅራቢ ነዋሪ የሆኑ ዜጎች ስላማቸው የታወከ መሆኑን መሸበራቸውን በምሬት ሲናገሩ ተደምጠዋል። የወያኔ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊሱ ጠብ መነሻ ምን እንደሆን ባይታወቅም ቀደም ብሎ አንድ የፖሊስ አባል በወታደሮች ተገድሎ ስለነበር ከዚያ ጋር በተያያዘ የመበቃቀል እርምጃ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ አሉ።

 

Ø አምነስቲ ኢንተርናሽናል በሚል ስም የሚጠራው የአለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት በዛሬው ዕለት ባሰራጨው ዘገባ የሻዕቢያ መንግስት በዜጎቹ ላይ የጫነው የወታደራዊ አገልግሎት ግዳጅ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ካለ በኋላ ዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ይህን የሻቢያ የግዳጅ ወታደራዊ አግልጎት  በሰባአዊ መብት ጥሰትነት መድቦና  አውግዞ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ ባደረገው ዘገባ በተለይ ወደ አውሮፓ የሚጓዙት አብዛኞቹ ኤርትራውያን ሰደተኞች ከአገራቸው የሚወጡት ይህንን የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎት በመፍራት መሆኑን ድርጅቱ ካነጋገራቸው ስደተኞች የተረዳ መሆኑን ገልጸዋል። የወታደራዊ አገልግሎት ስራ በጣም አድካሚ አስቸጋሪ  መሆኑና ግዳጁን አንፈጽምም በሚሉት ላይ የሚወሰደው ቅጣት ከባድ መሆኑን የሚያስረዱ መረጃዎች ከስደተኞቹ የተገኙ መሆናቸውን ድርጅት በዘገባው ላይ አካትቷል።

 

Ø ከአምስት ዓመት በፊት በጊኒ  የሽግግር መንግስት መሪ የነበሩትና ከዚያ በኋላ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አሰባሪ ኃይል ተጠሪ ተደርገው በድርጅት ተሰይመው የነበሩት ጄኔራል ሴኩባ ኮናቴ በርካታ ገንዘብ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ወደ አሜሪካ ለማስገባት ሞክረዋል በሚል ቀርቦባቸው የነበረውን ክስ በመቀበል ጥፋተኛነታቸውን ማመናቸው ተነገረ። ከሁለት ዓመት በፊት 64 ሺ የአሜሪካን ዶላር በሻንጣቸው ይዘው ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የተያዙት ጄኔራል በትናንትናው ቀን ፍርድ ቤት ለመቅረብ ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበረ ቢሆንም ጥፋታቸውን በማመናቸውና ከፍርድ ቤት ውጭ ስምምነት በማድረጋቸው ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ የተደረገ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ከፍርድ ቤት ውጭ በተደረገው ስምምነት መሰረት ጄኔራሉ በአምስት አመት እስራት የሚቀጡ መሆናቸውም ተነግሯል።

 

Ø በሰሜን ካሜሩን ዋዛ በሚባለው አካባቢ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷችው ቦምቦች ከአሸባሪዎቹ ጋር ባጠቃላይ ስድስት ሰዎች መሞታችው ተነግሯል። ቦኮሃራም የሚባለው አሸባሪ ቡድን ቀደም ብሎ በአካባቢ ጥቃት ሲያደርስ የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የትናንቱንም ጥቃት የፈጽሙት የዚሁ ድርጅት ታጣቂዎች ናቸው የሚል ግመት አለ።

 

Ø በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራም በዛሬው ሌሊት ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውን የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል። ከሞቱት መካከል አንደኛው የፖሊስ አባል ሲሆን ሌሎቹ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸው ታውቋል። የተኩስና የፍንዳታ ድምጾች በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች ሲሰሙ ያደሩ መሆናቸውም ተገልጿል።

 

Ø በናይጄሪያ በቢያፍራ ግዛት የተቀሰቀሰውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለመግታት ተጨማሪ የፌዴራል የፕሊስ ኃይል ወደ ቦታው የተላከ መሆኑ ተነግሯል። የአካባቢው ፖሊሶች ማንኛውንም ሕዝባዊ ስብሰባና የቡድን እንቅስቃሴ እንዲበትኑ ጥብቅ ትእዛዝ የተሰጠ ሲሆን ሕዝቡን በቀንደኛነት ለአመጽ ያነሳሳሉ ተብሎ የሚጠረሩ ዜጎችም ታስረው ለፍርድ እንዲቀርቡ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ተነግሯል። የቢያፍራ ግዛት ከናይጄሪያ እንድተገነጠል የሚቀሰቅሱ ክፍሎች እየተንቀሳቀሱ መሆናችው የሚታወቅ ሲሆን የአሁኑ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የጀመረበት ምክንያት ከጥቂት ጊዜ በፊት መቀመጫውን ለንደን በማድረግ የመገንጠልን መንፈስ የያዘ ፕሮጋንዳ ለአመታት ሲያስተላልፍ የነበረው ናምዲ ካኑ የተባለው ግለስብ መያዙን አለፍርድ መቆየቱን በመቃወም ነው ተብሏል።

 

Ø ዛሬ ጠዋት በምስራቅ ሊቢያ  የወታደራዊ ኦፕሬሽን መሪ የነበሩ ኮሎኔል አሊ አልቶማን የሚባሉ መኮንን በተቀበረ ፈንጅ ፍንዳታ የተገደሉ መሆናቸውን አንድ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ከቤንጋዚ ባስተላልፈው ዜና ገልጿል። መኮንኑ የቤንጋዚ ወታደራዊ ኦፕሬሽን መሪ ሲሆኑ በቅርቡ አክራሪ አማጽያንና የአይሲስን ቡድን ከቤንጋዚ ለማስወጣት በተካሄደው ወታደራዊ እርምጃ ቁልፍ ሚና የነበራቸው መሆኑ ይነገራል። የሊቢያው መሪ ጋዳፊ ከስልጣናቸው ከተወገዱ ጀምሮ በሊቢያ በርካታ የታጠቁ ኃይሎ እየተንቀሳቀሱ አገሪቱን እያመሷት ሲሆን  ራሳቸውን መንግስት ብለው የሰየሙ የ ሁለት ክፍሎች በአገሪቱ ምስራቅና ምእራብ አስተዳዳሮች  መስርተው ይገኛሉ።   

ህዳር 21 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአገሪቷ ላይ በተከሰተው የዝናም እጥረት ምክንያት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቦች በቂ ውሃ ሊያቁሩ ባለመቻላቸው ካለፈው በባሰ ሁኔታ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚይቋረጥ መሆኑን የወያኔ ባለስልጣኖች እየየተናገሩ ይገኛሉ። ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ጊቤ አንድ እና ሁለት የተባሉትና እንዲሁም በጣና በለስ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያዎች ላለፉት ሁለት ቀናት አገልግሎት አቋርጠው የነበሩ መሆናቸው ተገልጿል።  

የድርቁ ሁኔታ እየከፋ ሲመጣ የመብራት መጥፋትም እየተባባሰ እንደሚሄድ ከወዲሁ እየተነገረ ነው። የክረምቱ ወራት ካለፈ ገና ሁለት ወር ቢሆነውም የተከዜ፤ የቆቃና የመልካዋከና ግድቦች ውሃ በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱ ታውቋል።

 

Ø በተያያዘ ዜና ኅዳር 19 ቀን 2008 / ከረፋድ በኋላ ወያኔ ብዙ የተወራለት የአዲስ አበባው ቀላል ባቡር በመብራት መጥፋት ምክንያት ስራ ማቆሙና በወቅቱ ተሳፍረው የነበሩ ተሳፋሪዎች ድንገት ከቆመው በሩ ተዘግቶባቸው ለረዥም ጊዜ ከባቡሩ ሳይወርዱ መቆየታቸውን ለማወቅ ተችሏል።  ይህ የወደፊቱ ትውልድ በቀላሉ ሊከፍለው በማይችለው ብድር የተሰራው ቀላል ባቡር ወያኔ ለፖሊቲካ ፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ አድሮጎት የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መብራት ቢጠፋ እንኳ ራሱ በሚያጠራቅመው የኤሌክትሪክ ኃይል ይጓዛል እንጅ በፍጹም አገልግሎቱ አይቋረጥም እየተባለ ዲስኩር ሲሰጥበት መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ፍጥነቱ ከኤሊ ጉዞ ያልተሻለ ነው እየተባለ የሚታማው የከተማው ባቡር ህዳር 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ወገቤን በማለት ተሳፋሪዎችን እንደያዘ መሃል መንገድ ተገትሮ መቅረቱ ታውቋል።  

 

Ø በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም መሬቶችን ለመቀራመት የወያኔ ባለስልጣኖችት ያወጡትን እቅድ በመቃወም በተለያዩ ከተሞች የሚደረጉት የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የቀጠሉ መሆናቸው ከየቦታው የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ። ቀደም ብሎ በሃረማያ ዩነቨርስቲ ተቃውሞ ሲያሰሙ በነበሩ ተማሪዎች ላይ የወያኔ ፌዴራል ፖሊስ በወሰደው የጭካኔ እርምጃ የሞቱና የቆሰሉ ተማሪዎች መኖራቸው የተገለጸ ሲሆን   በባሌ መደወላቡ በተባለው ዩነቨርሲቲ ውስጥም  ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ታውቋል።

 

 

Ø በቡርኪና ፋሶ እሁድ ዕለት በተካሄደው ምርጫ ሚስተር ክርስቲያን ካቦሬ የተባሉት የቀድሞ መንግስት ሚኒስትርና የፓርቲው መሪ የጠቅላላውን ድምጽ 53.5 ከመቶ በማሸነፍ የሚቀጥለው የቡርኪና ፋሲ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን የአገሪቱ የምርጫ ቦርድ ገለጸ። ፕሬዚዳንቱ በቂ ድምጽ በማግኘታቸውም ሁለተኛ ዙር ምርጫ የማይካሄድ መሆኑም ተገልጿል። ሚስተር ካቦሬ ለሃያ ሰባት ዓመት በመሪነት የቆዩት የቀድሞ የአገሪቷ ፕሬዚዳንት ካምፓወሬ ለሌላ አምስት አመት ጊዜ ለመወዳደር ያወጡትን ፕላን በመቃወማቸው ከስልጣን የተገለሉ መሆናቸው ሲታወቅ የቀድሞው ፕሬዚዳንት በሕዝብ አመጽ ተገደው  ሲወርዱ ካቦሬ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፈው እንደነበር ይታወቃል።

 

Ø የቀድሞ የናይጄሪያ የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ ሚስተር ሳምቦ ዳሱኪ ሁለት ቢሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ ሰርቀዋል ተብለው ዛሬ ጠዋት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ተይዘው  ተወስደው በቁጥጥር ስር የተደረጉ መሆናቸው ታውቋል። ሚስተር ዳሱኪ የተከሰሱት አስራ ሁለት ሄሊኮፕተሮችን ሁለት ተዋጊ አውሮፕላኖችን እና መጠናቸው ከፍተኛ የሆኑ የጦር መሳሪያና ጥይቶችን ለመግዛት የሀሰት ስምምነት አድርገው ገንዘቡን ለራሳቸው ጥቅም አውለዋል በሚል ክስ ነው። የዛሬ ሁለት ሳምንት የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ  ሚስተር ዱሲኪ እንዲታሰሩ ካዘዙ ጀምሮ ግለሰቡ በቤታቸው ውስጥ በቁም እስር ላይ እንደነበሩ ይታወቃል። ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው  አንድ ቀን ቀደም ብሎ ተባባሪያቸው ናቸው የተባሉ የቀድሞ መንግስት ሚኒስትሮችና የቀድሞ ገዥ ፓርቲ ሹማንንት ልጆች የታሰሩ መሆናቸውም ተገልጿል። ሚስተር ዳሱኪ ክሱን ከመካዳቸው በተጨማሪ በራሳቸው በኩል ያለውን ሁኔታ ለማስረዳት እድል ያልተሰጣቸው መሆኑን ገልጸው በእሳቸው ላይ ለተወሰደው እርምጃ ምክንያቱ ፖለቲካዊ ነው ብለዋል።

 

Ø በብሩንዲ እየተባበሰ የሄደውን የእርስ በርስ ግጭት ለመግታት አስቸኳይ እርምጃ መወሰድ አለበት በማለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን አሳሰቡ። ባንኪ ሙን ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ሰኞ ዕለት በላኩት የደብዳቤ መልእክት ሶስት አማራጮችን ያቀረቡ ሲሆን ከምርጫዎቹ መካከል በተመድ የሚመራ  የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የሚከታተል፤ የእርቅ ውይይቶች እንዲደረጉ የሚገፋፋ እና ምናልባት የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ቦታው ሊገባ የሚችልበትን ሁኔታ የሚያጠና አንድ የተመድ ቡድን ወደ አገሪቱ እንዲላክ ጠይቀዋል። ዋና ጸሐፊው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ የሚላክበትን መንገድ ሙሉ በሙሉ ባይዘጉም ባሁኑ ወቅት አስፈላጊ አይደለም ብለዋል። ሰኞ ዕለት በዝግ ስብሰባ የተወያየው የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በቅርቡ አንድ የተባበሩት መንግስታት ቡድን ወደ ብሩንዲ ለመላክ ሳይወስን አይቀርም ተብሏል።

 

Ø ስትራትሞር በሚባለው የኬኒያ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተማሪዎች የሽብር ተግባሮችን በሚገባ ለመቋቋም የሚያስችላችውን ልምምድ እያደረጉ ባሉበት ወቅት በድንገት በተፈጠረ ድንጋጤና ሽብር ከፍተኛ የእርስ በርስ ግፊያ ተከስቶ አንድ ተማሪ ሲሞት 141 የሚሆኑ መጎዳታቸው ታውቋል። ከወትሮ  ለየት ያሉ ከፍተኛ ድምጾች በድንገት በመሰማታቸውና አንዳንድ ሰዎች አሸባሪዎችን መስለው በከፍተኛ ደረጃ በመንቀሳቀሳቸው  በተማሪዎች ውስጥ ፍርሃት በመፍጠሩ ሁሉም በአንድ አቅጣጫ ሲሞክር በተነሳው ግፊያ ጉዳት ሊደርስ ችሏል ተብሏል። ኬኒያ አልሸባብን ለመቋቋም ሶማሊያ ውስጥ ጦሯን ከላከች ጀምሮ በአልሸባብ ሽብረተኞች በተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰባት መሆኑ ይታወሳል።

 

Ø አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን በሲሪያ ውስጥ በተቆጣጠረው የነዳጅ ማምረቻ የሚመረትና በኢንዱስትሪ ድረጃ ጥቅም ላይ የሚውል የነዳጅ ዘይት የነዳጅ ዘይት ቱርክ በግዥ ወደ አገሯ እንደምታሰገባ ተጨማሪ መረጃ ደርሶናል ሲሉ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ፑቲን ተናገረዋል። የሩሲያ ፕሬዚዳንት ጨምረው እንደተናገሩት ቱርክ የሩሲያ የጦር አውሮፕላን መትታ የጣለቸው ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ከአይሲስ ተገዝቶ ወደ ቱርክ የሚላከውን ነዳጅ ለማሰናከል የሩሲያ የጦር አውሮፕላኖች እርምጃ በመውሰዳቸው ነው ብለዋል። የከባቢ አየር ብክለትን ለመቆጣጠር በፓሪስ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ  ስብስባ ላይ የተገኙት የቱርክ ፕሬዚዳንት ሰኞ ዕለት ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ የፕሬዚዳንት ፑቲንን ክስ አስተባብለው እውነትነቱን የሚያረጋግጥ መረጃ ከተገኘ ከስልጣኔ እለቃለሁ ብለዋል። ቱርክ በአይሲስ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ስታቅማማ የቆየች ከመሆኑንም በላይ በአሜሪካ መሪነት በአይሲስ ላይ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ላይ የተካፈለችው ዘግይታ መሆኗን ጉዳዩን በቅርብ የተከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ። የቱርክ ፕሬዚዳንትም ቱርክ የሩሲያን አውሮፕላን መትታ በመጣሏ ይቅርታ አትጠይቅም ብለዋል። በተያያዘ ዜና በቱርክ ተመቶ የወደቀውን የሩሲያ አውሮፕላን አብራሪ የነበረውና በጃንጥላ ሲወርድ በአማጽያን የተገደለው ፓይለት አስከሬንን ቱርክ ለሩሲያ ያስረከበች መሆኗ የተገለጸ ሲሆን አስከሬኑም ሞስኮ የገባ መሆኑ ተነግሯል።



ህዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም


Ø ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የመጠጥ ውኃ  ከሚሰራጭባቸው ግድቦች መካከል አንዱና ዋናው በሆነው በለገዳዲ ግድብ የውኃ እጥረት መከሰቱን  ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቸ ገልጸዋል።   በአገሪቱ ውስጥ በገባው ድርቅና የዝናብ እጥረት ምክንያት  በለገዳዲ የውኃ ማጠራቀሚያ ግድብ ውስጥ መኖር የነበረበት የውሃ መጠን  በጣም  እያነሰ በመምጣቱ ከዚህ ግድብ ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚሰራጨው ውኃ በፈረቃ እንዲሆን የወያኔ ባለስልጣኖች የወሰኑ መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል።  ከለገዳዲ ጀምሮ በአንቆርጫ አድርጎ እስከ ሽሮ ሜዳ ድረስ ወደ ሰባት የሚጠጉ የውሃ ማከማቻ ቦታዎች ያሉ ሲሆን ውሃውን በእነዚህ ማጠራቀሚያዎች ውስጥ ማስገባት ባለመቻሉ ሚስጥራዊ በሆነ መንገድ የፈረቃ ስርጭት ማድረግ ግዴታ ነው በማለት ባለስልጣኖቹ  የወሰኑ መሆኑ ታውቋል።  ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ለመስመር ኃላፊዎች መመሪያ የተሰጠ ከመሆኑም በላይ ውሃው በሚቋረጥበት ወቅትም አብሮ መብራት እንዲጠፋ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን በተጨማሪ የደረሰን ዜና ይገልጻል።  ከአራት ኪሎ ጀምሮ እስከ ሽሮ ሜዳ ባሉ የመኖሪያ ቦታዎች የመጠጥ ውኃ ከጠፋ ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን  ከለገዳዲ የሚሰራጨውን ውሃ በሚጠቀሙ ሌሎች አካባቢዎችም ውሃው  ለይስሙላ ሌሊት 11 ሰዓት ላይ ይለቀቅና ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ እንዲቋረጥ የሚደረግ መሆኑን ዘገባው ጨምሮ አስረድቷል።

 

 

Ø በትናንትናው ዕለት በ100 ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች  የከባቢ አየር ለውጥ አስመልክቶ  በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሰላማዊ ስልፎችንና ስብሰባዎችን ያደረጉ መሆኑ ታወቀ። በተለያዩ ቦታዎች ሰልፉን ያካሄዱት ዜጎች  እየተባለሸ የሄደውን የዓለም የከባቢ አየር ሁኔታ ለመቋቋም በዛሬው ዕለት በፓሪስ ከተማ በሚጀመረው ዓለም አቀፍ ስብስባ ላይ ተጨባጭ ስምምነት እንዲደረግ  መንግስቶቻቸው ላይ ጫና ለመፍጠር ነው ተብሏል።  በ170 አገሮች ውስጥ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ ሰዎች የተሳተፉባቸው ሰልፎች በሙሉ በስላም የተከናወኑ ሲሆን በፓሪስ ላይ የነብረው ስብስብ ግን በፖሊሶች የተበተነ  ከመሆኑም በላይ ህግን ተላልፋችኋል ተብለው ከ200 በላይ  የሆኑ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል። በፓሪስ ባለፈው ሁለት ሳምንት በከተማዋ ላይ በደረሰው የሽብር ተግባር ምክንያት ስብሰባዎችና ሰልፎች የተከለከሉ በመሆናቸው በመሃል ከተማ ውስጥ ለመሰብሰብ የሞከሩትን ሰዎች ፖሊሶች በትነዋል፤ አንዳንዶቹ አስረዋል። ሌሎች  የፓሪስ ነዋሪዎች በየመንገዱ ዳርቻ እጅ ለጅ ተያዘው ድምጻቸውን ያሰሙ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ ጫማቸውን በአደባባይ ላይ በማስቀመጥ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።  በኒውዩርክ በአውስታሊያ በባንግላዴሽና በእንግሊዝ የተደረጉት ሰልፎች ባለፈው ዓመት ከተደረጉት ሰልፎች የበለጠ መሆኑ ተገልጿል። ከሰልፉ በተጨማሪ በተለያዩ አገሮች 1.8 ሚሊዮን የሚሆኑ የተለያዩ አገር ዜጎች ፊርማቸውን በማስቀመጥ የከባቢ አየር ሙቀትን  ለመቋቋም አስቸኳይ ርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠይቀዋል።

 

Ø በከባቢ አየር ላይ እየጨመረ የመጣውን የሙቀት መጠን  ለመቋቋም የሚደረገው ዓለም አቀፍ ስብሰባ በዛሬው ዕለት በፓሪስ የተጀመረ ሲሆን የ150 አገሮች መሪዎችና 22ሺ የሚሆኑ ሌሎች ባለስልጣኖች ተገኝተዋል ተብሏል።  የሙቀቱ መጠን 2 ድግሪ ሴልሸስ ይጨምራል ተብሎ የሚገመተውን የዓለማችንን የከባቢ አየር ለውጥን ለመቋቋም እያንዳንዱ አገር  የካርቦን ጭስን በማሰረጨት በከባቢ አየር ላይ የሚያደርገውን ብክለት እንዲቀንስ የሚያስችለው ተጨባጭ እርምጃዎች ላይ ተሰብሳቢዎቹ ስምምነት ላይ ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø በትናትናው ዕለት የሮማው ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ  በዩጋንዳ የሚያደርጉትን ጉብኝት አጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የጸጥታ ውጥረት ያለባትን የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክን ለመጎብኘት በዋና ከተማው ባንጉዊ ገብተዋል። ጳጳሱ ባንጉዊ ሲገቡ ከአውሮፕላን ጣቢያ ጀምሮ በርካታ ሕዝብ በደስታ የተቀበላቸው ከመሆኑ በላይ በቤተ መንግስቱ ውስጥ በተደረገው የአቀባብል ስነስርዓት ላይ ባሰሙት ንግግር ስዎች በሌሎች ሰዎች ላይ፤ በሌሎች ጎሳዎች፤  በሌሎች ሃይማኖች ላይ ያለቸውን ጥላቻና ፍርሃት አስወግደው ወደ አንድነት መምጣት ይበጃቸዋ ብለዋል። ከከተማዋ ወጣ ብሎ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት  ያካሄዱትን ስርዓተ ቅዳሴ ፈጽመው ባደረጉት ንግግርም  በአገሪቱ የሚገኙ የአማጽያን ኃይሎች አባላት  መሳሪያቸውን አውርደው ፍትሕን፤ ፍቅርን፤ ይቅርታን እና ሰላምን እንዲታጠቁ ጠይቀዋል።   በዛሬው ዕለትም ባንጉዊ ከተማ ውስጥ የእስልምና ተከታይ የሆኑ ዜጎች ወደ ሚኖሩበት ስፍራ ሄደው መስጊድ ውስጥ ባደረጉት ንግግር  የክርስትናና የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወንድማማቾችና እህትማማቾች ስለሆኑ  በአንድ ላይ በፍቅር  መኖር አለባቸው የሚል መልክት አስተላልፈዋል።  ሁከትና ሽብር በበዛባት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ውስጥ ጳጳሱ ያደረጉት ጉብኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø በደቡብ ሱዳን በአማጽያኑና በሳልቫ ኬር በሚመራው የመንግስት ክፍል መካከል ሲደረጉ የቆዩ ስምምነቶች በተደጋጋሚ መጣሳቸው የሚታወስ ሲሆን ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ የተደረገው የመጨረሻው ስምምነትም አደጋ የተጋረጠበት መሆኑን የአፍርካ ህብረት ተወካዮች እየገለጹ ይገኛሉ። በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ድጋፍ ያላቸውና  የተኩስ አቁም ሁኔታ ለመከታተል የተመደቡ ታዛቢዎች ባለፈው ዓርብ በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ውስጥ የመጀመሪያ ስብሰባቸውን ያደረጉ ሲሆን ከአማጽያን በኩል የተመደቡት ተወካዮች በስብሰባው ሳይገኙ ቀርተዋል። የአፍሪካ ህብረት ተወካይ በገለጹት መሰረት የአማጽያኑ ተወካይ የክትትልና የግምገማ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ሁሉም ወገን መገኘት ሲገባቸው የአማጽያኑ ተወካዮች አለመገኘታቸው ሁኔታውን አሳሳቢ ያደረገዋል ብለዋል። አሜሪካ እንግሊዝና ኖርዌይ ተደራዳሪዎቹ በስበስው ካልተገኙ ስምምነቱ ሊፈርስ ይችላል ብለዋል።

 

Ø በምስራቅ ኮንጎ ኢሬንጌቲ በተባለችው ከተማ ውስጥ  በአማጽያንና በመግንስት ወታደሮች መካከል በተደረገ ግጭት 30 ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ከአካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ አድርጎ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና ወኪል ገልጿል። በትናንትናው ዕለት ራሱን የየተባበሩት የመከላከያ ኃይሎች ብሎ በሚጠራውና በመንግስቱ ወታደሮች መካከል የተካሄደው ውጊያ ለአስር ሰዓታት የቆየ ሲሆን ከሞቱት መካከል አንድ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል፤ እንዲሁም ሰላማዊ ሰዎችና ወታደሮች እንዳሉበት ታውቋል።  በከተማዋ ውስጥ 43 ቤቶች ሲቃጠሉ 10 ሰዎችም ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተነግሯል። ከዚህ በፊት አካባቢው ከዩጋንዳ በሚሚጡ አማጽያን ተድጋጋሚ ጥቃት የደረሰበት ሲሆን ባለፈው ዓመት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል እና የመንግስቱ ወታደሮች የአማጽያኑን ጥቃት ለመቋቋም ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ ማድረጋቸው ይታወሳል።

 

Ø በቡርኪና ፋሶ ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ የነበሩት መሪ በሕዝባዊ አመጽ ከተወገዱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በትናንትናው ዕለት አጠቃላይ ምርጫ ተካሂዷል። በትናንትናው ምርጫ 18 ሚሊዮን ሕዝብ ድምጹን ሰጥቷል ተብሎ የተገመተ ሲሆን የጸጥታው ሁኔታ ጥብቅ የነበረ መሆኑም ታውቋል። ምርጫው የተካሄደው ለፕሬዚዳንት ቦታ እና ለህግ አውጭው ምክር ቤት ሲሆን በርካታ ፓርቲዎች የተሳተፉ መሆናቸው ተነግሯል።  የቀድሞ መንግስት ባለስልጣኖችና ከስልጣን የተወገዱት ፕሬዚዳንት ቀንደኛ ደጋፊዎች ከውድድር ውጭ የተደረጉ ቢሆን ኮንግሬስ ፎር ዴሞክራሲ (CDP) የተባለው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ፓርቲ ተወካዮችን በማሰማራት እንዲወዳደር ተድርጓል። የትናንቱ ምርጫ ለረዥም ጊዜ ለቆየው ለሕዝቡ የዴሞክራሲ ጥያቄ መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።  ከሰላሳ ዓመት በላይ አገሪቷን ሲመሩ የቆየት ፕሬዚዳንት ካምፓወሬ ባለፈው ዓመት በሕዝባዊ አመጽ ተገድደው ስልጣናቸውን እንዲለቁ የተደረጉ መሆናቸውና ምርጫ እስኪደረግ ድረስ የሽግግር አስተዳደር ተሰይሞ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ባለፈው መስከረም ወር የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ የሆኑ ወታደሮች የሞከሩት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በሕዝብ አመጽ መክሸፉ እንዲሁም  መሪዎቹ መታሰራቸውና ተቋሙ መፍረሱም አይዘነጋም።  የምርጫው የመጀመሪያ ውጤት በዛሬው ዕለት ይገለጻል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን ማንም አሸነፈ ማን ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ እየጠበቀ ያለውን የሚመጠን ስራ ለመስራት ብርቱ ጥረት ይጠይቃል የሚሉ በርካታ ናቸው።





ህዳር 18
ቀን 2008 ዓ.ም 

Ø በአማራው አካባቢ ድርቁና ረሃቡ በከፋባቸው አካባቢዎች በተለይም  ወሎ ውስጥ አበርገሌ፤ ሰቆጣ፤ አርባጩፋ በተባሉ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች ረሃቡን መቋቋም አቅቷቸው ወደ መሃል ከተሞች በመሰደድ ላይ መሆናቸው ታውቋል። በዘንድሮ ድርቅ  የሰሊጥና የጤፍ አዝመራቸው በሙሉ የወደመ መሆኑ ብዙዎቹ ይናገራሉ። ተሰደው በሰፈሩበት ቦታ የሚሰጣቸው እርዳታ በቂ ካለመሆኑም በላይ የወያኔ ካድሬዎች አንተ የእገሌ ወገን ነህ አንተ የእገሌ ደጋፊ ነህ ስለሆነም እርዳታ አታገኝም በማለት የሚያንገላቷቸው መሆኑን እየተናገሩ ይገኛሉ። ይህ በንዲህ እንዳለ በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል ስድስት መቶ ሺህ ዜጎች የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው በአዋሳ የሚገኙ ክፍሎች ገለጹ ። ድርቅ አይደፍረውም እየተባለ የሚነገርለት የደቡብ አካባቢ ዘንድሮ ክፉኛ በድርቅ በመመታቱ ዜጎች የድርቅና የረሃብ ሰለባ ሆነዋል። በነብስ ወከፍ የአንድ ዙር እርዳታ መስጠት የተቻለው አርባ አምስት ሺህ ለሚሆኑት ብቻ ሲሆን ከአምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተረጂዎች አስቸኳይ እርዳታው ሊዳረስ ባለመቻሉ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ወድቀዋል ተብሏል። ተማሪዎችም በድርቁ ምክንያት ትምህርት ማቆም ሲሆን አንዳንዶቹም እየተሰደዱ መሆናቸው ታውቋል።   

 

 

 

Ø ሰሞኑን የአዲስ አበባ አስተዳደር ማስተር ፕላንን በመቃወም የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች እያካሄዱት ያለው እንቅስቃሴ  ተጠናክሮ በመቀጠሉ ውጥረቱ የተባባሰ ከመሆኑም በላይ ወደ አጎራባች ከተሞች የተዛመተ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በጊንጪ ከተማ ተማሪዎች በአካባቢያቸው እየተካሄደ ያለውን የመሬት ዘረፋ ተቃውመው መሰለፋቸው ታውቋል። በመንዲና በሌሎች ቦታዎች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችም ቀጥለዋል። የአግዓዚ ቅልብ  ወታደሮች የሚገኙበት የፌዴራል ፖሊስ አባላት በየከተሞቹ ነዋሪውን በተኩስ ከማሸበራቸው በላይ በርካታ ወጣቶችን በዱላ ቀጥቀጠው ጉዳት ላይ የጣሉ መሆናቸው ተነግሯል። የአካባቢው የወያኔ ባለስልጣናች ሃያ ብቻ ይበሉ እንጅ ከተለያዩ ቦታዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ተይዘው ወደ አልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውም ታውቋል።

 

Ø ባለፈው ሀሙስ ጠዋት የታንዛኒያ ፖሊስ በህገ ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብታችኋል በማለት  105 ኢትዮጵያውያንን ይዞ ማሰሩ ታወቀ። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት በዳሬሰላም ከተማ ውስጥ በሚገኘው ታቤታ ሳጌሪያ በተባለው ቀበሌ በአንድ ስሙ ባልተገለጸ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ መሆኑ ተነግሯል። ኢትዮጵያውያኑ ወደ ታንዛኒያ የመጡት በነፍስ ወከፍ አንድ ሺ ዶላር  እየተቀበለ በሚያስተላልፍ አንድ የብሩንዲ ተወላጅ አማካይነት እንደሆነ  የታንዛኒያ ፖሊሶች በምርመራ የደረሱበት መሆኑን ገልጸው ከምርመራው በኋላ ፍርድ ቤት የሚያቀርቧቸው መሆኑን ተናግረዋል። የወያኔ አስከፊ አገዛዝ በመሸሽ በሁሉም አቅጣጫዎች አገራቸውን እየጣሉ በህገ ወጥ መንገድ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውን ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን በታንዛኒያ የተያዙትም በተመሳሳይ መልክ አገራችው ውስጥ የሰላም ኑሮ መኖር ያቃታቸው ዜጎች ናቸው።

 

Ø የኬኒያ ጉብኝታቸውን አጠናቅቀው በትናንትናው ምሽት ኡጋንዳ የገቡት የሮማው ጳጳስ ከካምፓላ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ክፍት ቦታ ላይ በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ የካቶሊክ አማኞች በተገኙበት ስርዓተ ጸሎት ያካሄዱ መሆናቸው ተነገረ። ጳጳሱ ኡጋንዳ ሲገቡ ባደረጉት አጭር ንግግር ኡጋንዳ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊና እና ከደቡብ ሱዳን የመጡትን ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚገመቱትን ስደተኞች ማስተናገዷን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል። ጉብኝቴ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ለደሆዎች ለታሚሚዎችና ችግር ለደረሰባቸው ሁሉ እርዳታ እንዲደርግላቸው አበረታታለሁ ብለዋል። በዛሬው ዕለትም በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የዩጋንዳ ወጣቶች በተሰበሰቡበት ላይ ተገኝተው መልእክት አስተላልፈዋል።  በነገው ዕለት ወደ ማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቃል

 

Ø በሰሜናዊ ማሊ በተባበሩት መንግስታት ጦር ሰፈር ላይ ታጣቂዎች ባካሄዱት ጥቃት ሁለት የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትና አንደ ሰላማዊ ሰው የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ከእነዚህ በተጨማሪ 20 ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን የአራቱ ጉዳት ከበድ ያለ ነው ተብሏል። በታጣቂዎቹ የተገደሉት ሁለቱ የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት የጊኒ ተወላጆች ሲሆኑ ሰላምዊው ሰው ደግሞ ስራዎችን ተኮናትሮ የሚሰራ ግለሰብ ነው ተብሏል። ባለፈው ሳምንት በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ውስጥ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ በደረሰ ጥቃት 19 ሰዎች መገደላቸውና በርካታ ታግተው መለቀቃቸው ይታወሳል። በሰሜናዊ ናይጄሪያ ካኖ በሚባለው ግዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የሺያ እስልምናን የሚከተሉ ዜጎች እምነታቸው ለመግለጽና ሃይማኖታቸውን ለማስታወስ በየአመቱ የሚያደርጉትን የረጅም እርቀት  ጉዞ በሚያደርጉበት ወቅት የቦኮ ሃራም አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 21 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን ከአካባቢው የተገኘው ዜና ይገልጻል። ቦምቡ የፈነዳው ከካኖ ዋና ከተማ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዳካሶየ ከምትባለው መንደር ነው። ቀደም ብሎ በጥርጣሬ ፈንጅውን የአፈነዳውን ግለሰብ  በቁጥጥር ስር ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም ከመያዙ በፊት የታጠቀውን ቦምብ አፈንድቶ ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።  ተባባሪ በመሆን የተጠረጠረው ሌላው ግለሰብ ግን በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ጥቃቱን ለመፈጸም በቦኮሃራም የተላኩ መሆናቸውን ለመርማሪዎች ገልጿል። የቦምቡ ፍንዳታ ጉዳት ቢያስከትልም የእምነቱ ጉዞ ቀጥሎ በታቀደለት ሁኔታ ተፈጽሟል።

 

 

 

 

 

 

 

 

ህዳር 17 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø አዋሳኝ አካባቢዎችን ወደ  አዲስ አበባ ለማጠቃለል የወጣውንና እነ አባይ ጸሃዬ በግድ ተግባራዊ ለማድረግ እየጣሩ ያለውን እቅድ በመቃወም በአምቦ ከተማ ነዋሪዎች የሚደረገው እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን  የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተቃውሞውን እንዳይቀላቀሉ  ከፍተኛ ጥበቃ  እየተደረገ መሆኑን ከስፍራው የመጣው ዘገባ ያመለክታል።  ህዝባዊ ቁጣውን በኃይል ለማፈን ከአዲስ አበባ የፌዴራል አድማ በታኝ ኃይል ኅዳር 16 ቀን 17 አጥቢያ ወደ ስፍራው ያቀና መሆኑ የታመኑ የፖሊስ ምንጮች ይገልጻሉ። ዘጋቢያችን ከአምቦ ከተማ አጠናክሮ እስከላከልን  ኅዳር 17 2008 ዓም ረፋድ ድረስ በፖሊስ ዱላ በሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ሲታወቅ ወደ ሃያ የሚጠጉ የአምቦ ነዋሪ ፖሊሶች ጨለማን ተገን በማደረግ አፍነው  ወዳለታወቀ ቦታ የወሰዷቸው መሆኑን የአይን እማኞች መናገራቸው ተዘግቧል።

 

 

Ø ማዕከላዊ ምርመራ በሚባለው የወያኔ ማሰቃያ ስፍራ  በየቀኑ ቢያንስ 60 የሚሆኑ ሰዎች በጽኑ እንደሚገረፉና ከእነዚህም ውስጥ ቢያንስ አምስቱ ለጉዳት የሚዳረጉ መሆናቸውን ለማዕከላዊ ምርመራ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አጋለጡ። ድብደባው የሚደርስበት ዜጋ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መሄዱ በእጅጉ ያሳሰባቸው እነዚሁ ምንጮች ጨምረው እንደገለጹት በምርመራ ሽፋን ለሊት ለሊት ዘግናኝ ድብደባ የሚፈጸምባቸው ወጣቶች በብልታቸው ላይ ውሃ የተሞላ ኮዳ እንዲንጠለጠልባቸው መደረጉ ለከፋ ጉዳት የዳረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።   ከተለያዩ አካባቢዎች ታፍነው ወደ ማዕካለዊ ምርመራ የሚመጡና ድብደባ የሚፈጸምባቸው ወገኖች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ለቀረበው ጥያቄ ቁጥሩ በየጊዜው እንደሚለዋውጥና በአማካይ በየቀኑ  3ሚትር  3 ሚትር  በሆነ አንድ ክፍል ውስጥ ብቻ 40 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ተፋፍገው እንደሚታሰሩና በጠቅላላው አስር በሚሆኑ ክፍሎች ውስጥ ቢያንስ  አራት መቶ የሚሆኑ ክስ ያልተመሰረተባቸውና ወነጀላቸውን የማያውቁ ሰዎች እንደሚታሰሩ  ተናግረዋል። ከእነዚህ ውስጥ በአማካይ በየቀኑ ስድሳ የሚሆኑት ግርፋት እንደሚፈጸምባቸውና ቢያንስ አምስቱ ደግሞ ለከፋ ጉዳት እንደሚዳረጉ  ገልጸዋል።  ቤተሰቦቻቸው የት እንደታሰሩ እንኳን ስለማያውቁ  ብዙዎቹ እስረኞች ጠያቂም እንደሌላቸው ምንጮቹ አክለው አስረድተዋል።   

 

Ø የአባይ ግድብ ስራ መቀጠል ግብጽ በጣም እንዳሳሰባት የግብጽ የውሃ አገልግሎት ሚኒስትር አማካሪና የግድቡ ጉዳይ ቃል አቀባይ ማክሰኞ ዕለት በካይሮ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት በሁለቱ አጥኝ ቡድኖች መካከል በተነሳ አለመግባባት የታቀደው ጥናት መቋረጡን ግብጽ ያወገዘች መሆኑን ገልጸው ጉዳዩ የማይመለስበት ደረጃ ከመድረሱ በፊት ጥናቱ መቀጠል አለበት ብለዋል። ግድቡ ወደ ግብጽ የሚፈሰውን የውሃ መጠን ይቀንሳል ብላ አገራቸው በጽኑ ስለምታምን ጥናቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁለተኛው ዙር የግድቡ ስራ እንዲቋረጥ የግብጽ መንግስት በይፋ ወያኔን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል። 

 

Ø የኬኒያ ጉብኝታቸውን በዛሬው ቀን ያጠናቅቃሉ ተብለው የሚጠበቁት የሮማው ጳጳስ ኬኒያውያን አፍራሽ የሆነውን የዘር ልዩነት አስወግደው ወደ አንድነትን እንዲመጡ አሳሰቡ። በኬኒያ ዋና ከተማ ካሳራኒ በሚባለው የስፖርት ስታዲዩም ውስጥ  ለወጣቶች ባደረጉት ንግግር ላይ ጳጳሱ የአንድነት ጥሪ ከማሰማታቸው በላይ በስታዲዩሙ የተሰበሰበው አድማጭ አንድነቱን ለመግለጽ እጅ ለጅ እንዲያያዝ አድርገዋል። ጳጳሱ በንግግራቸው ውስጥ በየጊዜው በሙስና ወደኪስ የሚገባው ገንዘብ  “ልብን ይጎዳል፤ ማንነትን ያበላሻል  አገርንም ያጠፋል” በማለት በሙስና የተጨማለቁ ሰዎች በሰላም እንደማይኖሩ ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ብሎ ናይሮቢ  ውስጥ የሚገኘውን የድሆች መንደር ጎብኝተው በመንደሩ ውስጥ የሚኖሩት ስግብግብ በሆኑና ስልጣን ላይ ባሉ ሀብታሞች እየደረሰባቸው ያለው ጉዳት ከልብ የሚሰማቸው መሆኑን  ገልጸውላቸዋል።  

 

Ø ብሩንዲ ወደ አጠቃላይ ቀውስ እያመራች መሆኑን ግሬት ሌክስ በሚባለው የምስራቅ አፍሪካ አካባቢ የአሜሪካ ልዩ መልከተኛ  የሆኑ ባለስልጣን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ባለስልጣኑ ከጥቂት ሳምንታት በፊት አገራቸው በብሩንዲ የጸጥታ ሚኒስቴርና በሌሎች ስልጣኖች ላይ የጣለችውን ማዕቀብ አስታውሰው ወደፊትም እንደአስፈላጊነቱ በሌሎች ባለስልጣኖች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ ሊደረግ እንደሚችል አስረድተዋል። የቡርንዲው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ ለመወዳደር መወሰናቸው የችግሩ ምንጭ ሊሆን ቢችልም የአገሪቷ አጠቃላይ ችግር የፖለቲካ ችግር ነው ብለዋል። ከዚህ በፊት በአገሪቷ ተከስቶ እንደነበረው ዓይነት እልቂት ሊመጣ የሚችልበት እድል ከፍተኛ ስለሆኑ ሁኔታው ወደዚያ እንዳያመራ መንገዱን ለመዝጋት መጣር አለብን ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት አማካሪ የሆኑ ባለስልጣን ከቤታቸው ወጥተው ወደ ስራቸው እየተጓዙ እያሉ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው ያመለጡ መሆናቸው ተገልጿል። በደፈጣው ሙከራ ጠባቂያቸው የሆነ አንድ የፖሊስ አባል ሲገደል ባለስልጣኑ ግን ሳይጎዱ ለማምለጥ የቻሉ መሆናቸው ታውቋል። በአንድ የቶዮታ እቃ መጫኛ መኪና ላይ ሆነው ግድያውን የሞከሩት ገዳዮች ለጊዜው ሊያመልጡ ቢችሉም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በአንድ አካባቢ ጥለውት የሄዱት መኪና ተገኝቷል። በመኪናው ውስጥ ካላሽን ኮቭ መሳሪያዎች ጥይቶችና ፈንጅዎች የተገኙ መሆናቸውን ፖሊስ የገለጸ ሲሆን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ግድያውን ከሞከሩት ውስጥ ሁለቱ በአንድ የገበያ ቦታ ውስጥ ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው ተዘግቧል።

 

Ø ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በማሊ ዋና ከተማ በባማኮ በአንድ ከፍተኛ ሆቴል ላይ የተፈጸምውንና  ለሃያ ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነውን ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው ከሚጠረጠሩት ሰዎች መካከል ሁለቱን በቁጥጥር ስር አድርገናል በማለት  የማሊ የጸጥታ ባለስልጣኖች ገለጸዋል። የተሰጠው መግለጫ ሁለት የማሊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች በልዩ የጸጥታ ኃይሎች አማካይነት መያዛቸውን ከመግለጹ በስተቀር ስለማንነታቸውና ስለታሪካቸው የጠቀሰው ዝርዝር መረጃ የለም። እነዚህን ሰዎች በመጠየቅ የሚገኘው ተጨማሪ መረጃ ጥቃቱን ለመፈጽም ምን እንዳነሳሳችወና እንዲሁም ተባባሪ የሆኑ ሌሎች ግለስቦችን ለማወቅ ይቻላል በማለት መግለጫው ጨምሮ ገልጿል።

 

Ø ከናይጄሪያ የነዳጅ አምራች ከተማ እስከ ሌጎስ ከተዘረጋውና 250 ኪሎ ሜትር ርዝመት ካለው የነዳጅ ቱቦ ላይ ባለፈው ዓመት ብቻ ከ250 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግምት ያለው ነዳጅ በሌቦች እንደተዘረፈ ኩባንያው ጨምሮ ገልጿል። የናይጀሪያ ብሄራዊ የነዳጅ ኮርፖሬሽን በጠቅላላው በዓመት ውስጥ የተዘረፈው ነዳጅ መጠን ግማሽ ቢሊዮን ሊትር የሚሆን ነው ካለ በኋላ ይህም በናይጄሪያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ይፈጥራል ብሏል። በዚህ የነዳጅ ቱቦ አማካይነት በየቀኑ 35 ሚሊዮን ሊትር ወደጠቃሚው ለማድርስ የሚሞከር ቢሆንም በነዳጅ እጥረት ምክንያት ረዥም ሰልፎች በነዳጅ ጣቢያዎች ላይ እየታዩ መሆናቸው ታውቋል።   

 

 

 

 ህዳር 16 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት ሌሊት በአዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ የሚገኘውና በተለምዶ ጭድ ተራ ተብሎ በሚታወቀው ስፍራ ባልታወቀ ምክንያት የተነሳው እሳት ተቀጣጥሎ  ከፍተኛ ግምት ያለውን ንብረት ያወደመ መሆኑ ታወቀ።  የእሳት ቃጠሎ በርካታ  ሱቆችንና መደብሮችን ማውደሙ ሲታወቅ በየቦታው የነበሩት የመጥረጊያ ቁሳቁሶች ቃጠሎውን እንዳባባሱት በቦታው የነበሩ ወገኖች ይናገራሉ።  ከለሊቱ አምስት ሰዓት ላይ የተነሳውን እሳት ለማጥፋት አስራ አራት የእሳት ማጥፊያ መኪኖች  በማከታተል ለሶስት ሰዓት ያህል ጥረት ቢያደርጉም ግምቱ ያልታወቀ ንብረት በእሳቱ የወደመ መሆኑ ታውቋል። በሰው ላይ  ደረሰ አደጋ ስለመኖሩ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ የደረሰ መረጃ የለም። ከዚህ ቀደም በሙስና የዘቀጡት የወያኔ ባለስልጣናት የደሃውን ንብረት በተንኮል ካቃጠሉ በኋላ ቦታውን  ለባለሃብት በሊዝ ቸብችበው ኪሳቸውን የሚያደልቡበት ሁኔታ በተከታታይ የተከሰተ በመሆኑ በትናንተናው ምሽት እሳቱን አስነስተው ቦታውን ያወደሙት ባለስልጣኖቹ  ሳይሆኑ አይቀሩም የሚል ጥርጣሬ አለ።

 

 

Ø በአዲስ አበባ ፖሊስ ሰራዊት ውስጥ ከአንድ ሺ ሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ አባላት የስራ መልቀቂያ ጥያቄ በማቅረባቸው የተደናገጠው የወያኔ አስተዳደር ከትናንት ወዲያ ህዳር 14 ቀን 2008 ዓም ለፖሊስ አባላት ሽልማት ሲሰጥ የነበረ መሆኑ ተነገረ። ሽልማቱ የተሰጠው ሁለት ሺ ስምንት መቶ ለሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ሲሆን ከእነዚሁ ውስጥ አራቱ የኮሚሽነርነት ማዕረግ እንዲያገ ሲደረግ ሌሎቹ ደግሞ የሪባንና የገንዘብ ስጦታ ተደርጎላቸዋል። በዚህ ስነስርዓት ላይ ዜጎችን ለመሰለል አንድ ለአምስት የተባለው አደረጃጀት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም የቤት ለቤት ኮሚኒቲ ሰርቪስ በሚል ዘይቤ ልዩ ልዩ መረጃዎች የሚሰበስቡበት ሁኔታ እንዲስፋፋ  መመሪያ መሰጠቱ ታውቋል።  

 

Ø በአፋር ለረጅም ጊዜ የወያኔ አገልጋይ ሆኖ ሕዝብን ሲበድልና ሲዘርፍ የነበረው መሀመድ አሊ ሴሮ ከክልል አስተዳዳሪ ስልጣኑ የተነሳ መሆኑ ተነግሯል። ስልጣን አለቅም ብሎ አስቸግሮ የነበረው አሊሴሮ በወያኔ ግፊትና ማስፈራሪያ ስልጣኑን እንዲለቅ የተደረገ ሲሆን በምትኩ ከዚህ በፊት የአካባቢውን የከሰል ንብርት በመዝረፍና በማዘረፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያካብተውና የአካባቢውን የደህንነት ቢሮ በመምራት በንጽሃን ደም የተጨማለቀው ስዩም አሊ የተባለው ግለሰብ የአፋር ክልል ርዕሰ መስታደደር ተብሏል።  በየአመቱ ከአምስት መቶ ሺህ ብር በላይ ወጭ በማውጣት ልጁን በእንግሊዝ አገር ኪንግስተን ከሚባለው ትምህርት ቤት የሚያስተምረው አወል ረባ የተባለው ሌላው ግለሰብ  ደግሞ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ሆኖ የተሾመ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø በቅርቡ የወያኔ ቡድን ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደውን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም የአምቦና የአካባቢው ከተሞች ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ታወቀ። ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች እንደሚገልጹት በብዛት የተሰማሩት  ፖሊሶችና የጸጥታ ኃይሎች የተማሪዎችን የተቃውሞ ስልፍ ለመበተን የሚያስለቅስ ጢስና ውሃ ተጠቅመዋል። በግጭቱ የተጎዱ ተማሪዎች ስለመኖሩ የታወቀ ነገር ባይኖርም የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በትምህርት ቤታችው ውስጥ ታግተው መዋላችው ተነግሯል። ተቃውሞውን ያነሱት ወጣቶች የአዲስ አበባው ማስተር ፕላን አርሶ በከተማዋ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው ላይ ስለሚያፈናቅል መሰረዝ አለበት የሚል መልእክት ሲያሰሙ የነበረ ሲሆን ይህ የወጣቶቹ ተቃውሞ  በሌሎችም ከተሞች ይዛመታል ተብሎ ተፈርቷል። ባለፈው ዓመት የወያኔ የአዲስ አበባ የማስተር ፕላን እቅድ በመቃወም በተለያዩ ከተሞች በተነሱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በርካታ ወጣቶችን የገደሉ መሆናቸው ይታወሳል። የወያኔው ባለስልጣን አባይ ጸሐየም በአንድ ወቅት ማስተር ፕላኑን በግድ ተግባራዊ የታቀደ መሆኑን በመጥቀስ መዛቱም አይዘነጋም።

 

Ø በሱዳን  ህጋዊ ባልሆነ መንገድ የሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች 3 ሚሊዮን የደረሰ መሆኑና ከዚህም ውስጥ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን አንድ የሱዳን ከፍተኛ  የፖሊስ ባለስልጣን ገለጹ። ሌፍተናንት ጄኔራል አብዱልራሂም ሞሃመድ ሁሴን የተባሉትና የካርቱም ግዛት አስተዳዳሪ የሆኑት ግለሰብ ይህን የተናገሩት በካርቱም አካባቢ የጸጥታና ችግርና እና የህገወጥ  አስተላላፊ ወንጀሎችን ለመቆጣጠር በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ መሆኑ ታውቋል። የወያኔን አስከፊና አፋኝ አገዛዝ በመሸሽ በርካታ ኢትዮጵያውና ወደ ሱዳን መሰደዳቸው የታወቀ ቢሆንም ኢትዮጵያውያኑ ሰደተኞች በሱዳን መንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በወያኔ ካድሬዎች ከፍተኛ በደልና አፈና እየደረሰባችው መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø ይህ በእንዲህ እንዳለ ወያኔ እና የሱዳን መንግስት በሚቀጥለው ወር ላይ ወሰን  ለመካለል ያቀዱ መሆናቸውን በመግለጽ ሱዳን ትሪቡን የተባለው ጋዜጣ በአምዱ ላይ አስፍሮ አውቷል። ጋዜጣው የድንበር ማካለሉ ተግባር በሚቀጥለው ታህሳስ ወር እንደሚከናውን የገለጸ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ላይ ከወያኔ ጋር ለመነጋገር የሱዳኑ ምክትል ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገብተዋል ብሏል። ከዚህ በፊት ወያኔ ሰፋፊ የሆኑ የወሰን አካባቢዎችን ለሱዳን ለመስጠት መስማማቱን ተከትሎ ከፍተኛ ተቃውሞ የተነሳ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በድንበር አካባቢም አርሶ አደሮች በትጥቅ ሲፋለሙ መቆየታቸው ይታወቃል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት የሮማው ጳጳስ ፍራንሲስ ኬኒያ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።  ለስድስት ቀናት የሚቆየው  የአፍሪካ ጉብኝታቸው ወደ ኡጋንዳ እና የመከከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚወስዳቸው መሆኑ ተዘግቧል።   በዛሬው ቀንም ቁጥሩ 300 ሺ የሚገመት ሕዝብ በተገኘበት  በናይሮቢ ዩነቨርስቲ የቅዳሴ ስነስርዓት አካሂደዋል። ቀደም ብሎ በዚህ ስነስርዓት ላይ 1.4 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ይገኛል ተብሎ የተገመተ ቢሆን በነበረው ኃይለኛ ዝናም ምክንያት የህዝቡ ቁጥር ሊቀንስ ችሏል።   ከቅዳሴው ስነስርዓት ቀደም ብሎ ጳጳሱ በኬኒያ ከሚኖሩ የተለያዩ እምነት ተከታዮች መሪዎች ባካሄዱት ስብሰባ ሃይማኖት የኃይል ምንጭ መሆን የሌለበት መሆኑን ገልጸው በተለያዩ  የእምነት ተከታዮች መካከል ውይይት ማካሄድና መግባባት ላይ መድረስ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም የእስልምናና የክርስትና ተከታዮች  በመካከላቸው መቻቻልንና መግባባትን ፈጥረው አገሪቱን ለመምራት ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው ብለዋል። በናይሮቢ ዩኒቨርስቲ ባደረጉት የቅዳሴ ስነስርዓት ማብቂያ ላይም ባድረግቱ የመጀመሪያውን ይፋ ንግግር የቤተሰብ ኃላፊነትና ግዴታን በሚመለከት ሰፊ መንፈሳዊ ገለጻ ያደርጉ መሆናቸው ተነግሯል።፡

 

Ø ቻይና በጂቡቲ ውስጥ ለወታደራዊ አገልግልት ሊውሉ የሚችሉ ስፍራዎችን ለማቋቋም ከጂቡቲ መንግስት ጋር እየተደራደርች መሆኑን የቻይናው የመከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በዛሬው ዕለት ገልጿል። ቃል አቀባዩ የቻይና ወታደራዊ ተቋም በአፍሪካ ውስጥ የሰላም አስከባሪ ግዳጅ እየተሰጠው የሚያከናውን መሆኑንና  ሆነ በህንድ ውቅያኖስ አካባቢ ሲካሄድ የቆየወን የመርከብ ጠለፋ ወንጀል  ለመከላከል በሚደረገው ተግባር ላይ ተሳታፊ መሆኑን ጠቅሶ ጅቡቲ ውስጥ የሚመመሰረተው የቻይና ወታደራዊ አካል ይህንን የቻይና አለም አቀፍ ወታደራዊ ተልዕኮ ለማስተባበር ይረዳል ብሏል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ድርድር መደረጉን ያመነ ሲሆን የሚቋቋመው የወታደራዊ ጦር ሰፈር ነው በማለት አንዳንድ ክፍሎች የሚሰጡትን አስተያየት ግን ክዷል። ይህ የቻይና መግለጫ የተሰጠው ቻይና በጂቡቲ ውስጥ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ለማቋቋም የአስር ዓመት ውል የፈረመች መሆኗንና   ተመሳሳይ ጦር ሰፈሮች በሌሎች ቦታዎችም ለማቋቋም እቅድ እንዳላት በመግለጽ አንድ  የአሜሪካ ወታደራዊ ባለስልጣን ያደረጉትን ገለጻ ተከትሎ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በፊትም የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኦማር ገለህ በዚህ ጉዳይ ላይ ጂቡቲ ከቻይና ጋር ውይይት እያደረገች መሆኑን በመግለጽ ቻይናውያንን በደስታ እንድሚቀበሉ መናገራቸው አይዘነጋም። ጂቡቱ ውስጥ ፈረንሳይ፤ አሜሪካ እና ጃፓን የጦር ሰፈሮች ያሏቸው መሆኑ ሲታወቅ የቻይና መጨመር ወደፊት ምን ሊያስከትል እንደሚችል መገመት አልተቻለም።  

 

 

 

ህዳር 15 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በአሩሲ  27 ወረዳዎች መካከል 13  ዘንድሮ ለከፋ የረኃብ አደጋ የተጋለጡ መሆናቸውና በቅርቡ በአካባቢው የሚኖሩ ተማሪዎች ትምህርት አቁመው ወደ ሌሎች ከተሞች በመስደድ ላይ መሆናቸው ከስፍራው የሚደርሱን ዜናዎች ይገልጻሉ። በአካባቢው ስድሳ ሺ የሚሆኑ ዜጎች በድርቁ ምክንያት በሞት አፋፍ ላይ የሚገኑ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ለሕዝብ ችግር ደንታ የሌላቸው የወያኔ ባለስልጣናት ግን 15 ሺ የሚሆኑት ቀድሞውኑ ተረጅዎች ነበሩ በማለት እያላገጡ ናቸው።  በድርቁ ምክንያት ትምህርታቸውን ለማቆም የተገደዱት ወጣቶች ከአሩሲ ወደ ናዝሬት የቀን ስራ ፍለጋ በመፍለስ ላይ የሚገኙ ቢሆንም ከናዝሬት ምንጮች ለማረጋገጥ እንደተቻለው ወጣቶቹ የጠበቁትን ስራ እንደልብ  ባለማግኘታቸው ከመካከላቸው ብዙዎቹ የጎዳና ላይ ልመና የጀመሩ  መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። ከስፍራው የተገኘው ዜና አክሎ እንደገለጸው  በአርሲ በሚገኙ  ሶስት ወረዳዎች ውስጥ  በአመት አንድ ግዜ ማር በመሰብሰብ በሚያገኙት ገቢ ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ዜጎች በድርቁ ምክንያት ከፍተኛ ችግር ውስጥ የገቡ መሆናቸው ታውቋል። የወያኔ ባለስልጣኖች “በድርቅ አደጋ የሞተ የለም”፤ “እርዳታ የሚሰፈልጋቸው ቀድሞም ቢሆን የሚረዱ የነበሩ ናቸው”፤ “ለሚያስፈልጋቸው እርዳታ ሰጥተን አዳርሰናል” ወዘተ… እያሉ ቢመጻደቁም እስካሁን ድረስ ለአንድ ሰው አስራሁለት ኪሎ ስንዴና ሁለት ሊትር ዘይት መሰጠቱና ይህም ለአንድ ጊዜ ብቻ የተደረገ መሆኑን ከስፍራው የመጣው ዘገባ ያጋልጣል።

 

Ø በተያያዘ ዜና በበምዕራብ እና በምስራቅ ሀረርጌ በድርቁ ምክንያት የተረጅው ቁጥር ሃምሳ ከመቶ መጨመሩ ተነገረ። በምስራቅ ሀረርጌ እርዳታ እየተሰጣቸው ያለው ተረጅዎች ቁጥር 549 ሺ መሆኑን የወያኔ ባለስልጣኖች የገለጹ ሲሆን ከአንድ ወር በኋላ ይኸው ቁጥር ወደ ዘጠኝ መቶ ሺ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። በምዕራብ ሀረርጌም የተረጅዎች ቁጥር አሁን ካለበት 500 ሺ ተርጅዎች ወደ 720 ሺ ከፍ እንደሚል ተገልጿል። በእነዚህ አካባቢዎች ለተረጅዎች እየተሰጠ ያለው እርዳታ በቂ አለመሆኑን በአንዳንድ አካባቢም ምንም ዓይነት እርዳታ እየተሰጠ እንዳልሆነ ነዋሪዎች ለዜና ምንጮች ገልጸዋል።

 

Ø የአገራችንን ለም መሬት በገፍ በአነስተኛ ክፍያ በሊዝ ገዝተው ምርቱን  እንደልባቸው እያወጡ በመሸጥ ከፍተኛ ጥቅም ሲያገኙ የነበሩ የሳኡዲ ቱጃሮች ወንጀል ሰርታችኋል በሚል ምክንያት የወያኔ ባለስልጣኖች ሀብታችንን ዘረፈው ከአገር እንድንወጣ አደረጉን በማለት ቅሬታ ያሰሙ መሆናቸውን  አረብ ኒውስ የተባለውና በ ሳኡድ አረቢያ  በየቀኑ የሚታተመው ዕለታዊ ጋዜጣ በትናንትናው ዕትሙ በአምዱ ላይ አስፍሯል። መሀመድ አልሸውሪ የተባለውና የተወሰኑ የሳኡዲ ቱጃሮችን አስተባበሮ በአፍሪካ በልዩ ልዮ ቦታዎች መዋዕለ ንዋይ በማፈሰስ ስራዎችን እየሰራን ነው የሚል ግለሰብ በገለጸው መሰረት ቀደም ለወያኔ ባለስልጣኖች ገንዘብ በመስጠት በሊዝ መሬት ተቀብለው በእርሻ ምርት ሲያመርቱ የነበሩና በተለያዩ የስራ ቦታዎች ላይ የተሰማሩ የሳኡዲ ቱጃሮች ወንጀል ፈጽመችኋል በሚል ክስ የወያኔ ባለስልጣኖች በሊዝ ያገኙትን መሬት ሆነ የማምራቻ መሳሪውያዎቻቸውን  የወሰዱባቸው መሆኑን የገለጸ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 50 ከመቶ የሚሆኑት በኢትዮጵያ በተለያዩ የስራ መስክ ላይ የተሰማሩት የሳኡዲ ባለሃብቶች ንብረታችውን ትተው አገሪቷን ለቀው የወጡ መሆናቸውን ገልጿል። ባልሰሩት ስራ ወንጀል ፈጽማችኋል መባላቸው ያስፈራቸው በመሆኑ ወደኢትዮጵያ የማይመለሱ መሆናቸውንም ገልጿል። ቱጃሮቹ ለሁለቱ አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች ጉዳያቸውን ያመለከቱ ቢሆንም እስካሁን መልስ አላገኙም በማለት ግለሰቡ ለጋዜጣው በሰጠው መግልጫ ገልጿል። ተፈጸመ የተባለው ወንጀል ምን እንደሆኑ ግለሰቡ አልጠቀሰም። በወያኔ ባለስልጣኖችና በሳኡዲ ቱጃሮች መካከል የተፈጠረው የከረረ አለምግባባት ምን እንደሆን በውል ባይታወቅም ሌቦች የሚጣሉት የሰረቁትን ሲካፈሉ ነው እንደሚባለው የወያኔ ባለስልጣኖች ለግልጥቅም ከሚያደርጉት መሯሯጥ በሳኡዲ ቱጃሮች ላይ የወሰዱትን እርምጃ  አይፈጽሙም ማለት ግን አይቻልም።  

 

 

Ø የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ማክሰኞ ህዳር 14 ቀን 2008 ዓ..ም በፌስቡክ ባሰረጨው መልእክት ከፓርቲው ራሱን ያገለለ መሆኑንና ከእንግዲህ ወዲህ ራሱን እንጅ ማንንም ፓርቲ እንደማይወክል ገልጿል። የ27 ዓመት ወጣት የሆነው ዮናታን እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው ምክንያት ምን እንደሆነ ያልገለጸ ሲሆን ይህንን ጉዳይ በሚመለከትም ከፓርቲው ኃላፊዎች እስካሁን የተሰጠ መግለጫ የለም።

 

 

Ø በትናንትናው ዕለት በቱርክ ተመቶ የወደቀውን የሩሲያ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ሲያበሩ ከነበሩትና በፓራሹት ከወረዱት አብራሪዎች መካከል አንደኛው መገደሉን በትናንትናው ዘገባ የተገለጸ ሲሆን የሩሲያ ልዩ ኃይሎች የአስራ ሁለት ሰዓት ፍለጋ ካደረጉ በኋላ ሁለተኛውን አብራሪ በደህና በህይወት ያገኙት መሆናቸውን የሩሲያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። በአሁኑ ሰዓት አብራሪው ሶሪያ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ እንደሚገኝም ተገልጿል። የህይወት ማዳኛ ጃንጥላን በመጠቀም ከአውሮፕላኑ ላይ  ሲወርድ በአማጽያን ኃይሎች በተተኮስ ጥይት ተመቶ የወደቀው የሁለተኛው አብራሪ አስከሬን የት እንደደረሰ አይታወቅም። ቱርክ አውሮፕላኑን የጣለችው በአየር ክልሏ ውስጥ በመብረሩና ነው በማለት የቱርክ ፕሬዚዳንት የተናገሩ ሲሆን ውጥረቱ እንዲባባስ የማይፈልጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የሩሲያው ፕሬዚዳንት አውሮፕላኑ የቱርክን የአየር ክልል ያልጣሰ መሆኑን ገልጸው የቱርክ እርምጃ ጀርባችንን በጩቤ እንደመውጋት የሚቆጠር በመሆኑ በሩሲያና በቱርክ መካከል ያለው ግኝኙነት ከፍተኛ ችግር ይገጥመዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ግንኙነት ከፍተኛ የውጥረት ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን ሩሲያ አንድ የሚሳየል ጫኝ መርከብ በላታኪያ ወደብ አንቀሳቅሳ  ሶሪያ ውስጥ በሚገኝ የሩሲያ ወታደራዊ ካምፕ ላይ አደጋ ሊጥል ይችላል ተብሎ በሚገመትና በአየር ላይ ባለ  ማንኛውም ተንቀሳቅሽ አካል በረጅም እርቀት ሚሳየል እንዲመታ አዛለች። የሩሲያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሲያ የምትወስደውን የበቀል እርምጃ ከዘረዘሩ በኋላ የቱርክ ባለስልጣኖች አይሲስ ከሚባለው አሸባሪ ቡድን ጋር በነዳጅ ዘይት ንግድ ላይ የተመሰረተ የጋራ ጥቅም አላቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቱርክ ኩባንያዎች ሩሲያ ውስጥ ከመስራት እንዲታገዱ ለማደረግ እየተዘጋጀች መሆኑን ገልጸው ቱርክ ከቱሪስት ገቢ የምታገኘውን ገንዘብ ለመቀነስ የሩሲያ ዜጎች ወደቱርክ እንዳይሄዱ ምክር ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። በቱርክ በኩል ወደ አውሮፓ ሊዘረጋ ታስቦ የነበረውም የጋዝ ቧንቧ የሚሰረዝ መሆኑንም ተናገረዋል። የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በአሁኑ ወቅት ቱርክ የሩሲያን አውሮፓላን መትቶ ለመጣል የወሰደችው እርምጃ በቅድሚያ ያሰበችበትና  የተዘጋጀችበት መሆኑን የሚያሳይ ማስርጃ በዝርዝር አውጥቷል።  የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከለከያ ድርጅት (ኔቶ) የቱርክን አቋም ተቀብሎ ከቱርክ ጎን የሚቆም መሆኑ የገለጸ ሲሆን የሩሲያ አውሮፕላን በመመታቱና ፓይለቱም በመገደሉ የሀዘን ስሜት አለመግለጹ ለሩሲያ ያለውን የጠላትነት ስሜት የሚገልጽ ነው በማለት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገረዋል።   የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና አሜሪካ ሀሉቱ አገሮች  ችግሩን ከማባባስ እንዲታቀቡ ጠይቀዋል።  

 

Ø በቱኒዚያ ዋና ከተማ ቱኒስ ውስጥ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደሮች ይጓጓዙበት የነበረ አንድ አውቶቡስ ድንገት በፈነዳ ፈንጅ ጉዳት ደርሶበት በውስጡ የነበሩ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። ፈንጅው የፈነዳው አውቶቡሱ ተሳፋሪዎችን ሊያወርድ በቆመበት ጊዜ መሆኑ ታውቋል።  በደረሰው አደጋ ምክንያት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለሰላሳ ቀን የሚቆይ የሰዓት እላፊ አዋጅ ያወጁ መሆናቸው ተነግሯል። ለዚህ ጥቃት ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም ቱኒዚያ አይሲስ በተባለው አሸባሪ ቡድን በተደጋጋሚ ስትጠቃ የቆየች መሆኑ ይታወቃል። በኢራክና በሶሪያ የአሸባሪው የአይሲስ ቡድን አባሎች ሆነው ከሚዋግጉት መካከል ሶስት ሺ የሚሆኑት ከቱኒዚያ መሄዳቸው ይነገራል።

 

Ø የሱማሊያ የባህር መርከብ  ጠላፊዎች በኢራንና በታይ ሁለት የአሳ አጥማጅ መርከቦች  በወሰዱት ጥቃት የታይላንዱ መርከብ ሲያመለጥ  ጠላፊዎቹ የኢራኑን መርከብ ይዘው 15 የሚሆኑ የመርከቡ ሰራተኞችን ያገቱ መሆናቸው ታውቋል። ጠላፊዎቹ ሰዎችን ለማስፈታት የገንዘብ ክፍያ የሚጠይቁ ሲሆን አሁን ለያዟችው ሰዎች ምን ያህል ገንዘብ እንደጠየቁ አልታወቅም። ከአራት ዓመት በፊት በሱማሊያ ውስጥ በተመሳሳይ የመርከብ ጠለፋ የታገቱት ሰዎች ቁጥር 700 ደርሶ የነበረ ሲሆን  የመርከቦችን ደህንነት ለመጠበቅ የተለያዩ አገሮች በወሰዱት  እርምጃዎች ምክንያት ቁጥሩ በጣም ቀንሶ እስከ 56 ደርሶ እንደነበር ይታወሳል። በአሁኑ ወቅት ህገ ወጥ የሆኑ አሳ የማጥመድ ስራዎች በጣም እየተስፋፉ ያሉበት ሁኔታ የተስተዋለ ሲሆን ለአሁኑም የመርከብ ጠላፋ ምክንያት የሆነው ይኸው ህገወጥ የሆነ አሳ የማጥመድ ተግባር የሶማሊያ አሳ አጥማጆችን ስላስቆጣ ነው የሚል ምክንያት እየተሰጠ ነው።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን አንድ ሺ አንድ መቶ የሚሆኑ ተጨማሪ የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ደቡብ ሱዳን እንዲላኩ የጸጥታው ምክር ቤትን የጠየቁ መሆናቸው ተነገረ። ሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች ያደረጉትን የስምምነት ቃል የማይጠብቁ መሆናቸው የታወቀ ከመሆኑ በላይ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በመጣሱ ምክንያት በርካታ  ሰላማዊ ሰዎች ጉዳት ላይ በመወደቃቸው የሰላም አስከባሪ ኃይል ቁጥሩን መጨመር አማራጭ የሌለው ነው ብለዋል። 500 ወታደሮችና 600 ፖሊሲች ከ13 ሄሊኮብተሮችና የመጓጓዣ አውሮፕላን ጋር ወደቦታው እንዲላኩ ጠይቀዋል። በቤንቱ የሚገኘውና 100 ሺ ስደተኞችን የሚያስተናግደው የሜዳ የህክምና ጣቢያ ቁሳቁስና የሰው ኃይል ተጨምሮለት አገልጎቱን ጨምሮ እንዲያበርክት ጥያቄ አቅርበዋል።  

 

 ህዳር 14 ቀን 2008 ዓ.ም

Ø አንድ የሩሲያ ኤስ 24 የውጊያ አውሮፕላን በቱርክ የመከላከያ ኃይል ተመቶ መውደቁና አብራሪዎቹ ከአውሮፕላን ውስጥ በፓራሹት ለመውጣት የቻሉ መሆናቸው ተነገረ። የቱርክ ባለስልጣኖች አውሮፕላኑ የቱርክና ግዛት ጥሶ በመግባቱ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ በቱርክ ኤፍ 16 የጦር አውሮፕላን ተመቶ የወደቀ መሆኑን ገልጸዋል። የሩሲያ ፕሬዚዳንት ፑቲን አውሮፕላኑ በሶሪያ የአየር ክልል ውስጥ  በ6 ሺ ሜትር ከፍታና ከቱርክ ድንበት 1 ኪሎሜትር ርቆ  ሲበር  ከቱርክ ኤፍ 16 አውሮፓላን በተተኮስ የየአር በአየር ተመዝገዛጊ ሚሳየል ተመቶ የወደቀ መሆኑን ገልጸዋል። አውሮፕላኑ የወደቀውም ከቱርክ ወሰን አራት ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኘው የሶሪያ ግዛት ውስጥ ነው ብለዋል። አውሮፓላኑ ለቱርክ ጸጥታ የማያሰጋ ሆኖ ሳለ በቱርክ የጦር አውሮፓላን ተመትቶ መውደቁ ሩሲያ በአሸባሪዎች ላይ እርምጃ እየወስደች እያለች ወዳጅ ከምትባለው ከጀርባዋ ተመታለች ብለዋል። ቱርክም ይህንን በማድረጓ ከአሸባሪዎች ጋር ተባባሪ ሆናለች ብለዋል። ፑቲን የወደቀው አውሮፕላን ኢላማ አድርጎ ሲያጠቃ የነበረው ላቲኪያ በሚባለው ብዙዎቹ ከሩሲያ የመጡትንና በሶሪያ ግዛት ውስጥ የሚንቀሱትን  አሸባሪዎች ነበር ብለዋል። በእነዚህ አሸባሪዎች አስተናጋጅነት ከአካባቢው ነዳጅ እየተወሰደ ወደ ለቱርክ እንደሚሸጥና ሩሲያ ታውቅ ነበርና ይህንን  በቢሊዮን የሚቆጠረውን የአይሲስን የገቢ ምንጭ ለማድረቅ የተወሰደ እርምጃ ነበር ብለዋል። አይሲስ ተጠናክሮ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውና በርካታ ሰዎችን በየቦታው ለመግደል የቻለው በዚህ መንገድ  በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢ በማግኘቱ ነው ብለዋል። ሚስተር ፑቲን ሩሲያ በሶሪያ ላይ እያካሄደች ያለውን ጥቃት ለማስተባበር ከአሜሪካ ጋር ከተስማማች በኋላ በአሜሪካ በሚመራው የአየር ጥቃት ውስጥ ተካፋይ ነኝ የምትለው ቱርክ የወሰደችው እርምጃ እጅግ ያሳዘናቸው መሆኑን ገልጸው ሁኔታው በሩሲያና በቱርክ ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ችግር ሊፈጥር ይችላል ብለዋል።   ሩሲያ በሶሪያ የአየር ጥቃት ከጀመረች ጀምሮ ይህ ዓይነት አደጋ ሲፈጠር የመጀመሪያው ነው።  ከሁለቱ የአውሮፓላን አብራሪዎች መካከል አንደኛው በፓራሹት እየወረደ እያለ በአማጽያኑ ተመቶ የተገደለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ሁለተኛው በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳለ አልታወቀም።  

 

Ø በፓሪስ ከተማ ሰራተኞች ከአንድ የቆሻሻ ማጠራቂሚያ በርሚል ውስጥ አግኘተው ለፖሊስ ያስረከቡትንና   አሸባሪዎች ሲጠቀሙበት ነበር ተብሎ የተጠረጠረውን የቦምብ ትጥቅ የጸጥታ ኃይሎች እየመረመሩ መሆኑ ታወቀ። የተገኘው የቦምብ ትጥቅ ባለፈው ሳምንት በፓሪስ በተለያዩ ቦታዎች ጉዳይ ያደረሱት አሸባሪዎች ከተጠቀሙባቸው ትጥቆች ጋር  ተመሳሳይነት ያለው ሲሆን የተገኘውም የፓሪሱን ጥቃት በአቀነባባሪነት የመራውና አሁን እየተፈለገ ያለው ሳላህ አብዱሰላም የተባለው ግለስብ በመጨረሻ ወቅት የስልክ ልውውጥ ሲያደርግበት ነበር ከተባለ ቦታ ላይ ነው። ቀደም ብሎ የተገኘው የሳላህ አብዱሰላም የሞባይል ስልክ አብዱሰላም ከዚህ ቦታ ላይ የስልክ ልውውጥ ያደረገ መሆኑን የሚስረዳ መረጃ የያዘ ሲሆን አብዱል ሰላም ትጥቁን ቁሻሻ ማጠረቀሚያ ገንዳ ውስጥ የወረወረው ወይ አልሰራ ብሎት ነው አለዚያም  በመጨረሻ ጊዜ የውሳኔ ለውጥ አድርጎ ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ አለ።   

 

Ø በሱዳን መንግስትና ተጻራሪ በሆኑት አማጽያን መካከል ለአንድ ሳምንት ያህል በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የስለም ውይይት ያለስምምነት የተበተነ መሆኑ ተነገረ። በዳርፉር የሚገኙ የተለያዩ የአማጽያን ቡድን እና ኤስ ፒ ኤል ኤም ኖርዝ (SPLM N) ቡድን ተወካዮችና የሱዳን መንግስት ባለስልጣኖች መካከል በአፍሪካ ህብረት ተወካይ  በቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በሚስተር ታቦ ኢምቤኪ ሊቀ መንበርነት የእርቅ ውይይት ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ታውቋል። አደራዳሪዎቹ ቢያንስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሊደርሱ ይችላሉ የሚል ተስፋ ይዘው የገቡ ቢሆንም በዚህም ላይ ስምምነት ሊደርስ ባለመቻሉ ለጊዜው እንዲቋረጥ የተደረገ መሆኑ ተገልጿል። የእርቁ ስብስባ ወደፊት ይቀጥላል የተባለ ቢሆንም መቸ ሊሆን እንደሚችል ግን አልተገለጸም፡፤

 

Ø በግብጽ ሰሜናዊ የሲና ባህረሰላጤ በኤል አሪሽ ከተማ ስዊስ ኢን በሚባል ሆቴል  ውስጥ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎችና አንድ መሳሪያ የያዘ አሸባሪ ባካሄዱት የተቀነባረ ጥቃት አራት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች አስራ ሁለት ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸው ተነገሯል። ከተገደሉት መካከል አንድ ዳኛ ሁለት ፖሊሶችና አንድ ሲቪል የሚገኙበት ሲሆን ከቆሰሉት ውስጥ ደግሞ ሁለት ዳኞች ስምንት ወታደሮችና ምልምሎች እንዲሁም ሁለት ሲቪሎች አሉበት ተብሏል።  ከሟቾቹና ከቁስለኞቹ ውስጥ አብዛኞቹ ባለፈው እሁድና ሰኞ በአካባቢው ሲካሄድ የነበረውን የምክር ቤት የምርጫ ሂደት ሲቆጣጠሩና ሲታዘቡ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። በሆቴሉ ላይ የተደረገው የጥቃት እርምጃ የተቀነባበረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን አንደኛው አጥፍቶ ጠፊ መኪና ላይ ሆኖ ቦምቡን ካፈነዳ በኋላ ሌላኛው በወገቡ ላይ የታጠቀውን ቦምብ በሆቴሉ መግቢያ ላይ ያፈነዳ መሆኑና መሳሪያ የያዘው አሸባሪ በግርግሩ ሆቴል ክፍሎች ውስጥ በመግባት ዳኛውንና ሌሎችን ሊገድል የቻለ መሆኑ ተነግረዋል።፡    

 

   

 

ህዳር 13 ቀን 2008 ዓ.ም 

Ø ባለፈው ሳምንት በዋና ከተማዋ ባማኮ ውስጥ በሚገኘው የራዲሰን ሆቴል የተፈጸመውንና  የ29 ሰዎች ህይወትን ያጠፋውን የአሸባሪዎች ጥቃት ለማስታወስ ማሊ የሶስት ቀና ብሔራዊ ሀዘን ያወጀች መሆኑ ተነገረ። ሴኒጋል ሞሪታኒያና ጊኒም ሀዘናቸውን በመግለጽ ትብብራቸውን አሳይተዋል። አርብ ዕለት ለተካሄደው ጥቃትና ግድያ ሁለት የተለያዩ አሸባሪ ድርጅቶች ኃላፊነቱን ወስደዋል። ከእነዚህ መካከል አንደኛው “በእስላማዊ ማግረብ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ” የተባለው ቡድን ሲሆን ሌላኛው ደግሞ “ የማሲና ነጻ አውጭ ግምባር” የተባለው ነው።  አርብ ዕለት በሆቴሉ ውስጥ የታገቱትን የታገቱትን ሰዎች ለማስፈታት የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ ሁለት አሸባሪዎች መገደላቸው የተዘገበ ሲሆን ምን ያህል ሰዎች እንደተሳተፉ እና ከየት ከየት እንደመጡ ለማወቅ ምርመራ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ከአንድ የጸጥታ ምንጭ በተገኘው መረጃ በሆቴሉ ጥቃት ወቅት የተገደሉት ሁለቱ ስዎች እንግሊዘኛ የሚናገሩ መሆናቸው ተደርሶበታል። የማሊ ፖሊስ ስለግድያው የሚያደርገውን ምርመራ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በቅርብ ቀን ውስጥ በህይወት የሚገኙት ወንጀለኞች እና ተባባሪዎቻቸው ለፍርድ ይቀርባሉ የሚል መግለጫ ሰጥቷል።

 

Ø በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዮ መልእክተኛ በመሆን በቅርብ የተሾሙት ጀርመናዊው ሚስተር ማርቲን ኮብለር ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ በቶብሩክና በትሪፖሊ ከተሞች  ተጻራሪ ሆነው የተቋቋሙትን ሁለቱን  የሊቢያ አስተዳድሮች አባላትን አነገጋረዋል። ሚስተር ኮብለር በየራሳቸው መንግስት ነን የሚሉትን የሁለቱንም አስተዳደሮች አባላትን  ካነገገሩ በኋላ  በቶብሩክና በትሪፖሊ በሰጧቸው ጋዜጣዊ መግለጫዎች የሁለቱም ተጻራሪ ቡድኖች ባለስልጣኖች በተመድ የቀረበውን የእርቅ ሀሳብ እንዲቀበሉ ጠይቀዋል። ከዚህ ቀደም የተደረገው ድርድርና ስምምነት ሊፈርስም ሆነ ሊሻሻል የማይችል መሆኑን ገልጸው በሁለቱም ዘንድ የሚገኙት የምክር አባላት አቋማቸውን መርመረው እንደገና ድምጽ እንዲሰጡበት ተማጽነዋል። አገሪቱ ካለችበት የኢኮኖሚ ችግር ልትወጣ የምትችለውና ወደፊትም በእድገት ጎዳና ላይ ልትጓዝ የምትችለው ሁሉም ስምምነቱን ሲቀበል ነው ብለዋል። ቀደም ብለው የነበሩትና ስራቸውን የለቀቁት የተመድ ልዩ መልከተኛ በርናርዲኖ ሊዮን ለረጅም ጊዜ ሁለቱን ተጻራሪ ኃይሎች አደራድረው ያቀረቡት የእርቅ ሀሳብ ሁለቱም  ስልጣን በጋራ የሚካፈለቡትና አገሪቱን በበላይነት የሚመራ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አምስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችና ሶስት ከፍተኛ ሚኒስትሮች የያያዘ  የዘጠኝ ሰዎች የፕሬዚዳንት ካውንስል እንዲቋቋም የሚል ሲሆን  ረቂቅ ሀሳቡ በሁለቱም በኩል ውድቅ መደረጉ የሚታወስ ነው።

 

 

Ø የሲናን ባህረ ሰላጤ ወደ እስራኤል ሲሄዱ የነበሩ ስድስት ሱዳናውያን ተግድለው ሬሳቸው የተገኘ መሆኑ ታውቋል። ሌሎች አስራ አንድ የሚሆኑ የስዳን ዜጎች ወሰኑን ሊያቋርጡ ሲሞክሩ በጥይት የቆሰሉ መሆናቸውም ተዘግቧል። ሰዎቹ እንዴት እንደሞቱና ማን እንደገደላቸው እስካሁን ባለው ምርመራ አልታወቀም ተብሏል። የሲና ባህረ ሰላጤ የተባለው ቦታ የግብጹን ፕሬዚዳንት ሲሲን መንግስት የሚቃወሙ አማጽያን የሚንቀሳቀሱበት መሆኑ ግልጽ ቢሆንም ቀደም ብሎ ባህረ ሰላጤን አቋርጠው  ወደ እስራኤል ለመግባት ጥረታ ሲያደርጉ የነበሩ ስደተኞች በግብጽ መንግስት  የወሰን ጠባቂ ወታደሮች መገደላቸው ይታወሳል።

 

Ø እሁድ ጠዋት ማይዱጉሪ በተባለችውና በ ሰሜናዊ ምስራቅ ናይጄሪያ በምትገኘው ከተማ ውስጥ  የቦኮ ሃራምን ጥቃት ሸሸተው የመጡ ስምንት ሰዎች በአንዲት አጥፍቶ ጠፊ በፈንዳ ቦምብ የተገደሉ መሆናቸው ከአካባቢው ከተገኘ ዜና ማወቅ ተችሏል።  የተገደሉት ሰዎች የመጡት ዲክዋ ከተባለችው ሌላ አነስተኛ ከተማ  ሲሆን አብዛኞቹ ሴቶችና  ህጻናት እንደሚገኙበት ታውቋል።  ሰዎቹ በከተማዋ ዳርቻ ላይ በሚገኝ የፍተሻ ጣቢያ ላይ እንደደረሱ አንዲት የሃያ አመት ልጅአገረድ ከሰዎቹ ጋር በመቀላቀል የታጠቀችውን ቦምብ በማፈንዳት ራሷን ከመግደሏ በተጫማሪ ሌሎች ስምንት ሰዎችን ለመግደልና  ሰባት የሚሆኑትን ለማቁሰል ችላለች።  ዲክዋ ባለፈው ዓመት ሃምሌ ወር ውስጥ የመንግስት ወታደሮች  ከቦኮሃራም ቁጥጥር ነጻ ያደረጓት ከተማ ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የቦካ ሃራምን ጥቃት ሸሽተው በመጡ የአካባቢው ሰዎች ስትጨናነቅ ቆይታለች። ከተማዋ ውስጥ የምግብና የሌሎች ቁሳቁሶች እጥረት በመከሰቱ አንዳንድ ሰዎች ከተማዋን እየለቀቁ ወደ ማይዱጉሪ ከተማ  ለመሰደድ የተገደዱ መሆናቸው ታውቋል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ቅዳሜ ዕለት በካሜሩን ሰሜናዊ ግዛት ጥቃት ፈጽመው አራት ሴቶች ልጆችን የገደሉ ሲሆን በቻድ እና በናይጀርም ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመዋል።

 

 

 

 

ህዳር 11 ቀን 2008 ዓ.ም   

Ø አሸባሪዎችን እናድናለን በሚል ምክንያት የወያኔ ወታደሮች በሰሜናዊ ኬኒያ መርሳቤት በሚባለው ወረዳ ውስጥ  ገብተው ሶስት የኬኒያ ፖሊሶችን የገደሉ መሆናቸውን የኬኒያ ፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል ። የወያኔ ወታደሮች  የኬኒንያን ድንበር ጥሰው በመግባት የኦነግ ታጣቂዎች  ተደብቀውበታል ብለው የጠረጠሩትን አንድ የኬኒያ መንደር ከበው እርምጃ ለመውሰድ ሞክረዋል። መንድሯ በወያኔ ወታደሮች መከበቧ የተነገራቸው የኬኒያ ፖሊሶች የጸጥታ ሁኔታውን ለመቆጣጠር  በወታደራዊ መኪና ተጭነው ወደቦታው ሲመጡ በወያኔ ወታደሮች የደፈጣ ተኩስ ከፍተውባቸው የኬኒያ ፖሊስችን የገደሉ መሆናቸውና  ሌሌች አምስት የሚሆኑት ደግሞ ተበታትነው እስካሁን ያልተገኙ መሆናቸው ተነግሯል። የኬኒያ መንግስት በወያኔ ላይ የቅሬታ ክስ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።

 

Ø ከፓሪስ ግድያ ተመሳሳይ በሆነ መንገድ በርከት ያሉ ሰዎች በተለያዩ ቦታዎች ግድያ ለመፈጸም ተዘጋጅተዋል  የሚል የታመነ መረጃ ደርሶናለ በማለት የቤልጅም ባለስልጣኖች የአገሪቱን በተለይም የዋና ከተማዋን የብራስልስን የጸጥታ ጥበቃ መጠን የመጨረሻው ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንዲሆን ያደረጉ መሆናቸው ተነግሯል። በአሁኑ ወቅት እየተፈለገ ያለውና የፓሪሱን ግድያ በመሪነት አቀነባብሯል ተብሎ የሚነገርለ ሳላህ አብዱሰላም   ቤልጅም ገብቷል የሚል መረጃ ስለደረሰ ግለሰቡን የማደን አሰሳውም ተጠናክሮ ቀጥሏል። እስከ ሚቀጥለው ሰኞ ድረስ የምድር ውስጥ ባቡር መገልገያዎች ዝግ እንዲሆኑ የተደረገ ሲሆን በርካታ ሰው የሚሰሰብስባቸው ትልልቅ ስታዲዮሞች የሙዚቃና የቲያትር ቦታዎች ወዘተ.. ዝግ እንዲሆኑ ተደርጓል። ዜጎችም ወደ እነዚህ ቦታዎችና እንዲሁም ወደ ትላልቅ የገበያ ቦታዎች እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።  በርካታ ቁጥር ያላቸው  የጸጥታ ኃይል አባላትም በከተማዋ እንዲሰማሩ ተደርጓል። እሁድ ከሰዓት በኋላ ባለስልጣኖቹ ተሰብስበው የጸጥታውን ሁኔታ የሚገመግሙ መሆናቸውም ታውቋል።

Ø በተያያዘ ዜና የቱርክ ፖሊስ አንድ የቤልጅየም ዜግነት ያለው ሞሮካዊ ሰው በፓሪሱ ግድያ ላይ ተሳትፏል  ከሚል ጥርጣሬ በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑን የቱርክ የዜና ምንጮች ገልጸዋል።  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም በትናንትናው ዕለት ባደረገው ስብሰባ በፈረንሳይ መንግስት የቀረበውና ረቂቅና ሁሉም አባል አገሮች በአይሲስ ላይ የሚያደርጉትን ዘመቻ አጠናክረው እንዲቀጥሉ  የሚጠይቀውን ረቂቅ ውሳኔ በሙሉ ድምጽ ደግፎ ያጸደቀው መሆኑ ታውቋል።

 

Ø ትናንት በማሊ ዋና ከተማ በባማኮ በራዲሰን ሆቴል ላይ አሸባሪዎች በፈጸሙት ጥቃት 19 ሰዎች ሲሞቱ የታገቱት በሙሉ የተፈቱ መሆኑ ተነግሯል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል ሶስት ቻይናዎች፤ እንድ የቤልጀም ተወላጅ አንድ አሜሪካዊና የተወሰኑ ሩሲያውያን የሚገኙበት መሆኑን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የታገቱት ሰዎች ለማስፈታት የማሊ ልዩ የጸጥታ ኃይል ልዩ ጥረት ያደረገ ሲሆን   በከተማዋ የነበሩ የፍረንሳይ እና የአሜሪካ የጸጥታ ኃይሎች ተባብረዋል ተብሏል። ምን ያህል አሸባሪዎች በጥቃቱ ላይ እንደተሳተፉ በግልጽ ያልተነገረ ሲሆን ሁለት አሸባሪዎች የሞቱ መሆናቸው ተገልጿል። በጥቃቱ መሳተፋቸውና አለመሳተፋቸው ያልተገለጸ ሶስት ተጠርጣሪዎች እየተፈለጉ መሆናቸውን ባለስልጣኖቹ ተናግረዋል።

 

Ø ላይቤሪያ ከኢቦላ ነጻ መሆኗን የሚገልጽ ምስክር ወረቀት ከዓለም የጠና ድርጅት ባገኘች በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ ሶስት የኢቦላ ታማሚዎች የተገኙ መሆኑ ተገለጸ። ከህመምተኞቹ መካከል አንዱ የአስር አመት ልጅ የሆነው ሶስቱም ታማሚዎች የሚኖሩት በዋና ከተማዋ ዳርቻ በሆነ ስፍራ ነው። ሰዎቹ ከህብረተሰቡ በተነጠለ ቦታ ተቀምጠው ህክምና እንዲወስዱ ተደርጓል። የኢቦላ በሽታ ከተከሰተ ጀምሮ በላይቤሪያ 10 ሺ የሚሆኑ የኢቦላ በሽተኞች ህክምና የተደረገላቸው ሲሆን 4 ሺ የሚሆኑ ደግሞ በበሽታው ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ ይታወቃል። ከጥቂት ቀናት በፊት ጊኒና ሲየራ ሊዮን ከኢቦላ ነጻ ናቸው በመባላቸው ይታወሳል። ባለፉቱ ሁለት አመታት በምዕራብ አፍሪካ አካባቢው በበሽታው  ከ11 ሺ ሰው በላይ ህይወቱን ያጣ መሆኑ ሲታወቅ ከሞቱት ውስጥ አብዛኖቹ የላይቤሪያ የጊኒና የሴየራ ሊዮን ዜጎች ናቸው ።   

 

ህዳር 10 ቀን 2008 ዓ.ም   

Ø በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ራዲሰን በሚባለው ትልቅ የመዝናኚያ ሆቴል ውስጥ ማንነታቸው ያልታወቀና ቁጥራቸው ከ10 እስከ አስራ ሶስት የሚገመት ታጣቂዎች የሆቴሉን በር ጥሰው ገብተው ተኩስ የከፈቱ መሆናቸውና  170 የሚሆኑ ሰዎችን ያገቱ መሆናቸው ተነገሯል። ከታገቱት መካከል 30 የሚሆኑት የሆቴሉ ስራተኞች ሲሆኑ 140 የሚሆኑት ደግሞ በሆቴሉ  ያረፉ እንግዶች ነበሩ። ታጣቂዎቹ ወደ ሆቴሉ   እየተኮሱ ሲገቡ “አላህ ወ አክበር” “ አምላክ ትልቅ ነው” የሚል ቃል በአረቢኛ እያሰሙ የነበረ ሲሆን በመጀሪያ ወቅቶች  ከቁራን ውስጥ አንዳንድ ጥቅሶችን መናገር የቻሉትን  የለቀቁ መሆናቸው  ተዘግቧል። የማሌ ጸጥታ ኃይሎች በአሜሪካንና በፈረንሳይ ልዩ ኃይሎች ታጅበው በወሰዱት እርምጃ የታገቱት የተፈቱ ቢሆንም 27 ሰዎች መገደላቸው ተገልጿል። የእስላማዊ ማግርብ አልቃይዳ የተባለው ቡድን ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። የዛሬ ሶስት ዓመት ሰሜናዊ የማሊ ግዛት የአልቃይዳ ጋር ግንኙነት አለው ከሚባሉ የአክራሪ እስላማውያን ቁጥጥር ስር  ለረጅም ጊዜ የቆየ ሲሆን በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ አማጽያኑ ከአካባቢው ተጠርገው የወጡ መሆናችው ይታወሳል።

 

Ø በየመን በአረቢያ ባህረ ሰላጤ የአልቃይዳ ቅርንጫ የተባለው ቡድን ሃድራማውት በተባለ ግዛት ውስጥ የሚገኘውን አንድ የመንግስት ውታደራዊ ካምፕ የሆነን ቦታ ያጠቃ መሆኑ የተነገረ ሲሆን በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ከአልቃይዳ አባላት 14 ሰዎች ሲገደሉ 15 ወታደሮች የተገደሉ መሆናቸው ተገልጿል። ጥቃቱ የተጅመረው የቡድኑ አባል የሆነ ግለሰብ መኪና ውስጥ ሆኖ ራሱንም ጭምር የገደለውን ቦምብ ካፈነዳ በኋላ ሲሆን አከታትለው ከ 25 እስከ 30 የሚጠጉ ታጣቂዎች የእሩምታ ተኩስ በመክፈት ካምፑን ሊወሩ ችለዋል። የየመን የእርስ በርስ ጦርነት ሲጀመር ከአገሪቷ ወታደሮች መካከል ከፊሉ ሁቲዎችንና የቀድሞ ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳለህን መደገፋቸውና ከፊሉ ደግሞ የአሁኑን ፕሬዚዳንት ሃዲን ደግፈው  መቆማቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን በአልቃይዳ ጥቃት የደረሰበት ጦር የፕሬዚዳንት ሃዲ ደጋፊ መሆኑ ታውቋል ። የየመኑ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ ዋና ጠላት አድርጎ እየተዋጋ ያለው  ከሁቲዎች ጋር መሆኑ ግልጽ በሆነበት ሁኔታና የሳኡዲ ጥምር ኃይልና ይኸው ቡድን በሁቲዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የድብቅ ስምምነት አድርገዋል እየተባለ በሚነገርበት ሁኔታ  ባሁኑ ወቅት  የሃዲ ደጋፊ በሆነው ጦር ላይ ጥቃት አልቃይዳ ጥቃት የሰነዘረበት ምክንያት ግልጽ አይደለም። ውጊያው አሁንም ያላቆመ ሲሆን የሟችና የቁስለኛ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል የሚል ስጋት ፈጥሯል።

 

Ø ኢንተርናሽናል ኮንፈረንስ ኦን ዘ ግሬት ሌክ ረጅንስ (Internarional Conference on The Great Lake Regions) የሚባለው  የአካባቢው አገሮችን የሚያስተባበረው ድርጅት ዋና ጽሕፈት ቤት አሁን ከሚገኝበት ከብሩንዲ ዋና ከተማ ከቡጁምቡራ  ተነቅሎ በጊዜያዊነት ወደ ዛምቢያ  ዋና ከተማ ወደ ሉሳካ የተወሰደ መሆኑ ተነገረ። በብሩንዲ የጸጥታው ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባለሸ በመሄዱና  በየአውራ ጎዳናው የሚገለው ሰው እየበረከተ በመምጣቱ ምክንያት  የጽህፈት ቤቱን ሰራተኞችና የቤተሰቦቻቸውን ደህነነት ለመጠበቅ ሲባል መስርያ ቤቱን በጊዜያዊነት ማዛወር አስፈላጊ ነው ተብሏል። ይህ ድርጅት  የአካባቢው አገሮች የጸጥታ ሁነታን የሚጠበቅበትን እንዲሁም  የፖሊቲካ መረጋጋትንና እድገት የሚገኝበትን ሁኔታ ለመፍጠር የአካባቢ አገሮችን ለማስተባበር የተቋቋመ   ሲሆን ዋና መስርያ  ቤቱ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ እንዲሆን የተደረገው በ2000 ዓ.ም. ነው። የድርጅቱ አባል አገሮች አንጎላ፤ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፤ የኮንጎ ሪፕብሊክ፤ የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ፤ ኬኒያ፤ ኡጋንዳ፤ ሩዋንዳ፤ ደቡብ ሱዳን፤ ሱዳን፤ ታንዛኒና ዛምቢያ ናቸው። ክቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ ያለው የጸጥታ ሁኔታ በጣም እየተባባሰ የሄደ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ሰሞኑን  በአማጽያኑ ከርቀት የተተኮሰ ሞርታር  በፕሬዚዳንቱ ቤት መንግስት አጠገብ የወደቀ መሆኑ ተገልጿል።

 

Ø በትናነትናው ዕለት የደቡን ሱዳን ምክር ቤት (ፓርላማ) የአካባቢ ግዛቶችን ስልጣን  የሚያዳከመውንና የፕሬዚዳንቱን ስልጣን በጣም የሚጨምረውን አንቀጽ በመጨመር የአገሪቱን ህገ መንግስት የለወጠ መሆኑ ተነገረ። ምክር ቤቱ ያደረገው   የህገ መንግስት ለውጥ አዳዲስ ግዛቶች መመስረታቸውን የሚፈቅድ ሲሆን  እንዲሻሻል የተደረገውም  የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የአካባቢ ግዛቶች ቁጥር በሶስት እጥፍ እንዲጨምር ካደረጉ በኋላ ነው። ከጥቂት ጊዜ በፊት ከአማጽያኑ ጋር የተደረገው የስምምነት መሰረት ሚዛኑን የጠበቀ የስልጣን ክፍፍል ስለሆነ የግዛቶች ቁጥር መጨመር የስልጣን ሚዛኑን ስለሚያናጋ ስምምነቱን ሊያፈርስ ይችላል የሚል ስጋት አለ። የሰላም ስምምነቱ እስካሁን ሳይከበር የቆየ መሆኑና  ግጭቶችና ጦርነቶቹ የቀጠሉ መሆናቸው ግልጽ ቢሆንም በትናንቱ ዕለት የደቡብ ሱዳን ምክር ቤት የሰላም ስምምነቱን አጽድቆታል ተብሏል። በአሁኑ ወቅት ግጭቶቹና ጦርነቶቹ ወደ ደቡብ ግዛቶች እየተስፋፋ መሆኑ ይነገራል።  በትናንትናው ዕለት ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ወደ ኡጋንዳን ሲጓዙ በነበሩ አንድ አውቶቡስና አራት የጭነት መኪናዎች ላይ ደፈጣ አካሄደው አራት ሹፌሮችንና ሶስት ተሳፋሪዎችን የገደሉ መሆናቸው ተነግሯል።  ዩኒቲ፤ አፕር ናይልና ጆንግሌ በሚባሉት የአገሪቱ ሰሜናዊና ምስራቃዊ ግዛቶች ጦርነቱ ያልበረደ መሆኑና እንዲሁም በአንዳንድ ቦታዎች ተፋፍሞ የቀጠለ መሆኑ ይነገራል። በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት 2.3 ሚሊዮን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ ሲሆን 4.6 ሚሊዮን ሕዝብ ከፍተኛ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልገው ነው።

 

 

                                                                                                          

  ደሩ መሆናቸው ታውቋል።   

 

Ø በኮንጎ ሬፕብሊክ እሁድ ዕለት የአገሪቷን ሕገ መንግስት ለማሻሻል የውሳኔ ሕዝብ ምርጫ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ከምራጮቹ ዘጠና ከመቶ የሚሆነው መራጭ ህገ መንግስቱ ይሻሻል የሚለውን ሀሳብ የደገፈ መሆኑን የአገሪቱ የአገር ውስጥ ሚኒስትር በይፋ ገልጸዋል። የህገ መንግስቱ ማሻሻያ ሀሳብ ፕሬዚዳንቱ ከሁለት ጊዜ በላይ እንዲወዳደርና የሚፈቅደውና ሰባ ዓመት የሚለው የእድሜ ክልል እንዳያግደው የሚለው መሆኑ ይታወቃል። ሚኒስትሩ በተጨማሪ በሰጡት መረጃ ሊመርጥ ከሚችለው ሕዝብ ውስጥ 72 ከመቶ ድምጽ የሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል። ከእሁዱ ምርጫ በኋላ ተቃዋሚ ኃይሎች ለምርጫ የወጣው ሕዝብ ብዛት ከ10 ከመቶ እንደማይበልጥና ሕዝቡ ጥሪያቸውን ሰምቶ በምርጫ አለመሳተፉ ያረካቸው መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።   ምርጫውን በቅርብ የተከታተሉት  ዓለም አቀፍ የዜና ማሰራጫ ተቋሞችም በዋና ከተማዋ እና በሌሎች ከተሞች ተዘዋወረው የምርጫውን ሂደት የታዘቡ መሆናቸውን ገልጸው በበተመንግስቱ አቅራቢያ ከሚገኘው የምርጫ ጣቢያ በስተቀር በሌሎች የምርጫ ጣቢያዎች ለምርጫ የወጣው ሕዝብ ቁጥር በጣም አነስተኛ እንደነበር መስክረዋል። የመንግስቱን መግለጫ ከእውነት የላቀ ማጭበርበር ነው በማለት ተቃዋሚ ኃይሎች ድርጊቱን ማውገዝ የጀመሩ ሲሆን ከዚህ በኋላ የሚወስዱት እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም።

 

Ø ባለፈው ሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ውስጥ  ሮኬት ተኳሽ መሳሪያዎችንና መትረየሶችን የያዙ ግለስቦች ከፖሊሶች ጋር ባደረጉት ግጭት ሶስት ሰዎች መገደላቸውንና 15 የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸውን የብሩንዲ ፖሊስ ገልጿል።  ሰኞ ዕለት በአንድ አካባቢ በቆንጨራ የፖሊስ መኮንኖችን ሊገደል የሞከረው ሰው ወዲያውኑ መገደሉንና እንዲሁም ከጥቂት ጊዜ በኋላ አንድ ሌላ ሰው በፖሊሶች ላይ በወረወረው ቦምብ ሰባት የፖሊስ አባላትን እንዲሁም ሁለት ወታደሮችንና ሶስት ሰላማዊ ሰዎችን ሲያቆስል አንድ ሰላማዊ ሰው የገደለ መሆኑን የፖሊሱ ቃል አቀድባይ ተናግሯል። በሌላ ጊዜና ቦታ ደግሞ አንድ መሳሪያ የያዘ ሰው አንድ የፖሊስ መኮንን ገድሏል ተብሏል። በተለያዩ ቦታዎችና በተለያዩ ጊዜዎች በደረሱት ጣቆቶች  የሞቱትና የቆሰሉት ሰዎች ብዛት ፖሊስ ከሰጠው መረጃ ከፍተኛ ነው ብለው በቦታው የነበሩ የዓይን እማኞች ይግለጻሉ። በርካታ ፖሊሶች መገደላቸው የተነገረ ሲሆን ማክሰኞ ዕለት በጥይት የተበሳሱ አስከረኖች መንገድ ላይ ወድቀው ተገኝተዋል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ ለመወዳደር የወሰኑ መሆናቸውን ከገለጹበት ካለፈው ሚያዚያ ወር ጀመሮ በአገሪቷ ውስጥ በየመንገዱ ግድያ የተበራከተ መሆኑ እየተነገረ ሲሆን ወደ ጠቅላላ የእርስ በርስ ውጊያ ያመራል የሚል ስጋት ከፍተኛ መሆኑንም ተግልጿል። እስካሁን ባለው መረጃ ከ200 በላይ የሆኑ የአገሪቱ ዜጎች መሞታቸውና ከ200 ሺ በላይ መሰደዳቸው ይታወቃል።

 

Ø በግብጽ ለምክር ቤት አባልነት የሚደረገውን ምርጫ አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት ምርጫ ያልተካሄደባቸው ጠቅላይ ግዛቶች  በዛሬው ዕለት ምርጫ ሲካሄዱ መዋላቸው ተነግሯል። ከ27 ጠቅላይ ግዛቶች  መካከል 14 በሚሆኑት ባለፈው ሳምንት ምርጫ መካሄዱ የታወቀ ሲሆን ድምጽ በመስጠት የተሳተፈው ሕዝብ ብዛት  26.6 ከመቶ ብቻ እንደነበር ተገልጿል። በዛሬው ዕለት ለምርጫ የወጣው ሰው ብዛት ከፍተኛ ይሆናል ተብሎ አይጠበቅም። ዶኪ በሚባል ቀበሌ የምርጫው ጣቢያ ተከፍቶ ሰዓታት ከቆየ በኋላ 20 ሰው ብቻ ድምጹን ሲሰጥ መታየቱ ሕዝቡ በምርጫው ለመሳተፍ ፍላጎት የሌለው መሆኑን ያሳያል የሚሉ ታዛቢዎች በርካታ ናቸው። የዛሬ አራት አመት ለምክር ቤት አባልነት በተካሄደው ምርጫ ከመራጩ ቁጥር 62 ከመቶ የሚሆነው ድምጹን የሰጠ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በየመን በሁቲዎች ላይ በተከታታይ የአየር ጥቃት የሚያካሂደው በሳኡዲ የሚመራው የየአይር ኃይል ሳዳ በሚባለው ቦታ ድንበር የለሽ ሀኪሞች የህክምና አገልግሎት በሚሰጡበት ሃኪም ቤት ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃት አድረሶ ሃኪም ቤቱን ከማፈራረሱ በላይ በርካታ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ያደረሰ መሆኑን የድርጅቱ ቃል አቀባይ በቲውተር አማካይነት ባስተላለፈው ዜና ገልጿል። በሁቲ ቁጥጥር ስር ያለው የሳባ ዜና ወኪልም የሆስፒታሉን ዳይሬክተር ዋቢ በማድረግ ባስተላፈው መረጃ  በአየር ጥቃቱ ምክንያት የሆስፒታሉ ህንጻ እና በሆስፒታል ውስጥ የነበሩ የህክምና መሳሪያዎች ከጥቅም ውጭ መሆናቸውንና በርካታ በሽተኞችና ሰራተኞች መጎዳታቸውን አረጋግጧል። የዜና ወኪሉ በተጨማሪ በሰጠው መረጃ መሰረት የሳዑዲ የአየር ጥቃት በአካባቢው የሚገኘውን የሴቶች ትምህርት ቤት ደብድቦ ጉዳት ያደረሰ መሆኑን ገልጿል። የሳዑዲ መንግስት ስለጉዳዩ የሰጠው መግለጫ እስካሁን የሰጠው የለም። በተመሳሳይ ሁኔታ ከሶስት ሳምንት በፊት የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች በሰሜናዊ አፊጋኒስታን ኩንዱስ በተባለችው ከተማ ያለውን የድንበር የለሽ ሀኪሞች ሆስፒታል ደብድበው 22 ሃኪሞችና በሽተኞች መግደላቸው ይታወሳል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ ስህተት መሆኑን አምነው ይቅርታ የጠየቁ ቢሆንም “ድንበር የለሽ ሃኪሞች” የተባለው ድርጅት ጉዳዩ የጦርነት ወንጀል ስለሆነ በገለልተኛ አካል ምርመራ ተካሄዶ ጥፋተኞቹ ለፍርድ መቅርበ አለባቸው የሚል ጥያቄ ማቅረቡ ይታወቃል።     

 

  

 

 

ጥቅምት 15  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በዛሬው ዕለት የኃይሉ መጠን 7.5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰሜን አፍጋኒስታን የተከሰተ መሆኑ ተነግሯል። የመሬት መንቀጥቀጡ ማዕከል ያደረገው ቦታ የሂንዱ ኮሽ ተራራማ ቦታዎች ሲሆን ስሜቱ በህንድና በፓኪስታን አካባቢዎች ድንቃጤና ፍርሃትን ፈጥሯል። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በአፍጋኒስታንና በፓኪስታን ደግሞ 135 ሰዎች እንደሞቱ መረጃዎች ጠቁመዋል። አደጋው የደረሰው የመገናኚያ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በመሆኑ አደጋው ያደረሰው ጉዳት እየታወቀ ሲሄድ የሟቾቹ ቀጥር ሊያድግ የሚችል መሆኑ ተገምቷል። በአፍጋኒስታን በትምህርት ላይ ያሉ ተማሪዎች ከአደጋው ለማምለጥ ሙከራ ባደረጉበት ወቅት በተፈጠረ ግፍያና ጭንቅንቅ 12 ልጃአገረዶች የሞቱ መሆናቸው ታውቋል።  ላሆር በምትባለው የፓኪስታን ከተማ የስልክ መስመሮች የተቆራረጡ ሲሆን  በህንድም አንዳንድ ትምህርት ቤቶች እና  መስሪያ ቤቶች እንዲለቀቁ ተደርገዋል። በፓኪስታን በመሬት መንቀጥቀጡ ክፉኛ የተመታው ችትራል የተባለው ጠቅላይ ግዛት ሲሆን እስካሁን ድረሰ 11 ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ተነግሯል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተፈጠረው ከ200 ኪሎ ሜትር ጥልቀት በታች በመሆኑ በመሬቱ ላይ ሊያመጣ የሚችለው ጉዳት አነስተኛ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ። አካባቢው የመሬት መንቀጥቀጥ የሚያጠቃው መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ከአስር ዓመት በፊት ካሽሚር በሚባለው የፓኪስታን ግዛት የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ከ75 ሺ ሰው በላይ የገደለ መሆኑና ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ደግሞ በኔፓል የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ 9 ሺ ሰዎች ገድሎ 900 ሺ የሚሆኑ ቤቶች ያወደመ መሆኑ ይታወሳል።  

 

Ø እሁድ ዕለት በታንዛኒያ በአይቮሪ ኮስት እና በኮንጎ ምርጫዎች ተካሄደዋል። በታንዛኒያ ዜጎች ፕሬዚዳንታቸውን ለመምረጥ በብዛት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የጎረፉ ሲሆን ቀደም ብሎ በተካሄደው የአስተያየት መለከያ መሰረት ተወዳዳሪዎች ተቀራራቢ ድምጽ ያገኛሉ ተብሎ ተግምቷል። የምርጫ አስፈጻሚ ባለስልጣኖች በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የምርጫው ውጠት ሊታወቅ እንደሚችል ተናግረዋል። በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ረዣዥም ስልፎች ታይተዋል። አሸናፊ የሚሆነው ወገን በአነስተኛ ድምጽ የሚያሸንፍ ከሆነ ግጭትና ረብሻ ሊነሳ የሚችል ስጋት አለ።

 

Ø በተመሳሳይ ዜና ለረዥም ዓመታት ሽብርና ግድያ ሲካሄድ በነበረባት አይቮሪ ኮስት ውስጥ እሁድ ዕለት ፕሬዚዳንቱን ለመምረጥ የተደረገው ምርጫ  አገሪቱ ውስጥ ያለው የፖሊቲካ መረጋጋት የደረሰበትን ደረጃ  ሊያሳይ ይችላል የሚል አስተያያት በአንዳንድ ሰዎች ተሰጥቷል። የዛሬ አምስት አመት ለረዥም ገዜ ስልጣን ይዘው በቆዩት በሎሬንት ጋብጎ እና በአንድ ወቅት የዓለም የገንዘብ ድርጅት ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩት በአላሳን ኩዋታራ መካከል የተደረገውን የምርጫ ውድድር ተከትሎ በሁለቱ ሰዎች ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ከ3 ሺ ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወሳል። በፈረንሳይ ወታደሮች ድጋፍ  የኩዋታራ ደጋፊዎች የጋብጎ ወታደሮችን አሸንፈው ጋብጎ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ሲደረግ ኩዋታራ አሸናፊ ተብለው በስልጣን መቀመጣቸውም የሚታወቅ ነው ። ጋብጎ በቁጥጥር ስር ውለውና በሰው ማጥፋት ወንጀል ተከሰው በኒዘርላንድ እስር ቤት የሚገኙ ሲሆን የኩዋታራ ወታደሮች ላካሄዱት እልቂት ግን እስካሁን በተጠያቂነት ለፍርድ አልቀረቡም ሲሉ የሰብአዊ መብት ተከራራኪ ድርጅቶች ይከሳሉ። በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በአይቦሪ ኮስት የተረጋጋ የፖሊቲካ ሁኔታ  ተፈጥሯል ቢባልም አሁንም ቢሆን   አገሪቷ አማጽያን በሚቆጣጠሩት የሰሜን ግዛት እና የካታራ ደጋፊ  በሚገኙት በደቡብ ግዛት ተከፋፍላ ትገኛለች።  ከስድስት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ መራጮች ድምጽ ለመስጠት ይችላሉ በተባለለት የእሁድ ዕለቱ ምርጫ ምን ያህል ሰው እንደወጣ ለማወቅ ባይቻልም ቢያንስ በሰሜኑ ግዛት ለምርጫ የወጣው ሰው አነስተኛ መሆኑ ተነግሯል። የኩዋታራ ተወዳዳሪ ሆነው ከቀረቡት መካከል ፍትሃዊ አይደለም በማለት ቀደም ብለው ከምርጫው ራሳቸውን ያገለሉ ተወዳዳሪዎች መኖራቸው የታወቀ ሲሆን ሌሎች ግን በተለይ ከስልጣን የተነሱትን የአይቮሪያን ፖፑላር ፍሮንትን የተባለውን የጋብጎ ፓርቲን የሚወክሉት ቻርልስ ኮናን ባኒ ውድድሩን እስከመጨርሻው ለመቀጠል ፈቃደኛ ሆነዋል። የምርጫው የመጀመሪያ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

 

Ø በኮንጎ ሪፕብሊክ ደግሞ መራጮች ፕሬዚዳንታቸው ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ውድድር ሊቀርቡ ይችላሉ ወይስ አይችሉም በሚለው ጉዳይ ላይ ድምጻቸውን የሚሰጡበት ምርጫ እሁድ ዕለት ተካሄዷል። በስራ ላይ ባለው ሕገ መንግስት መሰረት ፕሬዚዳንቱ የሚመረጠው ለሁለት የምርጫ ጊዜ ብቻ ሲሆን ከ70 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ሰው ለፕሬዚዳንት ምርጫ እንዳይወዳደር ሀገ መንግስቱ ይከለክላል። የአሁኑ ፕሬዚዳንት ሳሱ እንጌሶ በሁለት ምርጫ ወቅቶች በስልጣን ላይ ከመቆየታቸውም በላይ ዕድሜያቸውም 71 ነው። ውሳኔ ሕዝቡ እንዲካሄድ የተደረገው የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን ለማራዘም ሆን ተብሎ  በተፈጠረ ተንኮል ነው በማለት በርካታ ተቃዋሚ ኃይሎች ተቃውማቸውን ከማሰማታቸው በላይ አንዳንዶቹ ሕዝቡ በምርጫው ላይ ባለመሳተፍ የአለውን የመረረ ተቃውሞ እንዲያሳይ ጥሪ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በትናንትናው ዕለት በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጩ ቁጥር አነሰተኛ መሆኑ የተቃዋሚ ኃይሎች ጥሪ የተሰማ ይመስላል።

 

 

የቀድሞ የናይጄሪያ የጸጥታ አማካሪ መሀመድ ሳምቦ ዳሱኪ ባለፈው ሐምሌ ወር በጉቦና ሕገ በሆነ መንገድ የገንዘብ ዝውውር ተግባር ላይ ተሰማርተዋል  በሚል ጥርጣሬ ፖሊሶች ቤታቸው ውስጥ ገብተው ፍተሻ ባካሄዱበት ወቅት 423 ሺየአሜሪካ ዶላር እና የናይጄሪያ ገንዘብ ከቤታቸው ውስጥ የተገኘ መሆኑን ከፍርድ ቤት ከተገኘ የሰነድ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። አዲሱ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ስልጣን በያዙበት ወቅት ሲመጡ በሙስና የተበከሉ ባለስልጣኖችን ለፍርድ ለማቅረብ ቃል መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን ምርመራ እንዲካሄድባቸው ከነበሩ ባለስልጣኖች መካከል አንዱ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ጉድ ላክ ጆናታን የቅርብ አማካሪ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ዳሱኪ ናቸው። ዳሱኪ ሰኞ ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል።  

 

 

 ጥቅምት 13  ቀን 2008 ዓ.ም   

       

Ø በድርቁ ሳቢያ በአፋር ግዛት እየሞቱ ያሉት  የቀንድ ከብቶች ቁጥር የጨመረ መሆኑ ከአካባቢው የሚገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። ከአሳይታ ከተማ በደረሰው መረጃ መሰረት በአካባቢው ቦና ይዟቸው በየቀኑ እየሞት የሚገኙ የቀንድ ከብቶችና ግመሎች ቁጥር በእጥፍ በመጨመሩ  ምክንያት አደጋው  አሳሳቢና አስደንጋጭ ደረጃ ላይ የደረሰ መሆኑ ተገልጿል። የቀንድ ከብቶች በብዛት በሚሞቱበትና  በርካታ ህጻናት በምግብ እጥረት በሚሰቃዩበት ሁኔታ የተከማቸ እህልም ሆነ የእንሣሳት መኖ  እያከፋፈልኩ ነው በማለት  በመገናኚያ ብዙሀን አማካይነት ነጋጠባ የሚለፍፈው ወያኔ በአካባቢው የተከሰተውን ችግር ለመቅረፍም ለመቀነሰ ያደረገው አስተዋጾ የሌለ መሆኑን ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይጠቁማሉ። በድርቁ ሳቢያ የሚያልቁት የቀንድ ከብቶቹና ግመሎች መጠን በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ሀብቱና ንብረቱ የቀንድ ከብትና ግመል ብቻ የሆነው አርብቶ አድር በታሪኩ አይቶት የማያውቀው ከፍተኛ ችግር ውስጥ ሊወድቅ የሚችል መሆኑ በግልጽ እየታየ ነው በማለት ታዛቢዎች እየተናገሩ ነው።

 

Ø የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ለቤት ሰራተኛነት ሆነ ለሌላ ስራ ወደ አገሩ ሊገቡ ስለሚችሉ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ አዲስ ህግ እያረቀቀ መሆኑን ጠቁሞ በዚህ በኩል የሚደርስበትን ውሳኔ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል። በሳዑዲ አረቢያም ሆነ በሌሎች አረብ አገሮች በግርድና የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ጉልበታቸው እየተበዘበዘና ሰብአዊ ክብራቸው እየተደፈረ ሲሰቃዩ የቆዩ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ይወጣል የተባለው አዲስ ህግ የእቶቻችንን መብት ያስጠብቃል ተብሎ አይጠበቅም የሚሉ አሉ። ጉልበታቸው እንዲበዘብዝ ዜጎቻችንን ወደ ውጭ በማስወጣት ከፍተኛ ንግድ የሚያካሄዱት የወያኔ ባለስልጣኖች የሳኡዲ አረቢያ መንግስት በዚህ በኩል የሚያደርገው ውሳኔ በአንክሮ እየተከታተሉት መሆኑ ለመገንዘብ ተችሏል።

 

Ø ለወያኔ አገልጋይና አሽከር ሆኖ በወያኔ የተፈጠረው ብአዴን የተባለው ድርጅት ለምስረታው በዓል ማዘጋጃ የሚሆን ገንዘብ አዋጡ በማለት በአማራው አካባቢ ያሉ ዜጎችን በማስጨነቅ ላይ ያለ መሆኑ ከተለያዩ ቦታዎች የተገኙ መረጃዎች ይገልጻሉ። በአነስተኛ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ500 ብር ጀምሮ በመካከለኛ ንግድ ላይ ያሉ ከአስር ሺ ብር ጀምሮ ባለሆቴሎቾና ታላላቅ በተባሉ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩት ደግሞ ከአምሳ ሺ ብር በላይ መዋጮ የተጣለባቸው መሆኑን ተነግሯል። የተጣለበትን መዋጮ ሳይከፍል የተገኘ ግለሰብ ትምህርት ሊሰጥ የሚችል የቅጣት እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑን የብአዴን ካድሬዎች ውስጥ ውስጡን በማሰራጨት ላይ መሆናቸው ተደርሶበታል።

 

Ø ካይሮ ፖስት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ አርብ ዕለት ባወጣው እትሙ ወደ አገር ውስጥ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ገብታችኋል በሚል ምክንያት 10 ኢትዮጵያውያን እና 11 የሱማሌ ዜጎች የግብጽ መንግስት ያሰራቸው መሆኑን ገልጿል። ስደተኞች የተያዙት በደቡብ የግብጽ ግዛት በባቡር ሲጓዙ መሆኑ ጋዜጣው በአምዱ ላይ ቢያሰፍርም ለምን ያህል ጊዜ  በግብጽ ውስጥ የቆዩ መሆናቸውን  አልገለጸም። ከሊቢያ ወደ አውሮፓ በብዛት እየጎረፉ ለሚገኙት ስደተኞች ግብጽ አንዷ የመተለለፊያ ቦታ እንደሆነች ሲታወቅ በብዛት ከሚገቡ ስደተኞች መካከል በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት ይታወቃል።  የወያኔን አስከፊ አገዛዝና በአገር ውስጥ ያለውን የኑሮ ችግር በመሸሽ በየአቅጣጫው ከአገራቸው እየወጡ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱ ሲታወቅ በግብጽ በኩል አቆራርጠው ወደ አውሮፓ የሚጓዙትም ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ግልጽ ነው።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሱማሊያ እና በሻዕቢያ ላይ ቀደም ብሎ በውሳኔ አስተላልፎት የነበረውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት ያህል እንድራዘም  በትናንትናው ዕለት ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑ ተገለጸ። በሱማሊያና እና በኤርትራ ያለውን ሁኔታ እንዲከታተል  ተቋቁሞ የነበረውና (Somalia and Eritrea Monitoring Group) እየተባለ የሚጠራው   አካል ለመጭው አንድ ዓመት በሃላፊነቱ እንዲቀጥል ምክር ቤቱ የወሰነ ሲሆን በተለይ የሻዕቢያ መንግስት ቡድኑን ስራውን ለመጀመር ወደ ኤርትራ  የሚገባበትን መንገድ እንዲያመቻቸ የሚጠብቅ መሆኑን ገልጿል። ከዚህም ጋር አያይዞ በኤርትራ ውስጥ ስለታሰሩት የጂቡቲ እስረኞች ሁኔታ መረጃ እንዲሰጥ የሻዕቢያ መንግስትን ጠይቋል። ምክር ቤቱ በሱማሊያ ውስጥ በሰብዓዊ ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለው አደጋ ያሳሰበው መሆኑን ገልጾ በድርጅቶች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት አውግዟል። በሱማሌያ ውስጥ በመንግስት ባለስልጣኖች  በሙስና የሚዘረፈው ሀብት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጾ የሱማሊያ የሰላምና የእርቅ ሂደትን የሚያጨናግፉ ባለስልጣናት ሁሉ ላይ ማዕቀብ የሚደረግባቸው  መሆኑንም በመግለጽ አስጠንቅቋል።

 

Ø የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ በትናንቱ ዕለት በቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር በመጭው የትምህርት ዘመን  ለትምህርት በሚደረገው ክፍያ ላይ ጭማሪ እንደማይደረግ አሳወቁ። ፕሬዚዳንቱ መልእክታቸውን በቴሌቪዥን በሚያስተላልፉበት ወቅት ከበርካታ የደቡብ አፍሪካ ከተሞች  ተቃውሟቸውን ለማሰማት የተሰባሰቡ  ተማሪዎች የመንግስት መቀመጫ ወደ ሆነው ወደ ዩኒይን ህንጻ ለመግባት ሲሞክሩ  ከፖሊሶች ጋር ግጭት ተፈጥሮ  የነበረ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪ ሚስተር ዙማ  በአሁኑ ወቅት በትምህርት ክፍያው ላይ  የተድረገው ጭማሪ የተነሳ ቢሆንም ከረዥም ጊዜ አንጻር መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮቹ ይኖራሉ ብለዋል። የትምህርት ክፍያው አለመጨመሩ በግምባር ቀደምትነት ሲታገሉ የነበሩ ተማሪዎችን ያረካ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም ይህ ውሳኔ ለምን ቀደም ብሎ እንዳልተወሰነ ብዙዎችን አስገርሟል። የተለያዩ የዩኒቨርሲቲ  ባለስልጣኖች የዩኒቨርስቲዎችን የትምህርት ደረጃ ለመጠበቅ ክፍያው መጨመሩ አስፈላጊ መሆኑን የገለጹ ሲሆን  የክፍያ ጭማሪውን ለመሸፈን ገንዘቡ እንዴት እንደሚከፈልና ማን እንደሚከፍለው  የማያውቁ መሆናቸውን የመንግስት ባለስልጣኖች ተናገረዋል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በማይዱግሪ ውስጥ አንድ ቦምብ ፈንድቶ 15 ሰዎች ከገደለ በኋላ ዮላ በተባለችው ከተማ ውስጥ አንድ በቅርቡ በተሰራ አዲስ መስጊድ ውስጥ በሌላ አጥፍቶ ጠፊ በፈነዳ ቦምብ 27 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል።  ዛሬ ጠዋት ደግሞ አራት አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ ሴቶች ወደ ማይዱጉሪ ከተማ ከመግባታቸው በፊት የአካል ፍተሻ እንዲደርግላቸው ከተማዋን በሚጠብቁ የሲቪል ሚሊሺያዎች ሲጠየቁ ፈቃደኛ ካለመሆናቸውም በላይ  የያዙትን ቦሞቦች አፈንድተው ራሳቸውንና አንድ ሰላማዊ ሰው ሲገድሉ ከ10 በላይ የሆኑ ሰዎች ያቆሰሉ መሆናቸውን የከተማዋ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ቦምቦቹ በማፈንዳት ኃላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም የቦኮሃራም ታጣቂዎች መሆናቸው ይታወቃል።

 

Ø በሊቢያ ምስራቃዊ ከተማ ቤንጋዚ ውስጥ ሰላማዊ የተቃውሞ ስልፍ በሚያደርጉ ዜጎች ላይ በተተኮሱ የሞርታር  ጥይቶች ስድስት ሰዎች መሞታቸውና ከ30 በላይ መቁሰላቸው ታወቀ። የተቃውሞ ስልፉ የተካሄደው በቅርቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዑክ ያቀረቡትን  የሽግግር መንግስት ምስራታ የእርቅ ሀሳብን በመቃወም ሲሆን ሞርታሮቹ የተተኮሱት በእስላማዊያኑ ቁጥጥር ስር ካሉ ቦታዎች መሆኑ ተነግሯል። ከላፈው ዓመት ጀምሮ በቤንጋዚ በወታደሩ እና በእስላማውያን ኃይሎች መካከል ግጭቶች ሲደረግ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን  ከአክራሪ እስላማውያኑ ኃይሎች መካከል አንሳር አል ሻሪያ የተባለውና ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ ከሚጠራው ጋር ግንኙነት እንዳለው በይፋ ያሳወቀው ቡድን አንዱ ነው።  

    

 

 

 

        ጥቅምት 12  ቀን 2008 ዓ.ም

                          

          

Ø ከአይርላንድ ዋና ከተማ ከደብሊን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ደለስ አይሮፕላን ጣቢያ ይበር የነበረው ኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለበረራ ከተነሳ ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ አንዱ ሞተር መስራት በማቆሙ በአስቸኳይ ወደ ደብሊን ተመልሶ በሰላም ያረፈ መሆኑ ተነግሯል። የበረራ ቁጥር ETH 500 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 787-800 ድሪም  ላይነር አውሮፕላን የተነሳው ከአዲስ አበባ ሲሆን እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከ45 ደቂቃ ላይ ደብሊን ገብቶ ከጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ ጉዞውን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ቀጥሎ ነበር። ለአንድ ሰዓት ከሰላሳ የበረራ ጊዜ በኋላ አብራሪዎቹ ባገኙት እክል ምክንያት አንዱን ሞተር ለማጥፋት በመገደዳቸው ይህንኑ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ለደብሊን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አሳውቀውና እና በቀላል ክብደት ለማስራፍ እንዲቻል አውሮፕላኑ ውስጥ ያለውን ብዙ ሺ ሊትር የሚገመት ነዳጅ ለአስር ደቂቃ ያህል ከአየር ላይ አራግፈው አውሮፕላኑን በሰላም እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ከሰላሳ ላይ ደብሊን አውሮፕላን ማረፊያ አሳርፈውታል። በአሁኑ ወቅት የችግሩ መነሻ በአዋቂዎች እየተመረመረ ይገኛል።  

 

Ø በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎች ተወካዮች የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማን ዛሬ አርብ በሚያነጋግሩበት ወቅት ድጋቸውን ለማሳየት በሁሉም አካባቢዎች ያሉ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ተማሪዎች በአውቶቡስና በባቡር ወደ ፕሪቶሪያ የሄዱ መሆናቸው ተነገረ። ከስፍራው በደረሰው ዘገባ መሰረት ተማሪዎቹ የላሲትክ ጎማዎችን በማቃጥልና ድንጋይ በመወርወር ተቃውሟቸውን በመግለጽ ከፖሊሶች ጋር የተጋጩ ሲሆን ፖሊሶችም ተጋፊ ውሃና አስለቃሽ ጢሶችን በመጠቀም ሰልፉን ለመበተን ሞክረዋል። ሚስተር ዙማ ከተማሪዎቹ ጋር በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የዩኒቨርስቲዎቹ  ባለስልጣኖች ይገኛሉ የተባለ ሲሆን  ሚስተር ዙማ ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ  የዩኒቨርስቲ የትምህርት ክፍያ የሚወሰነው በየዩኒቨርስቲዎቹ አስተዳደር መሆኑን ጠቁመው  ከደሃ ቤተሰብ የመጡ ተማሪዎች ጭማሪው እንዳይደረገ ጥያቄ ማቅረባቸው ተገቢ ነው ብለዋል። የዩነቭርስቲዎቹ አስተዳዳሪዎች በበኩላቸው የትምህርቱን ክፍያ ለመጨመር የተገደዱት መንግስት ይሰጥ የነበረው ክፍያ በጣም በመቀነሱና የትምህርቱን ደረጃ ለመጠበቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል። የተማሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የጀመረው ባለፈው ሳምንት በጆሃንስበር ከተማ በሚገኙት ሁለት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ሲሆን ከዚያ ወዲህ በሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ 10 ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ  የተዛመተ መሆኑ ይታወቃል። ስልፉን ያካሄዱት  አብዛኞቹ ተማሪዎች ከደሃ ቤተሰብ የመጡ ሲሆን ሃብታም ከሆኑ ቤተሰቦች የመጡ ነጮች ተማሪዎችም ትብብር ለማሳየት በሚል ሰልፉን ተቀላቅለዋል።  አንዳንድ ታዛቢዎች የተማሪዎቹ የተቃውሞ ሰልፍ ሕዝቡ በገዥው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ፓርቲ ላይ ያለው እምነት እመነመነ መምጣቱን ያሳያል ይላሉ።

 

Ø ዛሬ አርብ በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በማይዱጉሪ ከተማ በአንድ መስጊድ ውስጥ በአጥፍቶ ጠፊ በፈነዳ ቦምብ 28 ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውን በአካባቢው የሚገኙ  የሚሊሺያ አባሎች  ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዘና ወኪል ገልጸዋል። የዜና ትክክለኛነት ከሌሎች ነዋሪዎች የተረጋገጠ ሲሆን ጥቃቱ የተፈጸመው በቦኮሃራም እንደሆነ ተገምቷል።

 

Ø የአውሮፓው ህብረት ተወካዮች ሰኞ ዕለት በብራስልስ በሚያካሂዱት ስብሰባ  የብሩንዲ መሪዎችን ለውይይት ወደ ብራስልስ የሚጋብዝ የጥሪ ደብዳቤ የሚያጸድቁ መሆኑ ተነገረ። የአውሮፓው ኅበርት ይህንን ጥሪ ለብሩንዲ ባለስልጣኖች  የሚያስተላልፈው የሰብዓዊ መብት ሌሎች የአገሪቱን ዋና ዋና ችግሮች አስመልክቶ በአውሮፓው ህብረትና በብሩንዲ መካከል የውይይት መድረክ እንዲከፈት ለማድረግና በሁለቱም በኩል ተቀባይነት ያለው መፍትሔ ላይ ለመድረስ ጥረት ለማድረግ ነው ተብሏል። የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ለሶስተኛ ጊዜ ምርጫ ውስጥ መግባታቸውን ካሳወቁ ወቅት ጀምሮ በብሩንዲ በተነሳው ተቃውሞና በተከተለው ግጭት ከ120 ሰዎች በላይ ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 190 ሺ የሚሆኑ ዜጎች ለስደት ተዳርገዋል። የአውሮፓው ህብረት ይህንን ድርጊት አውግዞ በተወሰኑ የብሩንዲ ባለስልጣኖች ላይ ማዕቀብ የጣለ መሆኑ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩዋንዳው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናይሮቢ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሩዋንዳ በብሩንዲ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብታለች የሚለውን የብሩንዲን ክስ ማስተባበላቸው ተነግሯል። ሚኒስትሯ “የብሩንዲ ችግር የብሩንዲ እንጅ የሩዋንዳ አይደለም” ካሉ በኋላ “የአንድ አገር መሪ በአንድ ጉዳይ ላይ ውሳኔ ከወሰደ በኋላ ውሳኔው የሚያስከተለውን ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ መሆን አለበት” ብለዋል።  የሩዋንዳ ምኞት በብሩንዲ ውስጥ ሰላም ሰፍኖ በሩዋንዳ የሚገኙ ስደተኞች ወደ አገራቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች ነው ብለዋል።  በሩዋንዳ ውስጥ በርካታ ስደተኞች ከመኖራቸው በተጨማሪ የሩዋንዳ ዋና ከተማ ኪጋሊ የብሩንዲ ተቃዋሚ ኃይሎች፤ የሲቪክ ማህበረሰብ መሪዎችና ከብሩንድው ፕሬዚዳንት ፓርቲ የከዱ ታላላቅ ሰዎች መቀመጫ መሆኗ ይታወቃል።  ከብሩንዲ የከዱ ወታደሮችን በማደራጀት ሩዋንዳ  ጦር ልትከፍት አቅዳለች በማለት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ሩዋንዳን እየከሰሱ ይገኛሉ።     

       

 

 

 ጥቅምት 11  ቀን 2008 ዓ.ም                

 

      

Ø በጦርነት ቀጠና ውስጥ ያሉ 30 ሺ የደቡብ ሱዳን ዜጎች በምግብ እጦትና በረሃብ የተነሳ የሞት አደጋ ሊደርስባቸው እንደሚችል  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት  አካሎች የሆኑ ሶስት ድርጅቶች  በጋራ ባወጡት መግለጫ  ገለጹ።  የተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅት፣(FAO)  የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) እና የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ባወጡት የጋራ መግለጫ በከፍተኛ ደረጃ በምግብ እጥረት የተጎዳው ቦታ በነዳጅ ዘይት ሀብታም የሆነውና አሁን ጦርነት የሚካሄድበት የደቡብ ሱዳን ሰሜናዊ ክፍል ነው ብለዋል።  የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ወደ ቦታው ሄደው እርዳታ መስጠት ካልቻሉ ከፍተኛ እልቂት የሚፈጠር መሆኑን ገልጸው አካባቢዎችን የሚቆጣጠሩት ወገኖች እርዳታ ሰጭዎች  ወደ ቀጠናቸው ገብተው ስራቸውን ሊሰሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በተያያዘ ዜና ባለፈው ዓመት በነሐሴ ወር በአማጽያኑ በመንግስቱ መካከል  የተፈረመው  የሰላም ስምምነት በስራ ሊውል በሚችልበት ጉዳይ ላይ ለመወያያት አደስ ውይይት በአዲስ አበባ የተካሄደ መሆኑ ተገልጿል። ሁለቱ ተጻራራሪ ወገኖች ስምምነቱን በመጣሳቸው በአደራዳሪዎቹ በተደጋጋሚ መወገዛቸው የሚታወስ ሲሆን አዲስ ድርድር ውስጥ መግባት ባይቻልም ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ማክሰኞች ዕለት ውይይት ሲካሄድ መቆየቱ ተገልጿል።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ ተማሪዎች የሚያያካሂዱትን የተቃውሞ ሰልፎች አጠናክረው የቀጠሉ ሲሆንበትናንትናው ዕለት  በኬፕታውን ከተማ የሚኖሩ ተማሪዎች ከፓርላማ ውጭ የተቃውሞ ስልፍ አድርገዋል። ወደ ምክር  ሕንጻ ውስጥ ጥሰው ለመግባት ሙከራ ሲያደርጉ ፖሊስ አስላቃሽ ጋዞችንና አስመሳይ ፈንጅዎችን በማፈንዳት  ስልፉን ለመበትን ጥረት ያደረገ ሲሆን  29 ተማሪዎችን ይዞ ያሰረ መሆኑ አስታውቋል።  በዛሬው ዕለት  የታሰሩት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በሕዝብ መካከል ረብሻ በማስነሳት በሚል ክስ ተከሰዋል። የእምንት ክህደት ቃል እንዲሰጡ ያልተጠየቁ ሲሆን ጉዳያቸውም ለሚቀጥለው ጥር ወር ተቀጥሯል።   የደቡብ አፍርካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ነገ አርብ የተማሪዎችን ተወካዮች ለማነጋገር የሚፈልጉ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን የደሃ ተማሪዎች ጥያቄዎች አግባብ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት የሚጥሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።  መንግስት በ10 ከመቶ ለመጨምር አቅዶት የነበረውን የትምህርት ክፍያ ወደ ስድስት ከመቶ ዝቅ ያደርገ መሆኑን ቢገልጽም ተማሪዎች ያልተቀበሉት መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ በተቃዋሚ ኃይሎች የሚካሄዱት የተቃውሞ ስልፎች በትናንትናው ዕለትም ቀጥለው ለሁለተኛ ቀን ከፖሊሶች ጋር ግጭቶች ተፈጥረዋል። ማክሰኞ ዕለት ከፖሊሶች ጋር ተካሂዶ በነበረው ግጭት መንግስት 4 ሰዎች መሞታቸውን ቢገልጽም ተቃዋሚ ኃይሎች ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል። ረቡዕ ዕለት በተደረገው የተቃውሞ ስልፍም ከፖሊሶች ጋር ግጭቶች መከሰታቸው የተነገረ ሲሆን ጉዳት መድረሱና አለመድረሱ ግን አልታወቀም። በዚሁ ዕለት ስድስት የተቃውሞ ድርጅት ቃል አቀባዮች ለጋዘጠኞች መግለጫ ለመስጠት ሲሰናዱ ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø የሰዳን መንግስትን እና የ ሱዳን ሕዝብ ነጻ አውጭ እንቅስቃሴ በሰሜን  (SPLM N) የተባለውን ድርጅት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለማስታረቅ በጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ ስብሰባ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በዚሁ ስብሰባ ላይ ለመገኘት የሱዳን መንግስት ፈቃደኛ መሆኑን ገልጿል። የሱዳን ህዝብ ነጻ አውጭ እንቅስቃሴ በሰሜን የሚባለው ድርጅት ከ2004 ዓም ጀምሮ በደቡባዊ ብሉ ናይል እና በደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በስብሰባው ላይ ለመገኘት መወሰንና አለመወሰኑን  እስካሁን አልገለጸም። ይህ አዲስ የእርቅ ስብሰባ ጥሪ የመጣው የሱዳን መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ለመነጋገር እና ለመስማማት አንዳንድ እንቅስቃሴዎች ባደረገበት ወቅት ነው። ቀደም ብሎ የሱዳን መንግስት ትጥቅ ያነሱ ተጻራሪ ኃይሎች የሱዳን መንግስት ባቀደው ብሔራዊ ውይይት ላይ እንዲገኙ ያስተላለውን ጥሪ ሶስት የዳርፉት ድርጅቶች እና የሱዳን ሕዝብ ነጻ አውጭ ድርጅት በሰሜን (SPLM N) የሚገኙበት  የሱዳን ሪቮሉሽናሪ ፍሮንት (SRF) ተብሎ የሚጠራው የህብረት ግምባር የሱዳን መንግስትን ጥያቄ ያልተቀበለ መሆኑን ገልጾ ስብሰባው ገለልተኛ በሆነ ቦታ እንዲካሄድ ጠይቆ ለስድስት ወራት ያህል ተኩስ ለማቆም ዝጁነቱን መግለጹ  ይታወሳል። 

በተያያዘ ዜና በሱዳን ዳርፉር ግዛት ውስጥ ለተሰማሩት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የተላከ ራሽን የሱዳን መንግስት በፖርት ሱዳን ለሳምንታት አግቶ ካቆየ በኋላ የለቀቀ መሆኑ ተገልጿል።  በፖርት ሱዳን የታገቱት  190 ኮንቴነሮች ውስጥ 52 የተለቀቁ መሆናቸው ሲገለጽ ሌሎቹም የሚለቀቁ መሆናቸው ተነግሯል። የሱዳን መንግስት ራሽኖችን ያገደበት ምክንያት ያልገለጸ ቢሆንም  ዳርፉር ውስጥ ጦርነት ስለሌለ የተመድ አስከባሪ ኃይሎች ቦታውን ለቀው መውጣት አለባቸው የሚል ጥያቄ  የሱዳን መንግስት ማቅረቡና ተመድ ደግሞ ሁኔታው ገና ነው በማለት የሰላም አስከባሪ ኃይሉ እንዲቆይ ማድረጉ ይታወሳል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት ከወታደራዊ ጥቃት ለማምለጥ በሽሽት ላይ የነበሩ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች  በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ  በአራት መኪናዎች ተሳፍረው በነበሩ ሰዎች ላይ ተኩስ ከፍተው 20 ሰዎች የገደሉ መሆናቸውን ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል። የቦኮሃራም ታጣቂዎች በሰፈሩባችው ካምፖች ላይ በናይጄሪያ መከላከያ ሰራዊት ጥቃትና ከበባ የተደረገባቸው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ጥቃቱን  ወታደራዊ ፒክ አፖችን ሞተር ቢስክሌቶችን ተጥቅመው ጥቃቱን በመሸሽ ላይ የነበሩ የቦኮ ሃራም ታታቂዎች  ባጋጣሚ ባገኟቸው መኪኖች ላይ ተኩስ ከፍተው ሰላማዊ ሰዎችን ከመግደላቸውና መኪናዎችን ከማቃጠላቸውም በላይ  በአካባቢው የነበረውን መንደሩ መዝረፋቸውና ቤቶችንም  ያቃጠሉ መሆናቸው ተነግሯል።

 

Ø የኮንፊውሸስ የሰላም ሽልማት የሚባለውና በ2003 ዓም ከኖቤል ሽልማት ድርጅት ተጻራሪ ሆኖ በቻይና የተመሰረተው ድርጅት በዚህ ዓመት የሰላም ሽልማቱን ለዚምባብየው ሮበርት ሙጋቤ የሰጠ መሆኑን አስታውቋል። የድርጅቱ መሪ ኪያዎ ዳሞ ፔኪንግ ውስጥ በሰጡት መግለጫ ሙጋቤ ለዓለም ሰላም ላበረከቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የዚህ ዓመት የኮንፊውሸስ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ለውድድር ቀርበው የነበሩ ተወዳዳሪዎች ቢል ጌትስ፣ የተመድ ዋና ፀሐፊ ባንኪ ሙን እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ፓርክ ግየን ሃይ ሲሆኑ ሙጋቤ አሸናፊ ሆነው ተሸላሚ ሆነዋል። የኮንፊውሸስ ሽልማት የተጀመረው በ2003 የስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ለሆነውና   በእስር ላይ ለነበረው  ቻይናዊው ለሊዩ ዚያቦ ሽልማት ከሰጠ በኋላ በተወሰደ የአጸፋ እርምጃ ነው። በምዕራብ አገሮች እየተኮነኑና እየተወገዙ የሚገኙት  ሙጋቤ ለሕዝባቸው  የሚጠቅም  የፖሊቲካ እና የኢኮኖሚ ግንባታ አካሂደዋል የሚል ገለጻ በመስጠት ኮንፊውሸስ የኖቤል ሽልማት ድርጅት አወድሷቸዋል። ሽልማቱ 80 ሺ ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የአሰጣጥ ስነስርዓቱ በታህሳስ ወር ይደርጋል ተብሏል። የኮንፈውሸስ የሰላም ሽልማት በግል ገንዘብ የሚደጎም ነው የተባለ ሲሆን በዚህ ጉዳይ እስካሁን ድረስ ላይ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሰጠው መግለጫ የለም።     

 

 

 

           ጥቅምት 10  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø ትናንት በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በብራዛቪል እና ፖይንት ኑዋር  ከተሞች    የተካሄዱትን  የተቃውሞ ስልፎች ለመበተን ፖሊሶች  በከፈቱት ተኩስ አራት ሰዎች መገደላቸውንና ከ 10 በላይ የሚሆኑት ደግሞ መቁሰላቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። የአገሪቱ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ለመንግስት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ ሶስት ሰዎች በብራዛቪል ከተማ ሲሞቱ አንደኛ ድግሞ በፖይንት ኑዋር መሞቱን ተናግረዋል። በተጨማሪ ሚኒስትሩ  ሶስት የጸጥታ ኃይል አባላት መቁሰላቸውን ገልጸው አስራ ስድስት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል።  አምነሲት ኢንተርናሽናል የተባለው የስብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ፖሊሶች ጥይት ከመተኮስና  አላስፈላጊ ከሆነ ኃይል ራሳቸውን እንዲያቅቡ ጥሪ ሲያደርግ የአሜሪካ ረዳት ምክትል ጸሐፊ ኪንሻሳ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደግሞ ሁሉም ወገኖች የኃይል እርምጃን አስወግደው ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠይቀዋል።  ከትናንቱ የተቃውሞ ሰልፍ በኋላ መንግስት ሁኔታው የተረጋጋ መሆኑን ገልጾ ሁሉም ወደ ስራው እንዲመለስ ትእዛዝ ቢያስተላልፍም ሱቆች ትምህርት ቤቶችና ቢሮዎች ተዘግተው የዋሉ መሆናቸው ተነግሯል። በኮንጎ ለእሁድ የታቀደውን ሕዝበ ውሳኔ በመቃወም ሕዝቡ ሰላማዊ የሆነ  ጠቅላላ የአመጽ መነሳሳት እንዲያደርግ ፓን አፍሪካን ዩኒየን ፎር ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ የተባለው  የተቃዋሚ ድርጅት መሪ ጥሪ ማድረጋቸውም ተነግሯል።

 

Ø ከ700 በላይ የሚሆኑ የኬኒያ ዜጎች አልሸባብን ጥለው የመጡ መሆናቸውን በመንግስት ድጋፍ የተሰናዳ አንድ ዘገባ ገልጿል። ኬኒያውያኑ  ከጥቂት ጊዜ በፊት አልሸባብን ለመቀላቀል ወደ ሶማሊያ ሄደው ለተወሰነ ጊዜ በድርጅቱ ውስጥ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ቢሆንም በመጀመሪያ ቃል የተገባላቸውን በርካታ ገንዘብ  ለማግኘት ባለመቻላቸው ወደ አገራቸው ለመመለስ መወሰናቸው ተገልጿል።

 

Ø በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎችን ተቃውሞ ለማርገብ መንግስት የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪን ከ10 ከመቶ ወደ ስድስት ከመቶ ዝቅ ቢያደርግም ተማሪዎቹ ማሻሻያውን የማይቀበሉት መሆናችውን ገልጸዋል።  ከዋና ዋና የተማሪ ማህበሮች ውስጥ አንዱ የሆነውና “ሳውዝ አፍሪካ ስቱደንትስ ኮንግሬስ” የሚባለው የተማሪ ማህበር  ማሻሻያውን እንደማይቀበለው ገልጾ በደቡብ አፍሪካ ያሉ ሁሉም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ትምህርት አቁመው ዩኒቨርስቲዎችን  እንዲዘጉ ጥሪ አቅርቧል። የተማሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተጀመረው ባለፈው ሳምንት ጆሃንስበርግ ባሉ ሁለት ዩነቨርሲትዎች ውስጥ በሚማሩ ተማሪዎች አማካይነት መሆኑ ሲታወቅ ከዚያ ወዲህ ወደሌሎች ቦታዎች ተሻግሮ ቢያንስ ስደስት በሚሆኑ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል።

 

Ø የሩሲያ መንግስት በሶሪያ ላይ እያካሄደ ያለው የአየር ጥቃት ከአሜሪካው የአየር ጥቃት ጋር ግጭት ፈጥሮ አደገኛ ሁኔታ እንዳይከሰስት ለመከላከል ሁለቱ አገሮች ተነጋግረው ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለጸ። የስምምነቱ ዝርዝርዝ ነጥቦች ምን እንደሆኑ ባይገለጽም አንዱ አገር ጥቃት በሚያካሄድበት ወቅት ሌላኛው መረጃ የሚደርስበትን ሄኔታ ለማመቻቸት የሚችል ፕሮቶኮል በጋራ ቀይሰው የተስማሙ መሆናቸው ተነግሯል። ይህ በዚህ እንዳለ የሶሪያው ፕሬዚዳንት አሳድ ወደ ሞስኮ ሄደው ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ተገልጿል። ባለፉት አራት አመታት ፕሬዚዳንት አሳድ ከሶሪያ ውጭ ሲወጡ ይህ የመጀመሪያቸው ነው ተብሏል።  አሳድ ከፑቲን ጋር ለሶስት ጊዜ ያህል ተገናኝተው በቅርቡ በጋራ እየወሰዱ ባሉት ወታደራዊ እርምጃ እና በአገሪቱ የፖሊቲካ ሁኔታ ላይ የተወያዩ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ከስብሰባው በኋላ ፑቲን ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ አሁን በሚካሄደው ወታደራዊ እርምጃ ምክንያት ዘላቂነት ያለውና በሶሪያ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም የፖሊቲካ የብሔረሰብና የሃይማኖት ክፍሎችን የሚያጠቃልል የረዥም ጊዜ መፍትሔ  ለማስገኝት የሚቻል መሆኑን ተናግረዋል።    

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን በፓለስታይን ዜጎችና  በእስራዕሎች መካከል እየተካሄደ ያለውን ግጭትና ደም መፋሰስ ለማስቆም በአካባቢው ያልተጠበቀ ጉብኝት ያደረጉ መሆናቸው ተገለጸ። ባንኪ ሙን በእየሩሳሌም ለጋዜጠኞች በሰጡት ወደ አካባቢው ያመጣቸው የሁኔታው አሳሳቢነት  መሆኑን ገልጸው ባስቸኳይ መቆጣጠር ካልተቻለ ሊመለስ ወደማይቻልበት አደገኛ አዝማሚያ ይሄዳል ብለዋል። የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ነታንያሁን ካነነጋገሩ በኋላም ለጋዘጠኞች በሰጡት መገለጫ ግጭቶችን ለማብረድ ብቸኛው መንገድ የተያዙትን መሬቶች መሬቶች ከመልቀቅ ጀምሮ በድርድር በሚመጣ ሁለገብ የፖሊካ መፍትሔ ነው ብለዋል። ባንኪ ሙን  ለፓለስቲኒያን ወጣቶች ባደረጉት ንግግርም ያሉበትን አሳዛኝ ሁኔታ ከልብ  የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸው  ሁኔታውን ለመቀየር መሳሪያና ኃይል እንደማይጠቅም ተናግረዋል። በሌላ በኩል ለእስራዕል ዜጎችም ባደረጉት ንግግር “ሰላምና ጸጥታ ለማግኘት ያላቸውን ፍላጎት እሳቸውም እንደሚያጋሯቸው ገልጸው ቤቶች በማፍረስና በጸጥታ ኃይሎች አማካይነት የሃይል እርምጃዎች መውሰድ ግን  የሚፈልጉት ሰላምንም ሆነ ጸጥታውን እንደማያገኙት አስረድተዋል። የፓለስታይኑን መሪ ፕሬዚዳንት አባስን ራማላ በተባለው ከተማ አነግጋርረው ከወጡ በኋላ በሰጡት መግለጫ በእስራኤልና በፓለስቲያን አስተዳደር መካከል ትርጉም ያለው ድርድር እንዲደረግ  መሆኑን ከፍተኛ ጥረት የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

 

         

 

ጥቅምት 9  ቀን 2008 ዓ.ም

         

የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል( African Standby Force) የሚል ስያሜ የተሰጠውና ቋሚ ሆኖ በተጠባባቂነት እንዲያገለግል የታቀደው የአፍሪካ ህበረት የሰላም አስከባሪ የኃይል ለወታደራዊ ስልጠና መሰባሰቡ ተገለጠ። ከአምስት የአፍሪካ የኢኮኖሚ ክፍሎች የተውጣጣውና በቁጥር እስከ 25 ሺ ይደርሳል ተብሎ ከተተገመተው  ተጠባባቂ ኃይል ውስጥ 5000 የሚሆኑ ከየአገሩ የተውጣጡ የፖሊስና የመከላከያ ሠራዊት አባላት  ዛሬ ማክሰኞ በደቡብ አፍሪካ ስልጠና የሚጀምሩ መሆናቸው ተነግሯል። ወታደራዊ ስልጠና የሚቆየው እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ሲሆን ለልምምድ ተብሎ በታቀደ ቦታ እንቅስቃሴ አድርገው ብቃታቸው ይመዘናል ተብሏል።      በአፍሪካ ውስጥ የሚነሱትን የእርስ በርስ ጦርነቶችና ግጭቶችን ለማብረድ አፍሪካ የሌሎች አገሮችን እርዳታ ጠባቂ መሆን ስለሌለባት ይህን ኃይል ማደረጀት ያስፈለገው በሚል ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለስልጣኖች ይገልጻሉ።  በአመት  ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ በጀት የሚያስፈልገውን ግዙፍ ኃይል ለማንቀሳቀስ አፍሪካ የውጭ እርዳታ የምትጠይቅ በመሆኑ በሌሎች እርዳታ ላይ መተማመኑ አይቋረጥም ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከዚህም በላይ ይህን አደራጅቶ ለማንቀሳቀስ የማስተባበር ችግር ያለ ሲሆን   ኃይሉን በማደራጀት አንዳንድ አገሮች የሚያሳዩት ፍላጎት ዝቀተኛ ነው። ተጠባባቂው የሰላም አስከባሪ ኃይል  በአፍሪካ ህብረት አባላል አገሮች ውስጥ በማንኛውም ወቅት  የጅምላ እልቂት የሰው ልጅ የማጥፋት ወንጀልና የጦርነት ወንጀሎች በሚከሰትባቸው አገሮች ውስጥ ሳይጠራ ጣልቃ የሚገባ ኃይል ነው ተብሏል ።

 

ላለፉት ሰላሳ አመታት በስልጣን ላይ የቆዩት የኮንጎው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ እንዲወዳደሩ የሚያስችላቸው የሕግ መንግስት ለውጥ ለማድረግ እሁድ ዕለት ሕዝቡ ድምጽ እንዲሰጥ የታቀደ መሆኑ  የሚታወስ ሲሆን ተቃዋሚዎች ይህን በመቃወም የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ፕሬዚዳንቱ ከሁለት ጊዜ በላይ እንዳይወዳደርና ዕድሜውም ከሳባ አመት በላይ እንዳይሆን የሚከለክለውን ሕገ መንግስት ለመቀየር  ለሰላሳ አመታት በስልጣን የቆዩት እና ዕድማዕያቸው ሰባ ሁለት ዓመት የሆኑት ፕሬዚዳንት የሚያደርጉት ሙከራ መፈንቅለ መንግስት ማካሄድ ነው በማለት ተቃዋሚዎች ባለፈው ቅዳሜ ከፍተኛ ትዕይንተ ሕዝብ ያደረጉ ከመሆናቸውም በላይ በዛሬው እለትም በዋናው ከተማ በብራዛቪል ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞ ስልፎች ተደርገዋል። ወጣቶች በቡድን እየሆኑ በተለያዩ የከተማዋ ቦታዎች ጎማዎችን በማቃጥል ተቃውሟቸውን መግለጻቸው የተነገረ ሲሆን  ፖሊስ በየቦታው ስልፉን ለመበተን በየቦታው የተሰማራ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። መንግስት የሞባይል እና የኢንተርኔት አገልግሎትም ማቋረጡና ሱቆች፣ ትምህርት ቤቶችና አገልግሎት ሰጭ የሆኑ ሕዝባዊ ድርጅቶች መዘጋታቸው ተነግሯል።  

 

በናይጀር ዋና ከተማ በኒያሚ ውስጥ በትናንትናው ዕለት የሁለተኛ ደረጃና የኮሌጅ ተማሪዎች የትምህርት ሁኔታዎች እንዲሻሻሉ በመጠየቅ የተቃውሞ ስልፍ አድርገው የዋሉ ሲሆን ፖሊስ በወሰደው እርምጃ 7 ሰልፈኞች መጎዳታቸውና ወደ 80 የሚጠጉ ደግሞ የታሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።   በቂ አስተማሪዎች እንዲመደብላቸውና የሚማሩበት ክፍልቾም እንዲጨምሩላቸው ቀደም ብለው የጠየቋቸው  ጥያቄዎች በቂ መልስ ባለማግኘታቸው ተማሪዎቹ ስልፉን ማካሄድ መገዳዳቸውን ገልጸዋል። የተቃውሞ ስልፉ ሰላማዊ እንዲሆን ጥረት ቢያደርጉም ፖሊስ ሰልፉን ለመበተን በወሰደው አላስፈላጊ እርምጃ ምክንያት ግጭቶች የተከሰቱ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ዘጠና ከመቶ የሚሆነውን የተማሪዎቹን ጥያቄዎች መመለሳቸውን የመንግስት ተወካዮች ቢገልጹም ተማሪዎቹ ጥያቄያቸው ካልተመለሰ ተመሳሳይ ስልፎች ለማድረግ እቅድ ያላቸው መሆኑን ተናግረዋል። በተባበሩት መንግስታት የእድገት መለከያ መሰረት በድህነት ከዓለም የመጨርሻውን ቦታዎች ከያዙት መካከል  አንዷ ናይጀር መሆኗ ይታወቃል ።

 

ባለፈው ሰኞ በሊብያ ምስራቃዊ ከተማ ውስጥ በተተኮሰ የመድፍ ጥይት አምስት ሰዎች መሞታቸውን የሆስፒታል ምንጮች ገልጸዋል። ከሞቱት መካከል አብዛኞቹ ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ሲሆኑ አድራጊው ማን እንደሆን ባይታወቅም  ጥቃቱ የተፈጸመው ላይቲ በተባለቸው ከተማ ውስጥ እንደሆነ ተነግሯል።  በሌላ በኩል ደግሞ  ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ቡድን ጥፋተኛ ናቸው ባላቸው ሁለት ሰዎች ላይ የቅጣት እርምጃ የወሰደ መሆኑን ገልጿል። ቡድኑ በኢንተርኔት ባስተላለፈው የቪዲዮ መልእክት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውን መግንስት በወታደርነት በማገልግል ወንጀል ፈጸመዋል ያላቸውን አንድ የደቡብ ሱዳን የክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነው ግለሰብና  አንድ የሊቢያ ተወላጅ የሆነውን መግደሉን አሳውቋል። ሰኞ ዕለት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኘው የሊቢያ ምክር ቤት የተመድን የዕርቅ ሀሳብ ውድቅ ማድረጉን የዜና ምንጮች ተናግረዋል።

 

 

 

 

 

 

ጥቅምት 8  ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø ትናንት እሁድ በኢየር ሸቫ በምትባለው የደቡብ እስራኤል ከተማ አንድ የኤርትራ ተወላጅ ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ተመትቶ ከወደቀ በኋላ በአካባቢ በነበሩ ሰዎች ከባድ ድብደባ ስለደረሰብት ህይውቱ ሊያልፍ ችሏል። የኤስራኤል የጸጥታ ኃይል ቃል አቀባይ በሰጠው መረጃ መሰረት ኤርትራዊ ስደተኛ በእስራኤል ወታደር በጥይት ሊመታ የቻለው  ቀደም ብሎ አንድ   የእስራኤል ወታደር ገድሏል ከሚል የተሳሳተ መረጃ በእስራኤል ፖሊሶች በተተኮሰ ጥይት ከተመታ በኋላ በአካባቢ የነበሩ ሰዎች ተረባርበው ቀጥቅተውታል ብሏል። ለህክምና ወደ ሆስፒታል ቢወሰደም ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነብር ከሞት ሊድን አልቻለም። በአካባቢዎ የነበሩ ሰዎች ጭካኔ በተሞላበት መንገድ የደበደቡበት ምክንያት ግልጽ ባይሆንም  የግለሰቡ በዚህ ዓይነት መንገድ መገደል በእስራኤል አገር ተስፋፍቶ የሚገኘው ዘረኛነት የደረሰበትን ደረጃ ያሳይል ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ።

 

Ø ደቡብ አፍሪካ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚማመሩ ተማሪዎች ለትምህርት የሚከፍሉት ገንዘብ በጨመሩ ምክንያት የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ተማሪዎቹ ወደዮኒቨርስቲዎቹ የሚያስገቡትን መንገዶች በመዝጋትና  ጎማና ላስቲኮችን በማቃጠል ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመት የትምህርት ክፍያው በ10 ከመቶ እንዲጨምር በመደረጉ በተለይ ከደሃ ቤተሰብ የመጡ በርካታ ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ጭማሪውን ለመክፈል የማይችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የዩኒቨርስቲዎቹ አስተዳዳሪዎች ትምህርት ለጊዜው ተቋርጦ ክፍሎቹ እንዲዘጉ ያደረጉ ሲሆን ችግሩ ለምን ያህል ጊዜ ሊቆይ እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም። ጸጥታውን ለመቆጣጠር ፖሊስ በየኒቨርስቲዎቹ የተሰማራ መሆኑ ተነግሯል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ቀደም ብለው የገለጹ ሲሆን አሁን በመጨርሻ በተገኘው ዜና መሰረት መንግስት የ10 ከመቶ ጭማሪውን ለጊዜው ያገደ መሆኑ ታውቋል።

 

Ø እሁድ ዕለት በግብጽ የተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ አስመልክቶ ለምርጫው የወጣው ሕዝብ ቁጥር በጣም አነስተኛ ሲሆን የግብጽ መንግስ ሰኞ ዕለት ለሚቀጥለው ምርጫ  ለሰራተኞች የግማሽ ቀን ፈቃድ የሰጠ መሆኑ ተነገረ። የትናንቱና የዛሬው ምርጫ የተካሄደው በ ግብጽ 14 ጠቅላይ ግዛቶችና በ ጊዛ እና በአሌክሳንድሪያ ከተሞች ሲሆን በሌሎች 13 ጠቅላይ ግዛቶችና በካይሮ ደግሞ በሚቀጥለው ወር ይካሄዳል ተብሏል። በትናትናው ዕለት ምን ያህል ሰው ወጥቶ ድምጽ እንደሰጠ ከመንግስት በኩል የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም ሁኔታውን ተዘውረው የተመለከቱት ታዛቢዎች ወደምርጫ ጣቢያዎቹ የሄደው ሰው ቁጥር በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጸዋል። እንዳዳዱቹ ቁጥሩ ከሁለት ከመቶ እንደማይበልጥ ሲገልጹ የመረጡትም ቢሆን እድሜያቸው የገፋ እንጅ ወጣቶች እንዳልሆኑ ተናግረዋል። አንዳንድ ታዛቢዎች  ወደምርጫ ጣቢያዎቹ ቁጥር  አነስተኛ መሆን  ሕዝቡ ለወታደራዊ መንግስት ያለው ድጋፍ አነስተኛ ነው በማለት የሙባረክ የስልጣን ዘመን የፖሊቲካ ሁኔታ እየተደገመ መሆኑን ይገልጻሉ። 

 

Ø ባለፈው ቅዳሜ ምሽት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች የሆኑ ሴቶች ባፈነዷቸው ቦምቦች 11 ሰዎች ሲሞቱ ሌሎች በርካታ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን ፖሊስ እሁድ ዕለት ከሰጠው መግለጫ ማወቅ ተችሏል። አጥፍቶ ጠፊዎቹ ቦምቦቹን ያፈነዱት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ “አዳማዋ” በሚባለው ግዛት ውስጥ ባለ “ዳር” በሚባለው መንደር ሲሆን  ቦምቦቹን ለማፈንዳት የቻሉት የቦኮ ሃራምን ጥቃት ፈርተው ወደጫካ  በተሰደዱ ዜጎች መሀል ተመሳስለው በመቀላቀላቸው  መሆኑ ተዘግቧል። የሞቱትን ሰዎች ቁጥር አስመልክቶ በቦታው ላይ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች የሚሰጡት ግምት ከፍ ያለ ቢሆንም  ፖሊስ 11 ሰዎች ብቻ መሆናቸውን አረጋግጧል። ከዚህ ቀደም አካባቢው በቦኮሃራም ታጣቂዎች በተደጋጋሚ የተጠቃ ሲሆን ጸጥታውን ለመቆጣጠር በቂ ወታደሮች ባለመመደባቸው ሁልጊዜ በፍርሃት የሚኖሩ መሆናቸውን በመግለጽ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ያሰማሉ።  በተያያዘ ዜና በዚሁ በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በማይዱጉሪ ከተማ አንዲት አጥፍቶ ጠፊ በቦርሳዋ የያዘችውን ቦምብ ለማፈንዳት ወደ ዋናው ወታደራዊ ካምፕ  ለመግባት ስትሞክር በአንድ ወታደር በተተኮስ ጥይት ስትመታ ቦምቡ ፈንድቶ የገደደላት መሆኑ ታውቋል። የፈንዳው ቦምብ ሌላ ያስከተለው ጉዳት እንደሌለም ተገልጿል። ከመስከረም አጋማሽ እስካሁን ባለው ጊዜ ብቻ በናይጄሪያ በቦኮሃራም ጥቃት ከ100 በላይ የሆኑ ሰላምዊ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ  የተመረጡት  ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ደግሞ 1370 ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። ቦኮሃራም በሰሜን ምስራቅ እየሰነዘረ ያለውን ጥቃት የመንግስት ምንጮች የሽንፈትና የቀቢጸ ተስፋ ምልክት ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ መንግስት አዳክሜዋለሁ ቢልም  ቦካሃራም አሁንም ቢሆን በጥንካሬ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ መሆኑን የሚያሳይ ነው ይላሉ።

 

በሊቢያ ያሉት ተጻራሪ ወገኖች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሊቢያ የእርቅና የአንድነት  መንግስት ስለሚቋቋምበት ሁኔታ ያቀረበውን ሀሳብ ተቀብለው ተግባራዊ እንዲያደርጉ የምዕራብና የአረብ አገሮች ባወጡት የጋራ መግለጫ ጠይቀዋል። የጋራ መግለጫው የወጣው በአልጄሪያ፣ በእንግሊዝ፤ በፈረንሳይ፤ በጀርመን፤ በጣሊያን፤ በሞሮኮ፤ በቃጣር ፤ በስፔን፤ በቱኒሲያ በቱርክ በተባበሩት የአራብ ፤ኤምሬት እና  የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የአውሮፓው ኅብረት የፖሊሲ ሹም  ሲሆን በሊቢያ በተመድ አማካይነት እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት እና ድርድር ላይ የነበሩ ወገኖች ሁሉ የተደረሰበትን ስምምነት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጥሪ ያደርጋል። በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተመስርተው የነበሩ ሁለት መንግስት ነን የሚሉ ክፍሎችን ለማስታረቅ በተመድ አማካይነት ድርድር ሲካሄድ የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ጊዚያዊ የአንድነት መንግስት እንዲመሰረት ተመድ ሀሳብ ማቅረቡ ይታወቃል።  የአንድነት መንግስቱን  ፋይዝ ኤል ሲራጅ በተባሉ የትሪፖሊው ምክር አባል እንዲመሩትና  እንዲሁም ከምስራቅ ከምዕራብና ከደቡብ የሚወክሉ አንዳንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች እንዲመደቡ በተመድ በኩል  ሀሳብ መቅረቡ ይታወሳል።

 

 

 

          

ጥቅምት 6   ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø የዓለም ባንክ በትናንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው ዓመታዊ ዘገባ  ባለፉት 20 ዓመታት በአፍሪካ ውስጥ ድህነት በመጠኑም የቀነሰ መሆኑን ጠቅሶ የሕዝብ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ በመጨመሩ ምክንያት በከፍተኛ የኑሮ ችግርና በስቃይ የሚኖሩ ዜጎች ቁጥር አሁንም ቢሆን ከፍተኛ መሆኑን ገልጿል። ባንኩ በ1982 ዓም ከአፍሪካ ሕዝብ መካከል 56 ከመቶ የሚሆነው  በቀን አንድ ዶላር ከዘጠና ሳንቲም በታች በሆነ ገቢ ይተዳደር እንደንበርና  በ 2005 ዓም ወደ ቁጥሩ ወደ 43 ከመቶ ዝቅ ማለቱን ጠቅሷል። የድህነቱ መጠን በ25 ዓመታት ውስጥ 13 ከመቶ ያህል ዝቅ ቢልም አሁንም ቢሆን ወደ ግማሽ የሚሆነው የአፍሪካ ሕዝብ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይኖራል ተብሏል። ከሌሎቹ ክፍለ ዓለማት ይልቅ ድህነት በአፍሪካ ውስጥ ስር ሰዶ የሚገኝ መሆኑን ዘገባው ጠቅሶ 388 ሚሊዮን የሚሆኑ የአፍሪካ ዜጎች በድህነት አረንቋ ውስጥ እንደሚኖሩ ዘርዝሯል። የዛሬ 25 ዓመት 600 ሚሊዮን የነበረው የአፍሪካ የሕዝብ ብዛት ከአስራ አምስት ዓመት በኋላ ወደ 1.6 ቢሊዮን ከፍ ሊል እንደሚችል ተገልጿል። ዘገባው የድህነቱ ሁኔታ ከአገር አገር ና በከተማና በገጠር መካከል ልዮነት እንዳለው በመግለጽ አንዳንድ አገሮች መሻሻል ያሳዩ መሆናቸውን አትቶ የወያኔ አገዛዝ መጠነኛ መሻሻል ከታየባቸው አገሮች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁሟል።  ድህነት ተስፋፍቶ በገሃድ በሚታይበት አገርና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ድህነትን ሸሽተው አገራቸውን እየጣሉ በሚወጡበት ሁኔታ መሻሻል አለ የሚለውን የባንኩን ዘገባ የሚጠራጠሩ በርካታ ምሁራን ናቸው።   

 

Ø ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ  ባጋ በተባለችው በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ውስጥ በምትገኘው ከተማ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ያካሄዱትን ወረራና ያደረሱትን ጉዳት በሚገባ አልተከላከልክም በሚል አንድ የናይጄሪያ ጄኔራል ተከሰው የተፈረደባቸው መሆኑ ተገለጸ። በተባለው ጊዜ ቦኮ ሃራም ጥቃቱን ሲፈጽም  በከተማዋ የነበረው የናይጄሪያ ጦር በማፈግፈጉ ምክንያት  ታጣቂዎቹ በርካታ ወታደራዊ መኪናዎች 12 ፒክ አፕ ቶዮታዎች ሶስት የሮኬት አምጣቂ መሳሪያዎችና ከ 12 የበለጡ አውቶማቲክ መሳሪያዎች እንዲሁም በጣም በርካታ ጥይቶች ሊማርክ ችሏል የሚል መረጃ የቀረበ ሲሆን  የቦካ ሃራም ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን ሲገድሉ ሌሎችንም በተለይ ሴቶችን ይዘው ሄደዋል ተብሏል። በቦታው የነበረው የናይጄሪያ ጦር መሪ ብርጋዴር ጄኔራል ራንሳም ኩቲ ርዳታ በመጠየቅ ጭምር ጦሩ  የቦኮ ሃራም ታጣቂዎችን በሚገባ እንዲቋቋም ባለማድረጋቸውና  እንዲያፈገፍግ በመገፋፋታቸው ለስድስት ወራት ያህል እንዲታሰሩና ከሰራዊቱ  እንዲባረሩ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የፈረደባቸው መሆኑ ታውቋል።  ጠበቃቸው ጄኔራሉ ጦሩ እንዲያፈገፍግ ያደረጉት የቦካ ሃራም ታጣቂዎች በቁጥር በመብለጣቸው ነው የሚል መከራከርያ ቢያቀርብም በዳኞቹ በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። የወታደራዊው ፍርድ ቤት ውሳኔ በወታደሩ ውስጥ ተስፋፍቶ የነበረውን የተስፋ መቁረጥና የክህደት እንቅስቃሴ  ይቀንሳል ተብሎ ተገምቷል። በተባበሩት መንግስታት እና በሌሎች  የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ዘገባ የቦኮ ሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረበት ከ2002 ዓም ጀምሮ ከ17 ሺ ሰዎች በላይ መገደላቸው ታውቋል።   

 

Ø ከጥቂት ሳምንታት በፊት በቡርኪና ፋሶ ተሞክሮ የከሸፈውን መንፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል ዲየንዴሪ በወታደራዊ ፍርድ ቤት  በ 11 የወንጀል ክሶች መከሰሳቸው በትናንትናው ዕለት የወታደራዊ ፍርድ ቤት ቃል አቀባይ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል። ከክሶቹ መካከል በሰው ልጆች ላይ ወንጀል መፈጸም የሚለው አንዱ ሲሆን ሌሎች  23 የሚሆኑ ሰዎች አብረው የተከሰሱ መሆናቸው ተነግሯል። ከጄኔራሉ ጋር ከተከሰሱት 23 ሰዎች መካከል  ለታቀደው አጠቃላይ የምክር ቤት  ምርጫ ራሳቸውን በእጩነት አቅርበው የተከለኩት የጄኔራሉ ሚስት አንደኛዋ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግም የምርጥ ቡድኑ ከፍተኛ መኮንኖችና የቀድሞ መንግስት ባለስልጣኖች መሆናቸው ታውቋል።  የቀድሞው ፕሬዚዳንት ባለሟሎች በምርጫ ውስጥ እንዳይገቡ መከልካላቸውን ምክንያት በማድረግ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ የሚባለው ምርት ቡድን አባላት በአካሄዱት መፈንቅለ መንግስት ምክንያት በተከሰተው የስድስት ቀናት አለመረጋጋትና የመንገድ ላይ ግጭት 14 ሰዎች መገደላቸውና ከ251 በላይ የሆኑ  መሞታቸው ይታወቃል። የእነ ጄኔራል ዲየንዴሬ የክስ ሂደት የቀድሞውን ፕሬዚዳንት የሳንካራን ገዳዮች አጋልጦ ወደ ፍርድ ሊያመጣ ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቷል።  የክሱና የምርመራ ሁኔታ እየቀጠለ ከሄደ ከዛሬ 28  አመት በፊት በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነት የነበራቸውን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት  ሳንካራን አስገድለዋል ተብለው የሚጠረጥሩት የቀድሞ ፕሬዚዳንት ካምፕወሬ ለፍርድ ሊቀርቡ ይችላሉ በማለት የወታደራዊ ፍርድ ቤት ቃል አቀባይ ለጋዘጠኞች ተናግረዋል። የሳንካራ አስከሬን ተመርምሮ በበርካታ ጥይቶች ተመተው እንደሞቱ ተረጋግጧል ተብሏል።

 

Ø በማዕካለዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ዋና ከተማ በባንጉዊ ውስጥ በትናንትናው ዕለት በእስልምናና በክርስቲያን ተከታዮች መካከል እንደ አዲስ በማገርሸት በተፈጠረው ግጭት  አንድ ሰው ሲሞት ሌሎች 10 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን የሆስፒታል እና የወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል። ግጭቱ የተጀመረው ሐሙስ ማታ አንድ የእስልምና ተከተይ የሆነ ወጣት ጸረ ባላካ በተባሉ የክርስቲያን ሚሊሺያዎች በመገደሉ ሲሆን በሁለቱ ወገኖች መካከል ግጭቱ ተባብሶ ሌላ አንድ ሰው ሲገደል 10 ሰዎች መቁሰላችው ተነግሯል። አንዳንድ ነዋሪዎች የሞቱትን ሰዎች ቁጥር ወደ ሶስት ከፍ ያደርጉታል።  አርብ ጠዋት ሁኔታው መረጋጋት የታየበት ሲሆን ቀደም ብሎ ቤታቸውን ጥለው ሄደው የነበሩ ነዋሪዎች ወደ ቤታቸው  ሲመለሱ ታይተዋል።   የዛሬ ሁለት ዓመት የአገሪቱ መሪና የክርስትና እምነት ተከታይ የነበሩት ፍራንስዋ ቦዚዝ “ሰለካ” የሚል ስም በያዙት  የእስልምና ተከታይ አማጽያን ከተገለበጡ በኋላ በሁለቱ እምነቶች ተክታዮች መካከል የተፈጠረው ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወትን ያጠፋ መሆኑና ወደ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብን ያሰደደ መሆኑ ይታወቃል። ለነገ ለመስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው አገራዊ ምርጫ ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ይታወሳል።

 

 

 

 

 

ጥቅምት 5   ቀን 2008 ዓ.ም

 

Ø ዛሬ አርብ በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በምትገኘው ማይዱጉሪ በምትባለው ከተማ ዕድሜያቸው ከ11 እስከ 15 የሚገመቱ ሴቶች ልጆች አጥፍቶ ጠፊዎች በመሆን ባፈንዷቸው ቦምቦች 39 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና በርካት ያሉት ደግሞ የቆሰሉ መሆናቸው ከአካባቢው ከተገኘው ዜና ማወቅ ተችሏል። በትናንትናው ዕለትም በዚሁ ከተማ በሚገኝ አንድ መስጊድ ውስጥ በፈነዱ ቦምቦች ከ32 ሰዎች በላይ የሞቱ መሆናቸው ታውቋል። ቦምቦቹን ማን አንዳፈነዳቸው ኃይላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም ቦኮ ሃራም የሚባለው አሸባሪ ድርጅት መሆኑ ተገምቷል። ባልፉት ጥቂት ቀናት ብቻ በዚሁ ከተማ ውስጥ በደረሱ የቦምብ ጥቃቶች ከ100 ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል።

 

Ø የኬኒያ የታችኛው የሕግ አውጭ ምክር ቤት  በቅርቡ ህግ ሆኖ እንዲወጣ የወሰነው የሕግ ረቂቂ  በምክር ቤት አባል ላይ የስም ማጥፋት ተግባር ያካሄደ ማንኛው የሚዲያ ተቋም  እስከ 500 ሺ የኬኒያ ሽልንግ ወይም እስከ 4850 ዶላር ድረስ መቀጫ እንዲከፍል የሚደነግግ መሆኑ ተገለጸ። የታችኛው ምክር ቤት ምንም እንኳ በዚህ የህግ ረቂቅ ላይ ውሳኔውን ቢሰጥም የአገሪቱ ህግ ሆኖ የሚወጣው ሴኔት የተባለው የላይኛው የሕግ አውጭ ምክር ቤት ሲስማማበትና ፕሬዚዳን ኡሁሩ ኬኒያታ ሲፈርሙበት ነው።  ከሶስት ዓምት በፊትም ተመሳሳይ የሕግ ረቂቆች ቀርበው የላይኛው የምክር ቤት አካል ባለመስማማቱ ሕግ ሳይሆን መቅረቱ ይታወሳል። የሕግ አውጭዎቹ ሕጉን ለማውጣት ያስገደዳቸው በምክር ቤት አባላት ላይ በየጊዜው መሰረት የሌለው ክስ በመገናኚያ ብዙሀን በመጻፉ ነው ይላሉ።   የተለያዩ  የኬኒያ ጋዜጦች እና የመገኚያ ብዙሃን ተቋሞች በረቂቅ ሕጉ ላይ ያላቸውን ቅሬታ በከፍተኛ ስሜት የገለጹ ሲሆን በርካታ ጋዜጦች የሕግ ረቂቁን ኮንነውታል፡፤ ዘ ዴይሊ ኔሽን የተባለው ጋዜጣ “ከእንግዲህ ወዲያ የፓርላማ አባላትን የማያስደስቱና በጋዜጣ  የሚወጡ ጽሁፎች ሁሉ ወንጀል ሊሆን ነው” ያለ ሲሆን ስታንዳርድ የተባለው ጋዜጣ ደግሞ “ረቂቅ ህጉ የምክር ቤቱ አባላት ለመገኚያ ብዙሀን ያላቸውን ጥላቻ የገለጹበት ከመሆኑ ባሻገር የተዘፈቁበት ሙስና እንዳይጋለጥ ለመከላከል ያደረጉት  ጦርነት  ነው”  ብሎ ይህ ለኬኒያ ትልቅ የሀዘን ቀን ነው ብሏል። ጋዜጠው አስተያየቱን በመቀጠል የምክር ቤት አባላት የሚዘርፉት የመንግስት ገንዘብ፤ የሚያስቀምጧቸው ቅምጦች እና በተቃዋሚዎቻቸው ላይ የሚያደርሱት በደል እንዳይጋለጥ ያቀዱት ተንኮል መሆኑን ገልጾ የመገኛያ ብዙሃን ነጻነት የማገረሰስ መብት እንጅ ከመንግስት የተሰጠ ችሮታ አይደለም ብሏል። ትራስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም ከዚህ በፊት ባወጣው ዘገባ መሰረት ኬኒያ በዓለም ካሉ 174 አገሮች ውስጥ 145ኛ በመሆን የተመደበች ሲሆን ባለስልጣኖችን በሙስና ሲከሰሱ ቆይተዋል። በኬኒያ ሕዝቡ ለመንግስት ባለስልጣናት ጥሩ አመለካከት የሌለው ሲሆን የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ በኬኒያ የመንግስት ሰራተኛ መሆን የግል ሀብትን ለማካባት ዋናው መንገድ ነው ተብሎ ይታመናል። የኬኒያ ዋናው ኦዲተር በቅርቡ ባደረገው ምርመራ ከመንግስት ድርጅቶች መካከል  ገቢና እና ወጫቸውን በተገቢው የሂሳብ አያያዝ መንገድ የያዙ አንድ  ከመቶ ብቻ መሆናቸውን ገልጾ ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል።

 

Ø የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ባለፈው ማክሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ አንድ የዓለም አቀፍ ስደተኛ ድርጅት ባልደረባን ጨምሮ ዘጠኝ ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ድርጊቱን ኮንነው የብሩንዲ ባለስልጣኖች ጠልቅ ያለ ምርመራ አካሄደው ባስቸኳይ ጥፋተኞችን ለፍርድ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል። በግጭቱ  ሁለት ፖሊሶች የተገደሉ ሲሆን ከሟቾቹ መካከል አንድ የብሩንዲ ጋዘጠኛ እንዲሁም ሚስቱና ሁለት ልጆቹ የሚገኙበት መሆኑ ታውቋል።  የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ለምርጫ እቀርባለሁ ካሉበት ጊዜ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረው አመጽና አለመረጋጋት የበርካታ ሰዎችን ህይወት ያጠፋ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በየቀኑ ሰዎች እየተገደሉ መሆናቸው ተዘግቧል። ባለፈው ነሐሴ ወር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የብሩንዲ መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ባስቸኳይ እንዲነጋገር ውሳኔ መስጠቱና ዋና ጸሐፊው ወደ ብሩንዲ መልእክተኛ እንዲልኩ መመሪያ መስጠቱ ይታወሳል። በብሩንዲ መንግስት እምቢተኛነት ምክንያት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወደ አገሩ ልዕክ ለመላክ አለመቻሉም ታውቋል።

 

Ø በጂቡቲ የመንግስቱ ተቃዋሚ የሆነው ፍሩድ የሚባለው ድርጅት አባል እና ደጋፊ ናቸው ተብለው የሚጠረጥሩና እንዲሁም የድርጅቱ መሪዎች ዘመዶች የሆኑ ግለስቦች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እየተያዙ መሆናቸውን በመግለጽ  ኦ አር ዲ ኤች ዲ (ORDHD)  በሚል ምህጻረ ቃል የሚጠራው የጁቡቲ የሰብአዊ መብት ድርጅት  ገለጸ። የሰብዓዊ  መብት ድርጅቱ የጂቡቱ የጸጥታ ኃሎች ከመስከረም 23 ቀ 2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች ያሰሯቸውን የፍሩድን አባላትና ደጋፊዎች እና የባለስልጣኖችን ዘመዶች ስም በዝርዝር አውጥቶ ያጋለጠ ሲሆን የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ፍሩድ የተባለው የአማጽያን ኃይል በሚያደርገው ወታደራዊ ጥቃት ከመደናገጥ የመጣ ሳይሆን አይቀርም ብሏል። 

 

 

 

     

ጥቅምት 4   ቀን 2008 ዓ.ም

 

         

Ø የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያ ለማድረግ ወደ ቦትስዋና ሄደው ከነበሩ የኤርትራ የእግር ኳስ ተጨዋጮች መካከል 10 የሚሆኑት ቦትስዋና ውስጥ ቀርተው የፖሊቲካ ጥገኝነት የጠየቁ መሆናቸውን የቦትስዋና ባለስልጣኖች በዛሬው ዕለት ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። ተጨዋጮቹ ወደ ማረፊያ ሆቴላቸው ከመሄድ ፈንታ በገበያ ውስጥ የቀይ መስቀል መስሪያ ቤትን በመፈለግ ላይ ሳሉ በፖሊሶች ተይዘው  የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።  በቦትስዋና የሚገኘው የሻዕቢያ አምባሳደር ሰዎቹn ለመረከብ ጥረት ቢያደርግም ተጨዋቾቹ የፖሊቲካ ጥገኝነት ስለጠየቁ ያልተሳካለት መሆኑ ተገልጿል። የኤርትራ የእግር ኳስ ተጨዋጮች የሻዕቢያው አገዛዝ የሚያካሄደውን አፈናና ጭቆና በመሸሽ   በጊዜው በተለያዩ አገሮች የቀሩ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን የዛሬ ሶስት ዓመት በኡጋንዳ ቀርተው የፖሊቲካ ጥገኛነት ያገኙት  15 ተጨዋጮችና አንድ ዶክተር ከብዙዎቹ መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። በቅርቡ አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጥኝ ኮሚሽን ባወጣው ዘገባ የሻዕቢያ አገዛዝ የሚያካሄደውን የሰብአዊ መብት ረገጣ  ሰቆቃዊ ድርጊቲ ያጋለጠ ሲሆን የኤርትራ ወጣቶች  የጊዜ ወሰን በሌለው ወታደራዊ አገልጎት አለፍላጎታቸው በግዳጅ እንደተሰማሩ ገልጿል። የስፖርተኞች ወሬ ከተነሳ የወያኔን አስከፊ አገዛዝም በመሸሽ ባለፍቱ ዓመታት በተለያዩ አገሮች የፖሊቲካ ጥገኝነት በመጠየቀ በተለያዩ አገሮች  የቀሩት ኢትዮጵያውያን አትሌቶችና የእግር ኳስ ተጭዋቾች  ከፍተኛ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ የነበሩት የቤኒን የቀድሞ ፕሬዚዳንት በትናንትናው ዕለት ያረፉ መሆናቸው ተገለጸ። የዴሞክራሲ አባት ተብለው የሚጠሩት የቤኒን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሚስተር ማቲው ኬሬኩ በተወለዱ  በ82 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሚስተር ኬሬኩ ወደ ስልጣን የመጡት እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1972 ዓም በተደረገ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ሲሆን  ራሱን የግራ ርዕዮተ ዓለም አራማጅ በማለት የሚጠራው ብቸኛ ፓርቲ መሪ በመሆን ለ20  ዓመታት በስልጣን ላይ ቆይተዋል።  እአአ በ1991 ዓም. የብዙሃን ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በመቀበል ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ በመፍቀዳቸው  በወቅቱ በተካሄደው ምርጫ ከስልጣን የወረዱ መሆናቸው ይታወቃል። እአአ በ1996 ዓም እና በ2001 በተካሄዱ አገራዊ ምርጫዎች በተከታታይ አሸናፊ በመሆን አገሪቱን የመሩ መሆናቸው ይታወሳል።

 

Ø ቦኮ ሃራም ላይ የሚካሄደውን ጥቃት ለማጠናከር የአሜሪካ ወታደሮች የተሰማሩ መሆናቸውን ፕሬዚዳንት ባራክ  ኦባማ ገለጹ።  የእየር ላይ የስለላ ተግባራትን እንዲሁም ወታደራዊ አሰሳንና ቅኝትን ለማካሄድ  300 የሚሆኑ የአሜሪካ ወታደሮች ወደ ካሜሩን መላካቸው የተነገረ ሲሆን ለግዳጅ እስከሚፈለጉበት ድረስ በዚያው እንደሚቆዩ ተገልጿል። ወታደሮቹ ለራሳቸው መጠበቂያ የሚሆን የተሟላ ወታደራዊ ቁሳቁሶች የተመደበላቸው ሲሆን ከሶስት መቶ ወታደሮች ውስጥ ዘጠናዎቹ ባለፈው ሰኞ ወደ ቦታው በቅድሚያ የተላኩ መሆናቸው ተነግሯል።

 

Ø የኢቦላ በሽታ ተዋስያን በወንድ አባለ ዘር ውስጥ ለዘጠኝ ወራት ያህል ሊቆይ እንደሚችል ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገ ጥናት የታወቀ መሆኑን ኒው ኢንግላንድ ጆርናል ኦፍ ሜዲስን የሚባለው መጽሐት በአምዱ ላይ አስፍሮ አውጥቶታል። በዚህ የመጀመሪያ ጥናት የተደረሰበት ግኝት ከ11 ሺ በላይ የሆኑ ዜጎቻቸው በኢቦላ በሽታ ለተገደለባቸው የምዕራብ አፍሪካ አገሮች በጣም አሳሳቢ የሆነ የጤና ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል። ከዚህ በፊት አንድ በኢቦላ በሽታ የተለከፈ በሽተኛ በህክምና ርዳታ ተድርጎለት እስከ 82 ቀን ከቆየ ከኢቦላ ነጻ ይሆናል የሚል አመለካከት ነበር። በሽታው ከዚያን ጊዜ በላይ የሚቆይ ከሆነ አስጊነቱ እየጨመረ ከመሄዱም በላይ ክትትሉ በርካታ የሰው ኃይልና የገንዘብ ወጭን ይጥይቃል የሚል ግምት ተወስዷል።   

 

Ø በትናትናው ዕለት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የደቡብ አፍሪካ ዜጎች በጆሃንስበር ከተማ ዋና ዋና መንገዶች የተቃውሞ ስልፎች አድርገዋል። በደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የብረታብረት ሰራተኞች አንድነት ማህበር የተመራው ይህ ግዙፍ የተቃውሞ ስልፍ በአገሪቱ ተስፋፍቶ የሚገኘው ዓይን ያወጣ የባልስልጣኖች ሙስና በመቃወም የተደረገ ነበር። በተቃውሞ ስልፈኞቹ ተይዘው ከነበሩት መፈክሮች  መካከል“ ሙስና ይወገድ” “የዙማ መንግስት ይወገድ”   “ ሙስና ደሃውን እየቀረጠ ነው፤ እኛ ሀብታሞች ቀረጥ ይክፈሉ እንላለን”  የሚሉ እንደነበሩበት ለማወቅ ተችሏል። 13 ሚሊዪን የሚሆነው ሕዝብ በየቀኑ የሚባለው አጥቶ ወደ መኝታ በሚሄድበት  እና 50 ከመቶ የሚሆነው ሰራተኛ ከድህነት መስመር በታች በሆነ ገቢ በስቃይ በሚኖርበት ሁኔታ ጥቂት ባለስልጣኖች ዓይን ባወጣ መንገድ ተንደላቀው ይኖራሉ በማለት ስልፉን ካስተባበሩት መካከል አንደኛው ተናግረዋል። ከፍተኛ ዋጋ ያለው የፕሬዚዳንት ዙማ የግል መኖሪያ ቤት ለባለስልጣኖች በሙስና መዘፈቅ እንደምሳሌ የተጠቀሰ ሲሆን ለመኖሪያ ቤቱ  የጸጥታ መሳሪያዎችን ለማስገባት ብቻ 24 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መከፈሉ አይን ያወጣ የሙስና ተግባር ነው ተብሏል። ከተሰላፊዎቹ መካከል አንዳንዶቹ በአገሪቱ የሙስናና ባህል ያመጡት ፕሬዚዳንት ዙማ እንደሆኑ ጠቅሰው “እኛን ድሆችን ነጻ ያወጣል ብለን ያልነው ሰው ጩልሌ መንታፊ ሆነ” ብለው ከሰዋቸዋል። ከ1986 ዓም ጀምሮ በስልጣን ላይ ያለው ዙማ የሚመሩት የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ በሙስና በመተብተቡ በሚቀጥለው ምርጫ ላያሸንፍ ይችላል የሚሉ በርካታ ናቸው።

በተያያዘ ዜና ረቡዕ ምሽት ላይ የጆሃንዝበርግንና የፕሪቶሪያን ከተሞች በሚያገናኘው አውራ ጎዳና ላይ ተሰርቶ የነበረ አንድ ጊዜያዊ ድልድይ ወድቆ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ከሃያ በላይ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ከተጎዱት መካከል ቢያንስ አምስቱ በጸና የቆሰሉ በመሆናቸው የማቾቹ ቁጥር ሊያድግ ይችላል የሚል ስጋት አለ። ድልድዩ ሊወድቅ የቻለበት ምክንያት ምን እንደሆን እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም::    

  

 

  ጥቅምት 3   ቀን 2008 ዓ.ም

              

Ø በማላዊ እስር ቤት ታግተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ስደተኞች በከፍተኛ ስቃይ የሚኖሩ መሆናቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና ምንጭ ገለጸ። ጋዜጣው የእስር ቤት ኃላፊዎችን ስደተኞችንና እንዲሁም ወሰን የለሽ ዶክተሮች የሚባለውን የእርዳታ ሰጭ ተቋም አነጋግሮ ባወጣው ሰፊ ዘገባ ስደተኞቹ በተጨናነቀ ሁኔታ የታሰሩ መሆናቸውን፤ በቂ የሆነ የመጸዳጃ አገልግሎት እንደሌላቸውና በእስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያለ መሆኑም ጠቅሷል። ጋዜጣው ከእስር ቤት ኃልፊዎችና ከወሰን የለሽ ተቋሙ ባገኘው መረጃ መሰረት ለ100 ሰው ተብሎ በተሰራ ክፍል ውስጥ 380 እስረኞች ታጭቀው የሚገኙበት ለ800 እስረኞች ይበቃል ተብሎ  በተሰራ እስር ቤት ውስጥ ደግሞ 2650 እስረኞች ታጭቀው የሚኖሩበት መሆኑን አጋልጠዋል። ዘጠኝ መቶ እስረኞች የሚገለገሉት በአንድ የውሃ ቧንቧ ሲሆን አንድ መጸዳጂ 120 እስረኞች ይጠቀሙባቸዋል በማለት የእስር ቤቱን አሳዛኝ ሁኔታ ዘርዝሮ ገልጿል። ባሁኑ ወቅት ከ317 ኢትዮጵያን ስደተኞች በማላዊ እስር ቤት ውስጥ ታግተው ያሉ ሲሆን የታሰሩትም ምክንያትም ኑሯቸንን እናሻሽላለን በማለት ለስራ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ በህገ ወጥ መንገድ አገር ውስጥ ገብታችኋል ተብለው ነው። የዜና ምንጩ ያነጋገራቸው በርካታ ኢትዮጵያውን ከአገራቸው የወጡት መኖር የማይችሉበት ችግር ውስጥ በመግባታቸው መሆኑ የገለጹለት ሲሆን ማላዊ ውስጥ በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ መታሰራቸው ደግሞ ከስቃይ ወደስቃይ እንደሆነባቸው ተናግረዋል። አንዱ ኢትዮጵያዊ ለጋዜጣው በሰጠው ቃል ይጓዝ የነበረው ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደነበር ገልጾ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አንድ ዓመት ቢሰራ ኑሮውን ለማሻሻል የሚችል ከመሆኑ ባሻገር ቤት ለመስራት የሚችል አቅም ሊኖረው እንደሚችል ገልጾ  መሆኑን ገልጾ  ኢትዮጵያ ውስጥ ቀንቶት ስራ ያገኘ ሰው 20 ዓመትም ሆነ ከዚያ በላይ ቢሰራ እንኳን ቤት ለመስራት ለኑሮው ጠብ የሚል ገቢ የማያገኝ መሆኑን አስረድቷል። አብዛኞች እስረኞች የታሰሩት ባለፈው ዓመት ሰኔ ላይ ሲሆን የተጣለባቸውን የገንዘብ በመክፈልም ሆነ የተፈረደባችውን የእስራት ጊዜ ቢያጠናቅቁም ከእስር ሳይወጡ የስቃዩን ኑሮ እንዲኖሩ የተገደዱ መሆናችውን ገልጸዋል። የማላዊ ባለስልጣኖች እስረኞቹን ለማጓጓዝ በቂ ገንዘብ ባለመኖሩ እስረኞቹ በእስር ቤት አጉረው ለማቆየት የተገደዱ መሆናቸውን ይናገራሉ። ኢትዮጵያውያን በእንዲህ ዓይነት የስቃይ ኑሮ ውስጥ መውደቃቸው አሳዝዛኝና የሚወገዝ ተግባር ሲሆን አስፈላጊው ጥረት ተደርጎ ነጻነታቸው ማግኘት የሚችሉበትን ሁኔታ መፍጠር ያስፈላጋል ተብሏል።  በርካታ ኢትዮጵያን የወያኔ አስከፊ አገዛዝ እየሸሹ ከአገራችው መውጣት መቀጠላቸው የወያኔ ጥምር አሃዝ እድገት ምን ያህል ባዶ መሆኑን ያሳያል ሲሉ በጉዳዩ ላይ እውቀት ያላቸው ዜጎች ይተቻሉ።  

 

Ø በብሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ ውስጥ አንድ የመንግስት ቴሌቪዥን የካሜራ አንሽ የሆነ ሰውና ቤተሰቦቹ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች የተገደሉ መሆኑን የዜና ምንጮች ገለጹ። ሰዎቹ የተገደሉት በተጻራሪ ኃይሎች ታግቷል የተባለው አንድ ሌላ ሰው ለማስፈታት ባካሄዱት የአሰሳ ተኩስ ሲሆን  በጠቃላላው አስር ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። በከተማዋ  የመሳሪያና የፈንጅ ድምጽ ሌሊቱን በሙሉ ሲሰማ ያደረ ሲሆን ያደረሰው ጉዳት ግን እስካሁን አልታወቀም። ባለፈው ሚያዚያ ወር ጀመሮ በብሩንዲ የፖሊቲካ አለመረጋጋት ቀጥሎ በተቃዋሚዎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል በተካሄዱ ግጭቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸው ታውቋል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት የብሩንዲ የጸጥታ ዋና ሹም ከግድያ ማምለጣቸውም ይታወሳል።

 

Ø በመስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም  በናይጀሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ አጠገብ በሚገኙ ሁለት ቦታዎች ቦምቦች ፈንድተው ጉዳት ማድረሳቸው የሚታወስ ሲሆን  እነዚህን የቦምብ ጥቃቶች በማቀድና ተግባራዊ በማድረግ በኩል አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን  ሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማድረጉን  አስታውቋል። ኩጄ እና ኒያና በሚባሉ ሁለት ከዋና ከተማዋ ቅርብ በሆኑ ከተሞች ውስጥ በፈነዱት ቦምቦች 18 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል። ፖሊስ በመግለጫው ላይ አክሎ እንዳሳወቀው ሌሎች  የቦምቦ ጥቃቶችን ለማድረስ ሲያቅዱ የነበሩ ሰዎች የተያዙ መሆናቸውን ገልጾ 12 በቤት ውስጥ የተሰሩ ቦምቦችና 28 የኢሌክትሮኒክ ማቀጣጠያ መሳሪያዎች አብረው የተያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተጥርጣሪውቹን ፍርድ ቤት እንዲሚያቀርብ ፖሊስ ጨምሮ አስታውቋል።

በተያያዘ ዜና በትናንትናው ምሽት በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በምትገኘው ማይዱጉሪ በምትባለዋ ከተማ ሶስት አጥፍቶ ጠፊዎች በነዋሪዎች መንደር ውስጥ ባፈነዷቸው ቦምቦች ሰባት ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ተገልጿል። ሶስቱም ቦምቦች የፈነዱት በየሶስት ደቂቃ ልዩነት ሲሆን ሶስቱም አጥፍቶ ጠፊዎች አብረው መሞታቸውና ሌሎች 11 ሰዎች በፈንጅዎች ፍንጣሪ መጎዳታችው ተዘግቧል። ባለፉት አራት ሳምንት ብቻ በከተማዋ ከ100 በላይ ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ሲታወቅ የትናንቱም ጥቃት የተካሄደው በቦካሃራም መሆኑ ይጠረጣል። 

 

Ø ማክሰኞ ዕለት በሰሜን ማሊ በቲምበክቱ አካባቢ የሮኬት አምጣቂ መሳሪያዎችን የታጠቁ አማጽያን በወታደሮች ታጅቦ በሚንቀሳቀስ ኮንቮይ ላይ ባካሄዱት ጥቃት ስድስት ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸውንና  ሌሎች ሁለት ሰላማዊ ሰዎችና አንድ ወታደር ማቁሰላቸውን የማሊ መንግስት ቃል አቀባይ ገለጸ። እስካሁን ጥቃቱን መፈጸሙን አምኖ ኃላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም መንግስት ሽብረተኞች የሚላቸው እስላማውያን አማጽያን ሳይሆኑ ናቸው የሚል ጥርጣሪ እንዳለው ተናግሯል። በማሊ ያለው የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ኃይል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከስድስት በላይ ሊሆን እንደሚችል ገምቷል ።  ከሶስት ዓመት በፊት ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለው እስላማዊ ቡድን የሰሜን ማሊን ግዛት  ቁጥጥር ስር ማድረጉና  በኋላም በፈረንሳይ ወታድሮች ጥቃት  ደርሶበት አካባቢውን ለቅቆ መውጣቱ ይታወሳል። ባለፈው ሰኔ በማሊ መንግስትና ቱዋረግ በሚባሉ አማጽያን መካከል የሰላም ስምምነት ቢፈረምም አሁንም ቢሆን ሰፋ ያሉ ግዛቶች ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ መሆናቸው ይታወቃል።

 

 

 

 

 

 

 

       ጥቅምት 2   ቀን 2008 ዓ.ም                 

 

         

Ø በጊኒ የተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ውጤት በይፋ ከመነገሩ በፊት በምርጫው የተሳተፉት አብዛኞቹ የገዥው ፓርቲ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ አለመሆኑን በመጥቀስ አዲስ ምርጫ እንዲካሄድ በትናንትናው ዕለት ጠይቀዋል። እሁድ ዕለት በተካሄድው ምርጫ ላይ ምንም ዓይነት ግጭት ያልታየ ሲሆን የመራጩ ሕዝብ ቁጥርም በርካታ ነው ተብሏል። ከተቃዋሚዎች ውስጥ በግምባር ቀደምትነት የተሰለፈው ፓርቲ መሪ ሴሉ ዳለየን ዲያሎ ሌሎች ስድስት የተቃዋሚ መሪዎች በተገኙበት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተደረገ የተባለው ምርጫ ማጭበርበር የሞላበት በመሆኑ እንዲሰረዝና ሌላ አዲስ ምርጫ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል። ምርጫው ነጻና ፍትሀዊ አለመሆኑን ከሰጡት ምክንያቶች አንዳንዶቹ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግይተው መከፈታቸው፣ በርካታ መራጮች ያለመታወቂያ እንዲመርጡ መደረጋቸው ፣ በመዝገብ ላይ ስማቸው የሌለ ሰዎች እንዲመርጡ የተፈቀደላቸው መሆኑ እና ሌሎችም ናቸው። ሚስተር ዲያሎ ምርጫው ሲካሄድ ከፍተኛ ማጭበርበር ተደርጓል ካሉ በኋላ ደጋፊዎቻቸው ተከታታይ ሰልፎች ያደርጋሉ የሚል መልእክት አስተላልፈዋል። የገዥው ፓርቲ ቃል አቀባይ በበኩላቸው ምርጫውን አስመልክቶ ተቃውሚዎች የሰነዘሩት  ክስ አስገራሚና አስቂኝ ነው ካሉ በኋላ ህዝቡ በትዕግስት ውጤቱን እንዲጠብቁ ጠይቀዋል።  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባንኪ ሙን ምርጫው አለምንም ግጭት መካሄዱ ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸው በሁሉም በኩል ትዕግስት እንዲኖር ተማጽነዋል። ሌሎቹ ስድስት የተቃዋሚ መሪዎች እንደ ሚስተር ዲያሎ ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ አይደለም ቢሉም ደጋፊዎቻቸው ተቃውሞ እንዲያሰማ አልጠየቁም። እንዲያውም ከእነሱ ውስጥ አንደኛዋ የተቃዋሚ ድርጅት መሪ እንደገዥው ፓርቲ ሕዝቡ መረጋጋት ያለበት መሆኑን በመግለጽ ጥሪ አድርገዋል። የድምጽ ቆጠራው ከተጠናቀቀ የምርጫው ውጤት  ማክሰኞ ዕለት ይገለጣል የተባለ ሲሆን በሕዝቡ በኩል ያለው ተቀባይነት ምን ሊሆን እንድሚችል ወደፊት ሊታይ ይችላል ተብሏል።

 

Ø በተባበሩት መንግስታት የሴቶች ተቋም ተዘጋጀቶ ትናንት ሰኞ ይፋ የተደረገው ባለ400 ገጽ ዘገባ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በየቦታው የፈጸሟቸውን ወንጀሎች አይቶ ብይን ሊሰጥ የሚችል አንድ ዓለም አቀፍ ትሪቡናል እንዲቋቋም ጠየቀ። ይህ ጥሪ የተደረገው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች በተለይም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ህጻናትን አስገድዶ መድፈር የሚለውን ጨምሮ የተለያዩ ወንጀሎች በዜጎች ላይ ፈጽመዋል የሚሉ  ክሶች ከተሰሙ በኋላ ነው። ዘገባው የተዘጋጀው በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶችን እኩልነት ለማስጠበቅና ሰብእናቸው ለማስከበር በሚንቀሳቀሰው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ጉዳይ ተቋም ሲሆን ዘገባው የቀረበውም የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ሰለሴቶች ጉዳይ ያስተላለፈው ታሪካው ውሳኔ 15ኛው ዓመት በተከበረበት ወቅት ነው። ዘገባውን ያዘጋጁት ክፍሎች በሰጡት መግለጫ አሁን ባለው አሰራርና ህግ መሰረት ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ወታደሮች ጉድያቸው የሚታየው በየአገሮቻቸው ሕግና ደንብ መሰረት በመሆኑና እያንዳንዱ አገርም የራሱን ወታደር ለፍርድ የማቅረብ ፍላጎት የሌለው በመሆኑ  አንዲሁም በተጨማሪ አንዳንድ አገሮች ፍላጎቱ እንኳ ቢኖራቸው የተሟላ የፍርድ ተቋም የሌላቸው በመሆኑ ለሚፈጸሙት ወንጀሎች ፍትህን ለማስገኘት  የተሟላ ዓለም አቀፍ የፍርድ ተቋም ያስፈልጋል ብለዋል። ዘገባው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ መጨመር ያለበት መሆኑን ጠቁሟል። በዛሬው ዕለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ስለሴቶች ሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ይመክራል ተብሏል።

 

Ø ወደ ሰባ የሚደርሱ የሱዳን ዜጎች ራሱን እስላማዊ መንግስት የተባለውን አሸባሪ ቡድን የተቀላቀሉ መሆናቸውን የአገሪቱ የአገር ውስጥ ሚኒስቴር በትናትናው ዕለት ገለጹ። አሸባሪውን ቡድን ከተቀላቀሉት መካከል የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚገኙባችው ሲሆን አንዳንዶቹም የአሜሪካ የካናዳና የእንግሊዝ ፓርስፖርቶች የያዙ መሆናቸው ታውቋል። ሚኒስትሩ ከሌልች አገሮች ጋር ሲወዳደር ከሱዳን አሸባሪውን ቡድን ለመቀላቀል ከሱዳን የሄዱት አነስተኛ መሆናቸውን ገልጸው ከቱርክ መንግስት ጋር በተደረገ ትብብር በርካታ የሱዳን ወጣቶች ወደዚያ መሄዳቸውን ለማገድ ተችሏል ብለዋል። የሱዳን መንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና የትምህርት ተቋሞች   ወጣቶቹ ወደዚያ እንዳይሄዱ ለማድረግ አስፈላጊውን የቅስቀሳና የትምህርት ስራ እየሰሩ መሆናቸውንም ከመናገራቸውም በላይ ወደ ተወሰኑ አገሮች ለመውጣት በወጭ ቪዛ ላይ መንግስታቸው ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ በካርቱም ዩኒቨርስቲ ይማሩ የነብሩ 12 የህክምናና የቴክኖሎጂ ተማሪዎች ከከርቱም ተነስተው በቱርክ በኩል አይስስን የተቀላቀሉ መሆናቸውና በሌላ ጊዜ ደግሞ ሌሎች 9 የእንግሊዝ ፓርስፖርት የያይዙ ወጣቶች ከካርቱም ተነስተው በተመሳሳይ መንገድ ወደ ሲሪያ መሄዳቸው ይታወሳል።

 

Ø ከመስከረም 20 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ በየሩሳሌም በእስላራዕሎችና በፍልስጥዔሞች መክካል የተጀመረው ግጭት የብዙ ሰዎችን ህይወት ያጠፋ ከመሆኑ በላይ ችግሩ እየተባበሰ የሄደ መሆኑ ተገለጸ። በዛሬው ዕለት በተለያዩ ቦታዎች የተደረጉ ጥቃቶች ሶስት እስራዕሎች የተገደሉ መሆናቸውና ሌሎች የቆሰሉ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን አንድ የፍልስጥዔም ዜጋ መሞቱና ሌሎች በርካታ መቁሰላቸው ተገልጿል። ችግሩ የተነሳው ለእስልምና እምነት ተከታዮች ከመካ እና ከመዲና ቀጥሎ ሶስተኛ ታላቁ ክቡር ቦታ በሚባለውና በእየሩሳሌም ውስጥ ጉልህ ቦታ ላይ በሚገኘው በታዋቂው የአል አክሳ መስጊድ ውስጥ የአይሁድ እምነት ተከታዮች እየገቡ ጸሎት ማድረጋቸው የፍልስጥኤም  ተወላጆችን በማስቆጣቱ ነው። ከመስከረም 20 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ በተካሄዱ ግጭቶች  ሰባት እስራዕላውያን ሲሞቱ ከ28 በላይ የሆኑ ፍልስጥኤሞች ህይወታቸውን  ከ1900 በላይ  እንደቆሰሉ ጉዳዩን በቅርበት የተከታተሉ ወገኖች  ይገልጻሉ።  በዛሬው ቀን የፓለስቲንያን ድርጅቶች በምዕራብ ዳርቻ በጋዛና በምስራቃዊ እየሩሳሌም የሚኖሩ የፓለስታይን ዜጎች የአንድ ቀን  የተቃውሞ ቀን እንዲከበር ጥሪ  አድርገዋል። ሁኔታው እየተባባሰ ከሄደ ከፍተኛ ደም መፋሰስን ሊያስከትል የሚችል ሶስተኛው ጠቅላላ አመጽ ( ሶስተኛው እንቲፋዳህ) ሊከሰት እንደሚችል ብዙዎች ይተነብያሉ።

    

ጥቅምት 1   ቀን 2008 ዓ.ም 

 

Ø ቅዳሜ በቱርክ ዋና ከተማ በአንክራ ለበርካታ ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆኑትን ሁለት ቦምቦች ያፈነዳቸው ራሱን የእስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው አይ ኤስ የተባለው ቡድን ነው ሲሉ የቱሪክ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ። ቦሞቦቹን በማፈንዳት በኩል እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ ባይኖርም መንግስታቸው ድርጊቱ የተፈጸመው በዚህ ቡድን ለመሆኑ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንደሌላቸው ገልጸዋል። በቦምቦቹ ፍንዳታዎች የሞቱት ሰዎች በአንዳንድ ክፍሎች 128 ነው እየተባለ ቢጠቀስም  በመንግስት በኩል እስካሁን ድረስ  የተሰጠው አሀዝ 98 መሆኑ ታውቋል።  የአብዛኞቹ የቀብር ሥነ ስርዓትም በዛሬው ዕለት ተፈጸሟል።  ቅዳሜ ዕለት በቱርክ መንግስት እና ፒኬኬ በሚባለው የኩርድ የስራተኛ ፓርቲ መካከል ያለው ግጭት ቆሞ ሰላም እንዲወርድ የሚጠይቁ ዜጎች ትዕይንተ ህዝብ ለማድረገ በሚሰናዱበት ወቅት ሁለቱ ቦምቦች በአጥፍቶ ጠፊዎች መፈንዳታቸው ይታወሳል።

 

Ø ጄኔራል ጆንሰን ኦሎኒ የተባሉ አንድ የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ በመንግስትና በአማጽያኑ መካከል የተፈረመ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ሊሆን ባለመቻሉ ምክንያት  እንደገና ወደጦርነት ለመግባት የሚገደዱ መሆናቸውን ቢቢሲ ለተባለው የዜና ወኪል በሰጡት ቃል አስታውቀዋል። ጄኔራሉ የመጡበት ጎሳ ለዘመናት የያዘው መሬት በአሁኑ ወቅት በመንግስት ኃይሎች መያዙ እና አገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር የደቡብ ሱዳንን አስተዳደራዊ ክልሎች ከ10 ወደ 28 ከፍ ለማድረግ የወሰኑት ውሳኔ በጣም ያበሳጫቸው መሆኑን ገልጸው መንግስቱ በሰላም ስምምነቱ ላይ እምነት እምነት የለውም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት የመሬት ቅሚያው ጦርነት ውስጥ የከተታቸው መሆኑን አስታውሰው አሁንም  ሊደገም እንደሚችል ገልጸዋል።  በአሁኑ ወቅት በደቡብ ሱዳን አብዛኛው ሰው በጦርነቱ መሰላቸቱን ቢገልጽም  የተፈረመው ስምምነት በስራ ላይ ይውላል የሚለው ተስፋው የመነመነ ነው በማለት የቢቢሲው ጋዜጠኛ አክሎ ዘግቧል።  በተያያዘ ዜና ደቡብ ሱዳን ውስጥ የሰፈረው የኡጋንዳ መከላከያ ሰራዊት በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ ከደቡብ ሱዳን ለቅቆ መውጣት እንደሚጀምር አስታወቀ። በደቡብ ሱዳን ያለው የኡጋንዳ ሰራዊት መሪ ብርጋድደር ካያንጃ ሙሀንጋ ጦራቸው  ደቡብ ሱዳንን ለቅቆ እንዲወጣ መልእክት የደረሳቸው መሆኑ ገልጸው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ መልቀቅ ይጀምራል ብለዋል። በተለይ በዋና ከተማዋ በጁባ ያለውን ጸጥታ በማስከበር በኩል አስተዋጾ አድርጓል ተብሎ የሚነገርለት የኡጋንዳ ሰራዊት ሳልቫኬርን ለመርዳት ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የገባ ነው በማለት በአማጽያኑ ሲከሰስ መቆየቱ ይታወሳል።

 

Ø ትናንት እሁድ በሰሜናዊ ካሜሩን በአጥፍቶ ጠፊዎች የፈነዱ ሁለት ቦምቦች ዘጠኝ ሰዎች ሲገድሉ 29 የሚሆኑ ማቁሰላቸው ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል። ሞራ ከምትባለዋ ከተማ ርቆ በሚገኝ ካንጋለሪ እየተባለ በሚጠራ መንደር ውስጥ ሁለት ቦምቦችን በማፈንዳት ጥቃቱን የፈጸሙት ሁለት  አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል። ከዚህ በፊት አካባቢው በተደጋጋሚ በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰበት በመሆኑ የትናንቱንም ጥቃት ያደረሰው ቦኮሃራም ለመሆኑ ጠንካራ ግምት አለ። በተመሳሳይ ደረጃ ባለፈው ቅዳሜ በቻድ የቦኮ ሃራም ሽብረተኞች ያፈነዷቸው ሶስት ቦምቦች 41 ሰዎችን ሲገድሉ 48 ሰዎችን ያቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል።

Ø በተያያዘ ዜና የናይጀረያ መከላከያ ኃይል የቦኮ ሃራምን ይዞታ ሙሉ በሙሉ የከበበው መሆኑን ገልጾ በቡዱኑ ላይ የመጨርሻ ወሳኝ ጥቃት ለመፈጸም በዝግጅት ላይ እንዳለ በትናንትናው ዕለት አስታውቋል። የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ ከዚህ በፊት ከ200 በላይ የሚሆኑ የቦኮ ሃራም አባላት እጃቸውን በሰላም የሰጡ መሆናቸውን በመጠቆም የቀሩት የቦኮሃራም አባላት በሰላም እጃቸውን እንዲሰጡ ጥሪ አድርገዋል። ታጣቂዎቹ እጃቸውን በሰላም የማይሰጡ ከሆነ የናይጄሪያ መከለከያ ሰራዊት   የተደበቁበትን ካምፖች እና ጉድጓዶች ጠንቅቆ ስለሚያውቅ  ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስባችው የሚችል መሆኑን በመግለጽ የማስፈራሪያ መልእክት አስተላፈዋል። ከዚህ ቀደም 200 የሚሆኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች  እጃቸውን መስጠታችው የተዘገበ ሲሆን  መረጃው  እስካሁን ድረስ  ከሶስተኛ ወገን ማረጋገጫ አላገኘም።  ቦኮሃራም የከዱ አባላት የሌሉት መሆኑን በመግለጽ ዜናውን ማስተባበሉ ይታወሳል።

 

Ø በጊኒ የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ በትናንትናው ምሽት የተጠናቀቀ ቢሆንም ተቃዋሚ ድርጅቶች ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም በማለት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። የጊኒ የዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ትብብር ፓርቲ (The Union for the Democratic Forces of Guine party) የተባለው ግምባር ቀደሙ የተቃዋሚ ድርጅት እሁድ ማታ በሰጠው መግለጫ የምርጫ ሳጥኖችን በመንግስት ደጋፊዎች ሲሞሉ የነበሩ መሆናችውን ና ወታደሮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች እየተዘዋወሩ በማጭበርበር ሲመርጡ የነበረ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪም ወታደሮች ድምጸ ቆጣሪዎችን ካንዳንድ ቦታችም ያባረሯቸው መሆናቸውንና  ከ400 የሚበልጡ የምርጫ ጣቢዎች ደግሞ ጭራሽ  ያልተከፈቱ መሆናቸውን  አሳውቀዋል። የተለይዩ የተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች ዛሬ ሰኞ ተመሳሳይ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በተቃዋሚ ድርጅቶች በመካሄድ ላይ ያለው ተቃውሞ ወደ አመጽ ይሸጋገራል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለ።    

 

 

 

 

መስከረም 29  ቀን 2008 ዓ.ም   

        

Ø  ዛሬ በቱርክ ዋና ከተማ በአንካራ የሰላምና የዴሞክራሲ መልእክት  ለማሰማት ትዕየንተ ህዝብ እያደረጉ ባሉ ሰዎች መሀል የፈነዱ ሁለት ቦምቦች 30 ሰዎችን ለሞት ሲዳርጉ ከ128 በላይ የሆኑትን አቁስለዋል።የ። ቦምቦቹ የፈነዱት በአንድ የባቡር ጣቢያ አጠገብ ሲሆን ትዕየንተ ህዝቡን የሚያደርጉት ጉዞ ለመጀመር በሚሰናዱበት ወቅት ነው። ሰልፉ የተዘጋጀው በተለያዩ ድርጅቶች ሲሆን ኤች ዲ ፒ (HPD) የተባለው የኩርድ ፓርቲም አንዱ መሆኑ ታውቋል። የመንግስቱ ባለስልጣኖች ፍንዳታው የሽበርተኞች ተግባር ነው ያሉ ሲሆን  ቦምቦቹ  በአጥፍቶ ጠፊዎች ነው  የፈነዱት የሚለውን መረጃ የሚመረምሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኤች ዲ ፒ ኃላፊዎች ቦሞቦቹ የፈነዱት በመንግስት ኃይሎች እንደሆነ ገልጸው  የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል በሚያጓጓዙ ዜጎች ላይ ፖሊሶች ጥቃት ያደረሱባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በተፈጠረው ሁኔታ ስለፉ መሰረዙን አዘጋጆቹ ገልጸዋል። በሚቀጥለው ወር በቱርክ ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ የተነገረ  ሲሆን ፒኬኬ በተባለው የኩርድ አማጽያን ቡድንና በቱርክ የጸጥታ ኃይሎች መካካል የተፈረመው የተኩስ አቁም ስምምነት በመፍረሱ ምክንያ ምርጫው እንቅፋት ሊገጥመው ይችላል  የሚል ስጋት አለ።፡

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት ከመንግስት ኃይሎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ 23 አጃቢዎቻቸው የተገደሉባቸው የሞዛምቢኩ የሬናሞ ፓርቲ መሪ አፎንሶ ድላካማ ከተደበቁበት ሲወጡ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው በቤት ውስጥ ተገልለው እንዲቀመጡ የተደረጉ መሆናቸው ተገለጸ። መንግስት የፓርቲውን መሪ በቤት ውስጥ ለማሰር ለወሰደው እርምጃ የሰጠው ምክንያት የለም።  አጃቢዎቻቸው የተገደሉት ሟቾቹ በአንድ ታክሲ ላይ ጥቃት በማድረሳችው በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ነው የሚል ምክንያት ከመንግስት በኩል ሲሰጥ የሬናሞ ቃል አቀባይ ደግሞ መንግስት የሬናሞ መሪን ለመግደል ያካሄደው የደፈጣ ጥቃት ነው በማለት ይወነጅላል።

 

Ø በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል የሰው አልባ መንኮራኩር እንዳይጠቀም የደቡብ ሱዳን መንግስት የተቃወመ መሆኑ ተገለጸ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመከታተልና ለማጠናከር በአገሪቱ ውስጥ የሚገኘው የሰላም አስከባሪ ኃይል ተጨማሪ ሄሊኮፕተሮችና ሰው አልባ መንኩራሮች እንዲመደቡለት ወስኗል ። የሰው አልባ መንኮራኮሮች በደበብ ሱዳን እንዲበሩ የጸጥታው ምክር ቤት የወሰነው ጉዳይ አጨቃጫቂ  ከመሆን አልፎ አለመግባባትና ጥላቻን ስለሚፈጥር መንግስታቸው የማይቀበለው መሆኑን የደቡብ ሱዳን የተመድ አምባሳደር ገልጸዋል። ሰው አልባ መንኩራኩሮች በጥቅም ላይ ውለው አጥጋቢ ውጤት ካስገኙት አገሮች መካከል አንዱ  የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መሆኑን የምክር ቤቱ አባላት ገልጸው  በእግር ለመድረስ በማይቻሉ ወይም አደገኛ በሆኑ አካባቢዎች በማሰማራት ጥሩ ውጤት ያስገኙ በመሆናቸው በደቡብ ሱዳንም መሰማራታቸው አስፈላጊ ነው  ብለዋል። በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል ኃላፊ ኸርቭ ላድሱስ(Herve Ladsous) በደቡብ ሱዳን የሰላም አስከባሪ ተግባራትን ለማከናወንና የሰላማዊ ሰዎችንም ሆነ የሰላም አስከባሪ ኃይሉ አባሎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሰው አልባ መንኮራኩርን መጠቀም አስፈላጊ ነው ካሉ በኋላ የደቡብ ሱዳን መንግስት ትብብር አስፈላጊ ስለሆነ ጉዳዩን ከመንግስቱ ባለስልጣኖች ጋር እንደሚመክሩበት ገልጸዋል።

 

Ø በዓለማችን ላይ የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቆጣጠር መንግስታት ከመደቡት በጀት ውስጥ አፍሪካ የሚገባት ድርሻ እየተሰጣት አይደለም በሚል የአፍሪካ የልማት ባንክ ዋና ጸሐፊ አኪንዉሚ አዴሴና ገለጹ።የአየር ንብረት መዛባትን አስመልክቶ የሚካሄደው ስብስባ በሚቀጥለው ታህሳስ ወር የሚካሄድ ሲሆን  የዓለም ሀብታም አገሮች  ለሚቀጥሉት አራት አመታት የአየር ንበረት መዛባትን ለመቆጣጠር አንድ መቶ ቢሊዮን ዶላር ለመመደብ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ተገልጿል። የአየር ንብረቱን ለማዛባት ከጋዝና ከመሳሰሉት የሚመጣ የካርቦን  ብክለት ዋነኛው ሲሆን  ለብክለቱ  የአፍሪካ ድርሻ ሁለት ከመቶ ብቻ ነው፣ የአይር ንብረቱ መዛባት የሚያስከትለው የአየር ሙቀት መጨመርና ድርቅት አስመልክቶ  በብዛት የሚጎዱት  የአፍሪካ አገሮች ናቸው በማለት ዋና ጸፊው ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት የአየር ንብረት መዛባትን ለመቆጣጠር የወጣው ወጭ 62 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 76 ከመቶ የሚሆነው ገንዘብ የተመደበው  ከተሽከርካሪዎች ከፋብሪካዎችና ከመብራት አመንጭ ኩባንያዎች የሚወጣውን የጋዝ ጭስ ለመቀነስ ነው ብለዋል። በአፍሪካ የሚገኙት የተሽከርካሪዎችም  ሆነ የፋብሪካ ብዛት አነስተኛ ስለሆነ አብዛኛው ገንዘብ የሄደው  እንደ ህንድና ቻይና ለመሳሰሉ ለእስያ አገሮች ነው። የአየር ንብረትን የሚያዛቡ ሁኔታዎችን ከመቀነስ በተጨማሪ የአየር ንብረቱ ለውጥ ለሚያስከትለው አዲስ ሁኔታ ተስማሚ የሆኑ ስራዎችን መስራት አስፈላጊ ስለሚሆን በዚህ በኩል አፍሪካ ተጨማሪ ገንዘብ እንዲመደብላት ያስፈልጋል በማለት ዋና ጸሐፊው ተናግረዋል።   

 

 

 

 

   

        መስከረም 28  ቀን 2008 ዓ.ም

         

Ø አራት የቱኒዚያ ሕዝባዊ ድርጅቶች የዚህ ዓመት የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚዎች ሆነዋል። ሽልማቱን ያገኙት አራቱ  ድርጅቶች የቱኒዚያ የስራተኛ ማኅበር፤ የቱኒዚያ ኢንደስትሪ ኮንፌዴሬሽን፤ የቱኒዚያ ንግድ እና የእጃ ሥራዎች ማህበር፤ እና የቱኒዚያ ሰብአዊ መብት ሊግ የተባሉት ድርጅቶች ናቸው። በ2002 ዓም.  የቱኒዚያ የሽግግር ሂደት ወደ እርስ በርስ ጦርነትና ወደ ደም መፋሰሰ በማራበት ወቅት እነዚህ ድርጅቶች “አራቱ  የቱኒሲያ ብሔራዊ ውይይት አካል” (National Dialogue Quartet) በሚል ስም ተሰባሰበው እንቅስቃሴ የጀመሩና በኋላም ለተፈጠረው የፖሊቲካ መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ናቸው። የአራቱ ድርጅቶች ስብስብ በቱኒሲያ ግድያና ሽብር ተስፋፍቶ በነበረበት ወቅት በህብረተሰብ ውስጥ ሰላማዊ ውይይቶች እንዲካሄዱና ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር እንዲሁም የአንዳንዱ ዜጋ ሰብዕዊ መብቱ እንዲከበርና አገሪቱም ሕገ መንግስታዊ አስተዳደር እንዲኖራት በማድረግ በኩል ከፍተኛ ሚና ነበረው ተብሏል።  የኖቤል ኮሚቴ ተጠሪ በሽልማቱ አሰጣጥ  ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የአራቱ ድርጅቶች ስብስብ በቱኒሲያ ያበረከተው አስተዋጾ ጉልህ በመሆኑ በመካከለኛው ምስራቅ፤ በሰሜን አፍሪካ እና እንዲሁን በሌላው ዓለም ሰላምንና ዴሞክራሲን ለማራመድ ፍላጎት እና እምነት ላላቸው ወገኖች ከፍተኛ አርአያ ሊሆን ይችላል ብለዋል።

 

 

Ø በዛሬው ዕለት 20 የሚሆኑ ከኤርትራ የመጡ ስደተኞች በአውሮፕላን ከጣሊያን ወደ ስዊድን የሄዱ መሆናቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ህብረት አገሮች በጣሊያንና በግሪክ ካሉ ስደተኞች መካከል 120 ሺ የሚሆኑትን ለመውሰድና በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች ለማስፈር የተስማሙ ሲሆን በዛሬው ቀን የተጓጓዙት 20 ኤርትራውያን የመጀመሪያው መሆናቸው ነው። ከአፍሪካ እና ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ ጣሊያን እና ወደ ግሪክ የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ መሄዱ የተነገረ ሲሆን በዚህ ሳምንት በአንድ ቀን ብቻ 2000 ስደተኞች ጣሊያን የገቡ መሆናችው ታውቋል። የአውሮፓው ህብረት የአገር ውስጥ ሚኒስትሮች ባስተላለፉት ውሳኔ መሰረት ለፖሊቲካ ጥገኝነት ብቁ አይደሉም የሚባሉትን ስደተኞች ወደመጡበት ለመመለስ ካለፈው ረቡዕ ጀመሮ ከተለያዩ አገሮች የተውጣጡ መርከቦችና የጠረፈ ጠባቂዎች በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የተሰማሩ መሆናቸው ተነግሯል።

 

Ø ሐሙስ ዕለት የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ባለስልጣኖች  አቺሌ ታብሶባ የተባሉትንና  የኮንግሬስ ፎር ዴሞክራሲ አንድ ፕሮግሬስ (Congress for democracy and Progress )  ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትን በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸው ተነገረ። ፓርቲው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ካምፕወሬ የሚመሩት ሲሆን ለረዥም ዓመታት ስልጣን ላይ የነበረ ፓርቲ ነው።  አቺሌ የታሰሩት ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ በተሞከረው መፈንቅለ መንግስት ሴራ ውስጥ እጃቸው አለበት ተብሎ ሲሆን በዚህ ሳምንት ውስጥ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የቅርብ ሰው በመሆን በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሰዎች መካከል ሶስተኛው መሆናቸው ነው። የመፈንቅለ መንግስቱ መሪ ጄኔራል ዲየንዴሪ እና የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጅብሪል ባሶል በመንግስት ላይ ጥቃት መፈጸም እና ግድያ ማካሄድ በሚሉ ወንጀሎች መከሰሳችው ይታወቃል። መሆናቸው ታውቋል።

 

 

Ø በሚቀጥለው እሁድ በጊኒ ብሔራዊ ምርጫ የሚካሄድ ሲሆን ዛሬ በአግሪቱ ዋና ከተማ ኮናክሪ ውስጥ በፕሬዚዳንት ኮንዴ ደጋፊዎችና ግምባር ቀደም ተቃዋሚ በመሆን በሚወዳደሩት በሴሉ ዳሊየን ዲያሎ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ቢያንስ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ከ20 በላይ የሆኑ የቆሰሉ መሆናችው ተነግሯል። ግጭቱ በአገሪቱ ያለውን የጎሳ ልዩነት ውጥረት ውስጥ የከተተ ሲሆን አየተባባሰ ከሄደ አደገኛ ሊሆን ይችላል ተብሏል። ማሊንኬ የሚባሉ የፕሬዚዳንት ኮንቴ ደጋፊ ጎሳ አባላት የፉላኔ ነጋዴዎችን መዲና ወደተባለው የገበያ ቦታ እንዳይገቡ በመከልከላቸው ከፍተኛ ግጭት ሊነሳ ችሏል። የፉላኔ ጎሳ አባላት የተቃዋሚው መሪ ደጋፊዎች ናቸው።  ሀሙስ ዕለት ለአርብ አጥቢያም 20 የሚሆኑ የፉላኒ ጎሳዎች ሱቆች በኮንዴ ደጋፊዎች የተዘረፉና የተቃጠሉ መሆናቸው ታውቋል።

 

Ø በምዕራብ እና በምስራቅ ሊቢያ  መንግስት ያቋቋሙትን የሊቢያን ተጻራሪ ኃይሎች ለማስታረቅ አደረዳሪ የሆኑት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መልእክተኛ በሊቢያ ሊመሰረት ለታቀደው  የብሔራዊ የአንድነት  መንግስት በመሪነት ደረጃ ኃላፊነት ሊወስዱ ሰዎችን ስም ዝርዝር በሀሳብ ደረጃ ያቀርቡ መሆናቸው ታወቀ። በልዑኩ ሀሳብ መሰረት መንግስቱን የሚመራ አንድ ጠቃላይ ሚኒስትር እንዲኖርና የምዕራቡን የመካከለኛ ግዛቱንና የምስራቁን ግዛቶች ሊወክሉ የሚችሉ  የሚችሉ ሶስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ይመደባሉ የተባለ ሲሆን ፋይዝ ሳራጅ የተባሉት ሰው ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ሀሳብ ቀርቧል። የተመድ ሉዑክ ያቀረቡት ሀሳብ ከሁለቱም ወገኖች በኩል ጠንካራ ተቃውሞ የገጠመው በመሆኑ በስራ ላይ ሊውል የሚችልበት ሁኔታ አነስተኛ ነው  በማለት ታዛቢዎች ይተቻሉ። 

 

Ø እውቁ ጸሐፊ፣ ጋዜጠኛ እና ዲፕሎማት አምባስደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ረቡዕ በእንግሊዝ አገር በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አምባሰደር ዘውዴ ረታ በመጨርሻ የጻፉትን መጽሐፍ  ለማስመረቅ በእንግሊዝ አገር በጉብኝት ላይ የነበሩ ሲሆን በመንገድ ላይ እየሄዱ ባልታሰበ ሁኔታ ስለወደቁ ወደ ሆስፒታል ተወስደው  በህክምና እየተረዱ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። አምባሰደር ዘውዴ ረታ ከዚህ በፊት የተለያዩ መጽሐፍትን ደረሰው ለአንባብያን ያቀረቡ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የኢርትራ ጉዳይ፤ ተፈሪ መኮንን፤ እና የቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ መንግስት የሚባሉ ይገኙባቸዋል። አምባሰደር ዘውዴ ራታ በንጉሱ ዘመን በጣሊያንና በቱኒሲያ በአምባሳደርነት፤ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በካውንሰለርነት የሰሩ ሲሆን በአገር ውስጥም በማስታወቂያ ሚኒስቴር በተለያዩ ኃላፊነቶች ሰርተዋል። ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ ከአገር ተሰደው በጣሊያን አገር የተቀመጡ ሲሆን  ኢንተርናሽናል ፈንድ ፎር አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት (አይፋድ ) በሚባል አንድ ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። ለቤተሰቦቻቸውና ለሚያውቋቸው መጽናናትን እንመኛለን።

 

 

 

 

        

መስከረም 27  ቀን 2008 ዓ.ም

                

Ø ድንበር የለሽ ጋዘጠኞች (Reporters Without Borders) የተባለው ማዕከሉ ፈረንሳይ አገር የሆነው የመገናኚያ ብዙሐን አባላት መብትን  ለመንከባከብ የተቋቋመው ተቋም የወያኔ አገዛዝ በግፍ ያያዛቸውን አራት ጦማርያን እንዲፈታ በድጋሚ ጠየቀ። ተቋሙ ይህን ጥያቄ ያቀረበው የወያኔው ፍርድ ቤት የጦማርያኑን ጉዳይ ለማየት እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ነው። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ ዞን 9 በሚል ስም ተደራጅተው በወያኔ አገዛዝ ላይ ነቀፌታን ያዘለ ጽሁፍ በመጻፋቸው ብቻ   ስደስት ጦማርያንና ሶስት ጋዘጠኞች መታስራቸው ይታወሳል። የወያኔ አገዛዝ ግብሩን ለመሸፈን ባለፈው ሐምሌ ወር ላይ የተወሰኑትን የፈታ ቢሆንም አራቱ ማለትም አቤል ዋቤላ፣ ናትናኤል ፈለቀ፤ አጥናፍ ብርሃኔና በፈቃዱ ኃይሉ  በእስር ቤት የቀሩ መሆናቸው ይታወቃል። የወያኔው አቃቤ ህግ በእነዚህ እስርኞች ላይ በሀምሌ ወር ላይ በተፈተቱ በሁለቱ ጦማርያን ላይ ከአቀረበው  የተለየ መረጃ  ያላቀረበ መሆኑን በመጥቀስ ድንበር የለሽ የጋዘጠኞች ተቋም እስረኞቹ ባስቸኳ እንዲፈቱ ጠይቋል። የወያኔ አገዛዝ በአገዛዙ ላይ ነቀፌታ የሚያሰሙ  የመገናኚያ ብዙሀን አባላትን  የአሸባሪነ ስም በመስጠትና ህገ ወጥ  በሆነ መንገድ  በማሰረና በማሰቃየት በኩል አፋኝ ከሚባሉት የአፍሪካ አገዛዞች መካከል ሁለተኛ ደረጃውን የያዘ ሲሆን የፕሬስ ነጻነትን ሙሉ በሙሉ ከሚያስከብሩ 180 አገሮች ውስጥ  ደግሞ ደረጃው ወደ መጨረሻዎቹ አስከፊ አገሮች ተርታ የተቀመጠ መሆኑ ይታወቃል።  

 

Ø የብሩንዲ መንግስት አንድ የሩዋንዳን ከፍተኛ ዲፕሎማት ከአገሩ ያባረረ መሆኑ ተገለጸ። ዲዛየር ኒያሩሂሪራ የሚባሉትና ብሩንዲ በሚገኘው የሩዋንዳ ኤምባሲ ውስጥ ለረዥም ዓመታ ሲያገለግሉ የነበሩት ዲፕሎማት ከአገር እንዲወጡ የታዘዙት በአገሪቱ ውስጥ የሽብር ስራዎችን ከጀርባ ሆነው ያቀናጃሉ በሚል ምክንያት ነው። በአሁኑ ወቅት በብሩንዲና በሩዋንዳ መካከል ያለው ግንኙነት በጣም የቀዘቀዘ ሲሆን ባለፈው ሳምንት ውስጥ የቡሩንዲ ተቃዋሚዎች የሽብር ተግባር እንዲያካሄዱ ሩዋንዳ ስልጠና እየሰጠች ነው በማለት የብሩንዲ መንግስት የከሰሰ መሆኑ ይታወሳል።

በተያያዘ ዜና የሩዋንዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግሪን ፓርቲ የተባለው የተቀዋሚ ፓርቲ አቅርቦት የነበረውን ክስ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ተገለጸ። የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ መወዳደር የሚያስችላቸው የህገ መንግስት መሻሻል አስመልክቶ  ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ  የሩዋንዳው ምክር ቤት የደረሰበትን ውሳኔ በመቃወም ግሪን ፓርቲ የተባለው የሩዋንዳ ተቃዋሚ ፓርቲ ያቀረበው ክስ በከፍተኛው ፍርድ ቤቱ አይቶት  ውድቅ አድርጎታል። ፍርድ ቤቱ  ሕዝብ እንዴት ሊገዛ እንደሚችል የመወሰን መብት ሊኖረው ይገባል የሚል ምክንያት በመስጠት ክሱን ውድቅ ያደረገው መሆኑን ገልጿል። ፕሬዚዳንት ካጋሜ በ1993 እና በ2003 ዓ.ም በተደረጉ ብሔራዊ ምርጫዎ አሸናፊ ተብለው ስልጣን ላይ መቆየታቸው ሲታወቅ አሁን ያለው ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የምርጫ ጊዜ በሁለት የምርጫ ዘመን ይወስናል።

 

Ø በአውሮፓ ውስጥ የፖሊቲካ ጥገኝነት የተነፈጉት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ አገራቸው ባስቸኳይ የሚመለሱበትን ሁኔታ ለመወሰን  የአውሮፓው ህበረት የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትሮች በዛሬው ቀን የሚሰበሰቡ መሆናቸው ታወቀ። ሚኒስትሮቹ የተደበቁ ስደተኞችን እንዴት መያዝ እንደሚቻልና በምን ዓይነት መንገድ በፍጥነት ወደ አገራቸው መመለስ እንደሚቻል ባካተቱት የውሳኔ ረቂቆች ላይ ውሳኔ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ስደተኞቹ የመጡባቸው አገሮች ዜጎቻቸውን እንዲቀበሉ ለማድረግ  ጫና ማድረግ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ይወያያሉ ተብሏል።

 

Ø ከለፈው አንድ አመት ተኩል ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በጊኒ እና በሲየራ ሊዮን የኢቦላ በሽታ ለአንድ ሳምንት ያህል ሳይገኝ በመቅረቱ በሽታው ሊጠፋ ይችላል የሚል ተስፋን ፈንጥቋል። ላይቤሪያ ላለፉት 42 ቀናት አንድም የኢቦላ በሽተኛ ያልተየባት ስለሆነች ከኢቦላ ነጻ የሆነች አገር የሚል ስያሜ ተሰጥቷል። ጊኒ ካለፈው መስከረም 16 ውዲህ ፣ ሲየራ ሊዮን ደግም ከመስከረም 17 ወዲህ አንድም የኢቦላ በሽተኛ ያልተየባቸው በመሆኑ ከኢቦላ ነጻ የሆኑበትን የመጀመሪያ ሳምንት አክብረዋል። በጊኒ በላይቤሪያ እና በሲየራሊዮን እስካሁን ድረስ ከ አስራ አንድ ሺ ሰዎች በላይ በበሽታው የሞቱ መሆናቸው ይታወቃል። የተባበሩት መንግስታት የጤና ድርጅት በሽታው ባለፉት 10 ወራት በጣም እየቀነሰ የመጣ መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት እንደገና ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ብሏል።

 

 

Ø በትናንትናው ዕለት በየመን ከዋናው ከተማ ከሳንአ 100 ኪሎሜትር ላይ ርቃ በምትገኝ ሳንባን በተባለች ከተማ ውስጥ በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል በሰርገኞች በነበሩ ሰዎች ላይ ባደረሰው የአየር ጥቃት 13 ሰዎች መሞታቸውንና  ክ 38 ሰዎች በላይ የቆሰሉ መሆናቸውን የሆስፒታል ምንጮች ገለጹ። ላለፉት ሰባት ወራት በሁቲ አማጽያን ይዞታ ላይ ተከታታይ የአየር ጥቃት ሲያካሂድ የነበረው በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል ስላካሄደው ጥቃትና ስላደረሰው ጉዳት የሰጠው መግለጫ  የለም። ጥምር ኃይሉ በሰረገኞች ላይ ጥቃት ሲፈጽም  በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህ ሁለተኛ ጊዜው መሆኑ ነው። ባለፈው ሳምንት አልሞክሃ በተባለች የቀይ ባህር ዳርቻ ከተማ ውስጥ እየተካሄደ በነበረ አንድ የሰርግ በአል ላይ ጥምር ኃይሉ ባካሄደው የአየር ጥቃት ቢያንስ 131 ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል። በተያያዘ ዜና በየመን የስደተኛው መንግስት እና በሁቲ አማጽያን መካከል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት ሲካሄድ የቆየውና  በመሀሉ ተቋርጦ የነበረውን የእርቅ ውይይት እንደገና ለመጀመር ሁለቱም ወገኖች የተስማሙ መሆናቸው ተገልጿል። 

 

Ø የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ፌዴርሽን ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላትር፣ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ማይክል ፕላቲኒ እና ዋና ጸሐፈው ጀሮሜ ዋልኬ ለ90 ቀናት ያህል ከስራቸው የታገዱ መሆናቸው ተነገረ።  ፕሬዚዳንቱ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እና ዋና ጸሐፊው ላይ እገዳ የተደረገው ሰዎቹ በከፍተኛ ሙስና ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው በመሆኑ ነው። በእገዳ ጊዜያቸው ወቅት ሰዎቹ ከማናቸውም የእግር ኳስ ስራዎች የተገለሉ መሆናችው ተገልጿል። የቀድሞ የፊፋ ምክትል ፕሬዚዳንት ቹንግ ሞንግጁን በሙስና ተግባር ውስጥ መሳተፋችው በመረጋገጡ  ለስድስት ዓመታት ያህል ከእግር ኳስ ስራዎች የታገዱ ሲሆን 100 ሺ የስዊስ ፍራንክ መቀጫ እንዲከፍሉ ተበይኖባቸዋል።

 

 

        

 

 

 

 

መስከረም 26  ቀን 2008 ዓ.ም

                

Ø ባለፈው ሰኞ 14 ኢትዮጵያን በኬኒያ ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸውና እያንዳንዳቸው  20 ሺ የኬኒያ ሽልንግ ከፍለው እንዲለቀቁ የማይችሉ ከሆነም ለ 130 ቀናት ያህል እንዲታሰሩ  ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሲሆን  የተከሰሱት ደግሞ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ አገር ውስጥ ገብተዋል በሚል ክስ ነው። የኬኒያ ባለስልጣኖች ከኢትዮጵያ ወደኬኒያ  ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የሚገቡት ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መሄዱን ገልጸው ቦታው ሰፊ በመሆኑ ለመቆጣጠር አዳጋቸ መሆኑን ተናገረዋል። የወያኔ ግፈኛና አስከፊ አገዛዝ በመሸሽና ኑሯቸውን ለማሻሻል ወደ ኪኒያ እና ከዚያም አልፈው ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መሆኑን ጉዳዮን በቅርብ የሚከታተሉት ክፍሎች ይገልጻሉ። የዓለም አቀፉ የስደተኛ ድርጅት በቅርቡ ባወጣው ዘገባ በየቀኑ በአማካይ 30 ኢትዮዮጵያውያን  ወደ ኬኒያ እንደሚገቡና በወር ከ90 ሚሊዮን የኬኒያ ሽልንግ በላይ ለአስተላላፊዎች ጉቦ እንደሚከፍሉ ገልጿል። ራሱ የወያኔ ኢምባሲ በሰጠው ግምት እንኳ በደቡብ አፍሪካ ከ45 ሺ እስከ 50 ሺ የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ገልጿል። በሁሉም አቅጣጫ  ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚሰደደው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሄደ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ይህም ሀቅ ወያኔ ኢኮኖሚውን በጥምር አሃዝ እያሳደገነ ነው ብለው ከበሮ የሚደልቁትን ክፍሎች እያሳፈረ ነው በማለት ታዛብዎች ይተቻሉ።

 

Ø ከጥቂት ሳምንታት በፊት  በቡርኪና ፋሶ የተካሄደውንና ባጭር የተቀጨውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው ለፍርድ የቀረቡ መሆናቸው ተነገረ። የጄኔራል ዴየንዴሬን ጉዳይ አይቶ ፍርድ የሚሰጠው አካል ወታደራዊ ፍርድ ቤት ሲሆን ጄኔራሉ በአስራ አንድ ወንጀሎች የተከሰሱ መሆናቸውና ከነዚህም ውስጥ የመንግስትን ጸጥታ ማናጋት፤ ግድያ፤ ከውጭ ኃይሎች ጋር ተባብሮ አገርን ማጥቃት እና የንብረት ማውደም የሚሉ እንደሚገኙበት ተገልጿል። የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ጂብሪል ባሶል ከመፈንቅለ መንግስት አድራጊዎች ጋር ተባባሪ ናቸው የሚል ክስ ተመስርቶባቸው በወታደራዊ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ መሆናቸው ሲገለጽ ከቀረበባቸው የክስ ወንጀል ነጻ መሆናችውን መግለጻቸው ግታውቋል። ባለፈው ሳምንት ጄኔራል ዲየንዴሬ በቫቲካን ኤምባሲ መሸሸጋቸውና በኋላም ለቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ባለስልጣኖች እጃቸውን መስጠታቸው ይታወሳል። እሳቸው ከሚመሩት የወታደር ክፍል ውስጥ የተወሰኑት  ትጥቅ አናወርድም በማለታቸው የአገሪቱ መከላከያ ኃይል በወታደራዊ ሰፈራቸው ላይ ጥቃት ለማድረግ ተገዶ የነበረ መሆኑም አይዘነጋም።  

 

Ø በሚዲትራኒያን ባህር ላይ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ ስደተኞችን ወደ አውሮፓ ለማስረግ የሚንቀሳቀሱ ጀልባዎችንና መርከቦችን ለመቆጣጠር የአውሮፓው ህበረት አዲስ ስምሪት የጀመረ መሆኑ ታወቀ። የሶፊያ ኦፕሬሽን በሚል ስም በዛረው ቀን በተጀመረው እንቅስቃሴ  መሰረት በአውሮፓው ህብረት የተሰማሩ የባህር ኃይል አባሎች ስደተኞች አሉበት ብለው የሚጠርጥሯቸውን ማናቸውንም አነስተኛ መርከቦችና ጀልባዎች አስቁመው የሚመረምሩ መሆናቸውና እነዳስፈላጊነቱ መርከቦቹንና ጀልባዎችን ይዞ በቁጥጥር ስር ለማድረግም ሆነ ወደ መጡበት ለመመለስ ስልጣን የተሰጣቸው መሆኑ ታውቋል። እስካሁን ድረስ የአዎሮፓው ህብረት የባህር ኃይል መርከቦች በቅኝትና በነፍስ ማዳን ተግባር ላይ ብቻ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸው ይታወቃል። በዚህ ስራ ላይ ስድስት የጦር መርከቦች እንዲሁም በርካታ ሂሊኮፕተሮችና ስው አልባ ተንቀሳቃሽ በራሪዎች (ድሮኖች) የተሰማሩ መሆናቸውም ተገልጿል።  ባለፉት 10 ወራት ከ 130 ሺ ሰተኞች በላይ ከሰሜን አፍሪካ የባህር ዳርቻዎች ተነስተው አውሮፓ የገቡ መሆናቸው ሲታወቅ 2700 የሚሆኑት  ባህሩ ውስጥ ሰጥመው የሞቱ መሆናቸው ተዘግቧል።

 

Ø ቦኮሃራም በሚባለው አሸባሪ ቡድን ጥቃት እየታመሰ የሚገኘው የሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ ግዛት በዛሬው ዕለት በፈንጅ ጥቃት ጉዳት እየደረሰበት መሆኑ ተዘገበ። ዳማቱሩ በምትባለው የዩቤ አውራጃ ዋና ከተማ ውስጥ የአሸባሪው ቡድን አባሎች ባፈነዷቸው ሁለት ቦምቦች 14 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ገለጸ።  የቦኮ ሃራም አባል የሆነው አንደኛው አጥፍቶ ጠፊ በተወሰኑ ወጣቶች መካከል ያፈነዳው ቦምብ አራት ወጣቶችን ሲገድል ሌላኛው ደግሞ ቤተሰቦቹንና ጎረቤቶችን ሰብስቦ የሃይማኖት ስብከት እያደረገ እያለ የያዘውን ቦምብ በማፈንዳቱ 10 ሰዎች ሞተዋል። በተያያዘ ዜና የመንግስቱ ወታደራዊ ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ የተወሰኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች  በዮቤ አውራጃ ውስጥ ባለው ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ሰንዝረው የተኩስ ልውውጥ የተደረገ መሆኑንና በግጭቱም ከ100 በላይ የሆኑ ታጣቂዎችን ተገድለው ሌሎች መያዛቸውን እንዲሁም ከወታደሩ በኩል ሰባት ወታደሮች መሞታቸውን አሳውቋል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በቅርቡ በለቀቁት ተንቀሳቃሽ ስዕል ደግሞ አሸባሪዎቹ ለአይሲስ ታማኝ መሆናቸውንና እንዲሁም በመንግስት በኩል ተድረገ የተባለው ውታደራዊ ድል ውሸት መሆኑን ተናግረዋል። 

 

Ø የደቡብ ሱዳን መንግስት ከስምምነቱ ውጭ በገዛ ስልጣኑ የአካባቢ ግዛቶችን ቁጥር ከ10  ወደ 28 ከፍ እንዲል በማድረጉ  በመንግስቱና በአማጽያኑ መካከል ባለፈው ዓመት ነሐሴ 20 ቀን 2007 ዓ፣ም ተደርጎ የነበረው ስምምነት አደጋ ሊያጋጠመው እንደሚችል የአማጽያኑ ቃል አቀባዮች ማክሰኞ ዕለት አስታውቀዋል። በስምምነቱ ውስጥ የተቀመጠውን  የስልጣን ድርሻ በሚጻረር መልክ ባለፈው አርብ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ስልጣን የሚኖራቸውና በጎሳ ላይ የተመሰረቱ ግዛቶች ቁጥር ከ10 ወደ 28 ከፍ እንዲል አድርገዋል። አማጽያኑንም ሆነ ስምምነቱን የደገፉት አሜሪካ እንግሊዝ እና ኖርዌይ ይህ የሳልቫኬር ርምጃ  ቀደም ብሎ ተደረጎ የነበረውን የስልጣን ክፍፍል ስምምነት የሚጻረር መሆኑን ሲገልጹ የአውሮፓው ህበረት ደግሞ ሳልቫኬር ውሳኔያቸውን እንዲሽሩ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።  በመንግስቱ በኩል የተወሰደው እርምጃ በደቡብ ሱዳን ጎሳዊ ስሜቶችን አነሳስቶ በመካከላቸው ያልተቋረጠ ጦርነት እንዲካሄድ ነው በማለት የአማጽያኑ ቃል አቀባይ ተናግሯል። ባለፈው ዓመት በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎ ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ጦርነት ያላቆመ መሆኑ በየጊዜው ተዘግቧል።  ለተኩስ አቁሞ መጣስ ምክንያት አንዱ ሌላኛውን እየከሰሰ ቢሆንም የሚካሄደው ጦርነቱ ጉዳት ማድረሱ አልቀረም። በአካባቢው የሚገኙ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በጦርነቶቹ ምክንያት ስራቸውን ያቋረጡ በተለያዩ ቦታዎች ስራቸውን ማቋረጠቸው የተነገር ሲሆን የተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅትም በዚህ ዓመት በደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ረሃብ ሊከሰት እንደሚችል ተንብየዋል።፡

 

መስከረም 25  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በየመን ደቡባዊ ግዛት በኤደን ከተማ ከስደት የተመለሱት የየመን ጠቅላይ ሚኒስትርና የካቢኔ አባሎቻቸው አርፈውበት የነበረበት ካስር የሚባለው ሆቴል በሮኬት በመደብደቡ ምክንያት በርካታ ሰዎች መገደላቸውና መጎዳታቸው ተገለጸ። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ  ከሞቱት መካከል 15 የሚሆኑት በሳኡዲ የሚመራው የአረብ ጥምር ኃይል አባላት መሆናቸው ሲገለጽ ከእነዚህም ውስጥ 4 የኤምሬት ተወላጅ እና አንድ የሳዑዲ ተወላጅ ናቸው።  ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በሆቴል ያልነበሩ መሆኑ የተነገረ ሲሆን  የካቢኒ ሚኒስትሮችም ከአደጋው የዳኑ መሆናቸው ታውቋል። በሳኡዲ የሚመራው ጦር የሁቲ አማጽያንን ከኤደን ካስወጣ ጀምሮ የካስር ሆቴል ለየመን ስደተኛ መንግስት መቀመጫ ሆኖ በማገልገል ላይ ነበር። እስካሁን ድረስ በሆቴሉ ላይ ለደረሰው የሮኬት ጥቃት ኃይላፊነቱን የወሰደ ቡድን የለም። የሁቲ አማጽያን ከተማውን ከለቀቁ ጀምሮ በርካታ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸው ኃይሎችና ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ኃይል አባሎች ነን የሚሉ ቡድኖች እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች ይናገራሉ።  ባለፈው ዓመት መጋቢት ላይ የሁቲ አማጽያን የአገሪቱን ዋና ዋና ከተሞች በመቆጣጠራቸው  የየመን ፕሬዚዳንትና ሃዲና መንግስታቸው አገር ጥለው የተሰደዱ መሆንቸው ሲታወቅ ባለፈው ሐምሌ ወር በሳዑዲ የሚመራው ኃይልና የመንግስቱ ደጋፈዎች የሁቲ አማጽያንን ከኤደን ማስወጣቸው ይታወሳል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግምት የየመን ችግር ከተፈጠረ ካለፈው ስድስት ወር ጀምሮ በጠቅላላው 4900 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 2300 የሚሆኑት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።

 

Ø ሰኞ ሌሊት ለማክሰኞ አጥቢያ  የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በቻድ ባህር አጠገብ አንድ የቻድ ወታደራዊ ካምፕ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 13 የቻድ ወታደሮች የሞቱ መሆናቸው የቻድ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ ለዜና ምንጮች ገልጿል። 17 የሚሆኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች መገደላቸውንም ቃል አቀባዩ ጨምሮ ተናግሯል። ወታደሮቹ በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የቦኮሃራም ታጣቂዎች ወደመጡበት ያፈገፈጉ መሆናቸውና ወታደራዊ ኃይሉ እየተከታተላቸው መሆኑም ተገልጿል። ቻድ ቦኮ ሃራምን ለማዳከምና ለማጥፋት ከተለያዩ አገሮች ተውጣቶ የተቋቋመው ጥምር ኃይል ውስጥ አባል ከሆነችበት ጊዜ ጀምሮ በቦካሃራም ተከታታይ ጥቃት ሲደርስባት የቆየ መሆኑ ይታወሳል። የቦኮሃራም እንቅስቃሴ ከተጀመረ ጀምሮ በጠቅላላው በናይጄሪያና በአካባቢው አገሮች ከ17 ሺ ሰው በላይ ህይወቱን ማጣቱና ከ2.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቤቱን ጥሎ የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።

 

Ø በትናንተናው ዕለት ከሊቢያ ጠረፍ ተነስተው ወደ አውሮፓ ይጓዙ የነበሩ 1800 ስደተኞች  ከመስጠም አደጋ የዳኑ  መሆናቸውን የጣሊያን ጠረፍ ጠባቂዎች ገለጹ። ከጣሊያን፣ ከእንግሊዝ እና ከአየርላንድ የተውጣጡ መርከቦችን በመጠቀም እና ስድስት ዙር የማዳን ተግባሮችን በማካሄድ የስደተኞቹን ህይወት ለማትረፍ የተቻለ መሆኑ ታውቋል። ባለፉት 10 ወራት ግማሽ ሚሊዮን ሰደተኞች ከተለያዩ ቦታዎች ወደ አውሮፓ የተሻገሩ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን 2980 የሚሆኑ በባህሩ ውስጥ ሰጥመው ሞተዋል ተብሏል። ከቱርክ ተነስተው ባህር አቋርጠው ወደ አውሮፓ የሚሻገሩት ስደተኞች ከሶሪያ እና እንደአፍጋኒስታን ከመሳሰሉ የኤሽያ አገሮች የመይጡ ሲሆን ከሊቢያ ጠረፍ የሚነሱ ስደተኞች ደግሞ አብዛኞቹ ከአፍሪካ የመጡ መሆናቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች ይናገራሉ። ከነገ እሮብ ጀምሮ  ማንኛቸውም በዓለም አቀፍ ባህር ላይ ስደተኞችን ያመላልሳሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ጀልባዎችና አነስተኛ መርከቦች ፍተሻ እንዲካሄድባቸውና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የአውሮፓው ህበረት ለጠረፍ ጠባቂ ባለስልጣኖች ማዘዣ የሰጠ መሆኑ ታውቋል።  

 

Ø የጋና መንግስት ሰባት የሚሆኑ የጋና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኖችን ከስራቸው ያገደ መሆኑ ተነገረ። በዳኖቹ ላይ ውሳኔ መደረጉ የታወቀው ፕሬዚዳንቱን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንቱ በሰጡት መግለጫ ሲሆን ውሳኔው የተደረሰው  የፍርድ ነክ ጉዳዮች ካውንስል የደረሰበትን ውሳኔ ተመርኮዞ  መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት ለጉብኝት ፈረንሳይ  የሚገኙት  የጋናው ፕሬዚዳንት ከዚህ በፊት አንድ የጋና ጋዜጣ  የዳኞችን ሙስና አስመልክቶ በአምዱ ላይ ያሰፈረውን መረጃ በማድረግ ጉዳዩን እንዲመረመርና  ውሳኔ እንዲሰጥበት ለአገሪቱ ዋና ዳኛ መመሪያ ማስተላፋቸው ይታወሳል። በከፍተኛ ዳኖች ላይ የተሰጠው ይህንን ጉዳይ ለመመረመር የተቋቋመው የፍርድ ጉዳይ ኮሚሽን ጉዳዩን አጣርቶ ባቀረበው ሀሳብ መሰረት መሆኑ ታውቋል።  ባለፈው ወር 22 የዝቅተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ከስራ መባረራቸውና 12 የሚሆኑ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ምርመራ እንደደረግባቸው መታዘዙ ይታወሳል። የጋና መንግስት ይህንን እርምጃ ለመውስድ የተገደደው የጋና መገናኚያ ብዙሃን አባላት በርካታ ዳኞች ጉቦ ሲበሉ በድብቅ ያነሱት ፊልም ለሕዝብ እንዲታይ ተደርጎ በመጋለጡ ነው።

 

Ø በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠው የሊቢያ ምክር ቤት  ስልጣኑ የሚያበቃበትን ቀን ላልተወሰነ ጊዜ ያስተላለፈው መሆኑ ተገለጸ። ምክር ቤቱ በስልጣን እንዲቆይ ተወስኖ የነበረው እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2008 ዓ.ም. (October 20, 2015) ድረሰ የነበረ ሲሆን ቀኑ እንዲራዘም የቀረበው ሀሳብ ከ131 አባላት 129ኙ ደግፈውት የስልጣኑን እድሜ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። አንዳንድ የፖሊቲካ ታዛቢዎች ምክር ቤቱ ይህንን የወሰነው  ትሪፖሊ ላይ ከሚገኘው ተጻራሪ መንግስት ካቋቋመው  ክፍል  በመካሄድ ላይ ያለው የእርቅ ድርድር  ላይ ብዙዎቹ አባላት ተስፋ በመቁረጣቸው ነው የሚል አስተያየቶች ሲሰጡ ሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ደግሞ ውሳኔውን ለመወሰን የገፋፋቸው  እርቁ የማይሳካ ከሆነ የስልጣን ገዋ እንዳይፈጠር ነው ይላሉ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት እየተካሄደ ያለው የእርቅ ድርድር የቀን ገደቡ ጥቅምት 9 ቀን 2008 ዓ.ም (October 20, 2015) መሆኑ ይታወቃል።

 

 

    መስከረም 24  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በሳምንቱ መጨረሻ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ በመንግስቱ ተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት 12 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና ወኪል ከስፍራው የደረሰውን ዜና ዋቢ በማድረግ ገልጿል። ግጭቱ የተጀመረው ቅዳሜ እኩለ ቀን ላይ ሲሆን እስከ አሁድ ድረስ የዘለቀ መሆኑ ታውቋል። የፖሊስ ቃል አቀባይ በሰጠው መረጃ ቅዳሜ ዕለት  የመንግስት ተቃዋሚዎች በፖሊስ አባላት ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ሁለት ፖሊሶች መጎዳታቸውን የገለጸ ሲሆን ፖሊሶች በወሰዱት የአጸፋ ጥቃት ደግሞ ሁለት ሰዎች ሞተዋል ብሏል። በቦታ የነበሩ የአይን እማኞች በሰጠቱ መረጃ ግን ግጭቱ ከዚህ የሰፋ እንድነበርና የሞቱት ሰዎች ቁጥርም በርካታ እንደነበር ገልጸዋል። እሁድ ጠዋት ሲቢቶኬ በሚባለው የከተማው ቀበሌ ስድስት የሰላማዊ ሰዎች አስከሬን የተገኘ ሲሆን  ማታኩራ በሚባለው ደግሞ ሌሎች አራት አስከሬኖች መገኘታቸውን በቦታው የነበሩ ሰዎች ገልጸዋል። አንዳንዶቹ የተገደሉት ግምባራቸው ላይ በተተኮሰ ጥይት መሆኑም ተጠቅሷል። በአይን እማኞቹ መረጃ መሰረት ሊጀመር የቻለው ፖሊሶች ማታኩራ ከሚባለው የከተማው ክፍል ፖሊሶች ወጣቶችን ለማሰር ሙከራ ባደረጉበት ወቅት የአክባቢው ነዋሪ ተቃውሞ በማስነሳቱና ፖሊሶቹ ላይ ጥቃት በመሰንዘሩ ሲሆን ግጭቱ ወደ ሌላ ቀበሌ ተዛምቶ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል። ቀኑን ሙሉ የአውቶማቲክ መሳሪዎች እና የፈንጅዎች ድምጽ ሲሰማ የዋለ እንደነበርም የአይን እማኞች ገልጸዋል።  የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ ለመወዳደር ለምርጫ እቀርባለሁ ካሉበት ካለፈው ሚያዚያ ወር ጀምሮ በአንድ በኩል  መንግስት የጸጥታ ኃይሎችና ታጣቂ ቡድኖች  በሌላ በኩል  በመንግስት ተቅዋሚ  ኃይሎች መካከል ሲካሄዱ በቆዩ ግጭቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ መሰደዳቸው ይታወቃል።

 

Ø የሱዳን መንግስት ሁለት የታወቁ የኮንግረስ ፓርቲ አባላትን ከአገር እንዳይወጡ የከለለከ መሆኑ ታወቀ። ለበሽር መንግስት ጠንካራ ተቃዋሚ የሆነው የኮንግሬስ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አብዱል ጋይም ባዱር ቅዳሜ እለት በአውሮፕላን ወደ ካይሮ ለመጓዝ  ሲሞክሩ ከመውጣት የታገዱ ሲሆን ሲዲቅ ዩሱፍ የሚባሉ ሌላው የፓርቲው ባለስልጣንም እንደዚሁ በሌላ አውሮፕላን ወደ ካይሮ ለመሄዱ ሲሞክሩ ታግደዋል። ሁለቱ ሰዎች የሚወጡት ሌሎች የተቃዋሚ ኃይል መሪዎችን በካይሮና በፓሪስ ለመገናኘት እንደነበር ተገልጿል። ላለፈው 25 ዓመታት ስልጣን ጨብጠው የሚገኙት አል በሽር ወታደሩን ተገን በማድረግ ያካሄዱት አፈና የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን አድክሞ ይገኛል።  

 

Ø በደቡብ ምስራቅ ናይጀር በምትገኘው ዲፋ በተባለች ከተማ በሁለት አካባቢዎች በፈነዱ ቦምቦች አራት አጥፍቶ ጠፊዎች፣ አምስት ሰላማዊ ሰዎችና አንድ የፖሊስ አባል በድምሩ አስር ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል።  ቦምቡን ያፈነዱትና የተገደሉት አራት አጥፍቶ ጠፊዎች የቦኮሃራም አባላት መሆናቸው ፖሊስ የገለጸ ሲሆን ዓላማቸው በወታደሩ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ነበር ብሏል። በፈንጅው የቆሰሉ ሰዎች በህክምና እየተረዱ መሆናችውም ተገልጿል። ናይጀር ከሌሎች የምዕራብ አፍሪካ አገሮች ጋር በመሆን በቦካ ሃራም ላይ ጥቃት የሚፈጸም ጥምር ኃይል ካቋቋመችበት ጊዜ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ ቦኮሃራም ጥቃቱን አጠነክሮ በርካታ ሰዎች መግደሉ ይታወሳል።

በተያያዘ ዜና ባለፈው አርብ በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ አቅራቢያ ፈንድተው ከ18 በላይ ሰዎችንና የገደሉትንና ከ41 ሰዎች በላይ ያቆሰሉትን ፈንጅዎች በማፈንዳትና ጥቃቱን በመፈጸም በኩል ቦኮ ሃራም ኃላፊነቱን የወሰደ መሆኑን ገልጿል።  የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ቡሃሪም እሁድ ዕለት ወደ ቦታው በመሄድ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች አግኝተው ሲያበረታቱ መቆየታቸውንና  የህክምና ወጭአቸውንም መንግስት እንደሚሸፍነው ቃል የገቡላቸው መሆኑ ተነግሯል።

 

 

Ø በደቡብ አፍሪካ በማዕድን ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል ሲካሄድ በነበረው የክፍያ ድርድር ላይ ስምምነት ሊደረስ ባለመቻሉ 30 ሺ የሚሆኑ የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሰራተኞች ከእሁድ ጅምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ የሚያደርጉ መሆኑ ተገለጸ። ናሽናል ዩኒየን ኦፍ ማይን ዎርከርስ (National Union of Mine workers) የተባለው የሰራተኞቹ ማህበር ድርጅት መሪዎች ማህበሩ  እዚህ ውሳኔ ላይ ሊደርስ የቻለው ድርድሩ የትም ሊደርስ ስላልቻለ ነው ብለዋል። ማህበሩ ለሰራተኞቹ ከ13 እስከ አ14 ከመቶ የደሞዝ ጭማሪ የጠየቀ ሲሆን ከሶስት ወር ድርድር በኋላ አሰሪዎቹ ለመክፈል የተስማሙት የዚህን ግማሽ ብቻ መሆኑም ተገልጿል። የስራ ማቆም አድማው የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚን ሊጎዳ ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለ።

 

Ø በተመሳሳይ ዜና ላለፉት አምስት ሳምንታት ስራ አቁመው የነበሩ የኬኒያ መምህራን አንድ የኬኒያ ፍርድ ቤት በቅርቡ ያስተላለፈውን ትእዛዝ በመቀበል ወደ ስራ ገበታቸው የተመለሱ መሆናቸውና በዚህም ምክያት በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኬኒያ ተማሪዎች ትምህርት የጀመሩ መሆናቸው ታውቋል።  በ90 ቀናት ውስጥ ጉዳያቸውን ተነጋግረው በስምምነት እንዲጨርሱና እስከዚያው ድረስ አስተማሪዎቹ የስራ ማቆም አድማውን አቁመው ወደ ስራቸው እንደሚለሱ የሚለውን የፍርድ ቤት ውሳኔ የኬኒያ መምህራን ማህበር የሚያከብር መሆኑን ጠቅሶ በዚህ ሶስት ወር ውስጥ  የደምዝ ጭማሪ ጥያቄው በመንግስት በኩል በስራ ላይ የማይውል ከሆነ  መምህራኑ እንደገና ስራ ለማቆም የሚገደዱ መሆናቸውን  ገልጿል።

 

Ø የጊኒ ሁለተኛ ከተማ በሆነችው እንዜሬኮሬ በተባለችው ከተማ በተጻራሪ ቡድኖች መካከል ግጭት ተፈጥሮ ጉዳት በመድረሱ የሰዓት እላፊ አዋጅ የታወጀ መሆኑ ተገለጸ። በሚቀጥለው እሁድ ሊካሄድ የታቀደውን ብሔራዊ ምርጫ አስመልክቶ በድጋሜ የሚወዳደሩት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርገው ከሄዱ በኋላ በፕሬዚዳንቱ ደጋፍዎችና ተቃዋሚዎች መካከል በተነሳ ግጭት አንድ ሰው ሲሞት ከ80 በላይ ሰዎች  የቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል።

 

መስከረም 22  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø  

Ø ትናንት አርብ ከናይጄሪያ ዋና ከተማ ከአቡጃ ወጣ ብለው ባሉ ቦታዎች ላይ ሁለት ቦምቦች ፈንድተው 15 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውና በርካታ መቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል። አንደኛው ቦምብ የፈነዳው ከአቡጃ 40 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ኩጄ ከተባለ ቦታ ከአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ ሲሆን 15 ሰዎች መሞታቸውና በርካታ መቁሰላቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ጊዜ የፈነዳው ሁለተኛ ቦምብ ደግሞ ኒያና በተባለ ቦታ ከአንድ የአውቶቡስ ማቆሚያ ላይ ሲሆን በፍንዳታው ሁለት ሰዎች ሞተዋል፣ ሌሎች ቆስለዋል። ለዚህ እኩይ ተግባር ኃይላፊነቱን እስካሁን የወሰደ ባይኖርም የቦኮሃራም ታጣቂዎች ስራ እንደሆነ ተገምቷል። ቦኮ ሃራም ከዚህ በፊት አቡጃን ያጠቃ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ በፊት ትኩረቱ በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ የምትገኘውና የቦርኖ ክፍለሃገር ዋና ከተማ በሆነችው በማይዱጉሪ ላይ እንድነበር አይዘነጋም። ባለፈው ዓመት ኒያና በተባለው ቦታ በፈነዳ ቦምብ ምክንያት ዘጠና ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል። ቦኮ ሃራም እንቅስቃሴውን  በ2002 ዓም ከጀመረ ወዲህ  ከ17 ሺ ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል። ባለፈው ሐሙስ በደቡብ ምስራቅ ናይጀርም የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በናይጀር ወታደሮች ላይ ደፈጣ አካሄደው ሁለት ወታደሮች መግደላቸውና ሰባት መቁሰላቸው ተነግሯል።

 

Ø የቀድሞ የናይጀሪያ የነዳጅ ሚኒስትር የነበሩት ሚስስ ዲየዛኒ አሊስን ለንደን ውስጥ መታስራቸው ተነገረ። ወይዘሮዋ ከ 2002 ዓም እስከ 2007 ዓም ድረስ የናይጄሪያ የነዳጅ ሚኒስትር የነበሩ ሲሆን በሃላፊነት ላይ በነበሩበት ወቅት ከነዳጅ ሽያጭ ገቢ  20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር መሰረቁ ተገልጿል። ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ገንዘቡ መጉደሉን ያጋለጡት ሳኑሲ ላሚዶ የሚባሉ የናይጄሪያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ሲሆኑ ሴትየዋ እጃቸው የሌለበት መሆኑን በወቅቱ ገልጸው እንደነበር ይታወሳል። የብሔራዊ ወንጀል ክፍል የተባለው ተቋም በቅርቡ  ዓለም አቀፍ የሙስና ወንጀለኞችን የሚከታተል ቡድን ያቋቋመ መሆኑን ገልጾ አምስት ሰዎችን የያዘ መሆኑን አስታውቋል። የተያዙት ሰዎች እነማን እንደሆኑ  ተቋሙ ባይገልጽም የሚስስ ዳይዛኒ አሊሰን ቤተሰቦች ሴትየዋ በዚሁ ተቋም መያዛቸውን ተናግረዋል። በቅርቡ የተመረጡት የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ቃለ መሃላ በፈጸሙት በወቅት ከነዳጅ ገቢ   የተሰረቀውን በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ  ለማስመለስ ቃል መግባታቸው ይታወሳል።  

 

Ø የቱኒስያ ባለስልጣኖች ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ሱስ በተባለች ከተማ አሸባሪዎች 38 ቱሪስቶችን በገደሉበት ወቅት አውጀውትና በስራ ላይ አውለውት የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከአርብ እኩለ ሌሊት ጀመሮ ያነሱ መሆናቸውን በመገናኛ ብዙሃን አማካይነት ባስተለለፉት መግለጫ ገልጸዋል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ስልጣን የሰጠ ሲሆን የሕዝብን የመሰብሰብና  ሌሎች የመንቀሳቀስ መብት የሚገድብ ነበር።  ባለፈው ሐምሌ ወር አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለሁለት ወር የተራዘመ ሲሆን በዚሁ ወር የቱኒሲያ ፓርላማ አሸባሪዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ጠንካራ የሆኑ ህጎችን ማጽደቁ ይታወሳል።

 

Ø በደቡብ ሱዳን ዩኒቱ በተባለው ክፍለ ሃገር ካለፈው ሰኞ ጀምሮ እስከ ትናንት አርብ ድረስ በመንግስቱ ወታደሮችና በአማጽያኑ መካከል በተደረጉ ውጊያዎች ከሁለቱም በኩል ጉዳት የደረሰ መሆኑ የመንግስቱ  ወታደራዊ ቃል አቀባይ ለአሶስየትድ ፕሬስ የዜና ወኪል ገልጾ አማጽያኑ ስምምነቱ አፍርሰዋል ሲል ከሷል። ። የአማጽያኑ ቡድን የመንግስት ወታደሮች ይዞዎችን ባጠቃበት ወቅት 14 የመንግስት ወታደሮች ሲገደሉ ሌሎች 42 ቆስለዋል። በሌላ ውጊያ ደግሞ የመንግስት ወታደሮች 38 የሚሆኑ የአማጽያኑን ታጣቂዎችን ሲገድሉ ሁለት የያዙ መሆናቸውና 50 የሚሆኑ የሮኬት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማረኩ መሆናቸው ተገልጿል። የመንግስት ውታደሮች ይዘውት የተባለውን ቦታ ኮችክ የሚባለውን ቦታ በከፍተኛ ውጊያ የለቀቁ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን አማጽያኑ አፐር ናይል በተባለው ግዛት ጥቃታቸው ያፋፍማሉ በማለት ቃል አቀባዩ ተናግሯል። አያይዞም የተደረገውን ስምምነት በማፍረስ አማጽያኑ ጦርነቱን እያፋፋሙ ይገኛሉ የሚል ክስ ያቀረበ ሲሆን ስለ ቀረበው ክስ ከሶስተኛ ወገን ማረገጫ ወይም በአማጽያኑ በኩል መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።  

 

 

 

 

መስከረም 21  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኡማር አል በሽር የሻዕቢያውን የገንዘብ ሚኒስትር ብርሃኔ ሃብተማሪያምን    ሐሙስ ዕለት ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ሱዳን ከሻእቢያው ኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን ገልጸው በሁለቱ አገሮች መካከል እየተደረገ ያለውን ትብብር አመሰግነዋል።  ይህ የበሽር ንግግር ባለፈው ሰሞን ከሻእቢያ ሸሽተው ወደ ሱዳን የገቡትን የወያኔ ተቃዋሚ ኃይል አባላት ሱዳን በማስተናገዷና ወደ ኢትዮጵያ እንዲሄዱ በማድረጓ በሁለቱ አገሮች መካከል የግንኙነት መሻከር ተፈጥሯል የሚለውን ጥርጣሬ አዳክሞታል።  ከጥቂት ቀናት በፊት የወያኔ ባለስልጣኖች በሞላ አስገዶም የሚመሩ ወደ 800 የሚደርሱ ታጣቂዎች የሱዳን መንግስት ተቀብሎና ተንከባክቦ ለኢትዮያ መንግስት ባለስልጣኖች አስርክቧል፤ የሻእቢያ ድንበር ጠባቂዎች የሚከሩትን አደጋ እንዲቋቋሙ አድርጎ ታጣቂዎቹ ምግብና መጠለያ በመስጠት ወደ ኢትዮያ እንዲሄዱ አድርጓል በማለት የወያኔ ባለስልጣኖች የሱዳን መንግስት አመስግነው መግለጫ ማውጣታቸው ይታወሳል። በሽር በሱዳን እና በኤርትራ መካከል የጠነከረ ወዳጅነትና ግንኙነት አለ ብለው በይፋ መናገራቸው  ቀደም ብሎ በተፈጠረ ሁኔታ ምክንያት በሻእቢያና በሱዳን መካከል የግንኙነት መሻከር ተፈጥሯል በማለት የተሳሳተ መደምደሚያ ወስደው የነበሩ ክፍሎችን አስገርሟል። የሻዕቢያው የገንዘብ ሚኒስትር እና  አቻቸው የሱዳን የገንዘብ ሚኒስትር  ስለ ገንዘብ፤ ንግድ፤ ባንክ፤ ቀረጥ፤ ኢንሹራንስ እና ሌሎች ጉዳዮች ሰፋ ያለ ውይይት አድርገው አንዳንድ ስምንንት የደረሱ መሆናቸውን ሱዳን ትሪቡን ገልጿል።

 

Ø ሐሙስ ጠዋት በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ማይዱጉሪ በተባለችው ከተማ አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ አምስት ሴት ልጆች የታጠቋቸውን ቦምቦች በአንድ መስጊድ ውስጥ በማፈንዳታቸው ልጆቹን ጨምሮ 14 ሰዎች ሲሞቱ 39 የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸውን ወታደራዊ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ሴቶቹ የቦኮ ሃራም አባላት ናቸው ተብለው ይጠረጠራሉ። ማይዱጉሪ ቦኮ ሃራም እንቅስቃሴውን የጀመረባት ከተማ ስትሆን በዚህ በዱን በተድጋጋሚ ተጠቅታለች። ከሁለት ሳምንት በፊት በቡድን ተደረገ ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል። ቦኮ ሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረ ጀምሮ 17 ሺ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸው ማጣታተቸውና አዲሱ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ቡድኑ የሚያካሄደውን ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ አይዘነጋም።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ መፈንቅለ መንግስት ያካሄደው ወታደራዊ ተቋም መሪ ጄኔራል ዲየንዴሬ በትናንትናው ዕለት ሸሽተው ተሽሽገውበት ከነበረው ከቫቲካኑ አምባሰደር መኖሪያ ቤት እጃጀቸውን መስጠታቸውና በአሁኑ ወቅት በቡርኪና ፋሶ የጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ያሉ መሆናቸው ተገለጸ። የሚበየንብኝን ፍርድ ለመቀበል ወደ ኋላ አልልም በማለት በተደጋጋሚ ሲናገሩ የቆዩት ጄኔራል በአሁኑ ወቅት በዋና ከተማዋ ማህከል በሚገኘውና ፓስፓንጋ በሚባለው የፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ። የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ  መፈንቅለ መንግስቱን የመሩት ጄኔራል እና ተባባሪዎቻቸው  ለፍርድ የሚቀርቡ መሆናቸውን ገልጾ የመፈንቅለ መንግስቱን ሁኔታ የሚያጣራ ኮሚሽን ያቋቋመ መሆኑ አሳውቋል።  ክዴኢየንዴሬ በተጨማሪ ስድስት ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸው የተገለጸ ሲሆን በግለሰቦቹ  መያዝ በርካታ  ስው ደስታ እርካታ ያገኘ መሆኑ ታውቋል።  አር ኤስ ፒ እየተባለ የሚጠራው የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደራዊ ተቋም በጠቅላላ 1300 አባላት የነበሩት ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 800 የሚሆኑት እጃቸውን ሰጥተው በመከላከያ ተቋም ልዩ ልዩ ቦታዎች የተመደቡ መሆናቸውና  የተቀሩት ደግሞ  እየተፈለጉ ናቸው ተብሏል።

 

Ø በትናንትናው ዕለት የአውሮፓው ኅብረት በአራት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ላይ ማዕቀብ ያደረገ መሆኑ ተገለጸ። የአውሮፓው ህበረት ባወጣው መግለጫ ማዕቀብ የተጣለባቸው ባለስልጣኖች በብሩንዲ ውስጥ ዴሞክራሲ በትክክል ተግባራዊ እንዳይሆን እንቅፋት ሆነዋል ችግሩ ተገቢ መፍትሔ እንዳያገኝ መሰናክሎች የተባሉት ሲሆኑ በግለሰቦቹ ላይ የተጣለው ማእቀብ የጉዞ መከልከል እና በባንክ ያላቸው ሂሳብ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግን የሚያካታት መሆኑ መግለጫው አስታውቋል። በተጨማሪም መግለጫው በብሩንዲ የፖሊቲካ መፍትሔ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት በጣም እየተጓተተና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱንና ወደ ከፍተኛ ደም መፋሰስ እያመራ መሄዱን ገልጾ የፖሊቲካ መፍትሔ እውን እንዳይሆን እንቅፋት በሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ መጣል ግድ ሆኗል ብሏል። መግለጫው ማዕቀብ የተደረገባቸው ግለስቦች ማንነት  ግልጽ ባያደረግም ኤ ኤፍ ፒ የተባለው የዜና ተቋም ዲፕሎማቶችን ዋቤ በማድረግ ባሰራጨው ዜና  የብሩንዲ ብሔራዊ ፖሊስ ምክትል፤ በብሔራው ፖሊስ ጉዳይ የካቢኔ ሚኒስትር፤ የጸጥታ ሰራተኛ እና አንድ የቀድሞ ጄኔራል እንድሆኑ ገልጿል ።

 

በተያያዘ ዜና የብሩንዲው መንግስት ተቃዋሚ ናቸው ለሚባሉ ቡድኖች ሩዋንዳ ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠች ነው የሚል ክስ የብሩንዲ ባለስልጣኖች የከሰሱ መሆናቸው ታወቀ።  ከ70ሺ በላይ የሆኑ የብሩንዲ ስደተኞች ሩዋንዳ በካምፕ ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን ከእነዚሁ መካከል በሩዋንዳ ወታደራዊ ተቋም አሰልጣኝነት  ወታደራዊ ትምህርት እየተሰጣቸው ነው የሚል ክስ የብሩንዲ ባለስልጣኖች ይከሳሉ።   ባለፈው ጊዜ ብሩንዲ ውስጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሙከራ ያደረገው የወታደር ክፍል መሪንና ተባባሪዎቻቸውን ሩዋንዳ እያስተናገደች መሆኑ ግልጽ ሲሆን እነዚህ ሰዎች የሚመሩት ቡድን ወታደራዊ ጥቃት ለመሰንዘር በዝግጅት ላይ ናቸው በማለት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ተናግረዋል። የሩዋንዳ ባለስልጣኖች ብሩንዲ ያለባትን የውስጥ ችግር ለመሸፈን የምታወራው የፈጠራ ወሬ ነው በማለት ክሱን ያጣጣሉ መሆናቸው ተነግሯል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ግንኙነት ውጥረት የተሞላበት ሲሆን በሁለቱም አገሮች ውስጥ ጎሳን መሰረት ያደረገ ተመሳሳይ ውጥረቶች ያሉ መሆናቸው ይታወቃል።

 

 

 

 

 

መስከረም 20  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በኒውዮርክ በመካሄድ ላይ ከሚገኘው የተመድ አመታዊ ስብስባ  ተነስተው ባስቸኳይ ወደ አገራቸው የተመለሱት የማእከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ካትሪን ሳምባ ፓንዛ  ባለፉት ጥቂት ቀናት በአገሪቱ ውስጥ  ብጥብጥ ያስነሱት ቡድኖች  ዓላማቸው መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ነበር ብለዋል። ፕሬዚዳንቷ በብሔራዊ ራዲዮ አማካይነት ለሕዝብ ባስተላለፉት መልእክት ብጥብጡን ያነሳሱት ክፍሎች ፍላጎታቸው አንዱን የሕዝብ ክፍል በተቀነባበረ መንገድ በሌላው ላይ በማነሳሰት የአገሪቱ ሕዝብ በዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል ላይ እንዲነሳ ነበር ብለዋል።   ድርጊቱ  የመፈንቅለ መንግስት ሙኩራ ከማለት ውጭ ሌላ ስም ሊሰጠው የማይችል መሆኑን ገልጸው ሁሉም ታጣቂ ኃይሎች መሳሪያቸውን እንዲያወርዱ ጥሪ አድርገዋል። ሁከቱ በተካሄደበት ወቅት በተደረጉ ሰላማዊ ስልፎች ላይ  “ጊዜያዊ ፕሬዚዳንቷ ከስራቸው ይባረሩ”፤ “የፈረንሳይ ወታደሮችን ጨምሮ  የዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ከአገሪቷ ይውጡ” የሚሉ መፈክሮች ተይዘው የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። ባለፈው ቅዳሜ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ የሆነ  አንድ ታክሲ ነጅ መገደሉን ተከትሎ በተነሳው ግጭት 36 ሰዎች ሲሞቱ ከ30 ሺ ሰዎች በላይ ቤታቸውን እየለቀቁ ተሰደዋል።  በዋናዋ ከተማ በባንጉወየ የታወጀው  የሰዓት እላፊ አዋጅ በተግባር እየዋለ ሲሆን በዛሬው ቀንም በከተማዋ የተረጋጋ ሁኔታ ይታያል። በሚቀጥለው ጥቅምት ወር ሊካሄድ ታቅዶ የንበረው ጠቅላላ ብሔራዊ ምርጫ የተሰረዘ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጿል።

 

Ø በትናንትናው እለት በደቡብ አፍሪካ በፕሪቶሪያ እና በኬፕ ታውን ከተሞች በአገሪቱ ውስጥ እየተስፋፋ የሚገኘውን ሙስና በመቃወም ሰላማዊ ስልፎች የተደረጉ መሆናቸውን በሁለቱም ከተሞች የነበሩ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ደቡብ አፍሪካን የሚመራው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ የነጮችን አገዛዝ አስወግዶ ስልጣን በያዘበት ወቅት ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበት የነበረ ቢሆንም በሃያ ዓመት የአገዛዝ ዘመኑ  ብዙሃኑ ችላ ተብለው ጥቂት ሰዎች ብቻ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል  የሚል ተቃውሞ ከሕዝብ እየተሰማ መሆኑ ታውቋል። በየአንዳንዱ ከተማ ለሰላማዊ ሰልፍ የወጣው ሕዝብ ብዛት ወደ 2000 ገደማ ቢሆንም እንቅስቃሴው እያደገ ሊሄድ እንደሚችል አደራጆቹ ገልጸዋል። በሰልፉ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ የሰራተኛ ማህበሮች መሪዎችና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለረጅም አመታት የመንፈስና የእምነት መሪ በመሆን ሲታገሉ የነበሩት ዴዝመንድ ቱቱ ሰልፉን የደገፉት መሆኑን ቢገልጹም በህመም ምክንያት በቦታው ሳይገኙ ቀርተዋል። በሰልፉ ላይ “ ሙስና በደሃው ላይ የተጫነ ቀረጥ ነው”  እኛ ሀብታሞች ታክስ ይክፈሉ እንላለን” “ አፓርታይድ ታሪካችንን ሲሰርቅ ሙስና ደግሞ ተስፋችንን ሰረቀ የሚሉ መፈክሮች ታይተዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚታየው የሙስና መጠን ብዞዎችን አሳስቧል። የወጣት ስራ አጥ  ቁጥር 50 ከመቶ በደረሰበትና የኢኮኖሚ እድገቱ ወደ 2 ከመቶ ዝቅ ባለበት ሁኔታ  የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዙማ 24 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት መኖሪያ ቤታቸውን ለማሻሻል ማቀዳቸው በርካታ ዜጎችን ያስቆጣ መሆኑ ታውቋል።  ማክሰኞ ዕለት የጃፓኑ ኩባንያ ሂታቺ በአገሪቷ ውስጥ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ለመስራት ለአገሪቱ ባለስልጣኖች የማይገባ ጉቦ ከፍሏል በሚል አሜሪካ ያቀርበቸውን ክስ የደቡብ አፍሪካ ባለስልጣኖች ያስተባበሉ መሆናቸውም ተገልጿል። የጸር ሙስናው ሰልፍ ከአስራ አምስት ቀን በኋላ በተጠናከረ መንገድ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

 

Ø በናይጄሪያ የነዳጅ ዘይት በማውጣት ላይ የሚገኘው የሼል ኩባንያ ነዳጁ የሚጓጓዝበት ቱቦ ላይ ብልሽት በማጋጠሙና ነዳጅ ባልሆነ መንገድ በመፍሰሱ ምክንያት የነዳጅ ማውጣት ስራውን ለጊዜው ያቋረጠ መሆኑን ገልጿል። ኩባንያው በቀን 400 ሺ በርሚል ድፍድፍ ዘይት ያወጣ ስለነበር ስራውን ማቋረጡ በናይጄሪያ ኢኮኖሚ ላይ በቀላሉ የማይገመት ጉዳት ሊያመጣ ይችላል ብለው ታዛቢዎች ይተቻሉ። ናይጄሪያ በቀን 2 ሚሊዮን በርሚል ድፍድፍ ዘይት የምታመርት ሲሆን ይቋረጣል የተባለው የአገሪቱን አንድ አምስተኛ መሆኑ ነው። ከዚህ በፊት የነዳጁ ቱቦ ከመሃል እየተከፈተ ነዳጅ እንደሚሰረቅ እና እንዲሁም ነዳጁ አለአግባብ ፈስሶ አየሩን እንደሚበክል በመግለጽ የሼል ኩባንያ በተደጋጋሚ ቅሬታ ያሰማ ቢሆንም ሁኔታውን ለመቀልበስ የተወሰደው እርምጃ አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል። በአመት 6 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ድፍድፍ የነዳጅ ዘይት ከናይጀሪያ በስርቆት እንድሚዘረፍ ተገምቷል።

 

Ø የፍልስጥኤም ባለስልጣን ፕሬዚዳንት ሙሐሙድ አባስ  በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመታዊ ጉባዔ ላይ ንግግር ካደረጉ  በኋላ የአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ለመጀመሪያ ጊዜ ኒውዮርክ በሚገኘው በተመድ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሌሎች አገሮች ሰንደቅ ዓላማዎች ጎን እንዲውለበለብ ተደርጓል። ትናንት ረቡዕ መስከረም 19 ቀን በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ ሰባት ሰዓት  በተደረገው ስነስርዓት ላይ ፕሬዚዳንት አባስ ባደረጉት ንግግር ቀኑ ታሪካዊ ቀን መሆኑን ገልጸው የአገራቸውን ነጻነት ለማስከበር ህይወታቸውን ለሰጡትና  ለታሰሩት ማስታወሻ ይሆናል ብለዋል። ዌስት ባንክ እየተባለ በሚጠራው የፍልስጥዔም ግዛት በምትገኘው በራማላህ ከተማ በርካታ ፍልስጥኤማውያን በትልቅ የተሌቪሽን ስክሪን ስነስርዓቱን ተከታትለዋል። በ2005 ዓ.ም. የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ፍልስጥኤምን በታዛቢነት ደረጃ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል እንደትሆን የወሰነ መሆኑና በጳጉሜ 5 ቀን 2007 ዓ.ም ደግሞ የፍልስጥኤም ሰንደቅ ዓላማ በቅጥር ግቢው እንዲውለበለብ መወሰኑ ይታወሳል።

 

Ø ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ ተሞክሮ የነበረውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ ትናንት የአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት የጀመረውን በኃይል መስርያ ማስፈታት እርምጃ በመሸሽ  በአገሪቱ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ወደሚገኘው ወደቫቲካን ኤምባሲ ሄደው ጊዜያዊ መጠጊያ የጠየቁ መሆናቸው ታውቋል። ከቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ጋር እጃቸውን ስለሚሰጡበት ሁኔታ እየተወያዩ መሆናቸው ተገልጿል። ጄኔራል ዲየንዴሬ ከተደበቁበት ሆነው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ “እኔ እጄን ሰጥቸ የሚሰጠኝን ፍርድ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ” “የቡርኪና ፋሶ ሕዝብ የተደቀነበትን ችግር በውይይት እንደሚፈታ እምነቴ ነው”፣ “ቡርኪና ፋሶ ሁሉን የሚያካትት መፍትሔ ያስፈልጋታል” ብለዋል።  የአገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት በትናንትናው ቀን ባደረጉት ንግግር የአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት የወሰደውን እርምጃ ካመሰገኑ በኋላ የአገሪቱ ልዕልናና ክብር በአስተማማኝ ደረጃ ላይ ያለ መሆኑን ገልጸው ለቡርኪና ፋሶ አዲስ ምዕራፍ መጀመሩን አብስረዋል። አር ኤስ ፒ የተባለው የፕሬዘዳንቱ ጠባቂ  ወታደራዊ ቡድን አባላት ቀደም ብሎ ተደርጎ የነበረውን ስምምነት በመጣስ  መሳሪያ አንፈታም በማለታቸው  በትናንትናው ቀን የአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት በኃይል ለማስፈታት እርምጃ መውሰዱ ይታወሳል። የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ሕዝቡ በእነዚህ ወታደሮች ላይ ቂም እንዳይዝ የተማጠነ ሲሆን ብዙዎች የክፍሉ አባላት ከሌላው ወታደር ክፍል ጋር እንዲቀላቀሉ የሚደረጉ መሆኑን ቃል ሰጥቷል ።   

 

 

 

 

 

 

መስከረም 19  ቀን 2008 ዓ.ም

Ø በትናንትናው ዕለት የቡርኪና ፋሶ መከላከያ ሰራዊት አር ኤስ ፒ (RSP) እየተባለ በሚጠራው  እና የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ በሆነው ወታደራዊ ተቋም ጦር ሰፈር ላይ  ጥቃት በማድረስ ካምፑን የተቆጣጠረ  መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዜና ይገልጻል። የደረሰው ጉዳት በውል ባይታወቅም የቀላልና የከባድ መሳሪያ ድምጽ ሲሰማ የዋለ መሆኑ ተነግሯል። መከላከያ ሠራዊቱ ይህንን እርምጃ የወሰደው የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ የሆነውና ከጥቂት ቀናት በፊት መፈንቅለ መንግስት አካሂዶ የነበረው ወታደራዊ ተቋም  በተደረገው ስምምነት መሰረት የታጠቀውን መሳሪያ ለመፍታት ፈቃደኛ ሆኖ ባለመገኘቱ ነው ተብሏል። የቡድኑ መሪ ጄኔራል ዲየንዴሬ ካልታወቀ ስፍራ ላይ ሆነው ኤፍፒ ለተባለው የዜና ምንጭ በሰጡት ቃለ ምልልስ የደም መፋሰስ እንዳይኖር ወታደሮቻቸው እጃጀቸውን እንዲሰጡ የገፏፏቸው መሆኑን ገልጸው መከላከያ ሰራዊቱ በወሰደው እርምጃ በርካታ ወታደሮች ሳይሞቱ እንዳልቀሩ ተናግረዋል። ዲየንዴሬ ወታደሮቹ እና የወታደሮቹ ቤተ ሰቦቹ በካምፑ ውስጥ እንደነበሩ  ይናገሩ እንጅ የአገሪቱ መከላከያ  ሰራዊት ዋና አዛዥ ጄኔራል ፒንግሬኖማ ዛግሬ በሰጡት መግለጫ ካምፑን የተቆጣጠረው ሰራዊት በቦታው ምንም ሰው እንዳላገኘ ተናግረዋል። እሮብ ጠዋት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በዋናው ከተማዋ “ኡአጋ 2000” እየተባለ በሚጠራው ቀበሌ በብዛት ሆነው ፍተሻ ሲያካሄዱ የታዩ ሲሆን ያልተያዙ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደሮችን እየፈለጉ መሆናቸውን ተገልጿል።

 

Ø በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለመጭው ጥቅምት ወር ታቅዶ የነበረው ብሔራዊ ምርጫ የተሰረዘ መሆኑን በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስበሰባ ላይ የነበሩትና ሰሞኑን በተፈጠረው ሁኔታ ባስቸኳይ ወደ አገራቸው የተመለሱት የአገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ካትሪን ሳምባ ፓንዛ ገልጸዋል። ባለፈው ቅዳሜ አንድ ታክሲ ነጅ መገደሉን ተከትሎ በክርስቲያን እና በሙስሊም ቡድኖች መካከል በተነሳው ግጭት ምክንያት ሰላሳ ስድስት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ቢያንስ 10 ሺ የሚሆኑ ሰዎች ከአካባቢያቸው ሸሽተው ወደ ሌላ ስፍራ የሄዱ መሆናቸው ይታወቃል፡፤ ጸጥታውን ለማረጋጋት ባለስልጣኖቹ የሰዓት እላፊ አዋጅ አውጀዋል። አገሪቷ ባሁኑ ወቅት ውጥረት የስፈራባት ሲሆን  በ2005 እና በ2007 ወደነበረው የግጭትና የደም መፋሰስና ሁኔታ ውስጥ ልትገባ ትችላለች የሚል ስጋት ሰፍኗል።  የአገሪቷ ጊዚያዊ መንግስት የአገር ውስጥ ሚኒስትር  መንግስታቸው ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማድረጉን ቢገልጹም በአገሪቱ ውስጥ ሊፈነዳ የሚችል ከፍተኛ ውጥረት መኖሩን አልሸሸጉም። የጊዜያዊ መንግስት ፕሬዚዳንት ካትሪን ግጭቱ እንዲፈጠር በመቀስቀስና ሁኔታውን በማባባስ በኩል የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቦዚዜ እና ተከታዮቻቸው ቁል ሚና ተጫውተዋል በማለት ከሰዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቦዚዜ በሚቀጥለው ምርጫ እንዳይሳተፉ በመከልከላቸው ቅሬታ ያላቸው መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል።

 

Ø ላለፉት 21 ወራት በደቡብ ሱዳን ውስጥ ሲካሄድ በቆየው  የእርስ በርስ ጦርነት የተፈጸመውን  ወንጀል መርምሮ ፍርድ የሚሰጥ አካል ያቋቋመ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ገለጸ። እርምጃው ለአፍሪካ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት ነው ተብሏል። ፍርድ ቤቱ እንዲቋቋም የተደረገው የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኬር እና የአማጽያኑ መሪ ሬክ ማቻር አዲስ አበባ ላይ በፈረሙት ስምምነት መሰረት ሲሆን መቋቋሙ የተገለጸውም ሰሞኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓመታዊ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ወቅት በተካሄደው የደቡብ ሱዳን ጉዳይ ስብሰባ ለይ ነው።  በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ መሞታቸውና ከ2.2 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቤቱን ጥሎ መሰደዱ ይታወቃል። በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት በኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ሊቀመንበርነት ባለፈው ዓመት የተቋቋመው መርማሪ ኮሚቴ በደቡብ ሱዳን ግጭት በርካታ ግድያዎች፤ የማሰቃያ ምርመራዎች፤ ዝርፊያዎች እና የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች መፈጸማቸውን ያረጋገጠ ሲሆን የጅምላ ግድያ መድረጉን ግን መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን  ልዩ ፍርድ ቤት መቋቋሙን ደግፈው በጦርነቱ ምክንያት የተካሄደውን ወንጀል ለማካካስ ፍትህና ተጠያቂነትን ተግባራዊ ለማድረግ ይረዳል ብለዋል፡፤   

 

Ø በቲምበክቱ የሚገኘውን ታሪካዊ ቦታ በማቃጠልና በማጥፋት የተወነጀለው አህመድ አልፋህኪ አልማህዲ የተባለ የእስላማውያን አክራሪ ቡድን አባል ረቡዕ ዕለት ሄግ በሚገኘው  ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበ መሆኑ ተገለጸ። አልማህዲ የተከሰሰው ከሶስት ዓመት በፊት በማሊ ቲምበክቱ የሚገኘውን ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎችና እንዲሁም  መስጊዶች በማቃጠልና በማጥፋት ወንጀል መሆኑ ተገልጿል። በቲምበክቱ የሚገኘው ታሪካዊ ቦታ በዓለማችን ውስጥ ካሉ ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎች ውስጥ አንዱ ነው  ተብሎ በዪኔስኮ የተመደበ ስፍራ ሲሆን የዛሬ ሶስት ዓ.ም. በቦታው ከሚገኙ 16 ታሪካዊ ቦታዎ ውስጥ 14 ቱ ላይ ወረራ በማካሄድ  የእስላማውያን አክራሪ ድርጅት አባሎች እነዚህን ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎች ማቃጠላቸው ይታወሳል። የተቃጠሉት የተደረመሱት 14 ታሪካዊ ቦታዎች  በዮኔስኮ እንደገና ታድሰዋል። ከአልማህዲ ጋር ግብረ አበር በመሆን ወንጀሉን የፈጸሙት እስካሁን አልተያዙም።   ፍርድ ቤቱ መስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠውም  የመያዥ ትእዛዝ መሰረት የናይጀር መንግስት አልማህዲን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ወደ ሄግ የላከው መሆኑ ተዘግቧል።

 

መስከረም 18  ቀን 2008 ዓ.ም

 

 

 

 

 

 

 

 

   

 
 
 
 
 
 
 
 
 





 
Click below to Listen Live(በቀጥታ ያዳምጡ!) on your PC, Mac computers/Android, I phone or Windows phones!
        


        



Android (google)
Winamp (pc)
Windows Media (pc/win phones)
Real Audio (pc/mac with real audio)
QuickTime (mac/iphone)
iTunes(mac/iphone}
  

Satellite Frequency Information:

Channel Name: Finote Democracy
Satellite:
Nilesat
Azimuth:
 7 deg West
Frequency:
11,595 MHz
Polarization:
Vertical
Symbol Rate:
27500
FEC :
3/4


Listen Live via Phone #s:
1-401-347-0405 or 1-401-347-0175


ዜና ዘገባ (pdf)




ዝግጅት ክፍል ሀተታዎች(pdf)


















































































 
     
 


Copyright
Finote.org Since 2000.
Send us your comments, news, submissions or contributions to efdpu@aol.com