yekatit 2
Ø
በትናንትናው ዕለት በእስራዔል አገር የሚገኙ በርካታ ትውልደ
ኢትዮጵያውያን በሀምሌ 2006 ዓም
የሴፍ ሳላምሳ ለተባለው ዜጋ ህይወት መጥፋት ምክንያት ነበር
የተባለው የፖሊስ አባል በወንጀል እንዳይከሰስ የእስራኤል ባለስልጣኖች ያደረጉትን ውሳኔ
በመቃወም ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ መሆናቸው ታውቋል።
በሰልፉ ላይ በነበረ ግጭት ከስምንት ሰዎች
በላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተነግሯል። የዛሬ ሁለት ዓመት
ዮሴፍ ሳላምሳ ራሱን ለማጥፋት ምክንያት የሆነው ቀደም ብሎ ፖሊስ ዮሴፍን በቁጥጥር ስር ለማድረግ የኤሌክትርክ ንዝረት የሚረጭ
መሳሪያን በመጠቀም ራሱን እንዲሰት ስላደረገው ነው የሚል ማስረጃ ቢኖርም አቃቤ ህጉ ፖሊሱ በወንጀል እንዳይከሰስ የወሰነ መሆኑ
ታውቋል።፡
በተያያዘ ዜና የዛሬ ሁለት ዓመት ወደ ጋዛ ዘልቆ የነበረ የእስራኤል ዜግነት ያለው
ትውልደ ኢትዮጵያዊ እስካሁን ድረስ መዳረሻው የጠፋ በመሆኑ በሃማስ
ቁጥጥር ስር ሳይሆን አይቀርም ተብሎ ተገምቷል። አበራ መንግስቱ የአይምሮ
በሽተኛ የሆነ ትውልደ ኢትዮጵያ ነው የተባለ ሲሆን በ2006 ዓም ወሰን አቋርጦ ወደ ጋዛ ከገባ በኋላ የት እንደደረሰ
አልታወቀም። የአበራ መንግስት የቅርብ ዘመዶች ጄኔቫ ድረስ በመዝለቅ ግለሰቡን ለማስለቀቅ የዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ጋዛን
በሚያስተዳድረው በሃማስ ላይ ተጽእኖ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
አያይዘውም አበራ መንግስቱ ወታደር ሆኖ የማያውቅ የአእምሮ በሽተኛ በመሆኑ ሊለቀቅ ይገባል ብለዋል።
አበራ መንግስቱ ጥቁር በመሆኑ የእስራኤል መንግስት እስካሁን ድረስ
ጉዳዩን ችላ ብሎታል በማለት በርካታ ወገኖች የሚያቀርቡትን ክስ ዘመዶቹ አስተባብለዋል።
Ø
ሰኞ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓም በናይጀሪያ ከሌጎስ ከተማ አጠገብ
ከሚገኝ አንድ የአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት ውስጥ የታጠቁ ሰዎች ሶስት ልጃገረዶችን ጠልፈው የወሰዱ መሆናቸው
ተነግሯል። ሴት ተማሪዎቹ ተጠልፈው የተወሰዱት ከትምህርት ክፍል
ይሁን ከመኝታ ቤት አልታወቀም። አካባቢው
ጠለፋ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው የተባለ ሲሆን ፖሊሶች ከፍተኛ
ፍለጋ እያደረጉ መሆናቸው ታውቋል። በደቡብ ናይጄሪያ ውስጥ አብኛውን ጊዜ ካሳ ከተከፈለ በኋላ ተጠላፊዎቹ የሚለቀቁ ሲሆን
እነዚህም በፖሊሶች ካልተገኙ ተመሳሳይ ክፍያ በማድረግ ማስለቀቅ ይቻላል የሚል ግምትና ተስፋ ያላቸው በርካታ ናችው። ከጥቂት
ዓመታት በፊት ቺቦክ በሚባለው የሰሜን ናይጄሪያ ከተማ ከ200 በላይ የሚደርሱ በትምህርት ላይ የነበሩ ልጅአገረዶች በቦኮ ሃራም
ተጥልፈው መወሰዳቸው ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ከምትገኘው ማይዱጉሪ ከተማ አጠገብ ጉዎዛ በተባለው ቦታ ባለፈው
ቅዳሜ የካቲት 19 ቀን 2008 ዓም 76 የሚሆኑ ረሃብ ያጠቃቸው የቦኮ ሃራም አባላት እጃቸውን ለባለስልጣኖች የሰጡ መሆናቸውን
የወታደራዊ ቃል አቀባይ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 23 ቀን 2008 ዓም ገልጿል። እጃቸውን ከሰጡት መካከል ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት
ሲሆን ሁሉም በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። እጃቸውን የሰጡትና የተያዙት ይኖሩበት በነበረው አካባቢ ከፍተኛ የምግብ እጥረት
መኖሩን ገልጸው ሌሎች በርካታዎች እጃቸውን ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል። የናይጄሪያ ባለስልጣኖች ባለፉት
መስከረምና ጥቅምት ወራት በርካታ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች እጃቸውን መስጠታችውን መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን በፈቃደኛነት እጅ
የሚሰጡት ታጣቂዎች ትምህርት ከተሰጣቸው በኋላ ወደ ህብረተሰቡ እንዲመለሱ የሚደረጉ መሆናችው ተገልጿል።
Ø
ወደ ፊት እንጓዝ (Go forward) በሚል ስም የሚጠራው የዩጋንዳ
የተቃዋሚ ፓርቲ በዩጋንዳ የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ ውድቅ መሆን አለበት በማለት በአገሪቱ የበላይ ፍርድ ቤት ላይ ክስ የመሰረተ
መሆኑ ታውቋል። ፓርቲውን በመወከል የተወዳደሩት የምርጫው ኮሚሽን አገኙ ካላቸው ድምጽ በላይ ማግኘታቸውን ያረጋገጡ መሆናቸውን
በመዘርዘር ውድድሩ ማጭበርበር የተሞላበት የማስመሳያ ምርጫ ነበር በማለት ድርጅቱ ከሷል።
ከድምጹ 35 ከመቶ አግኝተዋል ተብለው በሁለተኛ ደረጃ እንዲቀመጡ
የተደረጉት የሌላው ፓርቲ መሪ ሚስተር ቢስጌ አሁንም በቤቱ ውስጥ ታግተው ያሉ ሲሆን በፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ ለመንግስቱ የህግ
ሽፋን መስጠት ነው በሚል ምክንያት ጉዳዩን ወደፍርድ ቤት ለመውሰድ አንፈልግም ብለዋል። ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ ቼንጅ የተባለው
ቢሲጌ የሚመሩት ፓርቲ በርካታ አባላት ምርጫው የተጭበረበረ መሆኑን
የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሰብሰው ለፍርድ ቤት ሊያቀርቡ በሚዘጋጁበት ወቅት በድንገት በኡጋንዳ የጸጥታ ኃይሎች
በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል። በርካታ ታዛቢዎች ምርጫው
ማጭበረበር የበዛበት፤ ገለልተኛነት እና ግልጽነት የጎደለው፤ ከፍተኛ ማስፍራራትና የኃይል እርምጃ የነበረበት
በመሆኑ ተአማኒነትና ተቀባይነት አይኖረውም ብለዋል።
የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ለአራት ወራት የቀጠለውን የሕዝብ ተቃውሞና ቁጣን ለማስታገስ የወያኔ
መሪዎች የራሳቸውን ከፍተኛ ካድሬዎች መስዋዕት በማድረግ ከስልጣንና ከኃላፊነት በማባራር ድርጅታዊ ብወዛ መጀመራቸው ታውቋል።
በዚህ መሠረት የወያኔው ኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበረው ዳባ ደበሌ ከስልጣኑ ተነስቶ የተባረረ ሲሆን በምትኩ
በወያኔው ኦህዴድ ውስጥ ታማኝነቱ አያጠራጥርም የተባለው በከር ሻሌ ተመድቧል። ከዚህ ቀደም በከር ሻሌን በጉምሩክና
ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ውስጥ ይሰራ እንደነበር ታውቋል። በናዝሬት ለተወሰነ ጊዜ ከንቲባ እንደነበረ ተገልጿል። የወያኔው
መሪዎች በኦህዴድ ውስጥ ከስራ የማገድ የማባረርና የማዛወር ሥራን በሰፊው ያካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ በዚህ እንዳለ ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም የጤና ድርጅት ሀላፊ
በመሆን
ለመመረጥ
ፍላጎት እያሳየ ስለሆነ ግለሰቡ ኃላፊነቱን ከለቀቀ
የደቡብ ህብረቱ
ዮናስ
ዮሴፍ እንዲተካው ሀይለማርያም ደሳለኝ እየለመነለት ነው ተብሏል።
Ø
የወያኔ ቡድን መሪዎች በአዲስ አበባ ታክሲ ሹፌሮችና ማህበራት ላይ
ያወጡትን ህግን ተከትሎ በትናንትናው ዕለት የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመደረጉ የወያኔ የትራንስፖርት ባለስልጣኖች የህጉን
ግንዛቤ ማስጨበጫ ጊዜ ለማራዘም በሚል ህጉ እስከሚቀጥሉት ሶስት ወር ድረስ ተባራዊ እንዳይሆን መወሰናቸው ታውቋል። የወያኔው
ትራንስፖርት ባለስልጣኖች ያወጡትን የህግ መዘግየት መግለጫ
ተከትሎ የተወሱን ታክሲዎች በመንገድ ላይ መታየት መጀመራቸው የታወቀ ሲሆን የወያኔ መሪዎች መሰረታዊ የሆነው የታክሲ ሹፌሮችና
ማህበራቱን ጥያቄ በአግባብብና በትክክለኛ መንገድ እስካለመለሱ ድረስ ትግሉና አድማው በማናቸው ጊዜና ወቅት ሊቀጥል እንደሚችል
ለታክሲ አሽከርካሪዎችና ማህበራት ቅርበት ያላቸው ምንጮች እየገለጹ ነው። ሌሎች ወገኖች ደግሞ የወያኔ ቡድን መሪዎች
ህጉን ለሶስት ወር እንዲዘገይ ያደረጉት በኢትዮጵያ ያለው የፖሊቲካ ትኩሳት እስኪበርድና ትንፋሽ መግዣ ጊዜ ለማግኘት
መሆኑን ጠቅሰው የታክሲ ሹፌሮችና ማኅበራት ይህን ታሳቢ በማድረግ በማናቸውም ጊዜና ሁኔታ አድማቸው ለመቀጠልና መብታቸውን
ለማስከበር ዝግጁ ሆነው መጠበቅ እንዳለባቸው ይናገራሉ። በተያያዘ ዜና የአዲስ አበባ ታክሲ ሹፌሮች አድማን ተከትሎ በሌሎች
ከተሞችና ስፍራዎች የሚገኙ ታክሲዎችና ባጃጆች የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ ሲሆን ይህም ሆለታንና
ሰላሌና አርሲ እንደሚጨምር ታውቋል ታውቋል። በናዝሬት
የወያኔ ኦህዴድ ባለሥልጣኖች የታክሲ ስራ ማቆም አድማ እንዳይዛመት በማለት በማንኛውም መልኩ አድማ ማድረግ አይፈቅድም በማለት
መግለጫ አውጥቷል።
Ø
የወያኔ ቡድን መሪዎች በሁሉም አቅጣጫ የተነሳባቸውን ተቃውሞ ቁጣ
ለማስታገስና የመልካም አስተዳደርና ስራ እየሰራን ነው ለማለት
ከአዲስ አበባ ከተማ በመሬት አስተዳደር ቢሮ ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ስልሳ አንድ ሹሞችን ይዞ ማሰሩን ይፋ አድርጓል። አገዛዙ
ከትናንንት በስቲያ በድንገተኛ መንገድ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሹሞች ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ መሬት እየሸነሸኑ መሸጣቸው
ካርታ እያዘጋጁ በይዞታነት ያረጋግጡ ነበር የሚል ውንጀላ ያለባቸው ሲሆን ከአስሩም ክፍለ ከተማ ውስጥ መያዛቸው ተብራርቷል።
በርካታ የሕግ ባለሙያዎች የሹሞቹ መታሰር የዘገየ መሆኑንና አሁንም ከሹሞቹ ጀርባ የጥቅምና ተካፋይነትና አይዞህ ባይ የወያኔ
መሪዎችና ባለስልጣኖችን ሳይነካ ሹሞቹን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ ፍትሓዊ አሰራር ሳይሆን የሕዝብ ቁጣን ማስተንፈሻ ነው በማለት
ይተቹታል።
Ø
የወያኔ ቡድን መሪዎች ከ 80 በላይ ኢትዮጵያውያን የሆኑ የወርቅ ማዕድን
ፈላጊዎች በሻዕቢያ ታግተዋል በማለት በአስቸኳይ እንዲለቀቁና ካልተለቀቁ
ግን ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን በማለት በኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ
በኩል መግለጫ ከሰጠ ወዲህ ታገቱ የተባሉት ኢትዮጵያውያን የወርቅ ማእድን ፈላጊዎች በነጻ መለቀቃቸውን የወያኔ ኮሚኒኬሽን ቦሮ
ተናግሯል። ይሁን እንጅ የወያኔው ቢሮ ታጋቾች ስንት እንደሆኑና እንዴት እንደተለቀቁ የገለጸው ነገር የለም። የወያኔ አገዛዝ
ከቀናት በፊት ዛቻ አዘል ማስጠንቀቂያና ስለ አጸፋው እርምጃ ይናገር እንጅ ምን ዓይነት የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ አላስታወቅም
ነበር። ለዲፕሎማቶች ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደገለጹት ከሆነ የሱዳን መንግስት ታጋቾቹ እንዲለቀቁና በሱንዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ
እንዲመለሱ የሽምግልና ጥረት ማድረጉን እየገለጹ ሲሆን የሱዳን መንግስት ግን አደረገው ስለተባለው የሽምግልና ጥረት የእምነትም
ሆነ የክህደት ቃሉን አልሰጠም።
Ø
በአዳራሽ ውስጥ የ1500
ሜትር ሩጫ አሸናፊ የነበረችውና ከጥቂት ጊዜ
በፊት በጋብቻ ምክንያት የስዊድን ዜግነት ያገኘችው አበባ አረጋዊ
የአካል
ጥንካሬን
የሚሰጥ ዕጽ መውስዷ በምርመራ ስለተጋለጠ
ከስፖርት
ውድድር ታግዳለች ።
እስካሁን ድረስ
በዚህ መንገደ
የተከሰሰ ከእሷ በቀር
አንድም
ኢትዮጵያዊ
አለመኖሩ ታውቋል።
Ø
የጉጂ
ሕዝብ በ ሼክ አላሙዲ ሚድሮክ የወርቅ ማዕድን ላይ የተቃውሞ ሰልፍ
ሲያደርግ መቆየቱ
በተደጋጋሚ የተገለጠ ሲሆን
ደርባ
የሚገኘው የሚድሮክ ሲሚንቶ ፋብሪካው እንዲሁ
ከፍተኛ
ተቃውሞ አጋጥሞታል ።
ሕዝቡ በሼኩ ላይ ጠንካራ
ተቃውሞውን እየገለጸ ያለው ሼኩ
ለአገሪቱ
መክፈል ያለበትን
በርካታ ገንዘብ ካለመክፈሉ በላይ ሰራተኞችን
በአነስተኛ ክፍያ እየበዘበዘ ነው በሚል
ነው።
ይህ በዚህ እንዳለ ብሔራዊ የዘይት የኢትዮጵያ ኩባንያ የተባለው
የሼኩ ተቋም
በጅቡቲ ያለውን የሊቢያ ኦይል የሚባለውን
ድርጅት
መግዛቱ ተነገሯል።
Ø
የጅቡቲ አምባገነናዊ
አገዛዝ በተቃዋሚዎች ላይ
እያካሄደ ያለው
አፈና የቀጠለ ከመሆኑ በላይ በታጁራህ ታስረው በተለያይ የማሰቃያ መንገዶች ሲሰቃዩ ከነበሩት መካከል
ሁሙድ እስማኤልና አብዶ አህመድ ሞሚን
ሕይወታቸው
ያለፈ መሆኑ ተነግሯል።
ኦቦክ በሚባለው ቦታ ታስረው ከነበሩት መካከል
ኦማን መሀመድ ቦዴ፤አሊ ሁሴን አሊ፤ከድር መሃመድ አይዳሂስ ና መሀመድ አሊ ሃጉስ
በከፍተኛ
ድብደባ
ተሰቃይተው
የሞቱ መሆናቸውን የጅቡቲ የሰብዓዊ መብት ተከላካይ ኮሚቴ ገልጿል
።
Ø
ከጥቂት ቀናት በፊት
ወያኔ ወደ ሶማሊያ ጦሩ መላኩን መዘገባቸን የሚታወስ ሲሆን ይህ ወደ ሶማሊያ የተላከው ውጋግን ሬጅመንት በመባል የሚታወቀው
ጦር በቁጥር 600 መሆኑና የሚመራው በኮሎኔል ታደሰ ወረደ ተስፋዬ በተባለ ግለስበ የሚመራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ጦሩ
የሚሰማራው በደቡብ ሶማሊያ ሲሆን የኪስማዮን ወደብ
ለመጠበቅ ነው ተብሏል።
የወያኔ፤የዩጋንዳና ኬንያ ጦሮች ሽብርተኛ የተባለውን አል
ሸባብን
በማዳከም በኩል ውጤት አግኝተናል ቢሉም
ቡድኑ
ሰሞኑን በሞቃዲስሾ
ጥቃት ሰንዝሮ
በርካታ ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል ።
Ø
ከሰባት ዓመታት በፊት
በደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ላይ ዴሞክራቲ አሊያንስ በሚባለው የተቃዋሚ ቡድን ቀርበው የነበሩት 738 ክሶች በፍርድ
ቤት እንደገና ቀርበው ይታያሉ የሚል ዜና ከሰሞኑ
ተሰምቷል። የፕሬዚዳንቱ ቢሮ ክሱን በጽኑ የሚከላከል
መሆኑን ጠቅሶ በ2001 ዓም በወቅቱ የነበረው አቃቤ ህግ ክሶቹ ወደ ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ማድረጉ ትክክል ነበር
የሚል ማብራሪያ ሰጥቷል። ክሱን ያቀረበው ተቃዋሚ ክፍል ያን ጊዜ የነበረው አቃቤ ህግ በፖሊቲካ ምክንያት ክስ እንዳይመሰረት
አደረገ እንጅ ክሶቹ ትክክል ነበሩ የሚል መከራከሪያ አቅርቧል። ከተዘረዘሩት ክሶች ውስጥ አንደኛው
በወቅቱ የጸጥታ ኃላፊ የነበሩት የአሁኑ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ በብዙ ቢሊዮን ዶላር በተደረገው የመሳሪያ ግዥ
ከፍተኛ የሆነ የጉቦ ገንዘብ ተቀብለዋል የሚል ነው። ዴሞክራቲክ አሊያንስ የተባለው የተቃዋሚዎች ህብረት የአገሪቱ
የታችኛው ምክር ቤት በፕሬዚዳንቱ ላይ እምነት የሌለው
መሆኑን የሚያረጋግጥ ድምጽ እንዲሰጥ የውሳኔ ሀሳብ ያቀረበ መሆኑ ታውቋል። በምክር ቤቱ ከፍተኛ የመቀመጫ ብዛት ያለው የአፍሪካ
ብሔራዊ ኮንግሬስ የተባለው የገዥው ፓርቲ ሲሆን የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ውድቅ ያደርገዋል ተብሎ ይገመታል።
Ø
ሰኞ የካቲት 21 ቀን 2008 ዓም በምስራቅ ኮንጎ
በምትገኝ አንድ መንደር ውስጥ ራሱን “የመከላከያ ኃይል ህብረት”
በሚል መጠሪያ የሚጠራ የታጠቀ ቡድን አባሎች
የመንደሩ ነዋሪ የሆኑትን 12 ሰዎች መግደላቸውን አንድ የሰብአዊ መብት ድርጅት ተቋም ከአካባቢው የአገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ
ገልጿል። መቀመጫቸው በኡጋንዳ ወሰን አካባቢ የሆነው ታጣቂዎች ግድያውን የፈጸሙት
በያዙት ቆንጨራ ሲሆን ምግብና የቤት እንስሳት
ዘርፈው የሄዱ መሆናቸው ተነግሯል።
የካቲት 21 ቀን
2008 ዓ.ም
Ø
ዛሬ በመላዋ አዲስ አበባ የሚገኙ የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ማድርጋቸው ታወቀ። የታክሲ አሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ
የመቱት የወያኔ አገዛዝ የአወጀውን የትራንስፖርትና የመንጃ ፈቃድ ህግን በመቃወም መሆኑ ታውቋል። ወያኔ ባወጣው አዲስ ሕግ
ማንኛውም ሹፌር ለሃያ አንድ ጊዜ ካጠፋ መንጃ ፈቃዱ እንደሚነጠቅ ይደነግጋል። የክፍለሀገር
ባለ አሽከርካዎችም በሥራ ማቆም አድማ ተሳታፊ መሆናቸው ሲታወቅ
አድማውን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት ችግር በአዲስ አበባ ከተማ መታየቱ ታውቋል። የታክሲ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ
የከተማው መነጋገርያ መሆኑ ተገልጿል። ብዙ አስተያየት ሰጭዎች የወያኔ አገዛዝ የአዲስ አበባ ታክስ ሹፌሮችንና ባለንብረቶችን
ከንግዱ ዓለም ለማባረርና በራሱ ድርጅቶችና ዘር አባላትን ለመተካትና የድህንነት አባላቱን ለማሰማራት በማሰብ ያወጣው ዕቅድ
መክሸፉንና የታክሲ ሾፌሮቹ ለሌሎች የኅብረተስብ ክፍል ያስተማሩበት አድማ ነው በማለት አስተያየት ይሰጣሉ።
ወያኔ ሕዝብ መናቅ የባሕርዩ ነውና በቀጥታ የሚመለከታቸውን ባለ ጉዳዮች ሳያማክርና ሕዝብ ሳይመክርበት ህግ ማውጣት ልማድ ብሎ
ይዞታል፡፡ የአዲስ አበባ የትንሿ አውቶብስ (የሚኒ ባስ) ባለንብረቶች ማህበር በየጊዜው እየናረ በመሄድ ላይ ያለው የጎማ፣
የዘይት፣ የመለዋወጫ ዋጋ አሁን ካለው ከታክሲ ታሪፍ ጋር የተመዛዘነ ባለመሆኑ የዋጋ ጭማሪ እንዲደረግ ከሚመለከተው የወያኔ አካል
ጋር ከስምምነት በድረሳቸው እየተገለጸ ባለበት ሾፌሮች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል የተደረገውን የትራፊክ ህግ
በመቃወም ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ሥራ ያቆሙት ባለታክሲዎች ከተማዋን የቀውስ መንደር አስመስለዋት እንደዋሉ በከተማዋ የተለያዩ
አቅጣጫዎች ተዘዋውሮ የነበረው ዘግቢያችን መታዘብ ችሏል፡፡ በከተማዋ ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ከሃምሳ ሺ በላይ ታክሲዎች ሙሉ በሙሉ
የአድማው ተባባሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በከተማዋ ውስጥ ውር ውር ሲሉ የነበሩ ታከሲዎች በአጠቃላይ ግፋ ቢል አንድ ሺ
እንደሚሆኑ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ውስጥ የሚሠሩ ወገኖች ያስረዳሉ፡፡ እነዚሁ ታክሲዎችም ንብረትናታቸው የሙሰኞቹ የወያኔ
ሹመኞች እንደሆኑ በአድማው ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሾፌሮች ያስረዳሉ፡፡ አብዛኛው ሠራተኛ ወደ ሥራ ሲሄድ በእግር ለመሄድ ተገዷል፡፡
ሲመለስ ምሽትም ስለሚሆን በእጅጉ ሕዝቡ አዳጋች ችግር ይገጥመዋል፡፡ ይህ አዲስ የወጣ ህግ የተረቀቀው በወያኔ ካድሬዎች ማለትም
ድንጋይ ማምረቻ እየተባለ ከሚጠራው ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ በወጡና በሥራው ላይ ከሁለት አመት ያልበለጠ ልምድ ባላቸው በመሆኑና
የነሱ የበላይ የሆኑትም በወያኔ ካድሬነት ብልጫ ቢኖራቸው እንጂ በህግ ትምህርት ምንም እውቀት እንደሌላቸው የዚህ ህግ የመረቀቅና
የመጽደቅ ሄደትን አጣርተው የሚያውቁ ያስረዳሉ፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ መካከለኛና ከፍተኛ አገር አቋራጭ አውቶብሶችም ሥራ ማቆማቸው
ታውቋል፡፡ ወያኔ በአድማው በመደናገጡ የወጣው ህግ እስከ ሦስት ወር በሥራ ላይ እንዳይውል መታገዱን ገልጾ ሾፌሮቹ ወደ ሥራ
እንዲመለሱ ለማባበል ያደረገው ሙከራ ሰሚ አላገኘም ፡፡ ወያኔ እራሱም ሆነ የሚያወጣው ህግ በሕዝብ ላይ የሚጫኑና የተጫኑ
በመሆናቸው በኃይል የመወገዳቸው ጀምበር እየቀደደ ለመሆኑ ከዚህ ወያኔን እያራደ ካለው አድማ መረዳት ተችሏል፡፡
Ø
የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ተከትሎ የቀጠለው ሕዝባዊ አመጽ አራተኛ ወሩን እያስቆጠረ ሲሆን የወያኔ ቡድን መሪዎች አመጹን
አቁመናል ንቅናቄውን ገትተናል ይበሉ እንጅ አሁንም ሕዝባዊ ተቃውሞና ቁጣው አንደቀጠለ መሆኑን ከየአካባቢው የሚመጡ መረጃዎች
ያመለክታሉ። እሁድ ዕለት፤ በሐረርጌ ፤ በወለጋ በአርሲና በሸዋ የሚገኙ ልዩ ልዮ ከተሞች ውስጥ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን የወያኔው
ነፍስ ገዳይ አጋዚ ወታደሮችም ወለጋ ውስጥ አንድ ፖሊስ ከሕዝብ ጋር ወግነሃል በማለት የገደሉት መሆናቸው ተዘግቧል። ከዚህም
በተጨማሪ በየከተሞቹ ከሕዝባዊ ተቃውሞችና ቁጣ ጀርባ እጃችሁ አለበት በማለት የልማት ሠራተኞች መምህራን ላይ ወከባ እስርና
የጭካኔ ተግባር እየተፈጸመባቸው መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል
ደግሞ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ከዳባት ከተማ ወደ አዲስ አበባና ወደ መቀሌ ሽሬ የሚወስደው መንገድ በተቃውሞ መዘጋቱ ታውቋል።
ከወልቃይት ሕዝብ ማንነት ጋር በተያያዘና ከሕግ፤ ከባህልና ከታሪክ ውጭ ወልቃይት ወደ ትግራይ መካለለሉን በመቃወም የወልቃይት
ነዋሪና ተወላጆች ተቃውሞ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን ትግሉ ወደ መንገድ መዝጋት ሲሸጋገር ይህ የመጅመሪያው ነው።
Ø
ከአስር ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ድንበሩ ሰላምና ጦርነት አልባ ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ሰሞኑን የወያኔ ቡድን መሪዎች በወርቅ
ማዕድን ፍለጋ ላይ የነበሩ 80 ሰዎች በሻዕቢያ ታግተው ተወስደዋል በሚል የወያኔ መሪዎች የክስ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸው ታውቋል።
የወያኔ ቃል አቀባይ ቀደም ሲል በጉዳዩ ላይ ማስጠንቀቂያ አዘል መግለጫ የሰጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የወያኔ የውጭ ጉዳይ
ሚኒስትር ቃል አቀባይ በበኩሉ ሻዕቢያ የታገቱትን ሰዎች በአስቸኳይ ካለቀቀ ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን በማለት ዝቷል።
የወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የታገቱት ሰዎች ቁጥር 80 መሆናቸውን ይግለጽ እንጅ ቀደም ሲል በወጡት መግለጫዎች የታገሩት
ማዕድን ፈላጊዎች ቁጥር 85 ተብሎ መዘገቡ ይታወቃል። ይህንን የተደጋገመ የወያኔን ማስጠንቀቂያና ዛቻ አስመልክቶ ሻዕቢያ የሰጠው
ይፋ አስተያየት የለም። የፖሊቲካ ታዛቢዎች ግን የወያኔ ቡድን በሀገር ውስጥ በአራቱም ማዕዘን የተነሳበትን ተቃውሞ ለማዘናጋትና
ለማረሳሳት ከሻዕቢያ ጋር እሰጥ አገባ ለመግባትና የጦርነት ከበሮ ለመደብደብ የወሰው የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ትኩሳቱን ለማረሳሳ
በማሰብ መሆኑን ይገልጻሉ።
Ø
ከሃያ ዓመት በላይ በእስር በራሱ ጦርነትና በሽብርተኞች ጥቃት የምትታመሰውን ሶማሊያን ለመታደግ የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ስለማ
አስከባሪ ተልዕኮ እሁድ ዕለት በጅቡቲ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል። በዚህ ስብሰባ ላይ ለሶማሊያው ሰላም አስከባሪ ተልእኮ
ወታደሮቻቸውን ካዋጡት አገሮች በተለይ ኬኒያ ኡጋንዳና ወያኔ በቅርብ የተጀመረው የአልሸባብ ጥቃት እያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የኬኒያ መንግስት በቅርብ በአልሸባብ ጥቃት 200 የሚደርሱ ወታድሮች ከተገደሉ ወዲህ ለሰላም አስካሪው ተልዕኮ ቀጣይነት ቢገልጽም
ተጨማሪ ጦር ማዋጣቱ ግን አጠራጣሪ ሆኗል። የወያኔ ቡድን መሪዎች ለሱማሊያ ተጨማሪ የሰላምና አስከባብሪ ኃይል ለመላክ ፈቃደኛ
መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወቃል። የወያኔ አገዛዝ የአፍሪካ ኅብረት ለሚጠራው የሰላም አስከባሪ ተልእኮ ወታደሮችን በመላክ የውጭ
ምንዛሬ መሰብሰቢያ ብቻ ሳይሆን በጦሩ ውስጥ ያሉትን የራሱን አንድ ዘር አዛዥና ወታደሮችንም መጠቀሚያ ማድርጉ ይታወቃል።
ይህ በዚህ እንዳለ ትናንት የካቲት 20 ቀን 2008 ዓም ባዮዳ በሚባለው የሱማሊያ ከተማ ውስጥ ሁለት ቦምቦች ፈንድተው ጉዳት
መድረሱን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ በፈነዱት ቦምቦች
ከ 30 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውና ከ 60 በላይ የሚሆኑ ቆስለው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል።
ሰዎች ተሰብስበው የአግር ኳስ ውድድር በሚያዩበት አንድ ሬስቶራንት አጠገብ የፈነዳው መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ በሰው
ህይወት ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ሁለተኛው ቦምብ ደግሞ አጥፍቶ ጠፊ በሆነ አንድ ግለሰብ በመንታ መንገድ መገኛኚያ ላይ
ፈንድቷል። ለጥቃቱ አልሸባብ ኃይላፊነቱን ወስዶ መግለጫ
ሰጥቷል። ይህ ባለፉት ሁለት ወራት ለአራተኛ ጊዜ በከተማዋ ውስጥ የደረሰው የቦምብ ፍንዳታ
የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተጠናከረ የመጣውን የአልሸብን ኃይል ለመቋቋም
ወታደራዊ ብቃቱን ለማጠናከር ቃል በገባ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ነው። ከጥቃቱ በኋላ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ
ጠርተው መወሰድ ስላለበት እርምጃ ተወያይተዋል ተብሏል።
Ø
የናይጀሪያ መንግስት ማንነታቸው የማይታወቅና በፈጠራ ስም ሲከፈል የነበረውን ደሞዝ በመሰረዝ በርካታ ገንዘብ ያዳነ መሆኑን
አስታወቀ። የቡሃሪ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች ናቸው ተብለው በደሞዝ መክፈያ ሊስት ውስጥ የነበሩት
24 000 የውሸት ስሞችን የሰረዘ ሲሆን ለእኒዚህ ሰዎች ይከፈላል ተብሎ በየወሩ ይበዘበዝ የነበረውን 15.5 ሚሊዮን
ዶላር ለማስቀረት የተቻለ መሆኑን ገልጿል። አንዳንድ ሰራተኞች በሌሉ ሰዎች ስም በርካታ ደሞዝ የሚቀበሉ መሆናቸው የተደረሰበት
መሆኑና ሌሎች ደግሞ ከሁለት ከሶስት ቦታ ደሞዝ የሚቀብሉ መሆናቸው በምርመራ ተረጋግጧል።
ሙስና በናይጄሪያ ውስጥ በተለያየ መንገድ ስር የሰደደ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ይህንን ለማስቀረት የቡሃሪ መንግስት
ከፍተኛ ጥረት የሚያደርግ መሆኑን ገልጿል።
ቤልጀየም ነዋሪ የነበረ አንድ አልጀሪያዊ ከጥቂት ወራት በፊት ፓሪስ ከተማ ውስጥ ተካሄዶ በነበረው ት በሚል ጥርጣሬ አክቡ
በምትባለው የአልጀሪያ ከተማ በቁጥጥር ስር መደረጉን ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ህዳር 3 ቀን 2008 ዓም በፓሪስ ከተማ በተካሄደው
የሽብር ጥቃት 130 የሚሆኑ ስዎችን መግደላቸው የሚታወስ ሲሆን ጥቃቱን ከፈጸሙት መካከል አራቱ በቤልጀየም ነዋሪ መሆናቸው
ተደርሶበታል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ በየአመቱ 600 000 (ስድስት መቶ ሺ) የሚሆኑ መንገደኞችን የሚያስተናግደው በምዕራብ ኬፕ የሚገኘው የጆርጅ
አውሮፕላን ጣቢይ ከጸሐይ ብርሃን የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጭ መሳሪያ በመትከል እና ስራውን እንዲጀምር በማድረግ ከአፍሪካ
የመጀመሪያ ሆኗል። በአሁኑ ወቅት አውሮፕላን ጣቢያው ከሚያስፈልገው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ አርባ ከመቶ የሚሆነውን
ከዚሁ መሳሪያ የሚያገኝ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በኋላ 100 ከመቶ የሚሆነው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ከዚሁ መሳሪያ ይገኛል ተብሏል።
ከጸሐይ ብርሃን የኤሌክትርክ ኃይል የሚያመነጨውን መሳሪያ ለመትከል አንድ ሚሊዮን ዶላር የፈጀ ሲሆን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሌሎች
አውሮፕላን ጣቢያዎች ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስዱ ይጠበቃል። የኤሌክትርክ ኃይል መሳሪያን በአየር ጣቢያዎች ላይ በመጠቀም ረገድ
ቀዳሚዋ ህንድ ስትሆን ባለፈው ዓመት በኮቺን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ላይ በ9.5 ሚሊዮን ዶላር የተተከለው
መሳሪያ በአይነቱ ከዓለም አንደኛ ነው ተብሏል።
የካቲት 19 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ትናንት የካቲት 18 ቀን እና ዛሬ የካቲት 19 ቀን 2008 ዓም
በተለያዩ ቦታዎች ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ቀጥለው
የዋሉ ሲሆን በምዕራብ እና በምስራቅ ሃረርጌ እንድሁም ምእራብ ሸዋ እና ቦረና አካባቢዎች ተማርዎቹ እና ሕዝቡ የተቃውሞ ሰልፎች
አድርገዋል። በሌላ በኩል እንቅስቃሴዎቹ በሚካሄዱባቸው የወያኔ
በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን አፈና አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በርካታ ዜጎችም የታሰሩ መሆናችው ተዘግቧል። ሶማሊያ
የነበረው ልዩ የአግአዚ ኃይል ወደ ምስራቅ ሃሮሚያ ገብቶ በርካታ ዜጎች ማሰሩን አንዳንድ ምንጮች ዘግበዋል። በተያያዘ ዜና
የወያኔ አገዛዝ የኦሮሚያ አካባቢን በወታደራዊ አስተዳደር ቁጥጥር ስር ለማድረግ ያደረገው ውሳኔ በአካባቢው ለሚገኙ ከፍተኛ
የጦርና የጸጥታው ተቋም መኮንኖች የተነገረ መሆኑ አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል። ውሳኔው የኦሮሚያ አካባቢን በ8 ወታደራዊ ቀጠና
ከፍሎ በዚያ የሚገኘውን የጸጥታም ሆነ የአስተዳደር ኃላፊነት በበላይነት መምራት ነው። በአካባቢዎቹ የሚገኙ የሲቪል አስተዳደሮች
ለወታደራዊ ቀጠና እዝ ታዛዥ እንዲሆኑ ተደርጓል ተብሏል።
Ø
በተመሳሳይ ዜና በወለጋና አካባቢው ላይ በተካሄዱት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ
በርካታ ተማሪዎች በተለያዩ መንገዶች ቅጣት የተፈጸመቫቸው
መሆኑን ከአካባቢው የመጣ ዘገባ ይገልጻል። ተይዘው ክስ የሚመሰረትባቸውና ታስረው የተለቀቁ ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን እንቅስቃሴው
ውስጥ ተሳታፊ ነበራችሁ በሚል ሰብ ብቻ ከትምህርታቸው የታገዱ ተማርዎች ቁጥር በርካታ መሆኑን
ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ከበላይ በመጣ
ትዕዛዝ መሰረት የወለጋ የሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት ርእሳነ መምህራን ተማሪዎቹ ከትምህርት እንዲታገዱ ውሳኔ
ያስተላለፉ ሲሆን ተማሪዎቹ በየትኛውም ትምህርት ቤት እንዳይማሩ የተደረገ መሆኑ ታውቋል።፡ በታዘዙት ድርጅታዊ ትእዛዝ መሰረት
መወሰኑን ከነቀምት የተገኘ መረጃ አስረድቷል።
Ø
አረና በመቀሌ ከተማ
የጠራው ሰልፍ የታገደ መሆኑን ከድርጅቱ አካባቢ የተገኘው ዜና ይገልጻል። አረና በኤርትራ ስለጠተለፉት ዜጎች፣ በኦርሚያ አካባቢ
እየተካሄደው ስላለው ሕዝባዊ ተቃውሞ እና እየተደረገ ስላለው ግድያ እና አፈና፤ ሰለ ህግ የበላይነት እንዲሁም
ስለድርቅ ጉዳዮች አስመልክቶ ድምጽ ለማሰማትና መልእክት ለማስተላለፍ ለየካቲት 20 ቀን 2008 ዓም በመቀሌ ከተማ
ሰልፍ ቢጠራም የወያኔ ባለስልጣኖች የአሁኑ ወቅት የተረጋጋ አይደለም በሚል ምንያት ሰልፉ የከለከሉ መሆናቸው ተነግሯል።
ለሚመለከታቸው እስካሳወቅን ድረስ ስልፉን ማካሄድ እንችላለን የሚሉ አባላት ቢኖሩም በእርግጠኛነት ሰልፉ መካሄዱ የሚታወቀው
በነገው ዕለት መሆኑ ተነግሯል።
Ø
ትናንት የካቲት 18 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ
በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ የአልሸባብ ታጣቂዎች በሰነዘሩት ጥቃት ቢያንስ 14 ሰዎች መሞታቸው
የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ሞጋዲሾ ውስጥ የሚገኘው
የሱማሊያ ወጣት ሊግ ሆቴል ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለት ሲሆን አጥቂዎቹ ጥቃታቸውን የፈጸሙት በመኪና ላይ የተጠመደ
ፈንጅ አጠገቡ በማፈንዳት ነው። ፒስ ጋርደን በሚል ስም የሚጠራ በአካባቢው ያለ ፓርክም እንዲሁ የፈንጅ አደጋ ደርሶበታል።
ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ ሊገቡ ጥረት አድርገው የነበሩትን አራት የአልሸባብ ታጣቂዎች ገድለው ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን
ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት ሁኔታውን ለመቆጣጠር የጸጥታ ኃይሎች በርከት ብለው የተሰማሩ ሲሆን በየቦታውም ፍተሻ እያካሄዱ መሆናቸው
ታውቋል። ከሶስት ቀን በፊት የአልሸባብ ኃይሎች የፕሬዚዳንቱ
መኖሪያ በሆነው በቤተ መንግስት አካባቢ ጥቃት ፈጽመው ሶስት ሰዎች መግደላቸው ይታወሳል።
Ø
በትናንትናው ዕለት በሊቢያ ቤንጋዚ ውስጥ አይሲስ የተባለው አሸባሪ
ድርጅት መኪና ላይ የተጠመደ ፈንጅ አፈንድቶ አምስት
የጸጥታ ተቋም አባላትን የገደለ መሆኑ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። አይሲስ በድረ ገጽ አማካይነት ባሰራጨው ዜና ፈንጅው ኢላማ
ያደረገው የምስራቅ ሊቢያ መንግስት የጦር ኢታ ማጆር ሹም ላይ ሲሆን በፈንጅው
ከ25 በላይ ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን ገልጿል። በምስራቅ ሊቢያ መቀመጫውን ያደረገውና በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ
ታዋቂነት በተሰጠው መንግስት ስር ያሉ የጸጥታ ኃይሎች ባለፈው
ማክሰኞች በሚድትራኒያን ባህር ጠረፍ ላይ የምትገኝ አንድ የወደብ ከተማ ከአይሲስ አስለቅቀው በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው ይታወሳል።
Ø
ከቦኮሃራም ጋር እየተፋለሙ ያሉትን የናይጄሪያ ወታደሮች
እንዲያሰለጥኑ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎች ወደ ናይጄሪያ የሚላኩ መሆናቸው ተነገረ።
ከጥቂት ጊዜ በፊት በናይጄሪያ መንግስት ጥያቄ
አንድ የአሜሪካ ወታደራዊ ቡድን ቅደመ ጥናት ለማድረግ ወደ ናይጀሪያ ተልኮ ምን እንደሚያስፈልግና ምን መደረግ እንዳለበት ጥናት
ሲያደርግ መቆየቱ ይፋ የሆነ ሲሆን በጥናቱ መሰረት የተወሰኑ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎችና አሰልጣኞች ወደ ናይጄሪያ እንደሚላኩ
ታወቋል። ቀደም ብሎ የአሜሪካ ወታደራዊ አማካሪዎች የናይጄሪያ ወታደሮችን በማሰልጠን ተግባር ላይ ተሰማርተው ሲያሰለጥኑ
መቆየታችው የሚታወስ ሲሆን የናይጄሪያ ወታደሮች ወታደራዊ ዲሲፕሊን የማይጠብቁና የሕዝቡን ሰብአዊ መብቶች የማከብሩ ናችው በሚል
ምንያት የማሰልጠኑ ተግባር ከሁለት ዓመት በፊት መቋረጡ ይታወቃል። ባለፈው ጥር ወር አሜሪካ ከተቀበሩ ፈንጅዎችና ከደፈጣ ጥቃቶች
መከላከል የሚያስችሉ 24 ወታደራዊ መኪናዎችን ለናይጄሪያ መንግስት የሰጠ ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ ያስገኙት ውጤት እና ጥቅም
እየተገመገመ ነው ተብሏል።
የካቲት 18 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በአዲስ አበባ መስፋፋት ስም መሬት የመቀማቱን እቅድ በመቃወም በተጀመሩትና ወደሶስት
ወር ለሚጠጋ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሲካሄዱ በነበሩት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በሻዕቢያ የሚደግፉ ኃይሎች እጃቸው
ያለበት መሆኑን የሚያረጋግጥ ተጨባጭ መረጃ የተገኘ መሆኑን በመጥቀስ የወያኔው አፈቀላጤ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ሕዝባዊ
እንቅስቃሴዎቹ የሕዝብ ብሶትና ብስጭት የወለዳቸው እንቅስቃስዎች መሆናቸው እየታወቀ ወያኔ የችግሩን ምንጭ ወደ ሻዕቢያ ለማዞር
የሞከረው በሕዝብ ድጋፍ እንቅስቃሴውን ለማብረድ ይቻላል ከሚል ስልት የተነሳ መሆኑን አንዳንድ ወገኖች ግምታዊ አስተያየት
ይሰጣሉ። ቀደም ሲል በድንበር አካባቢዎች በወርቅ ማዕድን
ላይ ሲሰሩ የነበሩና ቁጥራቸው ከ80 የሚበልጡ ዜጎች በሻዕቢያ ወታደሮች ተጠልፈው መወስዳቸውን ተከትሎ
በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች በሚያስተናግዷቸው ድረ ገጾችና በሌሎች መገናኛ ብዙሐን
በሻዕቢያ ላይ እርምጃ መወሰድ አለበት የሚል ጩኸት ሲያሰሙ የቆዩ
መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን የአሁኑ የወያኔ መግለጫ ይህንን ተከትሎ ለማስፈራራት የተደረገ ነው ነው የሚሉም አልጠፉም።
ቅስቀሳውም ሆነ ማስጠንቀቂያው
መጨረሻ
ምን
እንደሆነ
ግራ
ያጋባል
ያሉ
ክፍሎች
ወያኔ
ያለበትን
መረረ
ቀውስ
ለማርገብ
ጦርነት
ሊገባ
ወደኋላ
የማይል
ቢሆንም
እንደፈለገው
ተነስቶ
በሻዕቢያ ላይ ወረራ ሊያካሄድ
አይችልም
የሚል ድምዳሜ ይሰጣሉ።
Ø
በተያያዘ ዜና ባለፈው
ሰሞን
አንድ የሻዕቢያ ተቃዋሚ የሆነ የታጠቀ ኃይል
ወደ
ኢርትራ
ዘልቆ
ከሻዕቢያ
ወታድሮች
ጋር
ድንገት ተገናኝቶ
በተደረገ
የተኩስ
ልውውጥ
ከቡዱኑ አባላት መካከል አንዱ መገደሉንና ሌላ አንድ መቁሰሉን እንዲሁም ሶስት አባሎቹ መማረካቸውን አሥታውቋል።
ይህን ዜና ያሰራጨው የኤርትራ ብሔራዊ ካውንስል ሌዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚባለው ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ
በዚህ ዓመት ጠቅላላ ጉባዔ እንደሚያደርግም ድርጅቱን በሚመራው
ግለሰብ ተገልጿል።
ካውንስሉ
የመጀመሪያውን
አሰባሳቢ
ጉባኤ
ያደረገው
ከሁለት
ዓመት
በፊት
በአዋሳ
ከተማ
መሆኑ
የሚታወስ ሲሆን
ወያኔ
የሻዕቢያ
ተቃዋሚዎችን
በመርዳትና በማጠናከር ሻዕቢያን የማዳከም እቅዱ ተዳክሞ የማያውቅ ቢሆንምና በሱዳን
መንግስት የተያዙትን የጀብሃ መሪዎች አማላጅ ሆኖ በማስለቀቅ ቁልፍ ሚና ቢጫወትም
እስካሁን ድረስ የሻዕቢያ ተቃዋሚ የሆኑ ቡድኖችን ለማጠናከር
የወሰደው እርምጃ አጥጋቢ አይደለም
ሲሉ
አዲስ
አበባ
ያሉት
የሻዕቢያ
ተቃዋሚ ድርጅቶች
ሲከሱ ይደመጣሉ። የአሁኑ የወያኔ ማስፈራሪያ ምን መልክ እንደሚይዝ ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
Ø
ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2008 ዓም ሕዝባዊ ተቃውሞው
በተለያዩ ቦታዎች የቀጠሉ መሆናቸውን ከተለያዩ ምንጮች የሚገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። በምዕራብ ሀረርጌ በአሩሲና በምዕራብ ሸዋ
አካባቢ የተቃውሞው እንቅስቃሴ መቀጠሉ ተነግሯል። በአርሲ በርካታ ሰዎች በወያኔ አግአዚ ጦር የታሰሩ ሲሆን
የወያኔ ወታደሮች የሚገድሏቸውና የሚያቆስሏቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደው ማንነታቸው እንዳይታወቅ በአንዳንድ ቦታዎች
በተለይም በምስራቅ ሃርርጌ እና በምዕራብ ወለጋ በአግአዚ ቁጥጥር
የሚሆን ቁጥጥር የመስክ ሆስፒታሎች እየተሰሩ መሆኑ ተነግሯል።
Ø
በማሊ ውስጥ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል የነበረ አንድ የቻድ ወታደር ያለበትን ክፍል
አዛዥና አንድ ሌላ ዶክተር የገደለ መሆኑ ተነግሯል። ወታደሩና አዛዡንና ዶክተሩን የገደለበት ምክንያት ለጊዜው ግልጽ ባይሆንም
በቁጥጥር ስር የዋለው ወታደር በተለያዩ ሁኔታዎች ሲበሳጭ
የነበረ መሆኑ ተነግሯል ። በማሊ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ስር ያሉ የቻድ ወታደሮች ክፍያቸው እየዘገየ በመምጣቱ
በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ የቆዩ ሲሆን የቻድ መንግስትም በማሊ የሚገኙ ወታደሮች ትጥቅና መሳሪያ የተሟላ አይደለም በማለት
ቅሬታ ሲያሰማ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ስር ከ9000 በላይ የሆኑ የቻድ ወታድሮች ይገኛሉ።
Ø
ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የኡጋንዳ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ በጠቃላላው አገሪቱ ውስጥ ከ200 በላይ የሚሆኑ ደጋፊዎቹና አባሎቹ
የታሰሩ መሆናቸውን ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ ቼንጅ (Forum for Democratic Change) የሚባለው ዋናው የኡጋንዳ ተቃዋሚ
ፓርቲ ገለጸ። በየቦታው የታሰሩት አባላት አብዛኞች የአካባቢው የፓርቲ መዋቅር ባለስልጣኖች ሲሆኑ ምርጫው የተጭበረበረ መሆኑን
የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃዎች የያዙ መሆናቸውን የፓርቲው ቃል አቀባይ ገልጿል። የፓርቲው መሪ ቢሲግየ እስካሁን በእስር ላይ
መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን አባሎቹ አለአግባብ በመያዛቸው ፓርቲው ክስ ይመሰርታል ተብሎ ይጠበቃል። የኡጋንዳ የፖሊስ ቃል አቀባይ
በተለያዩ ቦታዎች በወንጀል ጉዳይ የተያዙ መኖራቸውን አምነው አንድም የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንዳልተያዘ ገልጸዋል።
Ø
የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ከተማ በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ውስጥ የፈነዳው ቦምብ አራት ፖሊሶችን
ሲገድል ከ6 በላይ ሰዎች ያቆሰለ መሆኑ ተነግሯል። ቦምቡ ከቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የተያዘ ሲሆን ተመርምሮ እንዲቀመጥ ለማድረግ
ጥረት በሚያድርጉበት ወቅት ሳይታሰብ ፈንድቶ ጉዳት ያደረሰ መሆኑ ታውቋል። የቦካሃራማ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ከተማዋን እንዲሁም
ፖሊስ ጣቢያውን ማጥቃታቸው የሚታወቅ ቢሆንም ይህኛው ቦምብ የተጠመደ ወይም የተቀበረ እንዳልሆነ ታውቋል።
Ø
የአምስት የአፍሪካ አገሮች መሪዎች ትናንት የካቲት 17 ቀን በብሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ መግባታቸው የተነገረ ሲሆን በአገሪቱ
ውስጥ በሚያደርጉት የሁለት ቀናት ቆይታ ከአገሪቱ ባለስልጣኖችና ከተቃዋሚ መሪዎች ጋር ተገንኝተው እርቅ ስለሚፈጠርበት ሁኔታ
ይወያያሉ ተብሏል። በብሩንዲ ታዋቂ የሆኑ የፖሊቲካ የሃይማኖት እና የሲቪክ መሪዎች አገሪቱን ለቀው በውጭ አገር በሚኖሩበት ሁኔታ
ትርጉም ያለው ውይይት አካሂዶ እርቅ ማውረድ አስቸጋሪ ነው ተብሏል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ከጥቂት ቀናት
በፊት ብሩንዲ ውስጥ ተገኝተው እርቅ እንዲመጣ ጥሪ ቢያደርጉም ግብኝታቸው ያስገኘው ውጤት አነስተኛ ነው የሚሉ በርካታ ናችው።
የብሩንዲ የተቃዋሚዎች ህብረት ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ ፕሬዚዳንቱ አክራሪ አምባገነን መሆናችውን ገልጸው ማዕቀብና ግፊት
ካልተደረገባችው ለስምምነት ዝግጁ አይደሉም ብለዋል።
Ø
ትናትን የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ እንደገና አገርሽቶ ቢያንስ ሶስት
ዩንቨርስቲዎች የተዘጉ መሆናችው ተነግሯል። ተማሪዎቹ
የተቃውሞ እንቅስቃሴ ያደረጉት ለትምህርት ቤት የሚከፍሉት ገንዘብ ከፍተኛ በመሆኑና በየትምህርት ቤቱ ዘረኛነት በመስፋፋቱ ነው
ተብሏል። ኖርዝ ዌስት ዩኒቨርስቲ በሚባለው ህንጻዎች
በእሳት የጋዩ ሲሆን በኬፕ ታውን ዩኒቨርስቲም የመማሪያ ክፍሎችን በሰው ሰገራ በማበላሸት ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።
ፖሊሶች የአስለቃሽ ጋዝ በመጠቀም ተማሪዎችን ለመበተን ሞክረዋል። በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎቹ ጥያቄ ለትምህርት
የሚከፈለው ዋጋ የበዛ መሆኑን በመጥቀስ ሲሆን በኬፕ ታውን ዩኒቨርስቲ ከትምህርቱ ክፍያ
በተጨማሪ አፍርካንስ የተባለው የነጮቹ ቋንቋ የትምህርት ቋንቋ እንዲሆን መደረጉን በመቃወም ተማሪዎች ተሰልፈዋል።
የዩኒቨርስቲዎቹ ሰራተኖች እና አስተማሪዎች የተማሪዎችን ጥያቄ በመደገፍ በተቃውሞ ሰልፉ ተቀላቅለዋል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባንኪ ሙን ትናንት የካቲት
17 ቀን 2008 ዓም በደበቡ ሱዳን ዋና ከተማ በጁባ ከፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ዋና ጸሐፊው
ከተቃዋሚው መሪ ከሪክ ማቻር ጋርም በስልክ የተወያዩ ሲሆን በትናንትናው ዕለት በሰጡት መግለጫ ሁሉም ወገኖች የሰላሙን ስምምነት
ተግባራዊ ከማድረግ በስተቀር ሌላ አማራጭ የላችውም ብለዋል። በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉት የደቡብ ሱዳን
ዜጎች ከሁለት ሚሊዮን በላይ መሆኑን ገልጸው የደቡን ሱዳን መንግስት ዜጎችን ለመንከባከብ ኃላፊነት አለበት ብለዋል። ተመድ 21
ሚሊዮን ዶላር ለእርዳታ እንደሚሰጥም ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም ዋና ጸሀፊው የደቡብ ሱዳን ባለስልጣኖች
ባለስልጣኖቹ ከፖሊቲካ ይልቅ ሰላምን እንዲያስቀድሙ ፤ ችግሮችን እንዲያስወግዱና በመቻቻል በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ
ተስማምተው የሽግግርና የአንድነት መንግስት እንዲያቋቁሙ መልእክት ለማስተላለፍ የሚወዱ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ነሐሴ ወር
በደቡብ ሱዳን ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የእርቅ ስምምነት መፈረሙ የሚታወስ ሲሆን ከዚያ ወዲህ በየቦታው በተካሄዱ ጦርነቶች በርካታ
ሰዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩም ቤት ንብረታቸውን ጥለው የተሰደዱ
መሆናችው ይታወቃል። በተያያዘ ዜና ደቡብ
ሱዳን
ነጻ
ወጣች
ከተባለ
ጀምሮ
4
ቢሊዮን
ድላር
ያህል
የእርዳታ
ገንዘብ
መሰረቁን
ያስረዱ
ክፍሎች
በቅርቡ
ደግሞ
የፕሮእዚዳንት
ሳልቫ
ኪር
ረዳቶች
በተጭበረበሩ
ፊርማዎችና
ሰነዶች
ከ
14
ሚሊዮን
ዶላር
ያላነሰ
መስረቃእውን
አጋልጠዋል።
የካቲት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ከሁለት
ወር
በፊት
የጀመረው
ህዝባዊ
የተቃውሞ
እንቅስቃሴ ትናንት የካቲት 16 ቀን እና ዛሬ የካቲት 17 ቀን በተለያዩ
ቦታዎች ቀጥሎ የዋለ መሆኑ ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱት ዜናዎች ይገልጻሉ። ዛሬ በያቤሎ ቦረናና እና በባሌ የተለያዩ አካቢቢዎች
እንቅስቃሴዎች መደረጋቸው የተዘገበ ሲሆን በትናንትናው ዕለትም በምዕራብ ሸዋና በወለጋና በቦረና በተካሄዱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች
በርካታ ሰዎች በአግአዚ ወታደሮች ጥይት መገደላቸው ታውቋል።
ይህ በዚህ እንዳለ በግንጭ እና በአምቦ ጉብኝት ያደረገ የውጭ አገር ጋዜጠኛ ነዋሪዎችን በማነጋገር ካገኝው መረጃ
የወያኔ ወታደሮች ከፍተኛ አፈናና በደል እያደረጉ መሆናቸውንና በተለያዩ አካቢቢዎች ፍርሃት የሰፈነ መሆኑን አጋልጠዋል።
መትረየሶች የጫኑ መኪናዎች መንግዶችን በመሙላታቸው እና በየቦታው የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች የሚያካሄዱትን ፍተሻ እና ተያይዞም
ያለው ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ ሕዝቡ እንደተለመደው በሰላማዊ ኑሮውን ለመግፋት ያልተቻለ
መሆኑን ዘርዝሮ ገልጿል። በጭለማ የሚንቀሳቀስ ወጣት በፖሊሶች
እንደሚያዙና እንደሚመረመሩ፤ የእጅ ስልካቾቻቸው ከተቃውሞ ጋር የተያያዙ ፎቶግራፎች ካሏቸው ወዲያውኑ እንደሚታሰሩ አንዳንዳቹም
እንደሚገደሉ፤ ወላጆች በየቀኑ ለልጆቻቸው እየተጨነቁ
እንዳሉ ዘግቧል። በአምቦ ውስጥ የወታደሩ ብዛት በጣም ከፍተኛ መሆኑን ከአንዳንድ ቦታዎች በስተቀር የንግድት ተቋሞችና ሆስፒታሎች
ዝግ መሆናቸውና ላለፉት ሶስት ወራት ትምህርት የተቋረጠ መሆኑን ተገልጿል። የወያኔ አገዛዝ በስልጣን እስካለ ድረስ አመጹ
የሚቀጥል መሆኑ ነዋሪዎች የገለጹለት መሆኑን ተናግሯል።
Ø
ኦክስፋም
የተባለው
የዓለም
አቀፍ
ድርጅት
በቅርቡ
ባወጣው
አዲስ
ዘገባ
በኢትዮጵያ
ውስጥ
የገባውን
ድርቅና
ረሃብ
በሚመከት
አዳድስ ጥናታዊ መረጃዎች ያቀረበ መሆኑ ታውቋል። ባለፈው ዓመት ከ 12
እስከ 18 ወራት ባሉት ጊዜያት ውስጥ የዝናቡ መጠን የተመጣጠኑ ባለመሆኑ ከ50 እስከ 90 በመቶ ምርት የቀነሰባቸው አካባቢዎች
መኖራቸውን፤ በአርብቶ አደሩ አካባቢ ሶስትና አራት በጎች ወይም ፍየሎች ሸጠው ምግብ ይገዙ የነበሩ ቤተሰቦች አሁን አንድ እንኳ
ሸጠው እህል ለመግዛት ባለመቻላቸው ህይወታቸው እየተጠበቀ ያለው
ሙሉ በሙሉ በእርዳታ እህል ላይ መሆኑ ዘግቧል።
ከሚያስፈልገው እርዳታ ውስጥ እስካሁን የተገኘው 58 ከመቶ
የሚሆነው ብቻ እንደሆነም ዘገባው ጠቅሶ ባስቸኳይ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት እርዳታ ካልተገኘ ከሚያዚያ በኋላ ከፍተኛ ችግር
ሊከተል እንደሚችልም የአለም አቀፉ ድርጅቶችን ዋቢ በማድረግ አሳስቧል። የሶማሌ
ጎሳዎች በሚኖርበት አካባቢ ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ
በረሃብ የተጠቃ መሆኑን ጠቅሶ በአንድ አካባቢ ብቻ 13500 የሚሆኑ ሰዎች የመጠጥ ውሃ የሚያገኙት ለጊዜው ከተቆፈረ
የውሃ ጉድጓድ ነው ብሏል። በሌላ በኩል ድርቅን ለመቋቋም
የሚያስችል የመስኖ ልማት ማስፋፋት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ተግባራዊ ማድረግ ሲገባው የወያኔ አገዛዝ ይህን ባለማድረጉ አገሪቷን
ለከፍተኛ ረሃብ እንድትጋለጥ አድርጓታል በማለት አንዳንድ
ወገኖች እየተናገሩ ሲሆን ለድርቅ ተጠቂ የማይሆኑ አዝርእትን መጠቀምም ድርቅን ለመቋቋም ይረዳል የሚሉ ሀሳቦችም እየተሰነዘሩ
ይገኛል።
Ø
በባህርዳር ከተማ በዚህ ሳምንት
መጀመሪያ ላይ በተጠራ ስብሰባ ላይ የተገኙት ነዋሪዎች በወያኔ
ሹመኞች ላይ ከፍተኛ ቁጣ ማሰማታቸው ከባህር ዳር ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ በፊት ግምገማ ተብለው በተጠሩ ስብሰባ የደረሰብንን በደል ነቅሰን ተናግረን እናንት እርምጃ ባለመውሰዳችሁ
ጠላት እንድናፈራ አድርጋችሁናል ካሉ በኋላ በእንዲህ ዓይነት ስብሰባ ለመሳተፍ ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ለባህርዳር ስፖርተኞች ማጎልመሻ በአስር
ሚሊዮን ብር በጀት የሚሰራ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ተቋሙ
የሚገነባበት ቦታ ቀደም ብሎ በተለያዩ አነስተኛ የንግድ
ስራዎች የተሰማሩ ዜጎች ይጠቀሙበት የነበረ ቦታ ሲሆን
ስፍራውን ለማስለቀቀ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል።
በእንጨት ንግድ፤ በመኪና ጥበቃ፤ በጉልት ችርቻሮ፤ ወዘተ…
የንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ጉሮሮ ይሸፍኑ የነበሩትን ዜጎች
ከቦታችው ከማንሳት ይልቅ የተባለውን ተቋም ወይ ወደ
ሌላ ቦታ መውሰድ አሊያም ዜጎቹ ሊነግዱበት የሚችሉበት ተለዋጭ ቦታ መስጠት ሲገባ ከፍተኛ ወከባና እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑን
ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል።
Ø
ባለፈው ወር በሶማሊያ ደቡባዊ ግዛት በአልሸባብ ኃይሎች የተገደሉት
የኬኒያ ወታደሮች ቁጥር 180 እስከ 200 ይደርሳል ሲሉ የሶማሊያ
ፕሬዚዳንት ከአንድ የሶማሊያ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉ ቃለ ምልልስ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ 180 እስከ 200 የሚደርሱ
የኬኒያ ወታደሮች መሞታቸው የተረጋገጠ ነው ካሉ በኋላ በወታደሮቹ የቀብረ ስነስርዓት ላይ መገኘታቸው ትክክል የነበረ መሆኑን
ገልጸው በአንዳንድ የሶማሊያ ዜጎች የተሰነዘረባቸውን ተቃውሞ
አጣጥለዋል። የኬኒያ ባለስልጣኖች የሱማሊያው ፕሬዚዳንት የሰጡት አዲስ መግለጫ
ሀሰት ነው በማለት የካዱ ሲሆን የሞቱት የኬኒያ ወታደሮች ምን ያህል መሆናቸውን ለመናገር ሳይደፍሩ ቀርተዋል።
አልሸባብ ከ100 በላይ የኬኒያ ወታደሮች መግደሉን የሚገልጽ መግለጫ በወቅቱ መስጠቱ ይታወሳል።
Ø
ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም ረፋድ ላይ ዮላ በምትባለዋ
በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በምትገኘው ከተማ ውስጥ በዋናው የፖሊስመስርያ ቤት ውስጥ
ከፍተኛ የሆነ የፈንጅ ድምጽ መሰማቱን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። በፈንጅው ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ እስካሁን መረጃ
ባይገኝም የህንጻዎች ግድግዳዎችና መስኮቶቹ የፈራረሱ መሆኑን የአይን እማኞች ይናገራሉ። ቦታው በተደጋጋሚ በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች
ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የአሁኑንም ፈንጅ የቦኮ ሃራም ድርጊት ሳይሆን አይቀርም በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚሰጡ በርካታ ናቸው።
ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2008 ዓም በጄኔቫ ሲወዘርላንድ ይፋ የሆነው
95 ገጾችን የያዘው የተመድ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ዘገባ ሊቢያ ውስጥ ስለሚገኘው አስከፊ ሁኔታ በሰፊው የዘረዘረ
መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ሊቢያ ውስጥ በተፈጠረው የፖሊቲካ ቀውስ አንገትን በመቁረጥ ጨምሮ በርከት ያሉት ግድያዎች መካሄዳቸውን፤
በርካታ ዜጎች የታሰሩ መሆናቸውን የኤሌክትሪክ ኃይልን ጨመሮ በድብደባ በመሳሰሉት በዜጎች ላይ የማሰቃያ ድርጊቶች መፈጸማቸውን
ዘገባው ገልጾ ወንጀለኞች ወንጀለኞቹ አለምንም ጥያቄ በነጻ ተቀምጠዋል ብሏል። ዘገባው መንገድ ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን፤
ለመግደል የተደረጉ ሙከራዎችን ማስፈራዊያዎችንና ማስጠንቀቂያዎችን እንዲሁም ሴቶች ላይ የተፈጸሙ አስከፊ ድርጊቶችን አካትቷል።
ዘገባውን ያወጣው የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን አያይዞ በሰጠው መግለጫ ድርጊቱን የፈጸሙት በሊቢያ የሚገኙ ተንቀሳቃሽ አካሎች
በሙሉ መሆናቸውን ጠቅሶ አገሪቱ በትናንሽ የጎሳ ቡድኖቹ፤ በአይሲስ ቅርንጫፍ ቡድኖች፤
ትሪፖሊ ላይ መቀመጫ ባደረገውና ራሱን መንግስት ነኝ
ብሎ በሚጠራው ቡድን እና የዓለም አቀፍ እውቅናን ባገኘውና መቀመጫውን በምስራቅ ሊቢያ ባደረገው ቡድን መከፋፈሏ ህግን ለማስከበር
አልተቻለም ብሏል። የተመድ የሰብአዊ ኮሚሽን መሪ ሚስተር ዘይድ ራእድ ድርጊቱን የፈጸሙት ሁሉ የጦርነት ወንጀል የፈጸሙ
በመሆናቸው ወደ ፍርድ ሊቀርቡ ይገባል ብለዋል። ዘገባው ከመጻፉ በፊት ከ250 በላይ ምስክሮች በላይ መረጃ የሰጡ ሲሆን 900
አቤቶታዎችን ዘገባውን ያወጣው ክፍል የመረመረ መሆኑ ታውቋል።
የካቲት 16 ቀን 2009
ዓ.ም
·
በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ የሚገኙት ሕዝባዊ የተቃውሞ
እንቅስቃሴዎች ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008 ቀን 2008
ዓም ቀጥለው መዋላችው ከልዩ ልዩ ምንጮች የሚገኙት ዜናዎች ይጠቁማሉ። በዛሬው ቀን በምስራቅ ሀረርጌ በዳሩ ላቡ አካባቢ ተቃውሞ
የቀጠለ ሲሆን እንዲሁም ካለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ በመቻራ፤ በሚቻ፤ በጋዱሎ፤ በቢልካየና በሳኩራ አካባቢዎች የሕዝቡ ተቃውሞ
የቀጠለ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በተጨማሪም በምዕራብ ወለጋ የተለያዩ ቦታዎችና
እንዲሁም በዚሁ አካባቢ አላሙዲ የወርቅ ማዕድኑን በሚዘርፍበት በዩብዶ ከፍተኛ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተደረገ መሆኑ
ተዘግቧል። በያቤሎ ቦረና አካባቢም ተመሳሳይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ
እንደነበር የተለያዩ ምንጮች ገልጸዋል።
·
እንደገና አገርሽቶ በመቀጣጠል ላይ ባለው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ
ምክንያት ውጥረት ውስጥ የገባው የወያኔ አገዛዝ በአንድ በኩል “የማያዳግም”
የኃይልና የጭካኔ እርምጃ የአግአዚው ጦር እንዲወስድ ጥብቅ መመሪያ እያስተላለፈ በሌላ በኩል ሰላም ሊያወርዱ ይችላሉ
ብሎ የሚገምታቸውን ወገኖች በመቅረብ እንቅስቃሴውን ለማኮላሸት ጥረት እያደረገ ይገኛል። በተለያዩ ቦታዎች ያሉትን አባገዳዎች
ጠርቶ ሁኔታውን እንዲያረጋጉ የግዳጅና የማስፈራሪያ ጥያቄ ማድረጉን ውስጠ አዋቂ ምንጮች እየተናገሩ ሲሆን ለሃይማኖት መሪዎችም
ተመሳሳይ ጥያቄ ትዕዛዝ አቅርቦ በጉዳዩ ላይ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸው ተነግሯል።
·
የሰማያዊ ፓርቲ የቀድሞው
የህዝብ
ግንኙነት
ኃላፊ
አቶ
ዮናታን
ተስፋዬ ትናንት የካቲት
15 ቀን 2008 ዓም ለሥተኛ ጊዜ አራዳ ፍርድ በዝግ ችሎት የቀረበ መሆኑ የተነገረ ሲሆን አቃቤ ህጉ የምርመራ ጊዜውን ያልጨረሰ
መሆኑ ገልጾ ጥያቄ በማቅረቡ
የ28
ቀናት
ተጨማሪ ጊዜ የተሰጠው መሆኑ ታውቋል። አቶ ዮናታን እስካአሁን ድረስ ለምርመራ ማንም እንዳላናገረው የተናገረ ሲሆን ከታሰረ ጀመሮ
ጠበቃውን ማነጋገር ያልቻለ መሆኑንም አስረድቷል። ከጠበቃው ጋር ሳይመካከር ቃሉ መስጠት እንደማይፈልግ ለፍርድ ቤቱ ተናግሮ
ጠበቃውን ለማነጋገር እንዲፈቅድለት ጠይቋል ተብሏል።
·
የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ሚስተር ብሌዝ ኮምፓዎሬ
(Blaise Compawore) የአቮሪ ኮስት ዜግነት የተሰጣቸው መሆኑ ዛሬ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. በይፋ ተነግሯል።
ባለቤታቸው የአይቮሪ ኮስት ተወላጅ የሆኑት ሚስተር ኮምፓወሬ ዜግነቱ የተሰጣቸው ከሁለት ዓመት በፊት በአገሪቱ ፕሬዚዳንት
በሚስተር ካታራ ሲሆን እስካሁን በሚስጥር ተደብቆ በዛሬው ዕለት በይፋ ተገልጿል።
ሚስተር ካምፓወሬ ከሁለት ዓመት በፊት በሕዝባዊ አመጽ ከስልጣን
ተወግደው ወደ አይቮሪ ኮስት የሄዱ ሲሆን ከእሳቸው በፊት የነበሩትን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራን በግፍ አስገድለዋል
በሚል ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው አይቮሪ ኮስት እንድታስረክባቸው የቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወቃል። የቀድሞ
ፕሬዚዳንት የአይቮሪ ኮስት ዜግነት ከተሰጣቸው የማስረከቡ ጥያቄ የማይፈጸም መሆኑ ተነግሯል።
·
በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለተፈናቀሉ ሰዎች የተሰራውን መጠለያ
ጣቢያ ሲጎበኙ የነበሩት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና
ጸሐፊ ባንኪ ሙን በዚህ ዓመት በአለም ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እርዳታ በመቀበል ላይ ያሉ ዜጎች
ቁጥር 60 ሚሊዮን መድረሱን ይፋ አድርገዋል። ዋና ጸሐፊው የወቅቱ የስደተኛ ቁጥር ባለፉት 65 ዓመታት ከነበረው ቁጥር ከፍተኛው
መሆኑን ገልጸው እርዳታው መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። በሚቀጥለው ግንቦት ወር በሚደረገው የሰብአዊ መብትና እርዳታ ስብሰባ
ላይ ጉዳዩ በሚገባ ተነስቶ ውይይት እንደሚካሄድበትም ቃል ገብተዋል። በኮንጎ ሀብታም የሆነውን የማዕድን ቦታ ለመቆጣጠር የተለያዩ
የታጠቁ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱ ሲሆን እነዚህ ቡድኖች በሚወስዷቸው የኃይል እርምጃዎች በርካታ ዜጎች ቤት ንብረታቸውን እየጣሉ
መሰደዳቸው ይታወቃል።
·
በሊቢያ የሚንቀሳቀሰው የአይሲስ ቡድን ሳብራታ (Sabratha)
በምትባለው ከተማ ውስጥ የሚገኘውን የመንግስቱን የጸጥታ ክፍል ጽ/ቤት ለጥቂት ጊዜ በቁጥጥር ስር አውሎ 12 ወታደራዊ መኮንኖችን
አንገታቸውን በስለት በመቁረጥ የገደላቸው መሆኑ የዜና
ምንጮች ገልጸዋል። ዛሬ ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓም የሊቢያ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ ከከተማው የተባረሩ
መሆናቸው ታውቋል። የአይሲስ ቡድን አባላት ወደ ጽ/ቤቱ ሊገቡ የቻሉት በከተማው የሚገኙ ወታደሮች በሌላ ግዳጅ ላይ መሰማራታቸውን
እና በስፍራው ላይ የጸጥታ ክፍተት በመከሰቱ ነው ተብሏል።
አሸባሪዎቹ ቦታውን ለሶስት ሰዓታት ያህል ለመቆጣጠር የቻሉት አንገታቸውን የቀሏቸውን ሰዎች አሰከሬን መሬት ላይ በማነጥፍ መንግድ
ለመዝጋት በመሞከራቸው ነው በማለት በአአባቢ የነበሩ እማኞች ይናገራሉ። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በሊቢያ የአይሲስ እንቅስቃሴ ጎላ
እያለ የመጣ ሲሆን ባለፈው ሳምንት በአሜሪካው የአየር ጥቃት የተወሰኑት መገደላቸው ይታወሳል።
·
በአፍሪካ ከሚገኙት አምስት ህጻናት መካከል አንደኛው ለተለያዩ
በሽታዎች መከላከያ የሆኑ ክትባቶች እንደማይደረግለት የአለም የጤና ድርጅት (WHO) ረቡዕ የካቲት 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ይፋ
ባደረገው ዘገባ አስታወቀ። እንደ ፈርንጆቹ አቆጣጠር ከ2000 ዓም ጀምሮ እስከ 2014 አመተ ምህረት ድረስ ባሉት አመታት
ለህጻናት የሚደረገው የክትባት አገልግሎት ከ57 ከመቶ ወደ 80 በመቶ ያደገ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በሌሎች የአለም አገሮች የጠፉ
በአፍሪካ ግን በስፋት የሚገኙትን በሽታዎች ለማጥፋት ብዙ ስራ መሰራት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
የካቲት 15 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በአገሪቱ ለገባው ድርቅና
ረሃብ ከዓለም አቀፉ ህብረተሰብ እየተሰጠ ያለው እርዳታ በቂ አለመሆኑን በኢትዮጵያ የሚገኙት የተመድ የህጻናት መርጃ ድርጅት
ተወካይ ገልጹ። እስከሚቀጥለው ግንቦት ወር ድረስ በቂ እርዳታ የማይገኝ ከሆነ እና እንደወትሮው ዝናም በወቅቱ ካልዘነበ የብዙ
ሰዎች ሕይወት ሊቀጠፍ
እንደሚችል ስለሁኔታው እውቀት ያላቸው ሰዎች
ይናገራሉ። በአፋር
አካባቢ
የቀንድ
ከብቶች
እያለቁ
መሆናቸውን የአይን እማኞች በየጊዜው የተናገሩ ሲሆን
እስከ ስኞ 14 ይደርሳል ተብሎ የተጠበቀው
የእርዳታ እህልም እንዳልደረሰ ያካባቢው ነዋሪዎች አጋልጠዋል
። በርካታ ሰዎች
በምግብ እጥረት
እንደተጠቁ የታወቀ ሲሆን በተለይም
ህጻናት
መሞት
የጀመሩ
መሆናቸውም
ተነግሯል። የወያኔ
አገዛዝ ከዚህ በፊት የድርቁን ሁኔታ በራሳችን ገንዘብ እና የሰው ኃይል እንቋቋማዋለን እንጅ ወደ ልመና አንገባም የሚል ዲስኩር
ሲያሰማን ቆይቶ በኋላ ባዕዳንን ሲለምን የታየ መሆኑን ያስታወሱት ዜጎች ከድርቅ በኋላ ረሃብ የሚከሰትበት ወቅት አልፏል እያለ
በደነፋ በጥቂት ቀናት ውስጥ በድርቁ ምክንያት ሰዎች መሞታቸው እየተዘገበ ነው በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።
Ø
በተያላዩ አካባቢዎች የሚደረገው ሕዝባዊ ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በምዕራብ ወለጋ በቤጊና በአይራ
የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ጎላ ያሉ እንደነበር ተዘግቧል።
ሰኞ የካቲት 14 በምስራቅ ሀራርጌ በተለያዩ አካባቢዎች ተቃውሞ ቀጥሎ የነበረ ሲሆን
አራሙሪ በተባለው መንደር በተከሰተ ሕዝባዊ ተቃውሞ ከአስር በላይ ሰዎች ሲገደሉ
በመቻራም በእድሜ ለጋ የሆኑትን ጨምሮ በርካታ ስዎች መገደላቸው ታውቋል። በቅርቡ እንደገና በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ
ተቃውሞ በጠቅላላው ከ43 በላይ ሰዎች በወያኔ አግአዚ ጦር መገደላቸውን አንዳንድ ምንጮች ይጠቁማሉ። የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር
በዛሬው ዕለት የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን ብሎ መዛቱ የታወቀ ሲሆን ይህም
የወያኔ አግአዚ ጦር ጭፍጨፋን ያጠናክረዋል ተብሏል።
Ø
በእስራኤል አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የመረረ የዘር መድሎዎ የሚደርስባቸው መሆኑ ከዚህ በፊት
በተደጋጋሚ የተዘገበ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ ጋብቻቸው ህጋዊ እንዲሆንና የጋብቻ የምስክር ወረቀት እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ወጣቶች
እውነተኛ የአይሁድ ሃይማኖት ተከታዮች አይደላችሁም በሚል ምክንያት ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገ መሆኑን የእስራዔል ጋዜጦች
አጋልጠዋል። ቤታህ ቲክቫ (Petah Tikva) በተባለችው የእስራዔል ከተማ በቅርቡ ከ30 በላይ የሆኑ አዲስ ትዳር መስራቾች
የጋብቻ የምስክር ወረቀት የተከለከሉ መሆናቸው ሲታወቅ
በሌሎች ቦታዎችም ተመሳሳይ ድርጊት የሚፈጸም መሆኑን በርካታ ዜጎች ይናገራሉ። ለመከልከሉ ዋናው ምክንያት የሃይማኖት ጉዳይ
ሳይሆን ዓይን ያወጣ ዘረኛነት መሆኑን ብዙዎቹ ይናገራሉ። ከጥቂት ወራት በፊት በእስራኤል የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን
የሚደርስባቸውን የዘረኛነት በደል በመቃወም ከፖሊስ ጋር ግጭት ማድረጋቸው ይታወሳል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ከሚመለከታቸው ወገኖች ጋር ንግግር
ለማድረግ ትናንት የካቲት 14 ቀን 2008 ዓም ከሰዓት በኋላ ብሩንዲ የገቡ ሲሆን ሌሊቱን
ከ10 በላይ የሚሆኑ ቦንቦች ፈንድተው በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸው እንዲሁም ከቆሰሉት መካከል ወታደሮች
እንደሚገኙበት ተነገረ። ቦምቦቹን ያፈነዳው የትኛው ወገን እንደሆን ካለመታወቁ በላይ ፖሊሶች በአገሪቱ ሰላም የለም የሚል
መልእክት ለተመድ ዋና ጸሐፊ ለማስተላለፍ ተቃዋሚዎች
ያካሄዱት የሽብር ተግባር ነው በማለት መግለጫ ሰጥተዋል።
የተመድ ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የመንግስትና የተጻራራሪ ወገኖችን
አግኝተው ያነጋገሩ መሆኑን ጠቅሰው ሁለቱም ወገኖች ተገናኝተው ለመወያያትና ላለፉት 10 ወራት በአገሪቱ የሰፈነውን የቀውስ ሁኔታ
ለመፍታት መስማማታቸውን ገልጸዋል። በተጻጻሪነት የተሰለፉት የብሩንዲ ተቃዋሚ ኃይሎች የተወሰኑት ከአገር የተሰደዱ ገሚሶቹ በእስር
ላይ የሚገኙኑ እና ከፊሎቹ ደግሞ ትጥቅ አንስተው የሚታገሉ ሲሆን በስልጣን ላይ ያለው ክፍል ተቀምጦ ለመነጋገር ፈቃደኛ የሆነው
ከየትኞቹ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር መሆኑ በግልጽ አልተነገረም። ይሁን እንጅ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ንክሩንዚዛ ማክሰኞ ዕለት በሰጡት
መግለጫ ንግግሩ አገሪቱ ውስጥ በሽብር ተግባር ከተሰለፉት በስተቀር ከሁሉም የብሩንዲ ዜጎች ጋር ሊደረግ ይችላል ማለታቸው ውይይቱ
ዋና ዋና ተቃዋሚዎችን ሊያገልል ይችላል የሚል ግምት አሳድሯል።
Ø
በሊቢያ ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው መንግስት አካል የሆነው የህግ
አውጭው ምክር ቤት ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም ለማካሄድ ያቀደው ስብስባ ምልአተ ጉባዔ ባለማግኘቱ በተባበሩት መንግስታት
ድርጅት ቀርቦ የነበረው የአንድነት መንግስት ምስረታ ረቂቅ ሀሳብ ሊጸድቅ ያልቻለ መሆኑ ተነገረ።
ስብሰባው ምልአተ ጉባዔ አግኝቶ እንዲካሄድ ለማደረግ 89 የምክር
ቤት አባላት በስብሰባው ላይ መገኘት የነበረባቸው ሲሆን ይህ ባለመገኘቱ ስብሰባው ሳይጀመር ሊበተን ችሏል። በርከታ የምክር ቤቱ
አባላት ወደ ስብሰባው መምጣት ያልቻሉት በቀረበው ረቂቅ ሀሳብ ላይ ልዩነት ስላላቸው ነው ተብሏል። ባለፈው ታኅሳስ ወር
በስምምነት የተመሰረተው የፕሬዚዳንት ካውንስል የተባለው አካል 18 የካቢኔ አባላት ያሉበት የአንደነት መንግስት ረቂቅ ሀሳብ
ያቀረበ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት ምክር ቤት እስካሁን ሳያጸድቀው ቀርቷል። በሚቀጥለው ሳምንት
ሌላ ስብሰባ የሚይጠራ መሆኑም ተነግሯል።
Ø
ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2008 ዓም የስፔይንና የሞሮኮ ፖሊሶች አራት
የአሸባሪ ቡድኖች አባሎችን የያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። የስፔይን ፖሊሶች ሶስት ሰዎችን በሴሜን አፍሪካ ከምትገኘውና ሴውታ
(Ceuta) ተብላ ከምትጠራው ከተማ መያዛቸው ከመነገሩ በተጨማሪ የሞሮኮ ፖሊስች ደግሞ ፋርካና በተባለችው የወሰን ከተማ አንድ
የሞሮኮ ዜጋ በቁጥጥር ስር አውለዋል። በሴውታ ከተያዙት መካከል አንደኛው በጓንታናሞ እስር ቤት ታግቶ የነበረ የአልካይዳ አባል
የነበረና በወታደራዊ ትምህርቶችና በቦምብ ስራዎች የሰለጠነ መሆኑ
ታውቋል። አራቱም ሰዎች ተባባሪዎች ለመመልመልና በወታደራዊ
ተግባር ላይ ለማሰልጠን ግንኙነት ሲያደርጉ እጅ ከፍንጅ የተያዙ መሆናቸው ተዘግቧል። በሞሮኮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
የጸጥታ ሁኔታ እየደፈረሰ በመምጣቱ ተጥርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማድረጉ ተግባር በተጠናከረ ሁኔታ ከመምጣቱ በተጨማሪ የስፔይን
ፖሊስም ካለፈው ዓመት ወዲህ 100 በላይ ተጥርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑ ይነገራል።
የካቲት 14 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ባለፉት ሁለት ቀናት በአሩሲ በምስራቅና በምዕራብ ሀረርጌ በምዕራብና በምስራቅ ወለጋ እንዲሁም በሸዋ ሱልልታ የተቃውሞ
እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ከየአካባቢዎቹ የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ። በአንዳንድ
ቦታዎች የአግአዚ ጦር እንዳይገባ ለመከላከል ተቃዋሚዎቹ መንገዶችን
የተዘጉ ሲሆን በምዕራብ ሀረጌና በምስራቅ ወለጋ የአግአዚ ጦር ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ በሚያሰሙ ንጹህ ዜጎች ላይ በከፈተው
ተኩስ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ሞተዋል። ባለፈው
ሳምንት በምዕራብ ሸዋ ተካሂዶ በነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ በንጹሓን ዜጎች ላይ ሲተኩሱ የነበሩና በሕዝቡ በተሰነዘረ ጥቃት ጉዳት
የደረሰባቸው አራት ወታደሮች በአዲስ አበባ የጦር ኃይሎች ሆስፒታል ህክምና እያደረጉ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም ከምዕራብ ሸዋ
ከአምቦ ከነቀምት ከነጆ ከጊንጪ ከግንደበረት ታፍነው የመጡ ወጣቶች አዲስ አበባ ማዕከላዊ ምርመራ ተብሎ በሚታወቀው እስር ቤት
የተለየ ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን አንዳንድ ምንጮች ይገልጻሉ።
Ø
ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት እሁድ የካቲት 13 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዘገባ በኦሮሚያ
አካባቢ የወያኔ አግአዚ ወታደሮች በሰላማዊ ዜጎች ላይ እያካሄዱት የሚገኙት የግፍ ጭፍጨፋ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን ዘግቧል።
የአግአዚ ወታደሮች ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሚያካሂዱ ዜጎች ላይ የእሩምታ ተኩስ በመተኮስ በርካታ ሰዎች
መግደላቸውን በሺ የሚቆጠሩትን ደግሞ አፍሰው ማሰራቸውን ዘገባው አጋልጧል። የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን መሰረዙንና
አሁኑ ሁኔታው የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ የወያኔ ባለስልጣኖች
ተደጋጋሚ መግለጫ ቢሰጡም እንቅስቃሴው ተባብሶ መቀጠሉን ዘገባው
በዝርዝር ገልጿል። በታኅሣስ እና በጥር ወራት 2008 ዓም ድርጅቱ ያነጋገራቸው ከስድሳ የሚበልጡ ሰዎች የአግአዚ ወታደሮች
በተቃውሞ ስልፎች ላይ ባሄዱት ተኩሶችም ሆነ ዜጎችን ከያዙ በኋላ በርካታ ዜጎች መግደላቸውን
በጅምላ ማሰራቸውናና የያዟቸውንም በቶርቸር ሲያሰቃዩ መቆየታቸውን በማረጋገጥ የመሰከሩ መሆናቸውን ዘገባው ገልጿል።
በአንዳንድ ቦታዎች በመንግስት ንብረቶችና በውጭ ባለሃብቶች ላይ
የደረሰ የዘረፋ ተግባር ቢኖርም ተቃውሞ በአብዛኛው ሰላማዊ እንደነበሩ ድርጅቱ በዘገባው ዘርዝሯል። በአንዳንድ አካባቢዎች
አስተማሪዎች እና ተማሪዎች በአግአዚ ወታደሮች በመታሰራቸው በሌሎች ደግሞ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ባለመሄድ ተቃውሞ በማድረጋቸው
በርካታ ትምህርት ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውም ተዘግቧል። በጥር ወር ላይ የአውሮፓው ፓርላማ ወያኔ እያካሄደ ያለውን ጭፍጨፋ
ቢያወግዝም ለወያኔ ከፍተኛ እርዳታ የሚያደርጉት እንግሊዝ አና አሜሪካ እንዲሁም ሌሎች መንግስታት ድምጽ አለማሰማታቸው ድርጅቱ
የሚያሳስበው መሆኑን ገልጿል።
Ø
በደቡብ ምዕራብ በኢትዮጵያ ኬኒያንና በደቡብ ሱዳን ወሰን ላይ የሚገኘውን ኤለሚ ትሪያንግል የሚባለው ቦታ ሶስቱም አገሮች
የይገባኛል ጥያቄ ያነሱ ሲሆን በቅርቡ በደቡብ ሱዳን እና በኬኒያ እንዲሁም በወያኔ ባለስልጣኖች መካከል ውይይት ለማካሄድ የታቀደ
መሆኑ ተነገረ። የኤሌሚ ትሪያንግል የሚባለው ቦታ የተለያዩ ማዕድናት የሚገኙበት ቦታ ሲሆን እንድ አውሮፓ አቆጣጠር ከ1956 ዓም
ጀምሮ በኬኒያ ቁጥጥር ስር ሆኖ የቆየ ነው። በ1907
ዓም ኢትዮጵያ ከእንግሊዝ ጋር በነበራት ውል መሰረት ቦታው ለኢትዮጵያ ተሰጥቶ ነበር የሚል ማስረጃ አለ ተብሏል።
Ø
ወያኔ
በዘመናዊ
ባርነት ወጣት ሴቶችን ለአረቦች በመሸጥ
የሚያገኘው
ገቢ
በጣም በርካታ መሆኑን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂዎች በቅርቡ ደግሞ
ሕጻናትን ለጉዲፈቻ በማቅረብ
ብቻ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገቢ ያደረገ መሆኑን ይናገራሉ።
አባትና
እናት የሞቱባቸውም ሆነ
ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ
ለቀጥታ ሽያጭ የተዘጋጁ
ህጻናት
ቁጥር
በአሁኑ ወቅት
ወደ 5 ሚሊዮን ይጠጋል ሲሉም
እነዚሁ ወገኖች
አጋልጠዋል ። እናቷ
እያለች ወላጆች
የላትም ተብላ
ለአሜሪካዋ አንጀሊና ጆሊ የተሸጠቸው ሴት ሕጻን ምስክር
ናት ተብሏል ።
በከፍተኛ ደረጃ
ለጉዲፈቻ ሕጻናት
የሚወሱዱባቸው አገሮች
ኮሪያ፤ካምቦዲያና
ሃአይቲ ሲሆኑ በነዚህ ቦታዎች የግዢው ውጋ ውድ
ነው
ያሉ ውስጠ አዋቂዎች የኢትዮጵያን
ልጆች ግን
በርካሽ
ዋጋ ማግኘት ይቻላል
ብለዋል ።
ይህ የሕጻናት ንግድ
በአብዛኛው የሚካሄደው
በወያኔ ወይም
በክልል
አንድ ተወላጆች እንደሆነም
ተጋልጧል ። የኢትዮጵያን ሕጻናት በመግዛት
በኩል ቀዳሚ
የሆኑት አሜሪካ፤ካናዳ፤
ፈረንሳይና ስዊድን ናቸው ።
Ø
የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዋና ተቃዋሚ በመሆናችው ከአርብ ከየካቲት 10 ቀን 2008 ጀምሮ በቤት ውስጥ የቁም እስር ላይ የነበሩት
ሚስተር ቢስግየ ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2008 ዓም ከቤታቸው ለመውጣት ሲሞክሩ በፖሊሶች ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ
የተወሰዱ መሆናቸው ተገልጿል። ፓሊስ ሚስተር ቢስግየ በቁጥጥር ስር ለማዋል የተገደደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዳቸው
ስለተደረሰበት ነው ብሏል። ባለፈው ሐሙስ በተደረገው
ምርጫ ሙሰቨኒ የድምጹን 60 ከመቶ በማግኘት አሸንፈዋል ቢባልም ምርጫው ግልጽነት የሌለበት፤ በፍርሃት እና በሽብር የተካሄደ
መሆኑን አውሮፓው ህብረት ታዛቢዎችና በሌሎችም ወገኖች ገልጸዋል።
ተቃዋሚዎችም ምርጫው መጭበርበሩ ግልጽና ይፋ ስለሆነ ውጤቱን አንቀበልም ብለዋል። ሙሰቨኔ ምርጫው ተጭብርብሯል የሚለውን ክስ
ያጣጣሉት ሲሆን በተቃዋሚዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ጸጥታን ለማስከበር ነው በማለት በተደጋጋሚ ሲናገሩ ተደምጠዋል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በዛሬው ቀን ወደ ብሩንዲ እንደተጓዙ ተግልጿል። ዋና ጸፊው በብሩንዲ ጉዟቸው ከመንግስት
እና ከተቃዋሚ ኃይሎች ባለስልጣኖች ጋር ተገናኝተው የሚወያዩ ሲሆን በሁለቱ ተጻራሪ ወገኖች መካከል ተጀምሮ የነበረውና በአሁኑ
ወቅት ተንጠልጥሎ የሚገኘው የሰላም ውይይት እንደገና ሊጀመር የሚችልበትን መንገድ ያመቻቻሉ ተብሏል። ማክሰኞ የካቲት 15 ቀን
ጠዋት የብሩንዲውን ፕሬዚዳንት በሚያናግሩበት ወቅት የጉዳዩን አሳሳቢነት በማንሳት ከፍተኛ ተጽእኖ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
Ø
በቱኒዚያ ከወራት በፊት ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፕሬዚዳንቱ
ለሌላ አንድ ወር ጊዜ የተራዘመ መሆኑን የመንግስቱ ቃል አቀባይ ገልጿል።
ባለፈው ህዳር ወር በቱኒዚያ በዋና ከተማ በቱኒስ የአይሲስ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 12 ሰዎች ከተገደሉ ወዲህ
በአገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ የሚታወስ ሲሆን አዋጁ ስብሰባንና የተቃውሞ ሰልፍን የሚከለክል እና የጸጥታ ኃይሎች
አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ልዩ ስልጣን የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል። የአዋጁ ጊዜ እንዲራዘም የተደረገው ከሁለት ቀን በፊት
በሊቢያ በአሜሪካ የአየር ጥቃት የተገደለው የአሸባሪዎች መሪ የቱኒዚያ ተወላጅ መሆኑ ከተነገረ በኋላ ነው። በተያያዘ ዜና በሞሮኮ
ዋና ከተማ በመገበያያ ቦታዎች እና በሆቴሎች ላይ ጥቃት
ለመፈጸም ተዘጋጅቶ የነበረ 10 አባላት ያሉት የሽብረተኞች ቡድን በቁጥጥር ስር መደረጉን የሞሮኮ ባለስልጣኖች
ገልጸዋል። የ”ሞሮኮ ሞል” በሚል የሚታወቀው በካዛብላንካ
የሚገኘው የገበያ ቦታ እና ሶፊቴል ሆቴል በጥቃቱ ኢላማዎች ውስጥ
እንዳሉበት ተነግሯል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሞሮኮ የአይሲስ እንቅስቃሴ እየተስፋፋ መምጣቱ ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል ሲሉ
ታዛቢዎች ይናገራሉ።
የካቲት 12 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም ፋሽስት ኢጣሊያ ከ30 ሺ በላይ
የሚሆኑ ኢትዮያውያንን በግፍ የጨረሰበት የሰማዕታት ቀን በዓል በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት የዓለም ክፍሎች ተከብሮ
ውሏል። በየካቲት 29 ቀን 1929 ዓም ፋሽስቱ ግራዚያኒ አርበኞች በጣሉበት ቦምብ በመቁሰሉ ምክንያት ፋሽስቶቹ በወሰዱት የበቀል
እርምጃ በአዲስ አበባ ከተማ ከ30 ሺ የማይንሱ ኢትዮጵያውያንን በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ መፈጀታቸውን በማስታወስ በየአመቱ
ኢትዮጵያውያን ቀኑን ሲያከብሩት መቆየታችው የሚታወስ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ ቦታዎች ተከብሯል። በአዲስ አበባ ከተማ
አርበኞች እና የከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት በየካቲት 12 አደባባይ ቀኑ የተከበረ ሲሆን በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍልና በመላው
ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች አስበውት ውለዋል።
Ø
ሰሞኑን አገርሽቶ እንደገና ተጠናክሮ በመቀጠል ላይ ያለው ሕዝባዊ
ተቃውሞ በተለያዩ ክፍሎች የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። በዛሬው ዕለት በነገሌ ቦረና የአካባቢው አርሶ አደሮች የተሳተፉበት ከፍተኛ
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የተደረገ ሲሆን በግፍ የታሰሩት ባስቸኳይ ይፈቱ፤ የአግአዚ ወታደሮች ከአካባቢው ይውጡ፤ ግድያው ይቁም፤
የአላሙዲ የወርቅ ማዕድን የህዝብ ንብረት ነው የሚሉ መፈክሮችን ሲያሰሙ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪ በትናንትናው
ዕለት በ ወለጋ በጊምቢ እና በጋዎ ቅቤ ከተሞች ተመሳሳይ
ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እንደነበሩ ተዘግቧል። ትናንት በአምቦ ከተማ ዋና እስር ቤት በተቃጠለበት ወቅት እሳቱን በመሸሽ ሲያመልጡ
የነበሩ ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ እስረኞች
በአግአዚ ወታደሮች ጥይት የተገደሉ መሆናችው አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል። በጉደር
ከተማ የኤልከትሪ ኃይል የተቋረጠ ሲሆን የአግአዚ ጦር ከፍተኛ የሆነ ተኩስ ሲያሰማ መቆየቱ ተነግሯል።
Ø
በተያያዘ ዜና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ምክትል ኃላፊ አቶ በቀለ
ገርባ እና ከሳቸው ጋር የተያዙት የፓርቲው አባላት፤ እንዲሁም የነገረ ኢትዮዮጵያ ዋና አዘጋጅ አቶ ጌታቸው ሽፈራውና የሰማያዊ
ፓርቲ አባል አቶ ዳንዔል ተስፋየ አርብ የካቲት 11 ቀን
2008 ዓም ፍርድ ቤት ቀርበው አቃቤ ህጉ ምርመራዬን አልጨረስኩም በማለቱ የ28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ የተፈቀደለት መሆኑ ታውቋል።
አቃቤ ህጉ ተጨማሪ ምርመራ ይቀረኛል፤ ምስክር አላዘጋጀሁም ቢልም ከታሳሪዎቹ መካከል አቶ ጌታቸው ሽፈራው አንድም ሰው
እንድላነጋገቸው ገልጸዋል። በተጫማሪም የአቶ ጌታቸው ጠበቃ ደንበኛቸውን ለማነጋገር እስካሁን ያልተፈቅደላቸው መሆኑን አስረድተው
አቶ ጌታቸውን እንዲያነጋገሩ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
Ø
ትናንት አርብ የካቲት 11 ቀን 2008 ዓም በታላቁ የአንዋር
መስጊድ ሳላት ሲያካሂድ የነበረው የሙስሊሙ ማህበረሰብ የወያኔ አገዛዝ የሚፈጽመውን የግፍ ድርጊት በማውገዝና ፍትህን በመጠየቅ
ከፍተኛ የተቃውሞ ድምጽ ሲያሰማ መዋሉ ታውቋል። በቦታው ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መካከል
ኮሚቴው
ይፈታ
፤
ድምጻችን
ይሰማ፤
ብሄራዊ
ጭቆና
ያብቃ፤
መንግስት
የለም
ወይ
? ነጻነት እንፈልጋለን የሚሉ ይገኙባቸዋል።
Ø
ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም የኡጋንዳ የምርጫ ኮሚሽን
ሀሙስ ዕለት በተካሄደው የአገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት ሙሰቭኒ አሸናፊ ሆነዋል በማለት ይፋ መግለጫ ሰጥቷል።
ፕሬዚዳንቱ ከድምጹ 60.75 አግኝተዋል የተባለ ሲሆን የቅርብ ተወዳዳሪያቸው የነበሩት ሚስተር ኪዛ ቢስግየ 35 ከመቶ ያገኙ
መሆናቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ኅብረት የተዛቢ ቡድን ምርጫው ማስፈራሪያ እና ግጭት የነበረበት በመሆኑ ታአማኒነት አይኖረውም ሲሉ
ተቃዋሚ ድርጅቶች ደግም ምርጫው ተጭበርሯል በማለት በይፋ ተናግረዋል። ሚስተር ቢስግየ ከአርብ ጀምሮ በእስር ላይ
የሚገኙ ሲሆን ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ የተያዙት በዋናው ከተማ ዙሪያ
በፖሊሶች አማካይነት እየተካሄዱ የነበሩትን ህገ ወጥ የምርጫ ሁኔታዎች ለማጋለጥ በሚዘጋጁበት ጊዜ መሆኑን ገልጸው
ምርጫው ግልጽ ማጭበርበር የነበረበት በመሆኑ ውድቅ መሆን አለበት ብለዋል።
ምርጫው የገዥው ፓርቲ አፈና በግልጽ የታየበት
ሲሆን በየቦታው በጸጥታ ኃይሎች ከተወሰዱት የአፈና እርምጃዎች በተጨማሪ አገዛዙ በርከት ያሉ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግየተው
እንዲከፈቱ በማድረግና ግልጽ የሆኑ ማስፈራሪያዎች በማራገብ የተቃዋሚ ደጋፊዎች በተገቢው መንገድ ድምጻቸውን እንዳይሰጡ አድርጓል
ተብሏል። በዛሬው ቀን በካምፓላ ከተማ መንገዶች ላይ የጸጥታ ኃይሎች በብዛት መሰማራታቸው ታውቋል።
Ø
የካቲት 11 ቀን 2008 በሊቢያ የአይሲስ ካምፕ ላይ በአሜሪካ በተደረገው
የአየር ድብደባ ከሶስት ወር በፊት በአይሲስ ተይዘው የነበሩት
ሁለት የሰርብያ ዲፕሎማቶች አብረው የተገደሉ መሆናቸውን ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም የሰርብያ ጠቅላይ ሚኒስትር
ተናግረዋል። በሊቢያ የሰርብያ ኤምባሲ የመገኛኚያ ኃላፊ የነበረውና ይጓዝበት የነበረውን ሲያሽከረክር የነበረው ሹፌር የተያዙት
አምባሳደሩ የሚገኙበት ቡድን በወታደራዊ አጀብ ታጅቦ በሰሜን ሊቢያ ባህር ዳርቻ ላይ ሲጓዙ ከአጥቂዎች በተሰነዘረ የደፈጣ ውጊያ
ነበር። የሰርብያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰዎች በአሜሪካ የአየር ጥቃት መሞታቸውን የሚያረጋግጥ የፎቶግራፍ መረጃ ያገኙ መሆናቸውን
ገልጸው ስዎችን ለማስፈታት በንግግር ላይ እንደነበሩ አስረድተዋል።
Ø
ቅዳሜ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓም በሞሪታኒያ ከዋናው ከተማ
አጠገብ ከሚገኝ ትልቅ እስር ቤት ውስጥ 40 የሚሆኑ እስረኞች ጠባቂዎችን በማጥቃት ከአስር ቤት ያመለጡ መሆናቸው ተዘግቧል።
እስረኞቹ የጠባቂዎቹን የመለዋውጫ
አመች ጊዜ ተጠቅመው ጥቃት በማድረስ አምልጠው በተለያዩ አቅጣጫዎች
የሸሹ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ ታስረው መመለሳቸውና ሌሎት
እየተፈለጉ መሆናቸው ተገልጿል። ከአመለጡት እስረኞች መካከል በአሸባሪነት የተያዙ የአክራሪ ቡድን አባሎች የሌሉበት መሆኑ
ተነግሯል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው ድርጅት በሞሪታኒያ ግለሰቦች በእስር ቤት የጭካኔ ምርመራ የሚካሄድባቸው መሆኑን
አጋልጦ የእስር ቤቱም ሁኔታ አስከፊ መሆኑ ዘግቧል።
በዛሬው ዕለት እስረኞቹ ያመለጠበት እስር ቤት 400 ሰዎችን ብቻ
የሚያስተናግድ ቢሆንም ከ1200 ሰዎች በላይ የታሰሩበት ነው ተብሏል።
የካቲት 11 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በአዲስ አበባ መስፋፋት ስም ታቅዶ በነበረው አይን ያወጣ ዘረፋ ተጀምሮ
በንጹኃን ዜጎች ላይ የተወሰደው የግድያና የእስራት ዘመቻን ይቁም በማለት እየተቀጣጠለ ያለውና የሕዝብ ብሶት የወለደው
የተቃውሞ እንቅስቃሴ ትናንት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓ/ም እና ዛሬም የካቲት 11 ቀን
በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ቀጥሎ መዋሉና ዜጎች መጎዳታቸውን ከየአካባቢው የደረሰን ዘገባ አስረድቷል። ትናንት የካቲት
10 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦ እና በጉደር ያሉ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸው በታጠቁ የአግአዚ ወታደሮች የተሰበረ ሲሆን ሰላማዊ
ዜጎች እየታፈኑ ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች መናገራቸው በዘገባው ተመልክቷል። ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ ለመውሰድ
በተደረገው ሙከራ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን ከአግአዚ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል የሚል ዜና አለ። በዛሬው ዕለትም በአምቦ
የሚገኘው ዋናው እስር ቤት ተቃጥሏል የሚል አንዳንድ ምንጮች ዘግበዋል።
የካቲት 10 ቀን 2016 ዓም በምዕራብ አርሲ አሳሳ በሚባለው ከተማ የወያኔ ቅልብ ወታደሮች
ሰላማዊ ሰዎችን ዘግናኝ በሆነ መንገድ ሲደበድቡ ነበር በማለት ምንጮች የገለጹ ሲሆን ትምህርት ቤቶችና መስሪያ ቤቶች
ስራ አቁመው መዋላቸው ተነግሯል። በምስራቅ ሀረርጌ የኦህዴድ
ጽህፈት ቤት ላይ ጥቃት መድረሱንና በሕዝባዊ ተቃውሞው ማዕበል መመታቱን የሚገልጹ ምንጮች የአህዴድ ሹማምንቶች ጽህፈት ቤቱንና
መኖሪያቸውን ጥለው የሸሹ መሆናቸውን አክለው ገልጸዋል። እንዲሁም በዛሬው ዕለት በምዕራብ ሀረርጌ በጭሮ ከተማ አካባቢ መንገድ
የተዘጋ መሆኑ አንዳንድ ምንጮች ገልጸዋል። በትናንት የካቲት 10 ቀን የአግአዚ ወታደሮችና በአድማ ብተና ልዩ ስልጠና የተሰጣቸው
ናቸው የተባሉ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ምሽቱን ተጉዘው ባሌ መግባታቸውን ለማወቅ ተችሏል። አርጆ ከተማ ላይ መንገድ በመዘጋቱ
የጅማ የነቀምት የትራንስፖርት መንገድ አገልግሎት መቋረጡን በትራንስፖርት ስራ ላይ የተሰማሩ አሽከርካሪዎች መናገራቸው ታወቋል
Ø
አንዳንድ የወያኔ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በወገናቸው ላይ እየተካሄደ ያለውን አሰቃቂ የሆነ ጭፍጨፋ
መቃወማቸውና ጥያቄ ማቅረባቸው ቀደም ብሎ መዘገቡ የሚታወስ ሲሆን ወያኔ በሰራዊቱ ውስጥ የተፈጠረውን ክፍተት ለማጥበብና ለሰራዊቱ
የማዕረግ እድገት ለመስጠት ሴራ ያቀደ መሆኑን ምንጮች አጋልጠዋል። የማዕረግ እድገት ለመስጠት የታሰበው
በያዝነው ወር የሚከበረውን የመከላከያ ሠራዊት ክብረ በዓል
ምክንያት በማድረግ ሲሆን በአብዛኛው ለበታች የሠራዊቱ አባላት
እንደሆነ ምንጮች ገልጸዋል። ለህገ መንግስቱ ታማኝ መሆን አለበት የሚባለው ሠራዊት ከድንበር ጥበቃ ይልቅ የመብት ጥያቄ ባነሱ
ሰላማዊ ሰዎች ላይ ቃታ መሳቡ ተገቢ አይደለም በሚል ቅሬታቸውን ለአቆቻቸውና እንዲሁም ለግምገማ በተዘጋጀ መድረክ በአደባባይ ላይ
ሲናገሩ የነበሩ መስመራዊ መኮንኖች በአሉታዊ ከመገምገማቸው አልፎ
ትጥቅ እንዲፈቱ ተደርገው የነበሩ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። ተቃውሞውን በሰፊው የሚያነሱትና የሚያባብሱት የበታች ወታደሮች
በመሆናቸው ወያኔ ጥያቄያቸውን ለማቀዝቀዝ የማዕረግ አድገት ሴራ
ጠንስሷል ተብሏል። በዚህ ሳምንት ማብቂያ ላይ በድሬዳዋ
የሚገኘው የምስራቅ እዝ የሠራዊቱ የበታች መኮንኖች የመስመራዊ መኮንነት እድገትና ለተራ ወታደሮች ደግሞ
የክንድ ማዕረግ እንደሚሰጥ ታውቋል።
Ø
ከአመታት በፊት በአዋጅ መልክ ጸድቆ በኦሮሚያ ክልል ተግባራዊ ተደርጎ የነበረው የጸረ ሙስና ህግ በድጋሚ
ማስተካከያ ሊደረግለት የታሰበ መሆኑ ታውቋል። ለህጉ መስተካከል በመልካም አስተዳደርና በኪራይ ሰብሳቢነት ለሚያጠፉ አጥፊዎች
ክፍተት ይሰጣል የሚል የማታለያ ምክንያት ከአገዛዙ ይሰጥ
እንጂ እቅዱና የመስተካከሉ ዓላማ ሌላ ነው በማለት የታመኑ ምንጮች
ያስረዳሉ። ሕጉ እንዲስተካከል የተፈለገው የኦሮሚያ ፕሬዚዳንትንም
ሆነ ከፍተኛ ባለስልጣኖችን ሊያስከሥስ የሚፈቅድ አንቀጽ የለውም በሚል ምክንያት ሲሆን ዋናው ዓላማ ግን እነሙታር ከድርና
ለመወንጀልና ለመቅጣት ነው ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከየኦሮሚያ ምክር ቤት እንዲያጸድቀው ከወያኔ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተሰጠ ሲሆን
በተሻሻለው እና በተጨመረው አንቀጽ ላይ የይስሙላ ውይይት ቢሾፍቱ ላይ እንዲደረግ መወሰኑን ከዘገባው ለመረዳት ተችሏል።
Ø
የወያኔ አገዛዝ በቅርቡ ተጨማሪ ወታደሮች ወደ ሱማሊያ የላከ መሆኑ ውስጥ አዋቂ ምንጮች አጋልጠዋል።
በሱማሊያ ተዳክሟል ሲባልለት የቆየው የአልሸባብ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመቀጠሉ ምክንያትና እንዲሁም የወያኔ ጦር ከፍተኛ ጉዳት
የደረሰበት በመሆኑ ተጨማሪ ጦር መላክ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም ምክንያት ቁጥሩን በውል ለማወቅ ያልተቻለ ጦር ሰሞኑን
ባስቸኳይ ወደ ሱማሊያ የተጓዘ መሆኑ ተነግሯል። ከዚህ በተጨማሪ
በሱማሊያ ውስጥ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አሰባሪ ኃይል ወያኔ እና ኬኒያ የጦርና የማመላለሻ ሄሊኮፕተሮች
ለመስጠት መስማማታቸውን ለማወቅ ተችሏል።
Ø
ትናንት የካቲት 10 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ ብሔራዊ ምርጫ
የተካሄደ ሲሆን እንደተጠበቀው የኡጋንዳ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአሁኑ ፕሬዚዳንት ሙሴቨኒ በምርጫው መሪነቱን የያዙ መሆናቸውን
ገልጿል። ዛሬ የካቲት 11 ቀን ቀን በተጻራሪነት በመቆም የፕሬዚዳንቱ ግምባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆኑት
ኪዛ ቢስግየ በፓርቲያቸው ጽሕፈት ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ
ለመስጠት በሚዘጋጁበት ወቅት በፖሊሶች ተይዘው የተወሰዱ መሆናቸው ታውቋል። ከፓርቲው ጽ/ቤት ውጭም በደጋፊዎቻችው ላይ
የሚያስለቅስ ጋዝ መተኮሱ ተነግሯል። ሚስተር ቢስግየ በፖሊሶች ተይዘው ሲታሰሩ ይህ ሶስተኛ ጊዜያቸው ሲሆን በዛሬው ዕለት በምን
ምክንያት እንደተያዙ ፖሊሶች የሰጡት ምክንያት የለም። ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዳልሆነ ብዙዎቹ እየተናገሩ ነው። በትናንትናው
ዕለት በርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግየተው የተከፈቱት መራጩ ድምጹን እንዳይሰጥ ተስፋ ለማስቆረጥ የተደረገ ሲሆን በትናንትናው
ዕለት ሳየከፈቱ ቀርተው ዛሬ ድምጽ የሚያሰጡ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውንም ለማወቅ ተችሏል። በትናንትናው ዕለት የቲውተርና የፌስ
ቡክ እንዲሆም የኢንተርኔት አገልግሎቶች እንዲቋረጡ የተደረጉ መሆናቸውም ይታወቃል። ወገንተኛነቱ ለሙሰቬኒ መሆኑ የሚነገርለት
የምርጫ ቦርድ እስካሁን በተቆጠረው ምርጫ ሙሰቨኒ 60 ከመቶ በማግኘት እየመሩ መሆናቸውን ገልጿል።
Ø
በደቡብ ሱዳን የርስ በርስ ጦርነት ምክንያት ከተሰደዱ
ዜጎች መካከል የሆኑና
እና ማላካል
በተባለ ሰፈር ተጠልለው የነበሩ ስደተኞች በእርስ በርስ የጎሳ ልዩነት በፈጠሩት ግጭት 18
መሞታቸውናና
ወደ 40
የሚደርሱ
መቁሰላቸው ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት ድርጊቱን ያወገዘ
መሆኑ ተነግሯል።
በዲንካዎችና
በሺሉኮች መሀል የተቀሰቀሰው ግጭት ተስፋፍቶ ዲንካዎችን ከኑዌሮችም ጋር አጋጭቷል ። የጎሳ
ልዩነት መዘዙ ብዙ ለመሆኑ የደቡብ ሱዳን ምሳሌነት ያለ ነው ። ስምምነት የተፈጠረና
ሰላም
የወረደ መሆኑ ቢነገርም
ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ተጻራሪያቸውን ሪያክ ማሻርን ሳይጠብቁ የሽግግርና የአንድነት መንግስት
ለመመስረት መነሳታቸው ራሱ ቀውሱን እንደገና ቀስቅሶታል ተብሏል። ጣልቃ ገብ የውጭ ሀይሎች የችግሩን
ምስረታ
ምንጭ በማድረቅ ፈንታ የእራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ በመጣራቸው ችግሩ የሚቀረፍ አልሆነም ተብሏል።
Ø
የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች በሊቢያ የሚገኘውን የአይሲስ የማሰልጠኛ
ጣቢያን የደበደቡ መሆኑ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። በአየሩ ድብደባ ከ40 በላይ የሆኑና አብዛኞቹ የቱኒዚያ ዜጎች ናቸው
የሚባሉ ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ኑረዲን ቹሴን የተባለውም መሪ ሳይገደል አይቀርም የሚል ግምት ተወስዷል።
ኑረዲን ቹሴን ባለፈው ዓመት ለ30 የእንግሊዝ ተወላጆች
መገደል ምክንያት የሆነውንና በቱኒሲያ የተካሄደውን የሽብር ተግባር
የመራ ነው ተብሏል። በሊቢያ የሚገኘው የአይሲስ ቡድን መንቀሳቀስ ከጀመረ አንድ ዓመቱን ያስቆጠረ ሲሆን 6000 የሚሆኑ የታጠቁ
ተዋጊዎች እንዳሉት ይገመታል። የቀደሞ አምባገነን መሪ ጋዳፊ ከስልጣን ከተወገዱ ካለፉት አራት አመታት ወዲህ ሊቢያ በቀውስ ላይ
የምትገኝ ሲሆን ቀውሱ እንዲፈጠርና እንዲባባስ ያደረጉት ምዕራባውያን ናቸው በሚል አስተያየት የሚሰነዝሩ በርካታ ናቸው።
Ø
ዛሬ የካቲት 11 ቀን 2008 በሰሜን ካሜሩን ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች
የመንገድ ላይ ነጋዴዎች መስለው ቦምቦች አፈንድተው ጉዳት ያደረሱ ሲሆን ሌሎች ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ደግሞ በአንድ ትምህርት ቤት
ላይ ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመዋል። ከሁለቱም ቦታዎች ከ20 ሰዎች በላይ ሲገደሉ ከ70 በላይ መቁሰላችውና ወደ ሆስፒታል መወሰዳችው
ተሰምቷል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በሰሜን ካሜሩን በተደጋጋሚ ጥቃት መፈጸማቸውና ጉዳት ማድረሳቸው በየጊዜው ተዘግቧል።
Ø
በግብጽ አንድ የፖሊስ አባል የተራንስፖርት መኪና አሽከርካሪ
የትራንስፖርት ዋጋ በዝቷል በማለት
ሹፌሩን መግደሉን ተከትሎ በቁጣ የተነሳሳው ሕዝብ ፖሊሱን ከመደብድቡ በተጫማሪ መንገድ በመዝጋት ተቃውሞውን የገለጸ
መሆኑን ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል። የግብጽ መንግስት የፖሊስ አባሉ የታሰረ መሆኑን መግለጫ ቢሰጥም የሕዝቡ አመጽ
ያልበረደ መሆኑ ተነግሯል። የግብጽ ሕዝብ ለወታደሩ አገዛዝ ያለውን ጥላቻ እየገለጸ መሆኑ የሚታይ ሲሆን ባለፈው ሳምንት ውስጥም
የሆስፒታል ዶክተሮችና ሰራተኞች ፖሊሶች የአስቸኳይ ጊዜ ህክምና ክፍሎችን ማጥቃታቸውን ተከትሎ ተቃውሞ ማሰማታችው ይታወሳል።
የግብጽ ፖሊሶችና ወታድሮች ለሰሩት ጥፋት ተጠያቂ አለመሆናቸውና ለፍርድ አለመቅረባቸው ሕዝቡን እያስመረረው ያለ ክስተት
መሆኑን የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ።
የካቲት 10 ቀን 2008 ዓም
Ø
በአንዳንድ አካባቢዎች የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በአርሲ ኮፈሌ መንገድ ተዘግቶ
በተካሄደ ከፍተኛ ተቃውሞ አራት ሰዎች መገዳላቸውና በርካቶች ለእስር መዳረጋቸው ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።ዛሬ
በምዕራብ አርሲ አዶ ከተማ የአግአዚ ወታደሮች ለሊቱን ቤት ለቤት በመግባት ወጣቶችን እያስወጡ ሲደበደቡ ማደራቸውንና
የታፈሱት ወጣቶች
በመሳሪያ ሰደፍ እየተመቱ ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል። ቤተሰቦቻቸውና የአካባቢው
ነዋሪዎች ድርጊቱን በመቃወም ከፍተኛ የሆነ ጩኸት
ከማሰማታቸውም በላይ ድንጋይ በመወርወር ለመከላከል መሞክራቸው ከአካባቢው የመጣው ዜና ጨምሮ ይገልጻል። በተመሳሳይ ዜና
በሀረርጌ ግራዋ ወረዳ ኦሮሚቱ ከተማ አህመድ ከማል በተባለው የከተማዋ አስተዳዳሪ ጥሪ ወደ ኦሮሚቱ ዘልቆ በነበረው
ነብሰ ገዳይ ወታደር አደም የተባለ የአስራ ዘጠኝ አመት እድሜ ያለው ወጣት መገደሉን የደረሰን መረጃ አሰረድቷል።
በዛሬው ቀን በተጨማሪ በምዕራብ አርሲ ዋቤ ከተማ በምስራቅ ሀረርጌ ግራዋ ዶጉ እና ቆቦ ከተሞች እንቅስቃሴዎቹ የቀጠሉ
ሲሆን በአምቦና በጉደር ከተሞች ወደ መንደሮች የሚያስገቡ መንገዶች መዘጋታቸው ተዘግቧል። በተያያዘ ዜና ለጂቡቲው ፕሬዚዳን
ለኦማር ገለህ ተሰጥተው የነበሩ የስሮፍታ እና የጎፈር የመንግስት እርሻዎች በተቃዋሚዎቹ በእሳት መቃጠላቸው አንዳንድ ምንጮች
ገልጸዋል።
Ø
ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓ/ም በአርሲ በሲንቂሌ ከተማ አካባቢ ቆርኪዎች በሚገኙበት ብሄራዊ ፓርክ
ላይ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በእንስሳቱ ላይ ጉዳት ባያደርስም እሳቱ ሙሉ በሙሉ አሁንም አለመጥፋቱን
ከስፍራው የደረሰበ ዘገባ ያስረዳል።ወያኔ ቃጠሎው የተነሳው የጸረ ሰላም ኃይሎች በለኮሱት እሳት ነው በማለት የሞከረ
ሲሆን በእሳቱ ምክንያት በእንስሳት ላይ ጉዳት ባይደርስም ዛፎች መቃጠላቸውና ፓርኩ መጎዳቱን የአይን እማኞች ይናገራሉ።
በከሁለት ወራት በፊት አንድ ቆርኪ መገደሉን ተከትሎ ሀምቢቱና
ዳዌ በተባሉ ጎሳዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ የነበረ መሆኑና በአባገዳዎች ከፍተኛ ጥረት ግጭቱን በፈጠሩት መካከል እርቅ
እንዲሰፍን ለማድረግ ጥረት ተደርጎ እንደነበር የአካባቢው ሰዎች ይናገራሉ። ከታመኑ ምንጮች ለማወቅ እንደተቻለው ዛሬ የካቲት 10
ቀን 2008 ዓም እና ነገ የካቲት 11 ቀን 2008 ዓም ልዩ የአግአዚ ጦር ወደ ስፍራው ተልኮ ካምፕ ሊመሰረት ታቅዷል ተብሏል።
Ø
በድርቅ ምክንያት የተጎዱ ዜጎች
የምግብ እርዳታ ማግኘት የሚችሉት በሴፍትኔት ከተደራጁ ብቻ መሆኑን ከትግራይ የመጣ ዘገባ ይገልጻል። በረሃብ የተጎዱ ስድስትና
ከዚያ በላይ የቤተሰብ አባላትን በኃላፊነት የሚያስተዳደሩ
አባወራዎች እርዳታ የሚሰጣችሁ ለአምስት የቤተሰብ አባላት
ብቻ ነው እየተባሉ የቤተሰቦቻቸው ቁጥር ከስድስት በላይ የሆኑ ቤተሰቦች እርዳታ መከልከቸውን የተገኘው ዘገባ አስረድቷል።
የተሰጠን መመሪያ በሴፍቲ ኔት ለተደራጁ አምስት የቤተሰብ አባሎች ብቻ ነው በማለት በግለስብ አ15 ኪሎ ስንዴና በቢራ ጠርሙስ
የተሰፈረ ዘይት ብቻ ለአምስት የቤተስ ሰብ አባላት ብቻ ሲሰጥ ከዚያ በላይ ቁጥር ያላቸው ቤተሰቦች እርካታ ተከልለው ከፍተኛ
ችግር ላይ መሆናቸውን የራያና አዘቦ ነዋሪዎች በምሬት እየገለጹ ይገኛሉ። ከዚህ በተጨማሪም በረሃብ የሚሰቃዩት ዜጎች ውሃ
ለማግኘት ሩቅ ስፍራ እንደሚጓዙና ከውጭ እርዳታ ተገኝቷል የተባለውን የህጻናት አልሚ ምግብ የሆነ አይተውት እንደማያውቁ
ተናግረዋል። በሌሎች የትግራይ ክፍሎችም ድርቁና ረሃቡ በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋቱና ዜጎች ከፍተኛ ችግር
ላይ መሆናቸው እየተነገረ ሲሆን የተቃዋሚ ኃይሎች ደጋፊዎች ናችሁ
በሚል የእርዳታ እህል የሚከለከሉ ዜጎች በርካታ መሆናቸውንም ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ።
Ø
ረቡዕ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓም በቱርክ ዋና ከተማ በአንክራ አንድ መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ
ወታደሮችን ጭኖ ይጓዝ በነበረ አውቶቡስ አጠገብ በመፈንዳቱ 28 ወታድሮች ሲገደሉ ከ61 በላይ የሚሆኑት የአካል ጉዳት
የደረሰባቸው መሆኑ ተዘግቧል። ዛሬ ሀሙስ የካቲት 10 ቀን ረፋዱ ላይ ደግሞ በደቡብ የቱርክ ግዛት አንድ ወታደራዊ የማመለሻ
መኪና በመንገድ ላይ በተቀበረ ፈንጅ ተመትቶ ቢያንስ ስድስት
ወታድሮች መሞታቸውና ሌሎች መቁሰላቸው ተዘግቧል። የአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በአንካራ ከተማ የፈንዳውን ቦምብ ያጠመደው
ሳሊህ ኔካር የሚባል የሶሪያ ተወላጅና የሶሪያ የኩርድ ድርጅት አባል መሆኑን ቢናገሩም በሶሪያ እና በቱርክ የሚገኙ የኩርድ
ድርጅቶች አመራር አባላት ለቦምቦቹ መፈንዳት እጃቸው የሌለበት መሆኑን ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን
ምንም እንኳ በሶርያ እና በቱርክ የሚገኙ የኩርድ ድርጅቶች መሪዎች ለቦምቡ መፈንዳት ኃላፊነት መውስደኡን ቢክዱም ቦምቡን
ያፈነዱት ድርጅቶቹ መሆናቸውን የሚያስረዱ ተጨባጭ መረጃዎች ስላሉን እርምጃ እንወስዳለን ብለዋል። የቱርክ መንግስት ፒኬኬ
በተባለው የቱርክ ኩርድ ድርጅት ላይም ሆነ ዋይ ፒ ጄ በሚባለው የሶሪያ ኩርድ ድርጅት ላይ እወስደዋለሁ
የሚለው እርምጃ ችግሮችን ከማቀጣጠል ውጭ
የሚያመጣው ውጤት የለም በማለት ያቀጣጥላል የፖሊቲካ ታዛቢዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።
Ø
መሀመድ ካራቲ የተባለው የአልሽባብ የኢንተለጀንስ ኃላፊ ከሌሎች 10 የአልሸባብ ወታደራዊ መሪዎች ጋር
በመሆን በኬኒያ የአየር ጥቃት የተገደለ መሆኑን የኬኒያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። በየአይር ጥቃቱ የአልሸባብ አባላት የተገደሉት
በጥር 30 ቀን 2008 ዓም በደቡብ ሶማሊያ ውስጥ ሲሆን በጥቃቱ
ሌሎች 40 የሚሆኑ የአልሸባብ አባላት ተገድለዋል ተብሏል። ባለፈው ወር ከ100 በላይ ለሆኑት የኬኒያ ወታደሮች ሞት ምክንያት
ለሆነውና በኬኒያ የጦር ሰፈር ላይ ለተወስደው እርምጃ
መሀመድ ካራቲ ቁልፍ ሚና የነበረው መሆኑን የኬኒያ ባለስልጥኖች
ገልጸዋል። አልሸባብ መሀመድ ካራቲ አልሞተም በማለት ዜናውን ያስተባበለ መሆኑ ታውቋል።
Ø
ዛሬ በዩጋንዳ በተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ላይ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች መከፈት ከነበረባቸው ስድስት
እና ሰባት ሰዓት ዘግየተው እንዲከፍቱ በመደረጉ በርከት ያሉ ወገኖች ቅሬታቸውን መግለጻቸው ታውቋል። ጣቢያዎቹ ዘግየተው
በመከፈታቸው የምርጫ ታዛቢዎች ሁኔታው አሳሳቢ ነው ያሉ ሲሆን የፕሬዚዳንቱ ተቃውሚዎች ደግሞ መራጮችን ተስፋ አስቆርጦ ወደ
ቤታቸው እንዲሄዱ ለማድረግ በመንግስት በኩል ሆን ተብሎ የተወስደ የተንኮል እርምጃ ነው ብለውታል። በአንዳንድ አካባቢዎች መራጮች
የምርጫ ካርዶች እስከመጡ ድረስ ከሰባት ሰዓታት በላይ ተሰልፈው ሲጠብቁ መዋላቸው ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሙሰቬኒን ሊያሸንፉ
ይችላሉ ተብለው የተገመቱት ኪዛ ቤሲግየ ሙሰቨኒን በአምባገነንት የከሰሷቸው ሲሆን ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ ለመሆኑ ጥርጣሬ ያላቸው
መሆኑን ገልጸዋል። በ28 ሺ የምርጫ ጣቢያዎች እ 15 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የካቲት 09 ቀን 2008
ዓ.ም.
Ø
በምዕራብ አሩሲ
በተከሰተው ሕዝባዊ አመጽ ሰባት የአግአዚ ወታደሮች መገደላቸውና በርካታ የወያኔ ንብረት መውደሙን በመግለጽ በትናንትናው ዘገባችን
መግለጻችን ይታወሳል። ባለፈው አርብ በምዕራብ አሩሲ አጄ በተባለች ከተማ የተቀሰቀሰው አመጽ ወደ ሻላ ሲራሮና ሻሸመኔ ከተሞች
ተዛምቶ በርካታ ጉዳት የደረሰ መሆኑ ተዘግቧል። የሕዝቡን እንቅስቃሴ ለማብረድ የወያኔ አግአዚ ጦር በከፈተው ተኩስ ቁጥራቸው
በውል ያልታወቀ ዜጎች መሞታቸው የተገመተ ቢሆንም በሻሽመኔ ኩየራ ሆስፒታል ህክምና ሲደረግላቸው ከነበሩት መካከል ቢያንስ አምስት
ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን በሻሸመኔ የሚገኙ የአይን እማኞች ገልጸዋል። ትናንት የካቲት ስምንት ቀን በሀገረ ማርያም ከተማ በእሳት
መጋየቱ እና እንዲሁም በአዶላ ከተማ አንድ የወታደር ካምፕ መቃጠሉን ከስፍራው የሚመጡ ያልተረጋገጡ ዜናዎች ይገልጻሉ። ከሻሽመኔ
በተለያዩ አቅጣጭዎች የሚሄዱ መንገዶች ዝግ ሆነው መቆየታቸው እየተሰማ ሲሆን ከከተማው አካባቢ በአካባቢው ያሉ እንደ አዶላ
የመሳሰሉ ቦታዎችም የአመጽ እንቅስቃሴ ታይቶባቸዋል።
ከኮፈሌ የሚያስወጡት መንገዶች በተቃዋሚዎች መዘጋታቸው
ከሚደርሱ ዘገባዎች ለማወቅ የተቻለ ሲሆን የአግአዚ ጦር ወደ ቦታው እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በዛሬው ቀን
በሰሜንና
በምስራቅ ሸዋ በምዕራብ ወለጋ እና በምስራቅ ሀረርጌ አመጹ
እየተስፋፋ መሆኑ እየተነገረ ነው።
Ø
የአንድነት
ለዴሞክራሲና
ለፍትሕ
ፓርቲ (አንድነት)
አመራር
አባል
አቶ
ሀብታሙ
አያሌውና
መምህር
አብረሃም
ሰለሞን፣
ማክሰኞ
የካቲት 8
ቀን 2008
ዓ.ም.
ከእስር
የተፈቱ መሆናቸው
ታውቋል፡፡ ባለፈው ሐሙስ የካቲት 3
ቀን 2008
ዓ.ም.የፌዴራል
ጠቅላይ
ፍርድ
ቤት
ይግባኝ
ሰሚ
ችሎት
አቶ
ሀብታሙ
አያሌው፣
አቶ
ዳንኤል
ሺበሺ፣
አቶ
አብረሃ
ደስታ፣
አቶ
የሺዋስ
አሰፋና
መምህር
አብረሃም
ሰለሞን
ከእስር
እንዲፈቱ፣
መወሰኑን ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወሳል።
ፍርድ
ቤቱ
በሰጠው
ውሳኔ መሰረት
የመፍቻ
ትዕዛዝ
ለማረሚያ
ቤት
አስተዳደር
መድረሱ
የተረጋገጠ
ቢሆንም፣ ከእስረኞቹ
መካከል ሁለቱ ሲፈቱ ሌሎች እስካሁን ያልተፈቱ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
ከሚዛን ወደ ቴፒ ሃምሳ ስድስት ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው የቴፒ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ መኪና ድልድይ
ውስጥ ገብቶ የአስራ አምስት ሰዎች ህይወት ወዲያወኑ ሲያልፍ 30 የሚሆኑ ከባድ በሆነ ሁኔታ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ
ታውቋል። ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ለህክምና ወደ ሀዋሳ ሲወሰዱ የተቀሩት አስር ሰዎች መኪናው የተጫናቸውና በውሃ የተወሰዱ
መሆናቸውን ዘገባው አመልክቷል። በሰርቪሱ ውስጥ የነበሩት
ሟቾችና ተጎጂዎች አብዛኞቹ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ማኅበረሰብ አባላት ናቸው።
Ø
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ፍራንስዋ ሜክሲኮን ሲገበኙ
በዚያች ሀገር
በሚኖሩ ውህዳን ብሄረሰቦች ላይ በቤተ ክርስቲያኗ የተደገፈ ፍጅትና በደል መድረሱን አምነው ሕዝቦቹን ይቅርታ መጠየቃቸው ታውቋል። ለጳጳሱ
የይቅርታ ጥያቄ ከፍተኛ አድናቆት የሰጡ ክፍሎች
የካቶሊኳ ቤተ ክርስቲያን
ከሙሶሊኒን ተባብራ በኢትዮጵያ ላይ
ላደረሰችው በደልና ግድያ እስካሁን ይቅርታ አለመጠየቋ የሚያስወቅሳት ነው ብለዋል። ሰሞኑን የሚከበረውን
የአድዋ ድል ታሪክ ለመፋቅ
ፋሽስቱ
ሙሶሊኒ ወራሪ ጦሩን ወደ ኢትዮጵያ
ሲልክ በወቅቱ የነበሩት
ጳጳስና ቤተክርስቲያኗ በአጠቃላይ ዘመቻው "አህዛብ የሆኑትን
አረመኔዎች ለማሰልጠን
የተደረገ ዘመቻ ነው” በሚል ሙሉ ድጋፍ በይፋ መስጠታቸው የሚታወስ ነው ።
ጣሊያን ባደረገው ወራራ ወደ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አልቀዋል ።
የካቶሊክ ቤተክርስያን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ
እንድትጠይቅ ላለፉት 30 ዓመታት ኢሕአፓ
ለቫቲካን ባለስልጣኖች በተደጋጋሚ ጥያቄ ያቀረበ መሆኑንና
እስካሁም
መልስ
አለማግኘቱን ድርጅቱ ለፍኖተ ዴሞክራሲ
በሰጠው መግለጫ ገልጿል ።
Ø
በአባይ ጉዳይ የተነሳ ግብጽ ከጥንት ጀምሮ ለኢትዮጵያ ደግ
የማትመኝና ተንኮል ስትሰራ የቆየች ሀገር ብትሆንም በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃና በተለይም በአፍሪካ ቀንድ
ሳውዲ አረቢያ ዋናዋ ጸረ ሰላም ሀገር ሆነ ተገኝታለች ሲሉ የፖለቲካ
ተመራማሪዎች
አሳስበዋል ። በአሁኑ ወቅት ሳውዲ አረቢያ በካታር
እየታገዘች መሆንዋ
የሚታወቅ ሲሆን
ሳውዲና
ቃታር
ወደ ኢርትራ ገብተው ጦር ሰፈሮችን
በማቋቋም
የመንን ለማጥፋት
ዘመቻ ላይ መሆናቸውንም
ከዕይታ ማራቅ አያስፈግም ብለዋል ። አይሲል የተባለውን ሆን አልቃይዳን በመርዳት ዋና የሆነችው ሳውዲ አረቢያ ጸረ
ኢትዮጵያ ገንጣይ ሀይሎችን --ወያኔን፤ ኦሮሚያ እስላሚያ፤የኦጋዴን ቡድኖችን-- በቀጥታም ሆነ በሱዳን በኩልም ስትረዳ መቅየትዋን
ጠቅሰዋል ። ሳውዲ በጦር ሀይል ወደ ኤርትራ መግባቷ ለኢትዮጵያ በቀላሉ የሚታይ አደጋ አይደለም ሲባል
ግብጽን ባሕር ዳር ያስገባና በአዲስ አበባም መሬት ሊሰጥ የተነሳው ከሃዲው የወያኔ ቡድን ይህን በተመለከተ ይህ ነው
የሚባል ተቃውሞ እንዳላሰማም ተጋልጧል ።
Ø
ብሩንዲ በንግድ ላይ
የተሰማሩትን የሞተር ቢስክሌት ታክሲ የከለከለች መሆኑ ከስፍራው ከተገኘ ዜና ማወቅ ተችሏል። በሞተር ቢስክሌት ላይ በመሆን
አጥቂዎች የሚያካሄዱት ግድያዎች እየበረከቱ በመምጣታቸው የብሩንዲ ባለስልጣኖች የሞተር ቢስክሌት ታክሲን ለመከልከል የተገደዱ
መሆናቸውን ገልጸዋል። ባለፈው ሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ በሞተር
ቢስኪሌት ላይ የተቀመጡ ሰዎች በወረወሯቸው ሶስት የእጅ ቦምቦች አንድ ሰው ሲሞት ሌሎች ቁጥራችው ያልታወቀ ሰዎች መቁሰላችው
ተዘግቧል። የሞተር ቢስኪሊት ታክሲ መከልከሉ በብሩንዲ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር የሚያመጣ ሲሆን በመስኩ
በተሰማሩ ዜጎች ላይም የኑሮ ችግር እንደሚፈጥር ታውቋል።
Ø
የቀድሞ የተባብሩት
መንግስታት ዋና ጸሐፊ የነበሩት ግብጻዊው ጴጥሮስ ጴጥሮስ ጋሌ በ93 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በ1985
የተባበሩት መንግስታ ዋና ጸሐፊ ሆነው የተሾሙት ጴጥሮስ ጵጥሮስ ጋሌ በሩዋንዳና በቦስኒያ የደረሰውን እልቂት ለማስቆም የወሰዱት
ርምጃ ደካማ ነበር ተብለው የተወቀሱ ሲሆን ኢርትራን ከኢትዮጵያ በማስገንጠል በኩል ቁልፍ ሚና ተጫውተዋ ተብለው በኢትዮጵያውያን
መከሰሳቸውም አይዘነጋም። የመጀመሪያውን የስልጣን ዘመም ከአምስት በኋላ ሲጨርሱ በአሜሪካ ተጽእኖ ሌላ የስልጣን ዘመን
ያልታደሰላቸውና ከስልጣን የተነሱ መሆናችው ይታወቃል። በተመሳሳይ ዜና የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት የጋማል አብደል ናስር አማካሪ
የነበሩትና ለ20 አመታት ጊዜ የግብጹ ታዋቂ ጋዜጣ የአልአህራም
አዘጋጅ የነበሩት መሀመድ ሃይከል ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2008 ዓም በ92 ዓመታቸው መሞታቸው ተነግሯል። አልአህራም ጋዜጣ በአረቡ
አለም ተወዳጅ የነበረ ሲሆን ታዋቂነታቸውም ከጋዜጣው ተወዳጅነት ጋር ተያይዞ የመጣ ነው። ሃይከል በፕሬዝዳንት ናስር የስልጣን
ዘመን የፕሬዚዳንቱ አማካሪ ከመሆናችው በተጨማሪ ለአጫጭር ጊዜያትም የማስታወቂያ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው
አገልግለዋል።
የካቲት 08 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በምእራብ አሩሲ በተካሄደ የሕዝብ
ተቃውሞ ከ7 ያላነሱ የአግአዚ ጦር አባላት የተገደሉ መሆኑን ከአካባቢው የመጣው ዜና ያስረዳል። ባለፈው አርብ ወታደሮች በአንድ
አውቶቡስ ተጭነው በሚሄዱ ሰልፈኞች ላይ ተኩሰው ጉዳት ካደረሱ በኋላ በአካባቢው የአመጽ እንቅስቃሴ ሲካሄድ መቆየቱን ተያይዞ
የመጣው ዜና ያስረዳል።
በዚሁ ዕለት ከሻሸሜኔ ወደ ተለያዩ አቅጣጫ
የሚወስደው መንገድ ለትራፊክ ዝግ ሆኖ እንደነበረና በመኪናዎችና በሌሎች ንብረቶች ላይ የቃጠሎ አደጋ መድረሱን ከአካባቢው የመጣው
ዜና ጨምሮ
ገልጿል።
Ø
በተያያዘ ዜና ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ በተካሄደው የወያኔ የሰሜን እዝ ስብሰባ ላይ የወያኔ ባለስልጣኖች
የአግአዚ ጦር በተለያዩ ቦታዎች ሕዝቡን በማግባባት ቅራኔውን ለማብረድ በቅቷል በማለት ውሸት የተሞላበት ንግግር ያሰሙት ለአግአዚ
ጦር አባላት የሞራል ድጋፍ ለመስጠት መሆኑ ታውቋል። እንዲያውም ሳሞራ ዩኑስ የተባለው የጦር አለቃ በሰሜን እዝ ውስጥ የወያኔ
አባላት ብቻ ለሆኑ ወታደራዊ አዛዦች ባደረገው ንግግር የወያኔ አግአዚ ጦር የወሰደው ትክክለኛ ርምጃ ትክክለኛና የሚያስመሰግን
መሆኑን ገልጾ ወደፊትም አሸባሪዎችን ለመቆጣጠር ተመሳሳይ እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ያሳሰበ መሆኑን ከታመኑ ምንጮች ከተገኘ ዜና
ለማወቅ ተችሏል።
Ø
ወያኔ ደደቢት ጫካ የገባበትን አርባ አንደኛ አመት እንዲያከበሩ በአዲስ አበባ አስሩ ክፍለ ከተሞች ውስጥ
የሚገኙ የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች መመሪያ የተላለፈላቸው መሆኑ ታውቋል። በዓሉን
በድምቀት ለማክበር እነዚሁ አባላትና ደጋፊዎች ለበአሉ የሚያፈልጉ ወጭዎችን ከኅብረተሰቡ በመውጮ የሚሸፈንበት መንገድ እንዲያመቻቹ
የታዘዙ ሲሆን የፎረሞችና የሊግ አባላት ቤት ለቤት በመዞር ገንዝብ እንዲያሰባስቡ ተነግረዋል ተብሏል። በዕቅዱ መሰረት
የሚሰበሰበው ገንዘብ ለበዓሉ አከባበር ከሚወጣው ወጭ በጣም ሊልቅ እንደሚችልና በብዙ ሚሊዮን የሚገመተው ትርግ ገንዘብ የወያኔ
ካዝና ውስጥ እንዲገባ ታቅዷል።
አዲስ አበባ በተለምዶ ሰንጋተራ ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ የሚገኘው
የኢህአዴግ የወጣቶች ፎረም ብቻ ለህወሃት በዓል ስድስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር የሚፈጅ ወጪ ለማውጣት የበጀት ማሳመኛ ንድፍ
በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ውስጠ አዋቂዎች ገልጸዋል።
Ø
የወያኔ አገዛዝ ፕራቬታይዜሽን በሚል ፖሊስ የመንግስትን ሀብት የነበሩትን ተቋሞች
ለግል ሀብታሞች የሸጠ ቢሆንም እስካሁን ድረስ በርከት ያለ የሽያጭ ገንዘብ ያላሰባሰበ መሆኑ ታወቀ። ለዚህ ጉዳይ ወያኔ ያቋቋመው
ተቋም 34 የሚሆኑ የንግድና የማምረቻ ተቋሞችን በ2.15 ቢሊዮን ብር የሸጠ ሲሆን እስካሁን ያስገባው 8.6 ሚሊዮን ብር ብቻ
ነው። የአልአሙዲው ንብረት የሆነው ሜድሮክ ኩባንያ 1.5 ቢሊዮን ብር ያልከፈለው እዳ ያለበት ሲሆን ይኸው ካጠቃላዩ ውስጥ ስድሳ
ከመቶ የሚሆነው መሆኑም ተዘግቧል። የመንግስትን ንብረት ለግል ባለሃብቶች መሸጥ በሚል ሽፋን የወያኔ ባለስልጣኖች በርካታ የሕዝብ
ሀብት መዝረፋቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው የሚሉ በርካታ ናችው።
Ø
ባለፈው እሁድ የካቲት 6 ቀን 2008 ዓም
በእስራኤል አገር ዮሴፍ ሳላምሳ የተባለውንና በኋላ ራሱን ያጠፋውን
ትውልደ ኢትዮጵያዊ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በቁጥጥር ስር እንዲውል
ያደረጉትን ሁለት ፖሊሶች የእስራኤል የፍርድ ሚኒስትር ነጻ በማድረጉ በእስራኤል አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ክፉኛ ማዘናቸውን
የገለጹ ሲሆን ካሪን ኤላሃራር እና አብራሃም ንጉሴ የተባሉ የእስራኤል የምክር ቤት አባላት በውሳኔው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ
ማሰማታቸው ታወቋል። ካሪን ኤል ሃራር የተባሉት የምክር
ቤት አባል በትውልደ ኢትዮያዊ እስራዔላውያን ላይ ፖሊሶች እየወሰዱ ያሉት አሰቃቂ የኃይል እርምጃ ከፍተኛ ችግር እየሆነው ነው
በሚል የተናገሩ ሲሆን አብርሃም ንጉሴ የተባሉትና ትውልደ
ኢትዮጵያዊ የሆኑት ሌላው የምክር ቤት አባል ደግሞ በፖሊስ ላይ
እምነታችንን አጥናል ብለዋል። በእስራኤል አገር የትውልደ ኢትዮጵያውያን ማህበር ኃላፊ የሆኑት ዚፋ መኮንን ደጉ በአሁኑ ወቅት
ከእየአንዳንዱ የትውልደ ኢትዮጵያን ቤተሰብ ቢያንስ አንድ ሰው መታሰሩን ወይም በወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን
ገልጸዋል። ዮሴፍ ሳላምሳ የዛሬ ሁለት ዓመት ስለት ያለው
ጩቤ ይዞ ወንጀል ሊፈጽም ነው በሚል ጥርጣሬ ፖሊሶች ከፍተኛ የኤሊክትርክ ኃይል በሰውነት ላይ የሚያሰራጨውን ስተን ጋን (stun
gun) የተባለውን መሳራያ በመጠቀም በቁጥጥር ስር አውለውት የነበረ ሲሆን ከተወሰነ
ጊዜ በኋላ ቢለቀቅም የአይምሮ ጭንቀት ስለደረሰበት ራሱን በራሱ ያጠፋ መሆኑ ይታወቃል። ዮሴፍን በቁጥጥር ስር ያዋሉት ፖሊሶች
ባለፈው እሁድ የእስራዔል የፍርድ ሚኒስትር ፖሊሶቹ የፈጸሙት የአሰራር ስህተት ቢኖርም ከመከሰስ ነጻ አድርጓቸዋል።
Ø
የካሜሩን ልዩ የጸጥታ ኃይሎች በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ የምትገኘውንና ጎሺ
(Goshi) የተባለችውን ከተማ ወረው 162 የቦኮሃራም
አክራሪዎችን የገደሉ መሆናቸውንና በከተማዋ ውስጥ የነበሩትን የቡድኑን የቦምብ ፋብሪካዎችንና መሳሪያዎችን ከጥቅም ውጭ አድርገው
ከተማዋን የተቆጣጠሩ መሆናቸው ታውቋል። ከየካቲት 3 እስከ 6 2008 ዓም በተካሄደ ዘመቻ የካሜሩን ልዩ የጸጥታ ኃይሎች
ከተማዋን በቁጥትር ስር ካደረጉ በኋላ ለናይጀሪያ መከላከያ ኃይሎች አስረክበዋል ተብሏል። በዚህ በጋራ ኃይሉ ስም በተደረገ ዘመቻ
በቦኮሃራም ቁጥጥር ስር የነበሩ ከ100 የበለጡ የናይጄሪያና የካሜሩን ዜጎች የተለቀቁ ሲሆን ሁለት የካሜሩን ወታደራዊ አዛዦች
በመንገድ ላይ የተጠመደ ፈንጅ በመኪና ሲሄዱ የተገደሉ መሆናቸውም ተገልጿል።
Ø
ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ የተቃዋሚ ደጋፊዎችን ለመበተን ፖሊስ
በወሰደው ርምጃ አንድ ሰው የተገደለ መሆኑን የኡጋንዳ የፖሊስ ምንጮች የገለጹ ሲሆን በሚቀጥለው ሐሙስ በሚካሄደው ምርጫ የፖሊስ
ኃይሎች ሚና አሳሳቢ ነው አሳሳቢ መሆኑ ጉዳዮ የሚከታተሉ ወገኖች እየገለጹ ይገኛሉ።
ለአጭር ጊዜ ተይዘው የተለቀቁትና በተቃዋሚነት የሚወዳደሩት ሚስተር
ቢስግየ የሐሙሱ ምርጫ ነጻና ፍትሓዊ እንደማይሆን ገልጸው ደጋፊዎቻቸው ከባለስልጣኖች እየተሰጡ ያሉትን ህጋዊ ያልሆኑ ትእዛዞች
እንዳይቀበሉ ጥሪ አድርገዋል። ህጋዊ ካልሆኑ ትዕዛዞች
መካከል አንደኛው መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች ሲሄዱ የሞባይል ስልክ እንዳይዙ የሚከለክለው ሲሆን ይህ ትእዛዝ የተላለፈው
በምርጫው ውስጥ የሚከሰቱ የማጭበርበር ተግባሮች እንዳይጋለጡ ለመከላከል ነው ተብሏል። ዋና ተወዳዳሪ የሆኑት ግለሰብ ሕዝቡ ለውጥ
እንደሚፈልግ ግልጽ በሆነና በማያሻማ መንገድ ገልጿል በማለት የተናገሩ ሲሆን ከ30 ዓመት በፊት ወታደራዊ ኃይልን ተጠቅመው
ወደስልጣን የመጡት ሙሰቨኒ ደግሞ የአገሪቱን ጸጥታ የሚፈታተን ሁሉ የኃይል ርምጃ ይወሰድበታል በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
የካቲት 07 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በአዲስ አበባ ከተማ አለአግባብ እና አለበቂ ክፍያ በሚደረገው የመሬት ንጥቂያ ነዋሪዎች በከፍተኛ ደረጃ
እየተጨነቁና እየተመረሩ መሆናቸውን ከየአካቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይጠቁማሉ።
ቁልፍ የሆኑ የከተማ ቦታዎች ከድሃ ነዋሪው ላይ እየተነጠቁ ለወያኔ ሹመኞችና ደጋፊዎች ማደለቢያ ሲሆን መቆየታቸው
የሚታወቅ ሲሆን ለመንገድ ማስፋፋያና ለመሳሰሉት ሕዝባዊ ተግባሮች ነዋሪዎች በአነስተኛ ክፍያ መሬታቸውን እንዲለቁ ሲገደዱ
መቆየታቸውም ይታወቃል። ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ከእግዚአብሄር አብ ቤተክርስትያን ታክሲ ማዞረያ ወደ መብራት ኃይል ያገናኛል የተባለውን መንገድ
ለመስራት ዳርና ዳር ያሉ ቤቶች እንዲፈርሱ መደረጉን ተከትሎ ነዋሪዎች
ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገቡ መሆናቸው ታውቋል። ከማፍረሱ ስራ
ጋር በተያያዘ ዓርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በቦሌ
ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ክልል ውስጥ የሚኖር ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት የሆነና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ
በአብራሪነት ሲያገለግል የቆየ አንድ ፓይለት የመኖሪያ ቤቱ የሚፈርስ መሆኑ ከአገዛዙ ትዕዛዝ ሲደርሰው ራሱን ማጥፋቱን ለማወቅ
ተችሏል። ሟቹ ለሚፈርሰው ባለአንድ ፎቅ መኖሪያ ቤቱ የማይመጣጠን
ካሳ እንደሚከፈለው የተነገረው ቢሆንም ለቤቱ ግንባታ የወጣው ወጪና ይሰጣሃል የተባለው የካሳ ክፍያ የማይገናኝ ሆኖ ስላገኘው
በሁኔታው በማዘንና በመበሳጨት ራሱን ለማጥፋት ተገዷል ተብሏል።
የተባለውን መንገድ ለመስራት ወደ ጎን ሁለት ሜትር ከሰማንያ
የነዋሪዎች ቤትና ግቢ እንደሚፈርስ በቤቶቹ ግድግዳዎችና አጥሮች ላይ ከተጻፈው ጽሁፍ ማወቅ ተችሏል።
Ø
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማና በአካባቢው ባሉ አንዳንድ አካባቢዎች የነብስ ግድያ ወንጀሎች
እየተበራከቱ መሆናቸው የሚደርሱ ዜናዎች ይገልጻሉ። ግድያውን የሚፈጽሙት እነማን እንደሆኑ በውል ባይታወቅም የጸጥታ ቁጥጥር
ከፍተኛ ነው በሚባሉባቸው አካባቢዎች ግድያዎቹ መብዛታቸው ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል ተብሏል።
ባለፈው ሳምንት በየረር ስድስት ወጣቶች በስለት ተወግተው
የተገደሉ ሲሆን ከሟቹ ውስጥ ሁለቱ ተወግተው የተጣሉበት ቦታ
ከአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ መቶ ሜትር በማይሞላ ርቀት ላይ እንደነበር የአይን እማኞች ተናግረዋል።
ለግድያዎቹ የፖሊስ ኃይሎች ዝምታን መምረጣቸው በእነሱ ተባባሪነት
የተፈጸመ ወንጀል ሳይሆን የሚል ግምት አሳድሯል።
Ø
የወያኔው አገዛዝና የሱዳን የማዕከላዊ ባንኮች ኃላፊዎች ባለፈው
ሳምንት በሱዳን ዋና ከተማ በካርቱም ላይ ተገናኝተው የሱዳን ፓውንድና የኢትዮጵያ ብር በሱዳንና በኢትዮጵያ ተቀባይነት
እንዲኖራቸው ለማድረግ የግንዛቤ ስምምነት ላይ የደረሱ መሆናቸው ታውቋል። ይህ የግንዛቤ ስምምነት ተግባራዊ የሚሆነው በወያኔ
አገዛዝና በሱዳን መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣኖች ከጸደቀ በኋላ ነው የተባለ ሲሆን የሱዳን ባለስልጣኖች የሁለቱ አገር ባንኮች
ባንድ ላይ የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲመቻች ጥሪ አድርገዋል። ስምምነት ተግባራዊ ቢሆንም እንኳ በአብዛኛው ሊሰራ የሚችለው በወሰን
አካባቢ እንጅ በሌሎች ቦታ እንዳልሆነ ታዛቢዎች ይጠቁማሉ።
Ø
ትናንት የካቲት 6 ቀን 2008 ዓም በአሜሪካ በተደረገው የቦስተን
ኦሎምፒክ ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊዎች ሆኑ። የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው እውቋ መሰረት ደፋር
የ3000 ሺ ሜትር ሩጫ አሸናፊ የሆነች ሲሆን ለመሮጥ የፈጀባት
ጊዜ 8 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ ከ83 ማይክሮ ሰከንድ ሆኖ ከሁለት ዓመት ወዲህ በአለም
ፈጣን ተብሎ ተሰይሟል።በሴቶች የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ሩጫ ኢትዮጵያዊቷ
ዳዊት ስዩም 4 ደቂቃ ከ1 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ
ሰከንድ በመግባት አንደኛ ከመሆኗ በተጨማሪ ከአለም ከፍተኛውን
ነጥብ አስቆጥራለች።
ደጀን
ገብረ
መስቀልም
በ3ሺህ
ሜትር
የወንዶች
ውድድሩን
7
ደቂቃ
ከ42
ሰከንድ
ከ94
ማይክሮ ሰከንድ በመግባት አንደኛ ሆኗል።
መሰረትናና ዳዊትን ደጀንን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።
Ø
ለኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ቦታ በሚቀጥለው ሀሙስ በሚደረገው ምርጫ ላይ
ተውዳዳሪ ሆነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት ሚስተር ቤሲግየ (Besigye) ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በካምፓላ መሀል ከተማ
ለደጋፊዎችቻቸው የምረጡኝ ቅስቀሳ ለማድረግ በሚዘጋጁበት ወቅት
በፕሬዚዳንት ሙሰቨኒ መንግስት የጸጥታ ኃይሎች በድንገት ታስረው የተወሰዱ ሲሆን ደጋፊዎቻቸውም በአስለቃሽ ጋዝ እንዲበታተኑ
ተደርጓል። ፓሊሶች ስብሰባውን የበተኑት ተወዳዳሪው ለስብሰባ የተከለከሉ የሕዝብ ቦታዎች ስለተጠቀሙ ነው የሚል ምክንያት ሲሰጡ
ተቃዋሚዎች ደግሞ መንግስት ምርጫው በሰላም እንዳይካሄድ የሚያካሂደው አፈና ነው ብለውታል። ከ30 ዓመታት በላይ በስልጣን ላይ
ያሉትን የኡጋንዳውን ፕሬዚዳንት ሙሰቨኔን ለማስወገድ ሰባት
ተቃዋሚዎች የሚወዳደሩ ሲሆን የፕሬዚዳንቱ የግል ዶክተር የነበሩት ሚስተር ቤሲግየ ሙሰቨኒን ለማሸነፍ እድል አላቸው ይባላል።
ባሁኑ ወቅት በኡጋንዳ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ውጥረት ከፍተኛ ሲሆን
በምርጫው ወቅት ወይም በኋላ በአገሪቱ ውስጥ ሁከት ለፈጥር ይችላል የሚለው ግምት ከፍተኛ ነው።
Ø
ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2008 ዓም በብሩንዲ ታጣቂ ኃይሎች የወረውሩት
የእጅ ቦምብ ጉዳት ያደረሰ መሆኑ ተነገረ። በሞተር ቢስኪሌት ላይ ከተቀመጡ ሰዎች በዋና ከተማዋ መህል ቦታ ላይ በተወረወሩ ሶስት
የእጅ ቦምቦች አንድ ህጻን ልጅ ሲሞት
ከ30 በላይ የሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ታውቋል።
ጥቃቱን የፈጸሙት ከየትኛው ወገን እንደሆኑ በውል የሚታወቅ ነገር
የለም። መንግስት እንዲህ ዓይነቱን የሽብር ተግባር የሚያሂዱት ተቃዋሚዎች ናቸው ብሎ ሲከስስ ተቃዋሚ ኃይሎችና ሌሎች አካሎች
የጅምላ ግድያ በማካሄድ የሚታወቀው የገዥው ፓርቲ የወጣት ድርጅትና ሚሊሺያው ነው በማለት የጥቃቱን ኃላፊነት በመንግስት ክፍሎች
ላይ ይለጥፋሉ። ወደ ጠቅላላ የእርስ በርስ ግጭት እየሄደ መሆኑ የሚነገርለት የብሩንዲ ችግር የአሁኑ ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ በሆነ
መንገድ ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ተወዳዳሪ መሆናቸውን በመቃወም የተጀመረ ሲሆን ለአስር ወራት ያህል የተካሄደው የእርስ በርስ ግጭት
በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት ማጥፋቱና ከ230 ሺ ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደጎረቤት አገሮች እንዲሰደዱ ያደረገ
መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስተባባሪነት በሊቢያ የአንድነት
መንግስት ለማቋቋም በተደረገው ስምምነት መሰረት የተዘጋጀውን
የመንግስቱን የካቢኔ አባላት ስም ዝርዝር በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው መንግስት ሳይቀበለው ውድቅ
ያደረገው የሚታወስ ነው። በትናንትናው ዕለት አዲስ ሌላ የስም ዝርዝር ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ዛሬ ሰኞ የካቲት 7 ቀን 2008
ዓም ለምክር ቤት የሚቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ቀደም ብሎ ቀርቦ የነበረው 32 አባላት የሚገኙበት ካቤኔ አባላቱ በዝተዋል በሚል
በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት አካል ምክር ቤት ውድቅ በማድረጉ በአሁኑ ወቅት 18 አባላት የሚገኝበት ካቢኔ እንዲሆን
ተደርጓል። ምክር ቤቱ የቀረበለትን ረቂቅ ሀሳብ ማጽደቁና አለማጽደቁ በዛሬው ምሽት ወይም ነገ ጠዋት ይታወቃል ተብሏል።
Ø
በደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ አለሸባብ በሚቆጣጠረው የጌዶ አካባቢ ውስጥ
አንድ የአሜሪካ ሰው አልባ መንኮራኩር (ድሮን) የወደቀ መሆኑን በአካባቢ ያሉ የአይን እማኞች ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ
ገልጸዋል። አለሸባብም በራዲዮ ጣቢያው ባስተላለፈው ዜና
ስድስት ሚሳይል የጫነውን የሰው አልባ መንኮራኩር በቁጥጥሩ ስር ያደረገ መሆኑን አሳውቋል። ከአሜሪካ መንግስት በኩል እሳካሁን
ስለጉዳዩ የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም የአካባቢው ነዋሪዎች መንኮራኩሩን በዓይናቸው እንዳዩት ገልጸዋል።
በተያያዘ ዜና የሱማሊያ የቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት ግለሰብ መኪና ውስጥ በተጠመደ ፈንጅ
መገደላችውን የሶማሊያ ፖሊስ ገልጿል። ከቀድሞ ሚንስትር ጋር የነበሩ ሁለት ሰዎችም በጸና ቆስለዋል ተብሏል። ግለሰቡ የዛሬ
ስምንት ዓመት የሶማሊያ የሽግግር መንግስት የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።
የካቲት 05 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
የግብጽና የሱዳን ፕሬዚዳንቶች እና የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር በየካቲት
ወር መጨረሻ ላይ ሻርም ኤል ሼክ በተባለው በግብጽ የመዝናኚያ ከተማ ተገናኝተው ስለአባይ ግድብ ሁኔታ እንደሚወያዩ ተገለጸ።
ሰሞኑን የሶስቱ አገሮች የውሃና የመስኖ ሚንስትሮች ካርቱም ሱዳን ላይ ተገኛኝተው ግድቡ ስለሚያስከትለው ጉዳት እንዲያጠኑ
የተመደቡት ሁለቱ የፈረንሳይ የጥናት ተቋሞች ባቀረቧቸው ረቂቅ ሀሳቦች ውይይትና ድርድር ያካሄዱ ቢሆንም ስምምነቱን ለመፈረም
ያልተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸው በያዝነው
ወር መካከል ላይ እንደገና ለመገናኘት ተስማምተዋል። የጥናቱ ሀሳብ
በመጨው ስብሰባ ላይ በሶስቱም አገሮች ጸድቆ ስምምነት ካገኘ ኩባንያዎቹ ከአንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ የጥናታቸውን
ውጤት ማስረከብ ይኖርባቸዋል ተብሏል። በሌላ በኩል የወያኔ የውሃ ሀብት ሚኒስትር ለቢቢሲ የአረቢኛ ክፍል በሰጠው መግለጫ የወያኔ
አገዛዝ የአባይን ግድብ ስራ እንደማያቆም ተናግሮ የኤሌክትሪክ ሽያጩን አስመልክቶ ሱዳን እና ግብጽ ቅድሚያ እንደሚያገኙ ገልጿል።
ግብጽ የግድቡ ስራ በኮታ ማግኘት አለብኝ የምትለውን
55.5 ሚሊዮን ኩቢክ ውሃ ይቀንሳል በማለት እየተከራከረች ሲሆን ወያኔ ደግሞ ግድቡ የውሃ መቀነስ አያመጣም ባይ
ነው።
Ø
ትናንት የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦና በዙሪያዋ የሚገኙ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም የመሰናዶ ትምህርት
ቤቶች ዋና እና ምክትል ርእሳነ መምህራን በተጨማሪም ሱፐርቫይዘሮች የተገኙበት ስብሰባ
በአምቦ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ ውስጥ ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን በቅርቡ
የተደረገው አመጽ አንዱ የመነጋገሪያ ርዕስ እንደነበር ታውቋል። በስብሰባው ላይ
በምዕራብ ሸዋ አምቦና አካባቢው በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተነስቶ የነበረው የተማሪዎች
ተቃውሞ የመጀመሪያው መንፈቅ ትምህርት ሳይጠናቀቅ መሆኑ ተገልጾ በሁለተኛው መንፈቅ የትምህርት ዘመን እንዳይደገም መምህራን የነቃ
ተሳትፎ ማድረግ ግዴታቸው መሆኑ እንደተነገራቸው ለማወቅ ተችሏል። ስብሰባውን
ሲመሩ የነበሩት የኦህዴድ ካድሬዎች በርካታ መምህራን ከተማሪዎች ጋር አብረው ተቃውሞ ያነሱ እንደነበር ገልጸው ችግሩ በድጋሚ
እንዳይነሳ ለመከላከል እነዚህን መምህራን ማጋለጥ ያስፈልጋል የሚል የማስፈራሪያ ቃል ሲናገሩ የተሰሙ መሆናቸውን የመጣው ዘገባ
ጨምሮ ገልጿል። ከተማሪዎቹ ጋር ተቃውሞ በማሰማት ተባባሪነታቸው የተጠቆመባቸው መምህራንን ከስራ ከመታገድ ጀምሮ እስከ እስራት
ድረስ በሚደርስ ቅጣት ሊቀጡ እንደሚችሉም ተገልጿል። በስብሰባው የተካፈሉት የየትምህርቱ ኃላፊዎች
ቢሮ ሃላፊዎችና ርዕሳነ መምህራን ወደ የመጡበት ትምህርት ቤት
ሲመለሱ በተቃውሞው ወቅት የባከነውን ግዜ መምህራን በበጎ ፈቃድ በማግባባት ያለምንም የተጨማሪ ሰዓት ክፍያ ተማሪዎችን
እንዲያስተምሩ እንዲያደርጉ የተነገራቸው ሲሆን እምቢ ያሉትንም በማስገደድ እንዲያስፈጽሙ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል ተብሏል።
Ø
በተመሳሳይ ዜና በቡራዩ ከተማ በድሪባ ኩማ የተመራ ተመሳሳይ መምህራንን የማስገደድና የማሸማቀቅ ስብሰባ ትናንት የካቲት 4 ቀን
2008 ዓ/ም መጀመሩን ከስፍራው የመጣ ዘገባ አስረድቷል። በቡራዩና አካባቢዋ የሚገኙ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ርዕሳነ
መምህራን በተካፈሉበት በዚሁ ስብሰባ መምህራንና ወላጆች ቀጣዩን ሁለተኛ መንፈቅ የትምህርት ዘመን ያለምንም ተቃውሞ የሚካሄድበትን
ሁኔታ መምከር እንደሚገባና በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ መተባበር ያልፈለገ ወላጅም ሆነ መምህር ኪራይ ሰብሳቢ እና የጸረ ሰላም
ኃይሎች ተባባሪ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል በማለት አስተያየት እየተሰጠ እንደነበር ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
Ø
እነ ሀብታሙ አያሌው ትናንት የሰበር ሰሚው ፍርድ ቤት በነፃ የለቀቃቸው ቢሆንም ይህ ዘገባ ተጠናቅሮ እስከመጣበት ዛሬ ቅዳሜ
የካቲት አምስት ረፋድ ድረስ እንዳልተለቀቁ ታውቋል። በእነ ዘላለም ወርቅ አገኘሁ የክስ ፤ መዝገብ በሽብር ወንጀል ተከሰው
የታሰሩት ሀብታሙ አያሌው፤ አብርሃ ደስታ፤ የሺዋስ አሰፋ፤ ዳንኤል ሺበሺ የሚባሉት የሰማያዊ የአረና እና የአንድነት ፓርቲ
አመራር አባላት እና መምህር አብርሃም ሰለሞን ከአንድ አመት ተኩል በላይ በእስር እንዲንገላቱ ተደርጎ በከፍተኛ ፍርድ ቤት
ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው ነሃሴ 14 ቀን 2007 ዓ/ም ከእስር እንዲፈቱ የወሰነውን ውሳኔ ዓቃቤ ህግ ይግባኝ በማለት
ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርቦ እንደነበር ዘገባው አስታውሷል። ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጪ ሳይፈቱ የቀሩት ተከሳሾች ባቀረቡት አቤቱታ
ጉዳያቸው ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሶ ትናንት ዓርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓ/ም በዳኛ ዳኜ መላኩ ትዕዛዝ በነጻ እንዲሰናበቱ
መወሰኑ ቢታወቅም የወህኒ ቤት ምንጮች ውሳኔው የተወሰነው አርብ ቀን
በመሆኑና መጪው ቅዳሜና እሁድ ነው በማለት እስር ቤቱ የሰበር ሰሚውን ፍርድ ቤቱ ውሳኔ
በመጣስ እስረኞቹን ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ለማንገላታት ችሏል።
Ø
አርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓም የሮማው ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ እና የሩሲያው የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያ
ፓትሪያርክ በኩባ ዋና ከተማ በሃቫና አውሮፕላን ማረፊያ ለሁለት ሰዓታት ተገናኝተው ባደረጉት ታሪካዊ ስብሰባ በሁለቱ ቤተ
ክርስቲያኖች መካከል አንድነት እንዲፈጠር ጥሪ አስተላልፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም በተለይ
በመካከለኛው ምስራቅ በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለውን
ግድያ ሁሉም እንዲከላከል ጥሪ አድርገዋል። ከ1000
ሺ ዓመት በፊት በአስራንደኛው ክፍለ ዘመን የካቶሊክና እና የኦሮቶዶክስ እምነት ተከተያዮች ከተለያዩ በኋላ በሁለቱ ቤተ
ክርስቲያኖች መሪዎች መካከል ግንኙነት ተፈጥሮ ውይይት ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው በመሆኑ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ከስብሰባው በኋላ
ሁለቱም ወገኖች በሰጡት መግለጫ ስብሰባው በቅንነትና በግልጽ የተካሄደ
የወንዳማማቾች ስብሰባ ነበር ብለውታል።
Ø
አርብ የካቲት አራት ቀን ሌሊት ለቅዳሜ አጥቢያ በብሩንዲ የገዥው ፓርቲ አባላት
የሆኑ ሁለት ሰዎች በታጠቁ ሰዎች መገደላችውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ በአንዲት ከተማ ውስጥ ገብተው
ነዋሪዎችን እንዲወጡ ካደረጉ በኋላ ከመካከላቸው በቅርቡ የገዥው ፓርቲ አባል በመሆን የተመደበውንና
አካባቢውን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠውን ግለሰብና የገዥው
ፓርቲ የወጣት ሊግ አባል የሆነውን ግለሰብ መርጠው በማውጣት ረሽነዋቸው የሄዱ መሆናቸው ተሰምቷል። የገዥው ፓርቲ የወጣት ሊግ
የተባለው ተቋም እንደሚሊሺያ በመታጠቅ በርካታ ተቃዋሚዎችን የገደለ መሆኑ ይታወቃል። ለተወሰነ ጊዜ ጸጥታ ነግሶበት የነበረችው
ብሩንዲ ሁከት እንደገና እያገረሸበት መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ።
Ø
ትናንት አርብ የካቲት 4 ቀን 2008 ዓም በካይሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ዶክተሮች በፖሊሶች የሚካሄደውን የአፈና ተግባር ተቃውመው
ድምጻቸውን ያሰሙ መሆናችው ታወቀ። ከአስራ አምስት ቀናት በፊት ማታረያ በሚባለው በሰሜናዊ ካይሮ በሚገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን
ሆስፒታል በመውረር ፖሊሶች ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን ሁለት ዶክተሮችንም በጽኑ የደበደቡ መሆናቸው ተነግሯል። የአቃቤ ህጉ ቢሮ
ድበደባውን ፈጽመዋል የተባሉትን 9 የፖሊስ አባላት መጀመሪያ አስሯቸው የነበረ ቢሆንም ሐሙስ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም
ካለምንም ማብራሪያ
የለቀቃቸው መሆኑ ተዘግቧል። ስራቸውን በሚገባ እያከናውኑ በነበሩት ዶክተሮች ላይ የጸጥታ ኃይሎች ድብደባ ማካሄዳቸው
አግባብ አለመሆኑን በመግለጽና ፖሊሶቹ ታስረው ፍርዳቸውን እንዲቀበሉ በመጠየቅ ዶክተሮቹ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል።
የካቲት 04 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በአባይ ግድብ ላይ ለመነጋገር በካርታሙ ሱዳን ተሰብስበው የነበሩት የግብጽ የሱዳንና የወያኔ የውሃና
የመስኖ ሚኒስትሮች ስለ ግድቡ ጥናት
የቴክኒክ ጉዳይና ለጥናቱ ስለሚከፈለው ገንዘብ በሰፊው የተውያዩና እያንዳንዳቸው ያላችውን አቋም የተለዋወጡ ቢሆንም
ሙሉ በሙሉ ስምምነት ላይ ባለመድረሳቸው ድርድሩን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ
አዲስ አበባ ላይ ለመቀጠል መስማማታችውን ኢጅፕት ኢንዲፔንደንት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ ከስብሰባው አካባቢ ያገኘውን
ዜና ዋቢ አድርጎ ሐሙስ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም ባሰፈረው ዘገባ ገልጿል። በአዲስ አበባው ጉባኤ ድርድሩ
በቴክኒክ ጉዳይና በገንዘብ አከፋፈሉ ድርድሩ የሚቀጥል መሆኑና
ስምምነት ከተደረገ አርተሊያና ቢአር ኤል የተባሉት ሁለቱ የአጥኚ
ኩባንያዎች ስራቸውን እንዲጀምሩ ኮርቴል የተባለው የእንግሊዙ ኩባንያ ኮንትራቱን እንዲያዘጋጅ ይነገረዋል ተብሏል።
Ø
በጉጂ አካባቢ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ
አባሎቹና የቅርንጫፍ ቢሮ አመራሮች የታሰሩበት መሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ
አዲስ አበባ ውስጥ ካዛንቺስ ከሚገኘው ቢሮው መግለጫ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። በጉጂ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ቤት ለቤት
ታድነው በፖሊስ ከተወሰዱ በኋላ እስካሁን ድረስ ክስ ያልተመሰረተብቸው መሆኑን ፓርቲው ጨምሮ ገልጿል።
በጉጂ የአላሙዲን ወርቅ ቁፋሮ ስራ
እንዲቆም የሚጠይቅ ሕዝባዊ ተቃውሞ አንዱና ዋናው ስለነበር አዲስ አበባ ውስጥ የአላሙዲን ድርጅቶችን በጥምረት
የሚመራው የእነ ዶክተር አረጋ ቡድን ተሰብስቦ የወያኔ
ባለስልጣኖች በጉዳዩ ላይ መፍትሄ እንዲሰጡ ጥያቄ ቢያቀርብም
በተፋፋመው ሕዝባዊ ቁጣ ሳቢያ ቁፋሮው ለግዜው መቆሙ ይነገራል። በወያኔ እና በደጋፊዎቹ አማካኝነት እየተወሰደ ያለው የሀብት
ዘረፋው ይብቃ የሚለው ጥያቄ የጉጂ ብቻ ሳይሆን የመላው
ኢትዮጵያዊ መሆኑን በተለያየ ግዜ ዜጎች አንሰተው የታገሉ
መሆናቸው ይታወሳል።
Ø
በአፋር ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ እየተደረገ ያለው ግምገማ
ባለስልጣኖችን ሊያግባባ ሳይችል በመቅረቱ የወያኔ ሹሙ
ካሳ ተክለ ብርሃን ስብሰባውን እንዲመራ መደረጉን ከሰመራ
የመጣው ዘገባ ገልጧል። የእስማኤል አሊ ሴሮን ወንበር የያዘው ስዩም አወል የተባለው የወያኔ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ስብሰባውን
እንዲመራ ታቅዶ የነበረ ቢሆን ባለስልጣኖቹ እርስ በእርሱ ውዝግብ
ውስጥ በመግባታቸው ምክንያት ተግባራዊ ሳይሆን ቀርቷል።በአፋር ባለስልጣኖችን ያወዛገበው የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጩ
የእከክልኝ ልከክልህ የሆነ የመዋቅር ችግር በመኖሩ ነው በማለት ዘገባው አስረድቷል።
በአፋር ለተከሰተው ድርቅ ዘላቂ መፍትሄው አርብቶ አደሩን ካለበት
አፈናቅሎ ወደሌላ አካባቢ መውሰድ ነው የሚለው እቅድ የአመለካከት
ችግር አለበት ከሚለው ቡድን ጋር መግባባት መግባባት ሊደረስ ባለመቻሉ ስብሰባውን ለማድረግ ሳይቻል ቀርቶ በካሳ ተክለብርሃን
በሌሎች የወያኔ ባለስልጣኖች አማካይነት ስብስበው እንዲመራ ተድረጓል።
Ø
በሩዋንዳ የሚገኙትንና ከሰባ ሺ በላይ የሚቆጠሩትን የብሩንዲ ስደተኞች ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እቅድ
እንዳለ የሩዋንዳ ባለስልጣኖች ገለጹ። ስደተኞች ወዴትኛው አገር እና በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚጓጓዙ በባለስልጣኖቹ ባይገለጽም
እቅዱ ባስቸኳይ እንደሚጀመር ተነግሯል። ሩዋንዳ የብሩንዲን መንግስት ተቃዋሚዎች በአገሯ ላይ በወታደራዊ ትምህርት ታሰልጥናለች
መሳሪያ ታስታጥቃለች የሚሉ ክሶች የተመድ የውይይት መድረክ
አባላትና እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣኖች መክሰሳቸው ይታወቃል። ከሁለት ቀናት በፊት የሩዋንዳው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ስደተኞችን ማባረር አንችልም በማለት የተናገሩት ቃል ተቀልብሶ በአሁኑ ወቅት ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እቅድ ያለ መሆኑ መገለጹ
ሩዋንዳ ከተመድ እና ከአሜሪካ ከፍተኛ ተጽእኖ የደረሰባት መሆኑን ያሳያል ሲሉ ታዛባዎች ይተቸሉ። የተመድ የስደተኞች ጉዳይ
ጽሕፈት ቤት እስካሁን ስለጉዳዩ የሰጠው መግለጫ የለም።
Ø
12 ከፍተኛ መኮንኖች የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ጥርሬ የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የገንዘብ ወንጀል
ኮሚሽን ለሚባለው ጸረ ሙስና ተቋም የተላለፉ መሆናቸውን
የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም አስታወቀ። ከፍተኛ መኮንኖቹ በስም ባይጠቀሱም ስድስቱ የጄኔራል ማዕራግ ያላቸው መሆኑ ታውቋል።
ኮሚሽኑ በምርመራ መኮንኖች የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ካረጋገጠ ጉዳያቸው በወታደራዊ ፍርድ ቤት እንደሚታይ ተገልጿል። ባለፈው
ዓመት በፕሬዚዳንቱ የተሰየመ አጣሪ ኮሚቴ ባደረገው ምርመራ በተጭበረበረና በሀሰት የመሳሪያ ግዥ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ
የአገሪቱ ሀብት መዘረፉን የደረሰበት መሆኑ ተገልጿል። የቀድሞ የፕሬዚዳንት የጸጥታ አማካሪ ሚስተር ዳሱኪ ባለፈው
ታኅሣሥ ወር 2008 ዓም 68 ሚሊዮን ዶላር
ዘርፈዋል ተብለው መከሰሳቸው ይታወሳል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሚስተር ጆናታን የቅርብ ረዳቶች የሆኑ በርካታ ስዎች በሙስና ፍርድ
ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቅሷል።
Ø
በሰሜናዊ ማሊ አንድ መኪና ላይ በተጠመደ ፈንጅ ቢያንስ ሶስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም
አስከባሪ ኃይል አባላት የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። እስካሁን ድረስ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም የእስላማውያን
ታጣቂዎች ናቸው የሚል ጥርጣሬ አለ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከ2004 ዓም ጀምሮ በማሊ የጸጥታ
ማስከበር ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል።
Ø
ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳን ከሳልቫ ኬር የካቲት 3 ቀን 2008 በተላለፈ አዋጅ የተቃዋሚው መሪ ሪክ ማቻር
የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው በይፋ ተገልጿል። ሪክ ማቻር የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቦታቸውን እንደገና
ለማግኘት የቻሉት ባለፈው ዓመት በተደረገው ስምምነት መሰረት ሲሆን ሐሙስ ዕለት የተላለፈው አዋጅ ስምምነቱን በተግባር ያዋለ
በመሆኑ ለሰላም አንድ ተስፋ ነው የሚል አስተያየት ተሰጥቷል። ይሁን እንጅ በተልያዩ ቦታዎች አሁንም ጦርነቱ የቀጠለ መሆኑ ሰላም
ለመመጣቱ የሚጠራጠሩ በርካታ ናችው። ሪክ ማቻር ከአዲስ አበባ ለዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ በአዋጁ የተነገረውን በደስታ
የሚቀበሉት መሆናቸውን ገልጸው ስምምነቱ በስራ እየዋለ
መሆኑ ይጠቁማል ብለዋል። ሪካ ማቻር ወደ ጁባ መች እንደሚሄዱና ከመሄዳችው በፊት ምን አይነት አስተማማኝ የጸጥታ ሁኔታ መዘጋጀት
እንዳለበት እስካሁን በግልጽ አልተነገረውም ። በየቦታው ጦርነቱ እስከቀጠለ ድረስና የሳልቫ ኬር
መንግስት የስምምነቱ መሰረት የሆነውን የአስተዳድር ክልሎችን መልክ ቀይሮ አዳዲስ የአስተዳደር ክልሎች በመፍጠሩ
ጦርነቱ ሊያበርድና ሰላም ሊገኝ አይችልም የሚሉ በርካታ ናቸው።
Ø
ሐሙስ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም የካሜሩን ወታደሮች ወደ ናይጄሪያ ግዛት ዘልቀው በመግባት ባካሄዱት
ወታደራዊ ዘመቻ 27 የቦኮሃራም ታጣቂዎች የገደሉ መሆናቸውን አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን ገልጿል። ጎሺ በምትባለው
የናይጄሪያ ግዛት ላይ በተደረገው ዘመቻ አንድ የካሜሩን ወታድር የሞተ ሲሆን ሰባት ወታድሮች የቆሰሉ መሆናችውም ተገልጿል።
ባለፈው ረቡዕ የቦኮሃራም አጥፍቶ ጠፊዎች በሰሜን ካሜሩን
ባፈነዱት ቦምብ 10 ሰዎች መገደላቸውና ከ 40 በላይ መቁሰላቸው ይታወሳል። ከታኅሣሥ 2007 ዓም ጀምሮ
ቦኮሃራምና ለማጥቃት የአካባቢው አገሮች ጥምር ኃይል መቋቋሙ
የሚታወስ ሲሆን በአክራሪው ኃይል ላይ በርካታ ወታደራዊ ዘመቻዎች መደረጋቸው ይታወሳል። የቦኮሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረ ካለፈው
ስድስት ዓመታት ጀመሮ ከ 20 ሺ ሰዎች በላይ የተገደሉ ሲሆን 2.5 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ
መሆኑ ይነገራል።
የካቲት 3 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በወሎ ክፍለሀገር
የሚገኘው የሎጎ ሃይቅ ቀደም ሲል
ከነበረው ይዞታው በአንድ አመት ውስጥ በ36 ሜትር ርዝመት መሸሹና ዙሪያውን ምንነቱ ባልታወቀ አዲስ መጤ አረም የተጠቃ መሆኑን
የአካባቢው ነዋሪዎች እየተናገሩ መሆናቸው ተዘገበ። በእርሻ ላይ ኑሯቸውን የመሰረቱ በአካባቢው የሚኖሩ አርሶ አደሮች የሎጎ
ሃይቅን ለመስኖ እርሻ ሲጠቀሙ መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት
ውሃው
በከፍተኛ ደረጃ በመጉደሉ በሃይቁ ውስጥ ይገኙ የነበሩት የቆሮሶና የአምባዛ
አሳ ዝርያዎች እየጠፉ መሆናቸው ይመሰክራሉ።
የሎጎ
ሃይቅ ዙሪያውን ከ28 ሺህ ስኩዌር በላይ የነበረው ሲሆን በአንድ አመት ወደ 22 ሺህ ስኩዌር ስፋት በመጥበቡ ጉዳዩ አሳሳቢ
መሆኑ ታውቋል። ስለአሳ ዝርያ መጥፋት ስለሃይቁ መትነንና በመስኖ
አርሶ አደሮች ውሃው እንዲወጣ ማድረጋቸውን ጨምሮ
በሃይቁ ዳርቻ በወረርሽኝ መልክ የተከሰተው አዲስ መጤ አረም አሳሳቢ መሆኑን ነዋሪዎቹ ለወያኔ ጉዳይ አስፈጸሚዎች ለብአዴን
ሹማምንቶች ቢያሳውቁም ጥበቃ ለማድረግም ሆነ መፍትሄ ለመሻት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የሎጎ ሃይቅ ለመድረቅ ግስጋሴ የጀመረ መሆኑን
ለማወቅ ተችሏል።
Ø
ከየካቲት 10 ቀን
2008 ዓ/ም አንስቶ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች
ስለይዞታቸው
ዳግም ማረጋገጫ እንዲወሰዱ ሊታዘዝ መሆኑን ለድሪባ ኩማ ቢሮ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አጋልጠዋል። ከድሪባ ኩማ ቢሮ በተዘጋጀ
ትዕዛዝ በአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተሞች ውስጥ የሚገኙ የመሬት አስተዳደር ኤጀንሲዎች አማካኝነት ነዋሪዎች በአዲስ መልክ
የይዞታ ማረጋገጫ እንዲወስዱ ይህን ካላደረጉ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እንዲያሳውቁ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል። ቀደም ሲል የይዞታ
ማረጋገጫቸውን የወሰዱና ካርታ በእጃቸው ላይ የሚገኝ ነዋሪዎችን ጨምሮ ይህ ዳግም ማረጋገጫ ለምን እንዳስፈለገ ለግዜው የታወቀ
ነገር የለም። በአዲስ አበባ ነዋሪዎች እያፈናቀለ ወደ ዳር አገር እንዲሰደዱ በማድረግ መሬታቸውን በሊዝ የሚቸበችበው ወያኔ
ቀደም ሲል ካርታ ያልወሰዱትን
ሰባ አምስት ካሬ ብቻ ይዞታቸው እንዲሆን በማድረግ ቀሪውን በካሬ ሜት አራት ሺህ ብር በሚጠጋ ክፍያ በማስከፈል ነዋሪዎችን
ለማስለቀስ የራሱን ኪስ በረብጣ ሊሞላ መሰናዳቱን መዘገባችን ይታወሳል።
በተያያዘ
ዜና
የመሬት ይዞታቸው ተረጋግጦላቸው
የአፈር
ግብር እየከፈሉ የነበሩ ዜጎች በድጋሚ ማረጋገጫ
ማግኘት እንዲችሉ የአየር ላይ ካርታ ይነሳል በሚል
ነዋሪውን እያመሱት መሆኑን ከባህርዳር የመጣ ዘገባ አስረድቷል።
Ø
ባለፈው ማክሰኞ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በቦርኖ
ግዛት ዲክዋ ከሚባለው የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ሁለት የሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 56 ሰዎች መሞታቸውንና ሌሎች
መቁሰላቸው ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። አጥፍቶ ጠፊዎቹ ቦምቡን ያፈነዱት በካምፑ ውስጥ የተጠለሉት ስደተኞች ለምግብ
ተሰልፈው በነበረበት ወቅት ሲሆን ተጎጅዎቹ በብዛት ሴቶችና ህጽናት መሆናቸው ተገልጿል። ቦምብ ታጥቀው ለማፈንዳት የመጡት ሴቶች
ሶስት የነበሩ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንደኛዋ ወላጆቿ በካምፕ ውስጥ መኖራቸውን ስትረዳ ቦምቡን ከማፈንዳት ተቆጥባ እጇን
ካምፑን ለሚጠብቁ የጸጥታ አባላት ሰጥታለች። ካምፑ
ከልዩ ልዮ ቦታዎች ተሰደው የመጡ ከ50 ሰዎች በላይ
ያሉበት ሲሆን አብዛኞቹ ሴቶችና ሕጻናት መሆናቸው ተረጋግጧል። የናይጄሪያ ባለስልጣኖች የካምፑ የጥበቃ ሁኔታ እንዲጠናከር መመሪያ
የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። ድርጊቱን የፈጸመው ቦኮሃራም መሆኑ የተገመተ ሲሆን ቡድኑ ባለፉት ስምንት ዓመታት በካሄዳቸው የሽብር
ጥቃቶች ከ20 ሺ ሰዎች በላይ መገደላቸውና ከ2 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ይታወቃል።
በተያያዘ ዜና
ለቦኮ ሃራም በርከት ያሉት የጦር መሳሪያና ጥይቶች
ሲያስተላልፉ የነበሩ ሁለት የናይጀሪያ ወታደሮች
በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የናይጄሪያ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ ገልጿል። ሁለቱ ወታደሮች በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ውስጥ
ተመድበው በፈንጅ ስራ ላይ ተመድበው ይሰሩ የነበሩ ሲሆን ከመሳሪያ ማስተላለፍ በተጨማሪ የቦኮሃራምን ታጣቂዎች የቦምብ የማምረት
ስራ ሲያስተምሯቸው ቆይተዋል የሚል ጥርጣሬ ፈጥሯል። ቦኮ ሃራም የናይጄሪያን ወታደራዊ ተቋም ስርጎ የገባ መሆኑ ከዚህ በፊት
በተደጋጋሚ ተነግሯል።
Ø
የተባበሩት መንግስት ድርጅት አንድ የፎረንሲክ ኤክስፕርቶች ቡድን ወደ ብሩንዲ
ለመላክ ያቀደ መሆኑን የድርጅቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ረቡዕ የካቲት 3 ቀን 2008 ዓም ባደረጉት መግለጫ ገልጸዋል። ቡድኑ ምርመራ
የሚያካሄደው ባለፈው ታኅሣሥ ወር በመንግስት ኃይሎች
በግፍ ተረሽነው ከተገደሉ በኋላ በተለያዩ ቦታዎች
በጅምላ ተቀብረዋል
የተባሉትን ከ100 በላይ የሆኑ ሰዎችን አስከሬን
ለመመርመርና ማንነታቸውን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት እርዳታ ለመስጠት ነው። የተመድ ባለስልጣን በሰጡት መግለጫ
የብሩንዲ ዜጋ የሆነ አቃቢ ህግ ክስ ለማቅርብ ምርመራ
የጀመረ መሆኑ ገልጸው የተመድ ቡድን በቦታው በመገኘት የፎርንሲክ አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።
በተያያዘ ዜና ሩዋንዳ ለብሩንዲ መንግስት ተቃዋሚዎች
በስደተኞች ጣቢያ
ወታደራዊ ስልጠና መስጠቷን አስመልክቶ
አንዳንድ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ድርጊቱን ማውገዝ መጀመራቸው
ተነግሯል። ሁለት ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣኖች
በትንናንትናው ዕለት በአሜሪካው ምክር ቤት ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ላይ ቀርበው በሰጡት የምስክርነት ቃል ሩዋንዳ የብሩንዲን
ተቃዋሚዎች ወታደራዊ ስልጠና መስጠቷ ተጨባጭ መረጃ ያላቸው መሆኑ ገልጸው ድርጊቱ ሊወገዝ ይገባል ብለዋል። የአሜሪካ የቅርብ
ወዳጅ የሆነው የካጋሚ መንግስት በባለስልጣኖች በይፋ ሲወቀስ ይህ የመጀመሪያው በመሆኑ ብዙዎችን አስገርሟል።
Ø
የቀድሞ የቱኒዚያ ፕሬዚዳንት ቢን አሊ የአገሪቱን ንብረት በመዝረፍ በግል
አከማችተውት ከነበረው ንብረት ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና የገባ መሆኑን አንድ የቱኒዚያ
ሚኒስትር ረቡዕ የካቲት 03 ቀን 2008 ዓም የተናገሩ መሆኑ ታውቋል። የዛሬ አመስት አመት በቱኒዚያ በተነሳው ሕዝባዊ አመጽ
ምክንያት ፕሬዚዳንት ቢን አሊ አገር ጥለው ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሲሰደዱ
የቢን አሊና የተባባሪዎቻቸው ንብረት የሆኑ የንግድ
ተቋሞች፤ ህንጻዎች የቅንጦት መኪናዎች ወርቅና አልማዝ እንዲሁም ሌሎች ጌጣጌጦች የተወረሱ መሆናቸው ይታወቃል። ባለፉት አምስት
አመታት አብዛኞች ንብረቶች ተሸጠው ከግማሽ ቢሊዮን ዶላር በላይ ወደ መንግስት ካዝና የገባ መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ያልተሸጡ በርካታ ንብረቶች ያሉ መሆናችውን ሚኒስትሩ ገልጸው
ባጭር
ጊዜ ውስጥ ለመሸጥ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
የካቲት 2 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር የሚገኘውና ህጻናትን እናድን
(ሴቭ ዘ ቺልድረን) የተባለው ተቋም ትናንት የካቲት 1 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት
በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ 245 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ካልተገኘ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የረሃቡ ሁኔታ አደገኛ
ሁኔታ ውስጥ ሊወድቅ እንደሚችል አስታውቋል። በአሁኑ ወቅት በምግብ
እጥረት የተጠቁ ከ400 ሺ በላይ የሆኑ ህጻናት ተጨማሪ
አልሚ ምግቦች የሚያስፈልጋቸው መሆኑንና ባጠቃላይ 1.7 ሚሊዮን የሚሆኑ ሴቶችና ህጽናት በከፍተኛ የምግብ
እጥረት ሊጠቁ እንደሚችሉ ገልጿል። የድርጅቱ የኢትዮጵያ ቅርጫፍ ዋና ዲሬክተር በጉዳዩ ላይ ተጫማሪ ማብራሪያ ሲሰጡ
ከረጅዎች የተባለው እርዳታ ካልመጣ አሁን ያለው የምግብ ክምችት በሚቀጥለው ሚያዚያ ወር ላይ ሊገባደድ የሚችል መሆኑን ገልጸው
ከግንቦት በኋላ ባሉት ወራት ከፍተኛ ችግር ሊከሰት እንደሚችል
ተናግረዋል። እህሉ ከውጭ ተሸምቶ ወደ አገር ውስጥ እስኪገባ ድረስ የሶስትና የአራት ወራት ጊዜ ስለሚያስፈልግ
በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት የተጠቀሰውን እርዳታ ማግኘት ወሳኝ ነው ብለዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ብቻ ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በረሃቡ የተጠቁ መሆናቸውን አንዳንድ ምንጮች የገለጹ
ሲሆን በአሁኑ ጊዜ አስቸኳይ እርዳታ እየተሰጣችው የሚገኙት ዜጎች ብዛት 10.2 ሚሊዮን ደርሷል ተብሏል። ባጠቃላይ በዚህ ዓመት
የድርቁና የረሃቡን ችግር ለመቋቋም 1.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል የተባለ ሲሆን እስካሁን በእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተሰበበው
680 ዶላር ብቻ መሆኑ ተዘግቧል።
Ø
ካርቱም ሱዳን ላይ ተሰብሰበው የሚገኙት የግብጽ የሱዳንና የወያኔ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የአባይ ግድብን
አስመልክቶ የፈረንሳዩ አጥኝ ኩባንያ ባቀረበው የጥናት ሀሳብ ላይ ያላቸውን አቋሞች ተለዋውጠው ትናንት ማክሰኞ የካቲት 1 ቀን
2008 ዓም ስምምነት ላይ መድረሳችው ታውቋል። አርቲሊያ እና ቢ አር ኤል የተባሉት የፈረንሳይ አጥኝ ተቋሞች ጥናት የሚያተኩረው
ግድቡ ወደ ሱዳንና ወደ ግብጽ የሚፈሰውን የውሃ መጠን ሊቀንስ መቻሉንና አለመቻሉን እንዲሁም በግድቡ ምክንያት በአካባቢው
የእጽዋት ሁኔታ ለውጥ ሊመጣ የሚችል መሆኑንና አለመሆኑን ነው። በስብሰባው ላይ ኩባንያዎቹ ለስራቸው የሚያስከፍሉትን የገንዘብ
መጠን የያዘ ኢንቮሎብ በይፋ በሶስቱም አገሮች መልክተኞች የተከፈተ መሆኑ ተገልጿል። ለጥናቱ የሚደረገውን ወጭ ሶስቱም አገሮች
በእኩል ደረጃ እንደሚያዋጡ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም የሶስቱ አገሮች የመስኖና የውሃ ሀብት
ሚኒስትሮች በሚገኙበት ስምምነቱ በይፋ ይፈረማል ተብሏል። ግብጽ በግድቡ ምክንያት ወደ አገሯ ከሚፈሰው ውሃ 55፣5 ቢሊዮን
ኪውቢክ ሜትር ይቀንሳል የሚል ስጋት የፈጠረባት ሲሆን የወያኔ አገዛዝ ግድቡ ምንም ዓይነት የውሃ መቀነስ እንደማያመጣ ተናግሯል።
Ø
በኩዌት አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ የአስሪዋ ልጅ የነረችውን የ23 ዓመት ወጣት በስለት
ከገደለቻት በኋላ የገዛ ህይወቷን ራሷን ወግታ በጽኑ ያቆሰለች
መሆኑ ታውቋል። ኢትዮጵያውያቷ የቤት ሰራተኛ ይህን ድርጊት ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ያልታወቀ ሲሆን ለጊዜው ወደ ሆስፒታል
የተወሰደች መሆኑ ታውቋል። በአረብ አገር ለግርድና እየተሸጡ በሚሄዱ ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ በደልና ጭካኔ የተመላበት ድርጊት
በአሰሪዎቻቸው መፈጸሙ በተደጋጋሚ የተነገረ ሲሆን ይህችን ኢትዮጵያዊት ወደ ዚህ ድርጊት ሊገፋፋት የቻለው የተፈጸመባት በደል
ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ በርካታ ናቸው። ራሷን ያቆሰለችው በጽኑ በመሆኑ በህይወት ልትተርፍ መቻሏና አለመቻሏ
አልተረጋገጠም።
Ø
በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በፍስሃ ገነት ከተማ ውስጥ በሚገኙ ስድስት
የጤና ጣቢያዎች ተቀጥረው በመስራት ላይ የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች የትርፍ ጊዜ ክፍያ አይሰጠንም በሚል ጥያቄ ያቀረቡ
መሆኑ ታወቀ። በዲፕሎም ዘርፍ የትርፍ ግዜ ክፍያ አርባ ስምንት ብር በዲግሪ ዘርፍ የትርፍ ግዜ ክፍያ ስድሳ ሁለት ብር
እንዲከፈል በህግ የተቀመጠ ቢሆንም የወረዳ አመራሮች ሊከፍሉን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል በማለት ምሬታቸውን በይፋ ሲገልጹ የተሰሙ
መሆኑ ታውቋል። ለጤና ባለሞያዎች የትርፍ ግዜ ክፍያ እንዲሆን
ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ለኮቸሬ ወረዳ የተመደበ ቢሆንም ክፍያው ያልተፈጸመ ከመሆኑ በላይ በጀቱ ተመላሽ ሳይደረግ የገባበት
ሳይታወቅ የቀረ መሆኑን ጉዳዩን የሚያውቁት ዜጎች ገልጸዋል።
Ø
በየመን በሁቲ አማጽያን የሚደገፈው የየመን ጦር በሳኡዲ አረቢያ
ደቡብ ምዕራብ በአሲር ክፍለ ሀገር ውስጥ ከሳኡዲ ወታደሮች ጋር ከባድ ውጊያ አካሄዶ አልራቦህ የተባለውን የሳኡዲ አረቢያ ከተማ
እና በአካባቢው ያሉትን መንደሮች በቁጥጥሩ ስር ማድረጉን
ገለጿል። የሳኡዲ ጦር በአውሮፕላንና በሌሎች ከባድ መሳሪያዎች ቢረዳም በጦርነት ከባድ ጉዳት ደርሶበት
መሳሪውያውን እየጣለ የሸሸ መሆኑን ዘገባው ገልጿል። ዘገባው በሌላ በሶስተኛ ወገን ማረጋገጫ አላገኘም። በሌላ በኩል
ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በየመን ዋና ከተማ በሳንአ በሳኡዲ የሚመራው የጥምር ኃይል ባደረገው የአየር ጥቃት የአንድ ቤተ
ሰብ አባል የሆኑ አምስት ሰዎች መገደላቸው ታውቋል።
Ø
ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም በማሊ ሞፕቲ በተባለው ግዛት
ሲጓዙበት የነበረው መኪና በመንገድ ላይ በተጠመደ ፈንጅ በመመታቱ ሶስት ወታደሮች መገደላቸውና ሌሎች መቁሰላችው የማሊ የመከላከያ
ሚኒስቴር ከሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ በተጨማሪም ትናንት የካቲት 1 ቀን 2008 ዓም ደግሞ ከቡርኪና ፋሶ አዋሳኝ
ላይ ባለችው ሞንዶሮ በተባለችው ቦታ በፈነዳ ቦምብ ሌሎች ሁለት ወታደሮች መቁሰላቸውን የመከላከያ ሚኒስቴሩ ገልጿል። ለእነዚህ
የተለያዩ ጥቃቶች እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም የማሲና
ነጻ አውጭ ድርጅት የሚባለው በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው እስላማዊ አክራሪ ድርጅት ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት
ተሰጥቷል።
Ø
ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2008 ዓም
በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ተኩል ላይ በሰሜን ካሜሮን ከናይጄሪያ ወሰን አካባቢ በአንድ መንደር
ውስጥ ሁለት ሴቶች አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷቸው ቦምቦች
ስድስት ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸውና ቁጥራቸው ከ30 እስከ
50 የሚደርስ ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል። ሁለቱ አጥፍቶ ጠፊዎችም አብረው የተገደሉ መሆናቸውንም ተያይዞ የመጣው ዜና ያስረዳል።
የመንደሩ ሰዎች የተሰበስቡት ለሀዘን ሲሆን አጥፍቶ ጠፊዎችም ሰዎችን ለመቀላቀል የቻሉት ሀዘናቸውን ለመድረስ የመጡ ዘመዶች
መስለው እንደሆነ ተጠቁሟል። ህይወታቸውን ካጡት መካከል የስድስት እና የአስራ አምስት አመት ልጆች የሚገኙበት ሲሆን አንድ
የአካባቢው የጸጥታ ኮሚቴ አባል መገደሉም ተገልጿል። ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባችው ለህክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል።
ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን እስካሁን ባይኖርም የቦኮሃራም ታጣቂዎች ለመሆናችው ከፍተኛ ግምት አለ። ባለፉት ጥቂት ሳምንታት
በአጥፍቶ ጠፊዎች አማካይነት በካሜሩን ከደረሱ የቦካ ሃራም ጥቃቶች
መካከል ይህኛው አምስተኛ ሲሆን አጥቂዎችን ለመቆጣጠር የተወሰደው እርምጃ እስካሁን አጥጋቢ ውጤት አልሰጠም በማለት
በርካታ ዜጎች ይተቻሉ።
የካቲት 1 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
በጋምቤላ የታጠቀውን ልዩ ኃይል መሳሪያ የማስፈታት ትእዛዝ ከፌዴራል
መሰጠቱን ተከትሎ የተወሰኑ አባላቶችን ትጥቅ ማስፈታት ቢቻልም
በርከት ያሉት ከነመሳሪያቸው መሰወራቸውን ምንጮች አጋልጠዋል። በኑዌርና በአኝዋክ ጎሳ አባላት መካክል የተነሳውን የእርስ በእርስ
ግጭት ለማብረድ ተችሏል በማለት የወያኔ አገዛዝ ደጋግሞ ቢናገርም በጋምቤላ ያለው እውነታ ግን ከዚህ ተቃራኒ መሆኑን መዘገባችን
ይታወሳል። ከጋምቤላ ጸጥታና ደህንነት ቢሮ የሰው ኃይል አስተዳደር መምሪያ የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው የታጠቁ የልዩ ኃይል
አባላት ብዛትና ትጥቅ በማስፈታቱ ዘመቻ ትጥቃቸውን አስረክበዋል
የተባሉት አባላት ቁጥር ፍጹም እንደማይገናኝ የታወቀ ሲሆን በርካታ ዜጎች ከእነትጥቃቸው ተሰውረዋል ተብሏል።
Ø
በጉጂ ሕዝባዊ በአላሙዲን ንብረት በሆነው
ሜደሮከ የሚቆፈረው የወርቅ ቁፋሮ እንዲቆም በመጠየቅ እየተካሄደ ያለው ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የቀጠለ መሆኑን ከአካባቢው
የሚደርሱ መረጃዎች እየተጠቆሙ ያሉ ሲሆን ሕዝባዊ ቁጣውም መርታችኋል የተባሉ ሰባት ወጣቶች በፖሊስ ታፍነው ወደ ሀገረ ማርያም
መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል።
በተያያዘ
ዜና በሀረር መኤሶ ከተማ አሰቦት ወረዳ ውስጥ የወያኔ አለቅላቂዎችና አድርባዮች ባደረጉት ጥቆማ መሰረት ፖሊሶች ቤት ለቤት
በመሄድ ተቃውሞውን መርታችኋ ተሳትፋችኋ የተባሉ ሰላማዊ ስዎችን የያዙ መሆናቸው ታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ
የኦህዴድ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊና የመኢሶ ከተማ አስተዳደር የነበረውን ሹም የነበረው የተያዘ መሆኑ ከስፍራው የደረሰን
መረጃ ይጠቁማል።
Ø
ትናንት ጥር 30 ቀን 2008 ዓ/ም በአርሲ ጎለልቻ በተባለው አካባቢ አንድ አይሱዙ የህዝብ ትራንስፖርት
መኪና ሁለት መቶ ሜትር ጥልቀት ባለው ገደል ገብቶ የተሳፋሪዎች ህይወት ማለፉን ከስፍራው የመጣ ዘገባ ገለጠ:: ተሽከርካሪው 55
ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ሲሆን በግሎልቻና በጮሌ ወረዳዎች መካከል የሚገኘውን ዳገት በመውጣት እንዳለ ተንሸራቶ ገደል ውስጥ
የገባ መሆኑ ተዘግቧል። በአደጋው 22 ሰዎች መሞታቸው የተነገረ ሲሆን የአካል
ጉዳት ደርሶባቸው በህይወት የተረፉትን ከገደል ለማውጣት
የተቻለ መሆኑ ታውቋል።
Ø
ትናንት ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም በዋሽንግተን ዲሲ
በሚገኘው ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስርያ ቤት ጀምሮ እስከ አሜሪካው ምክር ቤት ድረስ በርካታ ኢትዮጵያውያን የተገኙበት
ታላቅና ደማቅ ሰልፍ ተደርጓል። 21 የሚሆኑ የሃይማኖት የፖሊቲካ የሲቪክ ማህበራት የሴቶች ድርጅቶች በተውጣጣ የጋራ ኮሚቴ
የተዘጋጀው ሰልፍ ላይ ከዋሽንግተን፤ ከቦስተን ፤ ከፍሎሪዳ፤ ከአትላንታ፤ ከቺካጎ፤ ከኖርዝ ካሎራይና፤ ከፔንሴልቪኒያ እና
ከኒውዮርክ የመጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈው የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰምተዋል። ወያኔ መሬት ለመንጠቃ ያደረገውን ሙከራ
የተቃወሙትን ሰላማዊ ዜጎች በግፍ መጨፍጨፉን አውግዘዋል፤
በዘርና በሃማኖት የሚያደርገውን ክፍፍልን ተያይዞ የሚያካሄደውን
ጭፍጨፋ ኮንነዋል እንዲሁም መሬታችንን ለሱዳን አሳልፎ መስጠቱን በብርቱ ተቃውመዋል። የተላያዩ መፈክሮችም በአማርኛና በኦሮምኛ
ተሰምተዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ህጋዊ ሲኖዶስ ጳጳሳትና የኢትዮጵያ ሙስሊም አባቶች ተገኝተዋል።
Ø
ትናንት
ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም በኒውዮርክ ከተማ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መስርያ ቤት ፊት ለፊት የዳግ ሃመርሾልድ
አደባበይ በሚባለው ቦታ ላይ በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በወያኔ እየተካሄደ ያለውን ጸረ ሕዝብ ድርጊት በማውገዝ የተቃውሞ
ሰልፍ
አድርገዋል። ሰልፉ የተዘጋጀው በኒውዮርክ በኒው ጀርሲ እና በኮኔትኬት ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ሲሆን በሰልፉ ላይ
ልዩ ልዩ የወያኔ አገዛዝ ጸረ ሕዝብ ድርጊትን የሚያጋልጡና የሚያወግዙ መፈክሮች ከመሰማታቸውም በላይ የድንበሩን ስምምነት
በመቃወም የተሰባሰበው የኢትዮጵያውያን ፊርማ ለተመድ ባለስልጣኖች ተሰጥቷል። በሰልፉ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች ውስጥ - “በወያኔና
በሱዳን መካከል የተደረገው የወሰን ስምምነት ህጋዊ አይደለም፤ በየቦታው የሚደረገው ግድያ መቆም አለበት፤ የመሬት ዝርፊያ ይቁም፤
መሬት የሕዝብ እንጅ የማፊያዎች አይደለም፤ ሕዝብን ከቦታ ቦታ ማፈናቀሉ ይቁም፤ አንንደነት ኃይል ነው” የሚሉ ይገኙባቸዋል።
Ø
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የጸጥታ ሁኔታ
ለማጠናከር በሚል ሽፋን የገጠር መኖሪያ ቤታቸውን ለማሰራት
23 ሚሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ አልአግባብ አውጥተዋል የሚለውን ክስ ለመመርመር
የደቡብ አፍሪካ ሕገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ስራውን በጀመረበት
ወቅት ፍርድ ቤቱ ጠንከር ያለ እርምጃ እንዲወስድ በመጠየቅ የደቡብ
አፍሪካ የፖሊቲካ የተቃውሞ ሰልፎች አድረገዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት
ገለልተኛ የሆነ ኮሚቴ ባቀረበው ዘገባ ፕሬዚዳንቱ በገጠር መሬታቸው ላይ የመዋኛ ቦታዎችን፤ የቲያትር ቤት፤
የዶሮ እርባታና የቀንድ ከብቶች ማኖሪያ ተቋሞችን የያዘ ግንባታዎች
የመንግስት ገንዘብ በማውጣት ያስሩ መሆናቸውን ያረጋገጠ ሲሆን ፕሬዚዳንቱም ከፊሉን ገንዘብ ለመመለስ መስማማታቸው ታውቋል። ይሁን
እንጅ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተር ፓርቲ የሚባለውና ዴሞክራቲክ አሊያንስ የሚባለው ድርጅት የሚስተር ዙማ እርምጃ በቂ አይደለም
በማለት ጉዳዩ ከሙስና ጋር የተያያዘ መሆኑን በመግለጽና ሚስተር ዙማ ከስልጣን እንዲነሱ በመጠየቅ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
Ø
በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና
የተደረገለት የሊቢያ መንግስት ንብረት የሆነ አንድ ተዋጊ አውሮፕላን ደርና በተባለችው አይሲስ በተቆጣጠራት ከተማ ላይ ጥቃት
ሲፈጽም ወድቆ የተሰባበረ መሆኑ ተገልጿል። አውሮፕላኑ ወርዶ የተከሰከሰው በቴክኒክ ምክንያት ነው የሚል ማብራሪያ ከአንዳንድ
ወገኖች ይሰጥ እንጅ በአይሲስ ኃይሎች ተመቶ ሳይሆን አይቀርም የሚለው ግምት የጠንከረ ነው። የአውሮፕላኑ አብራሪ በጃንጥላ ወርዶ
ህይወቱ ሊተርፍ ችሏል። ከአንድ ወር በፊት አንድ ሚግ 23 አውሮፕላን በቤንጋዚ አካባቢ ተመሳሳይ ጥቃት
ሲፈጽም የወደቀ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ ባለስልጣኖቹ የቴክኒክ ችግር ነው ቢሉም የአይሲስ ኃይሎች አውሮፕላኑን
መትተው መጣላቸውን ተናግረዋል።
Ø
የሱዳን መካለካያ ኅያል ላለፉት ሁለት ሳምንታት በዳርፉር
ጀበል ማራ በተባለው አካባቢ ባካሄደው ወታደራዊ ጥቃት አካባቢውን ከተቀናቃኝ ኃይሎች ነጻ ያወጣ መሆኑን ገልጾ ነዋሪዎቹ ወደ
ቤታቸው እንዲመለሱ ጥሪ አድርጓል። የመንግስቱ ተጻራሪ የሆኑት
ታጣቂ ኃይሎች የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች አካባቢውን እንዳልተቆጣጠሩ በመግለጽ ጠንካራ መግለጫ የሰጡ ሲሆን የአለም
አቀፉ ህብረተሰብ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቀዋል። ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በሱዳን መንግስት ወታደሮችና በታጣቂ ኃይሎች መካከል
በተነሳው ግጭት በ10 ሺ የሚቆጠሩ የጀበል ማራ ነዋሪዎች አካባቢውን ጥለው የተሰደዱ መሆናቸው ይታወቃል። እስካሁን በተደረጉ
ጦርነቶች የመንግስት ኃይሎች አካባቢውንና ወደ ቦታው የሚወስዱትን መንገዶች ሁሉ በቁጥጥር ስር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት የስብአዊ መብት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ሁኔታው ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸው ከቤት ንብረታቸው ተፍናቅለው
የተሰደዱት ዜጎች እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል። ባለስልጣኖቹ ጨምረው እንደገለጹት የተመድ ስራተኞች በጸጥታው ምክንያት እስካሁን
ወደ ቦታው ሊሄዱ
ያልቻሉ በመሆናቸው በዚያ አካባቢ ያለውን ሁኔታ ማወቅ አይቻልም
ብለዋል። በዳርፉር ግጭት ከተጀመረ ከ 2003 ዓም ጀምሮ ከ300 ሺ ሰዎች በላይ ህይወታቸው የጠፋ መሆኑና እንዲሁም ክ2.5
ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት ዋና ጸሀፊ ባንኪ ሙን በአፍሪካ በተባበሩ መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የተፈጸመውን አስገድዶ የመድፈር
ወንጀል ጉዳይ እንዲያስተባብሩ አሜሪካዊቷን ጄን ሆል ሉት የተባሉትን ሴት የመደቡ መሆናቸው ተገልጿል። ሴትየዋ በአሁኑ ወቅት
የኢራቅ ስደተኞችን እንደገና ለማስፈር በሚደረገው ተግባር የባንኪ ሙን የቅርብ አማካሪ ሲሆኑ ከ2003 እስከ 2008 ባሉት
ጊዜያት ውስጥ በተለያዩ ኃላፊነት ስርተዋል።
ጥር 30 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ሶስት ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ተብለው በታንዛኒያ ውስጥ የታሰሩ
መሆናቸውን አንድ የታንዛኒያ የዜና ምንጭ ከፖሊስ አካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ ገልጿል። የታሰሩት ኢትዮጵያውያን ታሪኩ
መንቼ፤ ኢዲሤ ታገሰ፤ ዘውዱ ሸምቦ የሚባሉ ሲሆኑ ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት ኪሊሚንጃሮ ከሚባለው አካባቢ ወደ ዋናዋ ከተማ ወደ
ዳሬሰላም በአውቶቡስ ሲያመሩ መሆኑ ታውቋል። ሰደተኞቹ
ይጓዙ የነበረው ወደ ደቡብ አፍሪካ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ያለህግ አገሪቷ ውስጥ በመግባት ወንጀል ተከሰው በዛሬው እለት ፍርድ
ቤት እንደሚቀርቡ ተነግሯል።
Ø
ባለፉት ሁለት ወራት በተለያዩ ቦታዎች ሲደረጉ የነበሩ ሕዝባዊ
እንቅስቃሴዎች አሁንም ያልበረዱ መሆኑ ይነገራል። በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በምዕራብ ሀረርጌ ግራዋ አካባቢና በጉጂ አካባቢ ተቃውሞ
እንደቀጠለ መሆኑና በርከት ያሉ ዜጎች መታሰራቸው ተዘግቧል። በሌሎች አካባቢዎችም አንጻራዊ ሰላም ያለ ቢመስልም ውጥረቱ የቀጠለ
መሆኑ ታውቋል።
በዛሬው ዕለት በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ የፖሊቲካ ድርጅቶች፤ የሲቪክ
ማህበራት አባላት የተለያዩ የሃይማኖት ተቋሞችና የተለያዩ ብሄረሰቦች አባላት የሚገኙበት
ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል። ዝርዝሩን እናቀርባለን።
Ø
በአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በአነስተኛ ክፍያ ለብዙ ዘመናት ከኖሩበት ከተወለዱበት ቀየ ላይ እያስነሱ መሬትን
በሊዝ መሸጥ ተስፋፍቶ የቀጠለ ሲሆን በአራዳ ክፍለከተማ በተለምዶ ቤል ኤር የተባለው አካባቢ በሊዝ መልክ ለባለሃብት ሊሸጥ መሆኑ
ታወቋል። በክፍለ ከተማው የግል ይዞታ ያላቸው ዜጎች ለነገ የካቲት አንድ ቀን የተጠሩ ሲሆን ስብሰባው መሬታቸውን ለመሸጥ
መታቀዱን ለመግለጽና የቅድሚያ ማግባባት ለማድረግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን ዘገባው ጠቁሟል። የግል ይዞታ ያላቸውን ነዋሪዎች ቤት
ለቤት እየዞሩ በመመዝገብ ካርታ ያወጡና ያላወጡትን የመለየት ስራ ትናንት እሁድ ጥር 29 ቀን ሲካሄድ መቆየቱን የገለጹት
ምንጮች ቤታቸውን
ለቀው እንዲሄዱ የሚደረጉት ነዋሪዎች ስለሚከፈላቸው የካሳ ክፍያ እና ስለሚነሱበት ግዜ ቅድመ ማግባባት ለማድረግ በተጠራው ስብሰባ
ልይ ይገለጻል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።
Ø
በተያያዘ ዜና ለቡ በተባለው አካባቢ በሊዝ ተሰጥተው የነበሩ መሬቶችን ለቀው እንዲወጡ
መመሪያ በተሰጣቸው መሰረት ባለሃብቶቹ የግንባታ ዕቃዎቻቸውን
በማንሳት ላይ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። መሬቱን በሊዝ የሸጠላቸው የአዲስ አበባ መስተዳድር ተለዋጭ መሬት የምታገኙበትን
መንገድ እንፈልጋለን ከማለት በስተቀር እስካሁን የወሰደው እርምጃ እንደሌለም ታውቋል።
Ø
እሁድ ጥር 29 ቀን 2008 ዓም ሰሜን ኮሪያ አንድ የጠፈር ተምዘግዛጊ መሳሪያ ማምጠቋ ታውቋል። የሰሜን
ኮሪያ ባለስልጣኖች ተመዝግዛጊው መሳሪያ (ሮኬቱ) የተተኮሰው በህዋው ላይ የሳተላይት ጣቢያ ለማስቀመጥ ነው የሚል ምክንያት
ቢሰጡም ሌሎች አገሮች ግን ዋናው ምክንያት ሰሜን ኮሪያ የቦለስቲክ
ሚሳየል ተክኖሎጂን ለመሞከር ያደረገቸው ነው እያሉ ነው። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ሮኬት ያመጠቀችው አራተኛውን የኑክሌር ሙከራ
ባደረገች በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ነው። ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ እንዲሁም የምዕራብ አገሮች ጉዳዮ በጣም ያሳሰባቸው መሆኑን የገለጹ
ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ባስቸኳይ ተሰብስቦ
የሰሜን ኮሪያን ድርጊት ማውገዙና ተጨማሪ የማዕቀብ ርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱ ተገልጿል። ከዚህ በፊት በሰሜን ኮሪያ
ላይ በተከታታይ የተደረጉት ማዕቀቦች በአገሪቱ የኑክለር
ፍላግትና ተግባር ላይ ያመጡት ተጽእኖ አነስተኛ ሲሆን ወደፊት የሚወሰደውም ማዕቀብ ምን ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል ግልጽ
አይደለም። በተጨማሪም ቻይና የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ቢፈነገል የሚከተለው ቀውስ ወደ አገሯ እንዳይዛመት ስለምተሰጋ ከበድ ያለ
ማዕቀብ በሰሜን ኮሪያ ላይ እንዳይወሰድ ታደርጋለች የሚል ግምት አለ።
Ø
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከሶማሊያ ዋና ከተማ ወደ ጅቡቲ ይበር በነበረው የዳዓሎ አየር መንገድ ንብረት
በሆነው አውሮፕላን ላይ የደረሰው ጉዳት በላፕ ቶፕ ላይ በተጠመደ ፈንጅ ምክንያት መሆኑን የሚያሳይ የቪዲዮ መረጃ ከሲሲቲቪ ላይ
ያገኙ መሆናቸውን የሶማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ገልጸዋል። የተገኘው የቪዲዮ መረጃ አንድ ተሳፋሪ ላፕ ቶፕ የሚመስል ዕቃ ከአውሮፕላን
ማረፊያው ሰረተኛ ሲቀበል የሚያሳይ ሲሆን ተሳፋሪው አውሮፕላኑ አደጋ ሲደርስበት በተፈጠረው ክፍተት ተስፈንጥሮ ወጥቶ የሞተ መሆኑ
ተነግሯል። ቦምቡን ያፈነዳው ተሳፋሪ ቀደም ብሎ ሊሄድ የነበረው በቱርክ አየር መንገድ ሲሆን የቱርክ አውሮፕላን በመሰረዙ
ምክንያት የዳአሎ አየር መንገድ ተሳፋሪውን ተቀብሎ ያሳፈረው መሆኑ ታውቋል። በሴራው እጃቸው አለበት በሚል የሱማሊያ የጸጥታ
ኃይሎች ወደ 20 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
ሱማሊያው ውስጥ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ወደ 58 ሺ የሚደረሱ ህጻናት በቂ እርዳታ ካልተሰጣቸው
ህይወታቸውን ሊያጡ እንደሚችሉ የተመድ ባለስልጥኖች ስኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓም
ገለጹ። ቢያንስ 305 ሺ የሚሆኑ ህጻናት በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ መሆናቸውን ገልጸው ከእነዚህ ውስጥ58 ሺ
የሚደርሱት በሞት አፋፍ ላይ መሆናቸው ተናግረዋል። ለአራት ተከታታይ ዓመታት በሱማሊያ በአንዳንድ ቦታዎች ድርቅ፤ በሌሎች ቦታዎች
የጎርፍ አደጋ በመድረሱ የብዙ ዜጎች ህይወት የተቃወሰ
ሲሆን የአገሪቱ አርባ ከመቶ የሚሆነው 4.7 ሚሊዮን ሕዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ ዜና በደቡብ ሱዳን በጦርነት ቀጠና ውስጥ ያሉ ቢያንስ 40 ሰዎች እየተራቡ መሆናቸውን
የተባበሩት መንግስታት ሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በሰጠውም መግለጫ አስታውቋል። የአገሪቱ 25 ከመቶ የሚሆነው 2.8
የሚሊዮን የሚሆነው ሕዝብ እርዳታ የሚፈልግ ሲሆን በግጭቶች በመስፋፋታቸው ምክንያት እርዳታውን ለማድረስ ያልተቻለ መሆኑ
ተነግሯል። እርዳታውን በወቅቱ ከሚፈለገው ቦታ ለማድረስ የጸጥታው ሁኔታ አስተማማኝ መሆኑ አስፈላጊ በመሆኑ ጦርነት
በሚያካሄዱባቸው ክፍሎች ትብብር ካልተገኘ በርካታ ዜጎች በምግብ እጥረት ሊሞቱ እንደሚችሉ ይኸው የተመደ ዘገባ አስታውቋል።
Ø
በቡርኪና ፋሶ ከአልካይዳ ግንኝነት እንዳለው በሚነገርለት ቡድን ታግተው የነበረ አውስትራሊያዊ ባልና
ሚስቶች ቡድኑ ሊፈታቸው እንደሚፈልግ ቀደም ብሎ መገለጹ የሚታወቅ ሲሆን ትናንት ጥር 29 ቀን 2008 ዓም
የሰባ ስድስት አመት እድሜ ያላቸው ሚስስ ጆስሊን ኢሊየት ተፈተው
በአገሪቱ ዋና ከተማ በዋጋዱጉ የገቡ መሆናችው ታውቋል። ሴትየዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ባለቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈቱ ተስፋ
ያላቸው መሆኑን ገልጸው ከባላቸው ጋር በመሆን ላለፉት 44 አመታት ሲሰጡ የነበረውን አገልግሎት ለመቀጠል ፍላጎት ያላቸው መሆኑን
ገልጸዋል። በንግግራቸው የቡርኪና ፋሶን መንግስትና ሌሎች ትብብር ያደረጉላቸውን ወገኖች አመስግነዋል። ሰዎችን ለማስፈታት
መንግስት በተዘዋዋሪ ከአጋቾቹ ጋር መነጋገሩ ፍንጭ ያለ ሲሆን ምንም ዓይነት የገንዘብ ክፍያ ያልተከፈለ መሆኑን ግን የመንግስቱ
ባለስልጣኖች ተናግረዋል። የሴትዮዋ ባለቤት መች ሊፈቱ እንደሚችሉ
የሚገልጽ መረጃ እስካሁን አልተገኘም።
Ø
ትናንት እሁድ ጥር 29 ቀን 2008 ዓም በካይሮ ደቡባዊ ክፍል የግብጽ ፖሊሶች አንድ መኖሪያ ቤት
ለመፈተሽ ጥረት ባደረጉበት ወቅት በተነሳ የተኩስ ልውውጥ አራት
ሰዎች የተገደሉ መሆናችው ታውቋል። የግብጽ ባለስልጣኖች የተገደሉት ሰዎች አሸባሪዎች ናቸው ብለው የወነጀሏቸው ሲሆን ቤቱም ቀላል
ቦምቦች የመስርያ ቦታ እንደነበረ ተናግረዋል። የአሁኑ የግብጽ መንግስት በስልጣን ከተሰየመ ጀምሮ የአስልምና ወንድማማቾች ቡድን
በጸጥታ ኃይሎች ላይ የተለያዩ ጥቃቶች ሲፈጽም የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተገደሉት አራት ሰዎች ቀደም ብሎ ሁለት
ወታደሮችንና ሁለት ፕሊሲችን የገደሉ አሸባሪዎች መሆናቸውን የግብጽ የጸጥታ ባለስልጣኖች ገልጸዋል።፡
ጥር 28 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በጋምቤላ የነበረውን ግጭት በቁጥጥር ስር ለማደረግ የወያኔ አግአዚና የፌዴራል ጦር ወደ ከተማዋ
መግባቱ የተነገረ ቢሆንም ግጭቱና ውጥረቱ
እስካሁን ያልበረደ መሆኑን ከስፍራው የሚደርሱት የተለያዩ
መረጃዎች ይገልጻሉ፡፡ ትናንት ጥር 27 ቀን 2008 ዓም
በደል ደርሶብናል ያሉ የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት ፒንዩዲ
በተባለ የመጠለያ ጣቢያ ሄደው የኑዌር ተወላጆች ከሆኑ ጠባቂዎች
ጋር ባደረጉት ግጭት ሶስት የአኙዋክ ተወላጆችና አንድ የኑዌር ተወላጅ እንደሞተ ተነግሯል። በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ጎጆዎችም
በእሳት ተቃጥለዋል ተብሏል። የወያኔ ጦር በከተማ ሆነ በአንዳንድ ወረዳዎች የተሰማራ ቢሆንም በተለይ በአኙዋክ ብሔረሰብ አባላት
የተጠላና የማይታመን በመሆኑ ጸጥታውን ሙሉ በሙሉ ለማስከበር ያልቻለ መሆኑ ይነገራል። የእንግሊዝ መንግስትና ሌሎች የምዕራብ
አገሮች ዜጎቻቸው ወደ ጋምቤላ እንዳይንቀሳቀሱ መመሪያ ያስተላለፉ መሆናቸው ተያይዞ የመጣው ዜና ያስረዳል።
Ø
በመቀሌ ስለመልካም አሰተዳደር
ችግሮች ለመወያየት ተሰብሰቦ የነበረው የከተማዋ ነዋሪ የመጠጥ ውሃ
አቅርቦት ችግር በከፍተኛ ደረጃ እያስመረረው መሆኑኑን ገለጸ።
በመቀሌ በአራት ቀን በፈረቃ የመጠጥ ውኃ ለማዳረስ ቢሞከርም ህዝብ የመጠጥ ውሃ ችግሩ እየተባባሰ እንጂ መፍትሄ
ሆኖለት እንደማያውቅ ለማወቅ ተችሏል። የመሰለ ችግር
በምታስተናግደው መቀሌ የመልካም አስተዳደር ችግር ዙሪያ ውይይት አድርጉ የተባሉት ነዋሪዎች አብዛኞቹ የሚገኝ መፍትሔ የለም
በማለትና ተስፋ በመቁረጥ በስብሰባው ላይ ለመገኘት ፈቃደኛ
ሳይሆኑ ቀርተዋል ተብሏል።
Ø
ዛሬ ጥር 28 ቀን 2007 ዓም ከሌሊቱ አስር ሰዓት አካባቢ በታይዋን ደሴት በሬክተር መለከያ 6.4 ኃይል
ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰ መሆኑ ታውቋል። የመሬት መንቀጥቀጡ ቴይናን በተባለችው ከተማ የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሰነጣጠቀና
የደረመሰ ሲሆን እስካሁን ድረስ በደረሰው መረጃ 12 ሰዎች መሞታቸውና ከ500 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል። 30
ሰዎች በአንድ በፈረሰ ህንጻ ውስጥ መውጫ ያላገኙ መሆናቸው
የታወቀ ሲሆን ከሞቱት መካከል አንደኛው ገና የተወለደ ህጻን መሆኑም ተዘግቧል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች
ህይወት ለማትረፍ ከፍተኛ ጥረት የሚደረግ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የጦር ኃይል አባላት ለነፍስ አድኑ ሥራ መሰማራታቸውና በየቦታውም
የመጠላያ ቦታዎች መሰናዳታቸው ተገልጿል። የ256 ሰዎች መኖሪያ የነበረው ባለ አስራ ሰባት ፎቅ ህንጻ በመሬት መንቀጥቀጡ ኃይል
ከላይ እስከታች የፈረሰ መሆኑ ታውቋል።
Ø
ትናንት ጥር 27 ቀን 2008 ዓም በአልሸባብ ቁጥጥር ስር ወድቃ የነበረችውንና መርካ የተባለችውን የወደብ
ከተማ የሶማሊያ መንግስት የመከላከያ ጦር ከአፍርካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ማድረጋቸው
ታውቋል። ከአልሸባብ ታጣቂዎች የተደረገው ውጊያ አነስተኛ
ቢሆንም በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተዘግቧል። በከተማዋ የነበረው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ከከተማው
የወጣው ጨርሶ ለመልቀቅ ሳይሆን ከወታደራዊ ታክቲክ አንጻር መሆኑን በትናንትናው ዕለት መግለጹ ይታወሳል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ በተረደመስ አንድ የማዕድን ጉድጓድ ውስጥ የነበሩ 87 የማእድን ስራተኞች በህይወት ተርፈው
ከጉድጓድ ለመውጣት የቻሉ ሲሆን ከሰራተኞቹ ውስጥ ሶስቱ ግን እስካሁን በጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው ይገኛሉ። አደጋው የደረሰው
በትናንናው ሌሊት ሲሆን ለሰላሳ ስድስት ሰዓት በተደረገ ፍለጋ
የጠፉትን ሶስት ሰዎች ማግኘት ያልተቻለ መሆኑ ታውቋል። ህይወታቸው የዳነው 87 ሰራተኞች የህክምና ምርመራ
ተደርጎላቸው ምንም ዓይነት ጉዳት ያላጋጠማቸው መሆኑ ተነግሯል።
Ø
ባለፈው ወር አንድ የአውስትርሊያ ዶክተርንና ባለቤታቸውን በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ከሚገኝ
አንድ ሆቴል ውስጥ ጠልፎ እስካሁን አግቷቸው የቆየው አካል አል
ሙራቢቱን የተባለውና ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያለው ቡድን መሆኑን በድምጽ ካስተላለፈው መልእክት ለመረዳት ተችሏል። ቡድኑ አርብ
ዕለት ባስተላለፈው መልእክት የሰዎቹ መታገድ በመንግስት ታስረው የሚገኙትን የቡድኑን አባላት በለውጥ ለማስልቀቅ አላማ አድርጎ
የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ቡድኑ የያዛቸውን ሰዎች ያለምንም
ቅድመ ሁኔታ ለመልቀቅ የወሰነ መሆኑን ገልጿል። የአውስትራሊያው ዶክተርና ባለቤታቸው ከ 1980 ዓም ጀመሮ ጂቦ በምትባለው ከተማ
120 አልጋዎች ያሉት አንድ ክሊኒክ አቋቋመው የአካባቢውን ሰዎች ሲረዱ መቆየታቸው ይታወቃል።
ጥር 27 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ወያኔ በሠራዊቱ ውስጥ ድንገተኛ የሆነ የሰው ኃይል ቅነሳ አድርጎ አዲስ በሚመለመሉ ሊተካ መሆኑን የታመኑ
የመከላከያ ምንጮች አጋለጡ። ከጥቂት ቀናት በፊት የወያኔ የጦር አለቆች በተከታታይ የአካሄዱትን የግምገማ ስብሰባ ተከትሎ እዝን
ባለማክበር በተደጋጋሚ ትእዛዝ እየጣሱ ያሉትንና የተቃዋሚ ደጋፊ ናቸው ተብለው የሚጠረጥሩ የሰራዊት አባላትን በብዛት ለማባረር
መወሰኑን የታመኑ ምንጮች ባስተላለፉት መረጃ ለማወቅ ተችሏል። በሰራዊት ህግ መሰረት የፈጸሙት ጥፋታቸው እስራትና ሌሎች ከባድ
ቅጣቶች ሊያስከትሉ ቢችሉም በአሁኑ ወቅት ይህንን ተግባራዊ ማድረግ ሌሎችን አስቆጥቶ ተቃውሞ ያስነሳል ከሚል ስጋት ከሰራዊት
ማሰናበቱ የተሻለ መፍትሔ ይሆናል በሚል የወሰኑ መሆናቸው ታውቋል። በተለይ
ከሕዝባዊ ተቃዋሞ ጋር በተያያዘ
ሰላማዊ ሰዎችን በጥይት መገደል የለባቸውም የሚሉ አስተያየቶችን
የሰጡና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ጠይቀው የነበሩ
የሰራዊቱ አባላት ላይ የስንብቱ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚከናወን
ከምንጮቹ መረጃ ለመረዳት ተችሏል።
Ø
ስዋይን ፍሉ (የአሳማ ጉንፋን) የተባለው አደገኛ
የኢንፍሎንዛ በሽታ ኢትዮጵያ ውጥ የገባ መሆኑ ምንጮች አጋለጡ። በዚህ ሳምንት ውስጥ በየካቲት 12፤ በጥቁር አንበሳና በራስ
ደስታ ሆስፒታሎች የስዋይን ፍሉ የሚባለው የኢንፍሎንዛ ታማሚዎች መገኝታቸውን ለማወቅ ትችሏል። የወያኔው የጠና ሚንስቴር
እንደተለመደው አንዴ ስዋይን ፍሉ አይደለም ሌላ ጊዜ የዚህ በሽታ አደገኛነት አነስተኛ ነው በማለት ያጣጣለው ቢሆንም
በበሽታው አንዳንድ ሰዎች እንደሞቱ ይነገራል። የበሽታው ናሙና
ለምርመራ ወደ አሜሪካ የተላከ ስሆን ውጤቱ እየተጠበቀ ነው ተብሏል። ስዋይን ፍሉ የዛሬ ሰባት ዓመት ምንነቱ በምርመራ
የተደረሰበት ገዳይ የሆነ ተላላፊ በሽታ ሲሆን እንደማንኛውም የኢንፍሎንዛ በሽታ ከፍተኛ ትኩሳት፤ ደረቅ ሳር ራስ ምታት ያለውና
በተለይ በዕድሜ የገፉትንና በሌሎች በሽታዎች የተጠቁትን የሚጎዳ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በኢትዮጵያ የገባው ድርቅና ረሃብ በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን
የተለያዩ ክፍሎች እየገለጹ ይገኛሉ። ሰሞኑን በአፋርና በምስራቅ ትግራይ ተዘዋውሮ ሁኔታዎችን የተመለከተው ጋዜጠኛ የድርቁ ሁኔታ
በጣም አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል። በተዘዋወረባቸው ቦታዎች በርካታ የቀንድ ከብቶች መሞታቸውንና የሚበሉት ምግብ የሌላቸውን ዜጎች
የተመለከተ መሆኑን ገልጿል። በአንዳንድ ቦታዎች ምርቶች ጨርሶ የወደሙበት ወይም ከ90 ከመቶ በላይ የቀነሱብት እንደሆነ
ተጥቁማል። በሚቀጥሉት ወራት ከ15 ሚሊዮን በላይ በድርቁ የተጠቁ ሰዎች
እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ልዩ ልዮ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በጣም
አስቸኳይ በሆነ መንገድ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥ ከ10 ሚሊዮን በላይ መሆኑ ተጠቁሟል። በድርቅና በረሃብ የተጎዱ
ወገኖቻችንን ለመታደግ የሚያስፈልገው እርዳታ ከ 1.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተተመነ ሲሆን እስካሁን ከውጭ በእርዳታ መልክ
የተገኘው 169 ሚሊዮ ዶላር ብቻ መሆኑ ሁኔታውን በጣም አሳሳቢ ያደርገዋል ተብሏል።
Ø
ዛሬ ጥር 7 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልሸባብ
የተባለው ቡድን ከዋናዋ ከተማ ከሞጋዲሾ 70 ኪሎሜትር
ርቀት ላይ የምትገኘውንና መርካ የተባለችውን የወደብ ከተማ መቆጣጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ለዜና ተቋሞች በሰጡት መረጃ ገልጸዋል።
ላለፉት ሶስት ዓመታት በከተማዋ ሰፍሮ ጸጥታ ሲያስከብር የነበረው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ዛሬ ጥር 27 ቀን
2008 ዓም ከተማዋን ለቆ የወጣ ሲሆን የአልሸባብ ኃይሎች ወደ ከተማዋ የገቡት አለምንም ተኩስ መሆኑ ተረጋግጧል። ከተማዋ
በአልሸባብ ቁጥጥር ስር መውደቋ በሰላም አስከባሪው ኃይል አባላት ላይ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት የሚያስከትል ሲሆ በሞጋዲሾ
ለሚገኘውም የሱማሊያ መንግስት ከፍተኛ ተጽእኖ ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከሶስት ሳምንት በፊት ኤል አዴ በተባለ ቦታ አልሸባብ ጥቃት ፈጽሞ በዚያ የነበሩትን 100 የኬኒያ ወታደሮች መግደሉን
መግለጹና የኬኒያ መንግስት የሞቱትን ወታደሮች ቁጥር ባይገልጽም ጉዳት መድረሱን በመግለጽ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል።
Ø
ዛሬ ጥር 27 ቀን 2008 ዓም ማሊ ቲምበክቱ ከተማ ውስጥ በሚገኘው
የተመድ ዋና ጽቤት አጠገብ አንድ ቦምብ የፈነዳ መሆኑና በበጸጥታ ኃይሎች እና በአጥቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ የተደረገ
መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ገልጿል። አንድ ሰው የአካል ጉዳት ደርሶበት ህክምና ወደሚያገኝበት አካባቢ የተወሰደ ሲሆን
የተመድ ተልእኮ ቡድን መቀመጫውን የከተማ አውሮፕላን ጣቢያ ወደሚገኝበት አካባቢ ያዛወረ መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት የተመድ
ኃይሎችና የማሊ መንግስት ከአጥቂዎቹ ጋር ጦርነት የገጠሙ
መሆናቸው ታውቋል። የዛሬ አራት አመት ከአልካይዳ ጋር
ግንኙነት አላቸው ተብለው የሚጠረጠሩ አማጽያን የሰሜን ማሊን ግዛት ወርረው በቁጥጥር ስር ማድረጋቸውና በፈረንሳይ ወታደሮች
እርዳታ ከአካባቢ እንዲወጡ የተደረገ መሆኑ ይታወሳል።
Ø
አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውይይት ቡድን ላለፉት አራት
አመታት ለንደን በሚገኘው የኢኳዶር ኤምባሲ ተጠልለው የሚገኙት የዊኪሊክ መስራች ጁሊያን አሳንጅ ነጻ ናቸው የሚል ውሳኔ የሰጠ
መሆኑ ተገለጸ። አሳንጅ የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ኤምባሲዎች ሲያደርጉት የነበሩትን የሚስጥር መልእክቶች ልውውጦች በኢንተርኔት
አማካይነት ለሕዝብ ይፋ በማደረግና በማጋለጥ የታወቁ ሲሆን
አሳንጅ አሜሪካ መጥተው ለፍርድ እንዲቀርቡ የአሜሪካ ባለስልጣኖች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል። የስዊድን መንግስት
አሳንጅን ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር ወንጀል ተከሷልና ወደ ስዊድን መጥተው ራሳቸውን እንዲከላከሉ የእንግሊዝ መንግስትን የጠየቀው
ጥያቄ እሳቸውን ወደ አሜሪካ ለመላክ የተደረገ የሽፋን ሴራ ነው ከሚል ፍራቻ እንግሊዝ አገር በሚገኘው የኢኳደር ኢምባሲ ውስጥ
ጥገኝናት ጠይቀው ላለፉት አራት አመታት በኤምባሲ ውስጥ ቆይተዋል። አለአግባብ የሚታሰሩትን ሰዎች ጉዳይ ለመመርመር በተባበሩ
መንግስታት ድርጅት የተቋቋመውና አምስት ሰዎች የሚገኙበት
ፓናል የጁሊያን አሳንጅን ጉዳይ መርምሮ በሰጠው ውሳኔ በዓለም አቀፍ ህዝብ መሰረት አሳንጅ የሚያሳስራቸው ምንም ምክንያት የሌለ
መሆኑን ገልጾ እንግሊዝና ሲውድን አለአግባብ አስሯቸዋል የሚል ውሳኔ አስተላልፏል። የኮሚቴው ውሳኔ በስራ ላይ የሚውልበት ህጋዊና
መዋቅራዊ መሰረት ባይኖርም አሳንጅና የአሳንጅ ደጋፊዎች የሞራል
የበላይነትን አግኝተዋል ተብሏል። የእንግሊዝ መንግስት ባለስልጣኖች አሳንጅ በፈቃዳቸው በኢኳደር ኢምባሲ ገብተው ተደበቁ እንጅ
በእንግሊዝ መንግስት በኩል የተወሰደ እርምጃ እንደሌለ ገልጸው ውሳኔው መሰረተ ቢስ ነው ብለውታል። ሚስተር አሳንጅ ቀደም ብለው
ባስተላለፉት መልክት የተመድ ፓናል በዚህ መልክ ውሳኔ ከሰጠ ፓስፖርታቸው እንዲመለስላቸውና
በሳቸው ላይ የተጣለው ክስ ውድቅ እንዲሆን ጠይቀዋል።
ጥር 26 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ለቡ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአዲስ አበባ መስተዳድር ለኢንቨስትመንት
ግልጋሎት ተብሎ በሊዝ መሬት ተሸጦላቸው የነበሩትና ግንባታ
የጀመሩትም ሆነ ባለሀብቶች ግንባታዎችን ባስቸኳይ አፍርሰው መሬቱን እንዲያስክቡ የሚል ድንገተኛ መመሪያ የተሰጣቸው መሆኑን
የታመኑ ምንጮች አጋለጡ። ለቡ በተባለው አካባቢ ለኢንቨስትመንት በሊዝ መሬት ከአዲስ አበባ መስተዳድር ገዝተውና ተረክበው
የግንባታ ስራዎችን የሚሰሩ በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ አገር
ባለሃብቶች ያሉ ሲሆን በተሰጠው መመሪያው ምክንያት ከፍተኛ ኪሳራ ሊደርስባችው እንደሚችል ተገምቷል። መመሪያው የተሰጠው ከኦሮሚያ
ክልል ተብየው ባለስልጣኖች ሲሆን መሬቱ የኦሮሚያ ክልል
እንጅ የአዲስ አበባ መስተዳድር ስላልሆነ ባስቸኳይ ካላስረከቡ በኦሮሚያ አፍራሽ ግብረ ኃይል የሚፈርስ መሆኑ ተነግሯቸዋል።
በለቡ የተጀመረው የመሬት ነጠቃ ከቀጠለ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ገላን በተባለው አካባቢ
የኢንዱስትሪ ዞን ግንባታ በሚል የድሪባ ኩማ ቢሮ በሊዝ የሸጠላቸው የውጭና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች ከፍተኛ
ስጋት ላይ መሆናቸውን ታዛቢዎች ሳይጠቁሙ አላለፉም።
በለቡ አካባቢ በሊዝ መሬት ከአዲስ አበባ መስተዳድር የገዙ ባለሃብቶች
ማስጠንቀቂያ ሰጡን ያሉዋቸው ከኦሮሚያ ልዩ ዞን አስተዳደር የመጡ
የስራ ሃላፊዎች በመሆናቸውና በሁኔታው በመደናገጣቸው ሽያጩን ለፈፀመላቸው የአዲስ አበባ አስተዳደር ሊዝ ቢሮ አቤቱታ ማቅረባችውን
ተናገረዋል። አፋጣኝ መፍትሄ ባለማግኘታቸው ከንቲባው ድሪባ ኩማ ዘንድ አቤት ለማለት ቀጠሮ ማስያዛቸውም ተረጋግጧል።
Ø
በኦሮሚያ ባለስልጣናት መካከል እየተደረገ ያለው የውስጥ ግምገማው
ያልተጠናቀቀ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አንዳንድ የኦህዴድ ባለስልጣኖች
ለወያኔ ደህንነት ቃላቸውን እንዲሰጡ የተገደዱ መሆናቸው ታውቋል። በባለስልጣኖቹ ቤቶች ዙሪያ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን የሚጠቁመ
መረጃው እየመጡ ሲሆን አመጹን ለማብረድና ችግሩን ለመቅረፍ በየካቲት ወር በየዞኑና በየወረዳው ህዝባዊ ስብሰባ ለመጥራት
መታቀዱንም ለማወቅ ተችሏል። በተያያዘ ዜና በሕዝባዊ አመጽ ምክንያት በወያኔ አግአዚ ጦር ከየቦታው ተለቅመው የታሰሩ ወጣቶች
በየእስር ቤቱ ከፍተኛ ድብደባ እየተደረገባቸው መሆኑ ከየአቅጣጫው የሚደርሱት ዜናዎች ይጠቁማሉ።
Ø
ከመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ወያኔ ስብሰባ ጠርቶ እያነጋገረ ሲሆን
በተለያዩ ቦታዎች የተደረጉት ስብሰባዎች የጠበቀውን ውጤት
ያላስመዘገቡ መሆናቸው ተነግሯል። በአዲስ አበባ ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት በሚገኝ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ በተደረገው
ስብሰባ ላይ ስብሰባውን የመሩት የወያኔ ባለስልጣኖች የመልካም አስተዳደር ችግር የደረሰባችሁ ነዋሪዎች እየተነሳችሁ ማስረዳት
ትችላላችሁ በማለት ከሕዝብ መረጃ ለማግኘት ቢጥሩም “ህዝቡ
በተለያየ አጋጣሚ ሲናገርና ሲያለቅስበት የቆየበትን ችግር አናውቅም እያላችሁ እንዴት እንደ አዲስ ትጠይቁናላችሁ፤ በጉያችሁ
ያቀፋችሁትን አሜክላ ታውቁታላችሁና እናንተው እዚያው ጨርሱት” በማለት ነዋሪው መልስ የሰጣቸው መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።
በተጨማሪም በመለስተኛና በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ የንግድ ማህበረሰብ አባላትን ቤት ለቤት እየዞሩ
ያነጋገሩት የወያኔ ካድሬዎች መንግስት እንዲኖር ከፈለጋችሁና የንግድ ስራችሁ እንዲስፋፋ ከፈለጋችሁ ተደራጁ፤ ከተደራጃችሁ
መንቀሳቀሻ እንዳይቸግራችሁ ገንዘብ በረዥም ግዜ የሚከፈል ብድር እንሰጣችኋለን በማለት ለማግባባት ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር
የደረሰን መረጃ ይገልጻል።
Ø
የአባይን ግድብ አስመልክቶ ለመነጋገር የተመሰረተው የሶስቱ አገሮች
የቴክኒካል ኮሚቴ በሚቀጥለው እሁድ ካርቱም ሱዳን ላይ የሚሰበሰብ መሆኑን የግብጽ የመስኖን ሚኒስትር ረቡዕ ዕለት ለጋዘጠኞች
በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫ
የግብጹ የቴክኒክ ኮሚቴ የፈረንሳዩ አጥኝ ቡድን ሊያደርግ ስላለስበው ጥናት ጉዳይ ባቀረበው ሪፖርት ላይ የጀመረውን ውይይት በዚህ
ሳምንት አጠናቅቆ ወደ ካርቱም ይጓዛል ብለዋል።
በቅርቡ የፈረንሳይ አጥኝ ኩባንያ ስለግድቡ በሰጠው ሀሳብ ላይ የደረሱበትን መደምደሚያዎች ሶስቱም አገሮች በካርቱሙ ስብሰባ ላይ
የሚያቀርቡ ሲሆን ስምምነት ከተፈጠረ አጥኘው ኩባንያ ጥናቱን እንዲጀምር መመሪያ የሚሰጠው መሆኑ ታውቋል።
Ø
በጥብቅ ሚስጥር የተያዘ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር
ዘገባ የብሩንዲን ፕሬዚዳንት ከስልጣን ለማስወገድ የሩዋንዳ
መንግስት ወደ አገሩ ከተሰደዱት ስደተኖች መልምሎ ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አጋልጧል። በኮንጎ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ
እንዲከታተል በተመድ የተመደበው የሙያተኞች ቡድን ባቀረበው ዘገባ የተመለመሉት ስደተኞች በሩዋንዳ የወታደራዊ ካምፕ ውስጥ
ወታደራዊ ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል። የሙያተኛው ቡድን ኮንጎ ውስጥ አግኝቶ ያነጋገራቸውና ወታደራዊ ስልጠና የተሰጣቸው
18 የብሩንዲ
ተወላጆች የሰጡትን ቃል መሰረት በማድረግ
ባቀረበው ዘገባ ሩዋንዳ ውስጥ ከሚገኘው ከማህማ ስደተኞች ካምፕ መመልመላቸውንና ለሁለት ወራት ያህል ወታደራዊ ስልጠና በጫካው
ስጥ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጸዋል። በተመድ የሩዋንዳው ልዮ መልእክተኛ በሙያተኛው ቡድን ዘገባው
ላይ የቀረበውን ክስ መሰረተ ቢስ ነው በማለት ያጣጣሉት ሲሆን ቡድኑ
ከተሰጠውው ተልእኮና ኃላፊነት ውጭ እየሰራ ነው ብለዋል። ካለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀምሮ የብሩንዲው ፕሬዚዳንት
ለሶስተኛ የምርጫ ዘመን ለመወዳደር ያደረጉትን ውሳኔ በመቃወም በተነሳው ግጭት ምክንያት
በመቶ የሚቆጠሩ የብሩንዲ ዜጎች ያሉ የሞቱ ሲሆን በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ደግሞ መሰዳዳቸው ይታወሳል።
Ø
የአሸባሪው ድርጅት የአይሲስ መሪዎችና አባላት ባለፉት ጥቂት ወራት
ከኢራክና ከሶሪያ በመሸሽ ወደ ሊቢያ የገቡ መሆናቸውን የሊቢያ የጸጥታ ኃላፊዎች ገለጸዋል። በሊቢያ የምትገኘው ሰርት የምትባለው
ከተማ ባለፈው ዓመት በአይሲስ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መውደቋ የሚታወቅ ሲሆን ከኢራክና ከሶሪያ የሸሸቱ የድርጅቱ መሪዎችና አባላት
የገቡት ወደዚች ከተማ ነው ተብሏል። ባለፈው ማክሰኞች ጥር 24
ቀን 2008 ዓም አሜሪካንና እንግሊዝን ጨምሮ የ23 አገሮች ተወካዮች ሮም ውስጥ አይሲስ በሊቢያ ውስጥ በሚያመጣው አደጋ ላይ
ለመወያያት መሰበስባችው የታወቀ ሲሆን በሊቢያ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር አለመቻሉ
እርምጃ ለመውሰድ ያላስቻለ መሆኑ ተነገሯል።፡
Ø
አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የእርዳታ ሰጭ አገሮች ስብሰባ ላይ
የስዊዘርላንድ መንግስት በናይጄሪያ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ያለውን ቦኮ ሃራምን ለመቋቋም ለተደረገው ወታደራዊ ጥቃት የ12 ሚሊዮን
ዶላር ሰጥቷል ተብሎ የተሰጠው መረጃ ትክክል አለመሆኑን የስዊዘርላንድ መንግስት አስተባብሏል። የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ
ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ ስዊዘርላንድ በተፈጠሩ ግጭቶች ሁሉ ዘወትር የገለልተኛነት ሚናን የምትወስድ መሆኑ እየታወቀ የተሰጠው
ገንዘብ ለወታደራዊ ጉዳይ ነው የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ጠቅሶ የተባለው ገንዘብ የተሰጠው በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ዜጎች መርጃ
ነው በማለት መረጃው እንዲስተካከል ጠይቋል። አዲስ አበባ ላይ የተሰበሰበው የእርዳታ ሰጭ አገሮች ስብሰባ ቦኮ ሃራምን ለመቋቋም
250 ሚሊዮን ዶላር ለመርዳት ቃል መግባታቸው ታውቋል።፡
Ø
የዓለም የጤና ድርጅት ተወካይ ረቡዕ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም
በሰጡት መግለጫ በሲየራ ሊዮን የኢቦላ በሽታ እንደገና እየተስፋፋ መሄዱን ገልጸው በበሽታው የተለከፉ 48 ሰዎች
በመሰዋራቸው ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል። ባጠቃላይ በአሁኑ ወቅት በበሽታው የተለከፉ 70 ሰዎች ተገልለው ህክምና
እየተደረገላችው መሆኑን ጠቁመው ከጠፉት መካከል 18 የሚሆኑት የያዛቸው
በሽታ የአደጋ መጠን ከፍተኛ ነው ብለዋል። ተወካዩ በሆስፒታሎችና በመንደሮች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደርግም አሳስበዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የኢቦላ በሽታ በምዕራብ አፍሪካ በሚገኙ ሶስት አገሮች 11300 ያህል ሰው የጨረሰ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ
4000 የሚደርሱት የሲየራሊዮን ዜጎች መሆናቸው ይታወቃል።
ጥር 25 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ሰኞ ተነስቶ በነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ምክንያት የቡታጅራ ከተማ
አሁንም ውጥረት ነግሶ የሚታይበት ሲሆን ከወልቂጤ ተጠርቶ
በመጣው የአግአዚ ጦርና የፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወደ ወልቂጤ ተወስደው የነበሩ አስራ ስድስት የሚሆኑት ሰዎች ይህ ዘገባ
እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ያልተመለሱ መሆናቸውን
ከስፍራው ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የመሰንቃ ወረዳ አመራረሮችን ለመግደል ሙከራ አድርጋችኋል፤ የታጣቂዎችን መሳሪያ
ለመንጠቅ ሞክራችኋል ፖሊሶች ላይ ድብደባ ፈጽማችኋል የሚል ክስ ለማቅረብ ቃላቸውን እንዲሰጡ የተደረገ መሆኑን ጉድዮን የሚያውቁ
ምንጮች የገለጹ ሲሆን ሰኞ ለማክሰኞ አጥቢያ ከፍተኛ ድብደባ ሲፈጽምባቸው ያደሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
Ø
ጥር 7 ቀን 2008 ዓም ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ
በታንዛኒያ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ 83
ኢትዮጵያውያን ፍርድ ቤት ቀርበው እያንዳንዳቸው የሶስት ዓመት እስራት ወይም የአንድ ሚሊዮን የታንዛኒያ ሽልንግ (460 ዶላር)
ካሳ እንዲከፍሉ የተፈረደባቸው መሆኑ የታንዛኒያ የዜና
ምንጮች ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያኑን በአነሰተኛ የጭነት
መኪና አመላልሳችኋላ የሚል ክስ የቀረበባቸው ሁለት የታንዛኒያ ዜጎች እያንዳንዳቸው የአምስት አመት እስራት ወይም 1.5 ሚሊዮን
የታንዛኒያ ሽልንግ (688 ዶላር) እንዲከፍሉ የተፈረደባቸው መሆኑ ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
በተመሳሳይ መልኩ ከሁለት ቀን በፊት የዛምቢያ ፍርድ ቤት በ 33 ኢትዮጵያውያን ላይ የእስራት ፍርድ የፈረደ መሆኑ
የሚታወስ ሲሆን እነዚህ አገሮች በሰላማዊ ስደተኞች ላይ ይህን ዓይነት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እየወሰዱ ያሉት በወያኔ አገዛዝ
ግፊት ነው የሚል ግምት አለ። አገር ጥሎ ወደ ውጭ ለመውጣት
ከፍተኛ ችግር ያለ ቢሆንም ኑሮው አስመርሮት ወደ ውጭ የሚወጡት ኢትዮጵያውያን በጣም በርካታ መሆናቸው ይታወቃል። በሊቢያ በኩል
በአክራሪዎች መታረድና ውቅያኖስ ውስጥ ሰጥሞ መሞት እያለ፤ በአረብ አገሮች በኢትዮጵያውያን ሞትና ከፍተኛ የአካል ጉዳት
የሚያስከትሉ ወንጀሎች እየተፈጸሙ፤ እንዲሁም በደቡብ አፍርካ የአደባባይ ግድያ ወደ ዚያም ለመሄድ በመንገድ ላይ መያዝና እስራት
እያጋጠማቸው ስደተኞች አገራችውን አሁኑንም አገራቸው እየጣሉ መሰደዳቸው በወያኔ አረመናያዊ አገዛዝ ስር መኖር ምን ያህል አስከፊ
መሆኑን ያሳያል ሲሉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ።
Ø
በጎንደር ታች ጋይንት የተባለው ቦታ በድርቅ የተጠቃ ሲሆን በአካብቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ከድርቁ በተጨማሪ ተላላፊ በሆነ
ቆዳን በሚያሳክክ በሽታ ተጠቅተው እየተሰቃዩ መሆናቸውን
ከስፍራው የመጣ ዘገባ አስረድቷል። በሽታው በወረርሽኝ መልክ
የተከሰተ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት እስከ ትናንት ጥር 24 ቀን ድረስ ከሃያ ስድስት ሺህ በላይ ሰዎች
በህመሙ እየተሰቃዩ መሆኑን አካባቢውን የጤና ተቋማት ከተገኘ መረጃ ለመረዳት ተችሏል። የወያኔ አገዛዝ በሽታውን ለመቆጣጠር
የተለየ ትኩረት ባለመስጠቱ በሽታው ሊስፋፋ እንደቻለ የሚናገሩ ወገኖች በርካታ ናቸው።
Ø
ዛሬ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ሁለት ከፍተኛ ድምጽ ያላቸው ፈንጅዎች መፈንዳታቸው
ታውቋል። ቦምቦቹ የፈነዱት በከተማዋ የንግድ እና የቢዝነስ ቀበሌ አካባቢ ሲሆን ቢያንስ አራት ሰዎች የተጎዱ መሆናቸውን የሚግለጹ
ዘገባዎች ደርሰዋል። ቦምቡን ያፈነዳው ወገን ማን መሆኑና ለምን እንደፈነዳ ባይታወቅም ካለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ጀምሮ በብሩንዲ
ውስጥ በተጻራሪ ኃይሎች መካከል በተጀመረው የእርስ በርስ ግጭት በርካታ ሰዎች መገዳላቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ መሰደዳቸው
ይታወቃል።
Ø
ዛሬ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም አንድ የሱማሌ የሕዝብ ማመለላሻ አውሮፕላን ተጎድቶ በአንድ አካሉ ላይ ክፍተት (ቀዳዳ)
በመፈጠሩ በረራ ከጀመረ በኋላ በአስቸኳይ እንዲያርፍ ተደርጓል።
የዳሎ ኤር ላይንስ (Daallo Airlines) ንብረት የሆነው የመጓጓዣ አውሮፕላን 60 መንገደኞችን ጭኖ ይጓዝ የነበረው ወደ
ጅቡቲ ሲሆን ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለቱ ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተዘግቧል። በአውሮፕላኑ አካል ላይ ትልቅ ቀዳዳ
እንዲፈጠር ምክንያት የሆነው ምን እንደሆን ባይታወቅም አኮብኩቦ በረራ በጀመረ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ከአንድ አካባቢ እሳት የተያያዘ
መሆኑን በውስጡ የነበሩ ተሳፋሪዎች ተናግረዋል። ዳሎ አኤር ላይንስ መሰረቱ ዱባይ ሲሆን ወደ ጂቡቲና ወደ ሶማሊያ የጉዞ
አገልግሎት አለው።
በተመሳሳይ ዜና ዛሬ ጥር 25 ቀን 2008 ዓም በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ከተማ
አንድ ቀላል አውሮፕላን ከአየር ላይ ወድቆ በመሰባበሩ በውስጡ የነበሩ ሶስት ስዎች ወዲያውኑ የሞቱ መሆናቸውን በመግለጽ
የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አውሮፕላኑን የጣለው ምክንያት ምን
እንደሆን ለጊዜው ባይታወቅም የአውሮፕላን አደጋ በጣም
ዝቅተኛ ነች እየተባለ በሚነገርላት ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ይህ አደጋ መድረሱ ብዙዎችን አስገርሟል።
Ø
አንድ የግብጽ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀድም ብሎ ዝቅተኛው ፍርድ ቤት በ149 የእስልምና ወንድማማቾች አባላት ላይ ውስኖት
የነበረውን የሞት ፍርድ ገልብጦ ሌላ የፍርድ ሂደት እንዲካሄድ የወሰነ መሆኑ ታወቀ። ተከሳሾቹ የዛሬ ሶስት ዓመት በአንድ ፖሊስ
ጣቢያ ላይ ጥቃት በማካሄድ አስራ አንድ የፖሊስ መኮንኖችን ገድላችኋል ተብለው የተከሰሱ ናቸው። ነሐሴ 8 ቀን 2005 ዓም
በወቅቱ የፕሬዚዳንት ሞርሲን ከስልጣን መወገድና በግፍ መታሰር ተቃውሞ ሲያሰሙ በነበሩ የእስልምና ወንድማማቾች አባላት ላይ
የጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ወስደው በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች መግደላችው ይታወቃል። በዚያኑ ቀን ከዴሳና ማንያ በተባሉ ቦታዎች ላይ
በሚገኙ ሁለት የፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ተቃዋሚዎች ጥቃት አድርሰው 13 የፖሊስ አባላትን መግደላቸው ይታወሳል። ተከሳሾቹ የተከሰስቱ
የፖሊስ ጣቢያዎችን ለማጥቃት በተደረጉ እርምጃዎች ላይ ተሳትፋችኋል የሚል ነበር። ከፍተኛው ፍርድ ቀደም ብሎ በዝቅተኛ ፍርድ ቤት
የተሰጠውን ፍርድ ሽሮ በአዲስ መንገድ ይታይ ይበል መች እና በምን ዓይነት ሁኔታ ፍርዱ እንደገና እንደሚታይ አልተገለጸም።
Ø
በምዕራብ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያላገኘው ራሱን መንግስት ብሎ የሰየመው አካል የህግ አውጭ ምክር ቤት
በተመድ አማካይነት ሲካሄድ የነበረውን የእርቅ ስምምነት አለፈቃድና
ህገወጥ በሆነ መንገድ ፈርመዋል በሚል 10 የሚሆኑ የምክር
ቤት አባላቱን የአባረረ መሆኑ ተገልጿል። ባለፈው ታኃሳስ ወር በሞሮኮ በተደረገው የእርቅ ስብሰባ ላይ ያለፈቃደ የሥምምነት ፊርማ
በማስቀመጣቸው ከስራ ከተወገዱት አስር አባላት ውስጥ የምክር ቤት ምክትል መሪ እንደሚገኙበት ታውቋል።
ጥር 24 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ሰኞ
ጥር
23
ቀን 2008
ዓ.ም.
ከረፋዱ
አራት
ሰዓት
ላይ በቡታጅራ ከተማ
የወያኔ
ሹመኞች
አፍራሽ
ግብረ
ኃይል ይዘው ሁለት
የመኖሪያ
ቤቶችን
ለማፍራስ
ሙከራ ባደረጉበት ወቅት ሕዝቡ ድርጊቱን በመቃወም
በአንድነት
ወጥቶ
በኃይል
እንዳገዳቸው
ተረድተናል፡፡
ወዲያው
ከመቅጽበት
ከአምስት
ሺ
ሕዝብ
በላይ
የሚገመት ሕዝብ በቁጣ
ተምሞ
በመውጣት
ከተማዋን
አጥለቅልቋታል፡፡
የግለሰብ
ትራክተሮችንና መኪናዎን
በመሀል
መንገዱ
ላይ
በማቆም
መንዱን
ሙሉ
በሙሉ
የዘጉት
ሙሆኑንም
ከደረሰን
ዜና
መረዳት
ቸለኛል፡፡
የሕዝብ
ማመላለሻ
መነሀሪያ
ግቢ
ውስጥ
በመግባት
የተቆጣው
ሕዝብ
በዚያ
የሚገኙ
ቢሮዎችና
መለስተኛና
መካከለኛ
አውቶብሶች
ላይ
ጉዳት
ያደረሰ ሲሆን በርካታ ሕዝብ
“ሌባ፣
ሌባ
ወያኔ
ላባ!”
እያለ
መፈክር ያሰማ
እንደ
ነበር
ከሥፍራው
የደረሰን
መረጃ
ያስረዳል፡፡
ከከሰዓት
በኋላ
ጀምሮ
የከተመዋ
አራቱም
መግቢያና
መውጫ
በሮች
በሕዝቡ
ተዘግተዋል፡፡ተቃዉሞዉ
በተደረገበት ወቅት
ባንክ
ቤቶች፣ቤንዚን
ማደያዎች፣ሱቆች
ምግብ
ቤቶች
የተዘጉ
መሆናቸውና
ከሆሳእና፣ከአዲስ
አበባ
እና
ከዝዋይ
የሚያገናኘዉ
ዋና
መንገድ
ተዘግቶ
እንደነበርም
ለማወቅ
ተችሏል።ማምሻዉን
የወያኔ አግአዚ ጦር ከወልቅጤ
ከተማ
መጥቶ
ቡታጅራ
የሰፈረ መሆኑ ተዘግቧል።
Ø
በአዲስ አበባ አስተዳደር ውስጥ በሙስና እና በአስተዳድር ጉድለት ተጨማልቀዋል የተባሉ ከአንድ ሽህ
ስድስት መቶ በላይ የቀበሌና የወረዳ አመራሮች እና ሌሎች ሹማምንቶች ተነስተው በሌሎች የተተኩ መሆናችው የተገለጸ ሲሆን
በምትካቸው በትምህርት ወያም በአገልግሎት ጥራት ሳይሆን አፍቃሪ
ኢሃዴግነታቸው የተረጋገጠላቸው ግለስቦች የተመደቡ መሆናቸው ታውቋል። ስልጣን ሆነው ህዝብን ሲበድሉና ሲያስለቅሱ
የነበሩና ተከሰው ፍርዳቸውን ማግኘት የሚገባቸው ሹማምንቶችን ቦታ መቀየር ወይም ከስራ መደብ ዝቅ በማድረግ ችግሩ ለመሸፋፈን
የተደረገ መሆኑም ታውቋል። በተያያዘ ዜና በተግራይ በተመሳሳይ
መልኩ የይስሙላ የአስተዳደር እርማት እየተካሄደ ነው የተባለ ሲሆን 253 ግለሰቦች የሚሆኑ በአስተዳደር ጉድለት ክስ
ይመሰርትባቸዋል ተብሏል። ብዙዎቹ በ23 ዓመት ጊዜ በርካታ የሕዝብ ሀብት በመስረቅ የከፍተኛ ሕንጻዎች ባለቤቶች መሆናቸው
እየታወቀ የሚከሰሱት በሙስና ሳይሆን በአስተዳደር ጉድለት ብቻ መነገሩ የወያኔ ቁንጮ ባለስልጣኖች አገልጋዮቻቸውን ለመከላከል
የወሰዱት ርምጃ ነው በማለት ታዛቢዎች ይናገራሉ።
Ø
በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገግልጎትን በሙሉ ቁጥጥር ስር
ያደረገው ኢትዮ ቴሌኮም የተባለው መስርያ ቤት ሲሆን መስርያ ቤቱ በወያኔ መዳፍ ስር በመውደቁ ለሕዝብ የኢንተርኔት አገልግሎት
በመስጠት ደረጃ አገሪቱ ዝቅተኛ ከሆኑት አገሮች መካከል አንዷ ሆና ተመድባለች። በኬኒያ 69.6 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ
የኢንተርኔት ተጠቃሚ ሲሆን በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት የሚዳረሰው 3.7 ለሆነው ሕዝብ ብቻ መሆኑን ተገለጿል። በጣም
ዝቅተኛ የሆነ የመንግስት አገልግሎት የሚሰጥባት እና በጦርነት የተጠመደችው ደቡብ ሱዳን እንኳ ከሕዝቧ 15.9 የሚሆነው
የኢንተርኔት አገልግሎት የሚደርሰው መሆኑ ተዘግቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ
በኢሜል እና በሌላ መልክ ግንኙነት የሚያደርጉ ሰዎች ምን ያህል እንደሆኑ ባይታወቅም የወያኔ አገዛዝ ስፓይ ዌር
የተባሉትንና እና ሌሎች የመከታተያ መንገዶችን በመጠቀም ከፍተኛ
የስልላ ተግባሮችን የሚያከናውን መሆኑ ተዘግቧል። \
Ø
የአባይን ግድብ አስመልክቶ ጥናቶችን ለሚያካሂዱት ተቋሞች
የሚከፈለውን የአገልግሎት ገንዘብ ግብጽ ሱዳንና የወያኔ አገዛዝ በጋራ የሚሸፍኑት መሆኑን ለግብጽ
የውሃና የመስኖ ሚኒስትር ከቀረበው ዘገባ ማወቅ የተቻለ መሆኑን ካዮሮ ፖስት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ ጥር 23 ቀን
2008 ዓም ባወጣው እትሙ ገልጿል። ጥናቱ ተገባድዶ ስምምነት እስኪደረግ ድረስ በግድቡ ገንዳ ውስጥ ውሃ የመሙላቱ ተግባር
የሚዘገይ መሆኑም በተጨማሪ ተገልጿል። ጥናቱን
እንዲያካሄዱ ኃላፊነት የተሰጣቸው ቢ አር ዔል እና (BRL)
አረተሊያ (ARETELIA) የተባሉ የጥናት ተቋሞች ሲሆኑ በሶስቱ አገሮች ስም ከእነዚህ ተቋሞች ጋር ስምምነት የሚያደርገው የሕግ
አካል መቀመጫው እንግሊዝ አገር የሆነውና ኮርቤት እና ኩባንያው የሚባለው የሕግና የጥብቅና ተቋም ነው ተብሏል። ሁለቱ አጥኝ
ተቋሞች ከቴክኒክ አንጻር ጥናት ሊካሄድ የሚችላባቸውን መስኮች በመዘረዘር ያቀረቡት ረቂቅ ሀሳብ ለሶስቱም አገሮች የተላለፈ መሆኑ
ታውቋል። በቀረበው ሀሳብ በሁሉም በኩል ስምምነት ካለ ተቋሞቹ የሚጠይቁትን የክፍያ መጠን ለየአገሮቹ እንደሚተላለፍ ተገልጿል።
ተቋሞቹ ጥናቱን ከአንድ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አጠናቅቀው የሚያስረክቡ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን እስከዚያው ድረስ ግን
በግድቡ ገንዳ የመሉላቱ ተግባር እንደሚዘገይ ታውቋል።
Ø
በኢትዮጵያ የአንበሳ መንጋ ተገኘ። ቦርን ፍሪ ፋውንዴሽን
በሚባል የእርዳታ ስጭ ድርጅት በመታገዝ አንድ የኦክስፎርድ የእንሣት
ተንከባካቢ ቡድን ሰሞኑን በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ አልጣሽ በረሃ
በሚባለው አካባቢ በቁጥር እስከ 200 የሚደርሱ የአንበሳ መንጋ ቡድን ማግኘቱን በአካባቢው ካደረገው ጉዞ በኋላ
ባዘጋጀውና ትናንት ጥር 23 2008 ዓም ይፋ ባደረገው ዘገባ
ገልጿል። የአልጣሽ በረሃ የሚገኘው የጎንደርና የጎጃም ክፍለ ሀገርን በሚከፍለው የአይማ ወንዝ አካባቢ እና እስከ ሱዳን ግዛት
የሚዘልቅ ሲሆን አንበሶች በበረሃ ውስጥ መኖራቸው ቀደም
ብሎ በአካባቢው ነዋሪ እንደሚታወቅ ግልጽ ነው። ባለፉት 20 ዓመታት በአፍሪካ የሚገኘው የአንበሶች ቁጥር በ42 ከመቶ የቀነሰ
በመሆኑ በዚህ አካባቢ ከ200 በላይ የሚሆኑ አንበሶች በቡድኑ መገኘታቸው
ተስፋ የሚሰጥ ዜና ነው ተብሏል። አንበሶችን ለመታደግና ለመንከባከብ ከወያኔ አገዛዝ ከሱዳን ባለስልጣኖች ጋር በርካታ
ስራዎች መስረት እንደሚያስፈልግ ድርጅቱ አሳስቧል።
Ø
ባለፈው እሁድ ጥር 22 ቀን በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር
የተደረጉት የቀድሞ የኡጋንዳ የጸጥታ ኃላፊ ጄኔራል ሰጁሳ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው በወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸው
ተገለጸ። ጄኔራሉ የሙሰቪኒን ፖሊስ በመቃወም የሚታወቁ ሲሆን ከዋናው አዛዥ መመሪያ ውጭ በፖለቲካ ስብስባዎች ላይ ተገኝተዋል፤
ያለፈቃድ ከስራቸው ላይ ቀርተዋል፤ በፓርቲ ፖሊቲካ ውስጥ ተሳትፈዋል የሚሉ ክሶች ተሰንዝረውባቸዋል። ከሶስት አመት በፊት ጄኔራሉ
የሙሰቭን አገዛዝ በመቃወም ወደ እንግሊዝ አገር መሰደዳቸው የሚታወቅ ሲሆን ከ18 ወራት ቆይታ በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰው
ነበር።ከሰላሳ አመት በላይ በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚዳንት ሙሰቨኒ የሚወዳደሩበት ብሔራዊ ምርጫ
በሚቀጥለው ወር ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩን
ጨምሮ ሰባት ተወዳዳሪዎች በተቀዋሚነት ተሰልፈዋል። ጄኔራሉ ፕሬዚዳንቱን የሚቃወሙና ተቃዋሚዎችን የሚደግፉ ነበሩ።
Ø
የናይጄሪያ ጸረ ሙስና ተቋም አባላት የቀድሞ የናይጀሪያ
ምክትል ፕሬዚዳንት የሚስተር ናማዲ ሳምቦን ቤት ሰብረው በመግባት ፍተሻ ያካሄዱ መሆናቸው ታውቋል። የቀድሞ የአገሪቱ ምክትል
ፕሬዚዳንት በመሳሪያ ግዥ ሰበብ ከፍተኛ ጉቦ በልተዋል ተብለው የሚጠረጠሩ ሲሆን ቤታቸው በተበረበርት ወቅት አገር ውስጥ ያልነበሩ
መሆናቸው ተዘግቧል። በቀድሞ አስተዳደር ወቅት ከናይጄሪያ 2 ቢሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ መዘረፉ የታወቀ ሲሆን ባለፈው
ታኅሳስ ወር የቀድሞ የናይጄሪያ የጸጥታ አማካሪ 68 ሚሊዮን ዶላር በመዝረፍ መከሰሳቸው ይታወሳል። ሚስተር ናማዲ ስለጉዳዩ
እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።
ጥር 23 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
እሁድ
ጥር 23 ቀን 2008 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ዓም ከአፊሪካ ህብረት ስብሰባ ጎን ለጎን እየተካሄደ
በነበረው የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ አገሮች ተወካዮች ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባሰሙት ንግግር የዓለም አቀፉ ህብረተሰብ በችግር ጊዜ
ከኢትዮጵያ ጎን መቆም አለበት ካሉ በኋላ በአገሪቱ ውስጥ የገባውን ድርቅ ለመቋቋም እርዳታ ሰጭ አገሮች የሚሰጡትን የእርዳታ
መጠን ከፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። ዋና ጸሐፊው ንግግራቸውን በመቀጠል በአሁኑ ወቅት በጦርነትና በሌላም መልክ እርዳታ
የሚጠይቀው ሕዝብ ቁጥር ከፍተኛና ችግሩም ረጅም ጊዜ ሊቆይ
የሚችል መሆኑን ገልጸው በኢትዮጵያ የገባው ድርቅ በአሁኑ ወቅት ከባድ ቢሆንም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሊያልፍ እንደሚችል
ተናግረዋል። ችግሩ እስኪያልፍ ድረስ ግን የበርካታ ወገኖችን ህይወት ሊያጠፋ ስለሚችል አሁኑኑ በእርዳታው ላይ መረባረብ
ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚያኑ ዕለት ዋና ጸሐፊው ድርቅ ወደ አጠቃው ወደ ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ
ሄደው በዚያ የሚገኘውን የጤና ጣቢያ፤ የውሃ ጉድጓድና የእርዳታ ስርጭት ጣቢያን ጎብኝተዋል። ከጉብኝታቸው በኋላ
ባደረጉት ንግግር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአለም ባንክ ከአካባቢው ኃላፊዎች ጋር በመተባበር እያከናወኑ ያሉትን
ተግባር እንዲሁም ሕዝቡ ኑሮውን ለመቋቋም እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል። ችግሩ የሚያልፍ መሆኑን ጠቁመው
ድርቁን ለመቋቋም ተመድ የተቻለውን ያህል እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።
እስካሁን ድረስ ተመድ 25 ሚሊዮን ዶላር የሰጠ ቢሆንም ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። የአሜሪካ የዩስ
ኤድ ተወካይ በትናንትናው ዕለት አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ አሜሪካ 97 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ለመስጠት ቃል መግባቷን
አስታውቀዋል። ድርቁን ለመቋቋም የተገመተው ገንዘብ 1.4 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን እስካሁን የተሰጠው አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በዛምቢያ
መንግስት ታስረው የነበሩ 33 ኢትዮጵያውያን የአስራ አምስት አመት እስራትና እንዲቀጡና ከባድ ስራዎች እንዲሰሩ የተፈረደባችው
መሆኑን ዛምቢያ ታይምስ የተባለው ጋዜጣ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2008 ዓም ባወጣው እትሙ ገልጿል። ከኢትዮጵያውያኑ
ጋር አንድ የዛምቢያና አንድ የዚምባውየ ዘጎች
በህገ ወጥ መንገድ ሰዎችን ለማስተላለፍ አስተባባሪ ሆናችኋል በሚል ወንጀል ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ኢትዮጵያውያኑ ወደ ዛምቢያ
የገቡት ከህዳር 18 ቀን 2007 ዓም እስከ ህዳር 25 ቀን 2007 ዓም መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን ህገ ወጥ ዝውውርን የሚከለከለውን
ህግ በመተላለፍ እና ራሳቸው የዝውውሩ አካል ለማድረገ ፈቃደኛ መሆኑ በሚል ወንጀል ተከሰው ተፈርዶባቸዋል። ከ33 ቱ
ኢትዮጵያውያን መካከል ሁለት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ህጻናት እንደሚገኙበት ታውቋል። ለዜጎቹ ደህንነት ደንታ የሌለው የወያኔ
አገዛዝ አለአግባብ ፍርድ ለተፈረደባችው ኢትዮጵያውያን ድምጹን ያላሰማ ሲሆን ምናልባትም ዜጎቻችን በዚህ ዓይነት የግፍ ፍርድ
እንዲቀጡ ሳይገፋፋ አይቀርም የሚለው ግምት ከፍተኛ ነው።
Ø
በአቃቂ ክፍለ ከተማ ገላን በተባለ ቦታ 34 ሚሊዮን በላይ ብዛት ያላቸው የኮብል ስቶን ድንጋዮችን የአዲስ አበባ መንገዶች
ባለስልጣን ኃላፊዎች በገረጋንቲ መልክ በሚስጥር ሊሸጡ መሆናቸው ተደረሰበት። በገንዘብ ሲተመን
ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣል ተብሎ የሚገመተው
የከብልስቶን ድንጋይ ክምችት ደረጃውን ያልጠበቀ ነው በሚል
ከሁለት አመት በላይ ያለ አገልግሎት ተቀምጠው እነደነበር ታወቋል። ይህን አጋጣሚ በመጠቀም የመስሪያ ቤታቸው መዋቅር
ሳያውቅና ስውር በሆነ መንግድ ይህንኑ የተከማቸ ኮብልስቶን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሹማምንቶች
በገረጋንቲ መልክ ለኮንስትራክሽን ድርጅቶች አየር በአየር ሊሸጡ
መሆናቸውንና የታወቀ ሲሆን ከወዲሁ ገዥ በሚያመጡና ፊትለፊት ቆመው
በሚያስጭኑት መካከል የአንበሳው ድርሻ ይገባኛል በሚለው ላይ ንትርክ የያዙ መሆናቸውን ለማረገገጥ ተችሏል።
Ø
የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ትናንት እሁድ ጥር 22 2008 ዓም የተጠናቀቀ ሲሆን የቻዱ ፕሬዚዳን ኢድሪስ ዴቢ እና የሩዋንዳ
ፕሬዚዳንት ካጋሜ ለቀጣዩ ዘመን የአፍርካ ህብረት ፕሬዛዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ታውቋል። ለሁለት ቀን የቆየው
የመሪዎች ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተነጋገረ ሲሆን ከዚህ በፊት የአፍሪካ ህበረት 5000 የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትን
ወደ ብሩንዲ ለመላክ ያደረገውን ውሳኔ ሽሮ በምትኩ በተጻራሪ ወገኖች መካከል የእርቁ ውይይት የሚካሄድበትን ሁኔታ እንደሚያጠናክር
ወስኗል። የአፍሪካ አገሮች ከዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት እንደወጡ በኬኒያው ፕሬዚዳንት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በርከት ያሉት
የደገፉት ቢሆንም እያንዳንዱ አገር የመሰለውን ርምጃ ይውሰድ የሚል ስምምነት ደርሷል።
Ø
የደቡብ ሱዳን መንግስት ውታደሮች በቁጥጥር ስር የነበሩ ቁጥራቸው 50 የሚደርስ የደቡብ ሱዳን ዜጎችን በእቃ ማጓጓዥ በርሚል
ኮንቴነር ውስጥ በሙቀት አፍነው የገደሏቸው መሆኑን የተኩስ አቁም ስምምነቱን የሚታዘበውና የሚከታተለው ቡድን ለአፍሪካ ህበረት
ስብሰባ ባቀረበው ዘገባ አጋልጧል። የጋራ ክትትልና ግምገማ ኮሚሽን ተብሎ የተሰየመውና ከተለያዩ አገሮች የተውጣጣው ቡድን እሁድ
ጥር 22 ቀን 2008 ዓም ለአፍሪካ ህበረት ስብሰባ ባቀረበው ዘገባ ድርጊቱ የተፈጸመው ባለፈው ጥቅምት ወር መሆኑን ገልጾ
በመንግስት ወታደሮች የተወሰደ የበቀል እርምጃ ነው ብሏል። የደቡብ
ሱዳን ወታደሮች የብረት ኮንቴነሮች እንደእስር ቤት የሚጠቀሙበት መሆኑንና የአየሩ ሙቀት 40 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በሚደርስበት ሁኔታ
እስረኞች ከፍተኛ ስቃይ የሚደርስባቸው መሆኑ ተጠቁሟል። ዘገባው በመንግስት ወታደሮች የተፈጸሙትን የግድያ፤ አስገድዶ የመድፈር
እና የዝርፊያ ወንጀሎችን በዝርዝር አቅርቧል። ከደቡብ ሱዳን መንግስት ለዘገባው የተሰጠ መልስ ባይኖርም የመንግስቱ ቃል አቀባዮች
ቀደም ብሎ የቀረቡትን ተመሳሳይ ክሶች ሳይቀበሉ መቆየታቸው አይዘነጋም።
Ø
በአሁኑ ወቅት የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በዓለም ገባያ በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሱ ናይጀሪያ የ 11 ቢሊዮን ዶላር የበጀት እጥረት
የሚያጋጥማት መሆኑን ገልጻ ዓለም ባንክ ርዳታ እንዲያደርግላት የቅድሚያ ውይይት ለማካሄድ ማሰቧን ገልጻለች። የአለም ባንክ 2.5
ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጥ የተጠየቀ መሆኑን የድርጅቱ ባለስልጣኖች የገለጹ ሲሆን
ከአፍሪካ ልማት ባንክ ደግሞ አንድ ቢሊዮን ዶላር መጠየቁ ታውቋል።
በተያያዘ ዜና የናይጄሪያ መንግስት ከዚህ በፊት በጦርነት ላይ
ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ተከሰው በጡረታ ተገልለው የነበሩትን ሜጀር ጄኔራል አህማዱ ሙሐመድ እንደገና ወደ ስራቸው እንዲመለሱ
በማድረጉ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለውና ሌሎች የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸው ተዘግቧል። ከሁለት ዓመት
በፊት ለቦኮ ሃራም ጥቃት የአጸፋ መልስ ለመመልስ ጄኔራሉ 640 የሚሆኑ የታሰሩ ሰዎችን
ከአስር ቤት አውጥተው ያለፍርድ ገድለዋል የሚል ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታወሳል። ባለፈው ዓመት የተመረጡት
የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ጄኔራሉ በተከሰሱባችው ጉዳዮች ላይ ምርመራና ማጣራት
እንደሚደረግ ቃል የገቡ ቢሆንም ጄኔራሉ ወደ
ቀድሞ ስራቸው እንዲመለሱ ማድረጋቸው ብዙዎችን አስገርሟል።
ጥር 21 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ጥር 19 ቀን ማምሻውንና በነጋታው ጥር 20 ቀን 2008 ዓም
የወያኔ አግአዚ ጦር በወለጋ ዩኒቨርስቲ ቀን
በሴቶች መኖሪያ በመግባት ክፉኛ ድብደባ መፈጸሙን ከስፍራው የተገኘው መረጃ ገልጧል። በድብደባው በርካታ ተማሪዎች የተጎዱ ሲሆን ሌሎችም ከአደጋው ለማምለጥ ወደ
አካባቢው ጫካዎች መግባታቸው ተሰምቷል። አመጹ ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አልፎ ወደ ከተማው ሕዝብም የገባ መሆኑን አንዳንድ ዜናዎች
ይጠቁማሉ። በትናነትናው ዕለት በወለጋ የተለያዩ ቦታዎችና በሸዋ ኦቦቴ ተማሪዎች ተቃውሞ ሲያደርጉ የዋሉ መሆናቸው ከተለያዩ
ቦታዎች የተገኙት ተጨማሪ ዜናዎች ይጠቁማሉ።
Ø
ከጋምቤላ አካባቢ በተከታታይ
ከሚደርሱ ዜናዎች ማግኘት እንደተቻለው ካለፈው ሐሙስ
ጥር 19 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የዘለቀው የኑዌርና የአኝዋክ ጎሳዎች ግጭት የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈ
መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ግጭቱ ተጀመረ የተባለው የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት ቀደም ብሎ በነዌር ብሔረ ሰብ አባል ለተገደለው ዜጋ
የበቀል እርምጃ ሲወስዱ ነው ቢባልም ሆን ተብሎ በወያኔ የተጠነሰሰ ሴራ ነው የሚለው
ጥርጣሬ ሰፊ ነው። ሐሙስ ጥር 19 ቀን 2008 ዓም
የኑዌር ብሔረሰብ አባል የሆነውና
በጋምቤላ የገጠር መንገዶቸ ቢሮ
ምክትል ኃላፊ የነበረው ሰው
የተገደለ ሲሆን አርብ ጥር 20 ቀንም በአካባቢው ኮሌጅ
ውስጥ በተጣለ ቦምብ የኑዌር ብሔረሰብ አባላት መጎዳታቸው ታውቋል።
እስር ቤት ተሰብሮ ከሃያ በላይ የሚጠጉ እስረኞች የተገደሉ መሆናችውና በእርስ በርስ
ግጭቱ በርካታ ሰዎች መሞታቸው ከአካብቢው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
የኑዌር ብሔረሰብ አባላት ከወያኔ
የአግአዚ ጦር ጋር በመደባለቅ በወሰዱት እርምጃ መላው የአኝዋክ ብሔረሰብ አባላት የጋምቤላን ከተማ ለቀው መሰደዳቸው ተነግሯል።
ከሞቱት ሌላ በጥይት የቆሰሉና ህክምና
ያላገኙ ዜጎች በየመንገዱ ዳር ወድቀው መገኘታቸውን ዘገባው አመላክቷል። በጋምቤላ ሰፍሮ የሚገኘው የወያኔ አግአዚ ጦር
ከጥር 20 ቀን 2008 ዓ/ም እኩለ ቀን በኋላ ጀምሮ በከተማዋ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰማርቶ ቁጥጥር ማድረግ የጀመረ
ሲሆም ከዚያን ወቅት ጀምሮ ጋምቤላ በወያኔው የፌዴደራል ቁጥጥር ስር ወድቃ በቀጥታ ከአዲስ አበባ መመሪያ እየሰጠባት ትገኛለች።
ወያኔ የአኝዋክ ብሄረሰብ ነጥሎ ለመምታት ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት የጎሳ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ተንኮል ሲፈጥር የነበረ መሆኑ
የተዘገበ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ ይኽም ግጭት እንዲጀመር የወያኔ እጅ አለበት የሚሉ በርካታ ናቸው።
Ø
የአባይ ውሃ ተፋሰስን ሁኔታ እንዲያጠኑ ኃላፊነት ተሰጥቷቸው
የነበሩ ቢአር ኤል እና አረተሊያ(BRL and Artelia) የተባሉ
ሁለት የፈረንሳይ አጥኝ ተቋሞች ከቴክኒክ አንጻር ጥናታቸው ሊያካትት የሚችለውን ጉዳዮች አስመልክቶ ሁለት ሃሳቦች ያቀረቡ
መሆናቸውን የግብጽ የመስኖ ጉዳይ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሳን ሞጋዚ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ጨምረው እንዳስረዱት በጥናት ተቋሞቹ ከቀረቡት
ሀሳቦች መካከል አንደኛው ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳንና ግብጽ የሚፈሰው ውሃ ላይ ግድቡ ሊያደርስ ስለሚችለው ችግር ማጥናት መሆኑንና
ሁለተኛው በአጠቃላይ በአካባቢው የአየር ሁኔታ እና እጸዋት ላይ
ስለሚመለከተው ጥናት ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው የግብጹ
የቴክኒካል ኮሚቴ ጉዳይ በቅድሚያ ከተነጋገረበት በኋላ ለሶስቱ
አገሮች ኮሚቴዎች ቀርቦ ውይይት የሚደረግበት መሆኑን ተናግረዋል። ቀደም
ብሎ በተሰጠው መግለጫ መሰረት ጥናቱ በሚቀጥለው የካቲት ወር ተጀምሮ ለአስራ አንድ ወራት እንደሚቆይ መጠቀሱ ይታወሳል። ከዚህ
ጋር በማያያዝ በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሰደር የሆኑት አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ
እስካሁን ድረስ ህግ ተላልልፏል የሚል ሀሳብ ግብጽ የሌላት በመሆኑ
በወያኔ አገዛዝ ላይ ጥቃት ታነሳለች የሚለው ወሬ መሰረት ቢስ መሆኑን ገልጸው ግብጽ በአለም አቀፍ ደረጃ ጉዳዩን ለማቅረብና
ለመታገል ግን ሙሉ መብት አላት ብለዋል።
Ø
በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ዛሬ ቅዳሜ
ጥር 21 ቀን 2008 ዓም የጀመረ ሲሆን ህብረቱ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ስብሰባ ላይ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ስምምነት
ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ስብሰባው ከሚነጋግርባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሩንዲ ጉዳይ ሲሆን ከዚህ በፊት 5000
የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ ለመላክ ወስዶት የነበረውን አቋም ሊለውጥ እንደሚችል የሚጠቁሙ ጉዳዮች አሉ ተብሏል።
የህብረቱ የሰላምና የጸጥታ ካውንስል ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት የታንዛኒያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለጉዳዩ ከጋዜጠኖች በተነሳ
ጥያቄ ላይ መልስ ሲሰጡ አሁኑ ጉዳዩ ወደ ብሩንዲ ጦር መላክና አለመላክ ሳይሆን ተጻራሪ ኃይሎች ሊታረቁ የሚችሉበትን ሁኔታ
መፍጠር ነው ብለዋል። በሌላ በኩል በስብሰባው ለመገኘት አዲስ አበባ የተገኙት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ
ሙን በዛሬው ዕለት ባደረጉት ንግግር በብሩንዲ የሚካሄደው ግድያ መቆም ያለበት መሆኑን ጠቅሰው
ግድያውን ለማስቆም የሰላም አስከባሪ ኃይል መላክ ያስፈልጋል
ብለዋል። የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የህብረት አባሎችን ሁለት ሶስተኛ ድምጽ ማግኘት አስፈላጊ ሲሆን ይህ ድምጽ መገኘቱም
ሆነ አለመገኘቱ እንዲሁም ለሰላም አስከባሪው ኃይል
ወታደሮችን ለመላክ የትኞቹ አገሮች ፈቃደኞች እንደሚሆኑ አልታወቀም።
በተጨማሪም የአፍሪካ ህበረት ስብሰባ ይነጋግርበታል የተባለው የደቡብ ሱዳን ሁኔታን ሲሆን ተሰብሳቢዎች ምን ዓይነት
ቁርጥ አቋም እንደሚወስዱ አልታወቀም። የብሩንዲው ፕሬዚዳንት እንኩርንዚዛም ሆነ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በስበሰባው
አልተገኙም። በደቡብ ሱዳን፤ በብሩንዲ፤ በሳህል፤ በሊቢያ፤
በቻድ ባህር ወዘተ… አካባቢ ያለቱን የጸጥታ ሁኔታዎች
ስብሰባው ሊቃኝ የሚችል የተለያዩ ምንጮች የጠቆሙ ሲሆን በቅርቡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች የተነሱትን ሕዝባዊ አመጾች ለመቋቋም
በወያኔ አግአዚ ወታደሮች በግፍና የተገደሉትን ዜጎች ጉዳይ ግን ስብሰባው የሚያነሳው አይመስልም።
Ø
ሰሞኑን በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የተሰማሩ የሰላም
አስከባሪ ኃይሎች ህጻናትን አስገድደው ደፍረዋል የሚል አዲስ መረጃ መገኙትን የተመድ ኃይላፊዎች ሰሞኑን የገለጹ መሆናቸው
የሚታወቅ ሲሆን ይህንን ተከትሎ የፈረንሳይ መንግስት ከፍተኛ ምርመራ እንዲደረ መመሪያ መስጠቱን
አስታውቋል። ከዚህ በፊት ክስ የቀረረባቸው የፈረሳይ ወታደሮች ጉዳይ
ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን በቅርቡ የተሰነዘሩት ክሶችንም አስመልክቶ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።
በተመሳሳይ መንገድ የጆርጂያ መንግስትም ተመሳሳይ ምርመራ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
Ø
በሶርያ ዋና የተቃዋሚ ክፍል ነው የሚባለው ቡድን ቅዳሜ ጥር
21 ቀን በጄኔቫ ለመካሄድ ታቅዶ በነበረው ስበሰባ እንደማይገኝ ቀደም ብሎ ማስታወቁ የሚታወቅ ሲሆን ተወካዮቹ አርብ ዕለት
በሰጡት መግለጫ በሰብአዊ እርዳታ ሁኔታ ላይ የቀረቡት
ጥያቄዎች መመለስና አለመመለሳቸውን ለማረጋገጥ ወደ ጄኔቫ
የሚሄዱ መሆናቸው ገልጸዋል። አስራ ሰባት አባላት የሚገኙበትና በሳኡዲ አረቢያ የሚደገፈውና የሚረዳው ቡድን አባላት በዛሬው ዕለት
ጄነቫ እንደሚገቡ ይጠበቃል። የቡዱኑ መሪ ፋራህ አታሲ አርብ ጥር 20 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ስብሰባው ላይ
ለመገኘት ቡድኑ ቀደም ብሎ የሶሪያ መንግስት እያካሄደ ያለውን የአየር
ድብደባ እንዲያቆም፤ የስብአዊ እርዳታዎች ለሕዝብ እንዲደርሱ የሚሉት ቅድመ ሁኔታዎች አሁንም ያሉ መሆናቸውን ገልጸው
ወደ ጄኔቫ የሚሄዱት ለድርድር ሳይሆን ከተመድ
ባለስልጣኖች ጋር ስለሁኔታው ለመነጋገር ነው ብለዋል። በስብሰባው አካባቢ የሚገኙት የሩሲያ መልክተኛ
በአሁኑ ወቅት ቀጥታኛ ድርድር የማይደረግ መሆኑን እና ተጻራሪ
ኃይሎች የሚነጋገሩት በተዘዋዋሪ በሶስተኛ ወገን አማካይነት መሆኑን ገልጸው ለውይይቱ ምንም ዓይነት ቅደመ ሁኔታ አልተደረገም
ብለዋል።
ጥር 20 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት ጥር 19 ቀን 2008 ዓ/ም በደብረ ጽጌ ከተማ ሕዝባዊ
ቁጣ ተቀስቅሶ በተፈጠረው ግጭት ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ ሰላማዊ ዜጎች በወያኔ ፖሊስ ታፍሰው መወሰዳቸው ከስፍራው የመጣ ዘገባ
ገልጧል። ተማሪዎችና የከተማው ሕዝብ በከተማው የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ “ወገኖቻችንን
በግፍ የገደሉት ለፍርድ ይቅረቡ”፣ “የጅምላ እስራት ይቁም”፣
“ያለሃጢአታቸው የታሰሩ በአስቸኳይ ይፈቱ” የሚሉትን መፈክሮች ሲያሰሙ የነብረ ሲሆን
የወያኔ የአግአዚ ወታደሮች ሰልፉን ለመበተን የእሩምታ ተኩስ መክፈታቸውና
ቁጥራቸው ከሃምሳ በላይ የሚገግመት ሰልፈኞችን አፍነው
ወዳልታወቀ ስፍራ የወሰዷቸው መሆኑ ታውቋል። በተያያዘ መረጃ በምዕራብ ሀረርጌና በምስራቅ ሀረርጌ ሕዝባዊ ቁጣው
ተጋግሎ ከትናንት በስቲያ ረቡዕ እና ትናንት ሀሙስ የቀጠለ መሆኑን መረጃዎች እየደረሱ ሲሆን
እንደተለመደው የወያኔ የአግአዚ ወታደሮች በሰለማዊ
መንገድ ጥያቄዎች ያቀረቡ ወገኖችን ወዳልታወቀ ቦታ
መውሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል።
Ø
በናዝሬት እየተካሄደ ያለው የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ
በከፍተኛ ውዝግብ እና አለመግባባት ላይ መሆኑን ከስብሰባው አካባቢ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የስበሰባው ዋና አጀንዳ
የኦህዴድ ከፍተኛ ሹማምንቶችን መገምገም የነበረ ሲሆን
የድርጅቱ የጽህፈት ቤተ ኃላፊ ዳባ ደበሌ እና የክልሉ ፕሬዚዳንት ሙክታር ከድር ህዝባዊ ተቃውሞውን ለማስቆም ሲወሰድ በነበረው
እርምጃ ላይ የነቃ ተሳትፎ አላደረጉም በሚል ተወንጅለው እየተገመገሙ መሆናቸው የተገኘው ዜና ይገልጻል። አመጹን የቀሰቀሱትና
እርምጃም እንዲወሰድ ያደረጉት ራሳቸው የኦህዴድ ባለስልጣኖች ናቸው
በማለት ተጠያቂነቱን በኦህዴድ ላይ ለማላከክ የወያኔ
ባለስልጣኖች የኦሮሞ ተወላጆችን ለማሳመን ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ቀደም ብሎ የተዘገበ መሆኑ ይታወሳል። በስብሰባው ላይ ወያኔ
የኦህዴድን ባለስልጣኖች እርስ በርስ በማጋጨት ቀደም ሲል የጀመረውን ተንኮል በተግባር እያዋለ ነው የሚል አስተያየት እየተሰጠ
ነው። በአዳማ/ናዝሬት ቀንና ሌሊት እየተካሄደ በሚገኘው የአዲስ
አበባውን ማስተር ፕላን መሰረዝ አስመልክቶ ሙክታር ከድር በአመራር ብቃት ማነስና አቋምን በጽናት ተግባራዊ ለማድረግ አለመቻል
በሚል ግምገማ ተጠያቂና ጥፋተኛ ነኝ የሚል ግለሂስ እንዲያቀርብ የሚገደድ መሆንና ምናልባት ከኃላፊነት ሳይነሳ አይቀርም የሚለው
ግምት እየተሰራጨ ይገኛል። ከበስተጀርባ አባይ ጸሃዬን ጨምሮ
ከፍተኛ የወያኔ ባለስልጣኖች ግምገማውን እየተከታተሉት እንደሆኑ
የደህንነት ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
Ø
በጎንደር …. በደሴ
… በጎጃም …. በደቡብ ወሎና …. ሰሜን ወሎ ቀደም ብለው የነበራቸውን የትምህርት ደረጃ አሻሽለው ለደረጃ እድገት
ያመለከቱ መምህራን ጥያቄያችው ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከፍተኛ ምሬትና ብስጭት ውስጥ መሆናችው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የደሞዝ
ጭማሪ ለማግኘትና ህይወታቸውን ለማሻሻል በራሳቸው ወጪ ተምረው የትምህርት ደረጃቸውን ከሰርተፊኬት ወደ ዲፕሎም፤ ከዲፕሎም ወደ
ዲግሪ ለማሳደግ የቻሉ መምህራን የደረጃ መሻሻል እንዲደረግላቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም የበጀት እጥረት ስላለ የተሻሻለ የትምህርት
መረጃችሁን ተቀብለን ደረጃችሁን አናሳድግም የሚል መልስ የተሰጣቸው መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል።
Ø
ጥር 15 ቀን 2008 ዓም ምሽትና በማግስቱ ጥር 16 ቀን 2008
ዓ/ም በሬክተር ስሌት 4 ነጥብ 3 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሳ ከተማ ከደረሰ በኋላ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ተማሪዎች
በህክምና ሲረዱ ቆይተው ህይወታቸው ማለፉና ዩኒቨርስቲው ለተከታታይ አምስት ቀናት ትምህርት ያቆሙ መሆናቸውን ከስፍራው የመጣ
ዘገባ ገልጧል። የመሬት መንቀጥቀጡ በደረሰ የመጀመሪያው ቀን ከኤሌክትሪክ የተነሳ የእሳት አደጋ በዩኒቨርስቲው ግቢ ሲከሰት
ከቃጠሎው ራሷን ለማትረፍ ከሶስተኛ ፎቅ ላይ በመዝለል ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባት የነበረችውን ተማሪ ጨምሮ በቤተ መጻህፍት ውስጥ
ሳለ ጣራው ተንዶ በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት ደርሶበት የነበረው ተማሪ በህክምና ሲረዱ ቢሰነብቱም የሁለቱም ተማሪዎች ህይወት ማለፉን
ከአገኘነው ዘገባ ማወቅ ተችሏል። ትናንት ጥር 19 ቀን 2008 ዓ/ም አሁንም የመሬት መንቀጥቀጥ ድምጽ እየተሰማ ነው በማለት
በይፋ ትምህርት እንዲቆምና ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲሄዱ ጥያቄ ለማቅረብ ተሰባስበው በነበሩ ተማሪዎች ላይ ፖሊስ ጥይት መተኮሱና
ከተኩሱ ለማምለጥ በተፈጠረው ግፊያ በተማሪዎቹ ላይ መጠነኛ ጉዳት
ሳይደርስ እንዳልቀረ ታዛቢዎች ይናገራሉ።
በተያያዘ ዜና በህክምና ሲረዳ የነበረውና ህይወቱ ያለፈው
የአንደኛው ተማሪ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራው ጋምቤላ አሸኛኘት ለማድረግ ተማሪዎች እና መምህራን የትራንስፖርት ገንዘብ
ሲያሰባስቡ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው መግለጫ
በምዕራብ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ህጻናትን አስገደደው መድፈራቸውን የሚመለከት አዲስ ክስ
የቀረበባቸው መሆኑን ገለጹ። ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 16 የሚደርሱ ልጅ አገረዶች የአውሮፓ አገሮችን በመወከል በሰላም አስከባሪ
ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ የጂኦርጂያ ወታደሮች አስገድደው እንደደፈሯቸው ሰሞኑን የተመድ ባለስልጣኖች ባካሄዱት ምርመራ
ለማወቅ የቻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም የሰባት ዓመት ሴት ልጅና የዘጠኝ አመት ወንድ ልጅ በፈረንሳይ ወታደሮች
ተደፍረናል በማለት ክስ አቅርበዋል ተብሏል። የተባሉት ወንጀሎች የተፈጸሙት በ2006 ዓም ሲሆን በዋናዋ ከተማ በባንጉዊ
አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢው የሰፈሩትን ተፈናቃዮች በሚጠብቁ ወታደሮች ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ
ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አልሁሴን ዘገባውን አስመልክቶ በሰጡት
መግለጫ ሁኔታው ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ታኅሣሥ ወር አንድ ገለልተኛ የሆነ አጣሪ ቡድን የ ሰላም አስከባሪ አባላት
በመካከለኛው አፍሪካ ሪፕብሊክ ዜጎች ላይ ስለፈጸሙት ወንጀል ተመድ ምንም የወሰደው ርምጃ አለመኖሩን በመጥቀስ ወቀሳ
ማቅረቡ ይታወሳል።
Ø
አምነስቲ የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ዛሬ ጥር 20
ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ በብሩንዲ በመንግስት ወታደሮች ተገድለው በአንድ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ የተቀበሩበትን ቦታ
የሚያሳይ የሳተላይት ምስል ማረጋገጫ አግኝቻለሁ የሚል መግለጫ ሰጥቷል። ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ ከዚህ በፊት በመንግስት ወታደሮች
የተገደሉ ዜጎች ቡሪንጋ በሚባለው በዋናው ከተማ ዳርቻ በአምስት የተለያዩ ቦታዎች
በጅምላ ተቀብረዋል በማለት የአይን እማኞች የሰጡትን ምስክርነት
በታኅሣሥ ወር ለተከታታይ ቀናት በሳተላይት ከተነሱ ፎቶግራፎች የተገኘው መረጃ ያረጋግጣል ብለዋል።
በታኅሣስ ወር ውስጥ በመንግስት ወታደሮች ተገድለው በአንድ ጉድጓድ
ውስጥ የተጣሉት ሰዎች ቁጥር 87 ይደርሳል ተብሎ የተገመተ ሲሆን ከሳተላይቱ የፍቶግራፍ ምስል የተገኘው መረጃ ባለስልጣኖቹ
የወንጀሉ ሚስጥር እንዳይወጣ ለመደበቅ ያደረጉትን ጥረት ያጋልጣል ተብሏል። የብሩንዲ የውስጥ ችግር ከጀመረ ከአለፈው ዓመት
ሚያዚያ ወር ጀመሮ 439 ዜጎች መገደላቸውና ከ240 ሺ በላይ የሚሆኑት አገር ጥለው የተሰደዱ መሆናቸው ተዘግቧል።
በተያያዘ ዜና ብሩንዲ ውስጥ
አንድ የፈረንሳይ ዜጋ የሆነ የለሞንድ ጋዘጠኛና አንድ
እንግሊዛዊ ፎቶግራፍ አንሺ ለታጠቁ ወንጀለኞች ተባባሪ ሆናችኋል
በሚል ክስ ከሌሎች አስራ ሰባት የአገሪቱ ዜጎች ጋር የታሰሩ
መሆናችወን ዛሬ ጥር 20 ቀን 2008 ዓም የብሩንዲ ባለስልጣኖች ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።
የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዛሬው ቀን በሰጡት መግለጫ
የተያዙት ጋዜጠኞች ለረጅም ጊዜ ስለአገሪቱ ሁኔታ በገለልተኛነት
ሲዘግቡ የቆዩ መሆናቸውን ገልጸው ባስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።
ጥር 19 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአለም የምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ሚስተር አይሊየፍ
ትናንት ጥር 18 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋምና እስከ ሚያዚያ ወር
ድረስ ያሉትን የእርዳታ ፕሮግራሞች ለመሸፈን በሚቀጥለው
ወር ተሰብስቦ ማለቅ ያለበት የ500 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ባስቸኳይ የሚያስፈልግ መሆኑን ገልጸዋል። ዳይሬክተሩ ጥያቄው ለእርዳታ
ሰጭዎች ዱብ ዕዳ መሆኑን እንደሚገነዘቡ የገለጹ
ሲሆን እናት በምግብ እጥረት ምክንያት ልጆቿን ስታጣ ማየት ደግሞ የበለጠ ዱብ ዕዳ ነው በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት ሊያስረዱ
ሞክረዋል። በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት 1.4 ቢሊዮን ዶላር የሚያፈልግ መሆኑ በየገዜው ይገለጥ እንጅ በድርቁ ይጎዳሉ የተባሉ
ወገኖች ግምት ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ በመሄዱ ከተገመተው
የሚያስፈልገው የእርዳታ መጠን ከተገመተው በላይ ይሆናል የሚሉ
በርካታ ናችው። በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለተጎዱ ዜጎች ከፍተኛ እርዳታ በሚጠይቅበት ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና
ረሃብ የሚቸረው የእርዳታ መጠን በጊዜው ላይደርስ ይችላል የሚለው ስጋት ሰፊ መሆኑ ይነገራል።
Ø
በድርቁ ምክንያት በግድቦች የሚጠራቀመው ውሃ በማነሱ በጠቅላላው ከ500 ሚጋዋት
በላይ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ቀንሷል የሚለው ሰሞኑን ከወያኔ ባለስልጣኖች አካባቢ እየተሰራጨ ያለው ዜና አነጋጋሪ እየሆነ
መምጣቱን ዜጎች እየገለጹ ይገኛሉ። በተከዜ፣
በቆቃ፣
በፊንጫ
በአመርቲነሽና
በጊቤ የሚገኙት ግድቦች የውሃ
መጠናቸው የቀነሰ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ይህም የኤሌክትሪክ
አቅርቦቱን እንዲቀንስ አድርጎ ፋብሪካዎችን አንዳንድ የስራ
ቦታዎች በቀን ለስድስት ሰዓታት ብቻ ኢሌክትሪክ የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል ተብሏል። ሪፖርተር የተባለው ጋዜጣ በቅርቡ ከወያኔ
ባለስልጣኖች አገኘሁት ባለው ዜና መሰረት በርካታ የኤሌክትሪክ ኃይልን ማመንጨት ይችላል ተብሎ የተገመተውና በአካባቢው ሕዝብ ላይ
ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል ተብሎ የሚጠበቀው የግልግል ሶስት ስራ ለማፋጠን እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ገልጿል። የኢሌክትሪክ
አገልግሎት መቀነስ ለአመታት የተከሰተ መሆኑን ታዛቢዎች ገልጸው ድርቁ ለሽፋን የቀረበ ምክንያት እንጅ እውነተኛው ምክንያት
አይደለም በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። ወያኔ ከአራት
አመት በፊት ለጂቡቲ፤ ለሱዳን፤ ለኬኒያና ለሱማሌላንድ በከፍተኛ ደረጃ ኤሌክትሪክ ሲሸጥ መቆየቱና በአሁኑም ወቅት አጠናክሮና
አስፋፍቶ የቀጠለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን 400 ሚጋዋት የኤሌክትሪክ አገግልግሎት ለታንዛኒያ ለመሸጥ የሚያስችል ስምምነት ሁለቱ
አገሮች ስምምነት እንደሚፈራረሙ ስታር አፍሪካ የተባለው ተቋም
ረቡዕ ጥር 19 ቀን 2008 ዓም በድረገጹ ካሰፈረው ዘገባ ማወቅ ተችሏል። በአገሪቱ የኤሌክትሪክ አቀርቦት የቀንሰው በአንድ
በኩል ደረጃቸውን ያልጠበቁ ግድቦች በስራ ላይ በመዋላቸውና በመሳሪውያዎች ብልሸት ሲሆን በሌላ በኩል
የወያኔ ባለስልጣኖችን ኪስ ለማደለብ የኤሌክትሪኩ አቅርቦት ወደ ጎረቤት
አገሮች በገፍ በመሸጡ
መሆኑ ይታወቃል።
በተያያዘ ዜና
በሰሜን ጎነደር ደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች በመብራት እጦት ሁለት አመት ያለፋቸው
መሆኑና አሁንም ቢሆን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
በአንድ መንደር የሚኖሩ ከአንድ መቶ ሰላሳ በላይ አባወራዎች መብራት ለማግኘት ክፈሉ ተባሉትን አምስት መቶ ሃያ ሶስት
ሺህ አምስት መቶ አርባ አራት ብር ከከፈሉ በኋላ እጣ ይወጣላችኋል ጠብቁ የሚል መልስ ተሰጥቷቸው እየጠበቁ መሆናቸውን ከስፍራው
የመጣው ዜና ያስረዳል።
Ø
ከ2003 ዓ/ም እስከ ዓ/ም ድረስ
በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ምዝበራ ተካሄዶባቸውል ተብለው የሚጠረጠሩትን መስሪያ ቤቶች ለማጋለጥ የኦዲት ግኝት በሚል ስም አንድ
ጥናት እየተዘጋጀ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ጥናቱን የሚመራው የአዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በአዲስ
አበባ ያለጨረታ ግዢ የፈጸሙ፤ ያለደረሰኝ ሂሳብ ያወራረዱ፤ ዓመታዊ በጀታቸውን እንደፈለጉ ያባከኑ፤ ስለወጪያቸው ምንም መረጃ
የሌላቸው ተብለው ከተፈረጁት መካከል የአዲስ አበባ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፤ የህጻናትና ሴቶች ጉዳይ፤ የመንገዶች ባለስልጣን፤
ግንባር ቀደም መሆናቸውን የዋና ኦዲተር ጥናት አጋልጧል። ዋና
ኦዲተር አጠናሁት በጥናቱ መስሪያ ቤቶችን ያጋልጥ እንጂ የተጠቀሱት
መስርያ ቤቶች በወያኔ አባላት የሚመሩና ማንም ጠያቂ የሌላቸው መሆኑ የታወቀ
ስለሆነ የሚወሰድ እርምጃ አይኖርም በማለት ብዙዎች ይደመድማሉ።
Ø
የቀድሞ የአይቮሪ ኮስት ፕሬዚዳንት ሎረንት ጋብጎ ረቡዕ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም በኒዘርላን ሄግ በሚገኘው የዓለም
ፍርድ ቤት ላይ መቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን የተለያዩ ክሶች የቀረቡባቸው መሆኑ ታውቋል። በ2003 በአገሪቱ ተካሄዶ የነበረውን
አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ እሳቸውና የቀድሞ የሚሊሺያ መሪ ሚስተር ቻርልስ ጉዴ ግድያ በማካሄድ፤ ሴቶችን አስገድዶ በመድፈር፤
የግድያ ሙከራ በማድረግና ዜጎችን በአልሆነ መንገድ በማሰቃየት ክስ የቀረበባቸው ሲሆን ተከሳሹ በክሱ ላይ የተዘረዘሩትን ወንጀሎች
ያልፈጸሙ መሆናቸውን ክደዋል። ሚስተር ጋብጎ በ2003 ዓም በተደረገው ምርጫ በተወዳዳሪያቸው ተሸንፈዋል ቢባሉም ስልጣን
ለማስረከብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በተወዳዳሪው በሚስተር ኳታራና በእሳቸው ደጋፊዎች መካከል ለአምስት ወራት ያህል በዘለቁ ግጭቶች
የብዙ ሰዎች ህይወትን እንደጠፋና ብዙዎቹም አከለ ስንኩላን እንደሆኑ ይታወቃል። በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ የሚስተር ጋብጎ
ደጋፊዎች ከተሸነፉ በኋላ የቀድሞ ፕሬዚዳንት በቁጥጥር ስር ውለው
ወደ ሄግ ሊወሰዱ ችለዋል። ሂደቱ ከሶስት እስከ አራት
ዓመት ይወስዳል ተብሎ በተገመተው ክስ ሚስተር ጋብጎ ትክክለኛ ፍርድ ያገኛሉ የሚለው አጠራጣሪ ነው የሚሉ ብዙ ናቸው።
የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ዘረኛነትና አድሎ የበዛበት ነው የሚለው
ክስ በብዙ የአፍሪካ አገሮች የሚቀርብ ሲሆን ፍርድ ቤቱ በአፍሪካውያን ላይ ብቻ ያተኮረ እንጅ
በተለያዩ የአለም
ክፍሎች በተለይም በምዕራብ አገሮች የሚደረጉትን ወንጀል
ለማየት ያልደፈረና ያልቻለ ወገንተኛ አካል አድርገው ይመድቡታል።
Ø
ትናንት ረቡዕ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ በምትገኘው በቺቦክ ከተማ በርከት ያሉ አጥፍቶ ጠፊዎች
ባፈነዷቸው ቦምቦች 15 ሰላማዊ ሰዎችና አንድ ወታደር የተገደሉ መሆናቸውን እንዲሁም ቁጥራቸው ከፍ ያሉ ዜጎች የአካል ጉዳት
የደረሰባችው መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የአካል ጉዳት ከደረሰባችው መካከል የተወሰኑት በጽኑ የቆሰሉ ሲሆን
ለህይወታቸው አስጊ መሆኑን የሆስፒታል ምንጮች ጠቁመዋል። ቦኮ ሃራም ከሁለት ዓመት በፊት 300 የሚሆኑ የትምህርት ቤት ህጻናትን
ጠልፎ የወሰደው ከዚችው ከተማ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የረቡዕ ዕለቱን አደጋ ያደረሱት አጥፍቶ ጠፊዎች የቦኮ ሃራም አባላት
እንደሆኑ ተገምቷል።
Ø
በተያያዘ ዜና ዛሬ ሐሙስ ጥር 19 ቀን 2008 ኬራዋ በተባለችው የሰሜን ካሜሩን ግዛት ከተማ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች
ያፈነዱት ቦምብ አራት ሰዎችን የገደለ መሆኑ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ራስን ለመከላከል የተቋቋመው የአካባቢ ጥበቃ አካል አባላት
የሆኑ ግለሰቦች ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ በጾታቸው
ሴቶች የሆኑ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ከአንድ ትምህርት ቤት አጠገብ በሚገኝ መጠለያ ጣቢያ ላይ ጥቃቱን እንደፈጸሙ ተናገግረዋል።
አካባቢው በመስከረም ወር ተመሳሳይ ጥቃት ተፈጽሞበት ወደ 20 የሚጠጉ ሰዎች የሞቱ ሲሆን ባለፈው ሰኞ ዕለትም በሌላ ከተማ
በደረሰ ተመሳሳይ ጥቃት 37 ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል።
Ø
በግብጽ የሳይናይ ባህረሰላጤ ኤል አሪሽ
ከተማ የአሲስ ቅርንጫፍ ነኝ የሚለው አሸባሪ ቡድን በግብጽ
የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጥቃት ፈጽሞ አንድ ኮሎኔል እና ሶስት ወታደሮችን የገደለ መሆኑን ገልጿል። አሸባሪው ቡድን
የቀበረው ቦምብ ኢላማ ያደረገው ወታድሮቹ ይጓዙባቸው የነበሩባቸውን መኪናዎች ሲሆን በፍንዳታው ሌሎች 12 ወታድሮች መቁሰላችወ
ተጠቁሟል። አሸባሪው ቡድን ይህን ጥቃት የፈጸመው የሲሲ መንግስት
በሙርሲ ደጋፊዎች ላይ እየወሰደ ላለለው እርምጃ አጸፋውን ለመመለስ ጠቅሶ ተመሳሳይ ጥቃቶች እንደሚከተሉ አስጠንቋል። የግብጽ
መንግስት ባለስልጣኖች በመቶ የሚቆጠሩ የፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳይናይ ሰሜናዊ ክፍል በአሸባሪ ቡድኖቹ ጥቃት
የተገድሉባችውና የቆሰሉባቸው መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
ጥር 18 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአዲስ አበባ የተጀመረውን የአፍርካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባን ተከትሎ ለደህንነት ጥበቃ ሲባል የመኪና አከራይ ድርጅቶች
መኪናቸውን ለማን እንዳከራዩ የሚያበራራ የተሟላ መረጃ እንዲኖራቸው መመሪያ የተላለፈ ሲሆን መረጃቸውን ያላሟሉ አከራዮች ጥብቅ
እርምጃ የሚወሰድባቸው መሆኑ የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ሰሞኑን
የደህንነት ኃላፊዎች የመኪና አከራይ ድርጅቶችን ባለቤቶች
ጠርተው ኮድ ሁለት
የሆነ የግል ሰሌዳ የለጠፉ ተሽከርካሪዎች ብቻ
ለኪራይ እንደሚውሉ መመሪያ የሰጡ ሲሆን የመከና አከራዮች ባለቤቶችም መረጃዎቹን በማሟላት ፖሊስን ማገዝ እንደሚኖርባቸው
ተገልጾላቸዋል።
Ø
በደቡብ ክልል በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ችግር ፈጥረዋል፤ በሙስና ውስጥ ተዘፍቀዋል የተባሉትን ሹማምቶች ለመጠቆምና
ለማሰር እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን እስካሁን ድረስ እንቅስቃሴው ኢላማ ያደረገው የበታች ሹማንቶችን እንጅ የአገር ሃብትና
ንብረት የዘረፉትን እነ መኩሪያ ሃይሌን እንዳልነካና ውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቅሰዋል።
ከሚያገኘው ደሞዝ የማይመጣጠን ሃብት ያካበተው መኩሪያ ሃይሌ
በደቡብ ግሎባል ባንክ የሃያ አምስት በመቶ አክስዮን ድርሻ እንዳለው የሚያጋልጥ መረጃ ያለ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ወያኔ
ለማስመስልና ህዝቡን ለመደለል የመልካም አስተዳድር እያለ ይጩህ እንጅ አገልጋይ የሆኑትን ወንጀለኞች እንደማያጋልጥና እንዲያውም
ከፍተኛ ሹመት በመስጠት ወንጀላችውን ሲሸፍን የቆየ መሆኑ በተግባር የታየ ነው ተብሏል። በአገራችን በወያኔ ባለስልጣኖች
የሚካሄደው ሙስና ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መሄዱ በጉልህ እየታየ ሲሆን ሲሆን ሰሞኑን ይፋ የተደረገው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል
የተባለው ተቋም ዘገባ በዓለም ከፍተኛ ሙስና ከሚካሄድባቸው አገሮች መካከል ኢትዮጵያያን አንዷ አድርጎ እንደመደባት ታውቋል።
Ø
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የግል ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ለመውሰድ በካሬ ሜትር አራት ሺህ ብር የሚጠጋ ገንዘብ እንዲከፍሉ
ሊጠየቁ መሆናቸው ከውስጥ አዋቂዎች ከተገኘው መረጃ ማወቅ ተችሏል። በነዋሪነት ድርሻ ይዞታ የሚባለው ሰባ ሁለት ካሬ ሜትር ብቻ
ሲሆን በይዞታነት ተከልሎ የአፈር ግብር ሲከፈልበት የቆየ ድርሻቸውን ለማስከበር እና የግል ለማድረግ ቀሪው ስፍራ ተለክቶ
ለእያንዳንዱ ካሬ ሜትር ሶስት ሺህ ሰባት መቶ ስድሳ ብር እንዲከፍሉና በሊዝ እንዲያዛውሩ ለመጠየቅ የታቀደ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ
ቀደም የመሬት ባለቤት የሆነ ሰው የይዞታ ማረጋገጫ ለማግኘት የሚከፍለው
አምስት ሺህ ብር የነበረ ሲሆን አሰራሩን በመቀየር በካሬ ሜትር በሊዝ ድረጃ ተጨማሪ ገንዘብ በማስከፈል ወያኔ ከፍተኛ
ዝርፊያ ለማካሄድ ያቀደ መሆኑ ጉዳዩ የሚያውቁት ሰዎች ይናገራሉ።
Ø
የስፔን ባለስልጣኖች በአፍሪካ፤ በመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁ በሩቅ ምስራቅ ስደተኞችን በማመለስ ስራ ላይ ተሰማርተው
ከፍተኛ ሀብት የሚያካብቱትን ቡድኖች የግንኙነት መስመር የደረሰብት መሆኑን ገልጸው መረጃውን ለመሚለከታቸው አገሮች ያስተላለፉ
መሆናቸውን አስረድተዋል። ወደ አውሮፓ የተለያዩ ክፍልች ስደተኞችን ለማጓጓዝ ከሚጠቅሙባቸው መካከል የእንግሊዝ አውሮፕላን
ጣቢያዎች የሚገኙበት መሆኑም ተጠቁማውውል። አስተላላልፊዎቹ በአፍሪካ በሰሜን አሜሪካ በአውሮፓና በመከካለኛው ምስራቅ በከፍተኛ
ደረጃ ስራቸውን በማካሄድ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች ያስተላለፉ መሆናቸውንና እንዲሁም ብዙ ወጣት ሴቶችን ምርጫ በማሳጣት ሴትኛ
አዳሪ ለማድረግ ያስገደዷቸው መሆኑ ተረጋግጧል።
Ø
በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልኡክ የሆኑት ሚስተር ማርቲን ኮብለር ዛሬ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም ለጋዘጠኞች
በሰጡት መግለጫ ቀደም የአንድነት መንግስት ለመመስረት ስምምነት የተደረገባችው አንቀጾች ሊለወጡና ሊስተካከሉ እንደሚችሉ ገለጹ።
ከሁለት ቀናት በፊት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅናን ያገኘው ምክር ቤት በተመድ አደራዳሪነት የቀረበውን
የስምምነት ሰነድ ያልተቀበለው መሆኑ ይታወቃል። ምክር ቤቱ ሰነዱ ላይ የቀረበው የአንድነት መንግስት ካቤኔ
አባላት ቁጥር የበዛ መሆኑን ጠቅሶ የካቢኔው አባላት ቁጥር
እንዲቀነስ የጠየቀ ሲሆን በአንቀጹ ውስጥ የስፈረውንና የአገሪቷን
ከፍተኛ የጸጥታና ወታደራዊ ሹሞች የአንድነት መንግስቱ ይሾማል የሚለውን የስምምነት አንቀጽ ያልተቀበለው መሆኑ ይታወቃል።
ሚስተር ኮብለር ከዚህ ቀደም የስምምነቱን አንቀጾች መለወጥ ስምምነቱን ውድቅ ስለሚያደርገው አንቀበለውም ማለታቸው
የሚታወስ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ቀደም ብሎ የያዙትን አቋም መለወጣችው የምክር ቤቱ ውሳኔ ከፍተኛ ተጽእኖ በማሳደሩ ነው የሚል
ግምት ተወስዷል። የአውሮፓው ህብረት በሊቢያ ስምምነቱን ለማደናቀፍ እየተሯሯጡ ናቸው በሚሉት ግለስቦች ላይ ማዕቀብ ለመጣል
የተሰናዳ መሆኑን ገልጾ በአስር ቀናት ውስጥ ስምምነቱ ተግባራዊ ካልተደረገ ማዕቀቡ የሚጀመር መሆኑን ግልጽ አድርጓል። በሊቢያ
በአዲስ መልክ ስምምነት መኖሩና አለመኖሩ ወደፊት የሚታይ ሲሆን የስምምነቱ ተግባራዊነት እየተራዘመ ሲሄድ በአገሪቱ የሚገኙ
አክራሪና አሸባሪ ኃይሎች የሚጠናከሩበት ሁኔታ ይመቻቻል የሚሉ በርካታ ናቸው።
Ø
በሰሜን ካሜሩን በአጥፍቶ ጠፊዎች ለተወሰደው ጥቃት የአጸፋ መልስ ለማድረግ ባለፈው ሰኞ ማታ የካሜሩን ወታደሮች
የናይጄሪያ ወሰን ጥሰው በመግባት በወሰን አካባቢ የሚገኙ 40 የናይጀሪያ ዜጎችን የገደሉ መሆናችውን የአካባቢው ነዋሪዎች
ገልጸዋል። የካሜሩን ባለስልጣኖች ወታደራዊ እንቅስቃሴው የተደረገው በጋራው ኃይል ስር መሆኑን ገልጸው ወታደራዊ እንቅስቃሴው
የተደረገው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎችንና የጦርነት ደንቦችን በመከተል ነው በማለት በነዋሪዎቹ የቀረበውን ክስ
አስተባብለዋል። የናይጄሪያ ባለስልጣኖች ስለሆኔታው
እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።
Ø
በትናንትናው ዕለት በደቡብ ሶማሊያ የጦር ሰፈሩን ለቅቆ ከወጣው የኬኒያ ወታደራዊ ኃይል መካከል
በአንድ ማመለለሻ ላይ የተጫኑ ወታደሮች በተጠመደ ፈንጅ ተጠቅተው ቢያንስ አምስት ወታደሮች የሞቱ መሆናቸውን
የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ዛሬ ጥር 18 ቀን 2008 ዓም
አንድ የኬኒያ ከፍተኛ የፖሊስ አዛዥ የኬኒያ ወታድሮች በተጠመደ
ፈንጅ መገደላቸውን አምነው ምን ያህል እንደሞቱ ግን መርጃ
ሳይሰጡ የቀሩ ሲሆን አንድ ሌላ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ከፍተኛ የፖሊስ መኮንን አምስት ወታደራዊ መኮንኖች በቦምቡ ፍንዳታ
መሞታቸውን አረጋግጠዋል። በዛሬው ቀን ቀደም ብለው በአልሸባብ በተገደሉት የኬኒያ ወታደሮች የቀብር ስነስርዓት ላይ የኪኒያ
ፕሬዚዳንት አገሪቱን በመጎብኘት ላይ ካሉት የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ጋር የሚገኙ ሲሆን ፕሬዚዳንቱ ኬኒያ በአልሸባብ ላይ ተገቢውን
የአጸፋ እርምጃ ትወስዳለች ብለዋል። ኬኒያ በደቡብ ሶማሊያ ካሉት ጦር ሰፈሮች ወታደሮቿን ያስወጣችው ለወታደራዊ እንቅስቃሴ ነው
እንጅ ከሶማሊያ ጠቅልሎ ለመውጣት አይደለም የሚል መግልጫ መሰጠቷም ይታወሳል።
Ø
በሰሜን አፍሪካ የሚንቀሳቀሰው የአልካይዳ ቡድን ቲምበክቱ ከምትባለዋ የማሊ ከተማ ቢያትሪስ ስቶክሊ የተባሉ
አንዲት የስዊድን ተወላጅ ጠልፎ የወሰደ መሆኑን በድረ ገጹ ላይ
ባስተላለፈው ዜና ገልጿል። ራሱን የአልካይዳ የሳህራው ክንፍ በሚል ስም የሚጠራው ቡድን
ሴትየዋን ያገተ መሆኑን ገልጾ በማሊ የታሰረው መሪውና እንዲሁም በናይጀር የታሰረ ሌላ የድርጅቱ አባል ካልተፈቱ
ሴትየዋ የማይለቀቁ መሆናቸውን ግልጽ አድርጓል። የስዊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴትየዋ አለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የጠየቀ
ሲሆን ከማሊ መንግስትም ሆነ ከተጠላፊዋ ቤተሰቦች ጋር ግንኙነት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ባለፉት ሁለት ወራት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በተለያዩ ከተሞች በተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በወያኔ አግአዚ
ጦር የተገደሉ ዜጎች ቁጥር ከ 140 በላይ መሆኑ፤ በአንዳንዶች ግምትም እስከ ሁለት መቶ ደርሷል ተብሎ መነገሩ የሚታወስ ሲሆን
ከእነዚህ መካከል 17 የሚሆኑት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ መሆናቸውን የሚያረጋግጡ መረጃዎ አግኝቻለሁ በማለት ግሎባል ቮይስ
የተባለው ተቋም ትናንት ጥር 16 ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ከ17ቱ ህጻናት መካከል አብዛኞች ከ12 ዓመት እስከ 17 ዕድሜ ያላቸው
መሆናቸውን ተቋሙ ጠቁሞ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ህጽናትም የአካል ጉዳት እንደደረሰባችውና ታስረው እንደተወሰዱም አጋልጧል።
በኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚገኑኙ ከ60 ሺ በላይ ከሆኑ
የፖሊቲካ እስረኞች መካከል 20 ሺ የሚሆኑት ኦሮሚኛ ተናገሪዎች መሆናቸውን ገልጾ ወያኔ በዜጎች ላይ በተለይ በኦሮሚኛ ተናጋሪዎች
ዜጎች ላይ የሚፈጽመውን በደል አውግዟል።
በተያያዘ ዜና በዛሬው ዕለት በነቀምት ከተማ በወያኔ አገዛዝ ላይ የተቃውሞ እንቅስቃሴ
መደረጉ የተዘገበ ሲሆን የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ በዜጎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አልተቻለም።
በሀረርጌም ጭሮ ከተማ ተማሪዎች ትምህርት አቁመው የቆሰሉ ጓደኞቻቸውን ለማየት ወደ ሆስፒታል የሄዱ መሆናቸው ተዘግቧል።
ትናንት ጥቅምት 16 ቀን 2008 ዓም
በእስራዔልና በሲወዝርላንድ እንዲሁም በሌሎች ከተሞች የወያኔ አግአዚ ጦር
በኦሮሚኛ ተናጋሪ ወንድሞቻችንና በሌሎች ዜጎች
ላይ እየፈጸመ ያለውን ወንጀል በማውገዝ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል።
Ø
ከአገራቸው ተሰደው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ በታንዛንያ በኩል ሲያቆራርጡ የያዟቸውን በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ለወያኔ
አሳልፈው ለመስጠት የታንዛንያ ባለስልጣኖች የወሰኑ መሆናቸውን
አንድ የታንዛኒያ ጋዜጣ በዛሬው ዕለት አጋልጧል። የታንዛኒያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጡት መግለጫ በቁጥጥር ስር ያሉት
ኢትዮጵያውያንና የሌላ አገር ዜጎች ፍርድ ቤት የሚቀርቡ መሆናችውንና ከአገር
የሚያባረሩ መሆኑን ገልጸዋል። በተለያዩ ጊዜያት ወደ ደቡብ አፍሪካ በመጓዝ ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ታንዛንያ ውስጥ ተይዘው
የታሰሩ ሲሆን ባለፈው ወር ላይ 40 የሚሆኑ ተጥልለውባቸው ከነበሩት ቤቶች ተለቅመው የታሰሩ መሆናቸው ተዘግቧል። ለአስተላላፊዎች
ስደተኞቹ የሚከፍሉት ገንዘብ ከ አንድ ሺ እስከ ሁለት ሺ ዶላር የሚደርስ ሲሆን በጉዟቸውም ላይ ከፍተኛ ችግር እንደሚደርስባቸው
ታውቋል።
Ø
በፍቼ ከተማ ከዋና መንገድ ወደ ውስጥ የሚገቡና ሁለተኛ ደረጃ ተብለው የተመደቡ የከተማ መሬቶችን በሊዝ ለመሸጥ የወጣው ጨረታ
ዛሬ ጥር 17 ቀን 2008 ዓ/ም መጠናቀቁ ታውቋል። በካሬ ሜትር የተሸጠበት ዋጋና ምን ያህል ካሬ መሬት እንደተሸጠ ለጊዜው
ማጣራት ባይቻልም የገዙት ሰዎች የኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ዘመዶች መሆናቸውን የአይን እማኞችን ተናግረዋል።
Ø
በሶማሊያ በአፍሪካ ህብረት የስላም አስከባሪ ኃይል ስር በሁለት ከተሞች ውስጥ ተሰማርተው የነበሩ የኬኒያ ወታድሮች ከተሞችን
እየለቀቁ የወጡ መሆናቸው ታውቋል። ከሁለቱ ጦር ሰፈሮች መካከል አንደኛው ኤል አዴ በተባለውና ባለፈው ሳምንት አልሸባብ ጥቃት
አድርሶ 100 የኪኒያ ወታደሮች ገደልኩ ባለባት ከተማ የነበረው ጦር ሰፈር ሲሆን ሁለተኛዋ ባድሃዴ በተባለው ከተማ ውስጥ
የነበረው ጦር ሰፈር ነው። የኬኒያ ወታደሮች የባድሃዴን ከተማ ለቀው እንደወጡ በከተማዋ ዙሪያ የአልሸባብ ወታደሮች መታየታችውን
የአይን እማኞች ገልጸዋል። የኬኒያ ባለስልጣኖች በኤል አዴ ከተማ በተካሄደው የአልሸባብ ጥቃት
የፈነዳው ቦምብ ከ18 ዓመታት በፊት በናይሮቢ በአሜሪካ ኤምባሲ ላይ ከተጣለው የቦምብ ፍንዳታ ሶስት ጊዜ እጥፍ
የሚበልጥ መሆኑን ከመናገርና በፈንጅው የሞቱትን ሰዎች ዲ ኤን ኤ በመርመር ለማጣራት እየሞከሩ መሆናቸውን ከመግለጻቸው
በስተቀር ምን ያህል ወታደሮች እንደሞቱ እስካሁን የገለጹት ቁጥር
የለም። የአልሸባብ መግለጫ እውነት ከሆነ ድርጅቱ በአፍሪካ
ኅበረት ወታደሮች ላይ ካደረሳቸው ጉዳቶችን የጎላ ያለ ነው የሚሉ ወገኖች በርካታ ናችው።
የኬኒያ ባለስልጣኖች የተደረገው ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንጅ አንደኛውን ከጦር ሰፈሮች ጠቅልሎ ለመውጣት አይደለም የሚል
መግለጫ የሰጡ ሲሆን በኬኒያ ወታደሮች በተደጋጋሚ የደረሰባቸው ወከባ ያስመረራቸው መሆኑን የገለጹት
የኤል አዴ ነዋሪዎች ወታደሮቹ ጦር ሰፈራችውን
ጥለው መውጣታቸው ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸዋል።
Ø
በትናንትናው ዕለት ቦዶ በምትባል የሰሜን ካሜሩን ከተማ
በአንድ የገባያ ቦታ በፈነዱ ቦምቦች ቢያንስ 32 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውና 86 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ
ታወቀ። በገበያ ላይ አራት አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ ወጣት ሴቶች የያዝቱን ቦምብ አፈንድተው ከራሳቸው ጋር ገበያተኞችን የገደሉ ሲሆን
አጥፍቶ ጠፊዎቹ የቦኮ ሃራም አባሎች ናቸው የሚል ግምት ተወስዷል። አካባቢው በተደጋጋሚ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች
የጥቃት ሰለባ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባለፈው ወር በቦዶ ከተማ
ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች የያዙትን ቦምብ አፈንድተው ጉዳት ማድረሳችው ይታወሳል። ካሜሩን ቦኮሃራምን ለማዳከምና ለማጥፋት
ከናይጄሪያ፤ ከናይጀር፤ ከቤኒን እና ከቻድ ጋር የጋራ ኃይል በመመስረቷ በቦኮ ሃራም ተደጋጋሚ የአጸፋ ጥቃት ደርሶባታል።
Ø
በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘው የመንግስት ክፍል ፓርላማ ትናንት ጥር 16 ቀን 2008 ዓም ባደረገው ስብሰባ በተባበሩት መንግስታት
ድርጅት አስተባባሪነት አዲስ የአንድነት መንግስት ለመመስረት የቀረበውን ሀሳብ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ታውቋል። ከ104
ተሰባስባዎች መካከል 89 የሚሆኑት የአዲሱን የአንድነት መንግስት አመሰራረት በመቃወም ድምጽ የሰጡ ሲሆን የተሰጠው ምክንያት
የካቢኔ አባላቱ ቁጥር ከሚገባው በላይ ብዙ ነው የሚል ነው። አነስተኛ የካቢኔ ቁጥር ያለው መንግስት በአስር ቀን ውስጥ
እንዲቋቋም መመሪያ የሰጠ መሆኑን የምክር ቤቱ ቃል አቀባይ ገልጸዋል። ይመስረታል የተባለው አዲስ መንግስት ከፍተኛ የሆኑትን
የጸጥታ ተቋምና የወታደሩን ክፍልን መሪዎች ለመሾም ስልጣን አለው በሚል በስምምነቱ ረቂቅ ላይ የቀረበው የህግ አንቀጽ በምክር
ቤቱ አባላት ዘንድ ክርክር የከፈተ ሲሆን ምክር ቤቱ በዚህ ላይ
ዛሬ ማክሰኞ ጥር 17 ቀን 2007 ዓም ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህ አንቀጽ መሰረት በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ
ተወዳጅነትንና ተቀባይነት ያገኙት ጄኔራል ካሊፋ ሃፍታር ከስራቸው ላይ ሊነሱ ይችላሉ ከሚል ስጋት ስላደረባችው የምክር ቤት
አባላት ይህ አንቀጽ እንዲለውጥ ይጠይቃሉ የሚል ግምት ተፈጥሯል።
Ø
በተያያዘ ዜና የሊቢያ የነዳጅ ኩባንያ ኃላፊ ለንደን ውስጥ በሰጡት መግለጫ በሊቢያ ውስጥ ስምምነት ከጠፋ ሊቢያ ወደ ባሰ ቀውስ
የምትሄድ መሆኑንና ከነዳጅ የምታገኘውን ከፍተኛ ገቢ ልታጣ እንደምትችል አስታውቀዋል። ሊቢያ እስካሁን ከነዳጅ ዘይት ማግኘት
የነበረባትን 68 ሚሊዮን ዶላር ያጣች መሆኑን ገልጸው የአንድነት መንግስት ካልተቋቋመ ጸጥታ ሆነ መረጋጋት አይፈጠርም ብለዋል።
አክለውም አሸባሪና አክራሪ ኃይሎች ቀዳዳውን በመጠቀም ራሳቸውን ሊያደራጁና ከፍተኛ እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ በማለት ያላችውን
ስጋት ገልጸል።
ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተቀጣጠለው ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በተለያዩ ቦታዎች የቀጠለ ሲሆን ወያኔ እየወሰደ ያለውን አስከፊ እርምጃ በመቃወም አንዳንድ ክፍሎች
ድምጻቸውን እያሰሙ ነው ። ሰሞኑን በወለጋ ዩኒቨርስቲ የአግአዚ ወታደሮች በየተማሪዎቹ መኝታ ቤት ገብተው ባካሄዱት
ቢያንስ 15 ተማሪዎች የአካል ጉዳት ደርሶባችው ወደ ለቀምት ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናችው ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጽጥታው ምክር ቤት የልኡክ አባል በመሆን ወደ ብሩንዲ ሄደው የነበሩትና ስለብሩንዲ
ጉዳይ ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር ለመነጋገር አዲስ አበባ የተገኙት የአሜሪካው የተመድ ተወካይ ሳማንታ ፓወር በቲወተር
ባስተላለፉት መልክት ከወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከቴዎድሮስ አድሃኖም ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን ገልጸው በወያኔ
የተወሰደውን እርምጃ እንደማይደግፉና ችግሮችን በውይይት መፍታት እንዳለባችው የሚገልጹ መልእክቶች ማስተላለፋቸውን
ገልጸዋል።
Ø
በተያያዘ ዜና በወያኔና በኦህድዴ መካከል ያለው ውጥረት እየሰፋ
መሆኑን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱት ዘገባዎች ይጠቁማሉ። ስሞኑን ለወያኔ አባላት ብቻ የወረደው የውስጥ ማስታወሻ በተለያዩ
የኃላፊነት ቦታዎች ያሉ የወያኔ አባላት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያሳስብ መሆኑ ታውቋል። ማስታወሻው ሰሞኑን የጸጥታ
ሁኔታን ለመቋቋም የተወስደው እርምጃ በወያኔ ድርጅት ብቻ እንደተቀነባበረና እንደተካሄደ መሆኑን በመግለጽ በተለያዩ የፌዴራል
መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የኦህዴድ አባላት በወያኔ አባላት ርምጃ
ውሰዱ በማለት ወጣቶችን በመቀስቀስ ላይ ስለሆኑ ራሳችሁንና ድርጅታችሁን ጠብቁ የሚል መልእክት በመያዙ ከፍተኛ ውጥረት የፈጠረ
መሆኑን የተገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ።
Ø
ትናንት ምሽት በአዋሳ ከተማ አጠገብ የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰ መሆኑ ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል።
በደቂቃዎች ልዩነት ለሁለት ጊዜ ያህል የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ የንዝረቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ በትክክል ባይታወቅም
በሬክተር ስኬል እስከ 4 የሚደርስ ነው ተብሎ ተግምቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ በሰው ላይ የሕይወት አደጋ ባያደርስም አንዳንድ
ወገኖች በሁኔታ በመደናገጥ ከአደጋው ለማምለጥ ሲሮጡና ከፎቅ ላይ ሲዚሉ የአካል ጉዳት የደረሰባችውና ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ
መሆናቸው ተነግሯል። በአንዳንድ ህንጻዎች ላይ የመሰነጣጠቅ
ጉዳት ያደረስ ሲሆን ነዋሪዎች ድንኳን ዘርገተው ሌሊቱን ማሳለፋችው ታውቋል። በተለይ ሲገነቡ ጥራታቸውን ያልተበቁና አስተማማኝ
ያልሆኑ ፎቅ ቤቶች በመሬት መንቀጥቀጡ ሊፈርሱ ይችላሉ ከሚል ስጋት ብዙዎቹ ቤታቸውን እየተዉ አድረዋል።
Ø
እሁድ ጥር 15 ቀን 2008 ሌሊት ለሰኞ አጥቢያ በአዲስ አበባ የተለያዩ ስፍራዎችና አደባባዮች የተለያዩ
የቅስቀሳ ጹሁፎች በደማቅ ቀለሞች በትላልቁ ተጸፈው ያደሩ መሆናቸው ታውቋል። ተጽፈው ካደሩት መፈክሮች እና መልእክቶች መካከል
“ድምጻችን ይሰማ፤ “ግድያው ይቁም”፤ “በቃ”፤ “አምባገነናዊ ፍርድ አንቀበልም”፣ “ ብሔራዊ ጭቆና ይብቃ” የሚሉ ሲሆኑ
ለሃይማኖት መብት የሚታገሉት የሙስሊሙ ወገኖቻችን የድምጻችን ይሰማ አባላት መልእክቶች መሆናቸው
ግልጽ ነው። የወያኔን ጨቋኝና የአፈና አገዛዝ በመቃወም እየተደረጉ
ያሉ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች አገዛዙ ፋታ በመንሳት ላይ መሆናቸው እየታየ ነው።
Ø
የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ሰሞኑን አዲስ አበባ ላይ ለማካሄድ
የታቀደ ሲሆን ከመሪዎቹ ስብሰባ ቀደም ብሎ የሚካሄደው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በመቀሌ ከተማ እንዲካሄድ በመደረጉ ከተማዋ
በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ስር የወደቀች መሆኗ ታውቋል። በመቀሌ ከተማ የሚገኙ ከፍተኛ ሆቴሎች ማንም አዲስ እንግዳ እንዳያስተናግዱ
ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን አልጋ የሚያከራዩ ዝቅተኛ ሆቴሎችና ቡና ቤቶች ለፖሊስ ሳያሳውቁ ማንኛውንም ጸጉረ ልውጥ ሰው
እንዳያስተናግዱ ጥብቅ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ታውቋል።ከትግራይ
ፖሊስ በተጨማሪ የደህነነትና ልዩ ኃይል አባላት በተለያዩ የመቀሌ ከተማ መግቢያዎች ላይ ሲቪል ልብስ በመልበስ የነቃ ጥበቃ
እንዲያደርጉ ምደባ የተሰጣቸው ከመሆኑም በላይ የድርጅትና የፎረም አባላት በአንድ ለአምስትእድር ጃጀት ተጠቅመው ማንኛውንም መረጃ
ሪፖርት እንዲያደርጉ መመሪያ የተሰጠ መሆኑን ተያይዞ የደረሰን
መረጃ አስረድቷል።
Ø
በግብጽ በዛሬው ቀን አምስተኛ አመቱ የሚያከበረውና የአምባገነኑን የሙባረክን መንግስት ያስወገደው የግብጽ
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሌላ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እንዳይቀሰቅስ በመስጋት የግብጽ ወታደራዊ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ ጥበቃ
ማድረጉ ታውቋል። በአሁኑ የግብጹ ፕሬዚዳንት ሲሲ ላይ ተቃውሞ ለማሰማት ተዘጋጅተዋል ተብለው የተጠረጠሩ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች
መኖሪያ ቤቶች የተፈተሹና የተበረበሩ ሲሆን አድማ ያስነሳሉ ተብለው የተገመቱ በርካታ ግብጻውያን መታስራቸውንም ለማወቅ ተችሏል።
በዛሬውም ዕለትም በካይሮ ዋና ዋና መንገዶችና
ታህሪር በሚባለው አደባባይ ዙሪያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶችና
ወታደሮች የተሰማሩ ሲሆን ተቃውሞ ሊያሰሙ የሚችሉ ይሰባሰቡበታል የተባሉ ሻይ ቤቶችና ቡና ቤቶች እንዲዘጉ የተደረገ መሆኑና
በየፖሊስ ጣቢያዎች ጥበቃው የተጠናከረ መሆኑም የተገኙት መረጃዎች
ይጠቁማሉ። አምባገነን አገዛቸውን አጥብቀው የሚገኙት ሲሲ ስልጣን
ከያዙ ጀምሮ የሰብአዊ መብት ረገጣው በከፍተኛ ደረጃ መባባሱ የተገለጸ ሲሆን ስልጣን ላይ ባለው ቡድን ከ1000 ሰዎች በላይ
የተገደሉ መሆናቸውና ከ40 ሺ በላይ የሚገመቱ ሰዎች የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ጠባቂ የነበረውና በይፋ የፈረሰው ወታደራዊ ተቋም አባላት ናቸው የተባሉ
አምስት ወታደሮች በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸውን የቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለፈው አርብ ጥር 13 ቀን 2008
ዓም ንጋት ላይ በዋናዋ ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ከሚገኝ አንድ
የመሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ በመግባት የተወሰኑ መሳሪውያዎችንና የጸረ ታንክ ሮኬት መተኮሻዎችን የዘረፉትን ሰዎች ማደኑ ተጠናክሮ
ቀጥሏል። ቀድም ሲል ከተያዙት ጋር ተዳምሮ በአሁኑ ወቅት አስር ወታደሮችና አንድ ሲቪል በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በጋና ወስን
አካባቢ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሌላ የቀድሞ ወታደር ተገድሏል። መሳሪያው መዘረፉ የአገሪቱን የጸጥታ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ
ላይ ያደረሰ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የሚጠርጠሩ ሌላ ሰባት ወታደሮች እየተፈለጉ መሆናቸው ታውቋል። የቀደሞ
ፕሬዚዳንት ጠባቂ ወታደራዊ ተቋም 1300 የሚሆኑ አባላት የነበሩበት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ተቋሙን ይመሩ የነበሩት ጄኔራሎች
በዚህ ዓመት መስከረም ወር ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ካደረጉ በኋላ ተቋሙ በይፋ እንዲፈርስ የተደረገ መሆኑ ይታወሳል።
Ø
መቀመጫውን በምስራቅ ሊቢያ ያደረገውና ዓለም
አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው የሊቢያ ፓርላማ በቅርቡ በተባበሩት
መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት የቀረበውን የአንድነት መንግስት የስምምንት ረቂቅ ለማጸድቅም ሆነ ለመጣል ይሰብሰባል ዛሬ ጥር
16 ቀን 2008 ዓም ተብሎ ተጠብቋል። የምክር ቤቱ
አባላት ቁጥር 177 ሲሆን ስብሰባውን ለመጀመርም ሆነ ውሳኔውን ለማጸደቅ 89 አባላት መገኘታቸውን የሚጠይቀው ምልአተ ጉባዔ
መሟላት አለበት ተብሏል። በሊቢያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት ሁለት ተጻራሪ መንግስታት ያሉ ሲሆን አንደኛው በምዕራብ ሊቢያ ትሪፖሊ
ውስጥ መቀመጫውን ያደረገው በሚሊሺያዎች የተቋቋመው መንግስት ነው። በምስራቅ ሊቢያ በሚገኘው ምክር ቤት ውስጥ ስድሳ የሚሆኑ
የምክር ቤቱ አባላት የተመድን የእርቅ ሀሳብ የሚቃወሙ ሲሆን ረቂቅ የስምምነቱ ሀሳብ የአብዛኛውን ድምጽ ማግኘቱና አለማግኘቱ
እስካሁን አልታወቀም።
ጥር 14 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም ከተለያዩ ቦታዎች በወያኔ አግአዚ ጦር ተይዘው የታሰሩት ዜጎች
ቁጥር በአንዳንድ ወገኖች ግምት አምስት ሺ ይባል እንጅ ቁጥሩ ከዚያ በላይ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ቀደም ብሎ ከነበሩት ጋር
ተዳምሮ የእስረኞቹ ቁጥር በጣም በመብዛቱ የወያኔ ባለስልጣኖች የደርግ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በወረሳቸውና አሁን
የመንግስት ቤቶች ናቸው በሚባሉት ውስጥ እስረኞችን እያጎሩ መሆኑ
ታወቀ። በተለምዶ እንቁላል ፋብሪካ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ
በሚገኙ የተወረሱ ቤቶች፤ በአስኮ መንገድ ቀደም ሲል የወያኔ ባለስልጣናት ይኖሩበት በነበሩ ቤቶች ውስጥ እስረኞች
መታሰራቸው ታውቋል። በአበባ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ፤ አጠገቡ
ከሚገኘው ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ፤ ኮተቤ ደህንነት መስሪያ ቤት፤ ቦሌ
ወሎ ሰፈር በሚገኝ የደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ከቤተሰቦቻቸው ተሰውረው የታሰሩ እስረኞች ቁጥር ከፍተኛ
መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን ቀድም ብሎ ወደ መቀሌና ወደ ሌሎች ቦታዎች
ተወስደው የታሰሩ እስረኞች ቁጥርም እጅግ ብዙ እንደሆነ
ጉዳዩን የተከታተሉ ወገኖች ይናገራሉ።
Ø
በአገራችን በገባው ድርቅና ረሃብ ምክንያት የመኖሪያ ቀዬያቸውን እየለቀቁ ወደ አዲስ አበባ እየፈለሱ
የሚመጡ ዜጎች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሄዱ ታወቀ። ሰሞኑኑ ዘጋቢያችን በመርካቶ ራጉኤል ቤተክርስትያን
አካባቢ ያነጋገራቸው ወገኖች
ከትግራይና ከወሎ ቦረና የመጡ መሆናቸውን የገለጸሉት ሲሆ
የእርዳታ ስንዴ እንሰጣችኋለን ከሚል ተስፋ በስተቀር የተሰፈረልን
እህል ባለመኖሩ ልጆቻችን ሲሞቱ ከማየታችን በፊት በራችንን ዘግተን መምጣቱን መርጠናል ብለውታትል። በአሁኑ ወቅት በረሃብ
ምክንያት ከመኖሪያቸው ፈልሰው አዲስ አበባ የገቡት ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ እየታየ ሲሆን በእጃቸው ለሚጎትቷቸውና በጀርባቸው
ላዘሉዋቸው ሕጻናት የሚበላና የቀመስ ለማግኘት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ቤት በማንኳኳት እየለመኑ መሆናቸው ይታያል።
በተያያዘ ዜና ሕጻናትን አድን (Save
the Childeren) የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ አለም አቀፍ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሚስስ ካሎሪን ማይልስ
(Carolyn Miles) በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የድርቁን አካባቢዎች የጎበኙ መሆናቸውን ገልጸው በአሁኑ ወቅት በምግብ
እጥረት 10.2 ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚሰቃይ አስረድተዋል። የችግሩ መጠን በጣም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው የወያኔ አገዛዝ ችግሩን
ሊቋቋመው እንደማይችል ተናግረዋል። ለሚቀጥሉት 18 ወራት በኢትዮጵያ በድርቁ እየተሰቃዩ ላሉት
ሕጻናት መርጃ ድርጅታችው
144 ሚሊዮን ዶላር የተመነ ቢሆንም እስካሁን ድረስ የተገኘው ከ30 ሚሊዮን ዶላር ያልዘለለ መሆኑን አስረድተዋል። በረሃብ
ከተጠቁት ዜጎች መካከል 5.8 ሚሊዮን የሚሆኑት ሕጻናት መሆናቸውንም ሚስስ ማይልስ ተናግረዋል። ቀደም ብሎ የተባበሩት መንግስታት
የአለም የምግብ ድርጅት በእርዳታ አሰባሰብ በኩል ተመሳሳይ ችግር ያለበት መሆኑን መግለጹና ከሚያስፈልገው 685 ሚሊዮን ዶላር
ውስጥ ያገኘው 86 ሚሊዮን ዶላር ብቻ መሆኑ መናገሩ ይታወሳል።
በደቡብ ሱዳን ከሁለቱም ተጻራሪ ወገኖች በተውጣጡ ወኪሎች እንዲመሰረት ስምምነት ተደርሶበት የነበረው
ጊዜያዊ የአንድነት መንግስት በተግባር እንዲውል የተሰጠውን ቀነ ቀጠሮ ያሳለፈ መሆኑ ተገለጸ። የአንድነት መንግስቱ እንዳይመሰረት
እንቅፋት ከሆኑት አቢይ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የስልቫኬር መንግስት ከስምምነት ውጭ የአካባቢ አስተዳደሮችን ከ10 ወደ 28 ከፍ
ማደረጉንና 28 አስተዳዳሪዎች መሾሙን በሪክ ማቻር
የሚመራው የአማጽያን ኃይል በመቃወሙና ባለመቀበሉ መሆኑ ታውቋል።
በዕቅዱ መሰረት ከሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች የተውጣጣ የአንድነት መንግስት ከጥር 13 ቀን 2008 ዓም በፊት መመስረት ነበረበት።
ለስምምነቱ መፍረስ ሁለቱም ወገኖች እርስ በርሳቸው የተወነጃጀሉ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ
ሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች ጦርነቱን በማስፋፋት እንዲሁም በጦር
ሜዳዎች የጅምላ ርሸና በማካሄድ፤ የያዟቸውን ዜጎች ዱካ በማጥፋት፤ በቡድን ሴቶችን በመድፈር፤ ለወሲብ አገልግሎት ሴቶች አግቶ
በመያዝ ፤ አስገድዶ ጽንስን በማስወረድና የመሳሰሉ ወንጀሎችን
በመፈጸም በኩል ሁለቱም ወገኖች ተጠያቂዎች ናቸው ብሏል።
Ø
የቱኒዚያ ፕሬዚዳንት በአገሪቱ የተቀጣጠለውን ሕዝባው አመጽ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እየተባባሰ የመጣው
ስራ አጥነት ዜጎችን ማስቆጣቱ የሚጠበቅ መሆኑን ጠቅሰው መንግስታቸው ስራ አጥነትን ለመቀነስ የተቻለውን ጥረት እንደሚያደርግ ቃል
ገብተዋል። ትናንት አርብ ጥር 13 ቀን በራዲዮና በቴለቪዥን ባስተላለፉት መልእክት በስራ አጥነት ምክንያት የሚበላውን ያጣውንና
ኑሮውን መግፋት ያልቻለውን ሰው ትእግስት አድርግ ማለት አይቻልም ካሉ በኋላ እንደ አይሲስ ዓይነቱ አክራሪና አሸባሪ ቡድኖች
ሁኔታውን ተጠቅመው ትርምስ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ መንግስት 6000 ስዎች ባስቸኳይ ስራ
የሚያገኙበት ሁኔታ ያመቻቸ መሆኑን ገልጸው ስራ በመስጠት በኩል ያለውን የሙስና አስራር እንደሚመርምሩ ተናግረዋል። በተቃውሞ ስም
የሕዝብና የግል ንብረቶች በመውደማቸው ሰዓት እላፊ አዋጅ በዋና ከተማዋ የታወጀ መሆኑን የአገር ግዛት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የፈረንሳይ መንግስት በሚቀጥሉት አምስት አመታት 1.1 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ለቱኒዚያ ለመስጠት ቃል የገባ መሆኑም ተዘግቧል።
Ø
ሰሞኑን የብሩንዲን ባለስልጣኖች ሲያነጋግሩ የሰነበቱት የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ልኡካን
በአዲስ አበባ ተገኝተው ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር መነጋገራቸው ታውቋል። የቡርንዲ ባለስልጣኖች
ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ውይይትና ድርድር እንዲያደርጉ የሚለውንና የአፍሪካ ኅበረት የሰለም አስከባሪ ኃይል በብሩንዲ
ተገኝቶ ሰላም እንዲያስከብር የሚሉትን ሀሳቦች በጥብቅ የሚቃወሙ መሆናቸውን የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ለተመድ ሉኡክን በስብሰባ ላይ
ገልጸዋል። የልኡኩ አባል የሆኑት የአሜሪካው የጸጥታው ምክር ቤት ተወካይ የተመዱ የልኡክ ቡድን በብሩንዲ ለማከናወን
ያቀደው ተግባር ፍሬ ያልሰጠ መሆኑን ጠቅሰው በአገሪቱ
ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግድያ ለማስቆም የውጭ እርዳታ የሚጠይቁ
ወገኖች በርካታ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቀድሞ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ጃን ባፕቲስት ባጋዛ እና ሌሎች የቀድሞ የብሩንዲ
ባለስልጣኖች ተመድ በአገሪቱ ውስጣ አሉ የተባሉ የጅምላ መቃብሮችን እንዲያጣራና ግድያውን ለማስቆም ጥረት እንዲያደረግ ጥያቄ
ያቀረበ መሆኑ ተነግሯል። የተመድ የልኡካን ቡድን በአዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣኖች ጋር ምን እንደመከረ ባይገለጽም
በብሩንዲ ላይ ጠንከር ያሉ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ስምምነት ያለ መሆኑ ይታወቃል።
ጥር 13 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት ጥር 12 ቀን 2008 ዓ/ም በአዲስ አበባ ተከብሮ በዋለው የቃና ዘገለሊላ በዓል ላይ የበዓሉ
ታዳሚ በነበሩት ምዕመናንና በፖሊስ መካከል ግጭት ተነስቶ ለግዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በአካላቸው ላይ ጉዳት
እንደደረሰባቸውና በፖሊስ ታፍነው እንደተወሰዱ ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አስረድቷል። በተለምዶ ሾላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ
የሚገኘውን የየካ ቅዱስ ሚካኤል ታቦትን በማጀብ ወደ መንበሩ ለማስገባት ተሰባስበው የነበሩ ምዕመናን ባህላዊ ዘፈኖችና ጭፈራዎች
እያደረጉ በሚጓዙበት ወቅት ለጭፈራ ማድመቂያ የያዙትን
ዱላ በተለያዩ ስፍራዎች ቆሞ ይጠብቅ የነበረው የወያኔ የፖሊስ ኃይል ለመንጠቅ ሞከራ ሲያደረግ ከፍተኛ ግብግብ መከሰቱ
ታውቋል። ዱላቸውን የተቀሙት ወጣቶች እንደጀመራችሁ ጨርሱን በማለት
ፖሊሶችን ማጥቃት ስለጀመሩ በተነሳው ግጭት በርካታዎች የመፈንከት አደጋ የደረሰባቸው መሆኑና አንዳንዶቹ ከአደጋው ለማምለጥ ሲሮጡ
የእግር ወለምታ አጋጥሟቸው ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ከስፍራው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ብዙዎች ታስረው በመኪና ተጭነው ወደ
አልታወቀ ቦታ የተወሰዱ ሲሆን ከፖሊስ አባላት መካከልም ጉዳት የደረሰባችው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
Ø
ከዚህ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም መነሻ አድርጎ በተለያዩ ቦታዎች ተቀጣጥሎ
የነበረው ሕዝባዊ አመጽ አሁንም ያልበረደ መሆኑ ይነገራል። በምስራቅ ወለጋ በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞዎች የነበሩ ሲሆን እንዲሁም
በአሩሲ ዪኒቨርስቲ ሁለት ተማሪዎች መታጠቢያ ቤታቸው ውስጥ
በስለት ተወግተው ጉዳት እንደደረሰባችው ተዘግቧል። በተማሪዎቹ ላይ ጉዳት ያደረሱት እነማን መሆናቸው ለጊዜው ባይታወቅም የወያኔ
ሰላዩች ሳይሆኑ አይቀሩም የሚል ጥርጣሬ አለ።
Ø
በጋምቤላ በአኙዋክና በነዌር ብሐረሰብ መካከል ግጭት ተቀስቅሶ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ መሆኑ እየተነገረ
ነው። በግጭቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባችው በሆስፒታል እየታከሙ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ወደ ዋና ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት
የተቋረጠ መሆኑም ተዘግቧል። የወያኔ ባለስልጣኖች በከተማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ተጨማሪ የጸጥታ ኃይሎች በማሰማራት
ፍተሻ እያካሂዱ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
በቱኒዚያ ያለው ስራ አጥነት ጣራ በመንካቱ ምክንያት ሌላ የአመጽ እንቅስቃሴ የተቀሰቀሰ መሆኑ ተነገረ።
በቱኒዚያ ሰሜናው ግዛት ባለፈው ሳምንት አንድ ወጣት ለመንግስት ስራ ያቀረበው ማመልከቻ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከኤሌክትሪክ
ማስራጫ ምሰሶ ላይ ወጥቶ በኤሌክትሪክ ራሱን መግደሉን ተከትሎ የተጀመረው የተቃውሞ ስልፍ ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም
በቱኒዚያ የተለያዩ ከተሞች ተቀጣጥሎ የቀለጠለ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ፌሪያና በተባለችው ከተማ የተቃውሞ ስልፈኞቹ አንድ
የፖሊስ መኪና አነቃንቀው በመገልበጣቸው በውስጧ የነበረው አንድ ፖሊስ ህይወቱ ያለፈ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። የዛሬ አምስት
ዓመት ሞሃመድ ቦአዚዝ የተባለው ጎልማሳ ራሱን ማቃጠሉን ተከትሎ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ በወቅቱ የነበረውን የቢን አሊን
አገዛዝ ያስወገደ ቢሆንም ባለፉት አምስት አመታት የስራ አጡ ቁጥር እየጨመረ እንጅ እየቀነሰ አለመሄዱ ታውቋል። ባሁኑ ወቅት
ከተላለዩ የትምህርት ተቋሞች ተመርቀው ከሚወጡ ምሩቃን መካከል 62 ከመቶ የሚሆኑት ስራ የሌላቸው መሆኑ የሚታወቅ
ሲሆን ባለፉት አምስት አመታት ሌሎች የኢኮኖሚና የሶሻል ሁኔታዎች ያልተሻሻሉ መሆናቸውም ይነገራል። በትናንትናው የተቃውሞ ሰልፍ
ጉየበሊ በምትባለዋ ከተማ አንድ የፖሊስ ጣቢያ የተቃጠለ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ከ40 በላይ
የሚሆኑ ሰዎችና 59 ፖሊሶች ጉዳት የደረሰባችው መሆኑ ተዘግቧል።
Ø
በትናንትናው ምሽት በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ ታጣቂዎች በአንድ የምግብ ቤት ውስጥ ባካሄዱት ተኩስ
20 የሚሆኑ ሰዎችን የገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ታጣቂዎቹ ወደ ምግብ ቤቱ የገቡት በአካባቢው
በመኪና ላይ የተጠመዱ ሁለት ፈንጅዎችን ባፈነዱበት ወቅት ሲሆን
የምግብ ቤቱን አካባቢ ለሰዓታት ያህል ተቆጣጥረው እንደነበር ተዘግቧል። የሶማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር የተኩስ ልውውጥ
በማድረግ አካባቢውን የተቆጣጠሩ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባለስልጣኖች የታጣቂዎቹ መሪ በቁጥጥር ስር ተደርጓል የሚል መግለጫ
ሰጥተዋል። አልሸባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል።
Ø
በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት አርብ አልሸባብ በደቡብ ሱማሊያ በኬኒያ የሰለም አስከባሪ ኃይል አባላት
ላይ ጥቃት ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን ይህ ጥቃት ከመድረሱ ከ45 ቀናት በፊት ጥቃት በአካባቢው ጥቃት ሊሰነዘር እንደሚችል በመግለጽ
ለኪኒያ ወታደሮች ማስጠንቀቂያ የተሰጣችውም መሆኑን በጌዶ አካባቢ የሶማሊያ መንግስት መከላከያ ኃይል መሪ ጄኔራል ጉሬ ለዜና
ምንጮች ገልጸዋል። አልሸባብ ያሉትን በርካታ አባላት
ከሁሉም አካባቢዎች ወደ ጌዶ ግዛት እንደሚያመጣና
የሚመጡትም ጠንካራ ተዋጊዎች እንደሆኑ የሚገልጽ መረጃ አግኝተን ይህንን ለኬኒያውያን ወንድሞቻችን አስተላልፈናል ብለዋል።
አልሸባብ 100 የኬኒያ ወታደሮች ገድያለሁ ያለ ሲሆን የኬኒያ ባለስልጣኖች ምንም እንኳ በሶማሊያ ውስጥ የኬኒያ ወታደራዊ ተልእኮ
ይቀጥላል የሚል መግለጫ ቢሰጡም ምን ያህል ወታደሮች
እንደተገደሉባችው እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።
Ø
በካይሮ ፖሊሶች አሸባሪዎች ተደብቀውበታል ብለው የሚጠርጥሩትን በአንድ ሕንጻ ውስጥ የሚገኝ የመኖሪያ
ክፍልን ለመፈተሽ ጥረት እያደረጉ እያሉ አንድ ቦምብ ፈንድቶ ስድስት
ፖሊሶችንና ሶስት ሰላማዊ ሰዎች የገደለ መሆኑንና የፖሊስ ኃላፊውን ጨሞር ሌሎች 13 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ
ከቦታው የተገኘው ዜና ይገልጻል። የግብጽ መንግስት ባለስልጣኖች
አደጋውን ያደረሱት የእስላም ወንድድማቾች ድርጅት አባሎች መሆናቸውን ገልጸዋል። አደጋው የደረሰው የፒራሚድስ ሀውልቶች ካለበት
አጠገብ ከሚገኘው ጊዛ ከተባለው አካባቢ ነው። ሰሞኑን የግብጽ
መንግስት ለፕሬዝዳንት ሙባረክን ከስልጣን መወገድ ምክንያት የሆነው የግብጽ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የጀመረበት አምስተኛ አመት
መከበሩን ተከትሎ ችግር እንዳይነሳ የጸጥታ ሁኔታውን ማጥበቁ የሚታወስ ሲሆን በተባለው ህንጻ ላይ ፖሊሶች ፍተሻ ያካሄዱት
አሸባሪዎች አደጋ ሊያደርሱ እየተዘጋጁ ነው የሚል ጥቆማ ስለደረሳቸው መሆኑ ታውቋል።
Ø
ዛሬ ጥር 13 ቀን 2008 ዓም ከቱርክ ወደ ግርክ ስደተኞችን ጭና ስትጓዝ የነበረች አንዲት ጀልባ
በባህር ውስጥ በመስጠሟ ተጭነው ከነበሩት መካከል ቢያንስ 44 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። ። የግሪክ የጠረፍ ጠባቂዎች ቢያንስ 74
ሰዎች ያዳኑ መሆናችውን የተናገሩ ሲሆን ሞተው አስከሬናቸው ከተገኘው 44 ሰዎች መካከል 20 ህጻናት 17 ሴቶችና 10 ወንዶች
መሆናቸው ታውቋል። ስደተኞቹ አብዛኞቹ የሶሪያ ዜጎች ሲሆኑ ይጓዙበት የነበረው ጀልባ አስተማማኝ ያልነበረ መሆኑን
ብዙዎቹ ይናገራሉ። ባለፉት 22 ቀናት ብቻ 113 ስደተኞች ባህሩ ውስጥ ስምጠው የሞቱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ህጻናትን ጨምሮ
12 ስደተኞች መሞታቸው ተዘግቧል።
Ø
ወደ ብሩንዲ የተጓዙት የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የልኡካን ቡድን አባላት ዛሬ
አርብ ጥር 13 ቀን 2008 ዓም ከብሩንዲ የተለያዩ ባለስልጣኖች ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸው ተዘግቧል። የብሩንዲ ባለስልጣኖች
ከተቃዋሚ አባላት ጋር ተገናኝተው እንዲወያዩና ስምምነት እንዲያደርጉ እንዲሁም በአፍሪካ አድነት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል
የሚገባበትን መንገድ እንዲያመቻቹ የልዑኩ ቡድን አባላት ግፊት የሚያደርጉ መሆናቸው ታውቋል።
ቡድኑ በቅድሚያ የአገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት አግኝቶ ማነጋገሩ የታወቀ ሲሆን በስበስባው ወቅት ምክትል ፕሬዚዳንቱ
በአገር ውስጥ ችግር መኖሩን አምነው ችግሩን ለመቅረፍ የብሩንዲ መንግስት የተቻለውን እንደሚያደርግ ገልጸዋል። የልኡካኑ ቡድን
በፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት ከፕሬዚዳንቱ ጋር ንግግር ያደርጋለ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ
ኃይል ወደ አገሪቱ ስለሚገባበት ሁኔታ ፕሬዚዳንቱን ለማሳመን ከፍተኛ ግፊትት ያደርጋል ተብሎ ይገመታል። ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ
በዋናዋ ከተማ በደረሰ ግጭት አንድ ሰው መሞቱና አንድ ሌላ ሰው የአካል ጉዳት የደረሰበት መሆኑ ታውቋል።
ጥር 12 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት ጥር 11 ቀን 2008 ዓም በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ
የጥምቀት በዓል በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የአዲስ አበባ በዓል አከባበር ላይ
በወያኔ የደኅኔት ኃይሎች ተጥለቅሎ እንደንበር ከስፍራው የመጣው ዘገባ ገልጿል። ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነና የሲቪል
ልብስ የለበሱ የወያኔ የደህንነት ተቀጣሪዎች አስተናባሪ
የሚል ባጅ ደረታቸው ላይ ለጥፈው ታቦቱን አጅቦ ወደ መንበሩ ለማስገባት ከሚንቀሳቀሰው ሕዝበ ክርስትያን ጋር በመቀላቀል
ሲያስፈራሩ የነብሩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በአዲስ አበባ እና
በአካባቢዎ ባሉ አንዳንድ ቦታዎች ተቃውሞ የሚያሰሙ ወጣቶች የተደበደቡና ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው የታወቀ
ሲሆን በተለያዩ ከተሞችም የጥምቀት በዓሉን አስታኮ በወያኔ አገዛዝ
ላይ ተቃውሞ ሲሰማ መዋሉ ተነግሯል።
Ø
ካሪታስ ኢንተርናሽና የተባለው የካቶሊክ የአርዳታ ሰጭ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሚስተር ማይክል ሮይ ከቫቲካን
ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በኢትዮጵያ ለገባው ድርቅና ረሃብ አስፈላጊው እርዳታ ካልተደረገ በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ
ከፍተኛ የሆነ እልቂት ሊከተል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ምርት ከ90
ከመቶ በላይ መቀነሱና በዚህም 10.5 ሚሊዮን ሕዝብ በድርቁ እንደተጠቃና የ50 ዶላር እርዳታ የሚያስፈልግ መሆኑን በማስታወስ
ሚስተር ሮይ የችግሩን አስከፊነት ገልጸዋል። አያይዘውም ካሁኑ ጀምሮ በእርዳታው ላይ መረባረብ ካልተቻለ የዛሬ ሰላሳ አመት
ተፈጥሮ የነበረው ዓይነት የእልቂት ሁኔታ ሊደገም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በተያያዘ ዜና ሞጆ አካባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ በተራቡ ዜጎች ስም ለእርዳታ የመጣ ስንዴ በበርካታ
ጋሪዎች ተጭኖ ለጥቁር ገበያ ሲወጣ የተደረሰበት መሆኑ ከስፍራው ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ችለናል። በመቂ ከተማና በሞጆ ከተማ
መካከል በሚገኝ የህብረት ስራ ማህበር መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የነበረ ከእርዳታ የተገኘ ስንዴ ጥር 10 ቀን 2008 ዓ/ም
ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ገደማ ላይ አስራ አምስት በሚሆኑ በበቅሎ በሚጎተቱ ጋሪዎች ተጭኖ
ወደ ጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሲወጣ የተመለከቱ የአይን እማኞች የስንዴው ብዛት ሁለት ሺህ ኩንታል ሊጠጋ እንደሚችል
የገለጹ ሲሆን ጉዳዩን ለአካባቢው ባለስልጣኖች ቢያቀርቡም እርምጃ አለመወሰዱን አስታወቀዋል።
Ø
የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚ እና ተለጣፊ የሆነው የአፋር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የበላይና የበታች አመራር አባላት
በአፋር ሰመራ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲካሂዱት በነበረው ስብሰባ ላይ መግባባት ሳይቻል ቀርቶ ስብሰባው መበተኑን ከስፍራው የደረሰን
ዘገባ አስረድቷል። የስብሰባው ዋና ርዕስ በመልካም
አስተዳደር ዙሪያ ለመወያየት ቢሆንም በመካከላቸው ከፍተኛ የሆነ መወነጃጀል ስለተከሰተ ስብስባው የታቀደለት ጊዜ ሳያበቃ በድንገት
የተበተነ መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። በስብሰባው ወቅት ስራችሁን አልሰራችሁም፤ በህገ ወጥ ንግድ ላይ ተሰማርታችሁ
የግል ጥቅም አጋብሳችኋል፤ በሙዚቃ በመስማትና ጫት በመቃም ጊዜያችሁን ከማሳለፍ ውጭ ለአፋር ነዋሪ ያደረጋችሁት አንዳችም ነገር
የለም በማለት ባለስልጣኖቹ በበታች አመራር አባላት ስድብ አዘል ውንጀላ
ያወረዱባቸው ሲሆን ሌሎቹ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ በማንሳተቸው ስብሰባው ተበጥብጦ
እንዲቋረጥ የተደረገ መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
Ø
የኢቦላ በሽታ ጠፍቷል የሚል አዋጅ በተነገረ በሳምንት ጊዜ ውስጥ በምዕራብ አፍሪካ በሲየራ ሊዮን አዲስ
የኢቦላ በሽተኛ መገኘቱን የዓለም የጠና ድርጅት ዛሬ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም አስታወቀ። በኢቦላ በሽታ የታመመችውና አሁን
ህክምና እየተደረገላት የምትገኘው የ38 ዓመት ሴት ቀደም ብሎ በጥር 3 ቀን 2008 ዓም በኢቦላ የሞተችውንና አክስት
የምታሆናትን የ22 ዓመት ወጣት ሴት ስታስታምም የነበረችና በኋላም
ልጅቷ ስትሞት የሃማኖት ግዳጇን ለመወጣት ገላዋን ያጠበቻት መሆኑ ተነግሯል። የበሽተኛው ህመም የታወቀው ትናንት ጥር
11 ቀን ሲሆን ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ በመታከም ላይ መሆኗ ተጠቅሷል። የሲየራ ሊዮን ባለስልጣኖች ወደፊትም ተመሳሳይ
ህመምተኞች ሊታወቁ የሚችሉ መሆናቸውን ገልጸው ሕዝቡ በዚህ ምክንያት እንዳይደናገጥ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
Ø
የግብጽ የመከላከያ ሚኒስትር ዛሬ ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ
በሲና ባህረ ሰላጤ የአይሲስ ታጣቂዎች በአንድ መፈተሻ ቦታ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አምስት የግብጽ ወታደሮች የተገደሉ
መሆናቸውን ገልጸዋል። ወታደሮቹ የሞቱት ረቡዕ ጥር 11 ቀን ምሽት ላይ በአንድ መፈተሻ ጣቢያ ላይ የታጠቁ ሰዎች በጠባቂ
ወታደሮቹ ላይ ጥቃት ሰንዝረው በተካሄደው የተኩስ ልውውጥ ሲሆን አጥቂዎቹ እየተፈለጉ መሆናቸው ተገልጿል። አይሲስ የተባለው
አሸባሪ ቡድን በዌብ ሳይት ባሰራጨው ዜና ሶስት የአይሲስ ወታደሮች ኤል አሪሽ በሚባለው ስፍራ በግብጽ ወታደሮች ላይ ጥቃት
ፈጽመው ጉዳት ማድረሳቸውን ገልጿል። የረቡዕ ግድያ
የሙባረክን አገዛዝ ያወረደው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ አምስተኛ ዓመቱን ከሚከበርበት ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ የተካሄደ ሲሆን ሰሞኑን
ተመሳሳይ ጥቃቶች ይሰነዘራሉ በሚል የግብጽ የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
Ø
የጅቡቲ መንግስት ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ስምምነት የተፈራረመ መሆኑ ተገለጸ።
በትናንትናው ዕለት ቻይና የንግድ ዞኖችን በጂቡቲ ውስጥ ስለምታቋቁምበት ሁኔታና የቻይና ባንኮች በጂቡቲ ለመንቀሳቀስ
የሚያስችላቸውን ህጋዊ ሁኔታ አስመልክቶ ስምምነት የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ከጥቂት ጊዜ በፊት
ቻይና በጂቡቲ ውስጥ የባህር ኃይል የጦር ሰፈር እንድታቋቁም የጂቡቲ ባለስልጣኖች መፍቀዳቸው የተነገረ ሲሆን ይህም
ቀድም ብሎ በጂቡቲ ውስጥ የጦር ሰፈር ያላቸውን ፈረንሳይንና አሜሪካንን ማስከፋቱ ይታወሳል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት መልእክተኞች ዛሬ ጥር 12 ቀን 2008 ምሽት ላይ በብሩንዲ
ዋና ከተማ በቡጁምቡራ እንደሚገኙ ታወቀ። የመልእክተኞቹ ቁጥር 30 ሲሆን ከመካከላቸው ውስጥ የጸጥታው ምክር ቤት አባላት፣
ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች የሚገኙበት መሆኑ ታውቋል። በብሩንዲ መንግስት ባለስልጣኖች ላይ የሰላ ሂስ ሲያስተላልፉ የነበሩት የአሜሪካ
የጸጥታ ምክር ቤት ተወካይ ሳማንታ ፖወር ከመልእክተኞች ውስጥ አንዷ ሲሆኑ አቋማቸው
የብሩንዲን ባለስልጣኖች ሲያስቆጣ መቆየቱ ይታወቃል።
Ø
የኬኒያ መንግስት ማሊንዲ በሚባለው የባህር ዳርቻ ከተማ
የእስላም አክራሪዎች ናቸው የሚላቸውን አራት ግለሰቦች የገደለ መሆኑን አስታውቋል። አራቱ ሰዎች የተገደሉት በጸጥታ
አባላት ላይ ተኩስ በመክፈትና ቦምብ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሲሞክሩ መሆኑን ፖሊስ ገልጾ ከተገደሉት መካከል ባለፈው ታኅሣሥ
ወር ግድያ አካሂደው ሲፈለጉ የነበሩ አሸባሪዎች እንደሚገኙበት ገልጿል።
በተያያዘ ዜና ኬኒያ ወታደራዊ ተቋም ቺፍ ኦፍ ስታፍ የሆኑት ጄኔራል ባለፈው አርብ ሶማሊያ ውስጥ
የአልሸባብ ኃይሎች በፈጸሙት ጥቃት የኬኒያ ወታደሮች መገደላቸውን አምነዋል። ምን ያህል ወታደሮች እንደሞቱ ባይገልጹም አልሸባብ
በካምፑ ላይ ያፈነዱት ቦምብ ከአስራ ስምንት ዓመት በፊት ናይሮቢ አሜሪካን ኤምባሲ ውስጥ ከፈነዳው ቦምብ ሶስት እጥፍ የሚሆን
ኃይል የነበረው መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው አርብ በተደረገው ጥቃት አልሸባብ ከመቶ በላይ የሆኑ የኬኒያ ወታደሮችን ገድያለሁ
መግለጹ ይታወሳል።
ጥር 11 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ባለፈው ሳምንት በአዋሳ ከተማ በሚገኛው የመኪና መናኻሪያ ውስጥ ወደ
ሆሳዕናና ወደ ተለያዩ ከተማዎች በሚሄዱ መኪናዎች መቀመጫዎች ላይ ሞት ለወያኔ ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚል ርዕስ የያዛ ፅሁፍ
መበተኑን ከስፍራው ዘግየቶ ያገኘነው ዜና ይገልጻል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት በዲላ ዩኒቫርሲቲ ውስጥ በሚማሩ ተማሪዎች የወያኔ
አጋዚ ጦር ቦምብ ወርውሮ ሁለት ተማሪዎችን መግደሉና በሌሎች ላይ የመቁሰል አደጋ ማድረሱ የሚታወስ ሲሆን
በትናነትናው ዜናችን እንደገለጽነው ቁጥሩ ከተማሪዎቹ ጋር እኩል
ለኩል የሆነው የአግአዚ ጦር አሁንም ተማሪዎችን እየጨፈጨፈ፤ ሴቶችን እየደፈረና ንብረት በተለይም የተማሪዎችን የእጅ ስልክ
በመቀማት ከፍተኛ ግፍ እየፈጸመ መሆኑን ከስፍራው የሚደርሰን ዜና ይገልጻል።
Ø
በትናንትናው ዕለት በሀዲያ ዞን ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት
አገልግሎት በዛሬው ቀን በአንዳንድ አካባቢዎች የጀመረ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። የትራንስፖርት አገልግሎቱ ሊጀመር የቻለው
የወያኔ ባለስልጣኖች በሹፌሮችና በባለንብረቶች ላይ ያወጡትን የቅጣት መመሪያ
አንስተናል በማለታቸው አድማ መቸዎቹ በመስማማታቸው ሲሆን ውጥረቱና አለመተማመኑ ግን አሁንም ያለ መሆኑ ይታያል ተብሏል።
ከዋቸሞ ዩነቨርስቲ ተወስደው የደረሱበት ያልታወቁት ተማሪዎች ቁጥር በትናንት ዘገባቸን እንዳቀረብነው አራት ሳይሆን
ስምንት ተማሪዎች መሆናቸውን በመግለጽ በዚህ አጋጣሚ ለማረም እንወዳለን።
Ø
ትናንት ጥር 10 ቀን 2008 ዓም የአውሮፓው ህብረት ምክር
ቤት (ፓርላማ) ሰሞኑን በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን
የሕዝብ አመጽ አንተርሶ ባለ አስራምስት ነጥብ ጠንካራ ውሳኔዎች ማስተላለፉ ተገለጸ። የአውሮፓው ሕብረት ምክር ቤት (ፓርላማ)
ውሳኔዎቹ ላይ ለመድረስ ያበቁትን በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን አሳዛኝ ጉዳዮች
በዝርዝር ገልጧል።
ባለፉት ሁለት
ወራት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም በኦሮሚያ የተካሄዱትን አመጾች ለመግታት ወታደሮች
ከ140 ሰዎች በላይ መግደላቸውን፤ የአዲስ አበባ መስፋፋት ብዙ አርሶ አደሮችን ያፈናቀለ መሆኑን፣ በአካባቢው
የሰብአዊ መብት ጥሰት መኖሩን፤ የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች
አሸባሪዎች ናቸው በሚል በርካታ ሰልፈኞችን ማሰሩን፤
ከዚህም ጋር ተያይዞ የኦፌኮ መሪን አቶ በቀለ ገርባን የሚዲያ ሰዎችን እንደ አቶ ጌታቸው ሽፈራው፣ ዮናታን ተረሣ፣ ፈቃዱ ሚርካና
የመሳሰሉት መታሰራቸውን ግንዛቤ የወሰደ መሆኑን ገልጿል። እንዲሁም ወያኔ ከዚህ በፊት በርካታ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ ተቃውሞ
የሚካሂዱ ስልፈኞች፣ ተማሪዎችና እና ሌሎችን አስሮ በሽብረተኛ አንቀጽ ክስ በመመስረት እስር ቤት እያንገላታ መሆኑን
የእነ እስክንድር ነጋን፣ ተመስገን ደሳለኝን፣ ሰሎሞን ከበደን
ዩሱፍ ጌታቸው፣ ውብሸት ታየን፣ ሳለህ ኢድሪስንና ተስፋለደት ኪዳኔን ስም በመጥራት ዘገባ ሁኔታውን የተረዳ መሆኑን ገልጿል።
የወያኔ አገዛዝ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌንም ከየመን አፍኖ መውሰዱን የወያኔ ጦር በኦጋዴን ላይ የሚካሄደውን ጦርነትና ጭፍጨፋ
አስከፊ መሆኑን እንዲሁም ባለፈው ግንቦት የተካሄደው ምርጫ በማስፈራራትና በማፈን መሆኑን በተጨማሪም ወያኔ በየአመቱ 3ቢሊዮን
ዶላር እርዳታ ከምዕራብ አገሮች የሚያገኝ አገዛዝ መሆኑ፤ አርሶ አደሮች ለም ከሆነው መሬታቸው እየተነቀሉ መሬታቸው ለባዕዳን
ከበርቴዎች የሚሰጥ መሆኑን በመጥቀስ ምክር ቤቱ አጠቃላይ
ግንዛቤ ያለው መሆኑን ገልጾ ውሳኔዎች ያስተላለፈ መሆኑን
አሳውቋል። በውሳኔውም በኦሮሚያና በሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች የወያኔ ወታደሮች
የሚያደርሱትን ገደብ የለሽ ግድያ፤ የሰብአዊ መብት ረገጣ፤ ህገ ወጥ እስራትንና ሰቆቃዊ ድርጊትቶችን፤ የመናገርና የመጻፍ መብትን
ማገድን እንዲሁም ወንጀለኞች ለፍርድ ሳይቀርቡ በነጻ መለቀቃቸውን አውግዟል። በመንግስት የጸጥታ ወታደሮች እየተደረጉ ያሉት
የአፍናና የግድያ ተግባሮች ባስቸኳይ እንዲቆሙና መብታቸውን በመጠቀም በማሰማታቸው ብቻ የታሰሩ
ተማሪዎች፤ አርሶ አደሮች የፖለቲካ ተቃዋሚዎች፣ ምሁራን ጋዜጠኞችና ጦማራውያን በሙሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በተደረጉት ግድያዎች ላይ ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ ምርመራና ማጣራት እንዲካሄድና ጥፋተኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጥሪ
አስተላልፏል። ወያኔ የዓለም አቀፉንና የአፍርካ ህብረትን
የሰብአዊ መብት ቻርተርና ድንጋጌን ማክበር ያለበት መሆኑን ገልጾ በሚዲያ ላይ እያካሄደ ያለን የሞገድ አፈናና እንዲያነሳና ነጻ
የሆኑ ሚዲያዎች ስራቸውን በነጻ የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቋል። እየተካሄደ ያለው ያለ አግባብ የሆነ የሰፈራ ፕሮግራም
ምክር ቤቱን ያሳሰበው መሆኑን የገለጸ ሲሆን በአካባቢው የሚደረገው የልማት ስራ ከአካባቢው ሕዝብ ጋር ተመካክሮ መሆን
እንደሚገባው አሳስቧል። የአውሮፓ አገሮች ለልማት ስራዎች ለወያኔ የሚሰጡት እርዳታና ብድር ከአገሪቱ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ጋር
መመጣጠን መሆኑን ገልጾ የአውሮፓው ኅባረትና አባል አገሮች በንጹሐን ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለውን ርምጃ ኮንነው ድርጊቱን
ለማስቆም አስፈላጊውን ተጽእኖ እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስርያ ቤት
ቃል አቀባይ ሚስተር አድርያን ኤድዋርድስ ትናንት ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በየመን ከፍተኛ
የሆነ የእርስ በርስ ጦርነት እየተካሄደ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም
ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ከኢትዮጵያና ከሶማሊያ እየፈለሱ ወደ አገሪቷ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር 92 446
,
መድረሱን ጠቅሰው ከዚህ ውስጥ
82,268
ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል። ወደ የመን የተሰደዱት
ዜጎች ቁጥር በየገዜው እየጨመረ የሄደው በዚያ ያለውን ሁኔታ ካለማወቅ የተነሳ መሆኑን ገልጸው በአሁኑ ወቅት የስደተኞቹ ህይወት
በከፍተኛ ደረጃ አደጋ ላይ መሆኑን ዘርዝረው አስረድተዋል። ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም 106 ስደተኞችን የጫነች አንድ
አነስተኛ ጀልባ ባህሩ መሀል ላይ በመስጠሟ 36 ሰዎች የሞቱ ሲሆን
ሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ተገልጿል። ከተረፉት ሰባዎች መካከል አንዱ ብቻ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ታውቋል። ቃል አቀባዩ ይህን
አደገኛ የስደተኞች ጉዞ የሚያደራጁት ገንዘባቸውን ብቻ የሚያሳድዱትና ለሰው ህይወት ደንታ የሌላቸው አስተላላፊዎች መሆናቸውን
ገልጸው በየመን ስላለው አደገኛ ሁኔታና ለባህር ትራንስፖርት ብቃት በሌላቸው ጀልባዎች ላይ መሳፈር አደገኛ ስለመሆኑ ጉዳይ
ስደተኞቹ ሊያዉቁ የሚችሉበት ሁኔታ መፈለግ አለበት ብለዋል።
Ø
ራሷን ሶማሌላንድ ብላ የምትጠራው የሶማሌ ግዛት ባለስልጣኖች
ትናንት ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ሕገ ወጥ ስደተኞች የሚሏቸውንና በዋናዋ ከተማ በሀርጌሳ የሚገኙትን 300
ኢትዮጵያውያንና ለወያኔ አገዛዝ ባለስልጣኖች የሚያስረክቡ መሆናቸው ገልጸዋል። ከስደተኞቹ መካከል አብዛኞቹ የኦሮሞ ብሔረሰብ
አባላት መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ሰደተኞቹን ባስቸኳይ ለመመለስ ዝግጅቱ የተጠናቀቀ መሆኑን ባለስልጣኖቹ ገልጸዋል። ሱማሌላንድ
በ1982 ዓም ራሷን አገር በማለት ያወጀች ሲሆን እስካሁን ድረስ በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ እውቅናን አላገኘችም።
Ø
ዛሬ ጥር 11 ቀን 2008 ዓም በምዕራብ ፓኪስታን በቻርሳዳ
ከተማ በሚገኘው ባቻ ከሃን ዩንቨርስቲ ላይ ታጣቂዎች ባካሄዱት የቦምብ ጥቃት 19 ሰዎች መገደላቸውና ከ50 በላይ መቁሰላችወን
የፓኪስታን ፖሊስ ገልጿል። አጥቂዎቹ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተኩል ሲሆን የዩኒቨርስቲውን የጀርባ አጥር በመዝለል ጥቃቱን መሳሪያ
በመተኮስና ቦምብ በማፈንዳት መፈጸማቸው የተገለጸ ሲሆን ከዩኒቨርስቲው የጸጥታ አባላት ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል።
አንድ የታሊባን ወታደራዊ ኮማንደር ጥቃቱ የተወሰደው በታሊባን መሆኑን ጠቅሶ እርምጃውም በቅርቡ የፓኪስታን ወትደራዊ
ኃይል ለወሰደው ጥቃት የአጸፋ እርምጃ ነው ብሏል። በሌላ በኩል የታሊባን ቃል አቀባይ የሆነው ለቢቢሲ የዜና ወኪል በሰጠው ቃል
ድርጊቱን ታሊባን እንዳልፈጸመው ገልጾ ርምጃው ከሙስሊም ሃይማኖት ትእዛዝ ውጭ የተደረገ የሚወገዝ ድርጊት ነው ብሏል። ስለሆነም
ድርጊቱን ማን እንደፈጸመው እስካሁን በትክክል የተገኘ መረጃ የለም። ከዚህ በፊት ከተማዋ በታሊባን ተደጋጋሚ ጥቃት የተፈጸመባት
መሆኗና በርካታ ዜጎችም እንደሞቱ ይታወቃል።
Ø
የሱዳኑ ፕሬዚዳንት አልበሽር ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008
ዓም ባደረጉት ንግግር በግብጽ ቁጥጥር ስር ያለውና ሃላየብ ትሪያንግል በሚል ስም የሚጠራው ቦታ የሱዳን ስለሆነ መንግስታቸው
ቦታው ለሱዳን እንዲመለስ ከመታገል ወደኋላ የማይል መሆኑን
ገልጸዋል። በሱዳንና በግብጽ መካከል ያለው የወንድማማችነት ግንኙነት የጠነከረ ቢሆንም ከ1982 ጀምሮ በግብጽ አስተዳድር ስር
ያለው የሃላየብ ትሪያንግል በታሪክ የሱዳን መሬት በመሆኑ አገሪቱ ቦታው እንዲመልስላት ትፈልጋለች ብለዋል። ቀደም ብሎ የሱዳን
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉዳዩን በየዓመቱ በተመድ ስብሰባ ላይ የሚያነሱት መሆኑን ጠቅሰው በሰላማዊ መልክ እንዲያልቅ ማናቸውንም
እርዳታ ለማድረግ ጥረት የሚያደርጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የሱዳን የጸጥታና የኢንተለጀንስ ኃላፊ ሚስተር ሙሀመድ አባስ የአየሲስ (ዳሽ) አሸባሪዎች
ወደ ሱዳን ገብተው ጉዳት እንዳይደርሱ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃ እየወሰዱ መሆናችውን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት
አስቸኳይ የእርዳታ ሰጭ የሚበለው ጸረ ሽብር ግብረ ኃይል አባላት ምረቃ በተካሄድበት ወቅት መሆኑ ታውቋል። የሱዳን ወጣቶች
በብዛት ወደ ሊቢያ እየሄዱ አይሲስ የተባለውን ድርጅት ተቀላቅለው እየተዋጉ ነው የሚል መረጃ አለ። ባለፈው ዓመት በሱዳን የግል
ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች ወደ ቱርክና ሶሪያ በመሄድ አይሲስን ተቀላቀለው ሲዋጉ መቆየታቸው በተደጋጋሚ ከተገኘ ዜና ማወቅ
ተችሏል። ማረጋገጫ ባያቀርቡም የሱዳን የጸጥታ ኃላፊ በዳርፉር እየተዋጉ ያሉት አማጽያን አባላትም ሊቢያ ሄደው ከአይሲስ ጋር
ተቀላቅለው እየተዋጉ ነው የሚል መግለጫ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት በዳርፉር የመንግስት ወታደሮች ከጥቂት ቀናት
በፊት ያካሄዱትን ዘመቻ ለመደገፍ ነው ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ታዛቢዎች ወስደዋል።
በተያያዘ ዜና ባለፉት ጥቂት ቀናት በዳርፉር በመንግስት ኃይሎችና በአማጽያኑ መካከል ጦርነት ተጠናክሮ
እየተካሄደ ሲሆን በአካባቢው ያሉ ሰላማዊ ሰዎች በከፍተኛ
ችግር ውስጥ ሊወድቁ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣኖች ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም በይፋ
አስታውቀዋል። በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ሰዎች ቤት ንብረታችውን ለቅቀው ሊሰደዱ እንደሚችሉ ባለስልጣኖቹ ገልጸው በተለይ ሴቶች
እና ህጻናት ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ሊወድቁ ይችላሉ ብለዋል። በዳርፉ የሚገኘው የተመድ እና የአፍሪካ ኅበረት የሰላም አስከባሪ
ኃይል በዚሁ ቀን ባሰራጨው ዘገባ በማእከላዊ ዳርፉር አሁንም ጦርነቶች እየተካሄዱ መሆናቸውንና
ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ስዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ቤቶች መቃጠላቸውን የሚገልጹ ዘባዎች የደረሰው መሆኑን
ገልጿል።
ጥር 10 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሐዲያ ወደ ሆሳዕና
እና ወደ ተለያዩ ከተሞች የሚደረጉ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ዝግ ሆነው መዋላቸውን ከአካባቢው የተገኘው መረጃ ይገልጻል።
የትራንስፖርት አገልግሎት ያልነበረው በቅርቡ የተለለፈውን
መመሪያ የተቃወሙ
የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችና ታክሲዎች ባደረጉት አድማ ምክንያት ሲሆን መመሪያው
እስካልተነሳ ድረስ አድማው የሚቀጥል መሆኑ ከአካባቢው የሚገኘው ዜና ይገልጻል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቀደም ብለው ከወቻሞ
ዩኒቨርስቲ ተይዘው የተወሰዱት አራት ተማሪዎች የት እንደታሰሩ ባለመታወቁ ቤተሰቦቻቸው ከፍተኛ ሀሳብና ጭንቀት
ላይ
መውደቃቸውን ለማወቅ ተችሏል። በዲላም በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተማሪዎችና የአግአዚ ጦር አባላት ቁጥር እኩል ለእኩል መሆኑ የታወቀ
ሲሆን ተማሪዎቹ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው መሆኑና የእጅ ስልኮቻቸውንም የተቀሙ መሆናቸው ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች
ይገልጻሉ።
Ø
ትናንት ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሀረርጌ መኤሶ
ከተማ የአግአዚ ወታደሮች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ሲተኩሱ የዋሉ ሲሆን ቁጥራቸው
በርካታ የሆኑ ሰዎችን አስረው በከባድ ካሚዎን ወደ
ጂጂጋ የወሰዷቸው መሆኑን
ከአይን እማኞች የተገኘው መረጃ ይገልጻል።
ታስረው ወደ ጂጅጋ የተወሰዱት
ሰላማዊ ሰዎች ያለፈቃድ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥታችኋል በማለት እንደሚወነጀሉ
የተነገራቸው መሆኑንም ለማወቅ የተቻለ ሲሆን
ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘው ወደ ጂግጂጋ
የተዛወሩ እስረኞች ቁጥር አንድ መቶ ሃያ እንደሚሆኑ የአይን እማኞች አስረድተዋል
። የአዲስ አበባ ማስተር በመቃወም በየቦታው ተነስቶ በነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ
በአሁኑ ወቅት “የወገኖችን ህይወት በግፍ ያጠፉ ገዳዮቹ ለፍርድ ይቅረቡ”፤ “ታስረው የሚሰቃዩት ባስቸኳይ ይለቀቁ” ወደሚሉ
ሕዝባዊ ጥያቄዎች እየተሸጋገሩ መምጣታቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን ዘገባዎች የሚጠቁሙ ሲሆን ሰሞኑን በአሰቦት ምዕራብ
ሐረርጌ ፤ በሊሞ ምዕራብ ሸዋ እንዲሁም በጊዳ ምስራቅ ወለጋ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
Ø
ከሀሮማያ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመልጣችኋል ወይም ደብቃችኋል በሚል በሰላማዊ ዜጎች ላይ
የሚደርሰው የግፍ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ከአካባቢው የሚደርሰው ዜና ይገልጻል። በትናንትናው ዕለት በርከት ያሉ ሰዎች
ከየቤታቸው የተወሰዱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ለጊዜው ስሙ እንዳይገለጽ የተጠየቀ በንግድ ስራ ይተዳደር የነበረው እድሜው ከአርባ
እስከ አርባ አምስት ድረስ የሚገመተው ጎልማሳ በአግአዚ ወታደሮች እየተደበደበ ከመኖሪያ ቤቱ ታፍኖ ሲወሰድ በርካታ ዜጎችን
አስቆጥቶ ተቃውሞ ያስነሳ ከአካባቢው የመጣ ዜና ይገልጻል።
በተያያዘ
ዜና ከአዳማው የደህንነት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት የሶስት ቀን ስብሰባ በኋላ በድንገት ተይዘው የታሰሩት የደህንነት አባሎች
ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓ/ም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለምዶ እንግሊዝ ኤምባሲ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ
የደህንነት ቢሮ ውስጥ የተወሰዱ መሆናቸውና ከፍተኛ ምርመራ እንደተደረገባቸው መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።
ሕዝብን ለማሳመጽ
ቅስቀሳ አድረገናል በዚህም
ይህ የክህደት ወንጀል ፈጽመናል ብላችሁ እመኑ በማለት ተጽእኖ እየተደረገባቸው
መሆኑን ጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አረጋግጠዋል።
Ø
የናይጄሪያ የማስታወቂያ ሚኒስትር ትናንት ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም ለጋዜጠኞች በሰጡት
መግለጫ በሰባት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ የናይጄሪያ አገረ ገዠዎች፤ ሚንስትሮች የንግድ ተቋም ባለቤቶች ፤ የባንክ እና የመንግስት
ባለሥልጣኖች 9 ቢሊዮን ዶላር የአገሪቷን ገንዘብ አለአግባብ የዘረፉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የተሰረቀው ገንዘብ 1.35 ትሪሊዮን
የናይጄሪያ ናይራ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸው ይህም 36 ሆስፒታሎች ለመስራት ወይም 4000 ተማሪዎችን እስከዩነቨርስቲ ድረስ
ለማስተማር የሚያስችል ገንዘብ እንደነበር ገልጸዋል። ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸው ባሁኑ ወቅት አስፈላጊው ርምጃ መወሰድ
አለበት ብለዋል። ሚኒስትሩ የተዘረፈውን ገንዘብ ዝርዝር መረጃም አቅርበዋል።
ገንዘቡ
ተዘርፏል የተባለው እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2013 በአብዛኛው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን በስልጣን ላይ
በነበሩበት ወቅት ሲሆን የቀድሞ የጸጥታ አማካሪ የነበሩት ሚስተር ዳሱኪ 2 ቢሊዮን ዶላር ዘርፈዋል ተብለው መወንጀላቸው
ይታወሳል። በአሁኑ ወቅት የናይጄሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው ፒፕልስ ዴሞክራቲ ፓርቲ የአሁኑ እርምጃ
የፓርቲውን
አባላት ለማጥቃት ሆን ተብሎ በስልጣን ላይ ባለው
ኦል
ፕሮግሬሲቭ ኮንግሬስ በተባለው ፓርቲ
የተጠነሰሰ ሴራ የሚል ውንጀላ ሲያቀርብ ባለስልጣኖቹ ደግሞ የአገሪቱን ገንዘብ
የሰረቀ የማንኛውም ፓርቲ አባል ለፍርድ ይቀርባል ብለዋል።
Ø
የናይጀር መንግስት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጋራ በመሆን በናይጄሪያና በናይጀር ወሰን አካባቢ የሚገኙትን እና ለቦኮ
ሃራም ጥቃት የተጋለጡትን 99 ትምህርት ቤቶች የጸጥታ ሁኔታቸው ወደተሻለ አካባቢዎች ለማዛወር ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተመድ
ትናንት ጥር 9 ቀን 2008 ዓም ገልጿል። በናይጄሪያ እና በናይጀር ወሰን በሆኑ አካባቢዎች 12600 የሚሆኑ ተማሪዎችን
ያስተናግዱ የነበሩ 166 ትምህርት ቤቶች የተዘጉ ሲሆን ባለፉት ሁለት ወራት የጸጥታ ሁኔታቸው ደህና ነው በሚባልላቸው አካባቢዎች
የመማሪያ ክፍሎችን በመስራት 6000 ተማሪዎች እንዲዛወሩ የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
Ø
ከትቂት ጊዜ በፊት በተባበሩት
መንግስታት ድርጅት አማካይነት በሊቢያ የአንድነት መንግስት ለመመስረት
ስምምነት
ላይ የተደረሰ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም 32 አባሎች የሚገኙበት የዚህ የአንድነት መንግስት
ባለስልጣኖች ስም ይፋ ተደርጓል።
ስምምነት ተደርሶበታል ለተባለው የአንድነት
መንግስት ከሁለቱም ተጻራራሪ መንግስታት ምክር ቤት አባሎች ድጋፋቸውን የሰጡ
ከግምሽ በታች መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን
ዛሬ ይፋ የተደረገውን የ32
ሚኒስትሮችና
የከፍተኛ ባለስልጣኖች የስም ዝርዝር ምን ያህሉ የተጻራሪ ቡድኖች
ምክር ቤቶች አባላት እንደሚደግፏቸው ግልጽ አይደለም።
የምዕራብና
የሌሎች አገሮች መንግስታት እንዲሆም ዋና
ዋና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ተጻራሪ ወገኖች ስምምነት የተደረሰበትን የሊቢያን የአንድነት መንግስት እንዲቀበሉ ከፍተኛ ግፊት
ሲያደርጉ የቆዩ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን የተጠቀሱትን ባለስልጣኖች
እንዲቀበሉ
ግፊት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከአራት ዓመት በፊት የሊቢያ መሪ ሙአመር ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ ሊቢያ ቀውስ የገባች ሲሆን
በምስራቅና በምዕራብ ሊቢያ ሁለት ተጻራሪ መንግስታት መቋቋማቸውና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችም
የአይሲስ እና የአልቃይዳ አሸባሪዎች እንቅስቃሴ እየተጠናከረ መምጣቱ ይታወቃል።
ጥር 9 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአዲስ
አበባን ማስተር ፕላን በመቃውም የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ በተለያዩ ከተሞች
የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። በትናንትናው ዕለት በአምቦ ዪኒቨርስቲ የወንዶች ተማሪዎች መኝታ ክፍል የተቃጠለ ሲሆን
የቃጠሎው መነሻና ማን እንዳቃጠለው ለጊዜው አልታወቀም። በሀረር በሃሮማያ ከተማ ከአግአዚ ጦር ተኩስ ያመለጡትን ወጣቶች
ሸሽጋችኋል በማለት የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰዎችን ከቤት እያስወጡ ከፍተኛ ድብደባ ያካሄዱባቸው መሆኑ ታውቋል። በመኢሶም
ከፍተኛ የሕዝብ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን የአግአዚው ጦር በወሰደው ርምጃ ሰላማዊ ስዎች መገደላቸውና መቁሰላቸው
ተዘግቧል።
Ø
በአዳማ/ናዝሬት
ከተማ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የወያኔ የደህንነት አባላትና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ስብሰባ የተጠናቀቀ ሲሆን በስብሰባው
መጨረሻ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ሁለት የደህንነት አባላት መታሰራቸውን ከስብሰባው አካባቢ ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ግለሰቦቹ
የታሰሩት በስብሰባው ወቅት አመጽ በተካሄደባቸው አካባቢዎች በአግአዚ ጦር የተወሰደው እርምጃ አግባብ አይደለም በማለት አስተያየት
በመስጠታቸውና በጥብቅ በመከራከራቸው ነው ተብሏል።
Ø
ወይኔ እና ሱዳን ቀደም ብሎ አቋቁመውት የጋራ የወሰን
አካላይ ቴክኒካል ኮሚቴ በዚህ ዓመት ስራውን አጋባድዶ ወሰኑን ሊያካልል እንደሚችል የሱዳኑ የቴክኒካል ኮሚቴ ኃላፊ ሚስተር
አብደላ አል ሳዲክ የሱዳን ሚዲያ ሴንተር ለተባለ የሚዲያ ተቋም
መግለጻቸው ታወቀ። የሱዳኑ ባለስልጣን የሚካለለው ወሰን ርዝመት 725 ኪሎሜትር መሆንኑና ከዚሁ ውስጥ በሁለቱም አገሮች አርሶ
አደሮች ያለመግባባት የፈጠረው በደቡብ ምስራቅ የገዳሪፍ አውራጃ
የሚገኘው አል ፋሻጋ የተባለው 125 ኪሎሜትር ርዝመትና
ስድስት መቶ ሺ ኤከር ስፋት ያለው ለም የሆነ የእርሻ መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ቅዳሜ ጥር 7 ቀን 2008 ዓም
የሱዳኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለአልጄዚራ የቴሌሊቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ የአልፋሻጋ አካባቢ የሱዳን መሬት መሆኑን ወያኔ
አምኖልናል ካሉ በኋላ እስካሁን የኢትዮጵያ አርሶ አደሮችን መሬቱን እንዲያርሱ የፈቀድነው ለትብብር ካለን ፍላጎት ብቻ ነው የሚል
አስተያየት ሰጥተዋል። የሱዳን ባለስልጣኖች በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የሰጡት መረጃ የወያኔን ቅጥፈትና ውሸት አጋልጧል ተብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ነኝ ባዩን ጨምሮ የወያኔ ባለስልጣኖች በተለያዩ ወቅቶች ከሱዳን ጋር የተደረገ ስምምነት የለም በማለት ሲዋሹ
መቆየታቸው የታወቀ ሲሆን ከዚህ ተጻራሪ በሆነ መንገድ የሱዳን
ባለስልጣኖች የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ወያኔ የተስማማ መሆኑና የወሰን ማካለሉም ስራ በዚህ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቀ
ተናገረዋል።
Ø
የታንዛኒያ
ፖሊሶች 83 ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን ሕገ ወጥ ናቸው በሚል ያሰሩ መሆኑን ሲትዝን የተባለው የታንዛኒያ ጋዜጣ ዘግቧል። የፖሊሱ
መረጃ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በአንድ ጭነት መኪና ተጭነው ወደ ማላዊ ያመሩ እንደነበር ጠቁሞ የመኪናው ሹፌርና ወጣቶቹ ያረፉበት
ቤት ባለቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል። ኢትዮጵያውያኑ
በተያዙበት ወቅት በረሃብና በመንገድ ብዛት ደክመውና ተጎሳቁለው እንደነበር ተነግሯል። ከዚህ በፊት ታንዛኒያ ውስጥ በርካታ
ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተደጋጋሚ ተይዘው ለፍርድ የቀረቡ መሆናቸው ይታወሳል።
Ø
የአለም
የኢኮኖሚክ መድረክ የሚባለው አመታዊ ስብስባ ዳቮስ በተባለችው የስዊዘርላንድ ከተማ ነገ ጥር 10 ቀን 2008 ዓም ከመጀመሩ
አንድ ቀን ቀደም ብሎ ኦክስፋም የተባለው የእርዳታ ድርጅት ባሰራጨው ዘገባ በሃብታቸው የመጠን ከፍተኛውን ደረጃ የያዙት አንድ
ከመቶ የሚሆኑ ሃብታሞች ከተቀረው የዓለም ሕዝብ የበለጠ ሀብት እንዳላቸው ገልጿል። ዘገባው
በዓለም በሃብታቸው መጠን ከፍተኛ የሆኑት 62 ግለሰቦች የያዙት ሀብት የዓለምን ግማሽ ሕዝብ ሃብት ድምር መሆኑን
የሚገልጽ መረጃ አካትቷል። የአንድ ከመቶ ኢኮኖሚ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይኸው የኦክስፋም ዘገባ በየአገሮቹ ካለው ሀብት ውስጥ
የሰራተኞች ገቢ ድርሻ በየጊዜው እየቀነሰ መምጣቱን ገልጾ ከዚሁ ውስጥ የሴቶች ድርሻ ደግሞ በአሳሳቢ ደረጃ ዝቅ ያለ መሆኑን
አጋልጧል። ማክሰኛ ጥር 10 ቀን በሚጀመረው የአለም የኢኮኖሚክ
መድረክ ላይ 40 የሚሆኑ የአገር መሪዎች የሚገኙበት ሲሆን 2500 የሚሆኑ ተለያዩ የንግድና የብዙሃን ድርጅቶች መሪዎች
ይሳተፉብታል ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
በሱዳን
ዳርፉር የተሰማራው የተመድ እና የአፍሪካ ህብረት ጥምር የሰላም አስከባሪ ኃይል ቃል አቀባይ ትናንት እሁድ ጥር 8 ቀን 2008
ዓም በሰጠው መግለጫ ባለፉት ጥቂት ቀናት በመንግስት ኃይሎችና በአማጽያን መካከል ጀበል ማራ በተባለው ቦታ እየተካሄደ ያለው
ጦርነት ያሳሰበው መሆኑን ገልጿል። ጦሩ በሰፈረባት ነርቲቲ በተባለቸው ከተማ ውስጥ አምስት ቦምቦች የፈነዱ መሆናቸውና የቦምቡ
ፍንዳታ በካምፑ ውስጥ በደንብ ሊታወቅ የቻለ መሆኑን አብራርቷል። የተመዱ ቃል አቀባይ ስለጦርነቱ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም
ካለፈው አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ የመንግስት ወታደሮች ዳርፉር ውስጥ በሚገኙ በተለያዩ የአማጽያን ይዞታዎች ላይ
ጥቃት የፈጸሙ መሆናቸውን የሱዳን የዜና አውታሮች ገልጸዋል።
የመንግስት ወታደሮች 10 የሚሆኑ ወታደራዊ አውሮፕላኖችን በመጠቀምና በርካታ ወታደሮችን በማሰለፍ በመፈጸሙት ጥቃት ከፍተኛ ቁጥር
ያላቸው መንደሮች ተቃጥለው ወደ አመድ መቀየራችውና በሺ የሚቆጠሩ ዜጎች አካባቢያቸውን በመጣል መስደዳቸውን የዜና ምንጮቹ
ዘግበዋል። ጦርነቱ እየተካሄደ በመሆኑ ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱም ለማወቅ አልተቻለም ብለዋል። ከዚህ በፊት የሱዳኑ ፕሬዚዳንት
አል በሽር በመንግስት ወታደሮችና በአማጽያኑ መካከል የተደረገው የተኩስ ማቆም ስምምነት የሚቀጥል መሆኑን በተደጋጋሚ መናገራቸው
የሚታወስ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የመንግስቱ ወታደሮች ጥቃት ለመውሰድ ያስገደዳቸው አማፅያኑ በቅድሚያ ጦርነት በመክፈታቸው ነው
ተብሏል።
Ø
ዛሬ
ጥር 9 ቀን 2008 ዓም በሰሜናው ካሜሩን ግዛት በአንድ መስጊድ ውስጥ በአንድ አጥፍቶ ጠፊ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች
መሞታቸውንና ሁለት ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን የካሜሩን የጸጥታ ኃላፊዎች ለዜና ምንጮች
ገልጸዋል። ቦምቡ የፈነዳው እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ በመስጊድ ውስጥ የነበረው የጸሎት
ስነስርዓት እያለቀ በነበረበት ጊዜ ነው። ከዚህ በፊት አካባቢው በቦካሃራም ታጣቂዎች ጥቃት ሲደርስበት የቆየ መሆኑ የሚታወቅ
ሲሆን ከአምስት ቀን በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በፈነዳ ቦምብ 12 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።
ጥር 7 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና
የእርሻ ድርጅት በሚቀጥሉት ወራት ከፍተኛ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የእህል እጥረት ሊያጋጥም እንደሚችል ገልጾ የገባውን ድርቅና ረሃብ
ለመቋቋም የ50 ሚሊዮን ዶላር አሰቸኳይ ርዳታ እንደሚያስፈልግ ገልጿል።
በሚቀጥሉት
ሁለት ወራት በከፍተኛ ደረጃ እየተባባሰ ይሄዳል የተባለው ድርቅ በአሁኑ ወቅት በርካታ ወገኖቻችንን ያስራበ መሆኑኑና የቤት
እንሣዎችንና የቀንድ ከብቶችን በብዛት እየጨረሰ መሆኑ ተነግሯል። የተመድ የምግብና የርሻ ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑ
ሚስተር አማዶ አላሁሪ በሰጡት መግለጫ በመጭው የፈረንጆቹ ዓመት የድርቁ ሁኔታ በጣም እየተባባሰ ሊሄድ የሚችል መሆኑን ጠቅሰው
የእህል ዋጋ በጣም ሊጨምር እንደሚችልና ሳር እና መኖም ስለማይኖር
የቤት
እንስሳሳትና የቀንድ ከብቶች
በከፍተኛ
ደርጃ ጉዳት ሊደርስባቸው እንደሚችል ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በርካታ ሕዝብ እየተራበ ሲሆን በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ሕጻናትም
ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ድርጅቱ በቅርቡ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ገንዘብ መስጠት እንደሚጀመርና 100 000 ሺ
በጎችንና ፍየሎችን
ማደል ለመጀመር እቅድ እንዳለው ገልጸዋል። በርክታ
አካባቢዎች በድርቅ የተጎዱ ሲሆን አንዳንድ ቦታዎች የምርቱ ውጤት
ከ 50
እስከ
90 እጅ የቀነሰ መሆኑ ይታወቃል። ዜጎች አካባቢያቸውን ጥለው ወደ ተለያዩ ቦታዎች መሰዳድቸውም ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ
ተዘግቧል።
Ø
ትናንት ዓርብ
ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ በአንዋር መስጊድና በቤኒን መስጊድ የጁምዓ ጸሎት ሊያደርሱ በስፍራው በተገኙ አማኞች ላይ
ጥብቅ ፍተሻ ሲደረግ እንደነበር ከስፍራው ከመጣ ዜና ለማወቅ ተችሏል። ከሳምንታት በፊት በታላቁ አንዋር መስጊድ ወያኔ
ተላላኪዎቹን በማሰማራት የቦንብ ፍንዳታ እንዲካሄድ ካደረገ ጀምሮ የስግደት ስነርዓታቸውን ለመፈጸም ወደ መስጊድ የሚሂዱ
ሙስሊሞችን በፍተሻ አሳቦ ማዋከብ ማንገላታትና ማሰቃየትን ስራዬ ብሎ ተያይዞት የነበረ መሆኑ ይታወቃል ። በትናንትናው ቀን
ለሳምንታዊው
የጁምዓ የስግደት ጸሎት በታላቁ አንዋር መስጊድና በቤኒን መስጊድ የተገኙትን አማኞች ብዛት ያላቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት
በፍተሻ ስም በከፍተኛ ደረጃ
ሲያንገላቱዋቸውና
የስግደት ሰዓት እንዲያልፍባቸው ሲያደርጉ እንደነበር በሁለቱም መስጊዶች ተገኝተው የነበሩ ዘጋቢዎቻችን ከላኩት ዘገባ ለመረዳት
ተችሏል።
Ø
በአዲስ አበባና
በተለያዩ ከተሞቸ የህብረተሰቡን የስኳር ፍጆታ ለማሟላት
ከነበሩት ተቋሞች በተጨማሪ ሰባት አዳዲስ
የስኳር
ፋብሪካዎች ከፍተናል በማለት ሲደሰኩር የነበረው የወያኔ አገዛዝ ከውጭ አገር ስኳር ሲያስገባ መቆየቱ ይታወቃል።
ተቋቋሙ
የተባሉት አዳዲስ ፋብሪካዎች የተገጠመላቸው መሳሪያዎች ከጥቅም ውጭ በመሆናቸውና ቀደም ብለው የነበሩትም በእድሳት ምክንያት ስራ
በማቆማቸው ስኳር ከውጭ ለመግዛት ተገዶ የነበረ መሆኑን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ይናገራሉ። በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ባለው
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ስኳሩን ከውጭ ለማስመጣት ችግር በመፈጥሩ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ
ለነጋዴዎች በኪሎ አስራ አምስት ብር ሲሸጥ የነበረው
የስኳር ዋጋ አስራ ስምንት ብር ለመሸጥ የታቀደ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
በጥቁር ገበያ የሚሸጠው ስኳር በኪሎ 22 የሚደርስ
መሆኑ ሲገመት ከአዲስ አበባ ራቅ ባሉ እንደጋምቤላ አካባቢዎች የአንድ ኪሎ ስኳር ዋጋ ከእጥፍ በላይ ጨምሮ እስከ አርባ ሁለት
ብር
ሊደርስ
ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
ነገ እሁድ ጥር 8 ቀን 2008 ዓ/ም ከማለዳው 2 ሰዓት ተኩል አንስቶ በቻግኒ
ከተማ ነዋሪዎች ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ከስፍራው የደረሰን ዜና ይገልጻል። ስብሰባውን የጠሩት የወያኔ ተላላኪዎች በመባል
የሚታወቁት የብአዴን ባለስልጣኖች ሲሆኑ ስብሰባው ይመራዋል የተባለው የብአዴን መገኛኚያ ብዙሐን ነው ተብሏል። የከተማ ነዋሪ
ሕዝብ ከፍተኛ በደል እየደረሰበት ያለ መሆኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች የገለጸ ሲሆን በወቅታዊ ጉዳዮችና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ
ውይይት ይካሄዳል በተባለለት ስብስባም በከፍተኛ ደረጃ ብሶቱን ይገልጻል ተብሎ ይገመታል። ሕዝቡ ተቆጥቶ እርምጃ ሳይወስድብን
እናለሳልሰው በሚል ስሜት ሰሞኑን አንዳንድ እርምጃዎች በመውሰደ ላይ ያሉት የብዓእዴን ባለስልጣኖች ዝቅተኛ የአካባቢ ኃላፊዎችን
ከቦታቸው ያነሷቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። ብአዴንም ሆነ ወያኔ እያካሄድን ነው የሚሉት
የጥገና
ለውጥ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ የማይመልስ በመሆኑ በሕዝብ ቁጣ ከስልጣናቸው ተራርገው ከመወገድ እንደማይድኑ
ብዙዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።
Ø
ትናንት ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ማታ በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ አንድ
በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆቴል እና በአካባቢው ባለው ቡና ቤት ውስጥ
የታጠቁ
ኃይሎ ጥቃት ሰንስዘረው በርካታ ሰዎች አግተው እንደነበር ተዘግቧል። ሰዎችን ለማስፈታት በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የ18
የተለያዩ አገሮች ዜጎች የሆኑ 23 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ከሞቱቱ ውስጥ አራቱ ታጣቂዎቹ መሆናቸው ታውቋል።
በእስላማዊ ማግረብ የአልቃይዳ ክንፍ እየተባለ
የሚጠራው አሸባሪ ቡድን ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። በቅርቡ የተመረጡት የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ቅዳሜ ጠዋት በቦታው ተገኝተው
በሰጡት መግለጫ 150 የሚሆኑ ታጋቾችን ከታጣቂዎች ነጻ ለማድረግ የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል። የቡርኪና የጸጥታ ኃይሎችን
በመርዳት በአካባቢው የሚገኙ የፈረንሳይ ወታደሮች የተሳተፉ ሲሆን የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት አሸባሪዎቹ የወሰዱትን እርምጃ ኮንነዋል።
ከሁለት ወር በፊት በማሊ ዋና ከተማ በማኮ ተመሳሳይ ጥቃት ተፈጽሞ 19 ቱሪስቶች መገደላችው ይታወሳል። በሌላ ዜና ዛሬ ሌሊቱን
በበቡርኪና ፋሶ እና በማሊ ወሰን አካባቢ በሚገኝ ቦታ ላይ የኦስትሪያ ዜጎች የሆኑ አንድ ዶክተርና ባለቤቱ ተጠልፈው የተወሰዱ
መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል። አጋቾቹ እነማን እንደሆኑና ወዴት እንደወሰዷቸው የተገኘ መረጃ የለም።
Ø
በታይዋን ፕሬዚዳንቱን ለመምረጥ በተደረገ ብሔራዊ ምርጫ ዴሞክራቲክ ፕሮግሬሲቭ
ፓርቲ የተባለው ድርጅት መሪ የሆኑት ሚስስ ሳዪ ከፍተኛ ድምጽ አግኝተው በመመረጣቸው ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሴት ፕሬዚዳንት
ሆነዋል። ዴሞክራቲክ ፕሮግሬሲቭ ፓርቲ የተባለው ድርጅት አንድ ቻይና የሚለውን የሚቀበልና ነጻነትን የሚደግፍ በመሆኑ በቻይናና
በታይዋን መካከል የሚኖረው ግንኙነት ውጥረት የሞላበት ሊሆን እንደሚችል ብዙዎች ይገምታሉ። የቻይና ባለስልጣኖች ታይዋን የቻይና
ግዛት ናት በማለት የሚከራከሩ ሲሆን
ታይዋንን ወደ ቻይና ክልል ለማስገባት ኃይልም ጭምር
ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
Ø
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በብሩንዲ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድረገዋል
ተብለው በቁጥጥር ስር የሚገኙ ከፍተኛና ዝቀተኛ መኮንኖች በ30 ዓመት እስራት እንዲቀጡ አንድ የብሩንዲ ፍርድ ቤት ትናንት አርብ
ጥር 6 ቀን 2008 ዓም ፍርድ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። የመፈንቅለ መንግስት ሙከራው መሪ ሳይያዙ ያመለጡ መሆናቸው የሚታወስ
ሲሆን ቅጣቱ የተበየነው የእሳቸው ምክትል በሆኑ
በሶስት የጦር ጄኔራሎችና በአንድ የፖሊስ ጄኔራል ላይ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ዘጠኝ የበታች ሹማንቶች በተመሳሳይ መልክ የ30
ዓመት እስራት ተበይኖባቸዋል። በተከሳሾቹ ላይ የቀረቡት ክሶች
የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርጋችኋል፤ ወታደሮችን
ፖሊሶችንና የሲቪል ሰዎችን ገድላችኋል ንብረቶችን አውድማችኋል
የሚሉ
ሲሆን በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ተብለዋል። ተከሳሾቹ ከእስራቱ በተጨማሪ ለ 10 አመት ያህል የመንግስት ስራ ላይ በኃላፊነት
እንዳይቀመጡ የታገዱ ሲሆን ሌሎች ዘጠኝ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የበታች ሹሞች በአምስት የእስራት ዘመን እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ
ወስኗል።
ጥር 6 ቀን 2008
ዓ.ም
Ø
ከትናንት ከጥር 5 ቀን 2008 ዓም ማምሻ ጀምሮ በአምቦ ከተማ ሰላማዊ ዜጎች በታጠቁ ኃይሎች እየታፈሱ ወደ እስር
ሲጋዙ
እንደነበር የተመለከቱ የአይን እማኞቸ ዛሬ ጥር 6 ቀን 2008
ዓም ረፋድ ላይ የአግአዚ ወታደር በሰላማዊ ሰዎች ላይ ሲተኩስ
የነበረ መሆኑን ገልጸዋል። የተኩሱ መንስዔ በፖሊስ ጥይት
ጭንቅላቱን ተመቶ በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምና ሲደረግለት የቆየውና መዳን ባለመቻሉ ህይወቱ ያለፈውን አብደታ ኦላንሳ የተባለውን
ወጣት አስከሬን ለመቅበር በተሰባሰቡ ሰዎች ሳቢያ የተሰባሰቡ ሰዎችን ለመበተን የተደረገ መሆኑን የአይን እማኞቹ ጨምረው
ገልጸዋል። በከተማ ነዋሪዎች መከካል በተለይ በጨለማ
የሚደረገውን ግንኙነት ለማቋረጥ በዛሬው ቀን በአምቦ
ከተማ መብራት ሙሉ በሙሉ የጠፋ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በነበረውም ተኩስ ሁለት ሰዎች ሳይቆስሉ እንዳልቀሩ ተገልጿል። በትናንትናው
ዕለት በባሌ፤ በሐረር በሻሽመኔና እንቅስቃሴዎች የነበሩ ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ተዘግተው ውለዋል።
Ø
በአዲስ አበባ ከተማ የመብራት መጥፋት በተደጋጋሚ ሲከሰት መቆየቱ የታወቀ ቢሆንም ከቅርብ ቀናት ወዲህ ግን በእጅጉ የተባባሰ
መሆኑንና ከወትሮው በተለየ ሁናቴ በአንድ ሰፈር ውስጥ ከቤት ቤት እየነጠሉ ማጥፋት የተጀመረ መሆኑ ታውቋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስልክና የውሃ አገልግሎቶች
አብረው የሚጠፉበት ሁኔታ እየተለመደ በመምጣቱ በተለይ
በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ስራቸውን ለማካሄድ በእጅጉ መቸገራቸውን ለማወቅ ተችሏል።
አካባቢዎችን በዞን በመክፈል ወይም ከመንገድ በታች እና ከመንገድ
በላይ በማለት የፈረቃ ፕሮግራም ወጥቶ በቅድሚያ ቢነገረን ቁርጡን ማወቅ እንችል ነበር የሚሉት ነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት
ከግዜ ወደ ግዜ መሻሻል ሳያሳይ መቆየቱ አንሶ የአሁኑ የተለየና
የባሰበት በመሆኑ ተስፋ አስቆራጭ የሆነበት ደረጃ ላይ አድርሶናል ሲሉ ተሰምተዋል።
Ø
በደቡብ ሶማሊያ ኤል አዲ በምትባለው ከተማ ውስጥ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ጦር ሰፈር ላይ የአልሸባብ
ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰው የጦር ሰፈሩን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት መሆናችውን የቡድኑ ቃል አቀባይ ገልጿልዋል። ቃል አቀባይ
በተጨማሪ በሰጠው መግለጫ በጦር ሰፍሩ የነበሩት ከ60 በላይ የሚሆኑ የኬኒያ ወታደሮችም የተገደሉ መሆናችውን
አስረድቷል። የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢብሲ የዜና ወኪል በሰጡት መረጃ የአልሸባብ ወታደሮች በከተማዋ ውስጥ ሰንደቅ ዓላማቸውን
ያውለበለቡ መሆናቸውንና የሞቱ ወታደሮችን አስከሬን እያዞሩ ሲያሳዩ እንደንበር ገልጸዋል። የኬኒያ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ዜናውን
አስተባብሎ ጥቃቱ የተፈጸመው በኬኒያ ወታደሮች ላይ ሳይሆን በአካባቢው በነበሩ በሶማሊያ መንግስት ወታደሮች መሆኑንና ከሁለቱም
በኩል ምን ያህል ሰው እንደሞተ ያልታወቀ እንደሆነ ገልጿል። በከተማው ነዋሪ የሆኑ የአይን እማኞች እንደገለጹት ከንጋቱ አስራ
አንድ ሰዓት ተኩል ላይ በካምፕ አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የፈንጅ የመሳሪያ ድምጽ መስማታቸውንና
በርካታ ወታደራዊ መኪናዎች ሲቃጠሉ ማየታቸውን ገልጸዋል።
Ø
የአለም የጤና ድርጅት ሐሙስ ጥር 5 ቀን 2008 ዓ.ም
ላይቤሪያ ከኢቦላ ነጻ መሆኗን አረጋግጦ የምዕራብ አፍርካ አገሮች ከኢቦላ ነጻ ናቸው በማለት የማረጋገጫ ምስክርነት ቢሰጥም
ድርጅቱ መግለጫውን በሰጠ በሰዓታት ጊዜ ውስጥ አንድ የሲየራ ሊዮን ዜግነነት ያለው ግለሰብ በኢቦላ በሽታ መሞቱን የአገሪቱ
ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ግለሰቡ የሞተው በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ቢሆንም በሟቹ አስከሬን ላይ በተካሄድው ምርመራ የሞተው በኢቦላ
በሽታ መሆኑ ተረጋግጧል። ሲየራ ሊዮን ከሁለት ወር በፊት ከኢቦላ ነጻ ናት ተብላ ማረጋገጫ የተሰጣት የሚታወስ ሲሆን የምርመራው
ውጤት የኢቦላ በሽታ ከአካባቢው ገና ያልጠፋ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኃላፊ ሚስተር ዘይድ ራአድ አልሁሴን ዛሬ አርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም በሰጡት
መግለጫ በብሩንዲ በንጹሃን ሰዎች ላይ እየደረሰ የሚገኘው ግፍና በደል በጣም ያሳሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በርካታ ሴቶች
በወታደሮች መደፈራቸውን፤ በጎሳ ልዩነት ሰዎች መገደላቸውንና ብዙዎች በወታደሮች ተጠልፈው የደረሱበት የማይታወቅ መሆኑን እንዲሁም
በተለያዩ ቦታዎች የጅምላ መቃብሮች የተገኙ መሆናችውን የሚጠቁሙ መረጃዎች እንደደረሳችው ገልጸዋል።
በታኅሣሥ
ቀን 2008 ዓም በሶስት ወታደራዊ ካምፖች ላይ በተደረገው ጥቃት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 130 መድረሱ የተገለጸ ሲሆን
ይህንን ጥቃት አስመልክቶ ተመድ የሳይትላይት ስዕሎችን በመመልከትና ሁኔታውን የተመለክቱትን የዓይን እማኞች በመጠየቅ ምርመራ
የሚያካሂድ መሆኑን ገልጿል። ለዚህ ጥቃት የአጸፋ ምላሽ በሚል
የመንግስት ወታደሮች በዜጎች ላይ እያደረሱ ያሉት አሰቃቂ ድርጊቶች ግን በጣም አሳስቢ
መሆኑን የድርጅቱ ኃላፊ ገልጸዋል። ፖሊሲች እና ወታድሮች በየቤቱ
በመግባት ሴቶችን ከቤተሰቦቻቸው በመለየት አስገድደው እንደሚደፍሩና እንዲሁም ወጣት ወንዶች እየመረጡ
የማሰቃየት ምርመራ እንደሚያካሄዱባቸውና ሌሎችን እንደሚገድሉ
መረጃ የደረሳቸው መሆኑን አስረድተዋል። በደል እየደረሰባችው ያሉት የቱሲ ጎሳዎች መሆናችውን ገልጸው ሁኔታው ከተባባሰ በሁቲ እና
በቱሲው መካከል ከፍተኛ እልቂት ሊያስከትል የሚችል ግጭቶች ሊጀመሩ እንደሚችሉ በመግለጽ ስጋታቸውን ተናግረዋል።
Ø
በትናንትናው ዕለት በኢንዶኔዥያ ዋና ከተማ ጃካርታ ውስጥ በአንድ አካባቢ አሸባሪዎች ያደረሱትን ጥቃት ያቀነባረው ባህሩን ናይም
የተባለው ግለሰብ መሆኑና ከዚህ ጋር በተያያዘ ሶስት ሰዎች መያዛቸውን ፖሊሶች ገልጸዋል። ከተያዙት ሰዎች ውስጥ አንደኛው ቦምብ
በመስራት የሰለጠነ ሲሆን ሁለተኛው የመሳሪያ እውቀት ያለው ሶስተኛው ደግሞ የሃይማኖት አስተማሪ መሆኑ ታውቋል። ባህሩን ናይም
ከአራት ዓመት በፊት ያልተፈቀደ መሳሪያ በመያዝ ለአንድ ዓመት ታስሮ የተለቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከአይሲስ በሚደርሰው ገንዘብ
በደብብ ምስራቅ እሲያ የአሲስ ደጋፊ የሚሆኑትን ለማሰባሰብ ጥረት እያደረገ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። በጃቫ ባህረ ሰላጤም
ከሐሙሱ ጥቃት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገልጿል። በትናንትናው ዕለት በደረሰው አደጋ ሰባት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና
ከ20 በላይ መቁሰላችው ሲገለጸ ከሞቱት መካከል አምስቱ አሸባሪዎች ሲሆኑ አንድ የካናዳ ዜግነት ያለው ግለሰብና አንድ
የኢንዶኔዚያ ዜጋ በፍንዳታው ሞተዋል።
ጥር 5 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የወያኔ ባለሟልና አገልጋይ የሆነው ኦህዴድ የአዲስ አበባው ማስተር ፕላን እቅድ የተሰረዘ መሆኑን ቢናገርም
ወደ 200 የሚጠጉ ዜጎች ሳይሞቱ አይቀሩም የሚባልለትና ከአምስት
ሺህ በላይ የሚሆኑት ለእስራት የተዳረጉበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መልኩን ለውጦ እየተካሄደ መሆኑን
ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱት ዘገባዎች ያስረዳሉ::
በሀሮማያ፤ በምዕራብ ሀረርጌ፤ በድሬዳዋ፤ በጅማ፤ በአርሲ የተለያዩ ቦታዎች፤ በአምቦ እና በሌሎች ቦታዎች በተማሪዎች ፊት
አውራሪነት ተጠናክሮ የቀጠለው ሕዝባዊ ተቃውሞ በግፍ የታሰሩት ባስቸኳይ እንዲፈቱ እና በአግአዚ ጥይት ተመትተው የተገደሉት
ወገኖች ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን
ለማወቅ ተችሏል። ትናንት ጥር 4 ቀን 2008 ዓ/ም በአምቦ
በተማሪዎች በተካሄደ የተቃውሞ ስልፍ ላይ የአግአዚ ወታደሮች በተኮሱት ተኩስ አንዷ ተማሪ ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ ሌላዋ
በጽኑ መቁሰሏን መረጃው ያመለክታል።
በሀሮማያ ህዝባዊ ተቃውሞ ተጠናክሮ የቀጠለና ተማሪዎች ትምህርት
አቁመው የቆዩ ሲሆን ሲቪል በለበሱ የደህንነት ኃይሎች ወጣቶች እየታፈኑ ወደ
እስር ቤት ሲጋዙ መዋላቸውን የአይን እማኞች ያስረዳሉ።
በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ አመጽ አነሳስተው ተሰውረዋል የተባሉ ወጣቶችን
ለመከታተል የደህንነት ኃይሎች ገንደ ቆሬ በተባለው ሰፈር ቤት ለቤት አሰሳ ለማድረግ ወደ ስፍራው መንቀሳቀሳቸውን ዛሬ ማለዳ
ከስፍራው የመጣ ዘገባ አጋልጧል። በአርሲ ኮፈሌ ከተማ ሁለት ሰዎች በአግአዚ ወታደሮች ድብደባ ክፉኛ ተጎድተው ለህክምና ተወሰዱ
ቢባልም ወደየትኛው የህክምና ተቋምና ከእነማን ጋር እንደሄዱ አለመታወቁን የአይን እማኞች የተናገሩ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
በተያያዘ ዜና በሕዝባዊ ተቃውሞው ከአግአዚ ቅልብ ወታደሮች በተተኮሰ ጥይት የቆሰሉና ለህክምና አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ
ሆስፒታል ተኝተው ከነበሩ ቁስለኛ ተማሪዎች መካከል ሁለቱ እግራቸው እንዲቆረጥ በተወሱኑ ሀኪሞች ሀሳብ የቀረበ መሆኑና በሀሳቡ
ላይ ሀኪሞቹ መለያየታቸውን የሆስፒታል ምንጮች ተናግረዋል።
ከአምቦ ዩኒቨርስቲ እንደመጡ የሚነገርላቸው በጥይት የቆሰሉ ሁለት
ተማሪዎች በእግራቸው ላይ በደረሰው የከፋ ጉዳት ምክንያት እግራቸው ካልተቆረጠ በህክምና ሊመለስ የሚችል አይደለም የሚል ሀሳብ
በአንዳንድ ሀኪሞች ቢገፋም በሌሎች ሀኪሞች በኩል ከፍተኛ ህክምና ለማድረግ አንድ እድል ይሰጥ የሚል ሀሳብ ስለተገፋ ምናልባት
እግራቸው ሳይቆረጥ በረዥም ጊዜ ህክምና በከፊል ሊድኑ ይችሉ ይሆናል የሚለው
ግምትና ተስፋ በቤተሰቦቻቸው ላይ የተፈጠረ መሆኑ ታውቋል።
Ø
የወያኔው ሌላ ተልላኪና አገልጋይ የሆነው ብአዴን ለሶስት ተከታታይ ቀናት
ባህርዳር ላይ ባደረገው ስብሰባ የእርዳታ እህል እየሸጡ ለራሳቸው ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ እና ሌሎች በደል አድርሰዋል የተባሉ
የድርጅቱ አባላት የሆኑ የቀበሌ የወረዳና የዞን ሹማምንት እንዲታሰሩ መወሰኑና ውሳኔውም ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ታወቀ።
በሙስናና በመልካም አስተዳደር ችግር ተወንጅለው እስካሁን ድረስ
የታሰሩት በቀበሌ፤ በወረዳና በዞን የተሰማሩ የብአዴን
ሹማምንቶች ቁጥር እስከ መቶ ሰማንያ አምስት የሚደርስ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። የወያኔ አገልጋይ በመሆኑ የአገርና የሕዝብ ሕዝብ
ሀብት ሲያዘርፉ የቆዩትና ራሳቸውም በከፍተኛ ዝርፊያ ውስጥ የተሰማሩት የብአዴን ባለስልጣኖች አንድ ቀን በሕዝብ አመጽ ማዕበል
ተጠራርገው መቀመቅ መግባታቸው የማቀር መሆኑ ግልጽ ሲሆን በአሁኑ በትናንሾቹ ላይ ይህን እርምጃ የተወሰደው የሕዝብን ቁጣ
አቀዝቅዞ ከማዕበሉ ለመዳን ነው የሚል አስተያየት የሚሰነዝሩ በርካታ ናቸው።
Ø
ሰሞኑን ሲካሄድ የነበረውና ነገ ጥር 6 ቀን 2008 ዓም
ይጠናቀቃል የተባለው በአዳማ/ናዝሬት ከተማ የተጀመረው የደህንነት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ስብሰባ በከፍተኛ
ጥበቃ ስር እየተካሄደ መሆኑ ታውቋል። የስብሰባው አጀንዳ
ሆኖ ውይይት ከሚካሄዱባቸው ጉዳዮች መካከል በተማሪዎች ግንባር ቀደምትነት የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ በተመለከተ መመከትና
መከላከል ስለሚቻልበት እና እንዲሁም ከበስተጀርባ ያሉትን ኃይሎች
አድኖ ለመያዝ መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ላይ ሲሆን
በስብሰባው መጀመሪያ ላይ በተደረገው ውይይት ለመከላከል
የተወሰደው እርምጃ ከመጠን ያለፈ የበዛ በመሆኑ መቆም ይኖርበታል የሚለው አስተያየት በመሰንዘሩና ድጋፍ በማግኘቱ ከመሰብሰቢያው
አዳራሽ ውጭ ተራ አባላት በተለየ ጥበቃና ክትትል እንዲቆዩ መደረጉን ከቦታው የተገኘ መረጃ ይገልጻል። ስለ ስብሰባው ዝርዝር
ሁኔታ እንደደረሰን እናቀርባለን።
Ø
አለበቂ ጥናትና ዝግጅት ወያኔ በአባይ ላይ የሚገነባውን ግድብ አስመልክቶ በወያኔ በሱዳንና በግብጽ መካከል ውይይቶች
ሲካሄዱ የነበሩ ሲሆን በቅርቡም ካርቱም ላይ መሰብሰባቸው ይታወቃል። ወደ ግብጽ የሚፈሰው የአባይ ውሃ እንዳይቀንስ ውሃውን
ከግድቡ የሚያስወጡ ተጨማሪ ግድቦች እንዲሰሩ ግብጽ የጠየቀችውን ጥያቄ
የወያኔ አገዛዝ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ታውቋል። የወያኔ ባለስልጣኖች ግድቡ መጀመሪያም ሲሰራ በቂ ውሃ ከግድቡ
እንዲወጣ ታስቦ በመሆኑ ተጨማሪ የውሃ ማስወጫ ቱቦዎች መስራት
አያስፈልግም በማለት የግብጽን ጥያቄ ውድቅ አድርጓል። የግብጽ
ባለስልጣኖች ወያኔ የሚሰራው ግድብ ወደ ግብጽ የሚሄደውን ውሃ በከፍተኛ ደርጃ ይቀንሳል የሚል ጽኑ እምነት ያላቸው መሆኑ የታወቀ
ሲሆን ለጥያቄያቸው በወያኔ በተሰጠው የእምቢተኛነት መልስ ምክንያት ምን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ አልታወቀም።
Ø
የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ መንግስት ስደተኞች ተጠልለው የነበሩበትን ካምፕ በሃይል በማፍረሱና ሴቶችንና ህጻናትን ጨምሮ
በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን ከቦታው ማባረሩን አስመልክቶ በባልስልጣኖቹ
የተወሰደው ርምጃ ሰብአዊነት የጎደለውና ተቀባይነት የሌለው የሚወገዝ ድርጊት ነው በማለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ
እርዳታ ጉዳይ አስተባባሪ ኃላፊ ኮንነውታል። በካምፕ ውስጥ የነበሩት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች በገፍ እንዲባረሩና ወደ ካምፑ
እንዳይደርሱ መደረጋቸው የጅምላ ቅጣት ተብይኖባቸዋል
በማለት ወቀሳቸውን አሰምተዋል። የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ባለስልጣኖች የስደተኞችን ማረፊያ ሰፈር ዘግተው ሰዎችን ያባረሩት
በካምፑ ውስጥ መሳሪያዎች ተገኝተዋል በሚል ምክንያት ሲሆን ተመድ
ስደተኞቹ ወደ ሌላ ካምፕ እስኪዛወሩ ድረስ ጊዜ እንዲሰጠው ያቀረበውን ጥያቄ ባለስልጣኖቹ ሳይቀበሉት ቀርተዋል።
Ø
በዚምባብዌ መንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኘው ሄራልድ የሚባለው ጋዜጣ ዛሬ ጥር 5 ቀን 2008 ዓም
ባወጣው እትሙ ለረጅም ጊዜ በስልጣን ላይ የቆየቱ የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ሲንጋፖር ውስጥ በህክምና ላይ ሳሉ አርፈዋል በሚል የተሰራጨው ዜና ሀሰት ነው በማለት በይፋ
ያስተባበለ መሆኑ ታወቀ። በየአመቱ የፈረንጆቹ አዲስ አመት በመጣ ቁጥር የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት አርፈዋል የሚለው ዜና የሰለቸ
ውሸት መሆኑን የመንግስቱ ጋዜጣ ጠቅሶ ባሁኑ ወቅት ፕሬዚዳንቱ
በህይወት መኖራቸውንና
በሩቅ ምስራቅ የእረፍት ጊዜያቸውን እያሳለፉ መሆናቸውን ገልጿል።
የ91 ዓመቱ ሮበርት ሙጋቤ ከ1972 ዓም ጀምሮ በስልጣን ላይ የሚገኙ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በወሰዷቸው አቋሞችና እርምጃዎች
ምክንያት በርካታ የምዕራብ አገሮች በጠላትነት የሚመለከቷቸው መሆኑ ይታወቃል።
Ø
ዛሬ ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም በኢንዶኔዢያ ዋና ከተማ
ጃካርታ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የቦምብ ፍንዳታና የተኩስ ጥቃቶች
ተካሂደው ሰባት ሰዎች መገደላቸውንና ከሃያ በላይ መቁሰላችውን የኢንዶኔዢያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ከተገደሉት መካከል
አምስቱ ጥቃቱን ያደረሱ ግለሰቦች መሆናችው ሲታወቅ ለጥቃቱ አይሲስ የተባለው ቡድን ኃላፊነትን ወስዷል ተብሏል። የኢንዶኒኒዢያ
ባለስልጣኖች ጨምረው በገለጹት መረጃ መሰረት የዛሬው የሽብር እቅድ የተቀነባበረው የአይሲስ አባል ሆኖ በአገሪቱ ውስጥ የሽብር
ተግባሮችን ሲያካሂድ በነበረውና አሁን ሶሪያ ውስጥ በሚገኘው ባህሩን ናይም በተባለው ግለሰብ አማካይነት መሆኑን ገልጸዋል። ጥቃቱ
ኢላማ ያደረገው የጸጥታ እና የፖሊስ ኃይል አባላት ላይ ሲሆን በፍንዳታው የፖሊስ መኪናዎች መጎዳታቸው ታይቷል። እስካሁን
ከተገኘው መረጃ የተጎጅዎች ቁጥር በትክክል ያልታወቀ ሲሆን ምን አልባትም ከተሰጠው ቁጥር ከፍ ያለ ሊሆን እንደሚችል ብዙዎቹ
ይገምታሉ። በፍንዳታው ምክንያት 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች
የሚገኙባት የጃካርታ ከተማ ስትሸበር የዋለች መሆኑ ተነግሯል።፡
ጥር 4 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የሕዝቡ አመጽና እንቅስቃሴ እየተቀጣጠለ መሆኑን በማየትና
እየተጠናከረ ከሄደ ለስልጣኑ አስጊ መሆኑን በመረዳት ስጋት
ላይ የወደቀው የወያኔ አገዛዝ በአገልጋዩ በኦህዴድ አማካነይነት በዜና ማሰራጫዎች
ባሰራጨው መግለጫ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሙሉ በሙሉ የተሰረዘ መሆኑን ገልጿል። የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ
በአዳማ/ናዝሬት ባካሄደው የሶስት ቀን ስብሰባ ሰፊ ውይይት አካሂዶ የማስተር ፕላኑ እቅድ እንዲስረዝ ውሳኔ አስተላልፏል በማለት
የወያኔ መገኛኒያ ብዙሃን ዘግቧል። ቀደም ብሎ ወያኔ
የሕዝቡን አመጽ ለማቀዝቀዝ የሚችል መስሎት ማስተር ፕላኑ ሕዝቡ ሳይስማመበት በስራ ላይ አይወልም የሚል ተማጽኖ በተደጋጋሚ
ሲያሰማ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የወያኔ ውሸት የሕዝቡን አመኔታ ባለማግኘቱ አመጹ ተጠናክሮ ሲያካሄድ ቆይቷል። ከ200
በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በወያኔ አግአዚ ጦር የተጨፈፉበትም አመጽ መነሻ
የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም ይሁን እንጅ ሕዝቡ እየተገደለም እየቆሰለም እየታሰረም
በምሬት አመጹን የቀጠለው የወያኔን አስከፊ አገዛዝ
በመቃወም በመሆኑ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተሰርዟል የሚለው
የወያኔ መግለጫ የሕዝቡን ብሶትና አመጽ አይቀንሰውም የሚሉ በርካታ ናቸው። የወያኔ አገዛዝ ሳይወገድ በቀላሉ ሊበርድ የሚችልበት
ሁኔታ በአሁኑ ወቅት የማይታይ ሲሆን እንዲያውም አድማሱ ሰፍቶና
ወደሌሎች ስፍራዎች ተዛምቶ ሊቀጥል ይችላል የሚል ግምት አለ።
Ø
በኢትዮጵያ የገባው ረሃብ ከፍተኛ እልቂትን ሊፈጥር የሚችል
መሆኑን የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ያሳሰቡ መሆናቸውን ክርሲያቲያን ሳይንስ ሞኒተር የሚባለው ጋዜጣ በአምዱ ላይ አስፍሮ አውጥቷል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ በአለም
የምግብ ፕሮግራም መሰረት በኢትዮጵያ ከገባው ድርቅና ረሃብ ጋር
ተያይዞ ርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች በሶስት እጥፍ የጨመረ መሆኑን ገልጸው እስካሁን
ለእርዳታ ይውላል የተባለው ገንዘብ ከሚያስፈልገው አምስት ከመቶ
ብቻ ነው ብለዋል። ክርሲያን ኤድ የተባለው አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት ኃላፊ
በበኩላችው በሰጡት መግለጫ ደግሞ በሁለት ተከታታይ የመከር ወቅቶች በደረሰው የዝናም እጥረግ ምክንያት
በርካታ አርሶ አደሮች ምርት ለማምረት ያልቻሉ መሆናቸውን ገልጸው በተዘዋወሩበት ቦታዎች ከ10 ሺ በላይ የሚሆኑ
ከብቶችና የቤት እንሳስዎች መሞታቸውን የተመለከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከ250 እስከ 700 የሚደርሱ ወረዳዎች በድርቁ
ተጎድተዋል ካሉ በኋላ ባሁኑ ወቅት እርዳታው ካልደረሰ ከፍተኛ የሆነ
እልቂት ሊከተል ይችላል በማለት ፍራቻቸውን ገልጸዋል።
Ø
በጎንደር ክፍለ ሀገር በአዲስ ዘመን ከተማ ከ34 አመት
በፊት ተሰርቶ የነበረውን ንጹህ የመጠጥ ውሃ ማስረጫን በዘመናዊ መልክ ለማስፋፋት
በሚል ሽፋን 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበት የተሰራውና
በሃምሌ ወር 2007 ተመርቆ የነበረው የውሃ ማሰራጪያ ተበላሽቶ
ስራውን ያቆመ መሆኑን ከአካብቢው የደረሰን ዘና ይገልጻል። ከከተማው አካባቢ በሚደርሰው መረጃ
በከተማዋ የመጠጥ ውሃ ባለመኖሩ ነዋሪዎች በባጃጅ ተጉዘው ውሃ እየገዙ ለመጠጣት የተገደዱ መሆኑ ታውቋል። ለውሃ
ማሰራጫው ወጣ ከተባለው አርባ ሚሊዮን ብር ውስጥ አብዛኛው በባእዴን ባለስልጣኖች የተመዘበረ መሆኑን ውስጠ አዋቂ ምንጮች
ይናገራሉ።
Ø
በየአመቱ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ሕዝቡ በተለይም
ወጣቶች የሚደርስባቸውን በደል በመዘርዘር አገዛዙን በተደጋጋሚ ሲያወግዙ መቆየታቸው ይታወሳል። የጥምቀት በዓል በመጣ ቁጥር
ለወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ራስ ምታት ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ዘንድሮ በሚደረገው የጥምቀት በዓል ዜጎች ከፍተኛ ተቃውሞ ሊያሰሙ
ይችላሉ የሚል ስጋት በጸጥታ ኃይሎች አካባቢ የተፈጠረ መሆኑና ይህንንም ለመቋቋም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከጸጥታ
ሃይልች አካባቢ ከተገኘው ዜና መረዳት ተችሏል። በበዓሉ
ላይ ወጣቶች ምን አይነት ቀለም ያለው ካናቴራ እያዘጋጁ እንደሆነ በካናቴራዎቹ ላይ የሚያጻፉት ጥቅሶች
ምን እንድሆኑ ለማወቅ ፖሊሲች ጥረት እያደረጉ መሆኑንም ለማወቅ
ተችሏል።
Ø
ባለፈው ጥቅምት ወር በእስራኤል አገር በጸጥታ ኃይሎች
በጥይት ከተመታ በኋላ ወድቆ በድብደባ ህይወቱ ያለፈውን ኢርትራዊውን ሃብቶም ዘርኦምን የገደሉ አራት እስራዕላውያን ትናንት
ማክሰኞ ጥር 3 ቀን 2008 ዓም ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑ ተነገረ። በክሱ መሰረት የጸጥታ ኃይሎች ተሳስተው ሃብቶምን የመቱት
መሆኑንና ተመቶ በወደቀበት ጊዜም በአካባቢው የነበሩ አንድ ወታደርና ሁለት ሲቪሎች
በጣውላ ደብደው የገደሉት መሆናቸው ተጠቅሷል። ሃብቶም ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ህክምና እየተደረገለት ህይወቱ ያለፈ
መሆኑ ይታወሳል። በእስራኤል ውስጥ 34 ሺ ኤርትራውያን ስደተኞች
የሚገኙ ሲሆን እስካሁን ድረስ የእስራኤል መንግስት ለስደተኞች ጥገኝነት ከልክሎ ቆይቷል።
Ø
ዛሬ ጥር 4 ቀን 2008 ዓም በካሜሩንና በናይጄሪያ ድንበር
አካባቢ በምትገኝ ኮሎፋታ በተባለችው ከተማ በአንድ መስጊድ ውስጥ ሁለት ሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ መስጊድ ውስጥ
በመስገድ ላይ የነበሩ 10 ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውና ከ12 ሰዎች በላይ የቆሰሉ መሆናችውን የአካባቢው አሰተዳዳሪ ለዜና ምንጮች
በሰጠት መረጃ ገልጸዋል። ቦምቡን በማፈንዳት ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም አፈንጅዎቹ
ቦኮሃራም የተባለው አሸባሪ ድርጅት አባል ሳይሆኑ
አይቀሩም የሚል ግምት ተወስዷል። ከተማዋ በቦኮ ሃራም አሸባሪዎች በተደጋጋሚ የተጠቃች ከመሆኗ በላይ በመስከረም ወር ዘጠኝ
ሰዎች በ ታኅሳስ ወር ደግሞ ሰባት ሰዎች በቦምብ ጥቃቶች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።
Ø
ለሁለት አመታት ያህል በምዕራብ አፍሪካ አገሮች የበርካታ
ሰዎችን ህይወት ያጠፋው የኢቦላ በሽታ ባጠቃላይ የተወገደ
መሆኑ በመግለጽ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር ያለው የአለም የጤና ድርጅት ሀሙስ ጥር 5 ቀን ይፋ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ
ይጠበቃል። በታኅሣሥ 2006 ዓም በምዕራብ አፍሪካ በምትገኘው የደቡብ ጊኒ መንደር ውስጥ የፈነዳው የኢቦላ በሽታ ባጭር ጊዜ
የተቀረውን የጊኒ ግዛት፤ ላይቤሪያንን ሲየራ ሊዮንን አዳርሶ ከ11 ሺ ሰው በላይ ገድሏል። በሽታውን ለመቆጣጠር ከፍ ያለ
የገንዘብ ወጭ የተደረገበት ከመሆኑ ባሻገር በርካታ የዓለም ድርጅቶችንና መንግስታትን የጋራ ጥረት ጠይቋል። በሐሙሱ መግለጫ
የኢቦላ በሽታ በላይቤሪያ በመጨርሻ ከታየ 42 ቀን ያስቆጠረ መሆኑን በመግለጽ ባሁኑ ወቅት የኢቦላ በሽታ የተወገደ መሆኑ
ይገልጻል ተብሏል። በሌላ በኩል ቀደም ብሎ በሽታው ተወግዷል የሚል መግለጫ ከተሰጠ በኋላ እንደገና መመለሱን በማስታወስ አሁንም
ቢሆን ዜጎች ራሳቸውን ለመጠበቅ
የሚገባቸውን ጥንቃቄ እንዲወስዱ ምክር የሚሰጥ መሆኑን የላይቤሪያ የጤና ኃላፊ ገልጸዋል።
ጥር 3 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ሰኞ
ጥር
2
ቀን 2008 ዓም
በአዲስ
አበባ
የቤንዚን
እጥረት
ተከስቶ
በርካታ
ማደያዎች
በመኪኖች
ሰልፍ
ተጨናንቀው
መዋላቸው
ታወቋል። ትናንት ተከስቶ የነበረው የቤንዚን እጥረት ምክንያቱ ምን እንደሆን ለጊዜው ባይታወቅም ከማመላለሻ እጥረት ጋር ሳይሆን
አይቀርም የሚል ግምት ብዙዎቹ ይሰጣሉ። የነዳጅ እጥረቱ በትናንትናው እለት የዋጋ ጭማሪ ያላስከተለ ሲሆን እጥረቱ የሚቀጥል ከሆነ
ግን ሽያጩ ወደ ጥቁር ገበያ የሚሄድ ከመሆኑም ሌላ ዋጋው በበኣጭር ጊዜ ውስጥ በእጥፍ ወይም ከዚያ በላይ ሊጨምር እንደሚችል
ተገምቷል።
Ø
ትናንት
ጥር
2
ቀን 2008
ረፋድ
ላይ
ሀረርጌ ውስጥ የምትገኘው
የሀሮማያ
ከተማ
በከፈተኛ
ተከስ
ስትናወጥ
መዋለዋ
ከቦታው የተገኘው መረጃ ይገልጻል።
ወደ
ስፍራው
የገባው የወያኔ
አግአዚ
ወታደር
በሰላማዊ
ሰዎች
ላይ
በከፈተው
ተኩስ
የተወሰኑ ሰዎች
የቆሰሉ መሆናቸውና እንዲሁም በርካቶች
ታፍነው
መወሰዳቸውን
ዜናው ያስረዳል። በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ በሐረርጌ አብዛኛው ቦታ ውጥረት የነገሰ ሲሆን ከድሬደዋ ወደ አወዳይ የሚወስደው
መንግድም ተዘግቶ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ ባሌንና ከፋን ጨምሮ በሌሎች ቦታዎች ተቃውሞ
ተጠናክሮ መቀጠሉን ዘገባዎች ይገልጻሉ።
Ø
በወያኔ መከላካያ
ውስጥ
የኦሮሞ
ተወላጅ
የሆኑ
ከፍተኛ
ወታደራዊ
መኮንኖችን
ለማሰር
ሴራ
እየተጠነሰሰ
መሆኑን
ውስጠ አዋቂ ምንጮች አጋለጡ።
አበየቦታዊ
እየተካሄደ በሚገኘው ሕዝባዊ የተቃውሞ
እንቅስቃሴ
ላይ
እየተወሰደ
ያለው
የሃይል
እርምጃ
ከመጠንና ከገደብ
ያለፈ
ነው
በማለት
ጥያቄ
ያነሱ በርከት ያሉ
መኮንኖች
እንዳሉ ሲታወቅ ከእነዚህ መኮንኖች ውስጥ
አንዳንዶቹን
ቃሊቲ
ከሚገኘው
ሎጅስቲክ
መምሪያ
ናዝሬት
ወደ
ሚገኘው
የሎጂስቲክ
መምሪያ
እንዲዛወሩ
የተደረገ መሆኑ ታውቋል።
ከመከላከያ
ውስጥ በተገኘው መረጃ መሰረት
በቀጣይ
ግምገማ
ጠንካራ ተቃዋሚዎች የሆኑት እየተለቀሙ ከማእረግ
መግፈፍ
እሰከማሰር
ድረስ
በሚዘልቅ
እርምጃ
በመውሰድ ለመቅጣት
የታቀደ መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል
ደግሞ ወያኔ አመጹን በማፈን በኩል ከፍተኛ ሚና ለነበራቸውና ወደ ሌሎች ቦታዎች
ቢዛመት ተገቢ መካለክል ሊያደርጉ ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው መኮንኖች ከፍተኛ የማዕረግ እድገት ሊሰጥ የተዘጋጀ መሆኑ
ተዘግቧል።
Ø
በዛሬው ዕለት በቱርክ ዋና ከተማ በኢስታንቡል ቱሪስቶች በሚያዞትሩበት ቀበሌ
አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ 10 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ሌሎች 15 ሰዎች መቁሰላችው ታውቋል። ከሞቱት መካከል
ስምንቱ የጀርመን ዜጎች ሲሆኑ ከቆሰሉት መካከል ደግሞ ሁለቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል። ቦምቡን ያፈነዳው አጥፍቶ ጠፊ
በ1980
ዓም የተወለደ የሶሪያ ተወላጅ መሆኑን ጉዳዩን የሚመርምሩት የቱርክ የጸጥታ ኃላፊዎች የገለጹ
ሲሆን አይሲስ በሚባለው አሸባሪ ቡድን የተላከ መሆኑ ተነግሯል። በተያያዘ ዜና ሰኞ ዕለት ዕለት በኢራክ ዋና ከታማ በባግዳድ
በተለያዩ ቦታዎች በተካሄዱ ተኩሶችና የቦምብ ፍንዳታዎች ባጠቃላይ 51 ሰዎች የሞቱ መሆናችውንና በርካታዎች መቁሰላችውን በመጥቀስ
የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ባለፈው ሳምንት የኢራክ መንግስት አይሲስ የሚባለውን አሸባሪ ቡድን ከራማዲ
ከተማ አባርሬያለሁ ብሎ መግለጫ መስጠቱ የሚታወስ ሲሆን ትናንት በባግዳድ ላይ
በተከታታይ የደረሱት ጥቃቶች የአይሲስ የአጸፋ እርምጃ ሳይሆን አይቀርም ተብሏል። በአደጋው የቆሰሉት ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ
ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ባለስልጣኖች ተናግረዋል።
Ø
በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለአመታት በተካሄደው የእርስ በርስ ጦርነትና ችግር
7.5 ሚሊዮን የሚጠጉ የአገሪቱ ዜጎች እርዳታ የሚያስፈግልጋቸው መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ሰኞ ዕለት በሰጡት
መግለጫ አስታውቀዋል። ላለፉት 20 አመታት በአገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል የሚገኘውን የማእድን ስፍራ ለመቆጣጠር የተለያዩ ቡድኖች
ያካሂዱት የእርስ በርስ ግጭትና ውጊያ የብዙ ዜጎችን ህይወት ያጠፋ ሲሆን በርካታዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከአንዱ ስፍራ
ወደሌላው ለመሰደድ ተገደዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ ባስከተለው ቀውስ ምክንያት ነዋሪው በምግብ እጥረት በተላላፊ በሽታና
በድኽነት እየተሰቃየ እንደሚገኝ መግለጫው አብራርቷል። ከአገሪቷ ሕዝብ ዘጠኝ ከመቶ የሚሆነው እና ወደ 7.5 ሚሊዮን የሚገመተው
ሕዝብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው የተነገረ ሲሆን
ቢያንስ
አምስት ሚሊዮን የሚሆነው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያጋጠመው ነው ተብሏል። ከአገሪቱ ህጽናት መካከል በቁጥር ግማሽ የሚሆኑት ደግሞ
በከፍተኛ የምግብ እጥረት በሽታ እየተሰቃዩ መሆናቸውን ገልጿል። በኮንጎ ዴሞክራቲክ ረፕብሊክ ለሚገኙ ተረጅዎች ተገቢውን እርዳታ
ለማድረስ በተያዘው አመት 690 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ባለስልጣኖቹ ገልጸዋል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሕጻናት ጉዳይ መስርያ ቤት ዛሬ ጥር 3 ቀን
2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ከስድስት እስከ 15 ዓመት እድሜ ካላቸው የደቡብ ሱዳን ህጻናት ውስጥ
51 ከመቶ የሚሆኑት የትምህርት እደል የተነፈጋቸው መሆኑን ገልጿል። በደቡብ
ሱዳን በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት ከ800 በላይ የሆኑ ትምህርት ቤቶች የወደሙ ሲሆን 400 ሺ የሚሆኑ ተማሪዎች ከየክፍላቸው
እንዲወጡ ተገደዋል። 51 ከመቶ ለሚሆኑት ሕጻናት የትምህርት እድል በመንፈግ በኩል ሱዳን ከአለም አገሮች አንደኛ ስትሆን 47
ከመቶ የሚሆኑት ህጻናት የትምህርት እድል የማያገኙባት ናይጀር ደግሞ ተከታይዋ ሆናለች።
Ø
የአይሲስ አሸባሪዎች ዙየቲና የተባለችውን የሊቢያን የነዳጅ ማከማቻና መላኪያ
ከተማ
ከባህር ላይ ሆነው ለማጥቃት ያደረጉት ሙከራ ከተማውን በሚጠብቁ ወታደሮች ሊከሽፍ
የቻለ መሆኑን ከአካባቢው የተገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። ባለፈው ሳምንት ከተማዋን ለመቆጣጠር የአይሲስ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት
ሁለት ቦምብ 56 ስዎች የሞቱ ሲሆን ባለፈው እሁድ ጥር 1 ቀን 2008 ዓም ከባህር ላይ ሶስት ጀልባዎች ከተማዋን ለማጥቃት
ሲጠጉ በከተማው ጠባቂዎች በተደረገ የአጸፋ ተኩስ አንደኛው ጀልባ ሲመታ ሌሎች ሊያመልጡ የቻሉ መሆናቸው ተገልጿል። በሊቢያ ውስጥ
የአይሲስ እንቅስቃሴ እየተጠናከረ የመጣ ሲሆን የሊቢያን የነዳጅ ክምችት ቦታዎችን ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ ጥረት ማድረጉ ይታወሳል።
ጥር 2 ቀን 2008 ዓም
Ø
ግሎባል ቮይስ ኦን ላይን
የተባለው ድርጅት በቅርቡ በወያኔ አግአዚ ወታደሮች የተገደሉት ዜጎች ቁጥር
ከ140 በላይ መሆኑን ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለውን ድርጅት ዋቢ በማድረግ ጠቅሶ ከእነዚህ
ውስጥ ቢያንስ 10 የሚሆኑት በእስር ቤት በስየል ምርመራ (ቶርቸር) የሞቱ መሆናቸውን
የሚገልጽ መረጃ ያገኘ መሆኑን ዘግቧል።
ከሞቱት ውስጥ
የዩኒቨርስቲ
ተማሪዎች፤ ሴቶች አርሶ አደሮች እና መምህራን የሚገኙበት መሆኑን ዘግቦ 70 ከመቶ የሚሆኑት ወንዶች መሆናቸውን ጠቅሷል። አንዲት
የሰባት ወር እርጉዝ ሴት ከእህቷ ጋር ከአደጋው ለማምለጥ ሲሸሹ መገደላቸው መረጃ የደረሰው መሆኑን በመግለጽ
ድርጅቱ
ባወጣው ዘገባው ላይ ዘርዝሯል። በተያያዘ ዜና በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ ያሉት አመጾች የቀጠሉ መሆናችው ታውቋል። በጅማ
በሃረርጌ ክፍል ሃገር እና በሌሎች ቦታዎች ተማሪዎች የሚያካሂዱትን የተቃውሞ እንቅስቃሴ አጠናክረው መቀጠላችው የሚደርሱን
ዘገባዎች ይገልጻሉ።
Ø
በሞጆ ከተማ
ዙሪያና አካባቢ
የሚገኙ
አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ካሉበት ቦታ
በቅርብ
ግዜ
ውስጥ
የሚፈናቀሉ
መሆናቸውን ሁነታውን በቅርብ የሚያዉቁ ዜጎች አጋልጠዋል።
ነዋሪዎቹም
ሆነ
አርሶ
አደሮቹ
ለሚፈናቀሉበት ምክንያት በይፋ የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም
ለባህር
ትራንስፖርት
ቅርበት
ያላቸው
የታመኑ
ምንጮች
አንድ
ነጥብ
አምስት
ሚሊዮን
ብር
በጀት
የተያዘለት
የደረቅ
ወደብ
ማስፋፊያ
ፕሮጀክት
በቅርቡ በተጠቀሰው አካባቢ የሚጀመር መሆኑን ተናግረዋል።
ከሞጆ
እስከ
ናዝሬት
ያለውን
መንገድ
ተከትሎ
ከመንገዱ በሁለቱም ጎን ያሉ ነዋሪዎችና አርሶ አደሮች
በፕሮጀክቱ
ስራ ምክንያት እንደሚፈናቀሉ ይታወቅ እንጅ
ለተነሺዎቹ
ወይም
ለተፈናቃዮቹ
የተመጣጠነ
የካሳ
ክፍያ የሚደረግ መሆኑ አልታወቀም። በዚህም ምክንያት እንደ አዲስ አበባው ማስተር ፕላን
ይህም ከፍተኛ ተቃውሞ ሊቀሰቅስ ይችላል በማለት ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ወገኖች አስተያየታት ሲሰጡ ይሰማሉ።
Ø
በመልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ ለመወያየት በሚል ምክንያት ዛሬ
ጥር
2
ቀን
2008
በመቀሌ
ከተማ ሲካሄድ የነበረው
ሕዝባዊ
ስብሰባ
በተስብሳቢው
መካከል
ጭቅጭቅና አለመግባባት በመፈጠሩ ለጥር 3 ቀን 2008 ዓም መተላለፉ ታወቋል።
በስብሰባው
ከተገኙት ወደ
ሁለት
ሺህ
ከሚጠጉ ተሰብሳቢዎች
መካከል
አንድ
ሺህ
አምስት
መቶ
የሚሆት
ከመላው
ትግራይ
እስከ
ቀበሌ
ድረስ
የተሰገሰጉ
የወያኔ
አባላት
ሲሆኑ
በስብሰባው መጀመሪያ ላይ በርካታዎቹ ተሰብሳቢዎች
በመልካም
አስተዳደር
እጦት
ዜጎች እየተንገላቱ
መሆናቸውንና
በድርቁ
ምክንያትም
የሚከፋፈውለው
እርዳታ
ፍትሃዊ
ባልሆነ መንገድ እየተፈጸመ መሆኑን በመገልጽ ጠንካራ ስሜታችውን መግለጽ
በመጀመራቸው መድረኩን ይመሩ
ካደሬዎች
ስብሰባውን
በድንገት አቋርጠው ለሚቀጥለው ቀን ለማስተላለፍ ተገደዋል።
Ø
ለወያኔ ባለስልጣኖች ጠርቀም
ያለ ጉቦ በመክፈል ከ100ሽ ሄክታር በላይ የጋምቤላ ለም መሬት ተሰጥቶት የነበረውና በቅርቡ ኮንትራቱ ተሰርዟል የተባለው
የካራቱሪ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ለጋዜጠኖች በሰጠው መግለጫ በዓለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ ያገኘ መሆንና ጉዳዩን በአለም
አቀፍ አደራዳሪዎች አማካይነት በስምምነት እንዲወሰን የጠየቀ መሆኑን ገልጿል።
በወያኔ አገዛዝ በኩባንያው ላይ የተወሰደው እርምጃ ስምምነቱን የሚጥስ እና
ህጋዊ ያልሆነ ውርስና ዘረፋ ስራ መሆኑን ስራ አሲኪያጁ ጠቅሶ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ደረጃ
እንዲያልቅ የሚታገል መሆኑን ተናግሯል። በወያኔ አገዛዝ የተዘረዘሩት ክሶች ከእውነት የራቁ ናቸው ካለ በኋላ ኩባንያው ስራውን
በተገቢው መንገድ ለማካሄድ ያልቻለው ወያኔ ተግባራዊ ባደረጋቸው ማዕቀቦች ምክንያት
መሆኑን
ተናግሯል። የወያኔ ባለስልጣኖች የኩባንያው ምርት ወደ ውጭ እንዳይላክ በመከልከላቸው 180 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ኪሳራ
ያደረሰበት መሆኑና እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት ከሱዳን ነዳጅ እንዳይገባ በመከልከሉ ኩባንያው የሚፈለገውን
ያህል ሊሰራ አለመቻሉን ገልጿል። 100 ሺ ሂክታር መሬት በጉቦ የተሰጠው ካራቱሪ ለተወሰደብት መሬት ካሳ እንዲከፈለው ጠይቋል።
ወያኔ
3.3. ሚሊዮን ሂክታር
የኢትዮጵያን
ለም ቦታዎች በአነስተኛ ገንዘብ ለባዕዳን ባለሃብቶች ለመቸብቸብ አዘጋጅቶ በርከት ያለውን ለባዕዳን ባለሃብቶች የሰጠ መሆኑ
የሚታወስ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለባእዳን ከተሰጡት መካከል ለአገሪቱ ውጤት ያስገኘ አለመኖሩም ተረጋግጧል።
Ø
የሳኡዲ አረቢያ መንግስት
እሁድ ዕለት ያኒት ዳምጤ ፋሪድ የተባለቸውን ኢትዮጵያዊት አንገቷን በመቅላት የግድያ ቅጣት የፈጸመባት መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያዊቷ አሰሪዋን የሳኡዲ ተወላጅ በመጥረቢያ ገድላለች፤ ገንዘብና ወርቅ ሰርቃለች ተብላ የተከሰሰች ሲሆን ያኒት እርምጃውን
መውሰዷን ማመንና አለማመኗን እንዲሁም ስለፍርዱ ሂደትና ማረጋገጫ የተሰጠ ዝርዝር መረጃ የለም። በሳኡዲ ውስጥ የሚኖሩት ስደተኞች
ከፍተኛ ኢሰብአዊ የሆነ በደል እንደሚደርስባቸው በየጊዜው የተገለጸ ሲሆን
እርምጃውን
ወስዳ ከሆነም ይህ ለማድረግ ያስገደዳት የደረሰባት ከፍተኛ በደል ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ታዛቢዎች አሉ።
የሳኡዲው ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ባለፈው የፈረንጆቹ
ዓመት ብቻ ከ155 በላይ የሆኑ ሰዎችን አንገት በመቅላት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ
ቅጣት የፈጸመ ሲሆን በዚህም የአለምን ክብረ ወስን ይዟል በማለት የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ዘግበዋል።
Ø
ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት
በሶማሊላንድ ወደብ አካባቢ በቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በሰጠመው ጀልባ ውስጥ
የነበሩ 119 ስደተኞች መሞታችው የተረጋገጠ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች
እንደሚገኙበት ታውቋል። የወደብ ሰራተኞች የ ሰባ አምስት ሰዎችን ህይወት ያዳኑ ሲሆን የአካባቢው ሰዎች ወደ ወደቡ ተጥርገው
የመጡ
የ 119 ሰዎች
አስከሬኖች አግኝተዋል። ከሞቱትም ሆነ ተርፈው እየታከሙ ከሚገኙት መካከል ኢትዮጵያውን
እንዳሉበት የተረጋገጠ ሲሆን እነማን መሆናችውና ከየት እንደመጡ ለጊዜው የተገኘ መረጃ የለም።
Ø
በሱዳን በምዕራብ ዳርፉር ዋና ከተማ
ቤትና ንብረታቸው በጎሳ ሚሊያሺያዎች የወደመባቸው ዜጎች ከመንግስት መስሪያ ቤት ፊት ለፊት በመሆኑ የተቃውሞ ድምጽ እያሰሙ
በነበሩበት ሁኔታ የጸጥታ ኃይሎች ሰልፉን ለመበተን ባካሄዱት የእሩምታ ተኩስ አራት ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውን ከስፍራው
የደረሰው ዜና ይገልጻል። የመንግስቱ ባለስልጣኖች የተባለቱ አራት ሰዎች መገደላቸውን አስተባብለው ሰልፉን ለመበተን ያስገደዳቸው
ሰልፈኞቹ ሶስት መኪናዎችን በማቃጠላቸው ነው ብለዋል። ከአስራ ሁለት አመት በፊት በዳርፉር በተካሄደው የእርስ በርስ ጦርነት
ከ300 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን 2.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።
Ø
የናይጄሪያ ፕሬዚዳንቱ
የሚስተር ቡሃሪ የቅርብ ረዳትና ተባባሪ እንዲሁም የገዥው ፓርቲ አመራር አባል የሆኑት ሚስተር ላዋል ጃፋሩ ኢሳ በእስር ላይ
ከሚገኙት ከቀድሞ የብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ የተቀበሉትን 500 ሺ ዶላር የሙስና ገንዘብ ያስረከቡ መሆናቸው ተገልጿል። ሚስተር
ኢሳ ባለፈው ሳምንት 850 ሺ ዶላር ወስደዋል በሚል ክስ መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን
ከባለስልጣኖች ጋር በተደረገው ንግግር ስምምነት መሰረት ከወሰዱት ገንዘብ ውስጥ
500
ሺ ውን ብር መልሰው 380 ሺውን ወደፊት ለመስጠት ቃል በመግባት በዋስ የተፈቱ መሆናቸው የአካባቢ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ለቀድሞ የናይጄሪያ ብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ ለሆኑት ለሚስተር ዱሱኪ ቤት ለመግዛት ገንዘቡን መቀበላቸውን አምነው ገንዘቡን
በወሰዱበት ወቅት ከመንግስት ካዝና የወጣ የሙስና ገንዘብ መሆኑን የማያውቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
Contact us:
eramharic@googlegroups.com
ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 ዓም
Ø
አርብ ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም በግብጽ ኸርጋታ በምትባለው ቀይ ባህር ላይ በምትገኝ የወደብ ከተማ
ከአይሲስ ጋር ግንኙነት አላቸው የሚባሉ ሁለት ሰዎች
ቤላ ቪስት በሚባለው ሆቴል ውስጥ የነበሩ ሶስት ቱሪስቶችን በጩቤ ወግተው ማቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ መረጃ
ይገልጻል። ከቆሰሉት ቱሪስቶች መካከል ሁለቱ የአውስትራሊያ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ አንደኛው የስዊድን ዜጋ ነው። ፖሊሶች አንዱ
አሸባሪ የተገደለ መሆኑና ሁለተኛው መቁሰሉን አስታውቀው ሌሎች
መኖርና አለመኖራቸውን ለማወቅ ከፍተኛ ምርመራ እያካሄዱ
መሆናቸውን ገልጸዋል። አሸባሪዎች የአይሲስን ባንዲራ ያውለበለቡ ሲሆን ዓላማቸው ቱሪስቶችን ጠልፎ ወስዶ ለማገት
እንደነበር ታውቋል። የግብጽ መንግስት የሚያደርስባቸውን ተጽእኖ ለመቋቋም ጂሃዲስቶች እየወስዷቸው ካሉ እርምጅዎች
መካከል አንዱ ቱሪስቶችን ማጥቃትና አገሪቷ ከቱሪስት እንቅስቃሴ የምታገኘውን ገንዘብ ማስቀረት ሲሆን ባለፈው ሐሙስም በጊዛ
ፒራሚድ አጠገብ በአንድ የቱሪስት አውቶቡስ ላይ ጉዳት ባያደርሱም ጥቃት መሰንዘራቸው ይታወሳል።
Ø
በሰሜን ምስራቅ ኬኒያ በሚገኘውና ከ350 ሺ በላይ የሶማሌ ስደተኞችን በሚያስተናግደው ዳዳብ ከሚባለው ካምፕ ውስጥ የኮሌራ በሽታ
ተዛምቶ ከ1000 በላይ የሆኑ ሰዎች በበሽታው መታመማቸውንና
እስካሁን አስር ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን የተመድ ባለስልጣኖች ቅዳሜ ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 በይፋ ገልጸዋል። በሽታው በመጀመሪያ
የተከሰተው ከሁለት ወር በፊት መሆኑን ገልጸው ከካምፕ
ውስጥ ክሎሪን በመርጨትና ሳሙናዎችን በማከፋፈል በሽታውን ለማጥፋት ጥረት የተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። በሽታው በተበከለ
የመጠጥ ውሃ አማካይነት የሚተላለፍ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ባለፉት ሳምንታት በከፍተኛ ደረጃ የዘነበው ዝናብ በሽታውን ሊያስፋፈው
እንደቻለ ተናግረዋል። የዳዳብ የስደተኛ ሰፈር ውስጥ ከዛሬ 25 ዓመት በፊት ጦርነትና ረሃብ በመሸሸ የመጡ የሱማሌ ስደተኞች
የሚኖሩበት መሆኑ ይታወቃል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በሰላም አሰከባሪ ተግባር ላይ ተሰልፈው የሚገኙ የኮንጎ ወታደሮች
ባስቸኳይ እንዲወጡ የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስትን የጠየቀ መሆኑን አንድ የድርጅቱ ቃል አቀባይ አርብ ታኅሣሥ 29 ቀን
2008 ዓም አስታውቋል። ተመድ ለወሰደው እርምጃ ምክንያት የሆኑት ጉዳዮች ቃል አቀባዩ ሲዘነዝር የኮንጎ የሰላም አስከባሪ
ኃይሎች በመሳሪያ ጥራት እና ወታደሮችን በጥንቃቄ በመመልመልና በማዘጋጀት በኩል ተመድ የሚፈልገውን ደረጃ የማይመጥኑ ሆነው
በመገኘታቸው እንዲወጡ ተወስኗል ብሏል። ባለፈው ነሐሴ ወር ሶስት የኮንጎ ዴሞክራቲክ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ሶስት
ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ልጃገረዶችን አስገደደው ደፍረዋል ተብለው መከሰሳቸው ይታወሳል። ባሁኑ ወቅት በማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ
ውስጥ ከተሰማሩት 10 ሺ የተመድ
የሰላም አስከባሪ ኃይል መካከል 807 የሚሆኑት የኮንጎ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት መሆናቸውም ይታወቃል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ቅዳሜ ታኅሣሥ 30 ቀን 2008 ዓም በሰጠው መግለጫ ከሞላ ጎደል
ሰላማዊ በነበሩ የደቡብ ሱዳን ግዛቶች ውስጥ ጦርነት በመፋፋሙ ዜጎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው እየተሰደዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ባለፈው ታኅሣሥ ወር ብቻ የምዕራብ ኢኳቶሪያል ከሚባለው ግዛት ውስጥ ጦርነቱን በመሸሽ ከ 23 ሺ ሰዎች በላይ ቤት ንብረታቸውን
ጥለው ወደ ሌሎች ቦታዎች የሄዱና በየጫካው የተሸሸጉ ሲሆን
ከእኒዚህ ውስጥ ስምንት ሺ ያህሉ ወደ ጎረቤት አገሮች የተሰደዱ መሆናቸው ታውቋል። በደቡብ ሱዳን ላለፉት ሶስት ዓመታት ጦርነቱ
ሲካሄድ የነበረው በአገሪቱ ሰሜን ምስራቅ አካባቢ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በምዕራብ ኢኳቶሪያል ግዛት የተለይዩ ሚሊሺያ ኃይሎች
ተመስርተው ከመንግስት ወታደሮች ጋር ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ።
Ø
በሊቢያ 60 የፖሊስ ምልምሎች በተገደሉ ማግስት የአውሮፓው ኅብረት ስምምነት ለተደረሰበት አዲስ መንግስት የ100 ሚሊዮን ዩሮ (
109 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ የሚሰጥ መሆኑን ገለጸ። ይህ በይፋ የተገለጸው የአውሮፓው ኅብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ የሆኑት ሚስስ
ፌዴሪካ ሞገሪኒ ከሊቢያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በቱኒስ ከተማ በሰጡት የጋራ ጋዜጣዊ መገለጫ ላይ ሲሆን ኃላፊዋ ባሁኑ ወቅት
በሊቢያ የሚገኘው የጸጥታ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ መሆኑን ጠቅሰው አሸባሪዎችን ለመዋጋት
የአውሮፓው ኅብረት የመሳሪያና የቲክኒክ እርዳታ ያደርጋል ብለዋል።
Ø
በሚቀጥለው ወር በኡጋንዳ የሚካሄደውን አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ከፍተኛ የሆነ ብጥብጥ ሊነሳ ይችላል በማለት በምርጫው ተወዳዳሪ
የሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አስጠነቀቁ። ፖሊሶች
ደጋፊዎቻችንን እየደበደቡ ነው በማለት ተቃዋሚዎች ሲከሱ የመንግስት ክፍሎች ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሚሊሺያዎችን እያደራጁ ነው
የሚል ክስ እያሰሙ ይገኛሉ። ላለፉት ሰላሳ አመታት በስልጣን ተሰይመው የቆዩትን ፕሬዚዳንት ዩወሬ ሙሰቨኒን ከስልጣን ለማስወገድ
ሰባት የፖሊቲካ ድርጅቶች መሪዎች እየተወዳደሩ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ፕሬዚዳንቱን ሊያሰጉ ይችላሉ የተባሉት ፎረም ፎር ዴሞክራቲክ
ቼንጅ (Forum for Democratic Change) የተባለው ድርጅት መሪ ሚስተር አማማ እምባባዚ ናቸው። እስካሁን ሲደረጉ
በነበሩ የተቃዋሚ ኃይሎች ስብሰባዎች ላይ ፖሊሶች ደጋፊዎቻችንን ደብድበዋል አጉላልተዋል ብለው የድርጅቶቹ መሪዎች
የከሰሱ ሲሆን ምርጫው ሰላማዊ ካልሆነ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሊነሳ እንደሚችል ተንብየዋል። የመንግስቱ ጠቅላይ ሚኒስትር
በሰጡት መግለጫ ደግሞ የግል ሚሊሺያዎችን ያቋቋሙ ኃይሎች መኖራችውን ገልጸው እነዚህ ኃይሎች በምርጫ ከተሸነፉ በአገሪቱ ላይ
ጦርነት ለመክፈት የተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኡጋንዳ የፖሊስ ኃላፊ ግጭትን የሚከላከሉ ቁጥራቸው ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጥ
ሰላማዊ ዜጎች የመለመሉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሁሉም ተወዳዳሪዎች በጥር 4 ቀን 2008 የቴሌቪዥን ክርክር
ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም
Ø
የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ላለፉት ሁለት ወራት ሲካሄድ በቆየው
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ቢያንስ 140 ሰላማዊ ዜጎች
በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች መገደላችውን መቀመጫው አሜሪካ የሆነው የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዎች ትናንት
ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ድርጅቱ በግድያው የወያኔ አገዛዝን አውግዞ በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ
ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። የ54 ዓመቱ አቶ በቀለ ገርባ ታኅሣሥ 13
ቀን 2008 ዓም በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በተያዙበት ወቅት ታመው ለጥቂት ጊዜ ህክምና ሲደረግላቸው ከመታየታቸው ሌላ በአሁኑ
ወቅት ያሉበት ቦታ እንደማይታወቅ ዘገባው ገልጿል።
Ø
ባለፈው ሳምንት ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በተካሄደው ምርጫ የፕርዚዳንቱን የስልጣን ቦታ ለመያዝ
በግልጽ አሸናፊ የሆነ ተወዳዳሪ ባለመኖሩ ሁለተኛ ዙር ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ ተገለጸ። ለምርጫው የሚቀርቡት ሁለቱ ተወዳዳሪዎች
የድምጹን 24 ከመቶ ያገኙት ሚስተር ዶሎጉወሌና የድምጹን 19 ከመቶ ያገኙት ሚስተር ቱዋዴራ ናቸው። ሁለቱም ሰዎች ከዚህ በፊት
በተለያዩ ወቅቶች ያገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል። ሁለተኛው ዙር ምርጫ ጥር 22 ቀን 2008 ዓም የሚካሄድ መሆኑ
የምርጫ ኮሚሽኑ አስታውቋል።
Ø
ዛሬ
ታኅሣሥ 29 ቀን 2008 ዓም የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በመንግስት ራዲዮ በሰጡት መግለጫ ቀደም ብለው በተደረገው
ስምምነት መሰረት 50 የሚሆኑ የምክር ቤት መቀመጫዎችና የተለያዩ የሚኒስትር ስልጣኖች ለአማጽያኑ ክፍሎች የሚሰጡ መሆናቸውን
ገልጸዋል። ሁለቱን ወገኖች ለማስታረቅ የተቋቋመው ኮሚሽን ኃላፊ የሆኑት የቀድሞ የቦትስዋና ፕሬዚዳንት ፌስተስ ሞጌ በሰጡት
ማብራሪያ የመከላከያ፤ የብሔራዊ ጸጥታ፤ የገንዘብ እና የፍርድ
ሚኒስትርን ጨምሮ 16 የሚኒስትር ቦታዎች ለሳልቫኬር መንግስት የሚሰጡ መሆናችውንና
10 የሚኒስትር ቦታዎች ደግሞ ለአማጽያኑ ቡድን የሚሰጡ መሆናቸውን
ተናግረዋል። ለአማጽያኑ ቡድን ከተሰጡት የሚኒስትር ቦታዎች መካከል የነዳጅ ዘይት እና የሰብአዊ እርዳታ ሚኒስትሮች
ይገኙበታል። ቀደም ብለው ተይዘው ለተለቀቁ የፖሊቲካ ሰዎች
የውጭ ጉዳዩ እና የትራንስፖር ሚኒስቴር ቦታዎች የተሰጡ መሆናቸውና የካብኔ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የእርሻ ሚኒስቴር
የስልጣን ቦታዎች ደግሞ ለሌሎች ፓርቲዎች ተወካዮች የተደለደሉ
መሆናቸው ተነግሯል። በስምምነቱ መሰረት የአማጽያኑ መሪ ሪክ ማቻር የዛሬ ሶስት ዓመት የተባረሩበትን የምክትል ፕሬዚዳንቱን ቦታ
መልሰው የሚይዙ ሲሆን በምን ቀን ወደ ዋናው ከተማ መጥተው ስራቸውን እንደሚጀምሩ አልታወቀም።
በደቡብ ሱዳን ከሶስት ዓመት በፊት በተጀመረው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በ10 ሺ የሚቆጠሩ ስዎች ህይወታቸውን
ያጡ ከመሆናችውም በላይ 2.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ከቤት ንብረታቸው የተሰደዱ
4.6 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው መሆኑ ይታወቃል።
Ø
የብሩንዲ
ተጻራሪ ኃይሎችን ለማስታረቅ አደራዳሪ የሆኑት የኡጋንዳ የመከላከያ
ሚኒስትር ትናንትን በሰጡት መግለጫ የእርቁ ድርድር ሁሉን ያካተተ
ሆኖ ጉዳዩ የሚመለካታቸው ክፍሎች በሙሉ መገኘት አለባቸው ብለዋል። በዚህ ሳምንት መጀምሪያ ላይ የብሩንዲ መንግስት ተወካዮች
መፈንቅለ መንግስት ያካሄዱ ሰዎች መገኘት አይኖርባቸው በማለት ውይይቱን ማቋረጣቸው ይታወሳል። የኡጋንዳው መከለከያ ሚኒስትር
ከብሩንዲ መንግስት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆናቸውን ጠቁመው ለዘላቂ ሰላም ማንም ኃይል ከውይይቱ መወገደ የለበትም ብለዋል።
ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ የሚወዳደሩ መሆናቸውን በይፋ መግለጻቸውን ተከትሎ በተነሳው
ተቃውሞ እና የእርስ በርስ ግጭት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መሰደዳቸው ይታወሳል። በግንቦት ወር ተሞክሮ የነበረው መፈንቅለ
መንግስት ቢከሽፍም በየመንገዱ እየተካሄደ ያለው ግጭት እስካሁን ያልበረደ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በቅርቡ
የሺያ እምነት ተከታይ የሆኑትን ሼክ መገደላቸውን ተከትሎ በሳኡዲ አረቢያ መንግስት እና በኢራን መካከል የተካረረ ጠብ መፈጠሩና
ሁለቱ አገሮች በመካከላቸው የዲፕሎማቲክ ግንኙነት ማቋረጣቸው ይታወቃል። ከሳኡዲ ቀጥሎ ባህሬንና ሱዳን ከኢራን ጋር የነበራቸውን
የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያቋረጡ ሲሆን ትናንት ታኅሣሥ 28 ቀን
2008 ደግሞ የሱማሊያ መንግስት ከኢራን ጋር ያለውን የዲፕሎማቲክ ግንኙት ማቋረጡን ገልጾ የኢራን ዲፕሎማቶች በ72 ሰአት ጊዜ
ውስጥ ከአገሩ እንዲወጡ አዟል። የሱማሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ እንደጠቀሰው ርምጃው የተወሰደው ኢራን በተከታታይ በሱማሊያ
የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባቷ ምክንያት ነው ብሏል። ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይህ ለምክንያት የተሰጠ እንጅ ሱማሊያ
ሱዳንና ባህሬን ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲያ ግንኙነት ለማቋረጥ የወሰዱት እርምጃ ከሳኡዲ የገንዘብ ማባብያና ተጽእኖ ጋር የተያያዘ
ነው በማለት ይተቻሉ።
ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በኢትዮጵያ የገባውን ድርቅና ረሃብ ለመቋቋም ከአንድ ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ
የሚያስፈልግ መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ ባለሙያዎች እየተናገሩት ይገኛሉ። የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው ዜጎች ቁጥር ከ18
ሚሊዮን በላይ ሊሆን እንደሚችሉ ገልጸው በአሁኑ ወቅት በርካታ እንስሳት እየሞቱ እንደሚገኙና 400 ሺ ህጻናት በምግብ እጥረት
እንደተጠቁ ይገልጻሉ። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ሁኔታው ሊባባስ የሚችል መሆኑን ጠቁመው እርዳታው ካልደርሰ አገሪቷ በጣም አስጊ
ሁኔታ ውስጥ ልትገባ እንደምትችል ተንብየዋል።
የአሁኑ
የድርቅና የረሃብ ሁኔታ ከዛሬ 25 በፊት ከነበረው በጣም አይሎ የሚከስት ሲሆን እርዳታ በአሁኑ ወቅት
ቅድሚያ የሚሰጣቸው እንደሶርያ ደቡብ ሱዳንና የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ዓይነቶቹ
ቦታዎች በመኖራቸው ችግሩ
የዓለምን ትኩረት ስቦ ተፈላጊውን እርዳታ ለመሰብሰብ የማይቻል ይሆናል የሚል ስጋት የሚገልጹ አሉ።
Ø
ባለፈው ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም
ሰሜን ኮሪያ ለሙከራ ሃይድሮጅን ቦምብ አፈንድቻለሁ በማለት መግለጫ መስጠቷ
የሚታወስ ሲሆን የምዕራብ አገሮች ሙያተኞች የፈነዳው ቦምብ ኃይል የሃድሮጅን ቦምብ ያህል ጥንካሬ የለውም በማለት የሰሜን ኮሪያን
መግለጫ ያጣጣሉ መሆናችው ታውቋል። ይሁን እንጅ እነዚሁ የምዕራብ አገሮች መንግስታት
ማክሰኞ ዕለት የፈነዳው ቦምብ
ሰሜን ኮሪያ ከዚህ በፊት ካፈነዳቻቸው የኑክሊየር ቦምቦች ሁሉ በኃይልና በመጠን
የላቀ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን አውግዘው የአጸፋ ርምጃ እንደሚወስዱ ዝተዋል። ጃፓን ደቡብ ኮሪያና አሜሪካ የዓለም አቀፉ
ኅብረተሰብ በሰሜን ኮሪያ ላይ ሊወስድ የሚችለው እርምጃ በጋራ ለማስተባበር የተስማሙ ሲሆን የተባበሩት መንግስታትም አዲስ ማዕቀብ
የሚጥል መሆኑን ፍንጭ ሰጥቷል።
ደቡብ ኮሪያ የሰሜን ኮሪያ ድርጊት ከዚህ በፊት ሁለት አገሮች ያደረጉንን ስምምነት
የሚጥስ መሆኑን ገልጻ
አቋርጣ የነበረውን የፕሮፓጋንዳ ራዲዮ ስርጭት ከነገ አርብ ከታኅሣሥ 29 ቀን
2008 ዓም
ጀምሮ የምትቀጥል መሆኗን አስታውቃለች።
ደቡብ ኮሪያ በሁለቱ አገሮች ወሰን አካባቢ ምስጥራዊ ቦታዎች ላይ በተተከሉ 40
ግዙፍ የድምጽ ማጉያዎች አማካይነት የውጭ አገር ዜናዎችንና ቅስቀሳዎችን ለሰሜን ኮሪያ ወታደሮችና ለአገሪቱ ዜጎች ስታስተላልፍ
መቆየቷ የሚታወስ ሲሆን ይህም የሰሜን ኮሪያን ባለስልጣኖች ክፉኛ በማስደንገጡና በማስቆጣቱ ሁለቱን ወደ ጦርነት አፋፍ አድርሷቸው
እንደነበር ይታወሳል። በተከታታይ ንግግሮች በተደረሰ ስምምነት መሰረት
የፕሮፕጋንዳው ቅስቀሳ መቋረጡ ይታወቃል።
Ø
ሐሙስ ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም በሳኡዲ የሚመራው ጦር በየመንን ዋና ከተማ በሰንአ
ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ በርካታ ሰዎች የሞቱ
መሆናቸውን
ለዜና ምንጮች የገለጹ ሲሆን የኢራን መንግስትም በከተማው የሚገኘው ኤምባሲው ተጠቅቶ ጉዳት ደርሶበታል በማለት
ድርጊቱን
አውግዟል።
በየመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረና በዋናው ከተማ ሰንአ ላይ ወታደራዊ ጥቃቶች
ከተጠናከሩ በኋላ በርካታ አገሮች ኤምባሲያቸውን ዘግተው ወደ ሌላ ቦታ ያዛወሩ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን የኢራን ኤምባሲ ሙሉ በሙሉ
የሚሰራ መሆኑና አለመሆኑ አልታወቀም። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በአየር ጥቃቱ ኢምባሲው የፈረሰ መሆኑን እና
በውስጡ የነበሩ
በኢምባሲው ሰራተኞች መጎዳታቸውን ይግለጽ እንጅ የአካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት
እንዳልደረሰ መስክረዋል ተብሏል። የሺያ እምነት ተከታይ መሪ በሳኡዲ አረቢያ ባለስልጣኖች ከተገደሉ ወዲህ በኢራን እና በሳኡዲ
መካከል ያለው አለመግባባት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ሁለቱ አገሮች
ዲፕሎማቶቻቸውና
ከየአገሮቻቸው ከማስወጣታቸው በተጨማሪ ኢራን ከሳዑድ የሚመጡ ሸቀጦች ወደ አገሯ እንዳይገቡ አግዳለች።
Ø
ከትሪፖሊ 170 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዝሊተን በምትባለው የሊቢያ ከተማ ውስጥ
በአንድ የፖሊስ ማሰልጠኛ ጣቢያ ላይ በጭነት መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ
ቢያንስ
50 ሰዎችን የገደለ መሆኑና ከ127 በላይ ሰዎች ያቆሰለ መሆኑ ለዜና ምንጮች የደረሰው መረጃ ይገልጻል። በሞአመር ጋዳፊ ዘመነ
መንግስት ወታደራዊ ጦር ሰፈር የነበረው ቦታ አሁን የፖሊስ ማሰልጣኛ በመሆን እያገለገለ ሲሆን
አደጋው
በደረሰበት ወቅት 300 ያህል ምልምሎች በመሰልጠን ላይ የነበሩ
መሆናቸው ታውቋል። ባለፉት አራት ዓመታ ሁለት ራሳቸውን መንግስት ብለው የሰየሙ
ተጻራሪ ቡድኖች ሊቢያን እያስተዳደሯት ሲሆን
በርካታ
የታጠቁ ኃይሎች በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀሳቸው ምክንያት በአገሪቱ ውስጥ አለመረጋጋት ሰፍኖ ይገኛል። እየተጠናከር መምጣቱ
የሚነገርለት አይስስ የተባለው ቡድን ከዚህ በፊት ተመሳሳይ የአጥፍቶ ጠፊ ቦምቦችን ማፈንዳቱ የሚታወቅ ሲሆን በፖሊስ ማሰልጠኛ
ላይ የደረሰው አደጋ የአይሲስ ስራ ሳይሆን አይቀርም የሚል ጠንካራ ግምት አለ። በአደጋው የተጎዱት ወደ ሆስፒታል ተወስደው
እየታከሙ መሆናቸው ተነግሯል። በቅርቡ በተመድ አስተባባሪነት ሁለቱ ተጻራሪ መንግስታት የእርቅ ስምምነት ማድረጋቸው የሚታወስ
ሲሆን በሊቢያ የተመድ ልዕክ ማርቲን ኮብለር ድርጊቱን አውግዘው የሊቢያ ዜጎች ህብረታቸውን እንዲያጠናክሩ ተማጽነዋል።
ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም ሰሜን ኮሪያ የሰራቸውን የሃድሮጅን ቦምብ ለሙከራ ያፈነዳች መሆኑን ገልጻለች። የሰሜን
ኮሪያ ባለስልጣኖች በሰጡት መግለጫ ሰሜን ኮሪያን በማጥቃት ላይ የሚገኙትን እንደ አሜሪካ ዓይነት ኃይሎችን ለመቋቋም የኑክሊየር
ኃይል ያስፈልጋታል ብለዋል። የሰሜን ኮሪያን ድርጊት ቻይና፤ ደቡብ ኮሪያ፤ ጃፓን ራሺያና የአውሮፓው ኅብረት ያወገዙት ሲሆን
አሜሪካም ድርጊቱን አውግዛ አስቸኳይ ርምጃ እንወስዳለን ብላለች። የቦምቡ ፍንዳታ በአካባቢው 5-1 የሆነ የመሬት ንቅናቄ ግፊት
ማምጣቱ በተለያዩ የመሬት መንቀጥቀጥ መከታተያ ጣቢያዎች የተመዘገበ ሲሆን ቀደም ብሎ
በርከት ያሉት ቢጠራጠሩትም አንዳንድ ክፍሎች
የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ሰጥተው ነበር።
ሰሜን ኮሪያ ለሙከራ የኑክሊየር ቦምብ ስታፈነዳ ይህ አራተኛ ጊዜዋ ነው።
Ø
የቀድሞ
የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር ሚስተር ቤሎ ሃሊሩ መሀመድ እና ልጃቸው
1.5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆን የመንግስት ገንዘብ ወስደዋል ተብለው መከሰሳቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል።
ገንዘቡ የተወሰደው ቦኮሃራምን ሊቋቋም የሚችል ወታደራዊ ኃይል ለማጠናከር ለሚያስፈልገው የመሳሪያ ግዥ ከተመደበው ገንዘብ ውስጥ
መሆኑ ስለተረጋገጠ ሁለቱ ሰዎች ክስ ተመስሮትባቸዋል። ሁለቱም ጥፋተኛ አይደለንም በማለት ቃላቸውን ሰጥተዋል።
የናጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ለመሳሪያ ገዥ በሚል በተፈረሙ የሀሰት ኮንትራቶች ሽፋን
ከቢሊዩን የአሜሪካ ብር በላይ የሆነ የመንግስት ገንዘብ ተዘርፏል የሚለውን ክስ ለማጣራት አንድ መርማሪ ኮሚሽን ያቋቋሙ መሆናቸው
የሚታወስ ሲሆን በቀድሞ የመከላከያ ሚኒስትሩና በልጃቸው ላይ የተመሰረተው ክስ የመሪማሪ ኮሚሽኑ የስራ ውጤት መሆኑ ታውቋል።
ባለፈው ወር ይኸው ኮሚሽን የቀድሞ የአገሪቱ ብሔራዊ የጸጥታ አማካሪ በነበሩት በሚስተር ሳምቡ ዳሱኪ ላይ 19 የወንጀል
ዓይነቶችን በመዘርዘር ክስ የመሰረተባቸው መሆኑ ተዘግቧል። ሚስተር ቤሎ የቀድሞ መንግስት መከላከያ ሚኒስትር ሆነው የሰሩ ሲሆን
ባሁኑ ወቅትም ሕዝባዊ ዴሞክራሲያ ፓርቲ እየተባለ በሚጠራው የተቃዋሚ ድርጅት ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን አላቸው።
በተያያዘ ዜና ናይጄሪያን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የዓለም
አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ኃላፊ ሚስስ ክርስቲን ላጋርድ ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓም
ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ ድርጅታቸው ከናይጄሪያ መንግስት የተሰረቀውን ገንዘብ በማፈላለግና ወደፊትም ተመሳሳይ
ዝርፊያዎችን ለመከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ለፕሬዚዳንት ቡሃሪ የገለጹ መሆኑን ተናግረዋል።
አያይዘውም ናይጄሪያ ያለባትን የኢኮኖሚ ችግር ለመቋቋም በቂ ገንዘብ ስላላት ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ገንዘብ መበደር
የለባትም ብለዋል።
Ø
በአልጄሪያ አምስት አመት የሚቆየው የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን በሁለት የምርጫ ዘመን የሚወስን የህገ መንግስት ረቂቂ
በመንግስት በኩል የተነገረ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም
በርበር የተባሉት ውህዳን ብሔረሰቦች ቋንቋም እውቅና እንዲሰጠው ረቂቅ ህገ መንግስቱ ያውጃል። ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008
ዓም በይፋ በዜና ማሰራጫዎች የተነገረው ይህ ረቂቅ ህገ መንግስት የምክር ቤት አባላትን ድጋፍ አግኝቶ ከጸደቀ ለውሳኔ ሕዝብ
እንደሚቀርብ ይቀርባል ተብሏል። የአሁኑ ፕሬዚዳንት ቡተፍሊካ በከፍተኛ ህመም ውስጥ በነበሩበት ሁኔታ
የዛሬ ሁለት አመት ለአራተኛ ጊዜ ተመርጠው በስልጣን ያሉ መሆናቸው ይታወሳል።
Ø
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ለአቅመ ሄዋን ያልደረሱ ልጆችን አስገድደው ደፍረዋል
በማለት አዲስ ክስ የቀረበ መሆኑን በመግለጽ ሁኔታውን እየመረመሩት መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣኖች ማክሰኞ
ታኅሣሥ 26 2008 ዓም ተናገረዋል። ምርመራው ምን ያህል የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት እንዳሉበትና የየትኞቹ አገሮች አባላት
እንደሆኑ እንደሚዳስስና የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትና በአገሪቷ
ላይ ያሰማሩ አገሮች በራሳቸው ምርመራ እንዲያካሄዱ መመሪያ
የተሰጠ መሆኑን ተናገረዋል። በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ የተሰማሩ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ከዚህ በፊት
በተመሳሳይ ድርጊት በተደጋጋሚ መወንጀላቸው የሚታወስ ሲሆን ባለፈው ወርም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቂ ርምጃ አልወሰደም
የሚል ወቀሳ ይህንን ጉዳይ ለማጣራት ተሰይሞ ከነበረው ገለልተኛ ኮሚቴ
የተሰጠ መሆኑ ይታወሳል።
Ø
በደቡብ
ሱዳን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በመሸሽ ዜጎች በየአቅጣጫው አገራቸውን እየተው መውጣታቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ 7000
የሚሆኑ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በመግባት በስደተኛነት መመዝገባቸውን ማክሰኞ ታኅሣሥ 26 ቀን
2008 ዓም አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ገልጿል። ስደተኞቹ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኮንጎ የገቡት ባለፈው ወር ውስጥ ሲሆን
በአገሪቱ ሰሜን ምስራቅ በሚገኘው የመመዝገቢያ ጣቢያ የተመዘገቡ
መሆኑ ተገልጿል። የደቡብ ሱዳን ችግር ከተጀመረ ከታኅሣሥ
2006 ዓም ጀምሮ በአስር ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 2.2 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ
መሆኑ ይታወቃል። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ውስጥ በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ስምምነት ተፈርሟል ቢባልም ጦርነቱና ግድያው
መቀጠሉን የዜና ምንጮች እየዘገቡት ይገኛሉ።
ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የቀድሞ የብሩንዲ መከላከያ ሚኒስትር የነበሩት ሳይሪል ዳዩሩኪየ እና ሌሎች አራት
ተባባሪዎቻቸው ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ተሞክሮ የነበረውንና ሳይሳካ የቀረውን መፈንቅለ መንግስት በማደራጀትና
በማስተባበር
በተከሰሱበት
የወንጀል ክስ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኞች ናቸው በማለት ብይን መስጠቱን
ከአካባቢው
የተገኘው መረጃ ገለጸ። የመከላከያ ሚኒስትሩ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት የመከላከያ ቃል “ሰላማዊ ሕዝብ በገፍ በአውራ ጎዳናዎች ላይ
በፖሊሶች ሲገድሉና የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የተባሉት በሰው ደግሞ ሕዝብ እየሞተ
ኳስ
ሲጫወቱ እያየሁ፤ እጄን አጣጥፌ ለመቀመጥ አልችልም ብለዋል። ተባባሪዎች በመባል የተከሰሱት አራት ግለስቦች
ሁለት የሰራዊቱ ጄኔራሎችና ሁለት የፖሊስ ኮሚሽነሮች ናቸው። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ
ወር ውስጥ የብሩንዲ ፕሬዚዳንቱ ህገ መንግስቱን ተላልፈው ለሶስተኛ ጊዜ የሚወዳደሩ መሆናቸውን በይፋ ባወጁበት ወቅት በተነሳው
የተቃውሞ እንቅስቃሴ በርካታ ሰዎች መገዳላቸውና መሰደዳቸው ተከትሎ
በግንቦት
ወር ውስጥ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉ ይታወቃል። የመፈንቅለ መንግስቱ ቀንደኛ መሪ ናቸው ተብለው የተፈረጁት ጄኔራል እና
ሌሎች
ከፍተኛ መኮንኖኖች እስካሁን ሳይዙ ቆይተዋል። ፍርድ ቤቱ መፈንቅለ መንግስት በማካሄድ ክስ የተከሰሱትን የ28 ሰዎች ጉዳይ
ከታኅሣሥ 4 2008 ዓም ጀምሮ እያየ ሲሆን በሌሎች ተከሳሾች ላይም በቅርቡ ብይን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
በማዕከላዊ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው አገራዊ ምርጫ 30 ሰዎች ለፕሬዚዳንት ቦታ የተወዳደሩ
ሲሆን ከተወዳዳሪዎቹ ውስጥ 20 የሚሆኑት ምርጫው በርካታ እንከኖች ያሉበት በመሆኑ መሰረዝ አለበት የሚል ጥያቄ አቅርበዋል። ሰኞ
ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓም ባወጡት የጋራ መግለጫ በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ አሰጣጡ ስነስርዓትን ያልተከተለ መሆኑንና
በመራጮች ላይ በርካታ
ማስፈራሪያዎች የተደረጉ
መሆናችውን ገልጸው ይህ
በምርጫ ስም የተሸፈነ ማጭበርበር ስለሆን ምርጫው መሰረዝ አለበት ብለዋል። በታኅሣሥ 20
ቀን 2008 ዓም በተካሄደው ምርጫ ከተሰጠው ድምጽ አንድ አራተኛ የተቆጠረ ሲሆን
እስካሁን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ፎስተን ቱአዴራ የድምጹን 23 ከመቶ በማግኘት እየመሩ መሆናችው ተነግሯል። አሸናፊ
ሊሆን የሚችለው ተወዳዳሪ የድምጹን 50 ከመቶ ካላገኘ ሁለተኛ ዙር ምርጫ በጥር 24 ቀን 2008 ዓም ይካሄዳል ተብሏል። ላለፉት
ሶስት ዓመታት በእርስ በርስ ግጭት እየታመሰች ላለቸው የማአከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ይህ ምርጫ መረጋጋትን ያስገኛል የሚል ተስፋ
የነበረ ሲሆን በተካሄደው ምርጫ ላይ ተቃውሞ መነሳቱ ብዙዎችን ስጋት ላይ ጥሏል።
Ø
የዩጋንዳ ፖሊስ ሰኞ ዕለት በሰጠው መግለጫ ከ2004 እስከ 2006 ዓም ባሉት ጊዜዎች ውስጥ
ከዋናው አውሮፕላን ጣቢያ በየጊዜው ተይዘው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከነበሩት
አደንዛዥ
እጾች ውስጥ
80 ኪሎ የሚመዝንና
4 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ
እጽ መሰወሩን እና
በከፍተኛ
ደረጃ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል። ጉዳዩን የሚያውቁ ሰዎች ለዜና ምንጮች እንደገለጹት 80 ኪሎ የሚመዝን እጽ በከፍተኛ
ደረጃ ጥበቃ ከሚደረግለት መጋዘን ተወስዶ በምትኩ የስንዴና የካሳቫ ዱቄት የተቀመጠ መሆኑን ጠቁመዋል። እጹ መሰረቁን ለማወቅ
የተቻለው የመንግስት ተቆጣጣሪዎች ባለፈው ዓመት ከመጋዘኑ ለናሙና የወሰዱት ሲመረመር ከተገኘ መረጃ ነው የተባለ ሲሆን በወንጀሉ
የከፍተኛ ባለስልጣኖች እጅ ሳይኖርበት አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ አሉ።
Ø
በደቡብ ሱዳን ካሉት አቢይ በሽታዎች መካከል አንዱ የወባ በሽታ መሆኑ የታወቀ ቢሆንም በዚህ
ዓመት
በበሽታው የተለከፉት ሰዎች ብዛት ከዚህ በፊት ባልነበረ ደረጃ መጨመሩ ተገለጸ። የወባ በሽታ
ወቅት ነው በሚባሉት ከመስከረም እስከ ታኅሣሥ ባሉት ወሮች
1.6 በሽተኞች በወባ በሽታ የተለከፉ መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን በአንዳንድ
አካባቢዎች የበሽተኞቹ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲወዳደር
በእጥፍና ከዚያም በላይ የጨመረ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ። የተባበሩት መንግስታት
ድርጅትና የድንበር የለሽ ሃኪሞች ከመንግስት ተቋሞች ጋር በመተባበር የጠና አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉ ቢሆንም በመድኅኒት
እጥረት ምክንያት የተሟላ አገልግሎት ሊሰጥ ባለመቻሉ
በርካታ
ሰዎች ለሞት አደጋ የታጋለጡ መሆናቸውና አገልግሎቱን እየሰጡ ያሉ ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።
ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የሳኡዲ አረቢያ መንግስት የታወቁትን የሺያ እምነት ተከታዮች መሪ ሼክ ኒምር ከሌሎች 47
ሰዎች ጋር ባለፈው አርብ በሞት ከቀጣ ጀምሮ በመካከለኛው ምስራቅና በሌሎች ቦታዎች ከፍተኛ የሆኑ የተቃውሞ ስልፎች ተደርገዋል።
አልአዋሚያ በሚባለው የእምነቱ ተከታዮች በብዛት በሚኖሩበት የሳኡዲ ግዛት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ከሼክ ኒምር ቤት እስከ
ከተማው መካከል ተሰልፈው ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን “ሕዝቡ የሳኡዲ መንግስት እንዲወገድ ይፈልጋል” “ሞት ስልጣን ላይ ላለው
የሳኡድ ቤተሰብ” የሚሉ መፈክሮች ሲያሰሙ የነበሩ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል።
ባለፈው ቅዳሜ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ውስጥ የሼኩን መገደል የተቃወሙ ዜጎች
በሳኡዲ ኤምባሲላይ እሳት በመለኮስ ንብረት ያወደሙ ሲሆን ኢራን 40 ሰዎችን በቁጥጥር ማድረጓን ገልጻለች።
ይህንን
ተከትሎ ሳኡዲ አረቢያ ከኢራን ጋር ያላት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በማቋረጥ የኢራን ዲፕሎማቶች በ48 ሰዓት እንዲወጡ ስታደረግ
ኢራንም ተመሳሳይ እርምጃ ወስዳለች። በባህሬን ተከታታይ የተቃውሞ ስልፎች የተደረጉ ሲሆን
በሁለት
የሱኒ ተከታዮች መስጊዶች ላይ በተጣሉ ቦምቦች
አንድ
አሚር የሞቱ መሆናቸውና በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑ ተዘግቧል። ባህሬንም ከኢራን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
አቋርጣለች። የሼኩ
መገደል በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች፤ በእንግሊዝ፤ በፓኪስታን፤ እና በቱርክ ተቃውሞ አስነስቷል። የቀድሞ የኢራክ
ጠቅላይ ሚኒስትር አል ማሊኪ የኢራክ ሕዝብ ድርጊቱን እንደሚያወግዝ ገልጸው ይህ አሰቃቂ የሆነ ግድያ ለሳኡዲ ገዥዎች ከስልጣን
መወገድ ምክንያት ይሆናል ብለዋል። የሰብአዊ
መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም ድርጊቱን አውግዘው እርምጃው የተወሰደው በፖለቲካ ምክንያት ነው ብለዋል።
Ø
በኬኒያ ሰሜን ምስራቅ የሚገኘው የጋሪሳ ዩኒቨርስቲ ለ150 ሰዎች ህይወት መጥፋት
ምክንያት በሆነው በአልሸባብ ጥቃት ምክንያት ላለፉት ዘጠኝ ወራት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ
የተከፈተ
መሆኑ ተነግሯል። የዩኒቨርስቲው አስተዳዳሪዎችና መምህራን ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 25 ቀን 2008 ዓም ስራ የሚጀምሩ ሲሆን ተማሪዎች
ደግሞ ከህዳር 2 ቀን 2008 ዓም ጀምሮ ትምህርት እንደሚጀምሩ ታውቋል። የተማሪዎችን ደህንነት የሚጠበቅ የፖሊስ ጣቢያ
በዩነቨርሲት ውስጥ የተቋቋመ መሆኑም ተነግሯል።
Ø
በሊቢያ ሲድራ ከሚባለው የነዳጅ ማውጫ ወደብ አጠገብ ራሱን የእስላማዊ መንግስት ብሎ ከሚጠራው
አይሲስ ጋር ግንኙነት ያላቸው ኃይሎች ከወታደሮች ጋር እየተፋለሙ መሆናችው ታውቋል። በአሁኑ ወቅት ጦርነት በምን ያህል ርቀት
ላይ እየተካሄደ መሆኑ ባይታወቅም እይሲስን የሚደግፉት ኃይሎች ቀደም ብለው ከቦታው 30 ኪሎሜትር የሆነውን ቦታ የተቆጣጠሩት
መሆኑን ከአካባቢው የሚመጡ ዘገባዎች ገልጸዋል። ሁለት መኪና ላይ የተጫኑ ቦምቦች ፈንድተውም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት
አድርሰዋል ተብሏል። ይኸው ቡድን ከሁለት ወር በፊት ተመሳሳይ ጥቃት አድሮጎ የነዳጅ ማውጫውን ለመቆጣጠር የሞከረ ሲሆን ብርቱ
ተቃውሞ ስለገጠመው ሙከራው መክሸፉ ይታወሳል። ሲድራ የተባለውችው ቦታ በምዕራብ ሊቢያ ራሱን በመንግስትነት ባወጀው ኃይል ስር
እንዳለች ይታወቃል።
Ø
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ካጋሚ ለሶስተኛ ጊዜ ለመመረጥ እንዲችሉ ህገ መንግስት ማስቀየራቸውንና
እሳቸውም ለምርጫው ዝግጁ ነኝ በማለት ይፋ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ
መንግስታቸው ድርጊቱን በጽኑ የኮነነ መሆኑን ገልጸዋል። ቃል አቀባዩ ህገ መንግስቱን ተጠቅሞ የስልጣን ዝውውር ማድረግ
ለዴሞክራሲያ አሰራር ቁልፍ መሆኑን መንግስታቸው የሚያምንበት መሆኑን ገልጸው የስልጣን እድሜን ለማራዘም ብቻ ያለውን ህግና ደንም
መሻርና መለወጥ የሚወገዝ ነው ብለዋል። በተለይም አንድን ግለሰብ ስልጣን ላይ ለማቆየት የሚደረገው አግባብ ያልሆነ የህግ ለውጥ
ያሳስበናል ብለዋል። ፖል ካጋሚ የአሜሪካ ለረጅም ጊዜ የአሜሪካ አገልጋይና
ወዳጅ
ሆነው የቆዩ መሆናችው የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ መንግስት በካጋሚ ላይ ይህን የመሰለ ውግዘት ማሰማቱ
ብዙዎችን አስገርሟል።
Ø
የጣሊያኑ
ግዙፍ
ኩባንያ
ሳሊኒ
ኮንስትራክሽን
ኩባንያ
ለጊቤ
አራት
ኃይል
ማመንጫ
ጣቢያ
ግንባታ
የሚሆን
ፋይናንስ
ማግኘቱን
ማረጋገጫ
አቅርቦ
ወደ
ድርድር
ቢገባም፣
ሦስት
ዓለም
አቀፍ
ኩባንያዎች
ፕሮጀክቱ
እንዲሰጣቸው
ለጠቅላይ
ሚኒስትር
ጽሕፈት
ቤት
አዲስ
ጥያቄ
ማቅረባቸውን
ምንጮች
ገለጹ፡፡
ሳሊኒ
ቀደም
ሲል
ከአውሮፓ
ኢንቨስትመንት
ባንክ
ለፕሮጀክቱ
የሚሆን
ፋይናንስ
እንደሚያገኝ
ቢገልጽም፣
ከሳምንት
በፊት
ከጣሊያን
ኤግዜም
ባንክ
1.5
ቢሊዮን
ዩሮ
ብድር
እንደሚያመጣ
መተማመኛ
ማቅረቡ
ታውቋል፡፡
በዚህ
መሠረት
የኢትዮጵያ
ኤሌክትሪክ
ኃይል
ከፍተኛ
አመራሮችና
ባለሙያዎች
ያሉበት
ቡድን፣
ከሳሊኒ
ጋር
በፋይናንስና
በቴክኒክ
ጉዳዮች
ላይ
ድርድር
መጀመራቸው
ተገልጿል፡፡
ነገር
ግን
ይህ
ድርድር
እየተካሄደ
ባለበት
ወቅት
የቱርክ
ኩባንያ
አዝሚር፣
የብራዚል
ኩባንያ
ፔሮዝና
የቻይና
ኩባንያ
ሲኖ
ኃይድሮ
የጊቤ
አራት
ኃይል
ማመንጫ
ፕሮጀክት
እንዲሰጣቸው
ለጠቅላይ
ሚኒስትር
ጽሕፈት
ቤት
ጥያቄ
ማቅረባቸው
ታውቋል፡፡
ለጉዳዩ
ቅርበት
ያላቸው
ምንጮች
እንዳረጋገጡት
እነዚህ
ኩባንያዎች
ለግንባታ
የሚሆን
ፋይናንስ
እንደሚያመጡና
ለአገር
በቀል
ኩባንያዎችም
ሥራ
እንደሚሰጡ
በመግለጽ፣
መንግሥት
ውስን
ጨረታ
አውጥቶ
አሸናፊ
ለሚሆነው
ኩባንያ
ሥራውን
እንዲሰጥ
ጥያቄ
አቅርበዋል፡፡
ታኅሣሥ 23 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በተለያዩ ቦታዎች በወያኔ አገዛዝ ላይ የሚደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የቀጠሉ
ሲሆን ሐሙስ ማታ በዲላ ዩነቨርሲቲ ሰፍሮ የሚገኘው የአግአዚ ጦር እንዲወጣ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባደረጉበት ወቅት
በተወረወረ
ቦምብ ሁለት
ተማሪዎች
ወዲያውኑ
ሲሞቱ
ከስድስት
በላይ የሚሆኑ
ተማሪዎች
ከባድ
የመቁሰል
አደጋ
የደረሰባቸው መሆኑ
ከስፍራው
የተገኘው ዜና ይገልጻል።
የወያኔ አገዛዝ ቦምቡ የተወረው ባሸባሪዎች ነው ይበል እንጅ በአግአዚ ወታደሮች ለመሆኑ ጥርጣሬያቸውን የሚገልጹ በርካታ ናቸው።
በህይወት
የተረፉት
ተማሪዎች
ግቢውን
ለቅቀው
ለመውጣት
ሲሞክሩ
በወያኔ ወታደሮች
ከፍተኛ
ድብደባ
የደረሰባቸው ከመሆኑም በላይ በርከታዎቹ ታስረው የተወሰዱ መሆናቸውን
የአይን
እማኞች ይናገራሉ። ከተጎዱት
መካከል አራቱ በጽኑ የቆሰሉ ሲሆን በቦምቡ
ለህክምና ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናቸውም ታውቋል።
Ø
አዲስ አበባ በሚገኘው የወያኔ የማዕከለካዊ
ወንጀል
ምርመራ
ቅጥር ግቢ
ውስጥ
ሰሞኑን
ከአራት
መቶ
በላይ
እስረኞች
መታሰራቸውንና ለምርመራ በየቀኑ ከፍተኛ ድብደባ
እየተካሄደባቸው
መሆኑን ምንጮች
ገለጸዋል።
በእስር
ቤቱ
የጓሮ
አቅጣጫ
በሚገኙት
ሶስት
ክፍሎች
ውስጥ
ከመቶ
ሰማንያ
በላይ
የሚሆኑ
እስረኞች
ሲገኙ
ከፎቁ
ምድር
ቤት
ውስጥ
ባሉ
ሌሎች
ክፍሎች
ውስጥ
ደግሞ
ከሁለት
መቶ ሰማንያ
በላይ
ታፍገው
እንዲታሰሩ
መደረጉን
የሚናገሩት
እነዚሁ
ምንጮች
ከታሰሩበት
ክፍል
ሲወሰዱ በሚገባ እየተራመዱ የሚሄዱ እስረኞች ከምርመራው በኋላ
በወሳንሳ
ተይዘው
እንደሚመለሱ
ይናገራሉ።
Ø
በደቡብ ሶማሊያ በምትገኘው እና ከወታደራዊ አንጻር ቁልፍ ቦታ በያዘችው በኪስማዮ ከተማ ውስጥ
የሲየራ ሊዮንን ወታደሮችን በመተካት 250 የወያኔ ወታደሮች ተመድበው የተሰማሩ መሆናቸው ተነግሯል። ሲየራ ሊዮን በሱማሊያ ውስጥ
ከተሰማራው ከአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወታደሯቿን ያስወጣችው ባለፈው ዓመት የኢቦላ በሽታ አገሪቱን በከፍተኛ ደረጃ
ባጠቃበትና የሶማሊያ መንግስት ወታደሮቹ ኢቦላ ሊያስተላልፉ ይችላሉ የሚል ስጋት በገለጸበት ወቅት ነው። የአልሸባብ እንቅስቃሴ
በተዳከመ ሁኔታም ቢሆን ጥቃት መሰንዘሩን በመቀጠሉ የወያኔ ወታደሮች በተጨማሪ እንዲመደቡ ተደርጓል። ለጊዜው 250 ወታደሮች
ይሰማሩ እንጅ ሌላ 800 የሚሆኑ ተጨማሪ ወታደሮች በቅርቡ የሚመደቡ መሆናቸውን ምንጮች ይገልጻሉ።
ሶማሊያ ውስጥ በአልሸባብ በደረሰ ጥቃት በርካታ ወያኔን በማገልገል ላይ ያሉ
ወታደሮች እየሞቱ መሆናቸው በየጊዜው የተዘገበ ሲሆን የአካል ጉዳተኛ የሆኑትም በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች
ውስጥ
ሲታከሙ መቆየታቸውን የሚገልጹ ተከታታይ ዘገባዎች እንደነበሩ ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና ዛሬ ታኅሣሥ 23 ቀን 2008 ዓም በሶማሊያ ዋና ከተማ በሞጋዲሾ በሚገኝ
የምግብ ቤት ውስጥ የአልሸባብ አባል ነው ተብሎ የሚጠረጠር አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ ራሱን ከማጥፋቱ ሌላ አንድ ሰላማዊ ሰው
የገደለ መሆኑና ሶስት ሰዎች ያቆሰለ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ቦምቡ በፈነዳበት ወቅት በርከታ ጋዜጠኞች በምግብ ቤት
ውስጥ የነበሩ በመሆናቸው የአጥፍቶ ጠፊው ኢላማ
ጋዜጠኖችን ለመግደል ነበር የሚል ግምት ተሰጥቷል።
Ø
የሳኡዲ አሪቢያ መንግስት ከአራት አመት በፊት በቁጥጥር ስር ባደረጋቸውና
የወንጀል ክስ መስርቶ ባስፈረደባቸው 47 ሰዎች ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎ
የሞት ቅጣት እንዲፈጸም አድርጓል። የሞት ቅጣቱ ከተፈጸመባቸው መካከል የታወቁት የሺያ ሃይማኖት ተከታዮች መሪ ሼክ ኒሚር አል
ኒሚር አንዱ
በመሆናቸው በሳኡዲ ውስጥ የሚገኙት የሺያ እምነት ተከታዮች አመጽ ሊያነሱ ይችላሉ የሚል ፍራቻ ተፈጥሯል። የዛሬ አራት አመት
በአገሪቱ ምስራቅ የሚኖሩ የሺያ እምነት ተከታዮች የሚደርስባችውን በደል በመቃወም ከፍተኛ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ሲታወቅ የሳኡዲ
ባለስልጣኖች እንቅስቃሴውን ለማፈን ሃይልን ከመጠቀማቸው ሌላ ሼክ ኒሚርንና ተከታዮቻቸውን ይዘው ማሰራቸውና ለፍርድ ማቅረባቸው
ይታወሳል። ሼኩ በተያዙበት ወቅት በተነሳው ብጥብጥ ሶስት ሰዎች መሞታቸውም ይታወቃል። ሳኡዲ አረቢያ በሼኩ ላይ የሞት ቅጣት
መፈጸሟ ልትቋቋመው የማትችለው
ከፍተኛ ውርደት ይደርስበታል በማለት
የኢራን መንግስት ያስጠነቀቀ ሲሆን የሺያ እምነት ተከታዮች በሚኖሩበት በምስራቅ ሳኡዲ አረቢያ የሚገኙት
የሺያ እምነት ተከታዮች ከፍተኛ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ የሚል ስጋት አለ።
የሳኡዲ መንግስት የሺያ እምነት ተከታዮች በደል አልደረሰባችውም በማለት በተከታታይ መግለጫ የሰጠ ሲሆን ከተገደሉት 47 ሰዎች
መካከል ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸው የሱኒ እምነት ተከታዮችም ያሉበት መሆኑን ገልጿል።
ባለፈው የፈረጆቹ ዓመት ሳኡዲ አረቢያ ከ150 በላይ በሆኑ ሰዎች ላይ የሞት ቅጣት
የፈጸመች መሆኑ ሲታወቅ ባለፉት 20 አመታት ከተፈጸሙ የሞት ቅጣቶች የአለፈው
አመቱ ከፍተኛ ነው በማለት የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ይገልጻሉ።
Ø
በሌላ በኩል የመን ውስጥ ከሁቲ አማጽያንና ከቀደሞ የመን ፕሬዚዳንት ከሳላህ አብዱላህ ሳላህ ተከታዮች ጋር እየተዋጋ ያለው
በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል ከጥቂት ሳምንታት በፊት ተፈርሞ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ከዛሬ ከታኅሣሥ 23 ቀን ጀምሮ
የፈረሰ መሆኑን ገልጿል። በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቢፈረምም በተደጋጋሚ የተጣሰ መሆኑ የሚታወስ
ሲሆን ጥምር ኃይሉ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው አርብ ዕለት በሁቲ አማጽያን ወደ ሳኡዲ ግዛት የተተኮሰ ቦልስቲክ ሚሳየል ጠልፈው
መያዛቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል። የሳኡዲ መንግስት ፔቲሪየት የተባለው የሚሳየል መጥለፊያ መሳሪያ በመጠቀም በየጊዜው ከየመን
የተተከሱ በርካታ ሚሳየሎችን መጥለፋቸው የሚታወቅ ሲሆን ከ80 በላይ የሚደርሱ የሳኡዲ ወታደሮችና የወሰን ጠባቂዎች ከየመን
በተተኮሱ ሚሳየሎችና በወሰን አካባቢ በነበሩ ወታደራዊ ግጭቶች መሞታቸው ይታወሳል።
Ø
አልጄሪያን ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻ ለማድረግ በግምባር ቀደምትነት ከተዋጉት መካከል አንዱ
የሆኑትና የነጻነት ጀግና ተብለው የሚጠሩት ሆሲን አይት አህመድ በሰማንያ ዘጠኝ አመታቸው ባለፈው ረቡዕ በስደት በሚኖሩበት
በስዊዘርላንድ የሞቱ ሲሆን አስከሬናቸው ወደ አልጄሪያ መጥቶ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሀዘንተኞች በተገኙበት በከፍተኛ ክብር
የተቀበረ መሆኑ ታውቋል። በመንግስት ደረጃ ቀብሩ ተዘጋጅቶ የነበረ ቢሆንም የሟቹ ቤተሰቦች አስከሬኑ በተወለዱበት ስፍራ
እንዲቀበር በመጠየቃቸው ወደ ዚያው ተወስዶ አርብ ዕለት የቀብሩ ስነስርዓት ተፈጽሟል። ሟቹ በ1954 ዓም አልጀሪያ ከፈረንሳይ
ነጻ ስትወጣ የተመሰረተውን ወታደራዊ አስተዳደር በመቃወምና በሕዝብ የተመረጠ መንግስት እንዲሰየም በመጠይቅ በኩል ግምባር ቀደም
ሚና የተጫወቱ ሲሆን በነበራቸው የፖሊቲካ አስተሳሰብ ወደ ውጭ ተሰደው የኖሩ መሆናቸው ይታወቃል። ሆሲን አህመድ የመሰረቱ
የሶሻሊስት ኃይሎች ግምባር የሚባለው ፓርቲ ተቃዋሚ ፓርቲ ሲሆን የፓርቲው አባላት በቀብሩ ወቅት “ነጻና ዴሞክራሲያዊ አልጀሪያ”
የሚል መፈክር ያሰሙ እንደነበር ተዘግቧል።
ታኅሣሥ 22ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ዘጋቢዎቻችን
አዲስ
አበባ
በሚገኙ
የተለያዩ
የገበያ
ስፍራዎች
ተዘዋውረው ባጠናቀሩት ዘገባ መሰረት
የገና
በዓልን
ምክንያት
በማድረግ
በርከት ያሉ ዕቃዎች የገበያ
ዋጋ
ጭማሪ
ያሳዩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። የመቶ
ኪሎ
ጤፍ
ዋጋ ካለፈው በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር
ሁለት
ሺህ
ሶስት
መቶ
ብር
የገባ ሲሆን በዚህም
ምክንያት እንጀራ
እየጋገሩ
የሚሸጡ
ባልትና
ቤቶች
አንዱን
እንጀራ
ቀደም
ሲል
ሲሸጡበት
ከነበረው
ሶስት
ብር
ከሃምሳ
ላይ
ጭማሪ
አድርገው
አራት
ብር
መሸጥ መጀመራቸውና
አራት
ብር
ሲሸጡ
የነበሩት
ደግሞ
አራት
ብር
ከሃምሳ
ሳንቲም
በመሸጥ
ላይ
መሆናቸውን ለመገንዘብ ተችሏል።
አንድ በሬ
አስራ
ሶስት
ሺህ
አምስት
መቶ
እና
ከዚያ
በላይ በሆነ ዋጋ
በአዲሱ
ገበያ
እየተሸጠ ሲሆን
ጠቦት
በግ
ሁለት
ሺህ
ብር
የፍየል
ሙክት
አራት
ሺህ
ስምንት
መቶ
ብር
በመሸጥ
ላይ
ናቸው።
የአንድ
ኪሎ
ሽንኩርት
ዋጋ
ሃያ
ሁለት
ብር እንዲሁም የአንድ
ኪሎ
ቅቤ ዋጋ
መቶ
ሰማንያ
ብር
የደረሰ ሲሆን
የስጋን
ዋጋ
ወሰደ
የተባለው
ምስር
ክክ
ደግሞ
አንዱ
ኪሎ
ሃምሳ
ስድስት
ብር
እየተሸጠ
መሆኑ ዘጋቢያችን
ደርሶበታል።
ቀደም ብሎ ፈረሱላው እስከ
አንድ
ሺህ
ሰባት
መቶ
ብር
ሲሸጥ
የሰነበተው
በርበሬ
ወደ
ሁለት
ሺህ
አርባ
ብር
ማሻቀቡ
ታውቋል።
ቲማቲም
አንዱ
ኪሎ
ሃያ
ብር፤
ቃሪያ
አንዱ
ኪሎ
አስራ
ስምንት
ብር
፤ሎሚ
በኪሎ
ሃያ
አምስት
ብር፤
ብርቱካን
በኪሎ
ሰላሳ
ሁለት
ብር በመሸጥ ላይ ያሉ ሲሆን የአንዱ ማደባሪያ ከሰል ዋጋ ደግሞ ሶስት መቶ ሰማንያ ብር ገብቷል።
የምግብ ዕቃዋዎች ዋጋ ከአብዛኛው ሰው አቅም በላይ ሆነው ለረጅም
ጊዜ መቆየታቸው የታወቀ ቢሆንም ዘንድሮ ደግሞ ገና ዓመት ባሉ ቀናት ሲቀሩት በጣም መጨመሩ ሕዝቡን ከፈተኛ ስጋት ውስጥ
ከትቶታል። ምን ዓይነት ዘመን መጣ በማለት የመረረ ንግግር በይፋ እየተናገረ መሆኑ ይሰማል።
Ø
ታኅሣሥ 20 ቀን
2008 ዓም በሆሮ ጉዱሩ ዞን ጃርገዳ በሚባለው ወረዳ የአሊቦ ሁለተኛ ደረጃ መምህር የነበረውና የኦህዴዱ ከፍተኛ ባለስልጣን
ወንድም መምህር አዱኛ በትምህርት ቤቱ ውስጥ በአግአዚ ጦር
ጥይት ተመትቶ ለከፍተኛ ህክምና በአዲስ አበባው ሚኒሊክ ሆስፒታል ሲታከም ቆይቶ ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀ ረፋድ ላይ የሞተ
መሆኑ ታውቋል። የሟቹ ወንድም ድጉማ አሬሶ የሙክታር ከድር አማካሪና የኦርሚያ ክልል ተብየው የልማት ተቋማት ቢሮ ኃላፊ በመሆኑ
አስከሬኑን ለመረከብ በርካታ የኦህዴድ ባለስልጣንት በሚኒሊክ
ሆስፒታል ተገኝተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም በአሊቦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች
የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የወያኔው የአግዓዚ ጦር ከስፍራው በመገኘት ባካሄደው ጭፍጨፋ አንድ ተማሪና ሁለት መምህራን
መገደላቸውና ለጊዜው ቁጥራቸው ያለታወቀ ተማሪዎችም ማቁሰላቸው ሲታወቅ የትምህርት ቤቱ ምክትል ዳይሬክተርና መምህር የሆነው አዱኛ
ከቢሮ በማስወጣት በተኮሱት ጥይት ያቆሰሉት መሆኑ ታውቋል። ወያኔ በሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለፈው ጭፍጨፋ አገልጋዩ እና አሽከሩ
የሆነውን ኦህዴድንም እየለበለበ በመሆኑ የአገዛዙ ማክተሚያ ሊሆን ይችላሉ የሚል አስተያየት የሚሰጡ አልጠፉም።
በተያያዘ ዜና በተለያዩ
ቦታዎች ሲካሄዱ የነበሩት ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እንደገና ተቀስቅሰው እየተካሄዱ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በምዕራብ ወለጋና
በምዕራብ ሸዋ እንዲሁም በባሌ የተለያዩ ከተሞች በሁለተኛ ደረጃ በዩነቨርስቲ ተማሪዎች አማካይነት የሚካሄደው የተቃውሞ እንቅስቃሴ
ተጠናክሮ ቀጥሏል።
Ø
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት
ፖል ካጋሜ ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀን 2008 ዓም አዲሱን የፈርንጆች አዲስ ዓመት አስመልክቶ በራዲዩና በቴሌቪዥን ለሕዝባችው
ባደረጉት ንግግር በቅርቡ በተካሄደው የውሳኔ ሕዝብ ድምፅ
አብዛኛው ዜጋ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ፍላጎት ያሳየ መሆኑን ጠቅሰው የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት
ለሶስተኛ ጊዜ በሚቀጥለው ምርጫ የሚወዳደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የተደረገው የሕግ መንግስት ማሻሻያ ወቅቱን የጠበቀና አንደነትን አጠናክሮ በማስቀጠል በኩል ከፍተኛ አስተዋጾ ሊያደርግ
የሚችል ነው ብለዋል። ሚስተር ካጋሚ በሚቀጥለው ምርጫ ተወዳደረው አሁን ባለው ሕግ መንግስት መሰረት ለሌላ ሰባት ዓመት ያህል
በስልጣን ላይ ሊቆዩ የሚችሉ ሲሆን ከዚያ በኋላ በአዲሱ ህገ መንግስት መሰረት ለሌላ እያንዳንዳቸው አመስት አመት ለሆኑ የስልጣን
ዘመን ሊወዳደሩ የሚችሉ መሆናችው ታውቋል። ወደፊት በሚደረጉት
ምርጫዎች ሁሉ ካሸነፉ በጠቅላላው ከእንግዲህ ወዲያ ለአስራ ሰባት ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆዩ እንደሚችሉ ይገመታል።
ካጋሚ በምርጫ ወደ ስልጣን የመጡት በ1995 ሲሆን እስካሁን ለአስራ ሶስት አመታት ያህል በስልጣን ላይ ቆይተዋል። እድሜ
ከሰጣቸውና የሚቀጥሉትን ምርጫዎች ካሸነፉ በጠቅላላው ለሰላሳ አመታት በስልጣን ይቆያሉ ተብሏል። በቅርቡ በርካታ የሆኑ የአፍሪካ
አገሮች መሪዎች የስልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም ሕግ መንግስቱን ማሻሻላቸው ይታወቃል።
Ø
ጎረቤት በሆነችው
ብሩንዲ ውስጥም ፕሬዚዳንቱ ከሕግ ውጭ ለሶስተኛ ጊዜ በስልጣን ላይ ለመቆየቱ ያደረጉት ሙከራ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶ አገሪቱን
ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየወሰዳት ይገኛል። ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 22 ቀን 2008 ዓም በዋና ከተማዋ በቡጁምቡራ በተላያዩ
ቦታዎች በፈነዱ ቦምቦች አንድ ሰው ሲሞት በርካታ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል። በአንድ የገዥው ፓርቲ አባላት ያዘወትሩበታል
በተባለው ቡና ቤት ላይ የተጣለው ቦምብ አንድ ሰው መግደሉና በርካታዎችን ማቁሰሉ የታወቀ ሲሆን ሌሎች ሶስት የፖሊስ አባላት
በሌሎች ቦታዎች ላይ በተጣሉ ቦምቦች የቆሰሉ መሆናችውን ለማወቅ ተችሏል።
Ø
አዲስ የተመረጡት
ከሁለት ወራት በፊት የተመረጡት የአይቮሪ ኮስት ፕሬዚዳንት አላሳኔ ኩዋታራ በፈረጆቹ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ባደረጉት ንግግር
ለሶስት ሺ አንድ መቶ (3100) እሥረኞች የእስራት ቅናሽ ያደረጉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑት የሚፈቱ መሆናቸውን
ገልጸዋል። ከአምስት ዓመት በፊት በአገሪቱ ውስጥ የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ ለወራት በዘለቀው ብጥብጥ ሶስት ሺ የሚሆኑ ዜጎች
የተገደሉ እና በርካታዎቹ የተጎዱ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል እና በፈረንሳይ ወታደሮች አማካይነት
መረጋጋት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል። ከግጭቱ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች መያዛቸው የሚታወስ ሲሆን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጋብጎም
በቁጥጥር ስር ውለው ፍርዳቸውን ከአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት እየተባበቁ ናቸው።
Ø
በቅርቡ በሁለቱ የሊቢያ
ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የተፈረመው እርቅ በተለይ በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያገኘው የሊቢያ
መንግስት ምክር ቤት አባላት ተቃውሞ እንደገጠመው የሚታወቅ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት የእርቁን ሀሳብ እንዲቀበሉ ግፊት ለማደረግ
አንድ የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣን ወደ ምስራቅ ሊቢያ የሄዱ መሆናቸውን ከስፍራው ከተገኘ ዜና መረዳት ተችሏል።
ማርቲን ኮብለር የተባሉት የተመድ ልኡክ ሸሃት በተባለች ከተማ ተገኘተው ከመንግስት ባለስልጣኖችና ከምክር ቤቱ መሪ ጋር
ተገናኝተው የተወያዩ መሆናቸው ታውቋል። የተመድ የእርቅ
ሀሳብ ከሁሉም በኩል የተውጣጣ 17 አባላት የሚገኙበት የመንግስት አካል እንዲቋቋም የሚጠይቅ ሲሆን ከሁለቱም ተጻራሪ ኃሎች በኩል
ያሉ ባለስልጣኖች የፈረሙት ቢሆንም
የማይናቅ ቁጥር ያላቸው የምክር ቤት አባላት የተቃወሙት መሆናችው
ይታወቃል። የልዑኩ ጥረት ምን ያህሉን ሊያሳምን እንደሚችል እስካሁን ግልጽ አይደለም።
Ø
በግብጽ በአባይ ወንዝ
ላይ የነበረ አንድ የሕዝብ ማመለሻ ጀልባ ወንዝ ውስጥ በመስመጡ ሁሉም ተሳፋሪዎቹ ህይወታቸውን ሳያጡ አይቀርም የሚል ስጋት
ተፈጥሯል። የአደጋ መከላከያ ሰራተኞች እስካሁን ድረስ የአስራ አራት ሰዎች አስከሬን ከውሃ ውስጥ፡አግኝተው ያወጡ ሲሆን ፍለጋው
የቀጠለ መሆኑን የግብጽ የመንግስት ራዲዮ ገልጿል። ጀልባዋ ከተገለበጠች በኋላ ህይወት የማትረፉ ስራ ውዲያውኑ ባለመጀመሩ በርካታ
ህዝብ በቦታው በመገኝት ተቃውሞውን የገለጸ ሲሆን ፖሊስ አመጹ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይሆን እርምጃ ወስዷል ተብሏ። የግብጽ መንግስት
የሞት አደጋ ለደረሰባችው ቤተሰቦች የ1300 ዶላር ካሳ ለመክፈል ቃል የገባ ሲሆን የአካል ጉዳት ለደረሰበት ደግሞ 255 ዶላር
የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል። የአደጋው መነሻም ሆነ በጀልባዋ ላይ ምን ያህል ሰዎች እንደነበሩ እስካሁን የተሰጠ መረጃ የለም።
ታኅሣሥ 21 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአሜሪካው ኋይት ሃውስ ስር የሚገኘው የብሔራዊ ጸጥታ ካውንስል (National Security Council) ቃል አቀባይ ኔድ
ፕራይስ (Ned Price) ረቡዕ ዕለት በሰጡት መግለጫ የወያኔ መንግስት ስመ ጥፉውን የጸረ ሽብር አዋጅ በመጠቀም ጋዜጠኞች
ማሰሩን እንዲያቆም ጠይቀው የተያዙት እስረኞች ባስቸኳይ መፈታት አለባቸው ብለዋል። ቃል አቀባዩ የታሰሩትን ጋዜጠኞች በስም
ባይጠቅሱም በተለያዩ ቦታዎች አመጽ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ከወትሮ በተለየና ጠንከር ባለ ቋንቋ የአሜሪካንን ተቃውሞ
ማሰማታቸው ተጽእኖ ለማሳደር ነው የሚል ግምት የወሰዱ አሉ። ቃል አቀባዩ በቅርቡ በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው ርምጃ የአሜሪካንን
መንግስት ያሳሰበ መሆኑን ገልጸው የወያኔ መንግስት ባስቸኳይ ጋዜጠኞችንም ሆነ ሌሎች መብታቸውን ተጠቅመው ሀሳባቸውን በመግለጻቸው
ብቻ የተያዙ እስረኞች ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ይህ የአሜሪካ አቋም እንደሁልጊዜም ከመግለጫ ያለፈ እርባና እንደማይኖረው
በመግለጽ ብዙ ሰዎች ግምታቸውን ይሰጣሉ።፡
Ø
የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሀማዱ ቡሃሪ ረቡዕ ታኅሣሥ 20 ቀን
2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ከሁለት ዓመት በፊት ቦኮሃራም በተባለው አሸባሪ ድርጅት ተጠልፈው የተወስዱት ወደ 200 የሚደርሱ
የሴት ተማሪዎችን ሁኔታ የማያውቁ መሆናቸውን ገልጸው ልጃአገረዶቹን ለማስፈታት ከአሸባሪው ድርጅት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ
መሆናችውን ተናግረዋል። የዛሬ ሁለት ዓመት 276 የሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ቤታቸው ተጠልፈው የተወሰዱ መሆናቸውና 76
የሚሆኑት ወዲያውኑ አምልጠው ሲመለሱ ወደ 200 የሚጠጉት
እስካሁን የትእንዳሉ ሳይታወቅ መቆየቱ ይታወሳል። ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ ልጆቹ የት እና
በምን ዓይነት የጤንነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚያሳውቅ ምንም ዓይነት መረጃ ያልደረሳቸው መሆኑን ገልጸው የታሰሩትን ለማስፈታት
ከእውነተኞቹ የቦኮ ሃራም ድርጅት መሪዎች ጋር መደራደር የሚፈልጉ መሆኑን ገልጸዋል። ድርድሩን ለመጀመር ግን በቅድሚያ እውነተኛ
የድርጅቱ መሪዎች መሆናቸው መረጋገጥ አለበት ብለዋል። ቦኮሃራም ከቴክኒክ አንጻር ተሸንፏል በማለት ባለፈው ሳምንት ሚስተር ቡሃሪ
መግለጫ የሰጡ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ከዚያ ወዲህ
ታጣቂዎቹ ያካሄዷቸው ተከታታይ ጥቃቶችና ያደረሱት ጉዳት የፕሬዚዳንቱን መግለጫ ተአማኒነት አጠራጣሪ አድርጎታል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ የአካባቢው ንጉስና የኔልሰን ማንዴላ የቅርብ ዘመድ የሆኑት
ቡየለካያ ዳሊንዴይቦ ዘጎችን ጠልፎ በመውሰድና መኖሪያ ቤቶችን በማቃጠል ወንጀል ከተከሰሱ በኋላ ለሰሩት ወንጀል 12
ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው ወደ እስር ቤት የገቡ መሆናቸው ተነግሯል። ንጉሱ ወደ እስር ቤት የተላኩት ቀደም ብሎ የተፈረደባቸውን
ፍርድ ይግባኝ በማለት ያደረጉት ክርክር ውድቅ በመደረጉ ነው። የክሱ መነሻ ከ20 ዓመታት በፊት ከተከታዮቻቸው ጋር በነበራቸው
ግጭት ሲሆን የሰዎችን መኖሪያ ቤት በማቃጠል ሶስት ወጣቶችን በማስደብደብና የአንድ ተቃዋሚ የነበረ ግለስብ ሚስትና ልጆችን
በመጥለፍ ወንጀል ተከሰው ነበር። የአምሳ አንድ ዓመት ዕድሜ ያላቸው ንጉስ
በአካባቢው የቆየ ባህል መሰረት ንጉስ ተብለው የተሰየሙት በ1982 ዓም ሲሆን 700 ሺ የሚሆኑት የደቡብ አፍሪካ
ዜጎች ንጉስነታቸውን ተቀብለው በስራቸው የሚተዳድሩ መሆኑ ታውቋል። በደቡብ አፊሪካ
10 የሚሆኑ በይፋ እና በሕግ የታወቁ የአካባቢ ንጉሶች ይገኛሉ።
Ø
ከ20
ዓመት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ በተፈጸመው ከፍተኛ የሆነ የህዝብ እልቂት ላይ ተሳትፈው ነበር የሚባሉ አንድ የፔንቴኮስታል ቄስ
የሩዋንዳ ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት የፈረደባቸው
መሆኑ ተነገረ። ቄሱ ከአምስት ዓመት በፊት ኡጋንዳ ውስጥ በጥርጣሬ
ተይዘው ታንዛኒያ ውስጥ ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታውቋል። በታንዛኒያ
በሩዋንዳው እልቂት ጉዳይ ብያኔ ለመስጠት የተቋቋመው ኮሚቴ በዚህ ወር መጀመሪያ ስራውን አብቅቶ ሲዘጋ ቄሱ ወደሩዋንዳ
እንዲዛወሩ ተደርጎ ነበር። በቱሲዎች የሚመራው የሩዋንዳ
መንግስት ጉዳዩን ለማየት አይችሉም የሚል መከራከሪያ ቢያቀርቡም ወደ ሩዋንዳ ተዛውረው ክሳቸው ሊቀጥል ችሏል።
በክሱ መሰረት በ1987 ዓም ከዋና ከተማ ከኪጋሊ ዳርቻ ባለና ቄሱ
በሚያስተዳድሩት አንድ ቤት ክርስቲያን ዙሪያ የ2000 የሩዋንዳ ዜጎች ሬሳ መገኘቱና ለግድያ ቀሱ ተባባሪ እንደነበሩ በመረጋጡ
በአስራ ሁለት አመት እስራት እንዲቀጡ ፍርዱ ቤቱ የወሰነ ሲሆን ጠበቃቸው ብይኑን ይግባኝ እንደሚል ገልጿል። በሩዋንዳው እልቂት
ተሳታፊ ነበር የተባለ ሌላ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ባለፈው ወር በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መያዙ ይታወሳል።
Ø
በቅርቡ
በቡርኪና ፋሶ በተደረገው ምርጫ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የካምፒወሪ ቀኝ እጅ የነበሩት ሚስተር ሳሊፍ ዲያሎ የብሄራዊ ምክር ቤት መሪ
ሆነው መመረጣቸው ተነገረ። ከአንድ ቀን በፊት ሚስተር ክርሲያን ካቦሬ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል። ሁለቱ
ሰዎች የቀድሞ ፕሬዚዳንት አገልጋዮችና ባለስልጣኖች የነበሩ ቢሆንም ከሁለት አመት በፊት ከገዥው ፓርቲ ራሳቸውን በማግለል የሕዝብ
እድገት እንቅስቃሴ (Movemen of People Progress) የተባለ አዲስ ፓርቲ አቋቁመው በተቃዋሚነት መንቀሳቀሳቸው
ይታወቃል። ሚስተር ዲያሎ ለምክር ቤቱ መሪ ሆነው
የተመረጡት 127 መቀመጫ ካለው ምክር ቤት ውስጥ 78 ድምጽ በማግኘት ሲሆን ከተመረጡ በኋላ ባደረጉት ንግግር የምክር ቤት
አባሎች ሙስናንና የዝምድና አሰራርን እንዲዋጉ ጥሪ አድርገዋል። በአሁኑ ወቅት
የሁለቱ ሰዎች በከፍተኛ ስልጣን ላይ መቀመጥ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ደጋፊዎችንም ሆነ ተቃዋሚዎችን በማቀራረብ በአገሪቱ
ውስጥ ምቹ የፖሊቲካ ሁኔታ ሊፈጥር ይችላል የሚል አስተያየት የሚሰጡ አሉ።
ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ዛሬ ታኅሣሥ 20 ቀን
2008 ዓም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለህግ አውጭው ምክር ቤትና ለፕሬዚዳንቱ የስልጣን ቦታ ብሔራዊ ምርጫ መደረጉን
ከአካቢብው የተገኝው መረጃ ይገልጻል። ለፕሬዚዳንትነት ስልጣን የሚወዳደሩት ሰላሳ ሰዎች ሲሆኑ ከእኒዚህ ውስጥ ሶስቱ ቀዳሚ ቦታ
እንዳላቸው ታውቋል። የተባበሩት መንግስታት የሰላም አሰባሪ ኃይል አባሎች በየምርጫ ጣቢውያውና በአውራጎዳናዎች ተሰማርተው
ጸጥታውን ሲያስከብሩ የቆዩ ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች መዘግየት
ቢኖርም ብዙዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች በታቀደላቸው ጊዜ ተከፍተው መራጩን ሲያስተናግዱ ውለዋል። ከአምስት ሚሊዮን ሕዝብ መካከል
ለምርጫ የተመዘገበው 1.8 ሚሊዮን ነው የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ፡ድምጹን የሰጠው ሰው ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ እስከ አሁን
አልታወቀም። ለፕሬዚዳንትነት ቦታ ከሚወዳደሩት መካከል አሸናፊ የሚሆነው ከድምጹ ከአምሳ ከመቶ በላይ ያገኘ ብቻ ነው። ባሁኑ
ምርጫ ቀዳሚ ሆነው ከሚወዳደሩት መካከል ሊያሸንፍ ይችላል የሚለው ግምት የመነመነ በመሆኑ ምናልባት ሁለተኛ ዙር ምርጫ ሳይካሄድ
አይቀርም የሚሉ በርካታ ናቸው። የምዕራብ አፍሪካ ሪፐብሊክ
በክርስቲያን እና በእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል በተካሄዱ ግጭቶች በርካታ ሰዎች የሞቱ እና የተጎዱ ሲሆን
ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎችም ቤት ንብረታቸውን ጥለው
መሰደዳቸው ይታወቃል።
Ø
ባለፈው ሰኞ ታኅሣሥ
18 ቀን በዩጋንዳ የሰላም ውይይት ሲያደርጉ የነበሩ የብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎች አለምንም ውጤት ስብሰባውን ያጠናቀቁ ሲሆን ቀጣዩን
ስብሰባ ለማድረግ በመጨው ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓም በታንዛኒያ ከተማ አሩሻ ውስጥ
ለማድረግ የታቀደ
መሆኑን አደራዳሪዎቹ የዩጋንዳ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። የብሩንዲ መንግስት ተወካዮች በስበሰባው ወቅት ከመፈንቅለ መንግስት
አድራጊዎች ጋር ውይይት ለማካሄድ የሚያስቸግራችው መሆኑን መግለጻቸው የተጠቆመ ሲሆን የሚቀጥለው ስብሰባው መች ሊደረግ እንደሚችል
ስምምነት ላይ አለተደረሰም በማለት መግለጫ ሰጥተዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መሪ አዲስ አበባ ላይ
በሰጡት መግለጫ በሚቀጥለው ስብሰባ ላይ ያልተገኘ ወገን በአፍሪካ ኅበርት አገሮች ማዕቀብ የሚጣልበት መሆኑን
ተናግረዋል። የድርጅቱ ኮሚሽን መሪ ሚስስ ዙማ በሰጠቱ መግለጫ
የሚጣለው ማዕቀቡ ምን ሊሆን እንደሚችል ባይገልጹም በብሩንዲ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል የሚደረገውን ድርድር የሚያደናቅፍ፤ በታጣቂ
ኃይሎች አማ]ካይነት ወታደራዊ ጥቃቶችን በመንግስት ንብረቶች ላይ የሚፈጽም እና እንዲሁም ወደ እርቅ ጠረጴዛ ላይ ለመምጣት
ፈቃደኛ የማይሆን ወገን በሙሉ ማዕቀብ የሚጣልበት መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ኅብረት
5000 የሰላም አሰባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ መወሰኑና በማናቸውም መንገድ ለመላክ የቆረጠ መሆኑን
በተደጋጋሚ መግለጹና ይህንን የብሩንዲ መንግስት መቃወሙ ይታወሳል:: ዛሬ ታኅሣሥ 20 ቀን 2008 ዓም
ደግሞ የብሩንዲ ፕሬዚዳንት እንክሩንዚዛ ለብሩንዲ ሕዝብ በራዲዮና በቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር የአፍሪካ የሰላም
አስከባሪ ኃይል ወደ አገራቸው የሚላክ ከሆነ የአገሪቱን ሉዓላዊነት እንደደፈረ ወራሪ ኃይል ተቆጥሮ ውጊያ ሊገጥመው እንደሚችል
ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው በብሩንዲ ህገ መንግስት መሰረት የውጭ ኃይል ወደ አገሪቷ ሊገባ የሚችለው በአገሪቱ ውስጥ
የሚገኙ ተዋጊ ኃይሎች ሲጠይቁ ወይም በአግሪቷ ላይ በሕዝብ የተመረጠና ተቀባይነት ያለው መንግስት ከሌለ ብቻ ነው። ህጋዊ
መንግስት ባለበት ሁኔታ ወደ አግሪቱ የሚገባ ኃይል ሁሉ በጠላትነት የሚታይ ስለሆነ እንዋጋዋለን ብለዋል።
Ø
ባለፈው የፈረንጆች
ዓመት በዓለም የተለያዩ ቦታዎች 110 ጋዜጠኞች የተገደሉ መሆናቸውን ድንበር የለሽ ጋዜጠኞች የተባለው ድርጅት ማክሰኞ ታኅሣሥ
29 ቀን 2008 ዓም ባወጣው አመታዊ ዘገባ ገልጿል። 67
የሚሆኑ ጋዜጠኞች በስራ ላይ በነበሩበት ወቅት መገደላቸውን ድርጅቱ በዘገባው ላይ የገለጸ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 11 በኢራክ 10
በሶርያ እንዲሁም ደግሞ በፈረንሳይ አገር በቻርሊ አብዱ መጽሔት አዘጋጆች ላይ በደረሰው ጥቃት ሳቢያ 8 ጋዜጠኞች
መገደላቸውን ዘግቧል። 43 የሚሆኑ ጋዜጠኞች አገዳደላቸው ግልጽ
ባልሆኑ ምክንያት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሞቱ መሆናችውን ድርጅቱ ባወጣው ዘገባ ገልጿል። የተገደሉት ጋዜጠኞች ቁጥር ከሌሎች
ጊዜዎች ጋር ሲወዳደር ከፍተኛ መሆኑ የሚያመለክተው ጋዘጠኖች በአደጋ ሳይሆን ሆን ተብሎ እንደተገደሉ የሚያመልክት የድርጅቱ ዘገባ
የጠቀሰው ሲሆን የአብዛኞቹ ገዳዮች ደግሞ መንግስታዊ ያልሆኑ
የታጠቁ ክፍሎች መሆናችው በዘገባው ተካቷል። ድርጅቱ
የጋዘጠኞችን ህይወት ለመጠበቅ በዓለም አቀፍ ደረጃ አስፈላጊው እርምጃ መወሰድ እንዳለበትም አሳስቧል።
ታኅሣሥ 19 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የጋዜጠኞችን ደህንነት
ለመንከባከብ የተቋቋመው ሲፒጄ የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ትናንት ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም. ባወጣው መግለጫ
በቅርቡ በወያኔ አገዛዘ የተያዙት ሁለት ጋዜጠኞች ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም በወያኔ
አገዛዝ ቁጥጥር ስር የዋለው የኦሮሞ ራዲዮና ቴሌቪዥን ስርጭት ዜና አንባቢ የሆነው አቶ ፊቃዱ ሚርካና እና አርብ ታኅሣሥ 15
ቀን የተያዘው የነገረ ኢትዮጵያ አዘጋጅ አቶ ጌታቸው ሽፈራው በወያኔ የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው የታሰሩት በቅርቡ የአዲስ አበባን
ማስተር ፕላን በመቃወም ስለተቀሰቀሰው ሕዝባዊ አመጽ ዜና ዘግባችኋል በሚል ክስ ሲሆን የጋዜጠኖች ተንከባካቢ ድርጅቱ ባስቸኳይ
እንዲለቀቁ በመግለጨው ጠይቋል። መግለጫው አክሎ መሰረታዊ ሕዝብ መረጃ የማግኘት መብቱና ሌሎችም መሰረታዊ የሆኑት ሰብአዊ መብቶች
ሳይከበሩ ስለ እድገት ማውራት ብዙ ትርጉም የሌለው መሆኑ በመግለጽ በወይኔ አገዛዝ ላይ ወቀሳ አቅርቧል። በተጨማሪ ድርጅቱ
በመግለጫው ከሁለት ወራት በፊት በፍርድ ቤት ነጻ የሆኑት አራቱ የዞን 9 ጦማርያን በአቃቤ ህጉ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት
እንደገና ፍርድ ቤት መቅረባቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት
የአለም አቀፉ የጤና ድርጅት ደብሊው ኤች ኦ (WHO) ጊኒ ከኢቦላ
በሽታ ነጻ መሆኗን የሚያረጋግጥ ምስክርነት የሰጠ መሆኑ ተረጋገጠ። ለሁለት አመት ጊዜ በበሽታው ሲሰቃይ የነበረውና በግንኙነትና
በኢኮኖሚ በኩል ከፍተኛ ችግር የገጠመው የጊኒ ሕዝብ ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ከበሽታው ነጻ መሆኑን ማረጋገጫ በማግኘቱ
በርችትና በዘፈን ደስታውን ደስታውን ይገልጻል በሚል እየተጠበውቀ ነው።
ባጠቃላይ 2ሺ 5 መቶ የሚሆኑ የጊኒ ዜጎች በበሽታው ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በሲየራ ሊዮንና በላይቤሪያ 9 ሺ ሰዎች ህይወታቸውን
አጥተዋል። ሲየራ ሊዮን ባለፈው ወር ከኢቦላ ነጻ መሆኗን
የሚያበስር ማረጋገጫ ከዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ያገኘች መሆኗ የሚታወስ ሲሆን ባለፈው መስከረም ወር ነጻ መሆኗ ማረጋገጫ
በተሰጣት በላይቤሪ ግን አዳዲስ የኢቦላ በሽተኞች መገኝታቸው ታውቋል።
Ø
ባለፈው መስከረም ወር
በቡርኪና ፋሶ የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ታስረው የሚገኙትን ጄኔራል ዲየንዴሬን እና ጓደኞቻቸውን ለማስፈታት ጥረት አድርገዋል
ተብለው የተጠረጠሩ 20 ወታደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታወቀ። ወታደሮቹ ሰኞ ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓም ጄኔራሉንና ሌሎች
በመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ የተያዙትን እስረኞች በእስር ቤቱ ላይ ወረራ በማካሄድ ያቀዱት ሴራ ተጋልጦ ወደ 20 የሚጠጉ ወታደሮች
በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆናችው ታውቋል። በቅርቡ የአገሪቷ
ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ሚስተር ካቦሬ ስለወታደሮቹ መያዝ ባደረጉት ንግግር ቀደም ብለው በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በቁጥጥር
ስር የዋሉት ሁሉ ፍርዳቸውን ያገኛሉ። እንዲህ ዓይነት የወንጀል ሙከራ እቅዱ ገና ተግባር ሳይውል ሊጋለጥ እንደሚችል ሁሉም
ሊገባው ይገባል ብለዋል። በጥቅምት ወር ተሞክሮ በነበረው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በጠቅላላው 57 ሰዎች የተከሰሱ ሲሆን ከዚሁ
ውስጥ ጄኔራሉን ጨምሮ 20 ዎቹ የቀድሞ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ
ወታደራዊ ተቋም አባላት መሆኗቸው ታውቋል።
Ø
ሰኞ ታኅሣሥ 18 ቀን
2008 ዓም በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ግዛት በማዳጋሊ በሚባለው ከተማ ሁለት የሴት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 25 ሰዎች
መግደላቸው ታወቀ። በተጨማሪ አዋሳኝ በሆነው የቦርኖ ግዛት
የአሸባሪው ቡድን አባላት ባካሄዱት የተለያዩ ጥቃቶች 30 ሰዎች
መሞታችውና ከ100 በላይ የሆኑ ሰዎች መቁሰላቸው ከቦታው የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ባለፈው ሳምንት የናይጄሪው ፕርዚዳንት
ከቴክኒክ አንጻር ቦኮ ሃራም ተደምስሷል የሚል መግለጫ መስጥታቸው የሚታወስ ሲሆን የሰሞኑ የአሸባሪው ድርጅት ተከታታይ
ጥቃቶች
ድርጅቱ አሁኑም ህልውና እንዳለው የሚገልጽ
መልእክት ለማስተላለፍ ነው ተብሏል።
Ø
ዛሬ ታኅሣሥ 19 ቀን
2008 ዓም ከ21 አመት በፊት በሩዋንዳ ውስጥ የአንድ ከተማ ከንቲባ የነበረ ግለሰብ
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብሰበው የነበሩ ከ400 በላይ የሆኑ የቱሲ ተወላጆችን
ማስገደሉ በመረጋገጡ የጀርመኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት ፈርዶበታል። የዛሬ ሁለት አመት ግለስቡ በሰራው
ወንጀል በዝቅተኛ ፍርድ ቤት የአስራ አራት አመት እስራት ፈርዶበት የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም የፌዴራል አቃቤ ህጉ ቅጣቱ
ከሰራው ወንጀል ጋር ተመጣጣኝ አይደለም በሚል ምክንያት ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበው ይግባኝ ግለሰቡ የእድሜ ልክ እስራት
ሊፈረድበት ችሏል።
ታኅሣሥ 18 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የብሩንዲ ተጻራሪ
ኃይሎች ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን 2008 ዓም በዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፕላ ውስጥ የእርቅ ድርድር ለማድረግ መሰብሰባቸው
ተገለጸ። የብሩንዲው መንግስት ተወካዮች የሚመራው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሲሆን የተቃዋሚው ክፍል የህብረት ድርጅት መሪዎች
ተቃዋሚውን ክፍል እንደሚወክሉ ታውቋል። የሲቪክ ማህበረ ሰብ አባላትና የሃይማኖት ድርጅት መሪዎችም በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል።
ስብሰባውን የሚመሩት የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮወሪ ሙሰቨኒ ሲሆኑ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ባሰሙት ንግግር ሁለቱ ወገኖች ግልጽ
ውይይት አድርገው እንዲስማሙና ሕዝባቸውን ከእልቂት እንዲያድኑ ተማጽነዋል። ተቃዋሚውን በመወከል በስብሰባው ላይ የተገኙት
ተደራዳሪዎች ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ እንዲካሄድ ብሩንዲ ውስጥ በመንግስት ወታድሮች የሚደረገው ግድያ መቆም ያለበት መሆኑን ገልጸው
ሕዝብ እየሞተ ድርድር ማካሄድ አይቻልም ብለዋል። እስካሁን ድረስ የብሩንዲ መንግስት ተቃዋሚውን አሸባሪ ናቸው ብሎ በመሰየም
ድርድር ለማካሄድ ፈቃደኛ እንዳልነበር ይታወቃል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 5 ሺ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ
ለመላክ የወሰነውን ውሳኔ የብሩንዲ መንግስት ወራሪ ኃይል ነው በማለት የማይቀበለው መሆኑን ቢገልጽም የአፍሪካ ህብረት በማናቸውም
መንገድ የሚልክ መሆኑን አስታውቋል።
Ø
እሁድ ታኅሣሥ 27 ቀን
2008 ምሽት ላይ በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ ካለችው ከማይዱጉሪ ከተማ አጠገብ በምትገኝ አንዲት መንደር ውስጥ የቦኮ ሃራም
ታጣቂዎች ባካሄዱት ጥቃት 21 ሰዎች መግደላቸውንና 91 ሰዎች ማቁሰላቸውን የአካባቢው ባለስልጣኖች ለዜና ምንጮች ከሰጡት መረጃ
ለማወቅ ተችሏል። ታጣቂዎች በሶስት ከባድ መኪናዎች ላይ ተጭነው ወደ መንደሯ በመግባት በእሩምታ ተኩስ ባደረሱት ጥቃት በርካታ
ሰዎች ሊሞትና ሊቆስሉ ችለዋል። በአካባቢ የነበረው የመንግስት ወታደሮች ባደረጉት የአጸፋ ተኩስ 10 ታጣቂዎች የገደሉ መሆናቸውን
አስታውቀዋል። ሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን ጠዋት አንዲት አጥፍቶ
ጠፊ ወደ መስጊድ ለመግባት የሚካሄድውን ፍተሻ ለማለፍ ሰልፍ ተሰልፋ እንዳለች
ባፈነዳችው ቦምብ አንደ ሰው ገድላ ሌሎች ስድስት ሰዎች ያቆሰለች መሆኗን በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን እማኞች
ተናግረዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦኮሃራም ከቴክኒክ አንጻር ተደምስሷል ይበሉ እንጅ አሸባሪው ቡድን
አሁንም ጉዳቶችን እያደረሰ መሆኑ ይታያል።
Ø
በሰሜን ምስራቅ ኬኒያ
ትናንት እሁድ ታኅሣሥ 27 ቀን 2008 ዓም የታጠቁ ሰዎች በሰነዘሩት ጥቃት ሁለት ፖሊሶች የተገደሉ መሆናቸውንና ሌሎች ሁለት
ፖሊሶች መቁሰላቸውን የኬኒያ የቀይ መስቀል ድርጅት ከአካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። ለጥቃቱ
ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም በአካባቢው በተደጋጋሚ ጉዳት ያደረሰው አልሸባብ እንደሆነ ይጠረጠራል። ባለፈው ሳምንት ላይ
የኬኒያ ፖሲሶች አልሸባብ በአልካይዳና በአይሲስ ደጋፊነት እየተከፋፈለ መሆኑን ገልጸው አክራሪዎቹ በኬኒያ ላይ አዲስ የጥቃት
ዘመቻ ሊከፍቱ የሚችሉ መሆናቸውን ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
የአይሲስ ደጋፊ የሆኑት በኬኒያ ሰሜን ምስራቅ በማንዴራ ግዛት ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ የደረሱበት መሆናቸውን ገልጸዋል።
Ø
ባለፈው ቅዳሜ ታኅሣሥ
26 ቀን 2008 ዓም የቢኒንን ጠቅላይ ሚኒስትር ይዛ የነበረች አንዲት ሄሊኮፕተር ተከስክሳ
የወደቀች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አለምንም ጉዳት ከአደጋው ሊድኑ
የቻሉ መሆናቸው ታውቋል። አውሮፕላኑ ለምን እንደወደቀ እየተመረመረ ሲሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አባትን ጨምሮ በሂሊኮፕተሩ ውስጥ
የነበሩት ሰዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ቀርተዋል። የቤኒንና የፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላቸው የቤኒኑ ጠቅላይ ሚኒስትር
የቀድሞ የባንክ ሰራተኛ ሲሆኑ በሚቀጥለው የካቲት በሚደረገው የአገሪቱ ምርጫ ለፕሬዚዳንትነት ይወዳደራሉ ይባላል።
ታኅሣሥ 16 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በሱዳን በአልጋዳሪፍ
የክልል አስተዳድር የአንድ አካባቢ የምክር ቤት ተወካይ የሆኑ ሰው ለሱዳን ዜና ምንጮች በሰጡት መግለጫ ባለፈው ወር ብቻ
በድንበር አካባቢ 45 ሱዳናውያን በታጠቁ ኢትዮጵያውያን ተግድለዋል ብለዋል። በርካታ የሱዳን ዜጎች ታፍነው የተወሰዱ መሆኑን
ገልጸው የሱዳን ገበሬዎችን መግደል፤ ማሰርና፤ ከእርሻ ቦታቸው ላይ ማስነሳት የተለመደ ነው በማለት ተናግረዋል።
ባለፈው ወር የሱዳን ባለስልጣኖች ኢትዮጵያውያንን አባርረን
100 ሄክታር የሱዳን መሬት መልሰን ተቆጣጥረናል በማለት ያስራጩት
ዜና ሀሰት ነው በማለት አስተባብለዋል። “ከ2 ሚሊዮን ኤከር በላይ የሚሆነውን የሱዳን የእርሻ መሬት ተወስዶ የእኛ መንግስት
አንቀላፍቷል” በማለት ቅስቀሳ አዘል ንግግር አድርገዋል። በወሰን አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በወያኔ ወታደሮች ጥቃትና ተጽእኖ
የሚደርስባቸውን ተጽእኖ ተቋቁመው መሬታችውን ለማስመለስ የሞትና የሸረት ትግል እያካሄዱ መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን በርካታ
መስዋእትነትም እንደከፈሉ ይታወቃል። የወያኔ አገዛዝ የሱዳን መንግስት የጠየቀውን ሰፊ የኢትዮጵያ
መሬት ለማስርከብ መስማማቱ ቀደም ብሎ የተገለጸ ሲሆን አንድ
የወያኔ ከፍተኛ የመልክተኞች ቡድን ሐሙስ ታኃሣስ 13 ቀን
2008 ዓም ማታ ብሉል ናይል በሚባለው የሱዳን የአስተዳደር ክልል የገባ መሆኑ ከአካባቢው ከተገኘ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ወያኔ
የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለማስረከብ ያቀደውን እቅድ በመቃወም በርካታ ወገኖች ተቃውሞ ያሰሙ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን ኢሕአፓና
ሌሎች የፖሊቲካና የሲቪክ ድርጅቶ ለተመድ ዋና ጸሐፊ የተቃውሞ ደብዳቤ መጻፋቸው ይታወሳል።
Ø
የአፍሪካ ኅብረት ወደ
ብሩንዲ የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የወሰነው ውሳኔ የብሩንዲ መንግስት እንዲቀበል በድጋሚ ደብዳቤ የጻፈ መሆኑ የድርጅቱ
ጽህፈት ቤት በትናንትናው ዕለት በይፋ ገልጿል። ድርጅቱ 5000 የሚሆኑ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ
የወሰነው አገሪቱ ወደ አጠቃላይ የእርስ በርስ ጦርነት እንዳትገባ ለመከላከልና
የሕዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ እንጅ ለሌላ
ድብቅ ለሆነ ዓላማ እንዳልሆነ የድርጅቱ ባለስልጣኖች ተናግረዋል። የብሩንዲ መንግስት የአፍሪካ ኅብረት ለመላክ ያሰበውን የሰላም
አስከባሪ ኃይል ወራሪ ኃይል ነው በማለት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ውሳኔን ውድቅ ማድረጉ ይታወቃል። በብሩንዲ ውስጥ ችግር
ከተፈጠረ ካላፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ወዲህ በእርስ በርስ ግጭት ከ400
በላይ ሰላማዊ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውና በመቶ ሺ የሚቆጠሩ
ለስደት መዳረጋቸው የሚታወቅ ሲሆን። በቅርቡ ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀስ አንድ የታጠቀ የአማጽያን ቡድን ህልውናውን ይፋ
ማድረጉ ይታወሳል።
Ø
የደቡብ ሱዳን መንግስት
ያሉትን አስር የአስተዳደር ክልሎች ወደ 28 የአስተዳድር ክልሎች ለመለወጥ የወሰነው ውሳኔ በርካታ ተቃውሞ እየደረሰበት መሆኑ
ተገለጸ። የአስተዳድር ክልሎችን ለመለወጥ ስልጣን ያለው
አካል የህግ አውጭ ምክር ቤቱ እንጂ አስተዳደሩን የያዘው መንግስት ስላልሆነ የሳልቫኬር መንግስት የወሰነው ውሳኔ ህገ መንግስቱን
ይጥሳል ተብሏል። ቀደም ብሎ በአፍሪካ ህብረት አማካይነት በደቡብ ሱዳን መንግስትና በአማጽያኑ መካከል የተደረገው ስምምነት
መሰረት ያደረገው አስር የአስተዳደር ክልሎችን በመሆኑ የአሁኑ የመንግስቱ ውሳኔ ስምምነቱን ሊያፈርስ ይችላል የሚል አስተያየትም
እየተሰጠ ነው። የአማጽያኑ የአመራር አካሎች በተናጠል የመንግስቱን ውሳኔ የተቃወሙት ሲሆን ምን ዓይነት እርምጃ እንደሚወስዱ
እየተመካከሩ ነው ተብሏል። ስምምነቱን በተግባር ለማስፈጸም ባለፈው ሰኞ በ150 የአማጽያን ተወካዮች የሚገኙበት ቀዳሚ
ቡድን ጁባ የገባ መሆኑ ይታወሳል። በተያያዘ ዜና በደቡብ ሱዳን 3.1 ሚሊዮን ሕዝብ በከፍተኛ የምግብ ችግር ላይ
መሆኑን የተመድ አካል የሆኑት የምግብና የእርሻ ድርጅት
(FAO) የሕጽናት ተንከባካቢ ድርጅት (UNICEF) እና የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።
ባሁኑ ወቅት ቢያንስ 30 ሺ የሚሆኑት በምግብ እጥረት ምክንያት የሞት አደጋ ሊያጋጥማችው የሚችል ሲሆን ባጠቃላይ 3.1 ሚሊዮን
የሚሆኑት በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተጠቁሟል።
ታኅሣሥ 15 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በናይጄሪያ ደቡብ
ምስራቅ በምትገኘው ኒዊ በምትባለው ከተማ አንድ ቡታ ጋዝ የጫነ ቦቴ በጋዝ ማከፋፊያ ፋብሪካ አጠገብ በመፈንዳቱ ምክንያት በርካታ
ሰዎች መሞታቸውና መጎዳታቸው ተገለጸ። ከሞቱት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ የጋዝ ዕቃቸውን ለማስሞላት የተሰለፉ ሲሆን ሰራተኞችና
በአካባቢው የሚኖሩ ነዋሪዎች ይገኙበታል። አንዳንድ ዘገባዎች የሞቿቹን ቁጥር ከ35 በላይ የሚል መረጃ ሲያቀርቡ ሌሎቹ ከ100
በላይ እንደሆኑ ይገልጻሉ። በአካባቢው የሚገኙ የዓይን እማኞች
ለዜና ምንጮች በሰጡት መረጃ እሳቱ ሊያያዝ የቻለው የቦቴው ሞተር ገና ሳይበርድ ጋዙን ለማራገፍ በመሞከሩ ነው ይላሉ። በአደጋው
ጉዳት የደረሰባችው ሰዎች ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆኑ የሟቹ ቁጥር ሊጨምር ይችላል የሚል ስጋት አለ። በገና በዓል ምክንያት
በርካታ ሰዎች ጋዝ ለማስሞላት በቦታው ተገኝተው እንደነበር ታውቋል።
Ø
የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳን
ሳልቫ ኬር ተጨማሪ የአስተዳደር ክልሎችን በመፍጠራቸውና ገዥዎችን
በመሰየማቸው ከጥቂት ወራት በፊት ከተጻራሪው ቡድን ጋር የተፈረመው ስምምነት አደጋ ሊደርስበት ይችላል ተብሏል። ቀደም ብሎ
የነበረውን 10 የአውራጃ አስተዳደር ወደ 28 የአስተደድር ክልሎች ከፍ በማለታቸውና ለእየአንዳንዳቸው አስተዳዳሪ በመሾሙ
ስምምነቱ መሰረት ያደረገበትን የክልል ክፍፍል ዋና መርህ ያፈርሳል ተብሎ ይገመታል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በስምምነቱ
መሰረት የሽግግሩን ሂደት ለማመቻቸት በሚደረገው ንግግር ላይ ለመሳተፍ በተቃዋሚ ኃይል የተላከው ቀዳሚ ተደራዳሪ ቡድን ጁባ የገባ
መሆኑ የተገለጸ ቢሆንም አሁን የሳልቫ ኬር መንግስት እየወሰደ ያለው እርምጃ ንግግሩን ዋጋ ያሳጣዋል የሚሉ በርካታ ናቸው።
የተጻራሪ ቡድን ሪክ ማቻር ሐሙስ ዕለት በሰጡት መግለጫ በደቡብ ሱዳን ጦርነት መቆሙን የገለጹ ሲሆን ለተቀናቃኛቸው ለሳልቫ ኬር
መልካም የገና በዓልን በማንተራስ የመልካም ምኞት መልእክት
አስተላልፈዋል። ይሁኑ እንጅ ረቡዕ ዕለት በላይኛው የናይል ግዛት ውጊያ እንደነበር ሁለቱም ወገኖች ገልጸዋል። በአማጽያኑም ሆነ
በመንግስት ኃይሎች ቁጥጥር ስር ያልሆኑ በርካታ የሆኑ ታጣቂ ኃይሎች በመኖራቸው ስምምነቱን በስራ ላይ ለማዋል አስቸጋሪ ነው
በማለት አስተያየት የሚሰጡ ብዙ ናችው። ተደረገ በተባለው ስምምነት ከመነሻው እምነት ያልነበረው የሳልቫ ኬር መንግስትም ስምምነቱ
ሊፈርስ ይችላል ከሚል ግምት ለጠቅላላ ጦርነት እየተዘጋጀ ነው የሚል መረጃ ከየአቅጣጫው እየተሰማ ነው።
Ø
በሚቀጥለው እሁድ
ታኅሣሥ 17 ቀን 2008 ዓም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው ብሔራዊ ምርጫ ለታኅሣሥ 20 ቀን እንዲተላለፍ
የአገሪቱ የሽግግር መንግስት ባለስልጣኖች ሀሳብ ያቀረቡ መሆናቸው ታወቀ። በመጭው እሁዱ ታቅዶ በነበረው ምርጫ ለሚቀጥለው የምርጫ
ዘመን የሚያገለግሉ የአገሪቱ ፕሬዚዳንትና የምክር ቤት አባላት ለመመረጥ የተቃደ እንደነበር ተገልጿል። ባለስልጣኖቹ ምርጫው
ከእሁድ ወደ ረቡዕ እንዲተላለፍ የጠየቁበት ዋናው ምክንያት የምርጫውን ሂደት ለማዘጋጀትና የምርጫ አስፈጻሚዎችን ለማሰልጠን በቂ
ጊዜ ለማግኘት ነው ተብሏል። በአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ምርጫዎች መካሄድ ያለባቸው በእሁድ ቀኖች በመሆኑ ምርጫው
ረቡዕ ዕለት እንዲካሄድ የአገሪቱ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት ልዩ ሁኔታ ነው ብሎ መፍቀድ ይኖርበታል። ምርጫው ለሶስት ቀን
እንዲራዘም መጠየቀኡ ችግርን የሚያመላክት አይደለም በማለት የተመድ ባለስልጣኖች የተናገሩ ሲሆን በአገሪቱ ውስጥ በሚገኘው
ያልተረጋጋ ሁኔታ ምክንያት ምርጫው በተቻለ መጠን በጥንቃቄ መካሄድ አለበት ብለዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት ሕገ መንግስቱን
ለማጸደቅ በተካሄደው ምርጫ 93 ከመቶ የሚሆነው መራጭ ሕገ መንግስቱን ደግፎ ማጽደቁ ሕዝቡ ለሰላምና ለተረጋጋ ሁኔታ ያለውን
ፍላጎት ያሳያል ተብሏል።
Ø
በብሩንዲ አዲስ
የአማጽያን ድርጅት ተፈጥሯል ተብሎ መነገሩ አገሪቱን ወደ አጠቃላይ
የእርስ በርስ ጦርነት እየወሰዳት ነው የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው። በአንድ የቀድሞ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን የሚመራ
የብሩንዲ ሪፐብሊካን ኃይሎች (The Republican Forces of Burundi) የተባለ የአማጽያን ድርጅት የተቋቋመ መሆኑን
የዜና ምንጮች ገልጸዋል። የድርጅቱ ዋና ዓላማና ተልእኮ መብታቸውን ተጠቅመው ተቃውሟቸውን ያሰሙ ዜጎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች
የሚደርስባቸውን ጥቃት ለመቋቋምና የፕሬዚዳንት ኩርንዚዛን መንግስት ማስወገድ ነው ተብሏል። የድርጅቱ መሪ ለዜና ምንጮች በሰጡት
መግለጫ ከጥቂት ቀናት በፊት በብሩንዲ ዋና ከተማ በሶስት ወታደራዊ የጦር ሰፈሮች ላይ የተደረጉት የጥቃት ወረራዎች በዚህ ድርጅት
አማካይነት የተደረጉ መሆናቸውን ገልጸው በርካታ ወታደሮችና ዜጎች ድርጅቱን ተቀላቅለው እየተዋጉ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ታኅሣሥ 14 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የናይጄሪው ፕሬዚዳንት
ቡሃሪ ቦኮ ሃራምን ለመደምሰስ ለአገሪቱ የመከላከያ ኃይል የሰጡት ቀነ ቀጠሮ ጥቂት ቀናት የቀሩት መሆኑ የታወቀ ሲሆን
ከቢቢሲ ጋዘጠኛ ጋር ፕሬዚዳንቱ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ከቴክኒክ
አንጻር ቦኮ ሃራም ተሸንፏል በማለት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ ገለጻቸውን በመቀጠል “ቦኮ ሃራም ቦምቦችን በማፈንዳት አንዳንድ
ጥቃት እያደረሰ ቢሆንም በመደበኛ የውጊያ ስልት የመዋጋት አቅሙ በከፍተኛ ደረጃ ተሰብሯል” ብለዋል። ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ከተመረጡ
ወዲህ ቦኮሃራም ከበርካታ ቦታዎች እንዲወጣ የተደረገ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በአጥፍቶ ጠፊዎች በሚፈነዱ ቦምቦች
ጥቃት እየፈጸመ መሆኑና እና አንዳንድ የልማት ስራዎችን የማውደም
ስራውን የቀጠለ መሆኑ ይታወቃል። በቅርቡ የተባብሩት
መንግስታት የህጻናት ተንከባካቢ ድርጅት ዩኒሴፍ በቦኮ ሃራም ጥቃት ብቻ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የናጄሪያ ህጻናት
ከትምህርት አለም የተገለሉ መሆናቸውን ገልጿል።
Ø
በቡርኪና ፋሲ አንድ
ወታደራዊ ፍርድ ቤት የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደራዊ ጠባቂ ተቋም የቀድሞ መሪ የነበሩት ሚስተር ካፋንዶ ከ28 ዓመት በፊት
የቀድሞውን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራን ገድለዋል የሚል ክስ ያቀረበባቸው ከመሆኑ በላይ ግለስቡ ባስቸኳይ ተይዘው
እንዲታሰሩ ትእዛዝ ያስተላለፈ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ በሕዝባዊ አመጽ ከስልጣን የተወገዱትና
አሁን በአይቮሪ ኮስት በስደት ላይ የሚገኙት ካምፕዌሬም ሚስተር
ሳንካራን በማስገደል በኩል ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል በሚል የተከሰሱ ሲሆን ግለሰቡን አስሮ ወደ ቡርኪና ፋሶ እንዲመልሳቸው የአይቮሪ
ኮስት መንግስት የተጠየቀ መሆኑ ታውቋል።
Ø
በማሊ መንግስቱን
የሚደግፍ አንድ የታጣቂ ቡድን አራት የሚሆኑ አባላቱ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በፈረንሳይ ወታደሮች የተገደሉ መሆናቸውን ገለጸ።
ባለፉት ቀናት በማሊ የሚገኘው የፈረንሳይ ወታደራዊ ኃይል 10 ጂሃዲስቶችን መግደሉ ማስታወቁ የሚታወቅ ሲሆን የመንግስት ደጋፊ
የሆነው ታጣቂ ቡድን አራት የሚሆኑ
አባላቱ በፈረንሳይ ወታደሮች መገደላቸውን በመጥቀስ የወነጀለ መሆኑ
ታውቋል። ቡድኑ በወገን ላይ በስሀተት የተደረገ እርምጃ ነው በማለት የሚናገሩት የፈረንሳይ ወታደሮች በአካባቢው ተገኝተን
ጂሃዲስቶችን እንዳንዋጋ ከልክለውናል ብሏል። የፈረንሳይ ወታደራዊ ቃል አቀባይ የታጣቂ ቡድኑን ክስ ያስተባበለ መሆኑን ኤኤፍፒ
የተባለው የፈረንሳይ የዜና ምንጭ ገልጿል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት ማሊ የሚገኘውን የሰላም ማስከበር ተልኦኮ እንዲመሩ የቀድሞውን የቻድ የውጭ ጉድይ ሚኒስትር ሚስተር አናዲፍን መሾሙን
አስታውቋል። ሚስተር አናዲፍ ቀደም ብለው በማዕከላዊ
አፍሪካ ሪፐብሊክ በናይጀርና በሱዳን የሰላም ማስከበር ተልእኮን በመምራት ያገለገሉ ሲሆን በሱማሊያ ለሚገኘው የተመድ የሰላም
አስከባሪ ኃይል ዋና ሹም በመሆን የሰሩ መሆናቸው ታውቋል። ሚስተር አናዲፍ የሚተኳቸው የቱኒዚያው ዜጋ የሆኑት ሚስተር ሃማዲ ማሊ
ውስጥ በቱዋረግ ሚሊሺያዎች እና በመንግስቱ መካከል የእርቅ ስምምነት እንዲፈረም በማድረግ በኩል ቁልፍ ሚና ቢጫወቱም
እርቅን ለማምጣት መከናውን ያለባቸውን የመሸጋገሪያ ስራዎች
በተገቢው መንገድ በስራ ላይ እንዲውሉ ባለማድረጋቸው የቱዋረግ አማጽያን እንደገና ጥቃት መፈጸም የጀመሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በማሊ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ የቻድ ወታደሮች ቁጥር
ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትናንት ረቡዕ ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓም. ባደረገው ስብሰባ በቅርቡ ሞሮኮ ውስጥ ሁሉቱ የሊቢያ
ተጻራሪ መንግስታት የፈረሙትን ስምምነት የደገፈ መሆኑ ታወቀ።
ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡ የቀረበው በእንግሊዙ የተመድ አምባሳደር ሲሆን 15 ቱም የተመድ የጸጥታ ምክር ቤት አባላት ደግፈውታል።
የእንግሊዙ አምባሳደር የውሳኔው ሀሳብ ከጸደቀ በኋላ ባደረጉት ንግግር ስምምነቱ ሊቢያን ወደ ሰላምና የብልጽግና ጎዳና የሚወስዳት
ሲሆን በአገር ውስጥ እየተስፋፋ የሄደውን የዳኤሽ እንቅስቃሴ ለመግታትና የስደተኞችንም በር ለመዝጋት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል
ብለዋል። በሊቢያው የእርቅ ስምምነት ላይ ፊርማቸውን ያላኖሩት ወገኖችም ሁኔታውን ተረድተው ባስቸኳይ ፊርማቸውን እንዲያኖሩ ጥሪ
አቅርበዋል።
ታኅሣሥ 13 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የሶማሊያ መንግስት
የፈረንጆ ገናን በዓልን አስመልክቶ ይፋ የሆኑ ፓርቲዎችና ድግሶች እንዳይደረጉ
ያዘዘ መሆኑ ታወቀ። የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጠው መግለጫ የገናን በዓል ለማክበር የሚደረጉት ድግሶችና
ፓሪቲዎች ከእስልምና ጋር የተያያዙ ባለመሆናቸው በሆቴል ውስጥም ሆነ በሌሎች ሕዝብ በብዛት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች መደረግ
የማይችሉ መሆኑን ገልጿል። የሶማሌ የጸጥታ አባላት የገናን በዓል ለማክበር የሚሞከሩ ስብስቦችን ለመበተን ትእዛዝ የተሰጣቸው
መሆኑም አስታውቋል። የውጭ ዜጎች በየቤታቸው በዓሉን ለማክበር የተፈቀደላቸው ሲሆን የሰላም አሰባሪ ኃይል አባሎችም በየጦር
ሰፈሮቻቸው እንዲያከብሩ ትእዛዝ ተሰጥቷል። በገና በዓል ጊዜ በውጭ አገር የተወለዱ እና በውጭ አገር ያደጉ የሱማሊያ ዜጎች
ለእረፍት በብዛት ወደ አገራቸውን የሚመጡ ስለሆነ ባደጉትበት ባህል የገና በዓል ፓርቲና ድግስ ያካሄዳሉ የሚል ፍራቻ አለ።
የሶማሊያ መንግስት ይህንን መግለጫ ሲሰጥ የእስልምና ሃይምኖትን እንደምክንያት ይጠቀም እንጅ
አልሸባብ በዓሉን ለማክበር በሚደረገ ስብሰባዎች ላይ የጥቃት እርምጃ ይወስዳል የሚስል ስጋት
ዋናው ምክንያት መሆኑን የሚናገሩ በርካታ ናቸው።
Ø
የፈረንሳይ የመከላከያ
ሚኒስቴር ከፓሪስ በሰጠው መግለጫ ባለፈው ቅዳሜ ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም. በማሊ የሚገኙት የፈረንሳይ ወታደሮች በአገሪቱ
ምስራቃዊ ክፍል ከምትገኘው ከሜናካ ከምትባለው ከተማ አጠገብ ወታደራዊ ጥቃት ፈጽመው 10 የእስላማውያን ታጣቂዎች ቡድን አባላትን
የገደሉ መሆናቸውን አስታውቋል። ሙራቡቲን (Murabutin) የሚባለው ይህ ጽንፈኛ ድርጅት በማሊ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃት
ሲፈጽም የቆየ መሆኑ ሲታወቅ ባለፈው ወር በዋናው ከተማ ባማኮ በራዲሰን ሆቴል ላይ ባካሄደው ጥቃት 22 ሰዎች መገደላቸው
ይታወሳል። በማሊ ውስጥ ያለው የጸጥታ ስጋት እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት ባለፈው
ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓም የማሊ መንግስት ለአስር ቀናት የሚቆይ የተጠንቀቅ አዋጅ ያወጀ መሆኑ ተነግሯል።
Ø
ከጥቂት ቀናት በፊት
በናይጀሪያ ወታደሮች የተገደሉት ከ300 በላይ የሚሆኑ
የሺያ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ሁኔታ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው የተገኙ
መሆናቸውን ሂውማን ራይትስ ዎች የሚባለው የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ ድርጅት አጋለጠ። የወታደሩ ክፍል በሺያ እምነት
ተከታዮች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ያስገደደው ምክንያት አማኞቹ መንገድ በመዝጋት የወታድሩን መሪ ጄኔራል ለመግደል ሙከራ
በማድረጋቸው ነው የሚል ምክንያት የሰጠ ቢሆንም ቁጥራቸው ከ300 በላይ የሆኑትን የሺያ እምነት ተከታዮች ለመግደል ይህ ምክንያት
ሊሆን እንደማይችል የሰብአዊ መብት ድርጅቱ ኃላፊ አቶ ዳንኤል በቀለ ገልጸዋል። አቶ ዳንኤል በመግለጫቸው ላይ እንዳስረዱት
መንገድ መዝጋት ብቻ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመግደል አሳማኝ
ምክንያት ሊሆን እንድማይችል ገልጸው ወታደሩ ይህንን እርምጃ የወሰደው ወይ ከሚገባው በላይ ለሁኔታ የአጸፋ መልስ በመመለሱ
ነው አለበለዚያም ሆን ተብሎ የሺያ ሙስሊም እምነት ተከታዮችን
ለመግደል የተደረገ እቅድ ነው በማለት አብራርተዋል። የናይጄሪያ መንግስትም ባስቸኳይ ገለልተኛ የሆኑ አጣሪ አካል አቋቁሞ
ጥፋተኞችን በሕግ እንዲቀጣ ድርጅቱ ጥያቄ አቅርቧል።
Ø
በሰሜን ምስራቅ
ናይጄሪያ በምትገኘው የቦርኖ ግዛት በአንድ መንደር ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ የካሜሪን ወታደሮች ጥቃት ፈጽመው ከ70 በላይ
እንደገደሉ ከአካባቢው የተገኘውን ዜና ዋቢ በማድረግ የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ባለፈው እሁድ ታኅሣሥ 10 ቀን 2008 ዓም ማታ
የቦኮ ሃራም ታጣቂዎችን ያሳድዱ የነበሩት የካሜሩን ወታደሮች ወደ
መንደሯ በመግባት በነዋሪው ላይ የእሩምታ ተኩስ ከፍተዎ ብዙዎቹን
ነዋሪዎች አደናግጠው እንዲወጡ ያደረጉ ሲሆን ሰኞ ጠዋት ወደ መንደራቸው የተመለሱት ነዋሪዎች ከ70 በላይ የሆኑ ሰዎች በጥይት
ተመተው ያገኙ መሆናችውን ገልጸዋል። የካሜሩን መንግስት ወታድሮቹ
የሰብአዊ መብትን ለመጠበቅ የሰለጠኑ መሆናቸውን ገልጾ ግድያውን መፈጸሙን ቢክድም የናይጄሪያ
የቦርኖ አካባቢ
ባለስልጣኖች ነዋሪዎች መገደላቸውን አረጋግጠዋል።
ታኅሣሥ 12 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ቦኮ ሃራም በተባለው
አሸባሪ ቡድን እንቅስቅሴ ምክንያት አንድ ሚሊዩን የሚሆኑ የናይጄሪያ ህጻናት ከትምህርት ቤት ውጭ እንዲሆኑ የተገደዱ መሆናችውን
የተባበሩት መንግስታት የህጻናት ተንከባካቢ ድርጅት ዩኒሴፍ አስታወቀ። ከስድስት ዓመት በፊት እንቅስቃሴ የጀመረውና ቦኮ ሃራም
ትክክለኛ ትርጉሙ “ዘመናዊ ትምህርት ኃጢያት” ነው በሚል ስያሜ
የሚጠራው ድርጅት ባደረገው የሽብር እንቅስቃሴ በናይጄሪያ ውስጥ ከ2000 ትምህርት ቤቶች በላይ እንዲዘጉ ከማድረጉ በላይ
ከእነዚህ ውስጥ በመቶ የሚቆጠሩትን አቃጥሎ አውድሟል፤
ንብረቶቻቸውን ዘርፏል። ባለፉት ስድስት ዓመታት በዚሁ አሸባሪ ድርጅት ከ 17 ሺ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን
ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ለመሰደድ ተገደዋል። የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት በዚህ ወር መጨረሻ
ላይ ቡድኑ እንዲደመሰስ ለመከላከያው ተቋም መመሪያ ቢያስተላልፉም የቦኮሃራም የሽብር እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
Ø
ትናንት ሰኞ ታኅሣሥ
11 ቀን 2008 ዓም. ጂቡቲ ውስጥ በሕዝቡና በጸጥታ አባላት
መካከል በተነሳ ግጭት በርከት ያሉ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። ከዋናው ከተማ አጠገብ በሚገኘው ቡልድሆኮ በሚባለው አካባቢ በጸሎት
ላይ የነበሩ ሰዎችን የጸጥታ ኃይሎች ከነብሩበት ቦታ አስነስተው ወደ ሌላ ቦታ ለመውስድ በሚጥሩበት ወቅት በተነሳ ግጭት ሰባት
ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና በርካታዎቹ
መቁሰላቸው በአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተገልጿል። ዪኒየን ፎር ናሽናል ሳልቬሽን የሚባለው ተቃዋሚ ፓርቲ የሞቱት
ሰዎች ቁጥር 19 መሆኑና ከቆሰሉትም መካከል የድርጅቱ መሪ እንደሚገኙበት ገልጿል። ግጭቱ የተጀመረው የተሰበሰበው ሕዝብ ወደሌላ
አንሄድም ብሎ እምቢተኛነቱን በገለጸበት ጊዜ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቱ ገልጸው
ከተሰብሳቢው መካከልም
ጩቢ ገጀራና ቆንጨራ የያዙ እንዲሁም ቢያንስ ሁለቱ ደግሞ ካላሽን
ኮፍ የታጠቁ ሰዎች እንደነበሩበት ተናግረዋል። ግጭቱን ተከትሎ
በርካታ ሰዎች የተያዙ ሲሆን ቢያንስ 23 ሰላማዊ ሰዎች እና 50 ፖሊሶች መቁሰላቸው ተዘግቧል።
በጂቡት በርካታ አገሮች የጦር ሰፈር ያላቸው መሆኑ
ሲታወቅ የጂቡቱ ወታደሮችም ሱማሊያ ውስጥ የአፍሪካ ኅበረት ሰላም አሰባሪ ኃይል ውስጥ ተሰልፈው እየተዋጉ ናቸው።
Ø
የሰላም አስከባሪ ኃይል
ወደ ብሩንዲ እንዲላክ የአፍሪካ ኅብረት የወሰነውን ውሳኔ እንደተጠበቀው የአገሪቱ ምክር ቤት የተቃወመው መሆኑ ታውቋል። ምክር
ቤቱ በውሳኔው የአፍሪካ ኅብረትን ውሳኔ ካወገዘ በኋላ
የብሩንዲ መንግስት የሀገሪቷን ህልውና ለውጭ ኃይል አሳልፎ መስጠት የለበትም ብሏል። የምክር ቤት ሊቀ መንበር ብሩንዲ ውስጥ
አንዳንድ ችግሮች ቢኖሩም ባጠቃላይ ሰላም ሰፍኗል፤ ችግሮችም ቢሆኑ በጥንቃቄ እየተወገዱ ነው ብለዋል። ሌሎች ህገ አውጭዎች
በአገሪቱ ሽብር እየተካሄደ ነው የሚለው መሰረት የሌለውና መገናኚያ ብዙሀን የሚያወራው ወሬ ካሉ በኋላ የውጭ ጣልቃ ገብነትን
በምንም ዓይነት አንቀበልም ብለዋል። ባለፈው አርብ የአፍሪካ ህብረት 5000 ሺ ጦር ወደ ብሩንዲ እንዲላክ በወሰነበት ወቅት
የብሩንዲ መንግስት ቢቃወምም ጦር በግድ ወደ አገሪቱ ይላካል የሚል ውሳኔም አብሮ ማሳለፉ የሚታወስ ሲሆን የብሩንዲ መንግስት
ተቃውሞ ካደረገ በኋላ ድርጅቱ የሚወስደው ርምጃ እየተጠበቀ ነው።
Ø
የዓለም አቀፉ የስደተኛ
ድርጅት ዛሬ ታኅሣሥ 12 ቀን 2008 ዓም ባወጣው ዓመታዊ ዘገባ በዘንድሮ የፈረንጆች ዓመት ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች
ከአፍሪካ እና ከእስያ በስደተኛነት ወደ አውሮፓ የተሻገሩ መሆናቸውን ገልጿል። ከቱርክ በግሪክ በኩል
ወደ አውሮፓ የተሻገረው ስደተኛ ቁጥር 820 ሺ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 455 ሺው ከሶሪያ 186 ሺው ደግሞ ከአፍጋኒስታን
መሆኑ ተዘግቧል። የተቀረው ከአፍሪካ መሆኑ ይታወቃል። 3700 የሚሆኑ ሰዎች የሚዲትራኒያን ባህር ሲያቋርጡ የሞቱ መሆናቸውም
ድርጅቱ ዘግቧል። ከሁለተኛ ዓለም ጦርነት ወዲህ በአውሮፓ ውስጥ ከታዩት የስደተኛ ችግር የአሁኑ ከፍተኛው ሲሆን ስደተኞችን
በመቀበል በኩል በርካታ የአውሮፓ አገሮች ቸልተኛነትን አሳይተዋል። ስደተኞችን በብዛት ለማስተናገድ ፍላጎታቸውን ያሳዩት ጀርመንና
ስዊድን ሲሆኑ ብዙዎቹ ግን ስደተኞች እንዳይገቡ ለመከላከል ወሰኖቻቸውን በአጥር የከለሉ መሆኑ ይታያል።
Ø
በየመን ተጻራሪ ኃይሎች
መካከል ሲካሄድ የነበረው የእርቅ ድርድር ባለፈው እሁድ ታኅሣሥ 10 ቀን 2008 ዓም. ያለውጤት መጠናቀቁ ታውቋል።
የተኩስ አቁሙ ስምምነት ለአንድ ተጫማሪ ሳምንት እንዲራዘም ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 በሁለቱም በኩል ስምምነት
የተደረገ ቢሆንም ግጭት እና ጦርነቱ የቀጠለ መሆኑ ተነግሯል። ሰኞ ዕለት በየመን ደቡባዊ ግዛቶች ሁኔታው የተረጋጋ ቢመስልም
በሰሜናዊ ክፍሉ በአንዳንድ ቦታዎች ጦርነቶቹ ቀጥለዋል። የየመን
መንግስት ደጋፊዎች ከዋናው ከተማ 40 ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የሚገኘውንና
ኒህም የተባለውና በሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር የሚገኘውን ቦታ አጥቅተው 10 የሁቲ አማጽያን መግደላቸውን ገልጸዋል።
እንዲሁም በሳኡዲ ወሰን አካባቢ ያለውን የሁቲዎችን ይዞታ ለማስለቅቅ ወደ ቦታው እያመሩ መሆናቸውም ተገልጿል። በሌላ በኩል ደግሞ
የሁቲ አማጽያን ለአራተኛ ጊዜ ጃዛን ወደ ምትባለው የሳኡዲ የወሰን ከተማ የተኮሱትን የቦለስቲክ ሚሳየል በአየር ላይ እንዳለ
ያመከኑት መሆናቸውን የሳዑዲ ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል።
ሚሳየሉ የተተኮሰበትንም መሳሪያ በአየር ጥቃት ከጥቅም ውጭ አድርገነዋል ብለዋል። የሁቲ አማጽያን ሚሳየሉን መተኮስ ካላቆሙ
ከፍተኛ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በመግለጽ የሳኡዲ መንግስት ባለስልጣኖች ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአዲስ
አበባ
በመንግስት
ሆስፒታሎች
ውስጥ
በበሽተኞች
የተያዙ
አልጋዎች
ባስቸኳይ
እንዲለቀቁ
ከጤና
ጥበቃ
ሚንስቴር
ለየሆስፒታሎቹ አስተዳዳሪዎች
ጥብቅ
ትእዛዝ
የተላለፈ መሆኑን ከተገኘው
መረጃ ለማወቅ ተችሏል። በጠና ከታመሙት በስተቀር በበሽተኞች የተያዙ አልጋዎች እንዲለቀቁና ሆስፒታሎቹ
ምንም ዓይነት አዲስ በሽተኛ እንዳይቀበሉ የሚያዘው
መመሪያ በየዎርዱ ለበሽተኞች ጥቅም እንዲውል የተመደቡ መድኃንቶችም በአስቸካይ እንዲሰበሰቡ የሚል ትዕዛዝ ያካተተ መሆኑ ታውቋል።
በአሁኑ ወቅት
አልጋዎችን
ማስለቀቅ
ያስፈለገበት
ምክንያት በመመሪያው ያልተገለጸ ሲሆን ቀውሱ ወደጦርነት ሊያመራ ይችላል ከሚል ግምት
የቅድሚያ ዝግጅት ለማድረግ ነው የሚል አስተያየት ጉዳዩን
በቅርብ የሚያውቁ ሰዎች ይሰጣሉ። ይህ
በእንዲህ
እንዳለ
ከሰሞኑ
ሕዝባዊ
አመጽ
ጋር
በተያያዘ
ከሚኒልክ
ሆስፒታል
3
ሀኪሞች፣
ከጥቁር
አንበሳ
3
ተማሪዎች
በወያኔ
አፋኝ
ቡድኖች
ተይዘው
የተወሰዱ ሲሆን
እስካሁን
የት
እንደታሰሩ የሚጠቁም
ምንም
ዓይነት
መረጃ አልተገኘም
፡፡
Ø
ሰሞኑን
በሀገሪቱ
የተለያዩ ክፍሎች
የተቀሰቀሰው
ሕዝባዊ
አመጽ
አዲስ
አበባ
ውስጥም
ሊከሰት
ይችላል
ከሚል
ስጋት
የወያኔ
ካድሬዎች
ያደረጉት
ሰብሰባ
በአስደንጋጭ
ሁኔታ
ያለምንም
ውጤት
የተበተነ መሆኑ
ታወቀ፡፡
የስብሰባው
መሪዎች
የወያኔ
ቁንጮዎች
ሲሆኑ
የበታች
ካድሬዎች
ላይ
እየደነፉ
ቢናገሩም
የበታች
ካድሬዎች
ምንም
አይነት ሀሳብ
ባለመሰንዘራቸው
ሰብሳቢዎቹ
እንደተደናገጡ
መረዳት
ተችሏል፡፡
ከዚህ
ጋር
በተያያዘ
የወያኔ ባለስልጣኖች
በየቦታው
የቤት
እመቤቶችንና
ሽማግሌ
አባችቶችን
ሰብስበው
በየአካባቢዎቻቸው
አዲስና
እንግዳ
ሁኔታዎች ካስተዋሉና
ፀጉረ
ልውጥ
የሆኑ
ሰዎች
ካዩ
በአስቸኳይ
ለፖሊስ
እንዲጠቁሙ
ከማስጠንቀቂያ
ጋር
መመሪያ እንደሰጧቸው
መረዳት
ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል
በአባ
ዱላና
በሙክታር አህመድ ሰብሳቢነት
በተደረገው
የኦሮሞ
ሊሂቃንን
ሰብስባ ላይ በርካታው
ተሰብሳቢ ንዴትና ቁጣ በተሞላበት ሁኔታ ስሜቱን የገለጸ ሲሆን
ሰብሳቢዎችም ውርደታቸውን
ተከናንበው
ስብሰባው
ሳያልቅ
አዳራሹን
ለቀው
እንደወጡ
ለማወቅ
ተችሏል፡፡
Ø
ሰሞኑን
በሚያስገርም
ሁኔታ
ወደ አገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚደረገ የአውሮፕላን በረራዎች
እየታጠፉ ወደ መቀሌ እንዲበሩ የተደረጉ መሆናቸውን ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ችለናል። ወደ መቀሌ የዞሩት በረራዎች አንዴም በቀን
ሁለት ጊዜ የተደረጉ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን
የወያኔ
ድርጅቶችና
የወያኔ
ሸሪክ
የሆኑ
ነጋዴዎች
የሚያስገቧቸው
ሸቀጦች
በብዛት
በሚያስደነግጥ
ሁኔታ
ወደ
መቀሌ
እንዲጓጓዙ
ተደርጓል፡፡
የጉምሩክ
ኃላፊዎች
ወደ
መቀሌ
የሚጓዙዙትን
አውሮፕላኖች
እንዳይፈትሹ ያደረጉ ሲሆን
በድብቅ
ወደ
መቀሌ
እንዲጓጓዙ
ከተደረጉት
ሸቀጦች
መካከል
የጦር
መሣሪያዎች
ሊሆኑ
ይችላሉ የሚል ግምት ያለ
መሆኑን ቦሌ
ዓለም
አቀፍ
አውሮፕላን
ማረፊያ
ካሉ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ይገልጻል።
Ø
ከቀኖና
ውጪ
በወያኔ
ለሁለተኛ
ጊዜ
የተሸሙት
ፓትርያርክ
በጽኑ የታመሙት
በቤተ
ክህነት
ውስጥ
የተኮለኮሉት
የወያኔ
ካድሬዎች
ባሳደሩባቸው
ተጽእኖዎች ምክንያት ከአእምሮ ጭንቀት
የተነሳ
እንደሆነ ለማወቅ
ተችሏል፡፡
የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣኖች
ቤተ
ክርስቲያኗ
ለዓባይ
ግድብ
ከፍተኛ
መዋጮ
መክፈል
እንዳለባት የሚያስገደድ
መመሪያ በማስተላለፋቸው
በብዙ
ሚሊዮን
የሚቆጠር
ገንዘብ
በእነዓባይ
ፀሀይ
እየተበዘበዘ
መሆኑን
ለጉዳዩ
ቅርበት ያላቸው ወገኖች
በቁጭት
እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡
በቤተክስቲያኗ
ውስጥ
በእጅጉ
ከተንሰራፋው
ሙስና
ጎን
ለጎን
ዘረኝነትና
ኢሰብአዊነት
ወደር
የለሽ
እንደሆኑ
እየተነገረ
ነው፡፡
Ø
በሀዲያ ዞን ከተማ የሚ
ገኛው የዋቸሞ ዩኒቫርሲቲ ተማሪዎች ባለፈው ዓርብ ታሕሣሥ
8 ቀን 2008 ዓም የወያኔ አገዛዝ ን በመቃወም
እንቅስቃሴ አድ ርገዋል። አጋዝ ጦር ባዳረገው የአፈና ሁኔታ እንቃቃሴው ገብ ብሏል። እስካሁ ን
ድረስ ት / ቤቱ በወያኔ ቅልብ የአጋዝ ጦር ተከቦ ይገኛል። የህዝብን መብት ረግጦ በመሳሪያ ኃይል እገዛለሁ ማለት
ዘበት ስለሆነ ይህን ጨካኝ ፣ ሆዳምና የዘራፊዎች መንጋ ሥ ርዓት ለማስወገድ የ ሚደረገው ትግል በሁሉም ቦታ መቀጠል አለበት።
ሌሎች የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ፣ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃና የአንደኛ ደረጃ
ት / ቤት መምህራን ና ተማሪዎች እንዲሁም ሕዝቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ፈለግ መከተል ይኖርባቸዋል። ባሪነት
እስከመቼ ? ሐንቄቦ ከቦታው አስተላልፈዋል።
እንዲሁም በዚያው ዞን በሆሳዕና ከተማ ከሚገኛው እስር ቤት ለመምለጥ
የሞከረ እስረኛ ተገድሏል። ግ ለሰቡ የታሰረበት ምክንያትና ስሙ አል ታወቀም።
ቅርብ ጊዜ በዚሁ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች ከፌዴራልና ከክልል የመጡ የወያኔ / ኢህአዴግ ባለሥልጣናት ሕዝብ
ሰብስበው የነበረ ቢሆንም ሕዝቡ ከእናንተ የሚገኛው ምንም ነገር የለም የምንፈል ገው ለውጥ ነው በማለት አሳፍሮ መልሷል።
ዘንድሮ በዞኑ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ገበሬው የዘረው እህል በዋግ
ተመቷል። የ ገበሬው እ ህል በዋግ መመታቱን እያየ ጨካኙ የወያኔ ስርዓት የማዳበሪያ ዋጋ ክፈሉ በማለት ገበሬውን በማስቸገር ላይ
ቢገኝም ሕዝቡ የምንከፍለው ገንዘብ የለም እህሉ በዋግ ተመቷል በማለት ተቃውሞ በማሰማት ላይ ይገኛል።
Ø
ትናንት ታኅሣሥ 10
ቀን 2008 ዓም ንብረትነቱ የኤር ፍራንስ የሆነ ቦይንግ 777 አውሮፕላን 459 መንገደኞችን ይዞ ከሞሪሺየስ ወደ ፓሪስ ሲያመራ
በአውሮፕላን መታጠቢያ ቤት የታየወ አጠራጣሪ ዕቃ
የተጠመደ ቦምብ ሊሆን ይችላል ከሚል ፍራቻ ባስቸኳይ ሞባሳ አውሮፕላን ማረፊያ እንዲያርፍ የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ከካርቶ
የተሰራውና ውስጡ የወጥ ቤት ሰዓት መቆጣጠሪያ የነበረው ይህ ለየት ያለ እቃ የጠመደ ፈንጅ አለመሆኑን የፈንጅ አዋቂዎችና ፖሊሶች
በማረጋገጣቸው አውሮፕላኑ ጉዞውን ወደ ፓሪስ የቀጠለ መሆኑም ተነግሯል። ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 11 ቀን 2008 ዓም የፈረንሳይ
ፖሊሶች አውሮፕላኑ ፓሪስ ላይ እንዳረፈ ሁለት የሪዩኒየን ዜጎች የሆኑ
ባልና ሚስት በቁጥጥር ስር ያደርጉ መሆናቸው ተዘግቧል።
Ø
የናይጄሪያ መከላከያ
ኃይል በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በቦርኖ ግዛት ውስጥ በሶስት የተለያዩ ቦታዎች ጥቃት በመፈጸም 12 የቦኮ ሃራም ታጣቂዎችን
መግደሉን የወታደሩ ቃል አቀባይ ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ገልጿል። ከተገደሉት መካከል በአካባቢው አሚር ወይም መሪ የሆነ
ግለስብ የተገደለ መሆኑን መግለጫው ገልጾ በርካታ መሳሪያና ጥይት የተያዘ መሆኑንም አብራርቷል። የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ
የናይጄሪያ መከላከያ ኃይል እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ቦኮሃራምን ለማጥፋት የጊዜ ገደብ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን አሸባሪው
ቡድን አሁንም ጥቃት ከመሰንዘር ያላቆመ መሆኑ ታውቋል። እንዲያውም በትናንትናው ምሽት በዚያው በቦርኖ ግዛት ሁለት አጥፍቶ
ጠፊዎች ባፈነዱት ፈንጅ 6 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ተነግሯል።
Ø
የብሩንዲ መንግስት
የአፍሪካ ኅብረት የወሰነውን ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ምንም ዓይነት የውጭ ጦር ወደ አገሩ እንዲገባ የማይፈቅድ መሆኑን ገልጿል።
ይህን መግለጫ የሰጡት የብሩንዲ መንግስት ምክትል ቃል አቀባይ ሚስተር ካሬርዋ ሲሆኑ የአፍሪካ ኅብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል
ካለ ፈቃድ ወደ ብሩንዲ የሚገባ ከሆነ እንደ ወራሪ ጦር የሚቆጠር መሆኑንና የብሩንዲ
መካለክያ ኃይሎች አስፈላጊውን የመከላከል ርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱ መሆናችውን ገልጸዋል። ግለሰቡ በተጨማሪ በሰጡት መግለጫ
አፍሪካ ኅብረት ጦሩን ለመላክ የወሰነው ውሳኔ በተባበሩት መንግስታ
ድርጅት መጸደቅ ነበረበት የሚል ሀሳብ አቅርበዋል። ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የአፍሪካ ኅብረት ቁጥራቸው 5000 ሺ የሚሆኑ የሰላም
አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነ መሆኑንና የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ ባካሄደው
ስብስበስባ ሁሉም ወገን ወእርቅ ጠረጴዛ እንዲመጣ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። ሁለቱ
የብሩንዲ ምክር ቤቶች በጉዳዮ ላይ በዛሬው ቀን ይመክራሉ ተብሎ
የሚጠበቅ ሲሆን የአገሪቱ መንግስት ከሰጠው የተለየ ውሳኔ እንደማይሰጡ ተገምቷል።
ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ኅበረትም ሆነ የተባብሩ መንግስታት ድርጅት
በጉድዩ ላይ የሚወስዱት እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል ግልጽ
ባይሆንም የአፍሪካ ህብረት ጦሩን ለመላክ የወሰነው ውሳኔ ከብሩንዲ ተቃውሞ ከገጠመው በማናቸውም መንገድ ተግባራዊ ይሆናል ማለቱ
ይታወሳል።
ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት ታኅሣሥ 18
ቀን 2008 ዓም የአሜሪካ መንግስት በድርቅ ለተጠቁት ወገኖች መርጃ 88 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የምግብ እርዳታ መስጠቱን
አስታውቋል። ይህ እርዳታ በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት
የአሜሪካ መንግስት ለድርቅ የሰጠውን እርዳታ ወደ 435 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ያደረገው መሆኑም ተገልጿል። ወያኔ "ረሃብ
የለም፤ ያለውን የድርቅ ችግር እኛ እንቋቋመዋለን በማለት ሲያሰራጨው የነበረውን ፕሮፓጋንዳ ለውጦ በድንገት 1.4 ቢሊዮን ዶላር
ያስፈልገኛል ማለቱ የሚታወስ ሲሆን ከውጭ ለጋሾች ከሚጠበቀው እርዳታ ውስጥ እስካሁን ድረስ ምን ያህሉ እንደገባ አልታወቀም።
በትናንትናው ዕለት በይፋ የተነገረው የአሜሪካ እርዳታ 116 ሺ ቶን የምግብ እርዳታ ሲሆን በ74 ወረዳዎች ለሚኖሩ 2.6 ሚሊዮን
ለሚሆኑ ወገኖች ይደርሳል ተብሏል። የረሃብተኛው ቁጥር በቅርቡ ከ20 ሚሊዮን ያልፋል የሚል ግምት እየተሰጠ ሲሆን
እርዳታው በወቅቱ ካልደረሰ እልቂት ሊከተል እንደሚችል ብዙዎቹ
ስጋታቸውን ይገልጻሉ።
Ø
ዛሬ ታኅሣሥ 19 ቀን
2008 ዓም በሱማሊያ ዋና ከተማ ሞጋዲሾ ውስጥ በርካታ መንገደኞችን በሚያስተናግድ አውራ መንገድ ላይ በተጣለ ቦምብ የተወሰኑ
ሰዎች መሞታቸውንና መቁሰላቸውን ከስፍራው የመጣ ዜና
ይገልጻል። የሬውተር የዜና ምንጭ ሶስት ሰዎች እንደሞቱ ሲዘግብ የሟቾቹ ቁጥር ከዚህ ሊበልጥ እንደሚችል በቦታው የነበሩ የዓይን
እማኞች ይናገራሉ። ቦምቡን በማፈንዳት በኩል እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም አልሸባብ የሚባለው ቡድን መሆኑን
ብዙዎች ይጠረጥራሉ።
Ø
በሩዋንዳ የውሳኔ ሕዝብ
ድምጽ እንዲሰጥበት የተደረገው የሕገ መንግስት ማሻሸያ የጸደቀ መሆኑ ተነገረ። ሰባ ከመቶ በሆኑት የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ
የተገባደደ ሲሆን እስካሁን 98.1 ከመቶ የሆነው መራጭ ማሻሻያውን ደግፎታል ተብሏል። በሕገ መንግሥቱ ማሻሻያ መሰረት የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት ካጋሜ ለሚቀጥሉት 17 ዓመት በስልጣን ላይ ሊቆዩ የሚችሉበት ሁኔታ የተመቻቸላቸው መሆኑ ተገልጿል። በአገር ውስጥ ያሉ
ተቃዋሚ ድርጅቶች ከመነሻው ማሻሻያውን የተቃወሙት ሲሆን በቂ ጊዜ ተሰጥቶት ሕዝብ እንዲወያይበት ያልተደረገ መሆኑን በመጥቅስ
የምርጫውን ሂደት አውግዘው ትግላቸው የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የአንድን ግለሰብ የሥልጣን እድሜን ለማራዘም የተደረገው የሕገ
መንግስት ማሻሻያ የዴሞክራሲን ይዞታ ይጎዳል በማለት የምዕራብ አገሮች ሂደቱን መቃወማቸው ይታወሳል።
Ø
የአፍሪካ ኅብረት 5 ሺ
የሚሆኑ ወታድሮችና የፖሊስ አባላት ባስቸኳይ ወደ ብሩንዲ ለመላክ የወሰነ መሆኑ ተነገረ። በአራት ቀናት ውስጥ መልስ እንዲሰጥ
የብሩንዲው መንግሥት በይፋ የተጠየቀ ሲሆን የእምቢታ መልስ ቢመጣ እንኳ በውሳኔው መሰረት የሰላም አስከባሪው ኃይል አባላት
ባስቸኳይ የሚላኩ መሆኑ ተገልጿል። የብሩንዲ መንግስት
ባለስልጣኖች በተለያዩ ጊዜያት የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል በአገራቸው ውስጥ የመግባቱን ሁኔታ እንደማይቀበሉ
መግለጻቸው የሚታወቅ ሲሆን በቅዳሜው የድርጅቱ ውሳኔ ላይ ያላቸው አቋም ግን እስካሁን አልታወቀም። የሚላከው 5 ሺ ጦር
የሚውጣጣው ከየት ከየት አገሮች እንደሆነ ባይገለጸም ጦሩ በሰላም አስከባሪው ሥራ ላይ የሚሰማራው ቢያንስ ለስድስት ወር መሆኑና
ቁጥሩም እንደአስፈላጊነቱ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል። የጦሩ ተልዕኮ የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት መጠበቅና ተጻራሪ ኃይሎች
የእርቅ ውይይት ሊያደርጉ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት ነው ተብሏል። በሌላ በኩል የብሩንዲ ተጻራሪ ክፍሎች በመጭው ታኅሣሥ 18
ቀን በዩጋንዳ ዋና ከተማ በካምፓላ የእርቅ ውይይት ለማካሄድ የተስማሙ መሆናቸው ታውቋል። በውይይቱ ላይ የመንግሥቱ ክፍልን ጨምሮ
አስራ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማህበረሰቡ ተወካዮች በውይይቱ የሚካፈሉ ሲሆን ስብሰባውን የሚመሩት
የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ናቸው ተብሏል።
በተያያዘ ዜና የአሜሪካ መንግስት በብሩንዲ እየተካሄደ ላለው ግድያ ተጠያቂ ናቸው ባላቸው ሶስት ባለስልጣናት ላይ
ማዕቀብ ያደረገ መሆኑን አርብ ዕለት ገለጸ። ሶስቱ ማዕቀብ የተጣለባቸው
ግለሰቦች፡ የብሩንዲ የጸጥታ ሚኒስቴር
ቺፍ ኦፍ ስታፍ፤ ከዚህ በፊት በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ተሳታፊ የነበሩ አንድ የቀድሞ ጄኔራል እና መንግሥትን ደጋፊ የሆኑ
ሚሊሺያዎችን በማስተባበር በኩል ጉልህ ሚና የነበራቸው አንድ ሌላ
ግለሰብ ናቸው።
Ø
ቢየን በሚባለው የስዊስ
ከተማ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታራቂነት የእርቅ ውይይት እያካሄዱ ያሉት የየመን ተጻራሪ ኃይላት ተወካዮች ለአንድ
ሳምንት ታቅዶ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚከታተልና
ተግባራዊነቱን የሚያረጋግጥ አንድ ኮሚቴ ለማቋቋም ዛሬ ቅዳሜ ታኅሣሥ 9 ቀን 2008 ዓም. የተስማሙ መሆናቸው ተገለጸ። ኮሚቴው
በአንድ የሊባኖስ ጄኔራል የሚመራ ሲሆን በሳኡዲ ከሚመራው የጋራ ጦር ፤ ከፕሬዚዳንት ሃዲ ደጋፊዎች ፤ ከቀድሞው
ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳላህ ደጋፊዎችና ከሁቲ አማጽያን የተውጣጡ ወኪሎች እንደሚኖሩት ታውቋል። ባለፉት ጥቂት ቀናት በተለያዩ
ቦታዎች በተካሄዱ ግጭቶች ምክንያት የተደረገው የተኩስ አቁም ስምምነት ይፈርሳል የሚል ስጋት በብዙዎች ዘንድ የፈጠረ መሆኑ
ይታወቃል። ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ በስዊስ የሚካሄድው ውይይት ተቋርጦ የነበረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ስብሰባው የተቋረጠው
ታስረው
የሚገኙት የፕሬዚዳንቱ
ሃዲ ወንድም እና ሌሎች የየመን ከፍተኛ ባለስልጣኖች በእስረኞች ልውውጥ
እንዲፈቱ የተጠየቀውን ጥያቄ የሁቲ አማጽያን ውድቅ በማድረጋቸው ነው ተብሏል። የሁቲ አማጽያን ተወካዮች እስረኞቹን በእስር
ለማቆየት ፍላጎት እንደሌላቸው ገልጸው ሊፈቱ የሚችሉት ግን አጠቃላይ ስምምነት ላይ ሲደረስ ብቻ ነው ብለዋል። ስበሰባው በዛሬው
ዕለት የቀጠለ ሲሆን ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ያልተቻለ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ።
ታኅሣሥ 8 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በምስራቅ ያለውን የሊቢያ የአስተዳድር ክፍል ለመርዳት ወደ ሊቢያ ተልከው የነበሩ 20 የአሜሪካ ወታደሮች ከሌላው ክፍል
በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ አገሪቱን ለቀው የወጡ መሆናቸው ታውቋል። በምስራቅ ሊቢያ የተመሰረተውና የዓለም አቀፍ እውቅና አለው
የተባለውን መንግስት ነኝ የሚለውን ክፍል ለመርዳት ማዕከል
ከፍተኛና ዘመናዊ መሳሪያዎችን ታጥቀው የተላኩት የአሜሪካ ወታድሮች
በምዕራብ ሊቢያ በሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ ሊቢያ የገቡት ባለፈው ሰኞ ሲሆን
የወጡት ተጻራሪው ክፍል ባቀረበው ጠንካራ ጥያቄና ማስፈራሪያ መሆኑ
የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የአሜሪካ የአፍሪካ ወታደራዊ
ኮማንድ ለዜና ምንጮች በሰጠው መግለጫ ወታደሮቹ ሊቢያን ለቀው እንዲወጡ የተደረገው ግጭቶችን ላለመፍጠር ነው ብሏል። በተያያዘ
ዜና በትናንትናው ዕለት የሁለቱ ተጻራሪ አስተዳደር ተወካዮች ሞሮኮ ውስጥ በእርቅ
ስምምነት ሰነዱ ፈርመዋል የተባለ ቢሆንም የሁለቱ
ተጻራሪ ምክር ቤቶች መሪዎች በውስጣቸው ባለው አለመግባባት ምክንያት በቦታው ተገኝተው አለመፈረማቸው የስምምነቱን ውጤት አጠራጣሪ
ያደርገዋል ተብሏል።
Ø
ዛሬ ታኅሳስ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. የሩዋንዳ ዜጎች በአገሪቱ ህገ መንግስት ላይ የተደረገውን ማሻሻያ ለማጽደቅ ድምጽ
የሰጡ መሆናቸው ታውቋል። በዛሬው ዕለት 6.4 ሚሊዮን የሚሆኑ የሩዋንዳ ዜጎች ድምጽ ይሰጣሉ ተብለው የሚጠበቁ ሲሆን 34 ሺ
ለሚሆኑ በውጭ ለሚኖሩ ዜጎች ደግሞ በትናንትናው ዕለት ድምጽ የመስጠት እድል ተሰጥቷቸዋል።
የተሻሻለው ህገ መንግስት የሩዋንዳውን መሪ የስልጣን ዘመን
ለአምስት ዓመት እንዲሆን ቢወስንም ህጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀመረው በ2016
ዓም. በመሆኑ የአሁኑ ፕሬዚዳንት እድሜ ከሰጣቸው ስልጣናቸውን እስከ 2026 ዓም ድረስ ሊያራዝሙ የሚችሉበት እድል ከፍተኛ
መሆኑን ይነገራል። በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችና አንዳንድ የውጭ ኃይሎች የሕገ መንግስቱ ለውጥ ካጋሜን በስልጣን ላይ ለ34
ዓመት ለማቆየት ሆን ብሎ የታቀደ ነው በማለት ቅሬታቸውን ቢያሰሙም ካጋሜና ጓደኞቻቸው የውጭ ኃይሎች በሩዋንዳ የውስጥ ጉዳይ ምን
አያገባቸውም በማለት ነቀፌታቸውን አጣጥለውታል።
Ø
የአፍሪካ ህብረት የሰላምና የጸጥታና ኮሚቴ ትናንት
ሀሙስ ታኃሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም ባደረገው ስብሰባ ወደ ብሩንዲ የሰላም አስከባሪ ኃይል ለመላክ የተስማማ መሆኑ ተገለጸ። ቁጥሩ
ምን ያህል እንደሆነ ባይገለጸም ወደ ብሩንዲ የሚላከው የሰላም አስከባሪ ኃይል በምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ጦር ስር እንደሚሰማራ
ታውቋል። ጦሩ ወደ ብሩንዲ የሚላከው የብሩንዲው መንግስት ሲስማማ ወይም የአፍሪካ ህብረት አባል አገር መሪዎች አብዛኛዎቹ መላኩን
በድምጽ ሲደግፉት ነው ተብሏል። በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባንኪ ሙን በተጻራሪ ኃይሎች በኩል ውይይት
ሊያካሄድ የሚችል ተወካይ ወደ ቡሩንዲ የሚልኩ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ሐሙስ ዕለት ደግሞ የተመድ የሰብዕዊ መብት ሹም በአገሪቱ
ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግድያናና አፈና እንዲመረምር አንድ ገለልተኛ የሆነ ቡድን ወደ ብሩንዲ ለመላክ የታቀደ መሆኑን
ተናገረዋል።
Ø
የናይጀር
መንግስት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያከሸፈ መሆኑን
መሆኑን ትናንት ሐሙስ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም ፕሬዚዳንቱ ለሕዝባቸው በራዲዩና በቴለቪዥን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው አየር ኃይሉን በመጠቀም ሴራ ጠንሰሰው የነበሩት በሙሉ መያዛቸውን ገልጸው
ሁኔታው በቁጥጥር ሰር መዋሉንም አብራርተዋል።
መፈንቅለ መንግስቱን ለማካሄድ አሲረዋል ተብለው የተጠረጠሩ አራት
ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመግለጽ ቀደም ብሎ አንዳንድ የአገሪቱ መገናኚያ ብዙሀን ተናገረው የነበረ መሆኑ
ታውቋል። በሚቀጥለው የካቲት ወር በናይጀር ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ
የታቀደ ሲሆን የ63 ዓመቱ አዛውንት ፕሬዚዳንት ኢሱፉ የሚወዳደሩ መሆናቸውም ተነግሯል። የመፈንቅለ መንግስት ጠንሳሾቹ ዓላማ ምን
እንደሆን እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን ተቃዋሚ ኃይሎችም የሰጡት መግለጫ የለም። ላለፉት ሁለት ዓመታት ተቃዋሚ ኃይሎች ሊካሄድ
የታቀደው ምርጫ ብዙ ጉድለቶች ስላሉት ፍትሃዊ ሊሆን አይችልም በማለት የአገሪቱን የምርጫ ቦርድ ሲከሱ መቆየታቸው ይታወቃል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት በዘንድሮ የፈረንጆቹ ዓመት በዓለም ላይ ቤትና ንብረቱን ጥሎ
የተሰደደው ሕዝብ ቁጥር 60 ሚሊዮን መድረሱን አርብ ታኅሣሥ 8
ቀን 2008 ዓም. ባወጣው ዓመታዊ ዘገባ ገልጿል። በስደተኛነት፤
ጥገኛነት በመጠይቀና እንዲሁም በአገሩ ውስጥ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ የተሰደደው ሰው ቁጥር አምና 59.5 ሚሊዮን
የነበረ ሲሆን የዚህ ዓመቱ ቁጥር 500 ሺ የሚሆኑ ተጨማሪ
ሰዎች መሰደዳቸውን ይጠቁማል።
በአሁኑ ወቅት ከ122 በዓለም ላይ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ
ስደተኛ የሆነ ሲሆን በአማካይ በየቀኑ 4600 ሰዎች ቤት ንብረታችውን ጥለው እንደሚሰደዱ ዘገባው ገልጿል።
ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአፍሪካ ኅብረት ስለ
ብሩንዲ ሁኔታ በሰፊው ከተነጋገረ በኋላ በሰጠው መግለጫ ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት አገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለው የርስ በርስ ግጭት
በጣም ያሳሰበው መሆኑን ገልጾ ሌላ አገሪቱ ውስጥ እልቂት ሲካሄድ አይኑን ጨፍኖ እንደማይቀመጥ ይፋ አድርጓል።
የኅብረቱ የሰላምና የጸጥታ ካውንስል የስላም
አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ ስለሚላክበት ሁኔታ እየተነጋገረ መሆኑንም ተገልጿል። በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በአፍሪካ ህብረት
የተመደቡ አጣሪዎች በብሩንዲ ያለውን ሁኔታ ለተወስኑ ቀናት ካጣሩ በኋላ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን መዘገባቸው
የሚታወስ ሲሆን ህብረቱ እዚህ አቋም ላይ የደረሰው የአጣሪ ቡድኑን ዘገባ መሰረት በማድረግ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት
የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም በሰጡት መግለጫ ብሩንዲ ውስጥ በአሁኑ ወቅት እየታየ ያለው
በዘር ላይ የተሰመረተ የጥላቻ ግጭት የዛሬ 20 አመት
ከተከሰተው ጋር ተመሳሳይነት ስላለው አገሪቱ ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላላ የእልቂት ሁኔታ ውስጥ ልትገባ ትችላለች የሚል ስጋት
እንዳላቸው ገልጸዋል። በ 1982 ዓም በሁቱ እና በቱሲ ጎሳዎች መካከል በተነሳው ግጭት ምክንያት ከ300 ሺ ሰው በላይ ማለቁ
ይታወሳል።
Ø
በሊቢያ ተጻራሪ
መንግስትን ያቋቋሙት ወገኖች ተወካዮች ዛሬ ታኅሣሥ 7 ቀን 2008 ዓም.
በሞሮኮ ዋና ከተማ ራባት ላይ ተገኝተው ቀደም ብሎ የጋራ
መንግስት ለማቋቋም ደርሰውበታል የተባለውን ስምምነት በይፋ
ለመፈረም መዘጋጀታቸው የተገለጸ ሲሆን ፈራሚዎቹ ግን በየበኩላቸው
መንግስት ነን ያሉትን አስተዳደሮች አይወክሉም ተብሏል። በትሪፖሊ
የሚገኘው አስተዳደር መሪ አቡሳህማን ቀደም ብለው ለጋዘጠኞች
በሰጡት መግለጫ የሚፈረመው ስምምነት የአብዛኛውን የምክር ቤት አባላት ድጋፍ ያላገኘ በመሆኑ ህጋዊነት አይኖረውም ብለዋል።
በራሳቸው በኩል ስምምነቱን እንደማይቃወሙት ገልጸው ሌሎች አባላትን ለማሳመን ግን ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። በሌላ
በኩል በምስራቅ የሚገኘው መንግስታዊ አስተዳድር ወታደራዊ መሪ የሆኑ አንድ ጄኔራል የስምምነቱን ሀሳብ የሚቃወሙት መሆኑን
ገልጸዋል። ጄኔራሉ ስምምነቱን የተቃወሙት በስምምነቱ ረቂቅ ውስጥ
የአገሪቱን የመከላከያ ኃይል በመሪነት እንዲመራ ስሙ የቀረበ ግለሰብ ተጻራሪው አካል በ10 ቀን ውስጥ ስምምነቱን ገልጾ
ካላጸደቀው የቀረበው ተሽሮ በሌላ ይተካል የሚል አንቀጽ ስለያዘ
ነው ተብሏል። ስለሆነም የዛሬው የይፋ የስምምነት ፊርማ
ለይስሙላ እንጅ ተግባራዊነቱ አጠራጣሪ ነው ተብሏል።
Ø
ጆርዳን በአገሪቱ ውስጥ
ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ገብተዋል ያለቻቸውን 800 የሚሆኑ የሱዳን ዜጎች ወደ አገራቸው ለመመለስ የተዘጋጀች ሲሆን
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኛ ጉዳይ ኮሚሽን ስዎቹ ወደ
አገራቸው ቢመለሱ እጣቸው እስርና ግድያ መሆኑን ገልጾ ጆርዳን ሱዳናውያኑን እንዳታስወጣ ተማጽኗል። ጆርዳን ውስጥ ይገኛሉ ከሚባሉ
3500 ሱዳናውያን መካከል አብዛኞቹ የዳርፉር ተወላጆች በመሆናቸው ወደ አገራቸው ቢመለሱ ችግር ይድርስባቸዋል የሚል ከፍተኛ
ግምት አለ። ትናንት ታኅሳስ 6 ቀን 2008 ዓም የጆርዳን የጸጥታ
አባላት ስደተኞቹ የሰፈሩበትን ስፍራ ወርረውና የሸራ ድንኳናቸው
ቀዳድደው በቁጥጥር ስር ካደረጓቸው በኋላ አገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ያጓጓዟቸው መሆኑ ይታወሳል።
ስደተኞች አውሮፕላን ማረፊያ አጠገብ ቢያድሩም እስካሁን ያልተጓጓዙ መሆናቸው ከስፍራው ከተገኘ
ዜና ማወቅ ተችሏል።
Ø
በየመን ጎራ ለይተው
በሚፋለሙት ወገኖች መካከል ስምምነት የተደረሰበት የእስረኞች ልውውጥ በታቀደው መሰረት በስራ ላይ የዋለ ሲሆን ለአንድ ሳምንት
እንዲቆይ የታሰበው የተኩስ አቁም ስምምነት ግን እየተጣሰ መሆኑ ከአየቅጣጫው የሚደረሱ መርጃዎች ይጠቁማሉ። የተክሱ አቁም
ስምምነቱን በመጣስ ረገድ ሁለቱም ወገኖች በመወነጃጀል ላይ ናቸው። የአረብ የጋራ ኃይል ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን የሁቲ አማጽያን
ከ150 በላይ የሆኑ ግጭቶችን በመተንኮስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን መጣሳቸውን ገልጸው የጋራው ኃይሉን ራሱን ለመካለክል እርምጃ
ወስዷል ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ሁቲዎችን የማይስታግሱ ከሆኑ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ተግባራዊ ማድረግ
ይከብደናል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል። ከሁቲ አማጽያን ጋር አብሮ እየተንቀሳቀሰ ያለው የቀድሞ ፕሬዚዳንት የአሊ አብዱላህ
ሳላህ ቃል አቀባይ በበኩሉ በሰጠውም መግለጫ የጋራው ኃይል በመሬት በአየርና በባህር የተቀነባበረ ጥቃት ሰንስዝሮብናል በማለት
ክስ አቅርቦ ለዚህ ጥቃት ከፍተኛ የሆኑ ምላሽ እንሰጣለን ብሎ ዝቷል። ለአንድ ሳምንት ይቆያል የተባለው የተኩስ አቁም ስምምነት
ሊፈርስ ይችላል የሚል ስጋት ያለ ሲሆን በስዊዝ የሚካሄደውም የእርቅ ውይይት ብዙ ተስፋ የሚጣልበት እንዳልሆነ ታዛቢዎች
ይገልጽሉ። በትናንትናው ዕለት የተካሂደው የእስርኞች ልውውጥ መልካም እርምጃ ቢሆንም የተሳሩ ባለስልጣኖችን በማካተት የቀረበው
ሁለተኛ ዙር የእስረኞች ልውውጥ ሀሳብን የሁቲ አማጽያን ያልተቀብሉት መሆኑ ተግልጿል።
ታኅሣሥ 6 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በተባበሩት መንግስታት
ድርጅት አስታራቂነት በየመን የሚገኙ ተጻራሪ ቡድኖች ጄኔቫ
ላይ የሰላም ድርድር መጀመራቸውና ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ያደረጉ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ማክሰኞ
ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም. የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ
መስማማታቸው ታውቋል። በስምምነቱ መሰረት 360 የሁቲ
አማጽያን አባላትና 260 የሚሆኑ የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ተፋላሚዎች ከአጋቾቻቸው ተለቀው ወየቤታቸው ይሄዳሉ ተብሏል። ይህ
የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት እንዲደረግ ግፊት ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታራቂዎች ሲሆኑ ዛሬ ታኅሣሥ 6 ቀን
2008 ዓ.ም. ላህጅ በተባለው የደቡብ ግዛት ውስጥ
ከሁለቱም በኩል እስርኞች የተፈቱ መሆኑ ታውቋል። የደቡብ የመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረ ጀምሮ 5800 የሚሆኑ የመናውያን
ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ለስደት ተዳርገዋል። ባሁኑ ወቅትም 21 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች የምግብና ሌላም እርዳታ
የሚፈልጉ ናቸው ተብሏል።
Ø
በሊቢያ በየራሳቸው
መንግስት ነን በማለት የአስተዳደር አካል ያቋቁመት መሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በማልታ መገናኘታቸው ተገለጸ። በምስራቃዊ ሊቢያን
ማዕከል ያደረገው መንግስት መሪ አጂላ ሳላህ እና
በትሪፖሊ የሚገኘው የሊቢያ ብሔራዊ ኮንግሬስ መሪ ኑሪ አቡሳህማን
ማልታ ላይ ተገናኝተው ውይይት ያደረጉ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ከውይይት ያለፈ ስምምነት ለማድረግ ያልቻሉ መሆናቸው ታውቋል።
በሳምንቱ መጨረሽ ሮም ላይ የተገናኙት የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ተወካዮች የአሜሪካውና የአውሮፓው ኅብረት ባለስልጣኖች ባሉበት
ውይይት ማድረጋቸው የተነገረ ሲሆን የስምምነቱ ፊርማ ስነስርዓት ወደ ሐሙስ መተላለፉ ይታወሳል። በተጻራራነት በቆሙ ሁለቱ ምክር
ቤቶች ውስጥ በተባለው ረቂቅ ስምምነት ላይ ጠንካራ ተቃውሞ ያሰሙ በመኖራቸው ሐሙስ ዕለት ፊርማው ለመደረጉ የሚጠራጠሩ በርካታ
ናቸው። ሞአመር ጋዳፊ ከስልጣን ሲወገዱ በአግሪቱ በተፈጠረው ውጥንቅጥ
ወደ አውሮፓ ለሚጓዙ ስደተኞች አስተላላፊዎች ምቹ ቦታ መሆኗና
የአይሲስ እና የአልካይዳ ቅርንጫፎችም እየተጠናከሩ መምጣቸው የሊቢያ ሁኔታ የምዕራብ አገሮች ሲያሳስብ የቆየ መሆኑ
ግልጽ ነው።
Ø
ዛሬ ታኅሣሥ 6 ቀን
2008 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ በኬፕ ታውን እና በፕሪቶሪያ ከተሞች በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎች የተቃውሞ ሰልፍ
በማድረግ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ ጠየቁ። በቅርቡ ፕሬዚዳንት ዙማ ሁለት ጊዜ የገንዘብ ሚኒስትራቸውን መለወጣቸው በአገሪቱ
ውስጥ ተስፋፍቶ ከሚታየው የሙስና ወንጀል ጋር ተዳምሮ በመንግስታቸው ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ለማስነሳት ምክንያቶ ሆኖ መቆየቱ
ይታወሳል። በአውስትራሊያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር የሆኑት ግለሰብ ከዚህ በፊት የትራንስፖስፖርት ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት
665 ሺ ዶላር ጉቦ ተቀብለዋል በሚል ክስ ፍርድ ቤት መቅረባቸው የሙስናውን መጠንና ደረጃ ያሳይል የሚሉ በርካታ ናቸው።
የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ፓርቲ ከ986 ዓም. ጀምሮ
በስልጣን የነበረ ሲሆን በ2009 ዓም. በሚደረገው ብሔራዊ ምርጫ ስልጣኑን ሊያጣ ይችላል ተብሎ ተገምቷል።
በዛሬው ዕለት በየከተሞቹ በፕሬዚዳንት ዙማ ላይ ተቃውሞ ያሰሙት
ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን ተቃውሞ እያደገ እንደሚሄድ ብዙዎቹ ይገምታሉ።
Ø
በሚቀጥሉት አምስት
አመታት ሳኡዲ አረቢያ ለግብጽ ስምንት ቢሊዮን ዶላር የሚገመት መዋዕለ ንዋይ ለማፈሰስ እና እርዳታ ለመስጠት ያቀደች መሆኗን
ገለጸች ። የሳዑዲ አረቢያ ንጉስ ሳልማን መዋዕለ ንዋዩና እርዳታው እንዲደረግና የግብጽን የነዳጅ ፍላጎት ለማሟላት እርዳታ
እንዲሰጥ ማዘዛቸውን በመግለጽ የሳኡዲ ጋዜጦች በዛሬው ቀን
እትማቸው አስፍረዋል። የሳኡዲ መንግስት ለግብጽ እርዳታ ለመስጠት ቃል የገባው በነዳጅ ዋጋ መውደቅ ምክንያት ዘጠና ከመቶ
የሚሆነውን ገቢ ባጣበት ወቅት ነው። ግብጽ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጅምሮ በየመን ውስጥ በሳኡዲ ከሚመራው ኃይል ጋር ተሰልፋ
የሁቲ አማጽያንን እየወጋች ሲሆን ባለፈው ሰኞ የተቋቋመውም የአረብ አገሮች የጸረ ሽብር ህብረት አባል ናት። ባለፈው መጋቢት
የተባበሩት አረብ ኢምሬትና ኩዊት እያንዳንዳቸው 4 ቢሊዮን ዶላር ለግብጽ በርዳታ መልክ መስጠታቸው ይታወሳል።
Ø
በአፍሪካ ህብረት
የሚደገፈው የአፍሪካ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አጥኝ ቡድን ከህዳር 27 ቀን እስከ ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓም. በብሩንዲ ተገኝቶ
ሁኔታዎችን ከመረመረ በኋላ በሰጠው መግለጫ በአገሪቱ ውስጥ እየተካሂዱ ያሉት ግጭቶችና የሽብር ድርግቶች በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ
የደረሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። መርማሪ ቡድኑ በአገሪቱ ውስጥ ባደረገው ቆይታ በርካታ ያለፍርድ የሚገደሉ ያለ ህግ የሚያዙና፤
ሰቆቃዊ ድርጊት የሚፈጽምባቸው መኖራቸውን ገልጾ ባልታወቁ ሰዎች
የሚገደሉ፤ ንብረታቸው የሚወድም እና ያለፍላጎታቸው የሚሰደደዱ ሰዎች
በብዛት መኖራቸውን ለማወቅ የቻለ መሆኑን በመጥቀስ ሁኔታው ወደ
አጠቃላይ የርስ በርስ ጦርነት እያመራ ነው ብሏል። ጉዳዩ መፍትሄ ሊያገኝ የሚችለው በውይይትና በንግግር እንጅ በኃይል
እንዳልሆነም የቡድኑ አባላት ጫና ሰጥተው ተናገረዋል።
ታኅሣሥ 5 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የግብጽ መርማሪዎች
የሩሲያ አውሮፕላን በፈንጅ መውደቁን የሚያረጋግጥ ምንም መረጃ
አላገኘንም ማለታቸው ታወቀ። ከሁለት ወር በፊት የሩሲያ አውሮፕላን በግብጽ ሳይናይ ባህረ ሰላጤ ከአየር ላይ ወድቆ በመከስከሱ
224 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል። አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን ፈንጅ በመቅበር አውሮፕላኑ ከአየር እንዲወርድ ያደረገ መሆኑን
የገለጸ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሩሲያም ተበታትኖ ከወደቀው የአውሮፕላኑ አካል ላይ የፈንጅ ንጥረ ነገር ያገኘ መሆኑን በመግለጸ
በአይሲስ ላይ የተጠናከረ የአየር ጥቃት በማካሄድ ላይ ይገኛል። የግብጽ የመርማሪዎች ቡድን
በታህሣሥ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ
እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወይም ህገወጥ በሆነ
መንገድ መውደቁን የሚያሳይ ምንም ዓይነት መረጃ አላገኘም ብለዋል። ቡድኑ የአውሮፕላኑኑ 38 ኮምፒውተሮችና ሁለት ከሞተር ጋር
የተያያዙ የቴክኖሎጂ መሳርያዎችን የመረመረ መሆኑን ለ15 ጊዜ ያህል ወደ አውሮፕላኑ ወደ ወደቀበት ቦታ በመጓዝ ምርመራ ያካሄደ
መሆኑን ገልጿል፡፤ እስካሁን ድረስ ባደረገው ምርመራ
አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወድቆ ለመከስከሱ ፍንጭ የሚሆን ምንም ዓይነት መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል።
Ø
የቀድሞ የብሩንዲ
የመከላከያ ሚንስትር እንዲሁም ሌሎች 27 የጦር እና
የፖሊስ ጄኔራሎች ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆኑ ታውቋል።
ግለሰቦቹ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ የፕሬዚዳንት እንኩርንዚናን መንግስት ለመገልበጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ
ሞክራችኋል፤ ሰዎችን በማነሳሳት ግድያ እንዲፈጽምና በንበረት ላይ
ጉዳት እንዲደርስ አድርጋችኋል አ
የሚሉ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን የእምነት ክህደት ቃላቸው ሳይሰጡ የቀሩ መሆናችው ታውቋል። የመከላከያ ሚኒስትሩን
ጨምሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት አብዛኞቹ ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት
ቃል ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ በሆነና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በተገለለ ቦታ መታሰራቸውን እንዲሁም ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ
በባልዲ ውስጥ እንዲጸዳዱ
የተገደዱ መሆናቸውን ገልጸው የእስር ቤቱ ሁኔታ እስካልተሻሻለ ድረስ ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ እንደማይሆኑ አስረድተዋል።
በተያያዘ ዜና የአገሪቱ የእርስ በርስ ግጭት እየተባባሰ በመሄዱና
የጸጥታው ሁኔታ አስጊ እየሆነ በመምጣቱ ምክንያት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለስራ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ብሩንዲ
የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎች ወደ ብሩንዲ እንዳይሄዱና የሄዱት ከፍተኛ
ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ለዜጎቹ ማሳሰቢያ አስተላፏል።
Ø
ትናንት እሁድ ታኅሣሥ
3 ቀን 2008 ዓም. በናይጄሪያ ሰሜናዊ ግዛት ዛሪያ በተባለው
ከተማ የመንግስት ወታደሮች የሺያ እስልምና ተከታይ በሆኑ ዜጎች
ላይ ባካሄዱት ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ የተገደሉ መሆናቸውንና መስጊዱ መደምሰሱን የሺያ ሙስሊም እንቅስቃሴ የሚባለለው ድርጅት
ገልጿል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል የየእምነቱ መሪ የሆኑት የሼክ ኢብራሂም ዛግራኪ ባለቤትና ሁለት ልጆቻቸው የሚገኙበት ሲሆን
ሼኩ ተይዘው እንደደረሱ
ያልታወቀ መሆኑ ተነግሯል። በትናንትናው ቀን የናይጄሪያ
ወታደሮች ወደቦታው ሲገቡ የእምነቱ ተከታዮች የላሲቲክ ጎማ በማቃጥል
መንገድ መዝጋታቸው የተዘገበ ሲሆን የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር
ይጓዙበት በነበረ መኪና ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሞክረው እንደነበረም የአይን እማኞች ገልጸዋል። ጄኔራሉን
ለመግደል ሙከራ ተድርጓል በሚል ምክንያት የናይጄሪያ ወታደሮች በወሰዱት የበቀል እርምጃ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል።
በሰሜን ናይጄሪ የእስላምና ኃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን አብዛኞቹ የሱኒ እምነት ተከታዮች መሆናቸውም ይታወቃል።
Ø
ትናንት እሁድ ታኃሣሥ
3 ቀን 2008 ዓ.ም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በጊዜያዊ መንግስቱ የቀረበውን ረቂቅ ሕገ መንግስት ለማጽደቅ ምርጫ የተካሄደ
ሲሆን በዋናው ከተማዋ በባንጉ እና በሌሎች ቦታዎች ምርጫውን ለማስቆም የተለያዩ ኃይሎች በፈጠሩት ግጭት አምስት ሰዎች መሞታቸውና
ከ20 ሰዎች በላይ መቁሰላቸው ታውቋል። የቀረበው ረቂቅ ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የስልጣን እድሜ በሁለት የስልጣን ዘመኖች
የሚገድብ ሲሆን ፤ ሙስናና የሚቆጣጠርና የሚሊሺያዎችን ህልውና የሚገድቡ አንቀጾች ያሉት መሆኑም ተነግሯል።
Ø
የመን ተጻራሪ ኃይሎች
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በጄኔቫ የሰላም ውይይት ስብሰባ ከሚጀመሩበት
ከዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 4 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸው ተገለጸ።
የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን የየየመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያረጋገጡ ሲሆን የሁቲ አማጽያን ቡድንም ስምምነቱን
በማረጋገጥ መግለጫ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ ታይዚዝ በተባለችው የየመን ከተማ አንድ የሳኡዲ ኮሎኔል
እና የዩናይትድ አራብ ኤምራቲ ዜጋ ወታደራዊ መኮንን በርቀት በተተኮስ ሮኬት ህይወታቸው ያለፈው መሆኑ ተነግሯል። የየመን የርስ
በርስ ግጭት ከተጀመረ ጀምሮ ከ6 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አባዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።
ታኅሣሥ4 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የግብጽ መርማሪዎች
የሩሲያ አውሮፕላን በፈንጅ መውደቁን የሚያረጋግጥ ምንም መረጃ
አላገኘንም ማለታቸው ታወቀ። ከሁለት ወር በፊት የሩሲያ አውሮፕላን በግብጽ ሳይናይ ባህረ ሰላጤ ከአየር ላይ ወድቆ በመከስከሱ
224 ሰዎች መሞታቸው ይታወቃል። አይሲስ የተባለው አሸባሪ ቡድን ፈንጅ በመቅበር አውሮፕላኑ ከአየር እንዲወርድ ያደረገ መሆኑን
የገለጸ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሩሲያም ተበታትኖ ከወደቀው የአውሮፕላኑ አካል ላይ የፈንጅ ንጥረ ነገር ያገኘ መሆኑን በመግለጸ
በአይሲስ ላይ የተጠናከረ የአየር ጥቃት በማካሄድ ላይ ይገኛል። የግብጽ የመርማሪዎች ቡድን
በታህሣሥ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ
እስካሁን ድረስ አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወይም ህገወጥ በሆነ
መንገድ መውደቁን የሚያሳይ ምንም ዓይነት መረጃ አላገኘም ብለዋል። ቡድኑ የአውሮፕላኑኑ 38 ኮምፒውተሮችና ሁለት ከሞተር ጋር
የተያያዙ የቴክኖሎጂ መሳርያዎችን የመረመረ መሆኑን ለ15 ጊዜ ያህል ወደ አውሮፕላኑ ወደ ወደቀበት ቦታ በመጓዝ ምርመራ ያካሄደ
መሆኑን ገልጿል፡፤ እስካሁን ድረስ ባደረገው ምርመራ
አውሮፕላኑ በሽብር ተግባር ወድቆ ለመከስከሱ ፍንጭ የሚሆን ምንም ዓይነት መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል።
Ø
የቀድሞ የብሩንዲ
የመከላከያ ሚንስትር እንዲሁም ሌሎች 27 የጦር እና
የፖሊስ ጄኔራሎች ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆኑ ታውቋል።
ግለሰቦቹ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ የፕሬዚዳንት እንኩርንዚናን መንግስት ለመገልበጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ
ሞክራችኋል፤ ሰዎችን በማነሳሳት ግድያ እንዲፈጽምና በንበረት ላይ
ጉዳት እንዲደርስ አድርጋችኋል አ
የሚሉ ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን የእምነት ክህደት ቃላቸው ሳይሰጡ የቀሩ መሆናችው ታውቋል። የመከላከያ ሚኒስትሩን
ጨምሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት አብዛኞቹ ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት
ቃል ከሰብዓዊ ርህራሄ ውጭ በሆነና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በተገለለ ቦታ መታሰራቸውን እንዲሁም ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ
በባልዲ ውስጥ እንዲጸዳዱ
የተገደዱ መሆናቸውን ገልጸው የእስር ቤቱ ሁኔታ እስካልተሻሻለ ድረስ ቃላቸውን ለመስጠት ፈቃደኛ እንደማይሆኑ አስረድተዋል።
በተያያዘ ዜና የአገሪቱ የእርስ በርስ ግጭት እየተባባሰ በመሄዱና
የጸጥታው ሁኔታ አስጊ እየሆነ በመምጣቱ ምክንያት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለስራ አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ብሩንዲ
የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎች ወደ ብሩንዲ እንዳይሄዱና የሄዱት ከፍተኛ
ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ለዜጎቹ ማሳሰቢያ አስተላፏል።
Ø
ትናንት እሁድ ታኅሣሥ
3 ቀን 2008 ዓም. በናይጄሪያ ሰሜናዊ ግዛት ዛሪያ በተባለው
ከተማ የመንግስት ወታደሮች የሺያ እስልምና ተከታይ በሆኑ ዜጎች
ላይ ባካሄዱት ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ የተገደሉ መሆናቸውንና መስጊዱ መደምሰሱን የሺያ ሙስሊም እንቅስቃሴ የሚባለለው ድርጅት
ገልጿል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል የየእምነቱ መሪ የሆኑት የሼክ ኢብራሂም ዛግራኪ ባለቤትና ሁለት ልጆቻቸው የሚገኙበት ሲሆን
ሼኩ ተይዘው እንደደረሱ
ያልታወቀ መሆኑ ተነግሯል። በትናንትናው ቀን የናይጄሪያ
ወታደሮች ወደቦታው ሲገቡ የእምነቱ ተከታዮች የላሲቲክ ጎማ በማቃጥል
መንገድ መዝጋታቸው የተዘገበ ሲሆን የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስትር
ይጓዙበት በነበረ መኪና ላይ ድንጋይ በመወርወር ጥቃት ለመፈጸም ሞክረው እንደነበረም የአይን እማኞች ገልጸዋል። ጄኔራሉን
ለመግደል ሙከራ ተድርጓል በሚል ምክንያት የናይጄሪያ ወታደሮች በወሰዱት የበቀል እርምጃ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል።
በሰሜን ናይጄሪ የእስላምና ኃይማኖት ተከታዮች ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን አብዛኞቹ የሱኒ እምነት ተከታዮች መሆናቸውም ይታወቃል።
Ø
ትናንት እሁድ ታኃሣሥ
3 ቀን 2008 ዓ.ም. በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በጊዜያዊ መንግስቱ የቀረበውን ረቂቅ ሕገ መንግስት ለማጽደቅ ምርጫ የተካሄደ
ሲሆን በዋናው ከተማዋ በባንጉ እና በሌሎች ቦታዎች ምርጫውን ለማስቆም የተለያዩ ኃይሎች በፈጠሩት ግጭት አምስት ሰዎች መሞታቸውና
ከ20 ሰዎች በላይ መቁሰላቸው ታውቋል። የቀረበው ረቂቅ ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የስልጣን እድሜ በሁለት የስልጣን ዘመኖች
የሚገድብ ሲሆን ፤ ሙስናና የሚቆጣጠርና የሚሊሺያዎችን ህልውና የሚገድቡ አንቀጾች ያሉት መሆኑም ተነግሯል።
Ø
የመን ተጻራሪ ኃይሎች
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በጄኔቫ የሰላም ውይይት ስብሰባ ከሚጀመሩበት
ከዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 4 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸው ተገለጸ።
የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉን የየየመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያረጋገጡ ሲሆን የሁቲ አማጽያን ቡድንም ስምምነቱን
በማረጋገጥ መግለጫ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ ታይዚዝ በተባለችው የየመን ከተማ አንድ የሳኡዲ ኮሎኔል
እና የዩናይትድ አራብ ኤምራቲ ዜጋ ወታደራዊ መኮንን በርቀት በተተኮስ ሮኬት ህይወታቸው ያለፈው መሆኑ ተነግሯል። የየመን የርስ
በርስ ግጭት ከተጀመረ ጀምሮ ከ6 ሺ ሰዎች በላይ የሞቱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አባዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።
ታኅሣሥ 2 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በምዕራብ አፍሪካ
የምትገኘው ጋምቢያ እስልማዊ ሪፐብሊክ መሆኗን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ያያ ጃሜህ በተሌቪዥን ባሰሙት ንግግር አስታውቀዋል። ጃሜህ
በሰጡት መግለጫ አብዛኛው የአገሪቱ ህዝብ የእስልምና ተከታይ ስለሆነ አብዛኛው ከሚከተለው እምነት ጋር ለማጣጣም
የቅኝ ገዥዎች የጣሉብንን የባህልና የእምነት ጫናን አስወግደን አገራችንን እስላማዊ ሪፐብሊክ እንድትሆን መርጠናል
ብለዋል። ዜጎች አለባበሳቸውን እንዲቀይሩ የማይገደዱ ሲሆን የሌላ እምነቶች ተከታዮችም በነጻ መንቀሳቀስ ይችላሉ ተብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ በስልጣን ላይ ከ21 ዓመታት በላይ የቆዩ ሲሆን መንግስታቸው በቅርቡ በአገሪቱ ውስጥ ባለው የሰብአዊ መብት ረገጣ
ምክንያት ከምዕራብ አገሮች አገር አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል። በእስያ አህጉር
ፓኪስታንና ኢራን በአፍሪካ ደግሞ ሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ
መንግስታትን የመሰረቱ መሆኗቸው ይታወቃል።
Ø
በብሩንዲ ዋና ከተማ
በቡጁምቡራ ውስጥ ዛሬ ታኅሣሥ 2 ቀን 2008 ዓ.ም. የ21 ሰዎች አስከሬን መሬት ላይ ተዘርሮ የተገኘ መሆኑ የዜና ምንጮች
ገለጹ። ተገድለው ከተጣሉት መካከል ብዙዎቹ ወጣቶች ሲሆኑ እጃቸውን ወደ ኋላ ታስረው በጥይት የተገደሉ መሆናቸውንም ለማየት
ተችሏል። ይህ ግድያ የተፈጸመው የአማጽያን ኃይሎች በሁለት ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ ወረራ አካሄደው ጉዳት ባደረሱ ከአንድ ቀን
በኋላ ነው። የተባበሩት መንግስታት፣ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የመንግስት ባለስልጣናት በብሩንዲ ያለው ችግር በውይይትና
በእርቅ ካልተፈታ ወደ አጠቃላይ የእርስ በርስ እልቂት ሊያመራ የሚችል መሆኑን በተደጋጋሚ ማስጠንቀቃቸው አይዘነጋም።
በተያያዘ ዜና በአሜሪካ
አሳሳቢነት የተባብሩት መንግታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ካውንስል በሚቀጥለው ሳምንት ሐሙስ የብሩንዲው ጉዳይን አስመልክቶ
አስቸኳይ ስብሰባ ጄኔቫ ላይ የጠራ መሆኑ ታውቋል። ካውንስሉ
የሚወስነው ውሳኔ ዝርዝር ባይታወቅም በቡርንዲ ያንዣበበውን አስጊ ሁኔታ ለማስወግድ ይችላሉ በሚባሉ መፍትሄዎች ላይ ውስጥ ይሰጣል
ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
ላለፉት ሁለት ቀናት
በቱኒዚያ ከተማ በቱኒስ ሲወያዩ የቆዩት የሁለቱ የሊቢያ ተጻራሪ አስተዳደር ወኪሎች
በሚቀጥለው ሳምንት በሮማ ከተማ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ የሚቀርበውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርቅ ሀሳብ
ለመቀበልና ፊርማቸውን ለማኖር የተስማሙ መሆናቸው ተገለጸ። ስምምነቱ አንድ ብሔራዊ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር ሲሆን ዝርዝሩ
ምን ሊሆን እንደሚችል አልተገለጸም። በቱኒስ የተደረገውን ስምምነት የእያንዳንዱ አስተዳደር ምክር ቤት ገና ያላጸደቀው ቢሆንም
በሁለቱም በኩል ያሉት አብዛኞቹ አባላት ስምምነቱን ይደግፉታል በማለት ተወካዮቹ ተናግረዋል።
Ø
ናይጄሪያ በቦካ ሃራም
እንቅስቃሴ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተስደዱትን 2.3 ሚሊዮን ዜጓቿን ከሚቀጥለው
የፈረንጆቹ ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ የምታደርግ መሆኗን ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ገለጹ። ስደተኞቹ የተፈናቀሉባቸው
ከተሞችና መንደሮች አብዛኞቹን የመንግስቱ ወታደሮች ከቦኮሃራም ታጣቂዎች ነጻ ያደረጓቸው ሲሆን ቦኮሃራምን ለማዳከምና ለመደምሰስ
እየተወሰደ ያለው ወታደራዊ ርምጃ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ሰደተኛው ለማጓጓዝም ሆነ መልሶ ለማቋቋም በርካታ ገንዘብ
የሚያስፈልግ ሲሆን ብዙዎቹ ስደተኞቹ ቤቶቻቸው የፈረሱባቸው በመሆኑ በርካታ የግንባታ ስራ የሚያስፈልግ መሆኑ ተገልጿል።
ታኅሣሥ 1 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአባይ ግድብ ግንባታ ምክንያት ግብጽና ወያኔ ያልተስማሙ መሆኑ በተደጋጋሚ የተነገረ
ሲሆን ችግሩ ወደ ሌላ ደረጃ ከመዘዋወሩ በፊት የተባበሩት አረብ ኤምሬትን አስታራቂነት ግብጽ የጠየቀች መሆኑን ሚድል
ኢስት ሞኒተር የተባለ ጋዜጣ ገልጿል። እንደጋዜጣው መረጃ ባለፉት ሁለት ሳምንታት የአቡዳቢው አልጋ ወራሽና የኤምሬት የመከለካያ
ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት ሼክ መሀመድ ቢን ዜይድ ከሱዳኑ በሽርና ከወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ከኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር አቡዳቢ
ውስጥ የተነጋገሩ መሆኑን ገልጾ አልጋወራሹ በቅርቡ በዚህ
ጉዳይ ላይ ከወያኔ ባለስልጣኖች ጋር ንግግር ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሄዱ በመረጃ መልክ አቅርቧል። ሁለት ጊዜ አቡዳቢን
የጎበኙት የሱዳኑ በሽርም ግብጽና ወያኔ ባላቸው ልዩነት ሱዳን ወያኔን ደግፋ እንደማትቆም ተናግረዋል
ብሏል። የግብጹ ረዳት የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ለጋዜጣው በሰጠው ቃል
ግብጽ የተባበሩት አረብ ኤምሬትን አማላጅነት የጠየቀችው ከሁለት ዓመት በፊት መሆኑን ገልጾ አገሪቷ በኢትዮጵያ ውስጥ በእርሻ እና
በኢንዱትስትሪ መስክ ከፍተኛ መዋእለ ንዋይ ያፈሰሰች ስለሆነ ተጽእኖ ሊኖራት ይችላል ከሚል ግምት ነው ብሏል።
Ø
ኬኒያ ኡጋንዳ ሩዋንዳና
ደበቡ ሱዳን በጋራ በፈጠሩት ኖርዘርን ኮሪዶር ኢንተግሬሽን ፕሮጀክት (NCIP) በሚባለውና የተለያዩ የልማት ስራዎች በጋራና
በተቀናጀ መልክ ለመስራትና ለማስተባበር በተቋቋመው አካል ውስጥ አባል ለመሆን ወያኔ በይፋ የጠየቀ መሆኑ ታወቀ። ኪጋሊ ሩዋንዳ
በተደረገው ስብሰባ ላይ ጥያቄውን በይፋ ያቀረበው የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሲሆን እስከዛሬ ደረስ በታዛቢነት
ሲካፈሉ የቆዩ መሆናቸውን ገልጾ ከእንግዲህ ወዲያ በአባልነት ለመስራት የሚፈልጉ መሆናቸውን ተናግሯል። የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር
ኃይለማርያም ደሳለኝም በሚቀጥለው የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንደሚገኝ አስረድቷል።
Ø
በብሩንዲ ዋና ከተማ
ቡጁምቡራ ውስጥ፡አማጽያን በሁለት ወታደራዊ ጦር ሰፈሮች ላይ በሰነዘሯቸው ጥቃቶች ስምንት ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ሲታወቅ ከሞቱት
መካከል ጥቂቶቹ ጥቃቱን የሰነዘሩት መሆናቸው ታውቋል።
አማጽያኑ ከሌሊቱ አስር ሰዓት ላይ ጥቃቱን የጀመሩት ጋጋራ በተባለው ከተማው ሰሜን በሆነው አካባቢ እና ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያ
በሆነውና ሙሳጋ በሚባለው በከተማዋ ደቡብ በሚገኘው ቦታ ላይ ሲሆን ከሁለት ሰዓቶች ውጊያዎች በኋላ አጥቂዎቹ ያፈገፈጉ መሆናቸውን
የብሩንዲ ወታድራዊ ቃል አቀባዮች ገልጸዋል። ተኩሱ ከፍተኛ
ስለነበር ነዋሪዎች ወደ ስራቸው ለመሄድም ሆነ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ፈርተው በቤት ውስጥ የዋሉ መሆናቸውን
የሚደርሱት ዘገባዎች ይገልጻሉ። አካባቢዎቹ የቡርንዲን ፕሬዚዳንት የሚቃወሙት የአማጽያን ቡድን ጠንካራ ድጋፍ ያለባቸው ሲሆን ዛሬ
በወታደራዊ ካሞቹ ላይ የተካሂዱት ጥቃቶች ካለፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ወዲህ በወታደራዊ ተቋም ላይ ይህን የመሰለ ጥቃት
ሲደርስ የመጀመሪያው ነው ተብሏል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በወታደራዊና የጸጥታ ኃይሎች አባላት ላይ አማጽያኑ የሚያደርጉት
ደፈጣና ጥቃት እየጨመረ መሆኑ የሚነገር ሲሆን በዛሬው ቀን የተካሄዱትም ጥቃቶች
የታሰሩ እስረኞችን ለማስፈታት የተደረገ ነው የሚል መረጃ አለ። የመንግስት ወታደሮች አማጽያኑን ያባረሩ መሆኑን
ቢገልጹም በከተማዋ አንዳንድ ቦታዎች ለረጅም ሰዓታት ተኩስ ሲሰማ ቆይቷል። የካቢኒ ሚኒስትሮች አስቸኳይ ስብሰባ ያደረጉ መሆናቸው
ሲታወቅ ምናልባት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊታወጅ ይችላል የሚል ዜናም አለ። የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት እንኩሩንዚዛ ህገ ወጥ በሆነ ምክንያት ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ውድድር መቅረባቸውን በመቃወም በተነሳ የተቃውሞ
እንቅስቃሴ ቢያንስ 240 ሰዎች መገደላቸውና ከ200 ሺ ሰዎች በላይ መሰደዳቸው ይታወሳል።
Ø
የሊቢያ ተጻራሪ ኃይሎች
በቱኒዚያ ከተማ በቱኒስ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መገናኛታቸው ታወቀ። ስብሰባው ቀደም ብሎ በተመድ በቀረበውና ሁለቱም ወገኖች
በተቃወሙት ሀሳብ ላይ በይበልጥ ተወያይቶ መግባባት ላይ በመድረስ በመጭው እሁድ በጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ላይ ለሚካሄደው ስብሰባ
ሁኔታውን ለማመቻቸት ነው ተብሏል። በቱኒሱ ስብሰባ ላይ የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት የሊቢያ ጉዳይ ተወካይና የውጭ አገር መንግስት ዲፕሎማቶች በስበስባው ላይ መገኘታው ተነገሯል። የተመድ ተወካይ የሀሙሱ
ስብሰባ ፍሬያማ ነበር በማለት እሁድ በእሁዱ ስብሰባ ለሚጠናቀቀው ለመጨረሻው ስምምነት ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል። ስብሰባው
በዛሬውም ዕለት ይቀጥላል ተብሏል። እሁድ ዕለት በሮም
ከተማ የሚደረገውን ስብሰባ በሊቀ መንበርነት የሚመሩት የአሜሪካው እና የጣሊያኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሲሆኑ የሩሲያ የእንግሊዝ
የቻይናና የፈረንሳይ ተወካዮች የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል። ከጋዳፊ ውድቀት በኋላ በምዕራብና በምስራቅ ሊቢያ ሁለት ተጻራሪ
መንግስታት ተቋቋመው የሚንቀሳቀሱ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በፊት በተመድ ቀርቦ የነበረውን የእርቅ ሀሳብ በምስራቅ የሚገኘውና መንግስት
ነኝ የሚለው አካል ሳይቀብል መቆየቱ ይታወሳል። ባለፈው ሳምንት ሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች ቱኒስ ውስጥ ባደረጉት የመጀመሪያ ዙር
ውይይት በአገሪቱ ውስጥ የአንድነት መንግስት ለመፍጠር በመርህ ደረጃ ስምምነት ያደረጉ መሆናቸው ተነግሯል።
ህዳር 30 ቀን 2008 ዓ.ም
·
የተማሪዎችና የሕዝብ የተቃውሞ እንቅስቅሴ ቀጥሏል
·
በዋሽንግተን የተቃውሞ ስልፍ ተደረገ
·
ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች የባህል ቀን በጋምቤላ እያከበርኩ ነኝ ይላል፤ የሱዳኑ መሪ
በበዓሉ ላይ ተገኝተዋል
·
ናይሮቢ ውስጥ 54 ኢትዮጵያውን ህገ-ወጥ ናችሁ ተብለው ታሰሩ
·
ብሩንዲ ውስጥ ፖሊስ አምስት ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ረሸነ
·
ወደ አፍርካ ቀንድና የገልፍ አገሮች የተሰደዱ የመናውያን ቁጥር 170 ሺ ደረሰ
ተባለ
·
አራቱ የቱኒዚያ ሲቪል ማህበራት ተወካዮች ኦስሎ ውስጥ የኖቤል ሽልማታቸውን ተቀበሉ
·
በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ የሩዋንዳው እልቂት ወንጀለኛ ተያዘ
Ø
ትናንት ረቡዕ ህዳር
29 ቀን 2015 ዓ.ም. 54 በናይሮቢ ኬኒያ ውስጥ ፖሊስ 54 ኢትዮጵያውያንን ህገ ወጥ ናችሁ በማለት ይዞ ያሰረ መሆኑን
የናይሮቢ ፖሊስ አዛዥ ለአንድ የኬኒያ ጋዜጣ ከሰጡት መግለጫ ለማወቅ ተችሏል። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት በነዋሪዎች ጥቆማ ያድሩበት
ከነበሩት ሶስት የመኝታ ክፍሎች ሲሆን በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተገልጿል። ኬኒያን እንደመሸጋገሪያ አድርገው ወደ
ታንዛኒያና ኬኒያ የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ቁጥር የጨመረ የመጣ መሆኑና በሞያሌ እና በሌሎች ቦታዎች ከ20 በላይ የሚሆኑ
መፈተሻ ጣቢያዎች ቢኖሩም የስደተኞቹ ቁጥር ሊቀንስ ያልቻለ መሆኑ ተገልጿል። ለስደተኞቹ መተኛ ክፍሎችን ሰጥተዋል የተባሉ ሶስት
ኬኒያውያንም አብረው የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
ማክሰኞ ህዳር 28 ቀን
2008 ዓም ማታ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ማንነቱ አማጽያን ናቸው ተብለው ከሚጠረጠሩ ግለሰቦች የተወረወሩ ቦምቦች
ፈንድተው አንድ ፖሊስና እንድ ሰላማዊ ሰው የገደሉ ሲሆን አጸፋውን ለመመለስ በማግስቱ ረቡዕ ህዳር 29 ቀን 2008 ዓም.
ፖሊሶች በወሰዱት ርምጃ ቦምቦቹን ወርውረዋል ብለው የጠረጠሯቸውን አምስት
ሰዎች ግምባራቸውንና ጀርባቸውን በመምታት የረሸኗቸው መሆኑን የአይን እማኞች መስክረዋል። ፖሊስ በሰጠው መረጃ ሶስተኛ ቦምብ
ሲወረወር ፖሊሶች በወሰዱት የመከላከል ርምጃ ነው ያለ ቢሆንም የዓይን እማኞቹ ግን ሰዎቹ ከተያዙና በቁጥጥር ስር ከተደረጉ በኋላ
በቅርብ ርቀት ላይ ግምባራቸውና ጀርባቸው ተመቶ የተረሸኑ መሆናቸውን ይገልጻሉ። የዚህ ዓይነት የጅምላ ርሸና ብሩንዲ ውስጥ
እየተለመደ መምጣቱ አገሪቷ ወደ አጠቃላይ የርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው የሚለውን ግምት ያጠናከረ መሆኑ ታውቋል። በዚህ
ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣኖች ችግሮቹ በውይይት
ካልተፈቱ አገሪቷ እየገባችበት ያለው የእርስ በርስ ጦርነት ከፍተኛ እልቂት ሊያስከተል እንደሚችል ያላቸውን ስጋት መግለጻቸው
ይታወሳል።
Ø
በየመን እየተካሄደ
ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት 170 ሺ የሚሆኑ የመናውያን ጦርነቱን በመሸሽ ወደ አፍሪካ ቀንድ አገሮችና የገልፍ የአረብ
አገሮች የተሰደዱ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽንና አይ ኦ ኤም የሚባለው የዓለም አቀፍ
የስደተኛ ድርጅት ገልጸዋል። ድርጅቶቹ ይህንን መግለጫ የሰጡት ኬኒያ ውስጥ ስለእርዳታ
ጉዳይ ከተደረገው ስብሰባ ማጠናቀቂያ በኋላ ሲሆን ስደተኞች ወደ
ጂቡቲ፤ ኢትዮጵያ፤ ሶማሊያ ሱዳን እና ወደ ገልፍ አገሮች መሄዳቸውን ገልጸው ከ94 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ
እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የየመን የእርስ በርስ ጦርነት ከተጀመረ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ በርካታ ሰዎች በጦርነት የሞቱና አካላቸው
የጎደለ ሲሆን 2.3 ሚሊዮን የሚሆኑት ቤትና ንብረታቸውን
ጥለው ለመሰደድ ተገደዋል። ከአገሪቱ 80 ከመቶ የሚሆነው ህዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑም ተነግሯል።
Ø
ዛሬ ህዳር 30 ቀን
2008 ዓም አራቱ የቱኒዝያ የብሔራዊ የውይይት መድረክ የሚባሉት ማህበራት
ተወካዮች በአገራቸው ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው ያገኙትን የኖቤል ሽልማት ኖርዌይ ኦስሎ
በተካሄደ የሽልማት አሰጣጥ ስነስርዓት ላይ ተቀብለዋል። የኖርዌጂያኑ ኖቤል ኮሚቴ ተወካይ በስነስርዓቱ ላይ ባሰሙት ንግግር
በአገሪቱ ውስጥ አምባገነን ሥርዓት ከተወገደ በኋላ
አራቱ የህብረተሰብ ማህበሮች ዴሞክራሲያው ስርዓት በአገሪቱ እንዲሰፍን ቆራጥና ከፍተኛ አስተዋጾ በማድረጋቸው ሽልማቱ
ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ሽልማቱን ያገኙት አራቱ ድርጅቶች- የቱኒዚያ
ጠቅላላ የሰራተኞች ማህበር፤ የቱኒዚያ የኢንደስትሪ፣ የንግድና የእጅ ስራ ኮንፌዴሬሽን፤ የቱኒዚያ የሰብአዊ መብት ሊግ፤ የቱኒዚያ
የህግ ባለሙያዎች ማህበር ተወካዮች ናቸው።
Ø
ኒያኪዙ የተባለችው
የሩዋንዳ ከተማ ከንቲባ የነበረውና በ1987 ዓም 800 ሺ ህዝብ በጨረሸው የሰው ዘር ማጥፋት እልቂት በወንጀል ሲፈለገ የነበረው
ላዲስላስ እንታጋንዝዋ የተባለው የ53 ዓመቱ ወንጀለኛ
ባለፈው ሰኞ ኮንጎ ውስጥ መያዙን ባለስልጣኖች በዛሬው ዕለት ገልጸዋል። ባለፉት 20 ዓመታት ግለሰቡ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ
ሲሆን ወንጀለኛውን ይዞ ላስረከበ ወይም ለገደለ የ አምስት
ሚሊዮን ዶላር ካሳ የሚከፈል መሆኑ ተገልጾ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ግለሰቡ የከተማዋ ከንቲባ ሆኖ በሰራበት ወቅት በርካታ
ቱሲዎችንና ሰላማዊ ሁቲዎችን ጨርሷል ተብሎ የተወነጀለ ሲሆን እየተፈለጉ ከነበሩት ዘጠኝ ቀንደኛ ገዳዮችና አስገዳዮች መካከል
አንደኛው እንደነበር ይታወሳል።
ህዳር 29 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ከህዳር 26 እስከ ህዳር 27 ቀን ካርቱም ሱዳን ውስጥ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የግብጽ የሱዳንና የወያኔ ባለስልጣኖች
ስብሰባ በወያኔ ጠያቂነት ለታህሳስ 1 እና 2፣ 2008 ዓ.ም. እንዲተላለፍ
መደረጉን ተከትሎ የግብጽ የመስኖ ልማት አማካሪ
በወያኔ ላይ ክስ የሰነዘሩ መሆኑን ሱዳን ታይምስ የተባለው የሱዳን ጋዜጣ በትናንትናው ዕትሙ ላይ አውጥቶታል። ባለስልጣኑ ሲጀመር
በአንድ ወር ውስጥ ያልቃል ተብሎ የነበረው ውይይት ከስድስት ወር በላይ ሊፈጅ የቻለው በወያኔ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው የአነው
ሁኑን ስብስባውም ያራዘመው ግድቡ ሊፈርስ የማይችልበት ደረጃ እንዲደረስ ለግንባታው ስራ ጊዜ ለመግዛት ብለዋል። የ የወያኔ ቡድን
ስብሰባው እንዲዘገይ የጠየቀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኬኒያ ጋር በወሰን አካባቢ በተደረገው ስነስርዓት ላይ መገኘት ስላለበት
ነው ብሏል። የግብጽ መንግስት ባለስልጣኖች ግድቡ ወደ አጌራቸው የሚሄደውን የአባይ ውሃ መጠን ይቀንሳል የሚል እምነት ያላቸው
ሲሆን ባንድ ወቅት ግድቡን ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ አስበው እንደነበር ይታወሳል። ባለስልጣኑ ግብጽ ውሃው የሚቀንስ
መሆኑን ካረጋገጠች የግድቡ ስራ እንዲቆም በይፋ ትጠይቃለች ካሉ በኋላ ወያኔ ሌላ ዓላማ ካለውም ጉዳያችንን ለአለም አቀፉ ተቋሞች
እናቀርባለን የሚል መግለጫም ሰጥተዋል።
Ø
አሁን በስደት ላይ የሚገኙት የቀድሞ የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ፕሬዚዳንት
ፍራንስዋ ቦዚዜ
በታህሳስ 17 ቀን 2008 ዓም ሊደረግ በታቀደው ምርጫ ላይ እንዳይወዳደሩ ምርጫውን የሚያካሄደው የህገ መንግስት
ፍርድ ቤት በማገዱ ምክንያት ትናንት ህዳር 29 ቀን 2008 ዓም
በዋና ከተማዋ ተቃዋሚዎች አንዳንድ መንግዶችን በመዝጋት ትራፊክ ዘግተው መዋላቸውና በተለያዩ ቦታዎች የተኩስ ድምጽ ሲሰማ የዋለ
መሆኑን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፖሊስ እና የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ጸጥታውን ለመቆጣጠር በወሰዱት እርምጃ ምሽቱ ላይ
ሁኔታው ሊረጋጋ። የህገ መንግስቱ ምክር ቤት ጠለቅ ያለ ማጣራት ካደረገ በኋላ መመዘኛውን ያሟላሉ ብሎ
በምርጫው እንዲወዳደሩ የፈቀደላቸው ግለስቦች 30 ሰዎች ሲሆኑ
የቀድሞው ፕሬዚዳንት እና የክርሲያኑ ሚሊሺያ መሪ በምርጫ ውድድር
ውስጥ እንዳይገቡ አድርጓል። የአገሪቱን መሪ እና 141 የፓርላማ አባሎችን ለመምረጥ በሚከናወነው የምርጫ ሂደት ላይ ድምጹን
ለመስጠት ሁለት ሚሊዮን የሚሆነው የአገሪቱ ዜጋ የተመዘገበ መሆኑም ተገልጿል። በመጀመሪያ ዙር ከተወዳዳሪዎቹ መካከል በቂ ድምጽ
በማግኘት በግልጽ አሸናፊ የሆነ ከሌለ በጥር 6 ቀን 2008 ዓም ሁለተኛ
ዙር ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል። ምርጫው በተለያዩ ጊዜያት ሲተላለፍ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል
የእስልምና ተካታይ በሆኑ አማጽያን ቁጥጥር ስር በመዋሉ ምርጫውን ለማደራጀትና ለማዘጋጀት አስቸጋሪ የነበረ መሆኑ ተዘግቧል።
Ø
በሰው
ዘር ማጥፋት ሳቢያ ህይወታቸው የጠፋውን ወገኖች ለማስታወስ በየአመቱ በሚደረገው ዓለም አቀፍ በዓልን አስመልክቶ አንድ የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት ባለስልጣን በሰጡት ገለጻ የብሩንዲው ችግር በውይይትና በድርድር ፖሊቲካዊ መፍትሄ ካላገኘ በአገሪቱ ውስጥ
የዘር ማጥፋት የሚከሰትበት ሁኔታ ከፍተኛ መሆኑን
ተናግረዋል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስው ዘር ማጥፋትን
ለመካለል የተቋቋመው ተቋም አማካሪ የሆኑት ሚስተር አዳማ ዲየንግ በሰጡት በዚህ መግለጫ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ኃይሎች
በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በሁቲና በቱሲ መካከል የዘር ልዩነቱ ተካሮ ወደ እርስ በርስ ግጭትና የዘር ማጥፋት ሁኔታ አግሪቷን
እየከተቷት መሆኑን ተናግረዋል። ችግሩ በወታደራዊ ኃይል መፍትሄ ሊያገኝ የማይችል መሆኑን ከገለጹ በኋላ በሩዋንዳ የነበረውን
ተመሳሳይ ሁኔታ አስታውሰው ውይይት ተካሄዶ መፍትሄ ካልተገኘ በብሩንዲም ተመሳሳይ ሁኔታ ይፈጠራል በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
Ø
በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በሚቀጥለው ዓመት አጠቃላይ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት የፕሬዚዳንት ካቢላ መንግስት የተቃዋሚ ፓርቲ
መሪዎችን የሲቪክ ማህበራት አባላትንና ሌሎች ተቃዋሚ ግለሰቦችን በገፍ በማሰርና በማስፈራራት ተግባር ላይ መሰማራቱ ያሳሰበው
መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ዘገባ ገልጿል። ዘገባው የሚስተር ካቢላ መንግስት ከምርጫ ጋር ተያይዞ 143
የሰብአዊ መብት ጥሰት ያደረገ መሆኑና ያለምክንያት የሚታሰሩት ሰዎች ቁጥር 649 መድርሱን አስፍሯል። መንግስቱ አፈናውንና
እስራቱን ያስፋፋባቸው ቦታዎች ተቃዋሚዎች ጠንካራ ናችው
የሚባሉባቸው እንደ ኪንሻሳ ሰሜንና ደቡብ ኪቩ እንዲሁም ምስራቃዊ ካሳይ አውራጃዎች ናቸው ተብሏል። መንግስት እያካሄደ ያለው
አፈና የዴሞክራሲውን መድርክ ከማጥበቡ ሌላ ምርጫውን ተዓማኒና
ተቀባይነት እንዳይኖረው ያደርጋል በማለት በዘገባው ገልጿል። ፕሬዚዳንት ካቢላ ከ1994 ዓም ጀምሮ በስልጣን የነበሩ ሲሆን በህገ
መንግስቱ መሰረት ባሁኑ ምርጫ ለመወዳደር የማይችሉ መሆናቸው ይታወቃል። ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ወር
የእርቅና የውይይት ስብሰባ ለመጥራት ያስተላለፉትን ሀሳብ ተቃዋሚዎች ካቢላ የስልጣናቸውን እድሜ ለማራዘም ያቀዱት
ተንኮል ነው በማለት ውድቅ አድርገውታል።
Ø
በሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ የካሜሩን ወታደሮች በአንድ መንደር ላይ ወረራ አካሂደው አንድ መቶ አምሳ የመንደሩን ነዋሪዎች
መግደላቸውን እንዲሁም ከብቶች መዝረፋቸውንና ቤቶች ማቃጠላቸውን አንድ የመንደሩ ነዋሪ ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። የመንደሩ
ነዋሪዎች አደጋውን በመሸሽ ለስደት የተዳረጉ መሆናቸውም ተገልጿል። የካሜሩን
ባለስልጣኖች ድርጊቱን አልፈጸምንም በማለት ክሱን ያስተባበሉ ቢሆንም ሁኔታው በናይጄሪያ እና በካሜሩን መካከል ውጥረት ሳይፈጥር
አላለፈም ተብሏል። ግድያውና ዘረፋው የተካሄደው ባለፈው ወር ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓም. ሲሆን 643 የሚሆኑ የመንደሩ
ነዋሪዎች አዳማዋ ፉፉሬ ከሚባለው የመጠለያ ጣቢያ የደረሱ መሆናችው ታውቋል። ናይጄሪያ በቻድ ሃይቅ አካባቢ ዘይት ልታወጣ
እንዳቀደች በመግለጽ የናይጄሪያ የነዳጅ ሚኒስትር በቅርቡ ያደረጉት ንግግር በአካባቢው ውጥረት
ለመፈጠሩ ተጨማሪ ምክንያት ነው ተብሏል። ማክሰኞ ዕለት የናይጄሪያ የሰሜን ምስራቅ አውራጃ አስተዳዳሪ የካሜሩን
ባለስልጣኖች ዜጎቻቸውን በድብቅ ወደ ናይጄሪያ ያስገባሉ የሚል ክስ የሰነዘሩ ሲሆን የካሜሩን ባለስልጣኖች ደግሞ ቦኮሃራም ላይ
እርምጃ ለመውሰድ ከናይጄሪያ ጋር የጋራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸው ወታደሮቻቸው
የሰው ልጅ መብት እንዲያከበሩ ስልጠና የተሰጣቸው በመሆኑ
የቀረበባቸውን ክስ አንቀበልም ብለዋል።
ህዳር 28 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በሚቀጥለው ወር እስከ
15 ሚሊዮን ይድርሳል ተብሎ የሚገመተው የረሃብተኛው ወገናችን ቁጥር በአሁኑ ወቅት 10 ሚሊዮን የደረሰ መሆኑን የወያኔ
ባለስልጣኖች አምነዋል። ከጥቂት ጊዜ በፊት በራሳችን መንገድ እንቆጣጠረዋለን ብለው ሲመጻደቁ የነበሩት ባለስልጣኖች ለድርቁ 1.4
ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው እርዳታ መለመን ጀምረዋል። የድርቁ ሁኔታ በጣም እየተስፋፋ ከመሄዱም በላይ በመጠኑም ቢሆን
ሊሻሻል የሚችለው የሚቀጥለው የመከር ወቅት በቂ ዝናም ከተገኘ ብቻ ነው በሚል አዋቂዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።
የረሃብ ሁኔታን በቅድሚያ ለማሳወቅ የተቋቋመውና በአሜሪካ የሚደገፈው (The Famine
Early Warning System Network (FEWS NET),
የሚባለው ተቋም የምስራቅ ኢትዮጵያን አካባቢ የአስቸኳይ ጊዜ ቦታ ብሎ ሰይሞታል። ቀደም
ብሎ የወያኔ አገዛዝ ኢኮኖሚውን በጥምር አሃዝ እያሳደገ ነው፣ ድኽነትንም በግማሽ ቀንሶታል እያሉ ሲያዳንቁት የነበሩት የምዕራብ
ተቋሞች በአሁኑ ወቅት አገራችንን በዓለም አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ከማይገኝባቸው አገሮች መካከል ዋነኛ አድርገው ሲመድቧት
በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ህይወቱን ለማትረፍ በቂ ምግብ የሌለው እንዲሁም ለምግብ እጥረትና ለበሽታ የተጋለጠ ነው
ያላሉ።
Ø
በመካከለኛው አፍሪካ
ሪፐብሊክ በሰላም አስከባሪ ግዳጅ ላይ በነበሩበት ወቅት ህጻናትን አስገደደው ደፍረዋል የተባሉ አራት የፈረንሳይ ወታደሮች በፓሪስ
ለጥያቄ የቀረቡ መሆናቸው ተነገረ። በጠቅላላ የተከሰሱት ወታደሮች ቁጥር አስራ አራት ሲሆን አሁን ለጥያቄ የቀረቡት አራቱ ክሱ
ስለሚመለከታቸው የራሳቸውን ሁኔታ ለማስረዳት ይሁን ወይም
በሌሎች ላይ የምስክርነት ቃል ለመስጠት መሆኑ አልታወቀም።
ከጥር 2006 እስከ ሰኔ 2006 ቀን ተፈጸመ የተባለው ወንጀል ለረጅም ጊዜ ተደብቆ ቆይቶ ዘ ጋርዲያን የተባለው የእንግሊዝ
ጋዜጣ ካጋለጠው በኋላ የፈረንሳይ መንግስት ጥፋተኞችን ለመቅጣት ቃል መግባቱ ይታወሳል። ፈረንሳይና የተባበሩት መንግስታት ጉዳዩን
ደብቀዋል በሚል ከበርካታ ክፍሎች የተሰነዘሩትን ክሶች ማስተባበላቸው ይታወሳል።
Ø
አብዱራሂም ሳንድሂሬ
የተባለው የአልሸባብ ከፍተኛ መሪ እና ሌሎች ሁለት የድርጅቱ አባላት በአሜሪካው የሰው አልባ መንኮራኩር ተመተው የተገደሉ
መሆናቸውን የአሜሪካው የመከላከያ ተቋም ቃል አቀባይ ሰኞ
ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ኡካሽ
በሚል የቅጽል ስም የሚጠራው አብዱራሂም ሳንድሬ የተገደለው ከስድስት ቀን በፊት መሆኑን ገልጸው የግለሰቡ መገደል ለአልሸባብ
ከፍተኛ ክስረት የሚያመጣ መሆኑን ቃል አቀባዩ ጨምረው ተናግረዋል። አልሸባብ በከፍተኛ ደረጃ ተመቷል እየተባለ ቢነገርም አሁንም
ቢሆን በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት እየሰነዘረ ጉዳት ማድረሱን አላቆመም። በቅርቡም በድርጅቱ ውስጥ አይስስ የተባለውን አሸባሪ ድርጅት
በሚደግፉና በሚቃወሙ መካከል ልዩነት ተፈጥሯል የሚል ወሬ እየተወራ ሲሆን በልዩነቱ ምክንያት የተፈጠረውን ግጭት ያመለጠ አንድ
የአልሸባብ አባል በደቡብ ሱማሊያ ባራዊ በሚባለው ቦታ እጁን ለሰላም አስከባሪው ኃይል ሰጥቷል የሚል ዜና ተሰምቷል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት
ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ምክትል ጸሀፊ ሰኞ ህዳር 27 ቀን 2008 ዓም. ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ብሩንዲ ውስጥ
እየተባባሰ የሄደውን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጅምላ ግድያ ለማስቆም በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ የተወሰደው እርምጃ በቂ አለመሆኑን
ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን የሰየሟቸው ልዩ አማካሪ ወደ ብሩንዲ ሄደው በሁለቱ ተጻራሪ
መካከል እርቅ እንዲፈጥሩ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ የሚደገፍ መሆኑን ገልጸው እርምጃው በዚህ ብቻ የሚያበቃ ከሆነ ግን ችግሩ
የሚባባስ እንጅ የማይፈታ መሆኑን አስረድተዋል። የሰብአዊ መብት ምክትል ጸሐፊው
ወደፊት ብሩንዲ ውስጥ ከፍተኛ እልቂት ሊከተል የሚችል መሆኑን በማጤን የአለም አቀፉ ህብረተሰብ ተመጣጣኝ የሆነ
እርምጃ መውሰድ ይገባዋል ብለዋል። እርምጃዎቹ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ አልጠቀሱም።
Ø
በጋና በሙስና
ተበክለዋል የተባሉ 20 ዳኞች ከስልጣናቸው የተወገዱ መሆናቸው ተገለጸ። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ውስጥ አንድ ጋዘጠኛ በድብቅ
የጋና ዳኞች ለሚሰጡት ፍርድ ገንዘብና ዝሙት ሲጠይቁ ያነሳው ፊልም ለሕዝብ መታየቱና በፍርድ ተቋሙ ላይ በርካታ ተቃውሞ ማስነሳቱ
ይታወሳል። ከዚያን ጊዜ ጅመሮ የጋና የፍርድ ተቋም ባደረገው ጥልቅ ምርመራና ከፍተኛ ክትትል በሙስና ተጨማልቀዋል ያላቸውን 20
ዳኞች ከስልጣናቸው ያነሳ መሆኑን ተገልጿል። በሌላ በኩል ሌሎች 12 የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ጉዳይ እየተጣራ መሆኑና ምርመራው
ሲጠናቅቅ ብይን የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል።
Ø
ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በሰሜን
ሸዋ
እንሳሮና
ሚዳሮሞ
በተባሉ
ከተሞች
ውስጥ
የሚኖሩ
የ300
ቀበሌ
ነዋሪዎች
በመጠጥ
ውሃ
እጦት ምክንያት
ለከፍተኛ
ችግር
መጋለጣቸውን
ከስፍራው
የመጣ
ዘገባ
ገልጧል::
የመጠጡ
ውሃ
እጥረት የተከሰተው
ከድርቁ
ጋር
በተያያዘ
ሲሆን ችግሩ ከወራት በፊት የጀመሩ መሆኑን ዘገባው ጨምሮ
አስረድቷል። የከተማው ነዋሪዎች
አዋሳኝ ከሆነው ከደራ
ከተማ
ውሃ
በግዢ
ለመጠቀም የቻሉ ቢሆንም አሁንም ቢሆን ችግሩ ከበድ ያለ መሆኑን ይገልጻሉ።
Ø
በኬኒያና በኢትዮጵያ ወሰን አካባቢ የሚገኘውን የጸጥታ ውጥረት ለመቀነስና በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ የተባበሩት
መንግስታት ድርጅትና አንዳንድ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያቀዱት ፕሮግራም
ሞያሌ ከተማ ውስጥ የወያኔው ጠቅላይ ሚኒስትርና የኬኒያው ፕሬዚዳንት በሚገኙበት
በዛሬው ቀን የተጀመረ መሆኑ ተገለጸ።
በሁለቱ አገሮች ወሰን አካባቢ በሚኖሩ የተለያዩ ጎሳዎች መካከል
በየጊዜው በተከሰቱ ግጭቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸው
ለስደት መዳረጋቸውና በሁለቱ አገሮች ውስጥ ያሉ የጸጥታ ኃይሎች በሚወስዱት የኃይል ርምጃዎች ምክንያት አካባቢው የጸጥታ ውጥረት
ነግሶበት እንደነበር የሚታወቅ ነው።
ባለፈው ወር
የወያኔ ወታደሮች አሸባሪዎችን ለመያዝ በሚል ምክንያት ወሰን ጥሰው ሶስት የኪኒያ የጸጥታ ኃይል አባላትን መግደላቸውን
ተከትሎ ብዛት ያላቸው የኬኒያ ወታደሮች ወደ ወሰን አካባቢዎች እንዲሰማሩ በመደረጉ
የጸጥታው ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ
እንደነበር የሚታወስ ነው። ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ ቦረና አካባቢና
በኬኒያ መርሳቤት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችን እንዲያቀራርብ የታቀደ ሲሆን በንግድ በኢኮኖሚና በጸጥታ የሚኖረውን ግንኙነት ያካትታል
ተብሏል። ፕሮግራሙ በኢትዮጵያና በኪኒያ ባሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወኪሎች በወሰን አካባቢ ባሉ አስተዳደሮችና በሌሎች
ዓልም አቀፍና አካባቢ ድርጅቶች ጠንሳሽነት የተጀመረ ሲሆን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ምክክር የተደረገ መሆኑም ተገልጿል።
Ø
ባለፈው
መስከረም ወር በቡርኪና ፋሶ የተጨናገፈውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ የአገሩቱን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቶማስ
ሳንካራን በማስገደል ተባብረዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑ ታወቀ። የቀደሞ ፕሬዚዳንት በተወሰኑ ወታድሮች በጥይት
መገደላቸው ከሞቱ በኋላ በተደረገው የአስከሬን ምርመራ ሊረጋገጥ የቻለ ቢሆንም በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሞቱና ማን እንደገደላቸው
እስካሁን ሚስጥር ሆኖ ቆይቷል። ፕሬዚዳንት ሳንካራን የተኩት ሚስተር ካሞፒዎሬ የቀደሞ ፕሬዚዳንት የተገደለሉበት ሁኔታ እንዲያጣራ
መርማሪ አካል ቢያቋቁሙም ምርመራው ያላመጣ መሆኑ የሚታወቅ ከመሆኑም
በላይ የፕሬዚዳንት ሳንካራ የቅርብ ጓደኛ የነበሩትና በኋላም
ሚስተር ካምፒዎሬ የጸጥታ ሹም የነበሩት ጄኔራል ዲየንዴሬ በግድያው የሚጠረጠሩ አልነበረም። ሚስተር ካምፒዎሬ ከስልጣን ከተነሱ
በኋላ የተቋቋመው የሽግግር መንግስት ቀድሞውን ፕሬዚዳንት የአሟሟት ሁኔታ
እንዲመረመር አድርጎ በግድያው ተጠርጣሪ አድርጎ በ 10 ሰዎች ላይ ክስ የመሰረተ
ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ጄኔራል ዲየንዴሬ ናቸው ተብሏል።
ጄኔራሉ መፈንቅለ መንግስቱ ከከሸፈ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋላቸውና መንግስት ለመገልበጥ አሲረዋል
በሚል ክስም መወንጀላቸው ታውቋል።
Ø
በሊቢያ ምዕራብ
እና ምስራቅ በየራሳቸው መንግስት የመሰረቱት ተጻራሪ
ክፍሎች የጋራ መንግስት ለማቋቋም ጊዜያዊ ስምምነት ያደረጉ መሆኑ ተገለጸ። በቱኒሲያ ዋና ከተማ በቱኒስ ላይ የሁለቱ ተጻራሪ
ክፍሎች ተወካዮች ያደረጉት ስምምነት በአገሪቱ ውስጥ አንድ አገራዊ መንግስት ለመመስረትና በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ አጠቃላይ
ምርጫ ለማካሄድ መስማማታቸው ተነግሯል። በተደረገው ስምምነት መሰረት እስከ ምርጫው ድረስ የሚያገለግለውን ጠቅላይ ሚኒስቱር
የሚሰይም ከሁለቱም ክፍሎች የተውጣጣ አንድ ኮሚቴ እንዲሁም ህገ
መንግስቱን የሚመረምር ሌላ ኮሚቴ ለማቋቋም ተስማምተዋል። ይህ ስምምነት የተባበሩት መንግስታት በአስተባባሪነት ከሚካሄደው ጥረት
ጋር የተያያዘ ባይሆንም በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ተወካይ ማርቲን ኮብለር ጥሩ ጅምር ነው ብለውታል። በሚቀጥለው ሳምንት
በተመድ አስተባባሪነት የሚደረገው የሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች የድርድር ስብሰባ ሮም ላይ የሚካሄድ መሆኑ ተነግሯል።
በተያያዘ ዜና
ከስልጣናቸው በህዝባዊ እንቅስቃሴና በምዕራብ አገሮች ጣልቃ
ገብነት ከስልጣናቸው የተወገዱት የሞአመር ጋዳፊ ልጅ ትናንት እሁድ ህዳር 26 ቀን 2008 ዓም ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት
መቅረባቸው ታውቋል። ሳዲ ገዳፊ የተባሉት የ42 ዓመት ጎልማሳ የተከተሰሱባቸው ክሶች በ1998 ዓ.ም. አንድ የእግር ኳስ
አሰልጣኝ አስገድለዋል የሚል እና አባታቸው ከስልጣን በተነሱ ጊዜ በርካታ ዜጎችን በማስገደል የሽብር ተግባር ፈጸመዋል የሚል
ነው።
Ø
በቻድ ሃይቅ
ላይ በምትገኝ አንድ ደሴት ውስጥ ሶስት አጥፍቶ ጠፊ ሴቶች በሰነዘሩት ጥቃት 27 ሰዎች መገደላቸውንና ከ80 በላይ መቁሰላቸውን
የቻድ የጸጥታ ኃላፊዎች ገልጸዋል። ቦምቦቹ የፈነዱት በገበያ ቦታ በመሆኑ ከሞቱት ውስጥ በርካታዎቹ ገበያተኞች መሆናቸው
ይታወቃል። ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ኃይል ባይኖርም የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ለመሆናቸው ከፍተኛ ግምት አለ። ቻድ ቦኮ ሃራም
የሚባለው አሸባሪ ድርጅትን ለማጥፋት በተቋቋመው የጋራ ኃይል ውስጥ ተሰታፊ መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን በዚህም ምክንያት ከቡድኑ
ተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰባት መሆኑ ይታወቃል።
Ø
የከባቢ አየር
ብክለትን ለመቋቋም በፓሪስ ከተማ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ደኖችን ለመንከባከብና ለመጠበቅ እንዲሁም
የተመናመኑትንም ወደ ነበሩበት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት የሚያደርጉ መሆናቸውን በመግለጽ ቃል የገቡ መሆናቸው ተነገረ። እስካሁን
ባለው የዓለም እድሜ
ከግማሽ በላይ የሚሆነው ደን የጠፋ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን
የትሮፒካል ጫካዎች መመንመን ከባቢው አየር የካርቦንን ብክለው
እንዳይቋቋም በማድረግ በኩል ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል ተብሏል። በመጭው
2023 ዓም. 100 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነውን ምድረበዳ መሬት መልሶ በደን ለመሸፈን የአፍሪካ አገሮች ቃል የሰጡ መሆናቸው
ታውቋል። የከባቢ አየርን በመበከል በኩል የአፍሪካ አገሮች ተጠያቂ ባይሆኑም ይህንን ግዙፍ ስራ ለመሸከም ግን ዝግጁ ነን
ብለዋል።
ህዳር 25 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
አዲስ
አበባ
ከሚገኘው
የፌዴራል
ፖሊስ
የጸጥታና
ፍትህ
ማስከበር
ዳይሬክቶሬት
በተገኘው
መረጃ መሰረት ተጨማሪ የሆኑ የፌዴራል ፖሊስ
ልዩ
ኃይል አባላት
ተማሪዎች
አመጽ
ወዳነሱባቸው
የተለያዩ
አካባቢዎች
ባስቸኳይ እንዲሄዱ
መታዘዛቸው
ታወቋል። በትዕዛዙ መስረት
በዛሬ
ዕለት
ኅዳር 25
ቀን 2ዓ005
/ም
ከሰዓት
በኋላ
ቁጥራቸው በውል
ያልታወቀ የልዩ
ሃይል
አባላት
ወደ
ቦረና፤
ወለጋ
እና
ባሌ
አካባቢዎች
የተሰማሩ
ሲሆን
ሌላ
የፌዴራል
ደኅንነት
ቡድን
ደግሞ
ነገ
እሁድ
ኅዳር 26
ቀን
ወደ
ጎንደር
እንዲሰማራ
መመሪያ
የተሰጠው
መሆኑን
ለመገንዘብ ተችሏል። በተለያዩ ከተሞች የኦሮሞ ተማሪዎች እያካሄዱት ያሉት የተቃውሞ እንቅስቃሴ አሁንም ያልበረደ ሲሆን በዛሬው
ዕለትም በምስራቅ ሀረርጌ በድሬደዋ በደምቢ ዶሎና በአዲስ አበባ አዋሳኝ ቦታዎች ተቃውሞዎች ቀጥለው መዋላቸው ታውቋል። የተቃውሞ
እንቅስቃሴ ከተደረገባቸው አካባቢዎች ተማሪዎች ከየቤታቸው እየተለቀሙ የሚታሰሩ
በእስር ላይ የሚገኙትም ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው መሆኑን ከየቦታው የሚደርሱ ዘገባዎች ይገልጻሉ። ሂውማን
ራይትስ ዎች የተባለውና መቀመጫው አሜሪካ የሆነው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት በዛሬው ዕለት የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በኦሮሞ
ተማሪዎች እያካሄዱ ያሉትን ጭፍጨፋ በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል።
በተያያዘ ዜና
በአዲስ አበባም ተማሪዎች አመጽ ሊያስነሱ ይችላሉ ከሚል ፍራቻ ፖሊሶችና የጸጥታ ኃይሎች ጥበቃውና ክትትሉ እንዲቀጥል መመሪያ
የተሰጣቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
Ø
በአገራችን
የገባው ከፍተኛ ድርቅና ረሃብ በህጻናትና በደካሞች ላይ ከፍተኛ የጤና መታወክ ሊያስከትል የሚችል በመሆኑ ይህንን ለመቆጣጠር
የተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጤና ተቋም (WHO) አንድ የጤና ቡድን ወደ ኢትዮጵያ የላከ መሆኑን አስታወቀ። አንድ የድርጅቱ
ባለስልጣን ባሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ የሚገኘው የተረጅው ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅሰው ከዚህ በፊት ተስፋፍተው ከሚገኙ
በሽታዎች በተጨማሪ በምግብ እጥረት ምክንያት በተለያዩ በሽታዎች በከፍተኛ ደረጃ የተጠቁ ዜጎች መኖራቸውን አስረድተዋል። ካለፈው
ዓመት ጥር ወር ጀምሮ በየወሩ በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ ህጻናት ቁጥር እየጨመረ የሄደ ከመሆኑም በላይ በያዝነው ዓመት መጨረሻ
ላይ በአገሪቷ ውስጥ ወደ 400 ሺ የሚደርሱ ህጻናትና ወደ 700 ሺ የሚደርሱ እናቶች በምግብ እጥረቱ ሊጠቁ የሚችሉ መሆናቸው
ተገምቷል። ኤል ኒኖ ባመጣው ድርቅ የተጠቁ አካባቢዎች እንደወባ፤ የተቅማጥ በሽታ፤ ኮሌራና የመሳሰሉት በሽታዎች ተስፋፍተው
በዜጎች ጠና ላይ ከፍተኛ ችግር ሊያመጡ ይችላሉ ከሚል ግምት ድርጅቱ መድሃኒቶችን፤ የህክምና መሳሪያዎችንና ባለሙያዎችን ወደ
ቦታዎቹ እያንቀሳቀሰ መሆኑ እኝሁ የድርጅቱ ተናግረዋል። ድርቁ
የሚያስከትለው የጤና መዛባትን ለመከላከል በተጨማሪ ወደ 8 ሚሊዮን ዶላር የሚያስፈልግ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።
Ø
ትናንት አርብ
ህዳር 24 ቀን 2008 ዓም.በናይጄሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ በሚገኘው የቦርኖ ግዛት ውስጥ አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ ቢያንስ
ሶስት ሰዎች መገደላቸውና ሌሎች ስድስት ሰዎች መቁሰላቸው ታወቀ። ሁለት ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉትና አራቱ የቆሰሉት ሳቦን ጋሪ
በተባለቸው መንደር መግቢያ ላይ ባለ የፍተሻ ቦታ ላይ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ ሲሆን አንደኛው አጥፎት ጠፊ ኪምባ
በተባለው መንደር ያፈነዳው ቦምብ አንድ ሰው ለመግደልና ሁለት ሰዎችን ለማቁሰል ችሏል። ጥቃቱን ያደረሱት አጥፍቶ ጠፊዎች
የቦኮሃራም አባላት እንደሆኑ ይታወቃል።
Ø
በምእራብ
አፍሪካ ሪፐብሊክ የእስልምና ሃይማኖትን የሚከተሉና ራሳቸውን የቀድሞ ሰለካ አማጽያን ብለው የሚጠሩ ግለስቦች ሀሙስ ህዳር 23
ቀን 2008 ዓ.ም ምሽቱ ላይ በአንድ የመጠልያ ጣቢያ ላይ ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች መግደላቸውንና ከሞቱት ውስጥ አምስቱ
የአማጽያኑ አባላት መሆናቸውን አንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ቃል አቀባይ አስታወቀ። ከሰላማዊ
ሰዎች በኩል በርካታ ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን ሁለት ከአማጽያኑ በኩል
እንደቆሰሉም ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ሀሙስ ዕለት የክርቲያን አማጽያን የሆኑ የሌላ ቡድን አባላት ደግሞ ባንጉዊ ከተባለው
የአገሪቷ ዋና ከተማ ተነስቶ ባምባሪ ወደ ተባለ ከተማ
ይጓዝ የነበረውን የጭነት መኪናዎች ኮንቮይ በማጥቃት ከመኪናዎቹ ንብረቶችን የዘረፉ መሆናቸው ታውቋል። የተመድ ሰላም አስከባሪ
ኃይል አባላት ባስቸኳይ በቦታው ደርሰው አማጽያኑን ያባረሩ ከመሆኑ ባሻገር የአጥቂውን ቡድን መሪ በቁጥጥር ስር ያደረጉት መሆኑን
ገልጸዋል። በሚቀጥለው ታህሳስ 3 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሪቱ ረቂቅ ህገ መንግስት ላይ ህዝቡ ድምጽ እንዲሰጥበት የሚደረገ ሲሆን
በታህሳስ 17 ቀን 2008 ዓም
ደግሞ ጠቅላላ ምርጫ እንዲካሄድ ታቅዷል። በቅርቡ የሮማው ጳጳስ በአገሪቱ አጭር ጉብኝት በማድረግ እርቅ እንዲፈጠር መልእክት
ያስተላለፉ ቢሆንም የእርስ በርስ ግጭቱ ያልቀነሰ መሆኑ ይነገራል።፡
Ø
ከሊቢያ የሚመጡ
የህዝብ ማመለላሻ አውሮፕላኖች በቱኒሲያ ዋና ከተማ በቱኒስ በሚገኘው የቱኒዚያ ካርቴጅ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንዳያርፉ
የተከለከሉ መሆናቸውን የአገሪቱ የመገናኛ ሚኒስትር ገለጹ።
ሚኒስትሩ የሊቢያ አውሮፕላኖች ማረፍ የሚፈቀድላቸው ከከተማዋ 270 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ስፋክስ በሚባለው
አውሮፕላን ማረፊያ ብቻ መሆኑን ገልጸው ይህ ርምጃ የተወሰደው የአገሪቷን የጸጥታ ሁኔታ ለማጠናከር ነው ብለዋል። የቱኒዚያ አየር
መንገድ ባለፈው ነሐሴ ወር ወደሊቢያ የሚያደርገውን በረራ ያቋረጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን
ከአንድ ወር በፊትም ቱኒዚያ ከሊቢያ ጋር ያለውን ወሰን የዘጋች
መሆኑም አይዘንጋም። በተያያዘ ዜናም በትናንትናው ዕለት በዋና ከተማዋ እምብርት በሚባለው የሃቢብ ቡርጊባ ጎዳና ላይ ቦምብ
ሊያፈነዱ አስበዋል የተባሉ ሁለት ተጥርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የተደረጉ መሆናቸው ታውቋል።
ህዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በተለያዩ
ዩኒቨርስቲዎች
የሚማሩ
ተማሪዎች
እያድረጉ ያሉት የተቃውሞ
እንቅስቃሴ ተጠናክሮ
መቀጠሉን
ከየቦታው የሚመጡ መረጃዎች
ይገልጻሉ።
ሰሞኑን በሀሮማያ፤
በአምቦ፤
በመደወላቡ
ዩኒቨርስቲዎች በተካሄዱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የተወሰኑ ተማሪዎች በወያኔ ፖሊሶች ከመገደላቸውም በላይ በርካታ
ተማሪዎች በፖሊሶች የተደበደቡ መሆናቸውና መታሰራቸው ይታወቃል። በሃሮሚያ በፖሊስ ታፍነው ወደ አልታወቀ ቦታ የተወሰዱት ተማሪዎች
ቁጥር ከአምሳ በላይ ሲሆን በወደላቡ ከመቶ በላይ ተማሪዎች ተወስደው ታስረዋል። አሁንም ቢሆን በእነዚህ ዩኒቨርስቲዎች አካባቢ
ውጥረቱ ያልበረደ ሲሆን ሌላ ዙር እንቅስቃሴ ይደረጋል ብሎ በመፍራት ወያኔ የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ደረጃ አሰማርቶ ይገኛል።
ሰሞኑን በባህታ እስር ቤት ላይ ከደረሰው የእሳት አደጋ ጋር ተያይዞ ወያኔ ያካሄደውን ግድያና ጭፍጨፋ በመቃወም የጎንደር
ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባደረጉበት ወቅት ፖሊስ ወደ ግቢው በመግባት በርካታ ተማሪዎችን የደበደበ መሆኑና
በርካታዎችንም አስሮ መውሰዱን ከአካባቢው የደረሰን ዜና ይገልጻል።
Ø
በጎንደር ከተማ በባህታው የእስር ቤት ቃጠሎ
ወቅት ከፖሊስ ግድያ የተረፉትና ማምለጥ ያልቻሉት እስረኞች ከተማው ውጭ በአንገረብ ወንዝ ግድ አቅራቢያ ወደ አለው አዲስ እስር
ቤት መዛወራቸው የሚታወስ ሲሆን ለተከታታይ ቀናት ያለምግብና ያለውሃ እንዲቀመጡ የተደረጉትና ከዘመድ ጥየቃ የታገዱት እስረኞች
ያካሄዱትን አመጽ ለማቆም የወያኔ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ የተወሰኑ እስረኞች መገደላቸውና በርካታዎችም መቁሰላቸው
ታውቋል። ያመለጡም እስረኞች እንዳሉ ይነገራል። ከተወሰነ ጊዜ በኋላም እስር ቤት በእሳት የተቃጠለ መሆኑን አንዳንድ የአይን
እማኞች ይናገራሉ። በጎንደር ከተማ የወያኔ ወታደሮች
በብዛት ተሰማርተው የቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ሕዝቡን እያመሱት ሲሆን በበርካታ አካባቢዎችም የጥይት ድምጽ እየተሰማ መሆኑ
ይነገራል።
Ø
ሰሞኑን በጎንደርና በአንዳንድ የአሮሞ ክልል ከተሞች እየተደረገ ያለው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በሌሎች ቦታዎችም
እየተዛመተ መሆኑ እየተነገረ ነው። በባህር ዳር በአንዳንድ ቦታዎች የወያኔ አገዛዝ ይወገዱ የሚል መልክትን ያዘሉ በራሪ ወረቀቶች
ተብትነው ማደራቸውና በከተማው ውስጥ ውጥረት መኖሩን የሚጠቁሙ ዘገባዎች እየደረሱ ይገኛሉ።
Ø
በግብጽ ካይሮ ከተማ በአንድ ሬስቶራንት ውስጥ ሞልቶቭ ኮክቴል የተባለው የእሳት ቦምብ ተወርውሮ በደረሰው የእሳት
ቃጠሎ 16 ሰዎች መሞታቸውና በርካታ መቁሰላቸው ከዜና ምንጮች የተገኘው መረጃ ይገልጻል። ስዎቹ የሞቱት በእሳቱ ቃጠሎና በጭስ
በመታፈናቸው ሲሆን የሬስቶራንቱ ልዩ ልዩ ክፍሎችም በተነሳው እሳት ጋይተዋል። እሳቱን ያነሳሱት ሶስት ፊታቸውን በማስክ የሸፈኑ
ሰዎች መሆናቸው ከአካባቢው የሚደርሰው ዜና የሚገልጽ ሲሆን ሰዎቹ የእሳቱን ቦምብ ከጣሉ በኋላ ማምለጣቸውም ተገልጿል።
የእስላማውያን አማጺዎች ከዚህ በፊት በካይሮና በሌሎች ቦታዎች ተመሳሳይ ጥቃት መፈጸማቸው የሚታወቅ ሲሆን ሬስቶራንቱን ያቃጠሉት
የዚሁ የአማጽያን ቡድን አባላት ይሆናሉ የሚል ግምት ተሰጥቷል።
Ø
ከሊቢያ ወደ አውሮፓ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩትን ሁለት ሺ የሚሆኑ ስደተኞች አስራ አንድ ተከታታይ የነፍስ ማዳን
እንቅስቃሴዎች በማድረግ ከመስጠም ያዳኗቸው መሆኑን የኢጣሊያ ጠረፍ ጠባቂዎች ሐሙስ ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።
የጣሊያን ጠረፍ ጥበቃ፤ የባህር ኃይል፤ የድንበር የለሽ ሀኪሞች
መርከቦችና እንዲሁም ሁለት የአውሮፓ ህብረት መርከቦች የተሳተፉበት ይህ የነፍስ ማዳን ተግባር የተጀመረው
ስደተኞቹ በመስጠም አፋፍ ላይ መሆኖቸውን የሚገልጽ የስልክ መልክት ከደረሳቸው በኋላ መሆኑንና በወሰዱት ተከታታይ
እርምጃዎች ስደተኞችን ከስምንት ትናንሽ የላስቲካ ጀልባዎች አውጥቶ ወደ ትላልቅ መርከቦች ማዛወር የተቻለ መሆኑን ገልጸዋል።
Ø
አንድ ለመንግስት ሚዲያ ትሰራ የነበረች
የሱማሊያ ጋዜጠኛ በዛሬው ዕለት በመኪናዋ ውስጥ በተቀበረ ፈንጅ የሞተች መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል። ሂንዳ ሃጂ
መሀመድ የተባለችው ጋዜጠኛ ለመንግስት የዜና ማሰራጫ ተቋም በፕሮግራም አቅራቢነትና በዘጋቢነት ስትስራ የቆየች ሲሆን ባለቤቷም
ከሶስት ዓመት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ ሞጋዲሾ ውስጥ መገደሉ ይታወቃል። ጋዜጠኛዋ በፈንጅው የተመታችው በመኪናዋ መቀመጫ ስር
የተቀበረው ፈንጅ ከርቀት መቆጣጠሪያ በፈነዳበት ጊዜ ሲሆን ወዲያውኑ ወደ
ሆስፒታል ተወስዳ በህክምና ርዳታ ሊደረግላት ቢሞከርም ከተወስነ ጊዜ በኋላ መሞቷ ተገልጿል። ባለፉት አምስት ዓመታት
ብቻ በሱማሊያ ከሃያ አምስት ጋዜጠኞች በላይ በአልሸባብ ታጣቂዎች የተገደሉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ጥቃቱን የፈጸመው ይኽው ቡድን
እንደሆነ ይገመታል።
Ø
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ መወዳደር እንዲችሉ ህገ መንግስቱን ለማሻሻል የሩዋንዳ ምክር ቤት
የወሰነው ውሳኔ የዴሞክራሲ መርህን ይጎዳል በማለት
የአውሮፓው ህብረት ተቃውሞ ያሰማ መሆኑ ታወቀ። የሩዋንዳ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባሳለፈው ውሳኔ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት
የስልጣን ዘመን ከሰባት ወደ አምስት አመት ዝቅ እንዲልና አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት የስልጣን ዘመን በላይ እንዳይወዳደር
ቢደነግግም ህጉ ተግባራዊ የሚሆነው የአሁኑ ፕሬዚዳንት ካጋሜ ከሁለት ዓመት በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ተወዳድረው የስልጣን ዘመናቸውን
ከጨረሹ በኋላ ነው የሚል ውሳኔ አስተላልፏል። ምክር ቤቱ ያደረገው የህገ መንግስት ማሻሻያ ለውሳኔ ህዝብ ይቀርባል የተባለ
ቢሆንም ሕዝቡ ያጸድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል። የአውሮፓው ህብረት አንድን ግለስብ ለመጥቀም ሲባል በዚህ መንገድ የተደረገ
የህገ መንግስት ማሻሻያ ህጋዊነትን ካለመላበሱ በላይ ተቀባይነት አይኖረውም በማለት የሩዋንዳው ምክር ቤት
ያስተላለፈውን ውሳኔ አውግዟል። ባለፈው ማክሰኞ በተባበሩት መንግስታት የአሜሪካው
አምባሳደር ካጋሜ ለአፍሪካ ምሳሌ መሆን ያለባቸው በመሆኑ በኋላ
ከሁለት ዓመት በኋላ በህጉ መሰረት ከስልጣናቸው መውረድ
ይገባቸዋል የሚል ንግግር አሰምተዋል። ካጋሚ የሩዋንዳው እልቂት ከተጠናቀቀበት ከ1987 ዓም ጀመሮ ለ21 ዓመታት በስልጣን ላይ
የቆዩ ሲሆን በ 1986 እና በ 2003 ዓም በተደረጉ ምርጫዎች አሸናፊ ሆነው ስልጣን በመያዛቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ጊዜ
በላይ መወዳደር አይቻልም በሚለው የአገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት
ከሁለት ዓመት በኋላ ተሰናባች ነበሩ።
Ø
በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካና በቻይና መሪዎች መካከል በተካሄደው ስብሰባ ላይ ቻይና ለአፍሪካ 60 ቢሊዮን ዶላር
የሚገመት ርዳታና ብድር ለመስጠት ቃል መግባቷ ታወቀ። የሚሰጠው ብድር በአብዛኛው በልማት ስራዎች ላይ የሚውል ሲሆን ለተማሪዎች
የነጻ እድል ትምህርት መስጠትና ስራተኞችን የማሰልጠን ተግባርን ይጨምራል ተብሏል። ስብሰባውን የመሩት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት
ዙማ ቻይና ትልቋ የአፍሪካ የንግድ ሸሪክ መሆኗን ገልጸው ከአፍሪካ ከፍተኛ መጠን ያለው ጥሬ ዕቃ የምትገዛ መሆኗንና በአፍሪካ
ውስጥ ከፍተኛ ግምት ያለው መዋእለ ንዋይ በማፍሰስ ላይ የምትገኝ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን እንደታየው ቻይና በአፍሪካ አገሮች
የምታደርገው የንግድና የመውዕለ ንዋይ እንቅስቃሴ ቻይናና በስልጣን ላይ ያሉትን ጥቂት ግለሰቦችን እንጅ ሰፊውን ሕዝብ ሲጠቅም
አልታየም የሚሉ በርካታ ናቸው።
ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአባይ ላይ የሚሰራው ግድብ
መሰረታዊ ስራ ከተቋረጠ
ስድስት
ያለፈው መሆኑን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል
።
የወያኔ
ባለስልጣኖች
ስራው አለምንም እክል ይጠናቀቃል
እያሉ በየጊዜው የሚያሰሙት ጩኸት ውሸት ከመሆኑ ሌላ ለስራው መደናቀፍ ዋና ምክንያት ነው ተብሎ የሚከሰሰው ግለሰብ
ሜቲክ
በሚል ስም የሚጠራውን የወያኔ ድርጅት በአዛዥት የሚመራውና በጉቦኛነቱ
ወደር የለውም የሚባለው ጄኔራል ክንፈ
የተባለው ግለስበ
መሆኑን
ለማወቅ ተችሏል።
ግዙፍ ነው
ተብሎ ለሚነገርለት
ግድብ አስፈላጊውን
ቱቦዎችንና ሌሎች
ቁሳቁሶሽን
ሜቲክ ሊያቀርብ ይችላል በማለት የግንባታ ስራው እንዲቆም ካስደረገ ስድስት ወር ያለፈው መሆኑን ያጋለጡ ክፍሎች
በመጪው ዓመት
ስራው ይጠናቀቃል የተባለው ቢያንስ ለሁለት ዓመት ሊዘገይ የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።
የስራው መዘግየት የግድቡን ስራ ወጭ በስምንት ሚሊዮን ዶላር
እንዲጨምር የሚያደርግ ሲሆን ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ ለመክፈል በቦንድ ሽያጭ በመዋጮ መልክ ሕዝብ ላይ የሚጫን መሆኑ መሆኑ ግልጽ
ነው።
የወያኔው ጄኔራል ክንፈ ዙሪያውን
በችሎታ አልባ
የወያኔ
አባላት ተከቦ የሚገኝ ሲሆን
እጁን በሁሉም የግንባታ ዕቅዶች
ለማስገባት የሚያደርገው ሩጫ ባጠቃላይ የአገሪቷን
የግንብታ ስራ
እየጎዳ ነው ሲሉ
አንዳንድ
የወያኔ ባለስልጣኖች
ቅሬታ
ማሰማት
ጀምረዋል ። ክንፈ ከቻይናዎች ጋር በጉቦና
በጥቅም
ተሳስሮ ያለ አጥፊ
የወያኔ
ነው የሚሉ በርካታ ናቸው።
የፈረንሳይ ኩባንያዎችና
እንዲሁም ሌሎች በርካታ ድርጅቶች
ሜቴክ
የተባለው ድርጅት ያከሰራቸውና የጎዳቸው መሆኑን በመግለጽ
ክንፈን እየወነጀሉ ነው
ተብሏል ።
Ø
በተያያዘ ዜና በአባይ ግድብ ላይ የግብጽ የወያኔና የሱዳን ተወካዮች እያካሄዱት ያለው ስብሰባ መቋረጡ ከዚህ በፊት የተገለጸ
ሲሆን ስብሰባው እንደገና እንዲጀመር ከሱዳኑ አቻቸው ጋር እየመከሩ መሆኑን የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬው ህዳር 23 ቀን
2008 ዓ.ም፣ካይሮ ውስጥ አስታውቀዋል። ሱዳን ስብሰባው በሚቀጥለው ሳምንት እንዲደረግ ሀሳብ ያቀረበች ሲሆን ግብጽ በሀሳቡ
መስማማቷን ገልጻለች። በአሁኑ ወቅት ግብጽ የሚገኘው የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትርም በጉዳዩ ላይ ከግብጽ ባለስልጣኖች ጋር ይነጋገራል
ተብሏል።
Ø
ኅዳር 22
ቀን
2008
ዓ/ም
ከሰዓት
በኋላ
በጫንጮ
አንደኛ
ደረጃ
ትምህርት
ቤት የሚማሩ ወደ ሁለት መቶ የሚደርሱ ተማሪዎች
ምንነቱ
ባልታወቀ
ህመም
ተጠቅተው
በመማሪያ
ክፍላቸው
በድንገት
የወደቁ መሆናቸውና
ትንፋሽ
ሲያጥራቸው
ወደ
ጳውሎስ
ሆስፒታል
ተወስደው
ህክምና
የተደረገላችው መሆኑ ታውቋል። ተማሪዎች ከታከሙ በኋላ ወደ ቤታቸው የተመለሱ ቢሆንም
በዛሬው ዕለት
ኅዳር
23
ቀን 2008
ዓ/ም
በተመሳሳይ መልክ በህመሙ
ተጠቅተው በድጋሚ
ወደ
ሆስፒታሉ
የተወሰዱ መሆናቸውን
ለማረጋገጥ
ተችሏል።
ይህ
ምንነቱና
መነሻው ያልታወቀ በሽታ
የህክምና
ባለሙያዎች
ግራ
ያጋባ ሲሆን
በህመሙ የተጠቁት ወጣቶች
የትንፋሽ
እጥረትና
የልብ
ምት
መፋጠን ታይቶባቸዋል።
Ø
በጎንደር
ወህኒ
ቤት
ከተነሳው
የእሳት
ቃጠሎ
አደጋ
ነብሳቸውን
ለማዳን
ሲወጡ
የነበሩ
እስረኞች
ላይ
ፖሊስ በወሰደው
ጥቃት
የተገደሉት
ቁጥር
ከሰላሳ
በላይ
መሆኑን
ምንጮች እየገለጹ ይገኛሉ።
ኅዳር 21
ቀን
2008
ዓ/ም
ለሊት
በወህኒ
ቤቱ
የደረሰውን
ድንገተኛ
የእሳት
ቃጠሎ
በመከላከልና
በማጥፋት
ፈንታ
በእስረኞቹ
ላይ
የጥይት
እሩምታ
የከፈተው
ፖሊስ
ከእስረኞቹ
በተጨማሪ
በአካባቢው
ለእርዳታ
ሲጯጯሁ
የነበሩ
ንጹኃን
ዜጎችን
በጥይት የገደለ መሆኑ ታውቋል።
ከፖሊስ
ጥይት
ተርፈው
በዱላ
እጅና እግራቸው ከተሰበረው
በተጨማሪ
በእሳቱ የመለብለብ
አደጋ
የደረሰባቸው
በርካታ ዜጎች
በጎንደር
ሪፈራል
ሆስፒታል
ውስጥ
ተኝተው
ህክምና
እየተደረገላቸው መሆኑን ከአካባቢው የመጣው ዘገባ
የሚያመለክት ሲሆን ሆስፒታሉ ብዛት ባላቸው ፖሊሶች እየተጠበቀ መሆኑ ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት ከሞቱት ውስጥ የአንዳንዶቹ የቀብር ስነስርዓት ተፈጽሟል።
Ø
ትናንት ህዳር 22 ቀን በዩናይትድ ስቴትስ ካሊፎርኒያ ግዛት
ሳንበርናርዲኖ በተባለ ከተማ በአንድ የድኩማን መገልገያ ማዕከል ውስጥ ሶስት ሰዎች ተኩስ ከፍተው አስራ አራት ሰዎች
መግደላቸውንና 17 ሰዎች ማቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ
ዜና ይገልጻል። ግድያውን ፈጽመዋል ተብለው ከሚጠርጠሩ መካከል ሁለት ወታደራዊ ዩንፎርም የለበሱ ሰዎች በአንድ ኤስ ዩ ቪ መኪና
ሲያመልጡ የተገደሉ ሲሆን በመኪናቸውም
ውስጥ አውቶማቲክና ግማሽ አውቶማቲክ የሆኑ መሳሪያዎች ተገኝተዋል። የተገደሉት ሰዎች ባልና ሚስት መሆናቸው የተረጋገጠ
ሲሆን ስማቸው ሰይፍ ሪዝዋን ፋሩክ እና ታሽፊን ማሊክ እንደሚባሉ ተነግሯል።
ሶስተኛው ተጠርጣሪ ማንነቱ ባይገለጽም በቁጥጥር ስር
ውሏል ተብሏል። ስለግድያው ምርመራ በማካሄድ ላይ የሚገኙት
የፖሊስና የጸጥታ አባላት እስካሁን በተደረገው ምርመራ የግድያውን ትክክለኛ ምክንያት ማወቅ ያልተቻለ መሆኑን ገልጸው
የሽብር ተግባር ሳይሆን አቀርም የሚል ጥርጣሬ ያላቸውም መሆኑን
ጠቁመዋል። ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በኮሎራዶ ግዛት አንድ ግለሰብ ፕላንድ
ፓርንት ሁድ በሚባል የሚታወቀውና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ለሴቶች የጤና
በሚሰጠው ተቋም ውስጥ አንድ ግለስብ ባካሄደው ግድያ ሶስት ሰዎች
መሞታቸውና ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸው ሲታወቅ በአሜሪካ በትናንቱ
ዕለት የተገደሉት ሰዎች ብዛት በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው ነው ተብሏል። ከጥቂት ሳምንት በፊት ፓሪስ ላይ የአይሲስ
አሸባሪዎች ያካሄዱት ጥቃት በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥም ይካሄዳል የሚል ፍራቻ በብዙዎች ዘንድ ያለ መሆኑም ይታወቃል።
Ø
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩብዕ ሐሙስ ህዳር 23 ቀን 2008
ዓ.ም ለሩሲያ ህግ አውጭዎች ባደረጉት ንግግር ቱርክ የሩሲያ
አውሮፕላን መትታ በመጣል ለፈጸመችው አስከፊ
ተግባር ሩሲያ የአጸፋ ርምጃ አጠናክራ እንደምትወስድ አስታውቀው
ወደፊት በወሰደችው ርምጃ እንደምትጸጸት ተናግረዋል። ለሩሲያ ሕዝብ በቀጥታ በራዲዮና በቴለቪዥን በተላለፈው ንግግራቸው ፑቲን
ሩሲያ በቱርክ ላይ የምታደርገው የአጸፋ መልስ በንግድ ማዕቀብ ላይ ብቻ የሚወሰን አለመሆኑን
ገልጸዋል። አክለውም በኃላፊነቱ የሚጠየቀው የቱርክ አመራር እንጅ
የቱርክ ሕዝብ እንዳልሆነ ገልጸው የቱርክ አመራር ከአሸባሪው ከአይሲስ ቡድን ጋር ጥብቅ ግንኙነት ስላለው አይሲስን እየረዳ ነው
ብለዋል። ሩሲያ
ከአንድ ሺ ዓመት በላይ የቆየ፤ ወታደራዊ ጥንካሬ ያላትና በራሷ
የምትተማመን ኩሩ አገር መሆኗንም አስገንዝበዋል። የቱርክ ባለስልጣኖች የሩሲያ አውሮፕላን በቱርክ የአየር ክልል መመታቱን በድጋሚ
አስታውቀው ከአይሲስ ጋር የንግድ ግንኙነት አለ የተባለውን ክስ ክደዋል።
Ø
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት
የደቡብ ሱዳን አምባሳደር በመሆን የተሰየሙት በአገራቸው በተመድ
ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሰፈሩት 180 ሺ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ የቤታቸው እንዲሄዱ መደረግ አለባቸው በማለት ጥያቄ
ያቀረቡ መሆኑ ታወቀ። አምባሳደሩ በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ
እየተካሄዱ ያሉ ወንጀሎችና ግድያዎች እንዲሁም በሰፋሪው ላይ የሚታየው አሳዛኝ የኑሮ ሁኔታ ያሳሰባቸው መሆኑን ጠቅሰው የተኩስ
አቁም ስምምነቱ በስራ ላይ እየዋለ በመሆኑ ሰፋሪዎቹ ወደ የቤታቸው እንዲሂዱ ማበረታትና መግፋት ያስፈልጋል ብለዋል። በደቡብ
ሰዳን የሚገኘውን የተመድ የሰላም ኃይል ይዞታን ለማጠናከር 500 ተጫማሪ ወታደሮች 600 ተጨማሪ ፖሊሶች ተጨማሪ ሄሊኮፕተሮችና
ድሮኖች እንዲሚደቡ የተመድ ዋና ጸሐፊ የጸጥታውን ምክር ቤት መጠየቃቸው ተገልጿል።
ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም.
Ø
ከአንድ ዓመት ከስምንት ወር በፊት በደቡብ
ሱዳን ዋና ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ ተይዘውና በወያኔ ቁጥጥር ስር ተደረገው እስካሁን በእስር ላይ የሚገኙት የቀደሞ የወያኔ
የጋምቤላ ክልል አስተዳዳሪ አቶ ኦኬሎ አኳይ ኦቻላ በሽብር ወንጀል ተከሰው ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታውቋል። አቶ ኦኬሎ አኳይ
ኦቻላ በተያዙ ጊዜ በሽብረተኛነት መከሰሳቸው የሚታወቅ ከክሶቹም ውስጥ ከፊሎቹ “የክልሉን ሕዝብ ለአመጽ ካነሳሱ በኋላ
ኃላፊነታቸውን ጥለው ከአገር በመውጣት በአሸባሪ ድርጅት ውስጥ ተሳትፈዋል”፤ በጸረ ሽብር ኃይሎች መገናኚያ ብዙሃን አማካይነት
የክልሉን ህዝብ ለአመጽ አነሳስተዋል የሚሉት ነበሩ። አቶ ኦኬሎ ለፍርዱ ቤቱ በሰጡት ቃል በክልሉ ከአስር ዓመት በፊት ለደረሰው
የዜጎች ግድያና ጭፍጨፋ በዋናነት ተጠያቂ የሚሆኑት መለሰ ዜናዊ፤ አዲሱ ለገሰና በረከት ስምኦን መሆናቸውን ገልጸው እነሱ
በፈጸሙት ወንጀል እሳቸው ተጠያቂ መሆን የሌለባቸው መሆኑን በመግለጽ ተከራክረዋል።፡ የቀድሞ የፌዴራል ጉዳዮች ሹም የነበረው
ዶክተር ገብረአብ ባርናባስም ግድያውን በማስፈጸም በኩል ቀዳሚ ሚና እንደተጫወተም አጋልጠውል።
በወቅቱ በወያኔ ወታደሮች የተገደሉት ዜጎች ቁጥር ከ400 በላይ ሆኖ ሳለ 60 ብቻ ነው የሞተው ብለህ ተናገር
ተብለው በወያኔ ባለስልጣኖች መታዘዛቸውን ገልጸው ትእዛዙን ሳያከብሩ መቅረታቸውን አስረድተዋል።
Ø
በጎንደር በተለምዶ ባህታ ተብሎ የሚታወቀው እስር ቤት በትናንትናው ዕለት በእሳት የጋየ መሆኑን ታውቋል። ቃጠሎ
የተነሳበት ምክንያት ያልታወቀ ሲሆን ከእስር ቤቱ በርካታ እስረኞች ማምለጣቸው በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለዜና ምንጮች በሰጡት
መግለጫ ገልጸዋል። እስረኞች ሲያመልጡ በወያኔ ወታደሮች
በተተኮሰ የእሩምታ ጥይት ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን የሞቱት
ከ40 በላይ መሆናቸውም እየተነገረ ነው። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎችም በወያኔ የጸጥታ ስራተኞች ታፍነው ወደ አልታወቀ ስፍራ
የተወሰዱ መሆናቸውንም የአይን እማኞች ተናገረዋል።
Ø
የአዲስ አበባን ማስተር
ፕላን በመቃወም በተለያዩ ቦታዎች የሚደረገው የተቃውሞ እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት በነቀምት ከተማ የወለጋ
ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ነዋሪው ሕዝብ ከፍተኛ ተቃውሞ በማድረጉ የወያኔ አግዓዚ ሰራዊት በተከተማዋ የተሰማራ መሆኑን ለማወቅ
ተችሏል ። መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ከመደረጋቸውም በላይ የንግድ ሱቆች መስሪያ ቤቶች የተዘጉ መሆናቸውና መብራትም እንደጠፋ
ተሰምቷል። በተያያዘ ዜና በአምቦ አመጽ አስነስታችኋል ተብለው
የተያዙ ዜጎች ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ምርመራ መወሰዳቸውን ከአካባቢው
ከመጣ መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በቀንደኛነት አመጹን አስተባብራችኋል
ከተባሉት መካከል አበበ ቃበታ እና ሳሙዔል ነገዎች የሚባሉ ዜጎች የሚገኙበት ሲሆን ሌሎችም ስማቸውን ለጊዜው ማወቅ
ያልታቻለ በርካታ ሰዎች እንደተወሰዱ ታውቋል። በልዩ ልዩ ቦታዎች ዩነቨርስቲዎችና ትምህርት ቤቶች እየተዘጉ መሆናችውም እየተነገረ
ነው።
Ø
የወያኔ የመከላከያ
ደህንነት አባል በሆነ ግለስብ አለአግባብ እንዲደበደብ መመሪያ ሰጥቷል፤ በሚል
ክስ የተወነጀለው በሐረር የወያኔው የፈዴራል ፖሊስ ሹም በጥብቅ
እየተፈለገ መሆኑ ታወቀ። በድብደባ ተጎዳ የተባለው የወያኔ ሰራዊት አባል ለህክምና ወደ አዲስ አበባ የጦር ኃይሎች ሆስፒታል
የተወሰደ ሲሆን የፌዴራል ፖሊስ ሹሙን ለመፈለግ የወያኔ ወታደሮች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የነዋሪዎችን መኖሪያ ቤቶ እየፈተሹና
ህዝቡን እያሸበሩ መሆናቸው ታውቋል። በተለይ ከራስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኙ መኖሪያ ሰፈሮችና ወደ ቢራ ፋብሪካ በሚወስደው
መንገድ አቅራቢ ነዋሪ የሆኑ ዜጎች ስላማቸው የታወከ መሆኑን መሸበራቸውን በምሬት ሲናገሩ ተደምጠዋል።
የወያኔ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊሱ ጠብ መነሻ ምን እንደሆን ባይታወቅም ቀደም ብሎ አንድ የፖሊስ አባል
በወታደሮች ተገድሎ ስለነበር ከዚያ ጋር በተያያዘ የመበቃቀል እርምጃ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት የሚሰጡ አሉ።
Ø
አምነስቲ ኢንተርናሽናል
በሚል ስም የሚጠራው የአለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት በዛሬው ዕለት ባሰራጨው ዘገባ የሻዕቢያ መንግስት በዜጎቹ ላይ
የጫነው የወታደራዊ አገልግሎት ግዳጅ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ካለ በኋላ ዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ይህን የሻቢያ የግዳጅ
ወታደራዊ አግልጎት በሰባአዊ መብት ጥሰትነት መድቦና
አውግዞ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ ባደረገው ዘገባ በተለይ ወደ አውሮፓ
የሚጓዙት አብዛኞቹ ኤርትራውያን ሰደተኞች ከአገራቸው የሚወጡት ይህንን የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎት በመፍራት መሆኑን ድርጅቱ
ካነጋገራቸው ስደተኞች የተረዳ መሆኑን ገልጸዋል። የወታደራዊ አገልግሎት ስራ በጣም አድካሚ አስቸጋሪ
መሆኑና ግዳጁን አንፈጽምም በሚሉት ላይ የሚወሰደው ቅጣት ከባድ መሆኑን የሚያስረዱ መረጃዎች ከስደተኞቹ የተገኙ
መሆናቸውን ድርጅት በዘገባው ላይ አካትቷል።
Ø
ከአምስት ዓመት በፊት
በጊኒ የሽግግር መንግስት መሪ የነበሩትና ከዚያ በኋላ የአፍሪካ
ህብረት የሰላም አሰባሪ ኃይል ተጠሪ ተደርገው በድርጅት ተሰይመው የነበሩት ጄኔራል ሴኩባ ኮናቴ በርካታ ገንዘብ ህገ ወጥ በሆነ
መንገድ ወደ አሜሪካ ለማስገባት ሞክረዋል በሚል ቀርቦባቸው የነበረውን ክስ በመቀበል ጥፋተኛነታቸውን ማመናቸው ተነገረ። ከሁለት
ዓመት በፊት 64 ሺ የአሜሪካን ዶላር በሻንጣቸው ይዘው ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ በዋሽንግተን ዳላስ አውሮፕላን
ማረፊያ ላይ የተያዙት ጄኔራል በትናንትናው ቀን ፍርድ ቤት ለመቅረብ ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበረ ቢሆንም ጥፋታቸውን በማመናቸውና
ከፍርድ ቤት ውጭ ስምምነት በማድረጋቸው ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ የተደረገ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ከፍርድ ቤት ውጭ
በተደረገው ስምምነት መሰረት ጄኔራሉ በአምስት አመት እስራት የሚቀጡ መሆናቸውም ተነግሯል።
Ø
በሰሜን ካሜሩን ዋዛ
በሚባለው አካባቢ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዷችው ቦምቦች ከአሸባሪዎቹ ጋር ባጠቃላይ ስድስት ሰዎች መሞታችው ተነግሯል።
ቦኮሃራም የሚባለው አሸባሪ ቡድን ቀደም ብሎ በአካባቢ ጥቃት ሲያደርስ የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የትናንቱንም ጥቃት የፈጽሙት
የዚሁ ድርጅት ታጣቂዎች ናቸው የሚል ግመት አለ።
Ø
በብሩንዲ ዋና ከተማ
በቡጁምቡራም በዛሬው ሌሊት ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውን የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል። ከሞቱት መካከል አንደኛው የፖሊስ አባል ሲሆን
ሌሎቹ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸው ታውቋል። የተኩስና የፍንዳታ ድምጾች በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች ሲሰሙ ያደሩ መሆናቸውም ተገልጿል።
Ø
በናይጄሪያ በቢያፍራ
ግዛት የተቀሰቀሰውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለመግታት ተጨማሪ የፌዴራል የፕሊስ ኃይል ወደ ቦታው የተላከ መሆኑ ተነግሯል።
የአካባቢው ፖሊሶች ማንኛውንም ሕዝባዊ ስብሰባና የቡድን እንቅስቃሴ እንዲበትኑ ጥብቅ ትእዛዝ የተሰጠ ሲሆን ሕዝቡን በቀንደኛነት
ለአመጽ ያነሳሳሉ ተብሎ የሚጠረሩ ዜጎችም ታስረው ለፍርድ እንዲቀርቡ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ተነግሯል። የቢያፍራ ግዛት ከናይጄሪያ
እንድተገነጠል የሚቀሰቅሱ ክፍሎች እየተንቀሳቀሱ መሆናችው የሚታወቅ ሲሆን የአሁኑ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የጀመረበት ምክንያት
ከጥቂት ጊዜ በፊት መቀመጫውን ለንደን በማድረግ የመገንጠልን መንፈስ የያዘ ፕሮጋንዳ ለአመታት ሲያስተላልፍ የነበረው ናምዲ ካኑ
የተባለው ግለስብ መያዙን አለፍርድ መቆየቱን በመቃወም ነው ተብሏል።
Ø
ዛሬ ጠዋት በምስራቅ
ሊቢያ የወታደራዊ ኦፕሬሽን መሪ የነበሩ ኮሎኔል አሊ አልቶማን
የሚባሉ መኮንን በተቀበረ ፈንጅ ፍንዳታ የተገደሉ መሆናቸውን አንድ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ከቤንጋዚ ባስተላልፈው ዜና ገልጿል።
መኮንኑ የቤንጋዚ ወታደራዊ ኦፕሬሽን መሪ ሲሆኑ በቅርቡ አክራሪ አማጽያንና የአይሲስን ቡድን ከቤንጋዚ ለማስወጣት በተካሄደው
ወታደራዊ እርምጃ ቁልፍ ሚና የነበራቸው መሆኑ ይነገራል። የሊቢያው መሪ ጋዳፊ ከስልጣናቸው ከተወገዱ ጀምሮ በሊቢያ በርካታ
የታጠቁ ኃይሎ እየተንቀሳቀሱ አገሪቱን እያመሷት ሲሆን
ራሳቸውን መንግስት ብለው የሰየሙ የ ሁለት ክፍሎች በአገሪቱ ምስራቅና ምእራብ አስተዳዳሮች
መስርተው ይገኛሉ።
ህዳር 21 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአገሪቷ ላይ
በተከሰተው የዝናም እጥረት ምክንያት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድቦች በቂ ውሃ ሊያቁሩ ባለመቻላቸው ካለፈው በባሰ ሁኔታ የኤሌክትሪክ
አገልግሎት የሚይቋረጥ መሆኑን የወያኔ ባለስልጣኖች እየየተናገሩ ይገኛሉ። ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ጊቤ አንድ እና ሁለት
የተባሉትና እንዲሁም በጣና በለስ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያዎች ላለፉት ሁለት ቀናት አገልግሎት አቋርጠው የነበሩ
መሆናቸው ተገልጿል።
የድርቁ ሁኔታ እየከፋ
ሲመጣ የመብራት መጥፋትም እየተባባሰ እንደሚሄድ ከወዲሁ እየተነገረ ነው። የክረምቱ ወራት ካለፈ ገና ሁለት ወር ቢሆነውም
የተከዜ፤ የቆቃና የመልካዋከና ግድቦች ውሃ በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱ ታውቋል።
Ø
በተያያዘ ዜና ኅዳር 19
ቀን 2008
ዓ/ም
ከረፋድ
በኋላ
በወያኔ
ብዙ
የተወራለት
የአዲስ
አበባው
ቀላል
ባቡር
በመብራት
መጥፋት
ምክንያት
ስራ
ማቆሙና
በወቅቱ
ተሳፍረው
የነበሩ
ተሳፋሪዎች
ድንገት
ከቆመው በሩ ተዘግቶባቸው
ለረዥም ጊዜ ከባቡሩ ሳይወርዱ መቆየታቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ይህ የወደፊቱ ትውልድ በቀላሉ ሊከፍለው በማይችለው ብድር የተሰራው ቀላል ባቡር ወያኔ ለፖሊቲካ ፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ
አድሮጎት የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መብራት ቢጠፋ እንኳ ራሱ በሚያጠራቅመው የኤሌክትሪክ ኃይል ይጓዛል እንጅ በፍጹም
አገልግሎቱ አይቋረጥም እየተባለ ዲስኩር ሲሰጥበት መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ፍጥነቱ ከኤሊ ጉዞ ያልተሻለ ነው እየተባለ የሚታማው
የከተማው ባቡር ህዳር 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ወገቤን በማለት ተሳፋሪዎችን እንደያዘ መሃል መንገድ ተገትሮ መቅረቱ ታውቋል።
Ø
በአዲስ አበባ ማስተር
ፕላን ስም መሬቶችን ለመቀራመት የወያኔ ባለስልጣኖችት ያወጡትን እቅድ በመቃወም በተለያዩ ከተሞች የሚደረጉት የተቃውሞ
እንቅስቃሴዎች የቀጠሉ መሆናቸው ከየቦታው የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ። ቀደም ብሎ በሃረማያ ዩነቨርስቲ ተቃውሞ ሲያሰሙ በነበሩ
ተማሪዎች ላይ የወያኔ ፌዴራል ፖሊስ በወሰደው የጭካኔ እርምጃ የሞቱና የቆሰሉ ተማሪዎች መኖራቸው የተገለጸ ሲሆን
በባሌ መደወላቡ በተባለው ዩነቨርሲቲ ውስጥም ተማሪዎች
የተቃውሞ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ታውቋል።
Ø
በቡርኪና ፋሶ እሁድ
ዕለት በተካሄደው ምርጫ ሚስተር ክርስቲያን ካቦሬ የተባሉት የቀድሞ መንግስት ሚኒስትርና የፓርቲው መሪ የጠቅላላውን ድምጽ 53.5
ከመቶ በማሸነፍ የሚቀጥለው የቡርኪና ፋሲ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን የአገሪቱ የምርጫ ቦርድ ገለጸ። ፕሬዚዳንቱ በቂ ድምጽ
በማግኘታቸውም ሁለተኛ ዙር ምርጫ የማይካሄድ መሆኑም ተገልጿል። ሚስተር ካቦሬ ለሃያ ሰባት ዓመት በመሪነት የቆዩት የቀድሞ
የአገሪቷ ፕሬዚዳንት ካምፓወሬ ለሌላ አምስት አመት ጊዜ ለመወዳደር ያወጡትን ፕላን በመቃወማቸው ከስልጣን የተገለሉ መሆናቸው
ሲታወቅ የቀድሞው ፕሬዚዳንት በሕዝብ አመጽ ተገደው ሲወርዱ
ካቦሬ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን አትርፈው እንደነበር ይታወቃል።
Ø
የቀድሞ የናይጄሪያ
የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ ሚስተር ሳምቦ ዳሱኪ ሁለት ቢሊዮን ዶላር የመንግስት ገንዘብ ሰርቀዋል ተብለው ዛሬ ጠዋት በጸጥታ ኃይሎች
ከቤታቸው ተይዘው ተወስደው በቁጥጥር ስር የተደረጉ መሆናቸው
ታውቋል። ሚስተር ዳሱኪ የተከሰሱት አስራ ሁለት ሄሊኮፕተሮችን ሁለት ተዋጊ አውሮፕላኖችን እና መጠናቸው ከፍተኛ የሆኑ የጦር
መሳሪያና ጥይቶችን ለመግዛት የሀሰት ስምምነት አድርገው ገንዘቡን ለራሳቸው ጥቅም አውለዋል በሚል ክስ ነው። የዛሬ ሁለት ሳምንት
የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ሚስተር ዱሲኪ እንዲታሰሩ
ካዘዙ ጀምሮ ግለሰቡ በቤታቸው ውስጥ በቁም እስር ላይ እንደነበሩ ይታወቃል። ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው
አንድ ቀን ቀደም ብሎ ተባባሪያቸው ናቸው የተባሉ የቀድሞ መንግስት ሚኒስትሮችና የቀድሞ ገዥ ፓርቲ ሹማንንት ልጆች
የታሰሩ መሆናቸውም ተገልጿል። ሚስተር ዳሱኪ ክሱን ከመካዳቸው በተጨማሪ በራሳቸው በኩል ያለውን ሁኔታ ለማስረዳት እድል
ያልተሰጣቸው መሆኑን ገልጸው በእሳቸው ላይ ለተወሰደው እርምጃ ምክንያቱ ፖለቲካዊ ነው ብለዋል።
Ø
በብሩንዲ እየተባበሰ
የሄደውን የእርስ በርስ ግጭት ለመግታት አስቸኳይ እርምጃ መወሰድ አለበት በማለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ
ሙን አሳሰቡ። ባንኪ ሙን ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ሰኞ ዕለት በላኩት የደብዳቤ መልእክት ሶስት አማራጮችን ያቀረቡ ሲሆን
ከምርጫዎቹ መካከል በተመድ የሚመራ የሰብአዊ መብት
ጥሰቶችን የሚከታተል፤ የእርቅ ውይይቶች እንዲደረጉ የሚገፋፋ እና ምናልባት የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ቦታው ሊገባ የሚችልበትን
ሁኔታ የሚያጠና አንድ የተመድ ቡድን ወደ አገሪቱ እንዲላክ ጠይቀዋል። ዋና ጸሐፊው የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ወደ ብሩንዲ
የሚላክበትን መንገድ ሙሉ በሙሉ ባይዘጉም ባሁኑ ወቅት አስፈላጊ አይደለም ብለዋል። ሰኞ ዕለት በዝግ ስብሰባ የተወያየው የተመድ
የጸጥታው ምክር ቤት በቅርቡ አንድ የተባበሩት መንግስታት ቡድን ወደ ብሩንዲ ለመላክ ሳይወስን አይቀርም ተብሏል።
Ø
ስትራትሞር በሚባለው
የኬኒያ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተማሪዎች የሽብር ተግባሮችን በሚገባ ለመቋቋም የሚያስችላችውን ልምምድ እያደረጉ ባሉበት ወቅት በድንገት
በተፈጠረ ድንጋጤና ሽብር ከፍተኛ የእርስ በርስ ግፊያ ተከስቶ አንድ ተማሪ ሲሞት 141 የሚሆኑ መጎዳታቸው ታውቋል። ከወትሮ
ለየት ያሉ ከፍተኛ ድምጾች በድንገት በመሰማታቸውና አንዳንድ ሰዎች
አሸባሪዎችን መስለው በከፍተኛ ደረጃ በመንቀሳቀሳቸው በተማሪዎች
ውስጥ ፍርሃት በመፍጠሩ ሁሉም በአንድ አቅጣጫ ሲሞክር በተነሳው ግፊያ ጉዳት ሊደርስ ችሏል ተብሏል። ኬኒያ አልሸባብን ለመቋቋም
ሶማሊያ ውስጥ ጦሯን ከላከች ጀምሮ በአልሸባብ ሽብረተኞች በተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰባት መሆኑ ይታወሳል።
Ø
አይሲስ የተባለው
አሸባሪ ቡድን በሲሪያ ውስጥ በተቆጣጠረው የነዳጅ ማምረቻ የሚመረትና በኢንዱስትሪ ድረጃ ጥቅም ላይ የሚውል የነዳጅ ዘይት የነዳጅ
ዘይት ቱርክ በግዥ ወደ አገሯ እንደምታሰገባ ተጨማሪ መረጃ ደርሶናል ሲሉ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ፑቲን ተናገረዋል። የሩሲያ
ፕሬዚዳንት ጨምረው እንደተናገሩት ቱርክ የሩሲያ የጦር አውሮፕላን መትታ የጣለቸው ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ከአይሲስ ተገዝቶ ወደ
ቱርክ የሚላከውን ነዳጅ ለማሰናከል የሩሲያ የጦር አውሮፕላኖች እርምጃ በመውሰዳቸው ነው ብለዋል። የከባቢ አየር ብክለትን
ለመቆጣጠር በፓሪስ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ ስብስባ
ላይ የተገኙት የቱርክ ፕሬዚዳንት ሰኞ ዕለት ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ የፕሬዚዳንት ፑቲንን ክስ አስተባብለው እውነትነቱን
የሚያረጋግጥ መረጃ ከተገኘ ከስልጣኔ እለቃለሁ ብለዋል። ቱርክ በአይሲስ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ስታቅማማ የቆየች ከመሆኑንም በላይ
በአሜሪካ መሪነት በአይሲስ ላይ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ላይ የተካፈለችው ዘግይታ መሆኗን ጉዳዩን በቅርብ የተከታተሉ ወገኖች
ይገልጻሉ። የቱርክ ፕሬዚዳንትም ቱርክ የሩሲያን አውሮፕላን መትታ በመጣሏ ይቅርታ አትጠይቅም ብለዋል። በተያያዘ ዜና በቱርክ
ተመቶ የወደቀውን የሩሲያ አውሮፕላን አብራሪ የነበረውና በጃንጥላ ሲወርድ በአማጽያን የተገደለው ፓይለት አስከሬንን ቱርክ ለሩሲያ
ያስረከበች መሆኗ የተገለጸ ሲሆን አስከሬኑም ሞስኮ የገባ መሆኑ ተነግሯል።
ህዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ለአዲስ
አበባ
ነዋሪዎች
የመጠጥ
ውኃ
ከሚሰራጭባቸው ግድቦች መካከል
አንዱና
ዋናው
በሆነው
በለገዳዲ
ግድብ
የውኃ
እጥረት
መከሰቱን
ለጉዳዩ
ቅርበት
ያላቸው
ምንጮቸ
ገልጸዋል።
በአገሪቱ
ውስጥ በገባው ድርቅና የዝናብ
እጥረት
ምክንያት
በለገዳዲ
የውኃ
ማጠራቀሚያ
ግድብ
ውስጥ
መኖር
የነበረበት
የውሃ መጠን
በጣም
እያነሰ
በመምጣቱ
ከዚህ ግድብ ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚሰራጨው
ውኃ
በፈረቃ
እንዲሆን
የወያኔ ባለስልጣኖች
የወሰኑ
መሆኑን
ምንጮቹ አጋልጠዋል።
ከለገዳዲ
ጀምሮ
በአንቆርጫ
አድርጎ
እስከ
ሽሮ
ሜዳ
ድረስ ወደ
ሰባት
የሚጠጉ
የውሃ
ማከማቻ ቦታዎች ያሉ ሲሆን ውሃውን በእነዚህ
ማጠራቀሚያዎች ውስጥ ማስገባት ባለመቻሉ ሚስጥራዊ በሆነ መንገድ የፈረቃ ስርጭት ማድረግ ግዴታ ነው በማለት ባለስልጣኖቹ
የወሰኑ መሆኑ ታውቋል።
ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ
ለመስመር ኃላፊዎች መመሪያ የተሰጠ ከመሆኑም በላይ ውሃው በሚቋረጥበት ወቅትም አብሮ መብራት እንዲጠፋ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን
በተጨማሪ የደረሰን ዜና ይገልጻል።
ከአራት
ኪሎ
ጀምሮ እስከ ሽሮ ሜዳ ባሉ የመኖሪያ ቦታዎች የመጠጥ
ውኃ
ከጠፋ
ከሳምንት በላይ
ያስቆጠረ ሲሆን
ከለገዳዲ የሚሰራጨውን ውሃ በሚጠቀሙ ሌሎች አካባቢዎችም ውሃው
ለይስሙላ
ሌሊት 11
ሰዓት
ላይ
ይለቀቅና
ከሰላሳ
ደቂቃ
በኋላ
እንዲቋረጥ የሚደረግ መሆኑን
ዘገባው
ጨምሮ
አስረድቷል።
Ø
በትናንትናው ዕለት
በ100 ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች የከባቢ አየር ለውጥ አስመልክቶ
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሰላማዊ ስልፎችንና ስብሰባዎችን ያደረጉ
መሆኑ ታወቀ። በተለያዩ ቦታዎች ሰልፉን ያካሄዱት ዜጎች እየተባለሸ
የሄደውን የዓለም የከባቢ አየር ሁኔታ ለመቋቋም በዛሬው ዕለት በፓሪስ ከተማ በሚጀመረው ዓለም አቀፍ ስብስባ ላይ ተጨባጭ
ስምምነት እንዲደረግ መንግስቶቻቸው ላይ ጫና ለመፍጠር ነው
ተብሏል። በ170 አገሮች ውስጥ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሆኑ ሰዎች
የተሳተፉባቸው ሰልፎች በሙሉ በስላም የተከናወኑ ሲሆን በፓሪስ ላይ የነብረው ስብስብ ግን በፖሊሶች የተበተነ
ከመሆኑም በላይ ህግን ተላልፋችኋል ተብለው ከ200 በላይ የሆኑ
ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል። በፓሪስ ባለፈው ሁለት ሳምንት በከተማዋ ላይ በደረሰው የሽብር ተግባር ምክንያት
ስብሰባዎችና ሰልፎች የተከለከሉ በመሆናቸው በመሃል ከተማ ውስጥ ለመሰብሰብ የሞከሩትን ሰዎች ፖሊሶች በትነዋል፤ አንዳንዶቹ
አስረዋል። ሌሎች የፓሪስ ነዋሪዎች በየመንገዱ ዳርቻ እጅ
ለጅ ተያዘው ድምጻቸውን ያሰሙ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ ጫማቸውን በአደባባይ ላይ በማስቀመጥ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በኒውዩርክ በአውስታሊያ በባንግላዴሽና በእንግሊዝ የተደረጉት
ሰልፎች ባለፈው ዓመት ከተደረጉት ሰልፎች የበለጠ መሆኑ ተገልጿል። ከሰልፉ በተጨማሪ በተለያዩ አገሮች 1.8 ሚሊዮን የሚሆኑ
የተለያዩ አገር ዜጎች ፊርማቸውን በማስቀመጥ የከባቢ አየር ሙቀትን
ለመቋቋም አስቸኳይ ርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠይቀዋል።
Ø
በከባቢ አየር ላይ
እየጨመረ የመጣውን የሙቀት መጠን ለመቋቋም የሚደረገው ዓለም አቀፍ
ስብሰባ በዛሬው ዕለት በፓሪስ የተጀመረ ሲሆን የ150 አገሮች መሪዎችና 22ሺ የሚሆኑ ሌሎች ባለስልጣኖች ተገኝተዋል ተብሏል።
የሙቀቱ መጠን 2 ድግሪ ሴልሸስ ይጨምራል ተብሎ የሚገመተውን
የዓለማችንን የከባቢ አየር ለውጥን ለመቋቋም እያንዳንዱ አገር
የካርቦን ጭስን በማሰረጨት በከባቢ አየር ላይ የሚያደርገውን ብክለት እንዲቀንስ የሚያስችለው ተጨባጭ እርምጃዎች ላይ
ተሰብሳቢዎቹ ስምምነት ላይ ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
በትናትናው ዕለት
የሮማው ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ በዩጋንዳ የሚያደርጉትን ጉብኝት
አጠናቅቀው በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የጸጥታ ውጥረት ያለባትን የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክን ለመጎብኘት በዋና ከተማው ባንጉዊ
ገብተዋል። ጳጳሱ ባንጉዊ ሲገቡ ከአውሮፕላን ጣቢያ ጀምሮ በርካታ ሕዝብ በደስታ የተቀበላቸው ከመሆኑ በላይ በቤተ መንግስቱ ውስጥ
በተደረገው የአቀባብል ስነስርዓት ላይ ባሰሙት ንግግር ስዎች በሌሎች ሰዎች ላይ፤ በሌሎች ጎሳዎች፤
በሌሎች ሃይማኖች ላይ ያለቸውን ጥላቻና ፍርሃት አስወግደው ወደ አንድነት መምጣት ይበጃቸዋ ብለዋል። ከከተማዋ ወጣ
ብሎ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ያካሄዱትን ስርዓተ ቅዳሴ
ፈጽመው ባደረጉት ንግግርም በአገሪቱ የሚገኙ የአማጽያን ኃይሎች
አባላት መሳሪያቸውን አውርደው ፍትሕን፤ ፍቅርን፤ ይቅርታን እና
ሰላምን እንዲታጠቁ ጠይቀዋል። በዛሬው ዕለትም ባንጉዊ ከተማ
ውስጥ የእስልምና ተከታይ የሆኑ ዜጎች ወደ ሚኖሩበት ስፍራ ሄደው መስጊድ ውስጥ ባደረጉት ንግግር
የክርስትናና የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወንድማማቾችና
እህትማማቾች ስለሆኑ በአንድ ላይ በፍቅር
መኖር አለባቸው የሚል መልክት አስተላልፈዋል። ሁከትና
ሽብር በበዛባት በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ውስጥ ጳጳሱ ያደረጉት ጉብኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
በደቡብ ሱዳን
በአማጽያኑና በሳልቫ ኬር በሚመራው የመንግስት ክፍል መካከል ሲደረጉ የቆዩ ስምምነቶች በተደጋጋሚ መጣሳቸው የሚታወስ ሲሆን
ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ የተደረገው የመጨረሻው ስምምነትም አደጋ የተጋረጠበት መሆኑን የአፍርካ ህብረት ተወካዮች እየገለጹ
ይገኛሉ። በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ድጋፍ ያላቸውና የተኩስ አቁም
ሁኔታ ለመከታተል የተመደቡ ታዛቢዎች ባለፈው ዓርብ በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ውስጥ የመጀመሪያ ስብሰባቸውን ያደረጉ ሲሆን
ከአማጽያን በኩል የተመደቡት ተወካዮች በስብሰባው ሳይገኙ ቀርተዋል። የአፍሪካ ህብረት ተወካይ በገለጹት መሰረት የአማጽያኑ
ተወካይ የክትትልና የግምገማ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ሁሉም ወገን መገኘት ሲገባቸው የአማጽያኑ ተወካዮች አለመገኘታቸው ሁኔታውን
አሳሳቢ ያደረገዋል ብለዋል። አሜሪካ እንግሊዝና ኖርዌይ ተደራዳሪዎቹ በስበስው ካልተገኙ ስምምነቱ ሊፈርስ ይችላል ብለዋል።
Ø
በምስራቅ ኮንጎ
ኢሬንጌቲ በተባለችው ከተማ ውስጥ በአማጽያንና በመግንስት ወታደሮች
መካከል በተደረገ ግጭት 30 ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ከአካባቢው ያገኘውን ዜና ዋቢ አድርጎ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና
ወኪል ገልጿል። በትናንትናው ዕለት ራሱን የየተባበሩት የመከላከያ ኃይሎች ብሎ በሚጠራውና በመንግስቱ ወታደሮች መካከል የተካሄደው
ውጊያ ለአስር ሰዓታት የቆየ ሲሆን ከሞቱት መካከል አንድ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል፤ እንዲሁም ሰላማዊ
ሰዎችና ወታደሮች እንዳሉበት ታውቋል። በከተማዋ ውስጥ 43 ቤቶች
ሲቃጠሉ 10 ሰዎችም ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ተነግሯል። ከዚህ በፊት አካባቢው ከዩጋንዳ በሚሚጡ አማጽያን ተድጋጋሚ ጥቃት
የደረሰበት ሲሆን ባለፈው ዓመት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል እና የመንግስቱ ወታደሮች የአማጽያኑን ጥቃት ለመቋቋም ሰፊ
ወታደራዊ ዘመቻ ማድረጋቸው ይታወሳል።
Ø
በቡርኪና ፋሶ ለረዥም
ጊዜ በስልጣን ላይ የነበሩት መሪ በሕዝባዊ አመጽ ከተወገዱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በትናንትናው ዕለት አጠቃላይ ምርጫ ተካሂዷል።
በትናንትናው ምርጫ 18 ሚሊዮን ሕዝብ ድምጹን ሰጥቷል ተብሎ የተገመተ ሲሆን የጸጥታው ሁኔታ ጥብቅ የነበረ መሆኑም ታውቋል።
ምርጫው የተካሄደው ለፕሬዚዳንት ቦታ እና ለህግ አውጭው ምክር ቤት ሲሆን በርካታ ፓርቲዎች የተሳተፉ መሆናቸው ተነግሯል።
የቀድሞ መንግስት ባለስልጣኖችና ከስልጣን የተወገዱት ፕሬዚዳንት
ቀንደኛ ደጋፊዎች ከውድድር ውጭ የተደረጉ ቢሆን ኮንግሬስ ፎር ዴሞክራሲ (CDP) የተባለው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ፓርቲ ተወካዮችን
በማሰማራት እንዲወዳደር ተድርጓል። የትናንቱ ምርጫ ለረዥም ጊዜ ለቆየው ለሕዝቡ የዴሞክራሲ ጥያቄ መልስ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ከሰላሳ ዓመት በላይ አገሪቷን ሲመሩ የቆየት ፕሬዚዳንት ካምፓወሬ ባለፈው ዓመት በሕዝባዊ አመጽ ተገድደው ስልጣናቸውን
እንዲለቁ የተደረጉ መሆናቸውና ምርጫ እስኪደረግ ድረስ የሽግግር አስተዳደር ተሰይሞ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ባለፈው መስከረም
ወር የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ የሆኑ ወታደሮች የሞከሩት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በሕዝብ አመጽ መክሸፉ እንዲሁም
መሪዎቹ መታሰራቸውና ተቋሙ መፍረሱም አይዘነጋም።
የምርጫው የመጀመሪያ ውጤት በዛሬው ዕለት ይገለጻል ተብሎ ሲጠበቅ
የነበረ ሲሆን ማንም አሸነፈ ማን ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ እየጠበቀ ያለውን የሚመጠን ስራ ለመስራት ብርቱ ጥረት ይጠይቃል የሚሉ
በርካታ ናቸው።
ህዳር 18 ቀን
2008 ዓ.ም
Ø
በአማራው አካባቢ ድርቁና ረሃቡ
በከፋባቸው አካባቢዎች በተለይም ወሎ
ውስጥ አበርገሌ፤ ሰቆጣ፤ አርባጩፋ በተባሉ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች ረሃቡን መቋቋም አቅቷቸው ወደ መሃል ከተሞች
በመሰደድ ላይ መሆናቸው ታውቋል። በዘንድሮ ድርቅ
የሰሊጥና
የጤፍ አዝመራቸው በሙሉ የወደመ መሆኑ ብዙዎቹ ይናገራሉ። ተሰደው በሰፈሩበት ቦታ የሚሰጣቸው እርዳታ በቂ ካለመሆኑም በላይ
የወያኔ ካድሬዎች አንተ የእገሌ ወገን ነህ አንተ የእገሌ ደጋፊ ነህ ስለሆነም እርዳታ አታገኝም በማለት የሚያንገላቷቸው መሆኑን
እየተናገሩ ይገኛሉ። ይህ በንዲህ እንዳለ በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል ስድስት መቶ ሺህ ዜጎች የአስቸኳይ ምግብ እርዳታ
የሚያስፈልጋቸው መሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው በአዋሳ የሚገኙ ክፍሎች ገለጹ ። ድርቅ አይደፍረውም እየተባለ የሚነገርለት የደቡብ
አካባቢ ዘንድሮ ክፉኛ በድርቅ በመመታቱ ዜጎች የድርቅና የረሃብ ሰለባ ሆነዋል። በነብስ ወከፍ የአንድ ዙር እርዳታ መስጠት
የተቻለው አርባ አምስት ሺህ ለሚሆኑት ብቻ ሲሆን ከአምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተረጂዎች አስቸኳይ እርዳታው
ሊዳረስ ባለመቻሉ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ወድቀዋል ተብሏል። ተማሪዎችም በድርቁ ምክንያት ትምህርት ማቆም ሲሆን አንዳንዶቹም
እየተሰደዱ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
ሰሞኑን የአዲስ አበባ አስተዳደር ማስተር ፕላንን በመቃወም የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች እያካሄዱት
ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ
በመቀጠሉ ውጥረቱ የተባባሰ ከመሆኑም በላይ ወደ አጎራባች ከተሞች የተዛመተ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በጊንጪ ከተማ ተማሪዎች
በአካባቢያቸው እየተካሄደ ያለውን የመሬት ዘረፋ ተቃውመው መሰለፋቸው ታውቋል። በመንዲና በሌሎች ቦታዎች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችም
ቀጥለዋል። የአግዓዚ ቅልብ
ወታደሮች የሚገኙበት የፌዴራል ፖሊስ አባላት በየከተሞቹ ነዋሪውን በተኩስ
ከማሸበራቸው በላይ በርካታ ወጣቶችን በዱላ ቀጥቀጠው ጉዳት ላይ የጣሉ መሆናቸው ተነግሯል። የአካባቢው የወያኔ ባለስልጣናች ሃያ
ብቻ ይበሉ እንጅ ከተለያዩ ቦታዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ተይዘው ወደ አልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውም ታውቋል።
Ø
ባለፈው ሀሙስ ጠዋት የታንዛኒያ ፖሊስ በህገ ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብታችኋል በማለት
105 ኢትዮጵያውያንን ይዞ ማሰሩ ታወቀ። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት በዳሬሰላም ከተማ
ውስጥ በሚገኘው ታቤታ ሳጌሪያ በተባለው ቀበሌ በአንድ ስሙ ባልተገለጸ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ መሆኑ ተነግሯል። ኢትዮጵያውያኑ
ወደ ታንዛኒያ የመጡት በነፍስ ወከፍ አንድ ሺ ዶላር
እየተቀበለ በሚያስተላልፍ አንድ የብሩንዲ ተወላጅ አማካይነት እንደሆነ
የታንዛኒያ ፖሊሶች በምርመራ የደረሱበት መሆኑን ገልጸው ከምርመራው በኋላ ፍርድ
ቤት የሚያቀርቧቸው መሆኑን ተናግረዋል። የወያኔ አስከፊ አገዛዝ በመሸሽ በሁሉም አቅጣጫዎች አገራቸውን እየጣሉ በህገ ወጥ መንገድ
የሚሰደዱ ኢትዮጵያውን ቁጥር ከፍተኛ ሲሆን በታንዛኒያ የተያዙትም በተመሳሳይ መልክ አገራችው ውስጥ የሰላም ኑሮ መኖር ያቃታቸው
ዜጎች ናቸው።
Ø
የኬኒያ ጉብኝታቸውን አጠናቅቀው በትናንትናው ምሽት ኡጋንዳ የገቡት የሮማው ጳጳስ ከካምፓላ
ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ክፍት ቦታ ላይ በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ የካቶሊክ አማኞች በተገኙበት ስርዓተ
ጸሎት ያካሄዱ መሆናቸው ተነገረ። ጳጳሱ ኡጋንዳ ሲገቡ ባደረጉት አጭር ንግግር ኡጋንዳ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊና እና ከደቡብ
ሱዳን የመጡትን ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚገመቱትን ስደተኞች ማስተናገዷን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል። ጉብኝቴ ለአጭር ጊዜም
ቢሆን ለደሆዎች ለታሚሚዎችና ችግር ለደረሰባቸው ሁሉ እርዳታ እንዲደርግላቸው አበረታታለሁ ብለዋል። በዛሬው ዕለትም በብዙ ሺ
የሚቆጠሩ የዩጋንዳ ወጣቶች በተሰበሰቡበት ላይ ተገኝተው መልእክት አስተላልፈዋል።
በነገው ዕለት ወደ ማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቃል
Ø
በሰሜናዊ ማሊ በተባበሩት መንግስታት ጦር ሰፈር ላይ ታጣቂዎች ባካሄዱት ጥቃት ሁለት የተመድ
ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላትና አንደ ሰላማዊ ሰው የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። ከእነዚህ በተጨማሪ 20 ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን
የአራቱ ጉዳት ከበድ ያለ ነው ተብሏል። በታጣቂዎቹ የተገደሉት ሁለቱ የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት የጊኒ ተወላጆች ሲሆኑ
ሰላምዊው ሰው ደግሞ ስራዎችን ተኮናትሮ የሚሰራ ግለሰብ ነው ተብሏል። ባለፈው ሳምንት በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ውስጥ በሚገኝ
አንድ ሆቴል ላይ በደረሰ ጥቃት 19 ሰዎች መገደላቸውና በርካታ ታግተው መለቀቃቸው ይታወሳል። በሰሜናዊ ናይጄሪያ ካኖ በሚባለው
ግዛት በሺዎች የሚቆጠሩ የሺያ እስልምናን የሚከተሉ ዜጎች እምነታቸው ለመግለጽና ሃይማኖታቸውን ለማስታወስ በየአመቱ የሚያደርጉትን
የረጅም እርቀት
ጉዞ በሚያደርጉበት ወቅት የቦኮ ሃራም አጥፍቶ ጠፊዎች ባፈነዱት ቦምብ 21 ሰዎች የሞቱ
መሆናቸውን ከአካባቢው የተገኘው ዜና ይገልጻል። ቦምቡ የፈነዳው ከካኖ ዋና ከተማ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዳካሶየ
ከምትባለው መንደር ነው። ቀደም ብሎ በጥርጣሬ ፈንጅውን የአፈነዳውን ግለሰብ
በቁጥጥር ስር ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም ከመያዙ በፊት የታጠቀውን ቦምብ አፈንድቶ
ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።
ተባባሪ በመሆን የተጠረጠረው ሌላው ግለሰብ ግን በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ጥቃቱን
ለመፈጸም በቦኮሃራም የተላኩ መሆናቸውን ለመርማሪዎች ገልጿል። የቦምቡ ፍንዳታ ጉዳት ቢያስከትልም የእምነቱ ጉዞ ቀጥሎ በታቀደለት
ሁኔታ ተፈጽሟል።
ህዳር 17
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
አዋሳኝ አካባቢዎችን ወደ
አዲስ
አበባ
ለማጠቃለል
የወጣውንና እነ
አባይ
ጸሃዬ
በግድ ተግባራዊ ለማድረግ እየጣሩ ያለውን እቅድ በመቃወም በአምቦ ከተማ ነዋሪዎች የሚደረገው እንቅስቃሴ የቀጠለ ሲሆን
የአምቦ
ዩኒቨርስቲ
ተማሪዎች
ተቃውሞውን
እንዳይቀላቀሉ
ከፍተኛ
ጥበቃ
እየተደረገ
መሆኑን ከስፍራው የመጣው ዘገባ ያመለክታል።
ህዝባዊ
ቁጣውን
በኃይል
ለማፈን
ከአዲስ
አበባ
የፌዴራል
አድማ
በታኝ
ኃይል
ኅዳር 16
ቀን
ለ17
አጥቢያ
ወደ
ስፍራው
ያቀና መሆኑ
የታመኑ
የፖሊስ
ምንጮች
ይገልጻሉ።
ዘጋቢያችን
ከአምቦ
ከተማ አጠናክሮ እስከላከልን
ኅዳር
17 2008
ዓም
ረፋድ
ድረስ
በፖሊስ
ዱላ
በሶስት
ሰዎች
ላይ
ከፍተኛ
ጉዳት
መድረሱ
ሲታወቅ
ወደ
ሃያ
የሚጠጉ
የአምቦ
ነዋሪ
ፖሊሶች
ጨለማን
ተገን
በማደረግ
አፍነው
ወዳለታወቀ
ቦታ
የወሰዷቸው መሆኑን
የአይን
እማኞች
መናገራቸው
ተዘግቧል።
Ø
ማዕከላዊ
ምርመራ በሚባለው የወያኔ ማሰቃያ ስፍራ
በየቀኑ ቢያንስ 60 የሚሆኑ ሰዎች በጽኑ እንደሚገረፉና ከእነዚህም ውስጥ ቢያንስ አምስቱ
ለጉዳት የሚዳረጉ መሆናቸውን ለማዕከላዊ ምርመራ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አጋለጡ። ድብደባው የሚደርስበት ዜጋ ቁጥር በየቀኑ
እየጨመረ መሄዱ በእጅጉ ያሳሰባቸው
እነዚሁ ምንጮች ጨምረው እንደገለጹት በምርመራ
ሽፋን
ለሊት
ለሊት
ዘግናኝ
ድብደባ
የሚፈጸምባቸው
ወጣቶች
በብልታቸው
ላይ
ውሃ
የተሞላ
ኮዳ
እንዲንጠለጠልባቸው
መደረጉ
ለከፋ
ጉዳት
የዳረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ከተለያዩ
አካባቢዎች
ታፍነው
ወደ
ማዕካለዊ
ምርመራ
የሚመጡና
ድብደባ
የሚፈጸምባቸው
ወገኖች
ቁጥር
ምን
ያህል
እንደሆነ
ለቀረበው ጥያቄ ቁጥሩ በየጊዜው እንደሚለዋውጥና በአማካይ በየቀኑ
3ሚትር
በ3
ሚትር
በሆነ
አንድ
ክፍል
ውስጥ
ብቻ
ከ40
በላይ
የሚሆኑ
ሰዎች
ተፋፍገው
እንደሚታሰሩና
በጠቅላላው
አስር
በሚሆኑ
ክፍሎች
ውስጥ ቢያንስ
አራት
መቶ
የሚሆኑ
ክስ
ያልተመሰረተባቸውና
ወነጀላቸውን
የማያውቁ
ሰዎች
እንደሚታሰሩ
ተናግረዋል።
ከእነዚህ ውስጥ
በአማካይ
በየቀኑ
ስድሳ
የሚሆኑት
ግርፋት
እንደሚፈጸምባቸውና
ቢያንስ
አምስቱ ደግሞ ለከፋ ጉዳት እንደሚዳረጉ
ገልጸዋል።
ቤተሰቦቻቸው
የት
እንደታሰሩ
እንኳን
ስለማያውቁ
ብዙዎቹ እስረኞች
ጠያቂም
እንደሌላቸው
ምንጮቹ አክለው አስረድተዋል።
Ø
የአባይ ግድብ ስራ መቀጠል ግብጽ በጣም እንዳሳሰባት የግብጽ የውሃ አገልግሎት ሚኒስትር
አማካሪና የግድቡ ጉዳይ ቃል አቀባይ ማክሰኞ ዕለት በካይሮ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ከጥቂት ቀናት በፊት በሁለቱ
አጥኝ ቡድኖች መካከል በተነሳ አለመግባባት የታቀደው ጥናት መቋረጡን ግብጽ ያወገዘች መሆኑን ገልጸው ጉዳዩ የማይመለስበት ደረጃ
ከመድረሱ በፊት ጥናቱ መቀጠል አለበት ብለዋል። ግድቡ ወደ ግብጽ የሚፈሰውን የውሃ መጠን ይቀንሳል ብላ አገራቸው በጽኑ
ስለምታምን ጥናቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁለተኛው ዙር የግድቡ ስራ እንዲቋረጥ የግብጽ መንግስት በይፋ ወያኔን የሚጠይቅ መሆኑን
ተናግረዋል።
Ø
የኬኒያ ጉብኝታቸውን በዛሬው ቀን ያጠናቅቃሉ ተብለው የሚጠበቁት የሮማው ጳጳስ ኬኒያውያን
አፍራሽ የሆነውን የዘር ልዩነት አስወግደው ወደ አንድነትን እንዲመጡ አሳሰቡ። በኬኒያ ዋና ከተማ ካሳራኒ በሚባለው የስፖርት
ስታዲዩም ውስጥ ለወጣቶች
ባደረጉት ንግግር ላይ ጳጳሱ የአንድነት ጥሪ ከማሰማታቸው በላይ በስታዲዩሙ የተሰበሰበው አድማጭ አንድነቱን ለመግለጽ እጅ ለጅ
እንዲያያዝ አድርገዋል። ጳጳሱ በንግግራቸው ውስጥ በየጊዜው በሙስና ወደኪስ የሚገባው ገንዘብ
“ልብን
ይጎዳል፤ ማንነትን ያበላሻል
አገርንም ያጠፋል” በማለት በሙስና የተጨማለቁ ሰዎች በሰላም እንደማይኖሩ
ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ብሎ ናይሮቢ
ውስጥ የሚገኘውን የድሆች መንደር ጎብኝተው በመንደሩ ውስጥ የሚኖሩት ስግብግብ
በሆኑና ስልጣን ላይ ባሉ ሀብታሞች እየደረሰባቸው ያለው ጉዳት ከልብ የሚሰማቸው መሆኑን
ገልጸውላቸዋል።
Ø
ብሩንዲ ወደ አጠቃላይ ቀውስ እያመራች መሆኑን ግሬት ሌክስ በሚባለው የምስራቅ አፍሪካ አካባቢ
የአሜሪካ ልዩ መልከተኛ
የሆኑ ባለስልጣን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። ባለስልጣኑ ከጥቂት
ሳምንታት በፊት አገራቸው በብሩንዲ የጸጥታ ሚኒስቴርና በሌሎች ስልጣኖች ላይ የጣለችውን ማዕቀብ አስታውሰው ወደፊትም
እንደአስፈላጊነቱ በሌሎች ባለስልጣኖች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ ሊደረግ እንደሚችል አስረድተዋል። የቡርንዲው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ
ለመወዳደር መወሰናቸው የችግሩ ምንጭ ሊሆን ቢችልም የአገሪቷ አጠቃላይ ችግር የፖለቲካ ችግር ነው ብለዋል። ከዚህ በፊት በአገሪቷ
ተከስቶ እንደነበረው ዓይነት እልቂት ሊመጣ የሚችልበት እድል ከፍተኛ ስለሆኑ ሁኔታው ወደዚያ እንዳያመራ መንገዱን ለመዝጋት መጣር
አለብን ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቡሩንዲው ፕሬዚዳንት አማካሪ የሆኑ ባለስልጣን ከቤታቸው ወጥተው ወደ ስራቸው እየተጓዙ
እያሉ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው ያመለጡ መሆናቸው ተገልጿል። በደፈጣው ሙከራ ጠባቂያቸው የሆነ አንድ የፖሊስ አባል ሲገደል
ባለስልጣኑ ግን ሳይጎዱ ለማምለጥ የቻሉ መሆናቸው ታውቋል። በአንድ የቶዮታ እቃ መጫኛ መኪና ላይ ሆነው ግድያውን የሞከሩት
ገዳዮች ለጊዜው ሊያመልጡ ቢችሉም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በአንድ አካባቢ ጥለውት የሄዱት መኪና ተገኝቷል። በመኪናው ውስጥ ካላሽን
ኮቭ መሳሪያዎች ጥይቶችና ፈንጅዎች የተገኙ መሆናቸውን ፖሊስ የገለጸ ሲሆን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ግድያውን ከሞከሩት ውስጥ ሁለቱ
በአንድ የገበያ ቦታ ውስጥ ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው ተዘግቧል።
Ø
ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት በማሊ ዋና ከተማ በባማኮ በአንድ ከፍተኛ ሆቴል ላይ
የተፈጸምውንና ለሃያ
ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነውን ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው ከሚጠረጠሩት ሰዎች መካከል ሁለቱን በቁጥጥር ስር አድርገናል
በማለት
የማሊ የጸጥታ ባለስልጣኖች ገለጸዋል። የተሰጠው መግለጫ ሁለት የማሊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች
በልዩ የጸጥታ ኃይሎች አማካይነት መያዛቸውን ከመግለጹ በስተቀር ስለማንነታቸውና ስለታሪካቸው የጠቀሰው ዝርዝር መረጃ የለም።
እነዚህን ሰዎች በመጠየቅ የሚገኘው ተጨማሪ መረጃ ጥቃቱን ለመፈጽም ምን እንዳነሳሳችወና እንዲሁም ተባባሪ የሆኑ ሌሎች ግለስቦችን
ለማወቅ ይቻላል በማለት መግለጫው ጨምሮ ገልጿል።
Ø
ከናይጄሪያ የነዳጅ አምራች ከተማ እስከ ሌጎስ ከተዘረጋውና 250 ኪሎ ሜትር ርዝመት ካለው
የነዳጅ ቱቦ ላይ ባለፈው ዓመት ብቻ ከ250 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግምት ያለው ነዳጅ በሌቦች እንደተዘረፈ ኩባንያው ጨምሮ
ገልጿል። የናይጀሪያ ብሄራዊ የነዳጅ ኮርፖሬሽን በጠቅላላው በዓመት ውስጥ የተዘረፈው ነዳጅ መጠን ግማሽ ቢሊዮን ሊትር የሚሆን
ነው ካለ በኋላ ይህም በናይጄሪያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ይፈጥራል ብሏል። በዚህ የነዳጅ ቱቦ አማካይነት በየቀኑ 35
ሚሊዮን ሊትር ወደጠቃሚው ለማድርስ የሚሞከር ቢሆንም በነዳጅ እጥረት ምክንያት ረዥም ሰልፎች በነዳጅ ጣቢያዎች ላይ እየታዩ
መሆናቸው ታውቋል።
ህዳር 16
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት
ሌሊት
በአዲስ
አበባ
መርካቶ
አካባቢ
የሚገኘውና
በተለምዶ
ጭድ
ተራ
ተብሎ
በሚታወቀው
ስፍራ
ባልታወቀ
ምክንያት
የተነሳው
እሳት
ተቀጣጥሎ
ከፍተኛ ግምት ያለውን
ንብረት
ያወደመ
መሆኑ
ታወቀ።
የእሳት
ቃጠሎ
በርካታ
ሱቆችንና
መደብሮችን
ማውደሙ
ሲታወቅ
በየቦታው
የነበሩት
የመጥረጊያ
ቁሳቁሶች
ቃጠሎውን
እንዳባባሱት
በቦታው
የነበሩ
ወገኖች
ይናገራሉ።
ከለሊቱ
አምስት
ሰዓት
ላይ
የተነሳውን
እሳት ለማጥፋት
አስራ
አራት
የእሳት
ማጥፊያ
መኪኖች
በማከታተል
ለሶስት
ሰዓት
ያህል ጥረት
ቢያደርጉም
ግምቱ
ያልታወቀ
ንብረት
በእሳቱ
የወደመ
መሆኑ
ታውቋል።
በሰው
ላይ
የደረሰ
አደጋ
ስለመኖሩ
ይህ
ዘገባ
እስከተጠናቀረበት
ድረስ
የደረሰ
መረጃ
የለም።
ከዚህ
ቀደም
በሙስና
የዘቀጡት
የወያኔ
ባለስልጣናት
የደሃውን
ንብረት
በተንኮል
ካቃጠሉ
በኋላ
ቦታውን
ለባለሃብት
በሊዝ
ቸብችበው
ኪሳቸውን
የሚያደልቡበት
ሁኔታ
በተከታታይ
የተከሰተ
በመሆኑ
በትናንተናው
ምሽት
እሳቱን
አስነስተው
ቦታውን
ያወደሙት
ባለስልጣኖቹ
ሳይሆኑ
አይቀሩም
የሚል
ጥርጣሬ
አለ።
Ø
በአዲስ አበባ ፖሊስ ሰራዊት ውስጥ
ከአንድ ሺ ሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ አባላት የስራ መልቀቂያ ጥያቄ በማቅረባቸው የተደናገጠው የወያኔ አስተዳደር ከትናንት ወዲያ
ህዳር 14 ቀን 2008 ዓም ለፖሊስ አባላት ሽልማት ሲሰጥ የነበረ መሆኑ ተነገረ። ሽልማቱ የተሰጠው ሁለት ሺ ስምንት መቶ
ለሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ሲሆን ከእነዚሁ ውስጥ አራቱ የኮሚሽነርነት ማዕረግ እንዲያገ ሲደረግ ሌሎቹ ደግሞ የሪባንና
የገንዘብ ስጦታ ተደርጎላቸዋል። በዚህ ስነስርዓት ላይ ዜጎችን ለመሰለል አንድ ለአምስት የተባለው አደረጃጀት ተጠናክሮ እንዲቀጥል
እንዲሁም የቤት ለቤት ኮሚኒቲ ሰርቪስ በሚል ዘይቤ ልዩ ልዩ መረጃዎች የሚሰበስቡበት ሁኔታ እንዲስፋፋ
መመሪያ መሰጠቱ ታውቋል።
Ø
በአፋር ለረጅም ጊዜ የወያኔ አገልጋይ ሆኖ ሕዝብን ሲበድልና ሲዘርፍ የነበረው መሀመድ አሊ ሴሮ ከክልል አስተዳዳሪ ስልጣኑ
የተነሳ መሆኑ ተነግሯል። ስልጣን አለቅም ብሎ አስቸግሮ የነበረው አሊሴሮ በወያኔ ግፊትና ማስፈራሪያ ስልጣኑን እንዲለቅ የተደረገ
ሲሆን በምትኩ ከዚህ በፊት የአካባቢውን የከሰል ንብርት በመዝረፍና በማዘረፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያካብተውና የአካባቢውን
የደህንነት ቢሮ በመምራት በንጽሃን ደም የተጨማለቀው ስዩም አሊ የተባለው ግለሰብ የአፋር ክልል ርዕሰ መስታደደር ተብሏል።
በየአመቱ ከአምስት
መቶ
ሺህ
ብር በላይ ወጭ በማውጣት ልጁን
በእንግሊዝ
አገር
ኪንግስተን
ከሚባለው
ትምህርት
ቤት
የሚያስተምረው
አወል
ረባ የተባለው ሌላው ግለሰብ
ደግሞ
ምክትል
ርእሰ
መስተዳድር
ሆኖ
የተሾመ መሆኑ ተገልጿል።
Ø
በቅርቡ የወያኔ ቡድን ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደውን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን
በመቃወም የአምቦና የአካባቢው ከተሞች ተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ታወቀ። ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች
እንደሚገልጹት በብዛት የተሰማሩት
ፖሊሶችና የጸጥታ ኃይሎች የተማሪዎችን የተቃውሞ ስልፍ ለመበተን የሚያስለቅስ ጢስና
ውሃ ተጠቅመዋል። በግጭቱ የተጎዱ ተማሪዎች ስለመኖሩ የታወቀ ነገር ባይኖርም የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በትምህርት ቤታችው
ውስጥ ታግተው መዋላችው ተነግሯል። ተቃውሞውን ያነሱት ወጣቶች የአዲስ አበባው ማስተር ፕላን አርሶ በከተማዋ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ
አደሮች ከመሬታቸው ላይ ስለሚያፈናቅል መሰረዝ አለበት የሚል መልእክት ሲያሰሙ የነበረ ሲሆን ይህ የወጣቶቹ ተቃውሞ
በሌሎችም ከተሞች ይዛመታል ተብሎ ተፈርቷል። ባለፈው ዓመት የወያኔ የአዲስ አበባ
የማስተር ፕላን እቅድ በመቃወም በተለያዩ ከተሞች በተነሱ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በርካታ ወጣቶችን
የገደሉ መሆናቸው ይታወሳል። የወያኔው ባለስልጣን አባይ ጸሐየም በአንድ ወቅት ማስተር ፕላኑን በግድ ተግባራዊ የታቀደ መሆኑን
በመጥቀስ መዛቱም አይዘነጋም።
Ø
በሱዳን
ህጋዊ
ባልሆነ መንገድ የሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች 3 ሚሊዮን የደረሰ መሆኑና ከዚህም ውስጥ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን
መሆናቸውን አንድ የሱዳን ከፍተኛ
የፖሊስ ባለስልጣን ገለጹ። ሌፍተናንት ጄኔራል አብዱልራሂም ሞሃመድ ሁሴን
የተባሉትና የካርቱም ግዛት አስተዳዳሪ የሆኑት ግለሰብ ይህን የተናገሩት በካርቱም አካባቢ የጸጥታና ችግርና እና የህገወጥ
አስተላላፊ
ወንጀሎችን ለመቆጣጠር በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ መሆኑ ታውቋል። የወያኔን አስከፊና አፋኝ አገዛዝ በመሸሽ በርካታ ኢትዮጵያውና
ወደ ሱዳን መሰደዳቸው የታወቀ ቢሆንም ኢትዮጵያውያኑ ሰደተኞች በሱዳን መንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በወያኔ ካድሬዎች ከፍተኛ
በደልና አፈና እየደረሰባችው መሆኑ ይታወቃል።
Ø
ይህ በእንዲህ እንዳለ ወያኔ እና የሱዳን መንግስት በሚቀጥለው ወር ላይ ወሰን
ለመካለል
ያቀዱ መሆናቸውን በመግለጽ ሱዳን ትሪቡን የተባለው ጋዜጣ በአምዱ ላይ አስፍሮ አውቷል። ጋዜጣው የድንበር ማካለሉ ተግባር
በሚቀጥለው ታህሳስ ወር እንደሚከናውን የገለጸ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ላይ ከወያኔ ጋር ለመነጋገር የሱዳኑ ምክትል ፕሬዚዳንት አዲስ
አበባ ገብተዋል ብሏል። ከዚህ በፊት ወያኔ ሰፋፊ የሆኑ የወሰን አካባቢዎችን ለሱዳን ለመስጠት መስማማቱን ተከትሎ ከፍተኛ ተቃውሞ
የተነሳ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በድንበር አካባቢም አርሶ አደሮች በትጥቅ ሲፋለሙ መቆየታቸው ይታወቃል።
Ø
በትናንትናው ዕለት የሮማው ጳጳስ ፍራንሲስ ኬኒያ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል
ተደርጎላቸዋል።
ለስድስት ቀናት የሚቆየው
የአፍሪካ ጉብኝታቸው ወደ ኡጋንዳ እና የመከከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚወስዳቸው
መሆኑ ተዘግቧል። በዛሬው
ቀንም ቁጥሩ 300 ሺ የሚገመት ሕዝብ በተገኘበት
በናይሮቢ
ዩነቨርስቲ የቅዳሴ ስነስርዓት አካሂደዋል። ቀደም ብሎ በዚህ ስነስርዓት ላይ 1.4 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ይገኛል ተብሎ የተገመተ
ቢሆን በነበረው ኃይለኛ ዝናም ምክንያት የህዝቡ ቁጥር ሊቀንስ ችሏል።
ከቅዳሴው ስነስርዓት ቀደም ብሎ ጳጳሱ በኬኒያ ከሚኖሩ የተለያዩ እምነት ተከታዮች
መሪዎች ባካሄዱት ስብሰባ ሃይማኖት የኃይል ምንጭ መሆን የሌለበት መሆኑን ገልጸው በተለያዩ
የእምነት ተከታዮች መካከል ውይይት ማካሄድና መግባባት ላይ መድረስ አስፈላጊ
መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም የእስልምናና የክርስትና ተከታዮች
በመካከላቸው መቻቻልንና መግባባትን ፈጥረው አገሪቱን ለመምራት ኃላፊነት መውሰድ
አለባቸው ብለዋል። በናይሮቢ ዩኒቨርስቲ ባደረጉት የቅዳሴ ስነስርዓት ማብቂያ ላይም ባድረግቱ የመጀመሪያውን ይፋ ንግግር የቤተሰብ
ኃላፊነትና ግዴታን በሚመለከት ሰፊ መንፈሳዊ ገለጻ ያደርጉ መሆናቸው ተነግሯል።፡
Ø
ቻይና በጂቡቲ ውስጥ ለወታደራዊ አገልግልት ሊውሉ የሚችሉ ስፍራዎችን ለማቋቋም
ከጂቡቲ መንግስት ጋር እየተደራደርች መሆኑን የቻይናው የመከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በዛሬው ዕለት ገልጿል። ቃል አቀባዩ
የቻይና ወታደራዊ ተቋም በአፍሪካ ውስጥ የሰላም አስከባሪ ግዳጅ እየተሰጠው የሚያከናውን መሆኑንና
ሆነ በህንድ ውቅያኖስ አካባቢ ሲካሄድ የቆየወን የመርከብ ጠለፋ ወንጀል
ለመከላከል
በሚደረገው ተግባር ላይ ተሳታፊ መሆኑን ጠቅሶ ጅቡቲ ውስጥ የሚመመሰረተው የቻይና ወታደራዊ አካል ይህንን የቻይና አለም አቀፍ
ወታደራዊ ተልዕኮ ለማስተባበር ይረዳል ብሏል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ድርድር መደረጉን ያመነ ሲሆን የሚቋቋመው
የወታደራዊ ጦር ሰፈር ነው በማለት አንዳንድ ክፍሎች የሚሰጡትን አስተያየት ግን ክዷል። ይህ የቻይና መግለጫ የተሰጠው ቻይና
በጂቡቲ ውስጥ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ለማቋቋም የአስር ዓመት ውል የፈረመች መሆኗንና
ተመሳሳይ ጦር ሰፈሮች በሌሎች ቦታዎችም ለማቋቋም እቅድ እንዳላት በመግለጽ አንድ
የአሜሪካ ወታደራዊ ባለስልጣን ያደረጉትን ገለጻ ተከትሎ ሲሆን ከጥቂት ጊዜ በፊትም
የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኦማር ገለህ በዚህ ጉዳይ ላይ ጂቡቲ ከቻይና ጋር ውይይት እያደረገች መሆኑን በመግለጽ ቻይናውያንን በደስታ
እንድሚቀበሉ መናገራቸው አይዘነጋም። ጂቡቱ ውስጥ ፈረንሳይ፤ አሜሪካ እና ጃፓን የጦር ሰፈሮች ያሏቸው መሆኑ ሲታወቅ የቻይና
መጨመር ወደፊት ምን ሊያስከትል እንደሚችል መገመት አልተቻለም።
ህዳር 15
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በአሩሲ
ከ27
ወረዳዎች
መካከል 13ቱ
ዘንድሮ
ለከፋ
የረኃብ
አደጋ
የተጋለጡ መሆናቸውና በቅርቡ በአካባቢው የሚኖሩ ተማሪዎች
ትምህርት አቁመው ወደ ሌሎች ከተሞች በመስደድ ላይ መሆናቸው ከስፍራው የሚደርሱን ዜናዎች ይገልጻሉ።
በአካባቢው ስድሳ ሺ የሚሆኑ ዜጎች በድርቁ ምክንያት በሞት አፋፍ ላይ የሚገኑ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ለሕዝብ ችግር ደንታ
የሌላቸው የወያኔ ባለስልጣናት ግን 15 ሺ የሚሆኑት ቀድሞውኑ ተረጅዎች ነበሩ በማለት እያላገጡ ናቸው።
በድርቁ
ምክንያት
ትምህርታቸውን
ለማቆም
የተገደዱት
ወጣቶች
ከአሩሲ
ወደ
ናዝሬት
የቀን
ስራ
ፍለጋ
በመፍለስ
ላይ
የሚገኙ ቢሆንም
ከናዝሬት
ምንጮች
ለማረጋገጥ
እንደተቻለው
ወጣቶቹ
የጠበቁትን
ስራ
እንደልብ
ባለማግኘታቸው ከመካከላቸው ብዙዎቹ
የጎዳና
ላይ
ልመና የጀመሩ
መሆናቸውን
ለማወቅ
ተችሏል። ከስፍራው የተገኘው ዜና አክሎ እንደገለጸው
በአርሲ
በሚገኙ
ሶስት
ወረዳዎች ውስጥ
በአመት
አንድ
ግዜ
ማር
በመሰብሰብ
በሚያገኙት ገቢ ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ዜጎች በድርቁ ምክንያት ከፍተኛ ችግር ውስጥ የገቡ መሆናቸው ታውቋል። የወያኔ ባለስልጣኖች
“በድርቅ አደጋ የሞተ የለም”፤ “እርዳታ የሚሰፈልጋቸው ቀድሞም ቢሆን የሚረዱ የነበሩ ናቸው”፤ “ለሚያስፈልጋቸው እርዳታ ሰጥተን
አዳርሰናል” ወዘተ… እያሉ ቢመጻደቁም እስካሁን ድረስ ለአንድ ሰው አስራሁለት ኪሎ ስንዴና ሁለት ሊትር ዘይት መሰጠቱና ይህም
ለአንድ ጊዜ ብቻ የተደረገ መሆኑን ከስፍራው የመጣው ዘገባ ያጋልጣል።
Ø
በተያያዘ ዜና በበምዕራብ እና በምስራቅ ሀረርጌ በድርቁ ምክንያት የተረጅው ቁጥር ሃምሳ
ከመቶ መጨመሩ ተነገረ። በምስራቅ ሀረርጌ እርዳታ እየተሰጣቸው ያለው ተረጅዎች ቁጥር 549 ሺ መሆኑን የወያኔ ባለስልጣኖች
የገለጹ ሲሆን ከአንድ ወር በኋላ ይኸው ቁጥር ወደ ዘጠኝ መቶ ሺ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። በምዕራብ ሀረርጌም የተረጅዎች ቁጥር
አሁን ካለበት 500 ሺ ተርጅዎች ወደ 720 ሺ ከፍ እንደሚል ተገልጿል። በእነዚህ አካባቢዎች ለተረጅዎች እየተሰጠ ያለው እርዳታ
በቂ አለመሆኑን በአንዳንድ አካባቢም ምንም ዓይነት እርዳታ እየተሰጠ እንዳልሆነ ነዋሪዎች ለዜና ምንጮች ገልጸዋል።
Ø
የአገራችንን ለም መሬት በገፍ በአነስተኛ ክፍያ በሊዝ ገዝተው ምርቱን
እንደልባቸው እያወጡ በመሸጥ ከፍተኛ ጥቅም ሲያገኙ የነበሩ የሳኡዲ ቱጃሮች ወንጀል
ሰርታችኋል በሚል ምክንያት የወያኔ ባለስልጣኖች ሀብታችንን ዘረፈው ከአገር እንድንወጣ አደረጉን በማለት ቅሬታ ያሰሙ መሆናቸውን
አረብ
ኒውስ የተባለውና በ ሳኡድ አረቢያ
በየቀኑ የሚታተመው ዕለታዊ ጋዜጣ በትናንትናው ዕትሙ በአምዱ ላይ አስፍሯል።
መሀመድ አልሸውሪ የተባለውና የተወሰኑ የሳኡዲ ቱጃሮችን አስተባበሮ በአፍሪካ በልዩ ልዮ ቦታዎች መዋዕለ ንዋይ በማፈሰስ ስራዎችን
እየሰራን ነው የሚል ግለሰብ በገለጸው መሰረት ቀደም ለወያኔ ባለስልጣኖች ገንዘብ በመስጠት በሊዝ መሬት ተቀብለው በእርሻ ምርት
ሲያመርቱ የነበሩና በተለያዩ የስራ ቦታዎች ላይ የተሰማሩ የሳኡዲ ቱጃሮች ወንጀል ፈጽመችኋል በሚል ክስ የወያኔ ባለስልጣኖች
በሊዝ ያገኙትን መሬት ሆነ የማምራቻ መሳሪውያዎቻቸውን
የወሰዱባቸው
መሆኑን የገለጸ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 50 ከመቶ የሚሆኑት በኢትዮጵያ በተለያዩ የስራ መስክ ላይ የተሰማሩት የሳኡዲ ባለሃብቶች
ንብረታችውን ትተው አገሪቷን ለቀው የወጡ መሆናቸውን ገልጿል። ባልሰሩት ስራ ወንጀል ፈጽማችኋል መባላቸው ያስፈራቸው በመሆኑ
ወደኢትዮጵያ የማይመለሱ መሆናቸውንም ገልጿል። ቱጃሮቹ ለሁለቱ አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮች ጉዳያቸውን ያመለከቱ ቢሆንም
እስካሁን መልስ አላገኙም በማለት ግለሰቡ ለጋዜጣው በሰጠው መግልጫ ገልጿል። ተፈጸመ የተባለው ወንጀል ምን እንደሆኑ ግለሰቡ
አልጠቀሰም። በወያኔ ባለስልጣኖችና በሳኡዲ ቱጃሮች መካከል የተፈጠረው የከረረ አለምግባባት ምን እንደሆን በውል ባይታወቅም ሌቦች
የሚጣሉት የሰረቁትን ሲካፈሉ ነው እንደሚባለው የወያኔ ባለስልጣኖች ለግልጥቅም ከሚያደርጉት መሯሯጥ በሳኡዲ ቱጃሮች ላይ
የወሰዱትን እርምጃ አይፈጽሙም
ማለት ግን አይቻልም።
Ø
የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ማክሰኞ ህዳር 14
ቀን 2008 ዓ..ም በፌስቡክ ባሰረጨው መልእክት ከፓርቲው ራሱን ያገለለ መሆኑንና ከእንግዲህ ወዲህ ራሱን እንጅ ማንንም ፓርቲ
እንደማይወክል ገልጿል። የ27 ዓመት ወጣት የሆነው ዮናታን እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው ምክንያት ምን እንደሆነ ያልገለጸ ሲሆን
ይህንን ጉዳይ በሚመለከትም ከፓርቲው ኃላፊዎች እስካሁን የተሰጠ መግለጫ የለም።
Ø
በትናንትናው ዕለት በቱርክ ተመቶ የወደቀውን የሩሲያ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ሲያበሩ
ከነበሩትና በፓራሹት ከወረዱት አብራሪዎች መካከል አንደኛው መገደሉን በትናንትናው ዘገባ የተገለጸ ሲሆን የሩሲያ ልዩ ኃይሎች
የአስራ ሁለት ሰዓት ፍለጋ ካደረጉ በኋላ ሁለተኛውን አብራሪ በደህና በህይወት ያገኙት መሆናቸውን የሩሲያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰዓት አብራሪው ሶሪያ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ እንደሚገኝም ተገልጿል። የህይወት ማዳኛ ጃንጥላን በመጠቀም
ከአውሮፕላኑ ላይ ሲወርድ
በአማጽያን ኃይሎች በተተኮስ ጥይት ተመቶ የወደቀው የሁለተኛው አብራሪ አስከሬን የት እንደደረሰ አይታወቅም። ቱርክ አውሮፕላኑን
የጣለችው በአየር ክልሏ ውስጥ በመብረሩና ነው በማለት የቱርክ ፕሬዚዳንት የተናገሩ ሲሆን ውጥረቱ እንዲባባስ የማይፈልጉ
መሆናቸውን ገልጸዋል። የሩሲያው ፕሬዚዳንት አውሮፕላኑ የቱርክን የአየር ክልል ያልጣሰ መሆኑን ገልጸው የቱርክ እርምጃ ጀርባችንን
በጩቤ እንደመውጋት የሚቆጠር በመሆኑ በሩሲያና በቱርክ መካከል ያለው ግኝኙነት ከፍተኛ ችግር ይገጥመዋል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት
በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ግንኙነት ከፍተኛ የውጥረት ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን ሩሲያ አንድ የሚሳየል ጫኝ መርከብ በላታኪያ
ወደብ አንቀሳቅሳ
ሶሪያ ውስጥ በሚገኝ የሩሲያ ወታደራዊ ካምፕ ላይ አደጋ ሊጥል ይችላል ተብሎ በሚገመትና
በአየር ላይ ባለ ማንኛውም
ተንቀሳቅሽ አካል በረጅም እርቀት ሚሳየል እንዲመታ አዛለች። የሩሲያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሲያ የምትወስደውን የበቀል እርምጃ
ከዘረዘሩ በኋላ የቱርክ ባለስልጣኖች አይሲስ ከሚባለው አሸባሪ ቡድን ጋር በነዳጅ ዘይት ንግድ ላይ የተመሰረተ የጋራ ጥቅም
አላቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቱርክ ኩባንያዎች ሩሲያ ውስጥ ከመስራት እንዲታገዱ ለማደረግ እየተዘጋጀች መሆኑን ገልጸው
ቱርክ ከቱሪስት ገቢ የምታገኘውን ገንዘብ ለመቀነስ የሩሲያ ዜጎች ወደቱርክ እንዳይሄዱ ምክር ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። በቱርክ በኩል
ወደ አውሮፓ ሊዘረጋ ታስቦ የነበረውም የጋዝ ቧንቧ የሚሰረዝ መሆኑንም ተናገረዋል። የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በአሁኑ
ወቅት ቱርክ የሩሲያን አውሮፓላን መትቶ ለመጣል የወሰደችው እርምጃ በቅድሚያ ያሰበችበትና
የተዘጋጀችበት መሆኑን የሚያሳይ ማስርጃ በዝርዝር አውጥቷል።
የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከለከያ ድርጅት (ኔቶ) የቱርክን አቋም ተቀብሎ ከቱርክ
ጎን የሚቆም መሆኑ የገለጸ ሲሆን የሩሲያ አውሮፕላን በመመታቱና ፓይለቱም በመገደሉ የሀዘን ስሜት አለመግለጹ ለሩሲያ ያለውን
የጠላትነት ስሜት የሚገልጽ ነው በማለት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገረዋል።
የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት እና አሜሪካ ሀሉቱ አገሮች
ችግሩን
ከማባባስ እንዲታቀቡ ጠይቀዋል።
Ø
በቱኒዚያ ዋና ከተማ ቱኒስ ውስጥ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደሮች ይጓጓዙበት የነበረ
አንድ አውቶቡስ ድንገት በፈነዳ ፈንጅ ጉዳት ደርሶበት በውስጡ የነበሩ ቢያንስ 13 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። ፈንጅው የፈነዳው
አውቶቡሱ ተሳፋሪዎችን ሊያወርድ በቆመበት ጊዜ መሆኑ ታውቋል።
በደረሰው
አደጋ ምክንያት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለሰላሳ ቀን የሚቆይ የሰዓት እላፊ አዋጅ ያወጁ መሆናቸው ተነግሯል። ለዚህ ጥቃት ኃላፊነቱን
የወሰደ ወገን ባይኖርም ቱኒዚያ አይሲስ በተባለው አሸባሪ ቡድን በተደጋጋሚ ስትጠቃ የቆየች መሆኑ ይታወቃል። በኢራክና በሶሪያ
የአሸባሪው የአይሲስ ቡድን አባሎች ሆነው ከሚዋግጉት መካከል ሶስት ሺ የሚሆኑት ከቱኒዚያ መሄዳቸው ይነገራል።
Ø
የሱማሊያ የባህር መርከብ
ጠላፊዎች በኢራንና በታይ ሁለት የአሳ አጥማጅ መርከቦች
በወሰዱት ጥቃት የታይላንዱ መርከብ ሲያመለጥ
ጠላፊዎቹ
የኢራኑን መርከብ ይዘው 15 የሚሆኑ የመርከቡ ሰራተኞችን ያገቱ መሆናቸው ታውቋል። ጠላፊዎቹ ሰዎችን ለማስፈታት የገንዘብ ክፍያ
የሚጠይቁ ሲሆን አሁን ለያዟችው ሰዎች ምን ያህል ገንዘብ እንደጠየቁ አልታወቅም። ከአራት ዓመት በፊት በሱማሊያ ውስጥ በተመሳሳይ
የመርከብ ጠለፋ የታገቱት ሰዎች ቁጥር 700 ደርሶ የነበረ ሲሆን
የመርከቦችን
ደህንነት ለመጠበቅ የተለያዩ አገሮች በወሰዱት
እርምጃዎች ምክንያት ቁጥሩ በጣም ቀንሶ እስከ 56 ደርሶ እንደነበር ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት ህገ ወጥ የሆኑ አሳ የማጥመድ ስራዎች በጣም እየተስፋፉ ያሉበት ሁኔታ የተስተዋለ ሲሆን ለአሁኑም የመርከብ ጠላፋ
ምክንያት የሆነው ይኸው ህገወጥ የሆነ አሳ የማጥመድ ተግባር የሶማሊያ አሳ አጥማጆችን ስላስቆጣ ነው የሚል ምክንያት እየተሰጠ
ነው።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን አንድ ሺ አንድ መቶ የሚሆኑ
ተጨማሪ የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ወደ ደቡብ ሱዳን እንዲላኩ የጸጥታው ምክር ቤትን የጠየቁ መሆናቸው ተነገረ።
ሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች ያደረጉትን የስምምነት ቃል የማይጠብቁ መሆናቸው የታወቀ ከመሆኑ በላይ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በመጣሱ
ምክንያት በርካታ
ሰላማዊ ሰዎች ጉዳት ላይ በመወደቃቸው የሰላም አስከባሪ ኃይል ቁጥሩን መጨመር አማራጭ የሌለው
ነው ብለዋል። 500 ወታደሮችና 600 ፖሊሲች ከ13 ሄሊኮብተሮችና የመጓጓዣ አውሮፕላን ጋር ወደቦታው እንዲላኩ ጠይቀዋል።
በቤንቱ የሚገኘውና 100 ሺ ስደተኞችን የሚያስተናግደው የሜዳ የህክምና ጣቢያ ቁሳቁስና የሰው ኃይል ተጨምሮለት አገልጎቱን ጨምሮ
እንዲያበርክት ጥያቄ አቅርበዋል።
ህዳር 14
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
አንድ የሩሲያ ኤስ 24 የውጊያ አውሮፕላን በቱርክ የመከላከያ ኃይል ተመቶ መውደቁና
አብራሪዎቹ ከአውሮፕላን ውስጥ በፓራሹት ለመውጣት የቻሉ መሆናቸው ተነገረ። የቱርክ ባለስልጣኖች አውሮፕላኑ የቱርክና ግዛት ጥሶ
በመግባቱ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ከተሰጠው በኋላ በቱርክ ኤፍ 16 የጦር አውሮፕላን ተመቶ የወደቀ መሆኑን ገልጸዋል። የሩሲያ
ፕሬዚዳንት ፑቲን አውሮፕላኑ በሶሪያ የአየር ክልል ውስጥ
በ6
ሺ ሜትር ከፍታና ከቱርክ ድንበት 1 ኪሎሜትር ርቆ
ሲበር
ከቱርክ
ኤፍ 16 አውሮፓላን በተተኮስ የየአር በአየር ተመዝገዛጊ ሚሳየል ተመቶ የወደቀ መሆኑን ገልጸዋል። አውሮፕላኑ የወደቀውም ከቱርክ
ወሰን አራት ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኘው የሶሪያ ግዛት ውስጥ ነው ብለዋል። አውሮፓላኑ ለቱርክ ጸጥታ የማያሰጋ ሆኖ ሳለ በቱርክ
የጦር አውሮፓላን ተመትቶ መውደቁ ሩሲያ በአሸባሪዎች ላይ እርምጃ እየወስደች እያለች ወዳጅ ከምትባለው ከጀርባዋ ተመታለች
ብለዋል። ቱርክም ይህንን በማድረጓ ከአሸባሪዎች ጋር ተባባሪ ሆናለች ብለዋል። ፑቲን የወደቀው አውሮፕላን ኢላማ አድርጎ ሲያጠቃ
የነበረው ላቲኪያ በሚባለው ብዙዎቹ ከሩሲያ የመጡትንና በሶሪያ ግዛት ውስጥ የሚንቀሱትን
አሸባሪዎች
ነበር ብለዋል። በእነዚህ አሸባሪዎች አስተናጋጅነት ከአካባቢው ነዳጅ እየተወሰደ ወደ ለቱርክ እንደሚሸጥና ሩሲያ ታውቅ ነበርና
ይህንን
በቢሊዮን የሚቆጠረውን የአይሲስን የገቢ ምንጭ ለማድረቅ የተወሰደ እርምጃ ነበር ብለዋል።
አይሲስ ተጠናክሮ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውና በርካታ ሰዎችን በየቦታው ለመግደል የቻለው በዚህ መንገድ
በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢ በማግኘቱ ነው ብለዋል። ሚስተር ፑቲን ሩሲያ በሶሪያ ላይ
እያካሄደች ያለውን ጥቃት ለማስተባበር ከአሜሪካ ጋር ከተስማማች በኋላ በአሜሪካ በሚመራው የአየር ጥቃት ውስጥ ተካፋይ ነኝ
የምትለው ቱርክ የወሰደችው እርምጃ እጅግ ያሳዘናቸው መሆኑን ገልጸው ሁኔታው በሩሲያና በቱርክ ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ችግር
ሊፈጥር ይችላል ብለዋል። ሩሲያ
በሶሪያ የአየር ጥቃት ከጀመረች ጀምሮ ይህ ዓይነት አደጋ ሲፈጠር የመጀመሪያው ነው።
ከሁለቱ
የአውሮፓላን አብራሪዎች መካከል አንደኛው በፓራሹት እየወረደ እያለ በአማጽያኑ ተመቶ የተገደለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ሁለተኛው
በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳለ አልታወቀም።
Ø
በፓሪስ ከተማ ሰራተኞች ከአንድ የቆሻሻ ማጠራቂሚያ በርሚል ውስጥ አግኘተው ለፖሊስ
ያስረከቡትንና አሸባሪዎች
ሲጠቀሙበት ነበር ተብሎ የተጠረጠረውን የቦምብ ትጥቅ የጸጥታ ኃይሎች እየመረመሩ መሆኑ ታወቀ። የተገኘው የቦምብ ትጥቅ ባለፈው
ሳምንት በፓሪስ በተለያዩ ቦታዎች ጉዳይ ያደረሱት አሸባሪዎች ከተጠቀሙባቸው ትጥቆች ጋር
ተመሳሳይነት ያለው ሲሆን የተገኘውም የፓሪሱን ጥቃት በአቀነባባሪነት የመራውና
አሁን እየተፈለገ ያለው ሳላህ አብዱሰላም የተባለው ግለስብ በመጨረሻ ወቅት የስልክ ልውውጥ ሲያደርግበት ነበር ከተባለ ቦታ ላይ
ነው። ቀደም ብሎ የተገኘው የሳላህ አብዱሰላም የሞባይል ስልክ አብዱሰላም ከዚህ ቦታ ላይ የስልክ ልውውጥ ያደረገ መሆኑን
የሚስረዳ መረጃ የያዘ ሲሆን አብዱል ሰላም ትጥቁን ቁሻሻ ማጠረቀሚያ ገንዳ ውስጥ የወረወረው ወይ አልሰራ ብሎት ነው አለዚያም
በመጨረሻ
ጊዜ የውሳኔ ለውጥ አድርጎ ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ አለ።
Ø
በሱዳን መንግስትና ተጻራሪ በሆኑት አማጽያን መካከል ለአንድ ሳምንት ያህል በአዲስ አበባ
ሲካሄድ የቆየው የስለም ውይይት ያለስምምነት የተበተነ መሆኑ ተነገረ። በዳርፉር የሚገኙ የተለያዩ የአማጽያን ቡድን እና ኤስ ፒ
ኤል ኤም ኖርዝ (SPLM N) ቡድን ተወካዮችና የሱዳን መንግስት ባለስልጣኖች መካከል በአፍሪካ ህብረት ተወካይ
በቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በሚስተር ታቦ ኢምቤኪ ሊቀ መንበርነት የእርቅ
ውይይት ሲካሄድ የቆየ መሆኑ ታውቋል። አደራዳሪዎቹ ቢያንስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሊደርሱ ይችላሉ የሚል ተስፋ ይዘው የገቡ
ቢሆንም በዚህም ላይ ስምምነት ሊደርስ ባለመቻሉ ለጊዜው እንዲቋረጥ የተደረገ መሆኑ ተገልጿል። የእርቁ ስብስባ ወደፊት ይቀጥላል
የተባለ ቢሆንም መቸ ሊሆን እንደሚችል ግን አልተገለጸም፡፤
Ø
በግብጽ ሰሜናዊ የሲና ባህረሰላጤ በኤል አሪሽ ከተማ ስዊስ ኢን በሚባል ሆቴል
ውስጥ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎችና አንድ መሳሪያ የያዘ አሸባሪ ባካሄዱት የተቀነባረ
ጥቃት አራት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች አስራ ሁለት ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸው ተነገሯል። ከተገደሉት መካከል አንድ ዳኛ ሁለት ፖሊሶችና
አንድ ሲቪል የሚገኙበት ሲሆን ከቆሰሉት ውስጥ ደግሞ ሁለት ዳኞች ስምንት ወታደሮችና ምልምሎች እንዲሁም ሁለት ሲቪሎች አሉበት
ተብሏል። ከሟቾቹና
ከቁስለኞቹ ውስጥ አብዛኞቹ ባለፈው እሁድና ሰኞ በአካባቢው ሲካሄድ የነበረውን የምክር ቤት የምርጫ ሂደት ሲቆጣጠሩና ሲታዘቡ
የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። በሆቴሉ ላይ የተደረገው የጥቃት እርምጃ የተቀነባበረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን አንደኛው አጥፍቶ ጠፊ
መኪና ላይ ሆኖ ቦምቡን ካፈነዳ በኋላ ሌላኛው በወገቡ ላይ የታጠቀውን ቦምብ በሆቴሉ መግቢያ ላይ ያፈነዳ መሆኑና መሳሪያ የያዘው
አሸባሪ በግርግሩ ሆቴል ክፍሎች ውስጥ በመግባት ዳኛውንና ሌሎችን ሊገድል የቻለ መሆኑ ተነግረዋል።፡
ህዳር 13
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ባለፈው ሳምንት በዋና ከተማዋ ባማኮ ውስጥ በሚገኘው የራዲሰን ሆቴል የተፈጸመውንና
የ29
ሰዎች ህይወትን ያጠፋውን የአሸባሪዎች ጥቃት ለማስታወስ ማሊ የሶስት ቀና ብሔራዊ ሀዘን ያወጀች መሆኑ ተነገረ። ሴኒጋል
ሞሪታኒያና ጊኒም ሀዘናቸውን በመግለጽ ትብብራቸውን አሳይተዋል። አርብ ዕለት ለተካሄደው ጥቃትና ግድያ ሁለት የተለያዩ አሸባሪ
ድርጅቶች ኃላፊነቱን ወስደዋል። ከእነዚህ መካከል አንደኛው “በእስላማዊ ማግረብ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ” የተባለው ቡድን ሲሆን
ሌላኛው ደግሞ “ የማሲና ነጻ አውጭ ግምባር” የተባለው ነው።
አርብ
ዕለት በሆቴሉ ውስጥ የታገቱትን የታገቱትን ሰዎች ለማስፈታት የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ ሁለት አሸባሪዎች መገደላቸው
የተዘገበ ሲሆን ምን ያህል ሰዎች እንደተሳተፉ እና ከየት ከየት እንደመጡ ለማወቅ ምርመራ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ከአንድ የጸጥታ
ምንጭ በተገኘው መረጃ በሆቴሉ ጥቃት ወቅት የተገደሉት ሁለቱ ስዎች እንግሊዘኛ የሚናገሩ መሆናቸው ተደርሶበታል። የማሊ ፖሊስ
ስለግድያው የሚያደርገውን ምርመራ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በቅርብ ቀን ውስጥ በህይወት የሚገኙት ወንጀለኞች እና ተባባሪዎቻቸው
ለፍርድ ይቀርባሉ የሚል መግለጫ ሰጥቷል።
Ø
በሊቢያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዮ መልእክተኛ በመሆን በቅርብ የተሾሙት
ጀርመናዊው ሚስተር ማርቲን ኮብለር ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ በቶብሩክና በትሪፖሊ ከተሞች
ተጻራሪ ሆነው የተቋቋሙትን ሁለቱን
የሊቢያ
አስተዳድሮች አባላትን አነገጋረዋል። ሚስተር ኮብለር በየራሳቸው መንግስት ነን የሚሉትን የሁለቱንም አስተዳደሮች አባላትን
ካነገገሩ
በኋላ በቶብሩክና
በትሪፖሊ በሰጧቸው ጋዜጣዊ መግለጫዎች የሁለቱም ተጻራሪ ቡድኖች ባለስልጣኖች በተመድ የቀረበውን የእርቅ ሀሳብ እንዲቀበሉ
ጠይቀዋል። ከዚህ ቀደም የተደረገው ድርድርና ስምምነት ሊፈርስም ሆነ ሊሻሻል የማይችል መሆኑን ገልጸው በሁለቱም ዘንድ የሚገኙት
የምክር አባላት አቋማቸውን መርመረው እንደገና ድምጽ እንዲሰጡበት ተማጽነዋል። አገሪቱ ካለችበት የኢኮኖሚ ችግር ልትወጣ
የምትችለውና ወደፊትም በእድገት ጎዳና ላይ ልትጓዝ የምትችለው ሁሉም ስምምነቱን ሲቀበል ነው ብለዋል። ቀደም ብለው የነበሩትና
ስራቸውን የለቀቁት የተመድ ልዩ መልከተኛ በርናርዲኖ ሊዮን ለረጅም ጊዜ ሁለቱን ተጻራሪ ኃይሎች አደራድረው ያቀረቡት የእርቅ
ሀሳብ ሁለቱም ስልጣን
በጋራ የሚካፈለቡትና አገሪቱን በበላይነት የሚመራ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አምስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችና ሶስት ከፍተኛ
ሚኒስትሮች የያያዘ
የዘጠኝ ሰዎች የፕሬዚዳንት ካውንስል እንዲቋቋም የሚል ሲሆን
ረቂቅ
ሀሳቡ በሁለቱም በኩል ውድቅ መደረጉ የሚታወስ ነው።
Ø
የሲናን
ባህረ
ሰላጤ ወደ እስራኤል ሲሄዱ የነበሩ ስድስት ሱዳናውያን ተግድለው ሬሳቸው የተገኘ
መሆኑ ታውቋል። ሌሎች አስራ አንድ የሚሆኑ የስዳን ዜጎች ወሰኑን ሊያቋርጡ ሲሞክሩ በጥይት የቆሰሉ መሆናቸውም ተዘግቧል። ሰዎቹ
እንዴት እንደሞቱና ማን እንደገደላቸው እስካሁን ባለው ምርመራ አልታወቀም ተብሏል። የሲና ባህረ ሰላጤ የተባለው ቦታ የግብጹን
ፕሬዚዳንት ሲሲን መንግስት የሚቃወሙ አማጽያን የሚንቀሳቀሱበት መሆኑ ግልጽ ቢሆንም ቀደም ብሎ ባህረ ሰላጤን አቋርጠው
ወደ እስራኤል ለመግባት ጥረታ ሲያደርጉ የነበሩ ስደተኞች በግብጽ መንግስት
የወሰን
ጠባቂ ወታደሮች መገደላቸው ይታወሳል።
Ø
እሁድ ጠዋት ማይዱጉሪ በተባለችውና በ ሰሜናዊ ምስራቅ ናይጄሪያ በምትገኘው ከተማ ውስጥ
የቦኮ ሃራምን ጥቃት ሸሸተው የመጡ ስምንት ሰዎች በአንዲት አጥፍቶ ጠፊ በፈንዳ
ቦምብ የተገደሉ መሆናቸው ከአካባቢው ከተገኘ ዜና ማወቅ ተችሏል።
የተገደሉት ሰዎች የመጡት ዲክዋ ከተባለችው ሌላ አነስተኛ ከተማ
ሲሆን
አብዛኞቹ ሴቶችና ህጻናት
እንደሚገኙበት ታውቋል።
ሰዎቹ በከተማዋ ዳርቻ ላይ በሚገኝ የፍተሻ ጣቢያ ላይ እንደደረሱ አንዲት የሃያ
አመት ልጅአገረድ ከሰዎቹ ጋር በመቀላቀል የታጠቀችውን ቦምብ በማፈንዳት ራሷን ከመግደሏ በተጫማሪ ሌሎች ስምንት ሰዎችን
ለመግደልና
ሰባት የሚሆኑትን ለማቁሰል ችላለች።
ዲክዋ ባለፈው ዓመት ሃምሌ ወር ውስጥ የመንግስት ወታደሮች
ከቦኮሃራም
ቁጥጥር ነጻ ያደረጓት ከተማ ስትሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የቦካ ሃራምን ጥቃት ሸሽተው በመጡ የአካባቢው ሰዎች ስትጨናነቅ
ቆይታለች። ከተማዋ ውስጥ የምግብና የሌሎች ቁሳቁሶች እጥረት በመከሰቱ አንዳንድ ሰዎች ከተማዋን እየለቀቁ ወደ ማይዱጉሪ ከተማ
ለመሰደድ
የተገደዱ መሆናቸው ታውቋል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ቅዳሜ ዕለት በካሜሩን ሰሜናዊ ግዛት ጥቃት ፈጽመው አራት ሴቶች ልጆችን
የገደሉ ሲሆን በቻድ እና በናይጀርም ተመሳሳይ ጥቃት ፈጽመዋል።
ህዳር 11
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
አሸባሪዎችን እናድናለን በሚል ምክንያት የወያኔ ወታደሮች በሰሜናዊ ኬኒያ መርሳቤት በሚባለው
ወረዳ ውስጥ
ገብተው ሶስት የኬኒያ ፖሊሶችን የገደሉ መሆናቸውን የኬኒያ ፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል ። የወያኔ
ወታደሮች
የኬኒንያን ድንበር ጥሰው በመግባት የኦነግ ታጣቂዎች
ተደብቀውበታል ብለው የጠረጠሩትን አንድ የኬኒያ መንደር ከበው እርምጃ ለመውሰድ
ሞክረዋል። መንድሯ በወያኔ ወታደሮች መከበቧ የተነገራቸው የኬኒያ ፖሊሶች የጸጥታ ሁኔታውን ለመቆጣጠር
በወታደራዊ
መኪና ተጭነው ወደቦታው ሲመጡ በወያኔ ወታደሮች የደፈጣ ተኩስ ከፍተውባቸው የኬኒያ ፖሊስችን የገደሉ መሆናቸውና
ሌሌች አምስት የሚሆኑት ደግሞ ተበታትነው እስካሁን ያልተገኙ መሆናቸው ተነግሯል።
የኬኒያ መንግስት በወያኔ ላይ የቅሬታ ክስ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
Ø
ከፓሪስ ግድያ ተመሳሳይ በሆነ መንገድ በርከት ያሉ ሰዎች በተለያዩ ቦታዎች ግድያ ለመፈጸም
ተዘጋጅተዋል
የሚል የታመነ መረጃ ደርሶናለ በማለት የቤልጅም ባለስልጣኖች የአገሪቱን በተለይም የዋና
ከተማዋን የብራስልስን የጸጥታ ጥበቃ መጠን የመጨረሻው ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንዲሆን ያደረጉ መሆናቸው ተነግሯል። በአሁኑ ወቅት
እየተፈለገ ያለውና የፓሪሱን ግድያ በመሪነት አቀነባብሯል ተብሎ የሚነገርለ ሳላህ አብዱሰላም
ቤልጅም
ገብቷል የሚል መረጃ ስለደረሰ ግለሰቡን የማደን አሰሳውም ተጠናክሮ ቀጥሏል። እስከ ሚቀጥለው ሰኞ ድረስ የምድር ውስጥ ባቡር
መገልገያዎች ዝግ እንዲሆኑ የተደረገ ሲሆን በርካታ ሰው የሚሰሰብስባቸው ትልልቅ ስታዲዮሞች የሙዚቃና የቲያትር ቦታዎች ወዘተ..
ዝግ እንዲሆኑ ተደርጓል። ዜጎችም ወደ እነዚህ ቦታዎችና እንዲሁም ወደ ትላልቅ የገበያ ቦታዎች እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።
በርካታ
ቁጥር ያላቸው የጸጥታ
ኃይል አባላትም በከተማዋ እንዲሰማሩ ተደርጓል። እሁድ ከሰዓት በኋላ ባለስልጣኖቹ ተሰብስበው የጸጥታውን ሁኔታ የሚገመግሙ
መሆናቸውም ታውቋል።
Ø
በተያያዘ ዜና የቱርክ ፖሊስ አንድ የቤልጅየም ዜግነት ያለው ሞሮካዊ ሰው በፓሪሱ ግድያ ላይ
ተሳትፏል
ከሚል ጥርጣሬ በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑን የቱርክ የዜና ምንጮች ገልጸዋል።
የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም በትናንትናው ዕለት ባደረገው ስብሰባ በፈረንሳይ መንግስት የቀረበውና ረቂቅና ሁሉም
አባል አገሮች በአይሲስ ላይ የሚያደርጉትን ዘመቻ አጠናክረው እንዲቀጥሉ
የሚጠይቀውን ረቂቅ ውሳኔ በሙሉ ድምጽ ደግፎ ያጸደቀው መሆኑ ታውቋል።
Ø
ትናንት በማሊ ዋና ከተማ በባማኮ በራዲሰን ሆቴል ላይ አሸባሪዎች በፈጸሙት ጥቃት 19 ሰዎች
ሲሞቱ የታገቱት በሙሉ የተፈቱ መሆኑ ተነግሯል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል ሶስት ቻይናዎች፤ እንድ የቤልጀም ተወላጅ አንድ
አሜሪካዊና የተወሰኑ ሩሲያውያን የሚገኙበት መሆኑን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የታገቱት ሰዎች ለማስፈታት የማሊ ልዩ የጸጥታ ኃይል
ልዩ ጥረት ያደረገ ሲሆን በከተማዋ
የነበሩ የፍረንሳይ እና የአሜሪካ የጸጥታ ኃይሎች ተባብረዋል ተብሏል። ምን ያህል አሸባሪዎች በጥቃቱ ላይ እንደተሳተፉ በግልጽ
ያልተነገረ ሲሆን ሁለት አሸባሪዎች የሞቱ መሆናቸው ተገልጿል። በጥቃቱ መሳተፋቸውና አለመሳተፋቸው ያልተገለጸ ሶስት ተጠርጣሪዎች
እየተፈለጉ መሆናቸውን ባለስልጣኖቹ ተናግረዋል።
Ø
ላይቤሪያ ከኢቦላ ነጻ መሆኗን የሚገልጽ ምስክር ወረቀት ከዓለም የጠና ድርጅት ባገኘች በሶስት
ወር ጊዜ ውስጥ ሶስት የኢቦላ ታማሚዎች የተገኙ መሆኑ ተገለጸ። ከህመምተኞቹ መካከል አንዱ የአስር አመት ልጅ የሆነው ሶስቱም
ታማሚዎች የሚኖሩት በዋና ከተማዋ ዳርቻ በሆነ ስፍራ ነው። ሰዎቹ ከህብረተሰቡ በተነጠለ ቦታ ተቀምጠው ህክምና እንዲወስዱ
ተደርጓል። የኢቦላ በሽታ ከተከሰተ ጀምሮ በላይቤሪያ 10 ሺ የሚሆኑ የኢቦላ በሽተኞች ህክምና የተደረገላቸው ሲሆን 4 ሺ የሚሆኑ
ደግሞ በበሽታው ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ ይታወቃል። ከጥቂት ቀናት በፊት ጊኒና ሲየራ ሊዮን ከኢቦላ ነጻ ናቸው በመባላቸው
ይታወሳል። ባለፉቱ ሁለት አመታት በምዕራብ አፍሪካ አካባቢው በበሽታው
ከ11 ሺ ሰው በላይ ህይወቱን ያጣ መሆኑ ሲታወቅ ከሞቱት ውስጥ አብዛኖቹ
የላይቤሪያ የጊኒና የሴየራ ሊዮን ዜጎች ናቸው ።
ህዳር 10
ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በማሊ ዋና ከተማ ባማኮ ራዲሰን በሚባለው ትልቅ የመዝናኚያ ሆቴል ውስጥ ማንነታቸው
ያልታወቀና ቁጥራቸው ከ10 እስከ አስራ ሶስት የሚገመት ታጣቂዎች የሆቴሉን በር ጥሰው ገብተው ተኩስ የከፈቱ መሆናቸውና
170 የሚሆኑ ሰዎችን ያገቱ መሆናቸው ተነገሯል። ከታገቱት መካከል 30 የሚሆኑት
የሆቴሉ ስራተኞች ሲሆኑ 140 የሚሆኑት ደግሞ በሆቴሉ
ያረፉ እንግዶች ነበሩ። ታጣቂዎቹ ወደ ሆቴሉ
እየተኮሱ ሲገቡ “አላህ ወ አክበር” “ አምላክ ትልቅ ነው” የሚል ቃል በአረቢኛ
እያሰሙ የነበረ ሲሆን በመጀሪያ ወቅቶች ከቁራን
ውስጥ አንዳንድ ጥቅሶችን መናገር የቻሉትን
የለቀቁ
መሆናቸው ተዘግቧል።
የማሌ ጸጥታ ኃይሎች በአሜሪካንና በፈረንሳይ ልዩ ኃይሎች ታጅበው በወሰዱት እርምጃ የታገቱት የተፈቱ ቢሆንም 27 ሰዎች
መገደላቸው ተገልጿል። የእስላማዊ ማግርብ አልቃይዳ የተባለው ቡድን ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። የዛሬ ሶስት ዓመት ሰሜናዊ የማሊ
ግዛት የአልቃይዳ ጋር ግንኙነት አለው ከሚባሉ የአክራሪ እስላማውያን ቁጥጥር ስር
ለረጅም ጊዜ የቆየ ሲሆን በፈረንሳይ ወታደሮች እርዳታ አማጽያኑ ከአካባቢው
ተጠርገው የወጡ መሆናችው ይታወሳል።
Ø
በየመን በአረቢያ ባህረ ሰላጤ የአልቃይዳ ቅርንጫ የተባለው ቡድን ሃድራማውት በተባለ
ግዛት ውስጥ የሚገኘውን አንድ የመንግስት ውታደራዊ ካምፕ የሆነን ቦታ ያጠቃ መሆኑ የተነገረ ሲሆን በተደረገው የተኩስ ልውውጥ
ከአልቃይዳ አባላት 14 ሰዎች ሲገደሉ 15 ወታደሮች የተገደሉ መሆናቸው ተገልጿል። ጥቃቱ የተጅመረው የቡድኑ አባል የሆነ ግለሰብ
መኪና ውስጥ ሆኖ ራሱንም ጭምር የገደለውን ቦምብ ካፈነዳ በኋላ ሲሆን አከታትለው ከ 25 እስከ 30 የሚጠጉ ታጣቂዎች የእሩምታ
ተኩስ በመክፈት ካምፑን ሊወሩ ችለዋል። የየመን የእርስ በርስ ጦርነት ሲጀመር ከአገሪቷ ወታደሮች መካከል ከፊሉ ሁቲዎችንና
የቀድሞ ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳለህን መደገፋቸውና ከፊሉ ደግሞ የአሁኑን ፕሬዚዳንት ሃዲን ደግፈው
መቆማቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን በአልቃይዳ ጥቃት የደረሰበት ጦር የፕሬዚዳንት ሃዲ
ደጋፊ መሆኑ ታውቋል ። የየመኑ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ ዋና ጠላት አድርጎ እየተዋጋ ያለው
ከሁቲዎች
ጋር መሆኑ ግልጽ በሆነበት ሁኔታና የሳኡዲ ጥምር ኃይልና ይኸው ቡድን በሁቲዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የድብቅ ስምምነት
አድርገዋል እየተባለ በሚነገርበት ሁኔታ
ባሁኑ ወቅት
የሃዲ ደጋፊ በሆነው ጦር ላይ ጥቃት አልቃይዳ ጥቃት የሰነዘረበት ምክንያት ግልጽ
አይደለም። ውጊያው አሁንም ያላቆመ ሲሆን የሟችና የቁስለኛ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Ø
ኢንተርናሽናል ኮንፈረንስ ኦን ዘ ግሬት ሌክ ረጅንስ (Internarional Conference
on The Great Lake Regions) የሚባለው
የአካባቢው አገሮችን የሚያስተባበረው ድርጅት ዋና ጽሕፈት ቤት አሁን ከሚገኝበት
ከብሩንዲ ዋና ከተማ ከቡጁምቡራ ተነቅሎ
በጊዜያዊነት ወደ ዛምቢያ ዋና
ከተማ ወደ ሉሳካ የተወሰደ መሆኑ ተነገረ። በብሩንዲ የጸጥታው ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባለሸ በመሄዱና
በየአውራ ጎዳናው የሚገለው ሰው እየበረከተ በመምጣቱ ምክንያት
የጽህፈት
ቤቱን ሰራተኞችና የቤተሰቦቻቸውን ደህነነት ለመጠበቅ ሲባል መስርያ ቤቱን በጊዜያዊነት ማዛወር አስፈላጊ ነው ተብሏል። ይህ
ድርጅት
የአካባቢው አገሮች የጸጥታ ሁነታን የሚጠበቅበትን እንዲሁም
የፖሊቲካ መረጋጋትንና እድገት የሚገኝበትን ሁኔታ ለመፍጠር የአካባቢ አገሮችን
ለማስተባበር የተቋቋመ ሲሆን
ዋና መስርያ
ቤቱ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ እንዲሆን የተደረገው በ2000 ዓ.ም. ነው። የድርጅቱ
አባል አገሮች አንጎላ፤ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፤ የኮንጎ ሪፕብሊክ፤ የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ፤ ኬኒያ፤ ኡጋንዳ፤
ሩዋንዳ፤ ደቡብ ሱዳን፤ ሱዳን፤ ታንዛኒና ዛምቢያ ናቸው። ክቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ ያለው የጸጥታ ሁኔታ በጣም እየተባባሰ
የሄደ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ሰሞኑን
በአማጽያኑ ከርቀት የተተኮሰ ሞርታር
በፕሬዚዳንቱ ቤት መንግስት አጠገብ የወደቀ መሆኑ ተገልጿል።
Ø
በትናነትናው ዕለት የደቡን ሱዳን ምክር ቤት (ፓርላማ) የአካባቢ ግዛቶችን ስልጣን
የሚያዳከመውንና
የፕሬዚዳንቱን ስልጣን በጣም የሚጨምረውን አንቀጽ በመጨመር የአገሪቱን ህገ መንግስት የለወጠ መሆኑ ተነገረ። ምክር ቤቱ ያደረገው
የህገ
መንግስት ለውጥ አዳዲስ ግዛቶች መመስረታቸውን የሚፈቅድ ሲሆን
እንዲሻሻል
የተደረገውም የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት የአካባቢ ግዛቶች ቁጥር በሶስት እጥፍ እንዲጨምር ካደረጉ በኋላ ነው። ከጥቂት ጊዜ በፊት ከአማጽያኑ ጋር የተደረገው
የስምምነት መሰረት ሚዛኑን የጠበቀ የስልጣን ክፍፍል ስለሆነ የግዛቶች ቁጥር መጨመር የስልጣን ሚዛኑን ስለሚያናጋ ስምምነቱን
ሊያፈርስ ይችላል የሚል ስጋት አለ። የሰላም ስምምነቱ እስካሁን ሳይከበር የቆየ መሆኑና
ግጭቶችና
ጦርነቶቹ የቀጠሉ መሆናቸው ግልጽ ቢሆንም በትናንቱ ዕለት የደቡብ ሱዳን ምክር ቤት የሰላም ስምምነቱን አጽድቆታል ተብሏል።
በአሁኑ ወቅት ግጭቶቹና ጦርነቶቹ ወደ ደቡብ ግዛቶች እየተስፋፋ መሆኑ ይነገራል።
በትናንትናው
ዕለት ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች ወደ ኡጋንዳን ሲጓዙ በነበሩ አንድ አውቶቡስና አራት የጭነት መኪናዎች ላይ ደፈጣ አካሄደው
አራት ሹፌሮችንና ሶስት ተሳፋሪዎችን የገደሉ መሆናቸው ተነግሯል።
ዩኒቲ፤ አፕር ናይልና ጆንግሌ በሚባሉት የአገሪቱ ሰሜናዊና ምስራቃዊ ግዛቶች
ጦርነቱ ያልበረደ መሆኑና እንዲሁም በአንዳንድ ቦታዎች ተፋፍሞ የቀጠለ መሆኑ ይነገራል። በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት
2.3 ሚሊዮን ሕዝብ ቤት ንብረቱን ጥሎ የተሰደደ ሲሆን 4.6 ሚሊዮን ሕዝብ ከፍተኛ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልገው ነው።
ደሩ
መሆናቸው ታውቋል።
Ø
በኮንጎ ሬፕብሊክ እሁድ ዕለት የአገሪቷን ሕገ መንግስት ለማሻሻል የውሳኔ ሕዝብ ምርጫ መካሄዱ
የሚታወስ ሲሆን ከምራጮቹ ዘጠና ከመቶ የሚሆነው መራጭ ህገ መንግስቱ ይሻሻል የሚለውን ሀሳብ የደገፈ መሆኑን የአገሪቱ የአገር
ውስጥ ሚኒስትር በይፋ ገልጸዋል። የህገ መንግስቱ ማሻሻያ ሀሳብ ፕሬዚዳንቱ ከሁለት ጊዜ በላይ እንዲወዳደርና የሚፈቅደውና ሰባ
ዓመት የሚለው የእድሜ ክልል እንዳያግደው የሚለው መሆኑ ይታወቃል። ሚኒስትሩ በተጨማሪ በሰጡት መረጃ ሊመርጥ ከሚችለው ሕዝብ
ውስጥ 72 ከመቶ ድምጽ የሰጠ መሆኑንም ገልጸዋል። ከእሁዱ ምርጫ በኋላ ተቃዋሚ ኃይሎች ለምርጫ የወጣው ሕዝብ ብዛት ከ10 ከመቶ
እንደማይበልጥና ሕዝቡ ጥሪያቸውን ሰምቶ በምርጫ አለመሳተፉ ያረካቸው መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
ምርጫውን በቅርብ የተከታተሉት
ዓለም
አቀፍ የዜና ማሰራጫ ተቋሞችም በዋና ከተማዋ እና በሌሎች ከተሞች ተዘዋወረው የምርጫውን ሂደት የታዘቡ መሆናቸውን ገልጸው
በበተመንግስቱ አቅራቢያ ከሚገኘው የምርጫ ጣቢያ በስተቀር በሌሎች የምርጫ ጣቢያዎች ለምርጫ የወጣው ሕዝብ ቁጥር በጣም አነስተኛ
እንደነበር መስክረዋል። የመንግስቱን መግለጫ ከእውነት የላቀ ማጭበርበር ነው በማለት ተቃዋሚ ኃይሎች ድርጊቱን ማውገዝ የጀመሩ
ሲሆን ከዚህ በኋላ የሚወስዱት እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም።
Ø
ባለፈው ሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ ውስጥ
ሮኬት ተኳሽ መሳሪያዎችንና መትረየሶችን የያዙ ግለስቦች ከፖሊሶች ጋር ባደረጉት
ግጭት ሶስት ሰዎች መገደላቸውንና 15 የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸውን የብሩንዲ ፖሊስ ገልጿል።
ሰኞ
ዕለት በአንድ አካባቢ በቆንጨራ የፖሊስ መኮንኖችን ሊገደል የሞከረው ሰው ወዲያውኑ መገደሉንና እንዲሁም ከጥቂት ጊዜ በኋላ አንድ
ሌላ ሰው በፖሊሶች ላይ በወረወረው ቦምብ ሰባት የፖሊስ አባላትን እንዲሁም ሁለት ወታደሮችንና ሶስት ሰላማዊ ሰዎችን ሲያቆስል
አንድ ሰላማዊ ሰው የገደለ መሆኑን የፖሊሱ ቃል አቀድባይ ተናግሯል። በሌላ ጊዜና ቦታ ደግሞ አንድ መሳሪያ የያዘ ሰው አንድ
የፖሊስ መኮንን ገድሏል ተብሏል። በተለያዩ ቦታዎችና በተለያዩ ጊዜዎች በደረሱት ጣቆቶች
የሞቱትና
የቆሰሉት ሰዎች ብዛት ፖሊስ ከሰጠው መረጃ ከፍተኛ ነው ብለው በቦታው የነበሩ የዓይን እማኞች ይግለጻሉ። በርካታ ፖሊሶች
መገደላቸው የተነገረ ሲሆን ማክሰኞ ዕለት በጥይት የተበሳሱ አስከረኖች መንገድ ላይ ወድቀው ተገኝተዋል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት
ለሶስተኛ ጊዜ ለመወዳደር የወሰኑ መሆናቸውን ከገለጹበት ካለፈው ሚያዚያ ወር ጀመሮ በአገሪቷ ውስጥ በየመንገዱ ግድያ የተበራከተ
መሆኑ እየተነገረ ሲሆን ወደ ጠቅላላ የእርስ በርስ ውጊያ ያመራል የሚል ስጋት ከፍተኛ መሆኑንም ተግልጿል። እስካሁን ባለው መረጃ
ከ200 በላይ የሆኑ የአገሪቱ ዜጎች መሞታቸውና ከ200 ሺ በላይ መሰደዳቸው ይታወቃል።
Ø
በግብጽ ለምክር ቤት አባልነት የሚደረገውን ምርጫ አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት ምርጫ
ያልተካሄደባቸው ጠቅላይ ግዛቶች
በዛሬው ዕለት ምርጫ ሲካሄዱ መዋላቸው ተነግሯል። ከ27 ጠቅላይ ግዛቶች
መካከል 14 በሚሆኑት ባለፈው ሳምንት ምርጫ መካሄዱ የታወቀ ሲሆን ድምጽ በመስጠት
የተሳተፈው ሕዝብ ብዛት
26.6 ከመቶ ብቻ እንደነበር ተገልጿል። በዛሬው ዕለት ለምርጫ የወጣው ሰው ብዛት
ከፍተኛ ይሆናል ተብሎ አይጠበቅም። ዶኪ በሚባል ቀበሌ የምርጫው ጣቢያ ተከፍቶ ሰዓታት ከቆየ በኋላ 20 ሰው ብቻ ድምጹን ሲሰጥ
መታየቱ ሕዝቡ በምርጫው ለመሳተፍ ፍላጎት የሌለው መሆኑን ያሳያል የሚሉ ታዛቢዎች በርካታ ናቸው። የዛሬ አራት አመት ለምክር ቤት
አባልነት በተካሄደው ምርጫ ከመራጩ ቁጥር 62 ከመቶ የሚሆነው ድምጹን የሰጠ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በየመን በሁቲዎች ላይ በተከታታይ የአየር ጥቃት የሚያካሂደው በሳኡዲ የሚመራው የየአይር ኃይል
ሳዳ በሚባለው ቦታ ድንበር የለሽ ሀኪሞች የህክምና አገልግሎት በሚሰጡበት ሃኪም ቤት ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃት አድረሶ ሃኪም
ቤቱን ከማፈራረሱ በላይ በርካታ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ያደረሰ መሆኑን የድርጅቱ ቃል አቀባይ በቲውተር አማካይነት ባስተላለፈው
ዜና ገልጿል። በሁቲ ቁጥጥር ስር ያለው የሳባ ዜና ወኪልም የሆስፒታሉን ዳይሬክተር ዋቢ በማድረግ ባስተላፈው መረጃ
በአየር
ጥቃቱ ምክንያት የሆስፒታሉ ህንጻ እና በሆስፒታል ውስጥ የነበሩ የህክምና መሳሪያዎች ከጥቅም ውጭ መሆናቸውንና በርካታ በሽተኞችና
ሰራተኞች መጎዳታቸውን አረጋግጧል። የዜና ወኪሉ በተጨማሪ በሰጠው መረጃ መሰረት የሳዑዲ የአየር ጥቃት በአካባቢው የሚገኘውን
የሴቶች ትምህርት ቤት ደብድቦ ጉዳት ያደረሰ መሆኑን ገልጿል። የሳዑዲ መንግስት ስለጉዳዩ የሰጠው መግለጫ እስካሁን የሰጠው
የለም። በተመሳሳይ ሁኔታ ከሶስት ሳምንት በፊት የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች በሰሜናዊ አፊጋኒስታን ኩንዱስ በተባለችው ከተማ
ያለውን የድንበር የለሽ ሀኪሞች ሆስፒታል ደብድበው 22 ሃኪሞችና በሽተኞች መግደላቸው ይታወሳል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ
ስህተት መሆኑን አምነው ይቅርታ የጠየቁ ቢሆንም “ድንበር የለሽ ሃኪሞች” የተባለው ድርጅት ጉዳዩ የጦርነት ወንጀል ስለሆነ
በገለልተኛ አካል ምርመራ ተካሄዶ ጥፋተኞቹ ለፍርድ መቅርበ አለባቸው የሚል ጥያቄ ማቅረቡ ይታወቃል።
ጥቅምት 15 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በዛሬው ዕለት የኃይሉ መጠን 7.5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰሜን አፍጋኒስታን የተከሰተ መሆኑ ተነግሯል። የመሬት መንቀጥቀጡ
ማዕከል ያደረገው ቦታ የሂንዱ ኮሽ ተራራማ ቦታዎች ሲሆን ስሜቱ በህንድና በፓኪስታን አካባቢዎች ድንቃጤና ፍርሃትን ፈጥሯል። ይህ
ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በአፍጋኒስታንና
በፓኪስታን ደግሞ 135 ሰዎች እንደሞቱ መረጃዎች ጠቁመዋል። አደጋው የደረሰው የመገናኚያ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በመሆኑ
አደጋው ያደረሰው ጉዳት እየታወቀ ሲሄድ የሟቾቹ ቀጥር ሊያድግ የሚችል መሆኑ ተገምቷል። በአፍጋኒስታን በትምህርት ላይ ያሉ
ተማሪዎች ከአደጋው ለማምለጥ ሙከራ ባደረጉበት ወቅት በተፈጠረ ግፍያና ጭንቅንቅ 12 ልጃአገረዶች የሞቱ መሆናቸው ታውቋል።
ላሆር በምትባለው የፓኪስታን ከተማ የስልክ መስመሮች የተቆራረጡ ሲሆን
በህንድም
አንዳንድ ትምህርት ቤቶች እና መስሪያ
ቤቶች እንዲለቀቁ ተደርገዋል። በፓኪስታን በመሬት መንቀጥቀጡ ክፉኛ የተመታው ችትራል የተባለው ጠቅላይ ግዛት ሲሆን እስካሁን
ድረሰ 11 ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ተነግሯል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተፈጠረው ከ200 ኪሎ ሜትር ጥልቀት በታች በመሆኑ በመሬቱ ላይ
ሊያመጣ የሚችለው ጉዳት አነስተኛ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ። አካባቢው የመሬት መንቀጥቀጥ የሚያጠቃው መሆኑ የሚታወስ ሲሆን
ከአስር ዓመት በፊት ካሽሚር በሚባለው የፓኪስታን ግዛት የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ከ75 ሺ ሰው በላይ የገደለ መሆኑና ባለፈው
ዓመት ሚያዚያ ወር ደግሞ በኔፓል የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ 9 ሺ ሰዎች ገድሎ 900 ሺ የሚሆኑ ቤቶች ያወደመ መሆኑ
ይታወሳል።
Ø
እሁድ ዕለት በታንዛኒያ በአይቮሪ ኮስት እና በኮንጎ ምርጫዎች ተካሄደዋል። በታንዛኒያ ዜጎች ፕሬዚዳንታቸውን ለመምረጥ በብዛት
ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የጎረፉ ሲሆን ቀደም ብሎ በተካሄደው የአስተያየት መለከያ መሰረት ተወዳዳሪዎች ተቀራራቢ ድምጽ ያገኛሉ ተብሎ
ተግምቷል። የምርጫ አስፈጻሚ ባለስልጣኖች በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት የምርጫው ውጠት ሊታወቅ እንደሚችል ተናግረዋል። በአንዳንድ
የምርጫ ጣቢያዎች ረዣዥም ስልፎች ታይተዋል። አሸናፊ የሚሆነው ወገን በአነስተኛ ድምጽ የሚያሸንፍ ከሆነ ግጭትና ረብሻ ሊነሳ
የሚችል ስጋት አለ።
Ø
በተመሳሳይ ዜና ለረዥም ዓመታት ሽብርና ግድያ ሲካሄድ በነበረባት አይቮሪ ኮስት ውስጥ እሁድ
ዕለት ፕሬዚዳንቱን ለመምረጥ የተደረገው ምርጫ
አገሪቱ
ውስጥ ያለው የፖሊቲካ መረጋጋት የደረሰበትን ደረጃ
ሊያሳይ
ይችላል የሚል አስተያያት በአንዳንድ ሰዎች ተሰጥቷል። የዛሬ አምስት አመት ለረዥም ገዜ ስልጣን ይዘው በቆዩት በሎሬንት ጋብጎ
እና በአንድ ወቅት የዓለም የገንዘብ ድርጅት ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩት በአላሳን ኩዋታራ መካከል የተደረገውን የምርጫ ውድድር
ተከትሎ በሁለቱ ሰዎች ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ከ3 ሺ ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወሳል። በፈረንሳይ ወታደሮች ድጋፍ
የኩዋታራ
ደጋፊዎች የጋብጎ ወታደሮችን አሸንፈው ጋብጎ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ሲደረግ ኩዋታራ አሸናፊ ተብለው በስልጣን መቀመጣቸውም
የሚታወቅ ነው ። ጋብጎ በቁጥጥር ስር ውለውና በሰው ማጥፋት ወንጀል ተከሰው በኒዘርላንድ እስር ቤት የሚገኙ ሲሆን የኩዋታራ
ወታደሮች ላካሄዱት እልቂት ግን እስካሁን በተጠያቂነት ለፍርድ አልቀረቡም ሲሉ የሰብአዊ መብት ተከራራኪ ድርጅቶች ይከሳሉ።
በተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በአይቦሪ ኮስት የተረጋጋ የፖሊቲካ ሁኔታ
ተፈጥሯል
ቢባልም አሁንም ቢሆን አገሪቷ
አማጽያን በሚቆጣጠሩት የሰሜን ግዛት እና የካታራ ደጋፊ
በሚገኙት በደቡብ ግዛት ተከፋፍላ ትገኛለች።
ከስድስት
ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ መራጮች ድምጽ ለመስጠት ይችላሉ በተባለለት የእሁድ ዕለቱ ምርጫ ምን ያህል ሰው እንደወጣ ለማወቅ ባይቻልም
ቢያንስ በሰሜኑ ግዛት ለምርጫ የወጣው ሰው አነስተኛ መሆኑ ተነግሯል። የኩዋታራ ተወዳዳሪ ሆነው ከቀረቡት መካከል ፍትሃዊ
አይደለም በማለት ቀደም ብለው ከምርጫው ራሳቸውን ያገለሉ ተወዳዳሪዎች መኖራቸው የታወቀ ሲሆን ሌሎች ግን በተለይ ከስልጣን
የተነሱትን የአይቮሪያን ፖፑላር ፍሮንትን የተባለውን የጋብጎ ፓርቲን የሚወክሉት ቻርልስ ኮናን ባኒ ውድድሩን እስከመጨርሻው
ለመቀጠል ፈቃደኛ ሆነዋል። የምርጫው የመጀመሪያ ውጤት በሳምንት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
Ø
በኮንጎ ሪፕብሊክ ደግሞ መራጮች ፕሬዚዳንታቸው ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ ውድድር ሊቀርቡ ይችላሉ
ወይስ አይችሉም በሚለው ጉዳይ ላይ ድምጻቸውን የሚሰጡበት ምርጫ እሁድ ዕለት ተካሄዷል። በስራ ላይ ባለው ሕገ መንግስት መሰረት
ፕሬዚዳንቱ የሚመረጠው ለሁለት የምርጫ ጊዜ ብቻ ሲሆን ከ70 ዓመት ዕድሜ በላይ የሆነ ሰው ለፕሬዚዳንት ምርጫ እንዳይወዳደር ሀገ
መንግስቱ ይከለክላል። የአሁኑ ፕሬዚዳንት ሳሱ እንጌሶ በሁለት ምርጫ ወቅቶች በስልጣን ላይ ከመቆየታቸውም በላይ ዕድሜያቸውም 71
ነው። ውሳኔ ሕዝቡ እንዲካሄድ የተደረገው የፕሬዚዳንቱን የስልጣን ዘመን ለማራዘም ሆን ተብሎ
በተፈጠረ
ተንኮል ነው በማለት በርካታ ተቃዋሚ ኃይሎች ተቃውማቸውን ከማሰማታቸው በላይ አንዳንዶቹ ሕዝቡ በምርጫው ላይ ባለመሳተፍ የአለውን
የመረረ ተቃውሞ እንዲያሳይ ጥሪ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በትናንትናው ዕለት በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጩ ቁጥር አነሰተኛ
መሆኑ የተቃዋሚ ኃይሎች ጥሪ የተሰማ ይመስላል።
የቀድሞ የናይጄሪያ የጸጥታ አማካሪ መሀመድ ሳምቦ ዳሱኪ ባለፈው ሐምሌ ወር በጉቦና ሕገ በሆነ
መንገድ የገንዘብ ዝውውር ተግባር ላይ ተሰማርተዋል
በሚል
ጥርጣሬ ፖሊሶች ቤታቸው ውስጥ ገብተው ፍተሻ ባካሄዱበት ወቅት 423 ሺየአሜሪካ ዶላር እና የናይጄሪያ ገንዘብ ከቤታቸው ውስጥ
የተገኘ መሆኑን ከፍርድ ቤት ከተገኘ የሰነድ መረጃ ለማወቅ ተችሏል። አዲሱ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ስልጣን በያዙበት ወቅት ሲመጡ
በሙስና የተበከሉ ባለስልጣኖችን ለፍርድ ለማቅረብ ቃል መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን ምርመራ እንዲካሄድባቸው ከነበሩ ባለስልጣኖች
መካከል አንዱ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ጉድ ላክ ጆናታን የቅርብ አማካሪ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት ዳሱኪ ናቸው። ዳሱኪ ሰኞ
ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል።
ጥቅምት
13 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በድርቁ ሳቢያ በአፋር ግዛት እየሞቱ ያሉት
የቀንድ
ከብቶች ቁጥር የጨመረ መሆኑ ከአካባቢው የሚገኙ ዜናዎች ይገልጻሉ። ከአሳይታ ከተማ በደረሰው መረጃ መሰረት በአካባቢው ቦና
ይዟቸው በየቀኑ እየሞት የሚገኙ የቀንድ ከብቶችና ግመሎች ቁጥር በእጥፍ በመጨመሩ
ምክንያት
አደጋው
አሳሳቢና አስደንጋጭ ደረጃ ላይ የደረሰ መሆኑ ተገልጿል። የቀንድ ከብቶች በብዛት በሚሞቱበትና
በርካታ
ህጻናት በምግብ እጥረት በሚሰቃዩበት ሁኔታ የተከማቸ እህልም ሆነ የእንሣሳት መኖ
እያከፋፈልኩ
ነው በማለት
በመገናኚያ ብዙሀን አማካይነት ነጋጠባ የሚለፍፈው ወያኔ በአካባቢው የተከሰተውን ችግር
ለመቅረፍም ለመቀነሰ ያደረገው አስተዋጾ የሌለ መሆኑን ከአካባቢው የሚደርሱ ዜናዎች ይጠቁማሉ። በድርቁ ሳቢያ የሚያልቁት የቀንድ
ከብቶቹና ግመሎች መጠን በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ሀብቱና ንብረቱ የቀንድ ከብትና ግመል ብቻ የሆነው አርብቶ አድር በታሪኩ አይቶት
የማያውቀው ከፍተኛ ችግር ውስጥ ሊወድቅ የሚችል መሆኑ በግልጽ እየታየ ነው በማለት ታዛቢዎች እየተናገሩ ነው።
Ø
የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ለቤት ሰራተኛነት ሆነ ለሌላ ስራ ወደ አገሩ ሊገቡ ስለሚችሉ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ አዲስ ህግ እያረቀቀ
መሆኑን ጠቁሞ በዚህ በኩል የሚደርስበትን ውሳኔ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል። በሳዑዲ አረቢያም ሆነ
በሌሎች አረብ አገሮች በግርድና የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ጉልበታቸው እየተበዘበዘና ሰብአዊ ክብራቸው እየተደፈረ ሲሰቃዩ
የቆዩ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ይወጣል የተባለው አዲስ ህግ የእቶቻችንን መብት ያስጠብቃል ተብሎ አይጠበቅም የሚሉ አሉ።
ጉልበታቸው እንዲበዘብዝ ዜጎቻችንን ወደ ውጭ በማስወጣት ከፍተኛ ንግድ የሚያካሄዱት የወያኔ ባለስልጣኖች የሳኡዲ አረቢያ መንግስት
በዚህ በኩል የሚያደርገው ውሳኔ በአንክሮ እየተከታተሉት መሆኑ ለመገንዘብ ተችሏል።
Ø
ለወያኔ አገልጋይና አሽከር ሆኖ በወያኔ የተፈጠረው ብአዴን የተባለው ድርጅት ለምስረታው በዓል ማዘጋጃ የሚሆን ገንዘብ አዋጡ
በማለት በአማራው አካባቢ ያሉ ዜጎችን በማስጨነቅ ላይ ያለ መሆኑ ከተለያዩ ቦታዎች የተገኙ መረጃዎች ይገልጻሉ። በአነስተኛ ንግድ
ላይ የተሰማሩ ከ500 ብር ጀምሮ በመካከለኛ ንግድ ላይ ያሉ ከአስር ሺ ብር ጀምሮ ባለሆቴሎቾና ታላላቅ በተባሉ የንግድ ስራ ላይ
የተሰማሩት ደግሞ ከአምሳ ሺ ብር በላይ መዋጮ የተጣለባቸው መሆኑን ተነግሯል። የተጣለበትን መዋጮ ሳይከፍል የተገኘ ግለሰብ
ትምህርት ሊሰጥ የሚችል የቅጣት እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑን የብአዴን ካድሬዎች ውስጥ ውስጡን በማሰራጨት ላይ መሆናቸው
ተደርሶበታል።
Ø
ካይሮ ፖስት የተባለው የግብጽ ጋዜጣ አርብ ዕለት ባወጣው እትሙ ወደ አገር ውስጥ ህገ ወጥ
በሆነ መንገድ ገብታችኋል በሚል ምክንያት 10 ኢትዮጵያውያን እና 11 የሱማሌ ዜጎች የግብጽ መንግስት ያሰራቸው መሆኑን ገልጿል።
ስደተኞች የተያዙት በደቡብ የግብጽ ግዛት በባቡር ሲጓዙ መሆኑ ጋዜጣው በአምዱ ላይ ቢያሰፍርም ለምን ያህል ጊዜ
በግብጽ ውስጥ የቆዩ መሆናቸውን
አልገለጸም።
ከሊቢያ ወደ አውሮፓ በብዛት እየጎረፉ ለሚገኙት ስደተኞች ግብጽ አንዷ የመተለለፊያ ቦታ እንደሆነች ሲታወቅ በብዛት ከሚገቡ
ስደተኞች መካከል በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት ይታወቃል።
የወያኔን
አስከፊ አገዛዝና በአገር ውስጥ ያለውን የኑሮ ችግር በመሸሽ በየአቅጣጫው ከአገራቸው እየወጡ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከጊዜ
ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱ ሲታወቅ በግብጽ በኩል አቆራርጠው ወደ አውሮፓ የሚጓዙትም ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ግልጽ ነው።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሱማሊያ እና በሻዕቢያ ላይ ቀደም ብሎ
በውሳኔ አስተላልፎት የነበረውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት ያህል እንድራዘም
በትናንትናው ዕለት ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑ ተገለጸ። በሱማሊያና እና በኤርትራ
ያለውን ሁኔታ እንዲከታተል
ተቋቁሞ የነበረውና (Somalia and Eritrea Monitoring Group)
እየተባለ የሚጠራው
አካል ለመጭው አንድ ዓመት በሃላፊነቱ እንዲቀጥል ምክር ቤቱ የወሰነ ሲሆን በተለይ
የሻዕቢያ መንግስት ቡድኑን ስራውን ለመጀመር ወደ ኤርትራ
የሚገባበትን
መንገድ እንዲያመቻቸ የሚጠብቅ መሆኑን ገልጿል። ከዚህም ጋር አያይዞ በኤርትራ ውስጥ ስለታሰሩት የጂቡቲ እስረኞች ሁኔታ መረጃ
እንዲሰጥ የሻዕቢያ መንግስትን ጠይቋል። ምክር ቤቱ በሱማሊያ ውስጥ በሰብዓዊ ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለው አደጋ ያሳሰበው
መሆኑን ገልጾ በድርጅቶች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት አውግዟል። በሱማሌያ ውስጥ በመንግስት ባለስልጣኖች
በሙስና የሚዘረፈው ሀብት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጾ የሱማሊያ የሰላምና
የእርቅ ሂደትን የሚያጨናግፉ ባለስልጣናት ሁሉ ላይ ማዕቀብ የሚደረግባቸው
መሆኑንም
በመግለጽ አስጠንቅቋል።
Ø
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ በትናንቱ ዕለት በቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር በመጭው
የትምህርት ዘመን ለትምህርት
በሚደረገው ክፍያ ላይ ጭማሪ እንደማይደረግ አሳወቁ። ፕሬዚዳንቱ መልእክታቸውን በቴሌቪዥን በሚያስተላልፉበት ወቅት ከበርካታ
የደቡብ አፍሪካ ከተሞች ተቃውሟቸውን
ለማሰማት የተሰባሰቡ
ተማሪዎች የመንግስት መቀመጫ ወደ ሆነው ወደ ዩኒይን ህንጻ ለመግባት ሲሞክሩ
ከፖሊሶች ጋር ግጭት ተፈጥሮ
የነበረ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪ ሚስተር ዙማ
በአሁኑ
ወቅት በትምህርት ክፍያው ላይ የተድረገው
ጭማሪ የተነሳ ቢሆንም ከረዥም ጊዜ አንጻር መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮቹ ይኖራሉ ብለዋል። የትምህርት ክፍያው አለመጨመሩ በግምባር
ቀደምትነት ሲታገሉ የነበሩ ተማሪዎችን ያረካ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም ይህ ውሳኔ ለምን ቀደም ብሎ እንዳልተወሰነ ብዙዎችን
አስገርሟል። የተለያዩ የዩኒቨርሲቲ
ባለስልጣኖች የዩኒቨርስቲዎችን የትምህርት ደረጃ ለመጠበቅ ክፍያው መጨመሩ አስፈላጊ
መሆኑን የገለጹ ሲሆን
የክፍያ ጭማሪውን ለመሸፈን ገንዘቡ እንዴት እንደሚከፈልና ማን እንደሚከፍለው
የማያውቁ
መሆናቸውን የመንግስት ባለስልጣኖች ተናገረዋል።
Ø
በትናንትናው ዕለት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በማይዱግሪ ውስጥ አንድ ቦምብ ፈንድቶ 15 ሰዎች
ከገደለ በኋላ ዮላ በተባለችው ከተማ ውስጥ አንድ በቅርቡ በተሰራ አዲስ መስጊድ ውስጥ በሌላ አጥፍቶ ጠፊ በፈነዳ ቦምብ 27
ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘው ዜና ያስረዳል።
ዛሬ
ጠዋት ደግሞ አራት አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ ሴቶች ወደ ማይዱጉሪ ከተማ ከመግባታቸው በፊት የአካል ፍተሻ እንዲደርግላቸው ከተማዋን
በሚጠብቁ የሲቪል ሚሊሺያዎች ሲጠየቁ ፈቃደኛ ካለመሆናቸውም በላይ
የያዙትን ቦሞቦች አፈንድተው ራሳቸውንና አንድ ሰላማዊ ሰው ሲገድሉ ከ10 በላይ
የሆኑ ሰዎች ያቆሰሉ መሆናቸውን የከተማዋ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ቦምቦቹ በማፈንዳት ኃላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም
የቦኮሃራም ታጣቂዎች መሆናቸው ይታወቃል።
Ø
በሊቢያ ምስራቃዊ ከተማ ቤንጋዚ ውስጥ ሰላማዊ የተቃውሞ ስልፍ በሚያደርጉ ዜጎች ላይ በተተኮሱ
የሞርታር
ጥይቶች ስድስት ሰዎች መሞታቸውና ከ30 በላይ መቁሰላቸው ታወቀ። የተቃውሞ ስልፉ የተካሄደው
በቅርቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዑክ ያቀረቡትን
የሽግግር መንግስት ምስራታ የእርቅ ሀሳብን በመቃወም ሲሆን ሞርታሮቹ የተተኮሱት
በእስላማዊያኑ ቁጥጥር ስር ካሉ ቦታዎች መሆኑ ተነግሯል። ከላፈው ዓመት ጀምሮ በቤንጋዚ በወታደሩ እና በእስላማውያን ኃይሎች
መካከል ግጭቶች ሲደረግ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን
ከአክራሪ
እስላማውያኑ ኃይሎች መካከል አንሳር አል ሻሪያ የተባለውና ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ ከሚጠራው ጋር ግንኙነት እንዳለው በይፋ
ያሳወቀው ቡድን አንዱ ነው።
ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ከአይርላንድ ዋና ከተማ ከደብሊን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ደለስ አይሮፕላን ጣቢያ ይበር የነበረው
ኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለበረራ ከተነሳ ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ አንዱ ሞተር መስራት በማቆሙ በአስቸኳይ ወደ
ደብሊን ተመልሶ በሰላም ያረፈ መሆኑ ተነግሯል። የበረራ ቁጥር ETH 500 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ
787-800 ድሪም ላይነር
አውሮፕላን የተነሳው ከአዲስ አበባ ሲሆን እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከ45 ደቂቃ ላይ ደብሊን ገብቶ ከጠዋቱ
አስራ ሁለት ሰዓት ላይ ጉዞውን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ቀጥሎ ነበር። ለአንድ ሰዓት ከሰላሳ የበረራ ጊዜ በኋላ አብራሪዎቹ ባገኙት
እክል ምክንያት አንዱን ሞተር ለማጥፋት በመገደዳቸው ይህንኑ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ለደብሊን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች
አሳውቀውና እና በቀላል ክብደት ለማስራፍ እንዲቻል አውሮፕላኑ ውስጥ ያለውን ብዙ ሺ ሊትር የሚገመት ነዳጅ ለአስር ደቂቃ ያህል
ከአየር ላይ አራግፈው አውሮፕላኑን በሰላም እንደ አገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ከሰላሳ ላይ ደብሊን አውሮፕላን
ማረፊያ አሳርፈውታል። በአሁኑ ወቅት የችግሩ መነሻ በአዋቂዎች እየተመረመረ ይገኛል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎች ተወካዮች የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማን ዛሬ አርብ
በሚያነጋግሩበት ወቅት ድጋቸውን ለማሳየት በሁሉም አካባቢዎች ያሉ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ተማሪዎች በአውቶቡስና በባቡር ወደ ፕሪቶሪያ
የሄዱ መሆናቸው ተነገረ። ከስፍራው በደረሰው ዘገባ መሰረት ተማሪዎቹ የላሲትክ ጎማዎችን በማቃጥልና ድንጋይ በመወርወር
ተቃውሟቸውን በመግለጽ ከፖሊሶች ጋር የተጋጩ ሲሆን ፖሊሶችም ተጋፊ ውሃና አስለቃሽ ጢሶችን በመጠቀም ሰልፉን ለመበተን ሞክረዋል።
ሚስተር ዙማ ከተማሪዎቹ ጋር በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የዩኒቨርስቲዎቹ
ባለስልጣኖች
ይገኛሉ የተባለ ሲሆን ሚስተር
ዙማ ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ የዩኒቨርስቲ
የትምህርት ክፍያ የሚወሰነው በየዩኒቨርስቲዎቹ አስተዳደር መሆኑን ጠቁመው
ከደሃ
ቤተሰብ የመጡ ተማሪዎች ጭማሪው እንዳይደረገ ጥያቄ ማቅረባቸው ተገቢ ነው ብለዋል። የዩነቭርስቲዎቹ አስተዳዳሪዎች በበኩላቸው
የትምህርቱን ክፍያ ለመጨመር የተገደዱት መንግስት ይሰጥ የነበረው ክፍያ በጣም በመቀነሱና የትምህርቱን ደረጃ ለመጠበቅ አስፈላጊ
በመሆኑ ነው ብለዋል። የተማሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የጀመረው ባለፈው ሳምንት በጆሃንስበር ከተማ በሚገኙት ሁለት ዩኒቨርስቲዎች
ውስጥ ሲሆን ከዚያ ወዲህ በሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ 10 ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ
የተዛመተ መሆኑ ይታወቃል። ስልፉን ያካሄዱት
አብዛኞቹ
ተማሪዎች ከደሃ ቤተሰብ የመጡ ሲሆን ሃብታም ከሆኑ ቤተሰቦች የመጡ ነጮች ተማሪዎችም ትብብር ለማሳየት በሚል ሰልፉን
ተቀላቅለዋል። አንዳንድ
ታዛቢዎች የተማሪዎቹ የተቃውሞ ሰልፍ ሕዝቡ በገዥው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ ፓርቲ ላይ ያለው እምነት እመነመነ መምጣቱን
ያሳያል ይላሉ።
Ø
ዛሬ አርብ በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በማይዱጉሪ ከተማ በአንድ መስጊድ ውስጥ በአጥፍቶ ጠፊ
በፈነዳ ቦምብ 28 ሰዎች የተገደሉ መሆናቸውን በአካባቢው የሚገኙ
የሚሊሺያ
አባሎች
ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዘና ወኪል ገልጸዋል። የዜና ትክክለኛነት ከሌሎች ነዋሪዎች
የተረጋገጠ ሲሆን ጥቃቱ የተፈጸመው በቦኮሃራም እንደሆነ ተገምቷል።
Ø
የአውሮፓው ህብረት ተወካዮች ሰኞ ዕለት በብራስልስ በሚያካሂዱት ስብሰባ
የብሩንዲ መሪዎችን ለውይይት ወደ ብራስልስ የሚጋብዝ የጥሪ ደብዳቤ የሚያጸድቁ
መሆኑ ተነገረ። የአውሮፓው ኅበርት ይህንን ጥሪ ለብሩንዲ ባለስልጣኖች
የሚያስተላልፈው
የሰብዓዊ መብት ሌሎች የአገሪቱን ዋና ዋና ችግሮች አስመልክቶ በአውሮፓው ህብረትና በብሩንዲ መካከል የውይይት መድረክ እንዲከፈት
ለማድረግና በሁለቱም በኩል ተቀባይነት ያለው መፍትሔ ላይ ለመድረስ ጥረት ለማድረግ ነው ተብሏል። የብሩንዲ ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ
በሆነ መንገድ ለሶስተኛ ጊዜ ምርጫ ውስጥ መግባታቸውን ካሳወቁ ወቅት ጀምሮ በብሩንዲ በተነሳው ተቃውሞና በተከተለው ግጭት ከ120
ሰዎች በላይ ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 190 ሺ የሚሆኑ ዜጎች ለስደት ተዳርገዋል። የአውሮፓው ህብረት ይህንን ድርጊት አውግዞ
በተወሰኑ የብሩንዲ ባለስልጣኖች ላይ ማዕቀብ የጣለ መሆኑ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩዋንዳው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ናይሮቢ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሩዋንዳ በብሩንዲ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብታለች የሚለውን የብሩንዲን ክስ ማስተባበላቸው
ተነግሯል። ሚኒስትሯ “የብሩንዲ ችግር የብሩንዲ እንጅ የሩዋንዳ አይደለም” ካሉ በኋላ “የአንድ አገር መሪ በአንድ ጉዳይ ላይ
ውሳኔ ከወሰደ በኋላ ውሳኔው የሚያስከተለውን ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ መሆን አለበት” ብለዋል።
የሩዋንዳ ምኞት በብሩንዲ ውስጥ ሰላም ሰፍኖ በሩዋንዳ የሚገኙ ስደተኞች ወደ
አገራቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች ነው ብለዋል።
በሩዋንዳ
ውስጥ በርካታ ስደተኞች ከመኖራቸው በተጨማሪ የሩዋንዳ ዋና ከተማ ኪጋሊ የብሩንዲ ተቃዋሚ ኃይሎች፤ የሲቪክ ማህበረሰብ መሪዎችና
ከብሩንድው ፕሬዚዳንት ፓርቲ የከዱ ታላላቅ ሰዎች መቀመጫ መሆኗ ይታወቃል።
ከብሩንዲ
የከዱ ወታደሮችን በማደራጀት ሩዋንዳ ጦር
ልትከፍት አቅዳለች በማለት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ሩዋንዳን እየከሰሱ ይገኛሉ።
ጥቅምት
11 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በጦርነት ቀጠና ውስጥ ያሉ 30 ሺ የደቡብ ሱዳን ዜጎች በምግብ እጦትና በረሃብ የተነሳ የሞት
አደጋ ሊደርስባቸው እንደሚችል የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት አካሎች
የሆኑ ሶስት ድርጅቶች በጋራ
ባወጡት መግለጫ
ገለጹ።
የተባበሩት
መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅት፣(FAO)
የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) እና የተባበሩት
መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ባወጡት የጋራ መግለጫ በከፍተኛ ደረጃ በምግብ እጥረት የተጎዳው ቦታ በነዳጅ ዘይት
ሀብታም የሆነውና አሁን ጦርነት የሚካሄድበት የደቡብ ሱዳን ሰሜናዊ ክፍል ነው ብለዋል።
የእርዳታ
ሰጭ ድርጅቶች ወደ ቦታው ሄደው እርዳታ መስጠት ካልቻሉ ከፍተኛ እልቂት የሚፈጠር መሆኑን ገልጸው አካባቢዎችን የሚቆጣጠሩት
ወገኖች እርዳታ ሰጭዎች
ወደ ቀጠናቸው ገብተው ስራቸውን ሊሰሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻት ይኖርባቸዋል
ብለዋል።
በተያያዘ ዜና ባለፈው ዓመት በነሐሴ
ወር በአማጽያኑ በመንግስቱ መካከል የተፈረመው
የሰላም
ስምምነት በስራ ሊውል በሚችልበት ጉዳይ ላይ ለመወያያት አደስ ውይይት በአዲስ አበባ የተካሄደ መሆኑ ተገልጿል። ሁለቱ ተጻራራሪ
ወገኖች ስምምነቱን በመጣሳቸው በአደራዳሪዎቹ በተደጋጋሚ መወገዛቸው የሚታወስ ሲሆን አዲስ ድርድር ውስጥ መግባት ባይቻልም
ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ማክሰኞች ዕለት ውይይት ሲካሄድ መቆየቱ ተገልጿል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ ተማሪዎች የሚያያካሂዱትን የተቃውሞ ሰልፎች አጠናክረው የቀጠሉ
ሲሆንበትናንትናው ዕለት በኬፕታውን
ከተማ የሚኖሩ ተማሪዎች ከፓርላማ ውጭ የተቃውሞ ስልፍ አድርገዋል። ወደ ምክር
ሕንጻ ውስጥ ጥሰው ለመግባት ሙከራ ሲያደርጉ ፖሊስ አስላቃሽ ጋዞችንና አስመሳይ
ፈንጅዎችን በማፈንዳት
ስልፉን ለመበትን ጥረት ያደረገ ሲሆን
29 ተማሪዎችን ይዞ ያሰረ መሆኑ አስታውቋል።
በዛሬው
ዕለት የታሰሩት
ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በሕዝብ መካከል ረብሻ በማስነሳት በሚል ክስ ተከሰዋል። የእምንት ክህደት ቃል እንዲሰጡ ያልተጠየቁ
ሲሆን ጉዳያቸውም ለሚቀጥለው ጥር ወር ተቀጥሯል።
የደቡብ
አፍርካ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ነገ አርብ የተማሪዎችን ተወካዮች ለማነጋገር የሚፈልጉ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን የደሃ ተማሪዎች
ጥያቄዎች አግባብ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት የሚጥሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
መንግስት በ10 ከመቶ ለመጨምር አቅዶት የነበረውን የትምህርት ክፍያ ወደ ስድስት
ከመቶ ዝቅ ያደርገ መሆኑን ቢገልጽም ተማሪዎች ያልተቀበሉት መሆናቸው ይታወሳል።
Ø
በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ በተቃዋሚ ኃይሎች የሚካሄዱት የተቃውሞ ስልፎች በትናንትናው ዕለትም ቀጥለው ለሁለተኛ ቀን ከፖሊሶች
ጋር ግጭቶች ተፈጥረዋል። ማክሰኞ ዕለት ከፖሊሶች ጋር ተካሂዶ በነበረው ግጭት መንግስት 4 ሰዎች መሞታቸውን ቢገልጽም ተቃዋሚ
ኃይሎች ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል። ረቡዕ ዕለት በተደረገው የተቃውሞ ስልፍም ከፖሊሶች ጋር ግጭቶች መከሰታቸው
የተነገረ ሲሆን ጉዳት መድረሱና አለመድረሱ ግን አልታወቀም። በዚሁ ዕለት ስድስት የተቃውሞ ድርጅት ቃል አቀባዮች ለጋዘጠኞች
መግለጫ ለመስጠት ሲሰናዱ ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
የሰዳን መንግስትን እና የ ሱዳን ሕዝብ ነጻ አውጭ እንቅስቃሴ በሰሜን
(SPLM N) የተባለውን ድርጅት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለማስታረቅ
በጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓም በአዲስ አበባ ስብሰባ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በዚሁ ስብሰባ ላይ ለመገኘት የሱዳን መንግስት
ፈቃደኛ መሆኑን ገልጿል። የሱዳን ህዝብ ነጻ አውጭ እንቅስቃሴ በሰሜን የሚባለው ድርጅት ከ2004 ዓም ጀምሮ በደቡባዊ ብሉ ናይል
እና በደቡብ ኮርዶፋን ግዛቶች እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በስብሰባው ላይ ለመገኘት መወሰንና አለመወሰኑን
እስካሁን አልገለጸም። ይህ አዲስ የእርቅ ስብሰባ ጥሪ የመጣው የሱዳን መንግስት
ከተቃዋሚዎች ጋር ለመነጋገር እና ለመስማማት አንዳንድ እንቅስቃሴዎች ባደረገበት ወቅት ነው። ቀደም ብሎ የሱዳን መንግስት ትጥቅ
ያነሱ ተጻራሪ ኃይሎች የሱዳን መንግስት ባቀደው ብሔራዊ ውይይት ላይ እንዲገኙ ያስተላለውን ጥሪ ሶስት የዳርፉት ድርጅቶች እና
የሱዳን ሕዝብ ነጻ አውጭ ድርጅት በሰሜን (SPLM N) የሚገኙበት
የሱዳን ሪቮሉሽናሪ ፍሮንት (SRF) ተብሎ የሚጠራው የህብረት ግምባር የሱዳን
መንግስትን ጥያቄ ያልተቀበለ መሆኑን ገልጾ ስብሰባው ገለልተኛ በሆነ ቦታ እንዲካሄድ ጠይቆ ለስድስት ወራት ያህል ተኩስ ለማቆም
ዝጁነቱን መግለጹ ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና በሱዳን ዳርፉር ግዛት
ውስጥ ለተሰማሩት የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የተላከ ራሽን የሱዳን መንግስት በፖርት ሱዳን ለሳምንታት አግቶ ካቆየ በኋላ
የለቀቀ መሆኑ ተገልጿል። በፖርት
ሱዳን የታገቱት
190 ኮንቴነሮች ውስጥ 52 የተለቀቁ መሆናቸው ሲገለጽ ሌሎቹም የሚለቀቁ መሆናቸው ተነግሯል።
የሱዳን መንግስት ራሽኖችን ያገደበት ምክንያት ያልገለጸ ቢሆንም
ዳርፉር ውስጥ ጦርነት ስለሌለ የተመድ አስከባሪ ኃይሎች ቦታውን ለቀው መውጣት
አለባቸው የሚል ጥያቄ የሱዳን
መንግስት ማቅረቡና ተመድ ደግሞ ሁኔታው ገና ነው በማለት የሰላም አስከባሪ ኃይሉ እንዲቆይ ማድረጉ ይታወሳል።
Ø
በትናንትናው ዕለት ከወታደራዊ ጥቃት ለማምለጥ በሽሽት ላይ የነበሩ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች
በሰሜን
ምስራቅ ናይጄሪያ
በአራት መኪናዎች ተሳፍረው በነበሩ ሰዎች ላይ ተኩስ ከፍተው 20 ሰዎች የገደሉ መሆናቸውን
ከስፍራው የደረሰው ዜና ይገልጻል። የቦኮሃራም ታጣቂዎች በሰፈሩባችው ካምፖች ላይ በናይጄሪያ መከላከያ ሰራዊት ጥቃትና ከበባ
የተደረገባቸው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ጥቃቱን
ወታደራዊ
ፒክ አፖችን ሞተር ቢስክሌቶችን ተጥቅመው ጥቃቱን በመሸሽ ላይ የነበሩ የቦኮ ሃራም ታታቂዎች
ባጋጣሚ ባገኟቸው መኪኖች ላይ ተኩስ ከፍተው ሰላማዊ ሰዎችን ከመግደላቸውና
መኪናዎችን ከማቃጠላቸውም በላይ በአካባቢው
የነበረውን መንደሩ መዝረፋቸውና ቤቶችንም
ያቃጠሉ መሆናቸው ተነግሯል።
Ø
የኮንፊውሸስ የሰላም ሽልማት የሚባለውና በ2003 ዓም ከኖቤል ሽልማት ድርጅት ተጻራሪ ሆኖ
በቻይና የተመሰረተው ድርጅት በዚህ ዓመት የሰላም ሽልማቱን ለዚምባብየው ሮበርት ሙጋቤ የሰጠ መሆኑን አስታውቋል። የድርጅቱ መሪ
ኪያዎ ዳሞ ፔኪንግ ውስጥ በሰጡት መግለጫ ሙጋቤ ለዓለም ሰላም ላበረከቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የዚህ ዓመት የኮንፊውሸስ ሽልማት
ተሰጥቷቸዋል ብለዋል። ለውድድር ቀርበው የነበሩ ተወዳዳሪዎች ቢል ጌትስ፣ የተመድ ዋና ፀሐፊ ባንኪ ሙን እና የደቡብ አፍሪካ
ፕሬዚዳንት ፓርክ ግየን ሃይ ሲሆኑ ሙጋቤ አሸናፊ ሆነው ተሸላሚ ሆነዋል። የኮንፊውሸስ ሽልማት የተጀመረው በ2003 የስዊድኑ
የኖቤል ሽልማት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ለሆነውና
በእስር ላይ ለነበረው
ቻይናዊው ለሊዩ ዚያቦ ሽልማት ከሰጠ በኋላ በተወሰደ የአጸፋ እርምጃ ነው።
በምዕራብ አገሮች እየተኮነኑና እየተወገዙ የሚገኙት
ሙጋቤ
ለሕዝባቸው
የሚጠቅም
የፖሊቲካ እና የኢኮኖሚ ግንባታ አካሂደዋል የሚል ገለጻ በመስጠት ኮንፊውሸስ
የኖቤል ሽልማት ድርጅት አወድሷቸዋል። ሽልማቱ 80 ሺ ዶላር የሚያስገኝ ሲሆን የአሰጣጥ ስነስርዓቱ በታህሳስ ወር ይደርጋል
ተብሏል። የኮንፈውሸስ የሰላም ሽልማት በግል ገንዘብ የሚደጎም ነው የተባለ ሲሆን በዚህ ጉዳይ እስካሁን ድረስ ላይ የቻይና የውጭ
ጉዳይ ሚኒስትር የሰጠው መግለጫ የለም።
ጥቅምት 10 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክ በብራዛቪል እና ፖይንት ኑዋር
ከተሞች
የተካሄዱትን
የተቃውሞ
ስልፎች ለመበተን ፖሊሶች
በከፈቱት ተኩስ አራት ሰዎች መገደላቸውንና ከ 10 በላይ የሚሆኑት ደግሞ
መቁሰላቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። የአገሪቱ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ለመንግስት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ ሶስት
ሰዎች በብራዛቪል ከተማ ሲሞቱ አንደኛ ድግሞ በፖይንት ኑዋር መሞቱን ተናግረዋል። በተጨማሪ ሚኒስትሩ
ሶስት
የጸጥታ ኃይል አባላት መቁሰላቸውን ገልጸው አስራ ስድስት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል።
አምነሲት ኢንተርናሽናል የተባለው የስብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ፖሊሶች ጥይት
ከመተኮስና
አላስፈላጊ ከሆነ ኃይል ራሳቸውን እንዲያቅቡ ጥሪ ሲያደርግ የአሜሪካ ረዳት ምክትል ጸሐፊ
ኪንሻሳ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደግሞ ሁሉም ወገኖች የኃይል እርምጃን አስወግደው ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠይቀዋል።
ከትናንቱ
የተቃውሞ ሰልፍ በኋላ መንግስት ሁኔታው የተረጋጋ መሆኑን ገልጾ ሁሉም ወደ ስራው እንዲመለስ ትእዛዝ ቢያስተላልፍም ሱቆች
ትምህርት ቤቶችና ቢሮዎች ተዘግተው የዋሉ መሆናቸው ተነግሯል። በኮንጎ ለእሁድ የታቀደውን ሕዝበ ውሳኔ በመቃወም ሕዝቡ ሰላማዊ
የሆነ
ጠቅላላ የአመጽ መነሳሳት እንዲያደርግ ፓን አፍሪካን ዩኒየን ፎር ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ
የተባለው የተቃዋሚ
ድርጅት መሪ ጥሪ ማድረጋቸውም ተነግሯል።
Ø
ከ700 በላይ የሚሆኑ የኬኒያ ዜጎች አልሸባብን ጥለው የመጡ መሆናቸውን በመንግስት ድጋፍ
የተሰናዳ አንድ ዘገባ ገልጿል። ኬኒያውያኑ
ከጥቂት ጊዜ በፊት አልሸባብን ለመቀላቀል ወደ ሶማሊያ ሄደው ለተወሰነ ጊዜ
በድርጅቱ ውስጥ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ቢሆንም በመጀመሪያ ቃል የተገባላቸውን በርካታ ገንዘብ
ለማግኘት
ባለመቻላቸው ወደ አገራቸው ለመመለስ መወሰናቸው ተገልጿል።
Ø
በደቡብ አፍሪካ የተማሪዎችን ተቃውሞ ለማርገብ መንግስት የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪን ከ10
ከመቶ ወደ ስድስት ከመቶ ዝቅ ቢያደርግም ተማሪዎቹ ማሻሻያውን የማይቀበሉት መሆናችውን ገልጸዋል።
ከዋና
ዋና የተማሪ ማህበሮች ውስጥ አንዱ የሆነውና “ሳውዝ አፍሪካ ስቱደንትስ ኮንግሬስ” የሚባለው የተማሪ ማህበር
ማሻሻያውን
እንደማይቀበለው ገልጾ በደቡብ አፍሪካ ያሉ ሁሉም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ትምህርት አቁመው ዩኒቨርስቲዎችን
እንዲዘጉ
ጥሪ አቅርቧል። የተማሪዎቹ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተጀመረው ባለፈው ሳምንት ጆሃንስበርግ ባሉ ሁለት ዩነቨርሲትዎች ውስጥ በሚማሩ
ተማሪዎች አማካይነት መሆኑ ሲታወቅ ከዚያ ወዲህ ወደሌሎች ቦታዎች ተሻግሮ ቢያንስ ስደስት በሚሆኑ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚማሩ
ተማሪዎች ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል።
Ø
የሩሲያ መንግስት በሶሪያ ላይ እያካሄደ ያለው የአየር ጥቃት ከአሜሪካው የአየር ጥቃት ጋር
ግጭት ፈጥሮ አደገኛ ሁኔታ እንዳይከሰስት ለመከላከል ሁለቱ አገሮች ተነጋግረው ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለጸ። የስምምነቱ
ዝርዝርዝ ነጥቦች ምን እንደሆኑ ባይገለጽም አንዱ አገር ጥቃት በሚያካሄድበት ወቅት ሌላኛው መረጃ የሚደርስበትን ሄኔታ ለማመቻቸት
የሚችል ፕሮቶኮል በጋራ ቀይሰው የተስማሙ መሆናቸው ተነግሯል። ይህ በዚህ እንዳለ የሶሪያው ፕሬዚዳንት አሳድ ወደ ሞስኮ ሄደው
ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ተገልጿል። ባለፉት አራት አመታት ፕሬዚዳንት አሳድ ከሶሪያ ውጭ ሲወጡ
ይህ የመጀመሪያቸው ነው ተብሏል። አሳድ
ከፑቲን ጋር ለሶስት ጊዜ ያህል ተገናኝተው በቅርቡ በጋራ እየወሰዱ ባሉት ወታደራዊ እርምጃ እና በአገሪቱ የፖሊቲካ ሁኔታ ላይ
የተወያዩ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ከስብሰባው በኋላ ፑቲን ለጋዘጠኞች በሰጡት መግለጫ አሁን በሚካሄደው ወታደራዊ እርምጃ
ምክንያት ዘላቂነት ያለውና በሶሪያ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም የፖሊቲካ የብሔረሰብና የሃይማኖት ክፍሎችን የሚያጠቃልል የረዥም ጊዜ
መፍትሔ
ለማስገኝት የሚቻል መሆኑን ተናግረዋል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን በፓለስታይን ዜጎችና
በእስራዕሎች
መካከል እየተካሄደ ያለውን ግጭትና ደም መፋሰስ ለማስቆም በአካባቢው ያልተጠበቀ ጉብኝት ያደረጉ መሆናቸው ተገለጸ። ባንኪ ሙን
በእየሩሳሌም ለጋዜጠኞች በሰጡት ወደ አካባቢው ያመጣቸው የሁኔታው አሳሳቢነት
መሆኑን ገልጸው ባስቸኳይ መቆጣጠር ካልተቻለ ሊመለስ ወደማይቻልበት አደገኛ
አዝማሚያ ይሄዳል ብለዋል። የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ነታንያሁን ካነነጋገሩ በኋላም ለጋዘጠኞች በሰጡት መገለጫ ግጭቶችን
ለማብረድ ብቸኛው መንገድ የተያዙትን መሬቶች መሬቶች ከመልቀቅ ጀምሮ በድርድር በሚመጣ ሁለገብ የፖሊካ መፍትሔ ነው ብለዋል።
ባንኪ ሙን ለፓለስቲኒያን
ወጣቶች ባደረጉት ንግግርም ያሉበትን አሳዛኝ ሁኔታ ከልብ
የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸው
ሁኔታውን ለመቀየር መሳሪያና ኃይል እንደማይጠቅም ተናግረዋል። በሌላ በኩል
ለእስራዕል ዜጎችም ባደረጉት ንግግር “ሰላምና ጸጥታ ለማግኘት ያላቸውን ፍላጎት እሳቸውም እንደሚያጋሯቸው ገልጸው ቤቶች
በማፍረስና በጸጥታ ኃይሎች አማካይነት የሃይል እርምጃዎች መውሰድ ግን
የሚፈልጉት
ሰላምንም ሆነ ጸጥታውን እንደማያገኙት አስረድተዋል። የፓለስታይኑን መሪ ፕሬዚዳንት አባስን ራማላ በተባለው ከተማ አነግጋርረው
ከወጡ በኋላ በሰጡት መግለጫ በእስራኤልና በፓለስቲያን አስተዳደር መካከል ትርጉም ያለው ድርድር እንዲደረግ
መሆኑን ከፍተኛ ጥረት የሚያደርጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ጥቅምት 9 ቀን 2008 ዓ.ም
የአፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል( African Standby Force) የሚል ስያሜ
የተሰጠውና ቋሚ ሆኖ በተጠባባቂነት እንዲያገለግል የታቀደው የአፍሪካ ህበረት የሰላም አስከባሪ የኃይል ለወታደራዊ ስልጠና
መሰባሰቡ ተገለጠ። ከአምስት የአፍሪካ የኢኮኖሚ ክፍሎች የተውጣጣውና በቁጥር እስከ 25 ሺ ይደርሳል ተብሎ ከተተገመተው
ተጠባባቂ ኃይል ውስጥ 5000 የሚሆኑ ከየአገሩ የተውጣጡ የፖሊስና የመከላከያ
ሠራዊት አባላት
ዛሬ ማክሰኞ በደቡብ አፍሪካ ስልጠና የሚጀምሩ መሆናቸው ተነግሯል። ወታደራዊ ስልጠና የሚቆየው
እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ሲሆን ለልምምድ ተብሎ በታቀደ ቦታ እንቅስቃሴ አድርገው ብቃታቸው ይመዘናል ተብሏል።
በአፍሪካ
ውስጥ የሚነሱትን የእርስ በርስ ጦርነቶችና ግጭቶችን ለማብረድ አፍሪካ የሌሎች አገሮችን እርዳታ ጠባቂ መሆን ስለሌለባት ይህን
ኃይል ማደረጀት ያስፈለገው በሚል ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለስልጣኖች ይገልጻሉ።
በአመት
ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ በጀት የሚያስፈልገውን ግዙፍ ኃይል ለማንቀሳቀስ
አፍሪካ የውጭ እርዳታ የምትጠይቅ በመሆኑ በሌሎች እርዳታ ላይ መተማመኑ አይቋረጥም ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ። ከዚህም በላይ ይህን
አደራጅቶ ለማንቀሳቀስ የማስተባበር ችግር ያለ ሲሆን
ኃይሉን በማደራጀት አንዳንድ አገሮች የሚያሳዩት ፍላጎት ዝቀተኛ ነው። ተጠባባቂው
የሰላም አስከባሪ ኃይል በአፍሪካ
ህብረት አባላል አገሮች ውስጥ በማንኛውም ወቅት
የጅምላ
እልቂት የሰው ልጅ የማጥፋት ወንጀልና የጦርነት ወንጀሎች በሚከሰትባቸው አገሮች ውስጥ ሳይጠራ ጣልቃ የሚገባ ኃይል ነው ተብሏል
።
ላለፉት ሰላሳ አመታት በስልጣን ላይ የቆዩት የኮንጎው ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ
እንዲወዳደሩ የሚያስችላቸው የሕግ መንግስት ለውጥ ለማድረግ እሁድ ዕለት ሕዝቡ ድምጽ እንዲሰጥ የታቀደ መሆኑ
የሚታወስ
ሲሆን ተቃዋሚዎች ይህን በመቃወም የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑ ታውቋል። ፕሬዚዳንቱ ከሁለት ጊዜ በላይ
እንዳይወዳደርና ዕድሜውም ከሳባ አመት በላይ እንዳይሆን የሚከለክለውን ሕገ መንግስት ለመቀየር
ለሰላሳ
አመታት በስልጣን የቆዩት እና ዕድማዕያቸው ሰባ ሁለት ዓመት የሆኑት ፕሬዚዳንት የሚያደርጉት ሙከራ መፈንቅለ መንግስት ማካሄድ
ነው በማለት ተቃዋሚዎች ባለፈው ቅዳሜ ከፍተኛ ትዕይንተ ሕዝብ ያደረጉ ከመሆናቸውም በላይ በዛሬው እለትም በዋናው ከተማ
በብራዛቪል ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞ ስልፎች ተደርገዋል። ወጣቶች በቡድን እየሆኑ በተለያዩ የከተማዋ ቦታዎች ጎማዎችን
በማቃጥል ተቃውሟቸውን መግለጻቸው የተነገረ ሲሆን
ፖሊስ
በየቦታው ስልፉን ለመበተን በየቦታው የተሰማራ መሆኑን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። መንግስት የሞባይል እና የኢንተርኔት አገልግሎትም
ማቋረጡና ሱቆች፣ ትምህርት ቤቶችና አገልግሎት ሰጭ የሆኑ ሕዝባዊ ድርጅቶች መዘጋታቸው ተነግሯል።
በናይጀር ዋና ከተማ በኒያሚ ውስጥ በትናንትናው ዕለት የሁለተኛ ደረጃና የኮሌጅ
ተማሪዎች የትምህርት ሁኔታዎች እንዲሻሻሉ በመጠየቅ የተቃውሞ ስልፍ አድርገው የዋሉ ሲሆን ፖሊስ በወሰደው እርምጃ 7 ሰልፈኞች
መጎዳታቸውና ወደ 80 የሚጠጉ ደግሞ የታሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።
በቂ
አስተማሪዎች እንዲመደብላቸውና የሚማሩበት ክፍልቾም እንዲጨምሩላቸው ቀደም ብለው የጠየቋቸው
ጥያቄዎች በቂ መልስ ባለማግኘታቸው ተማሪዎቹ ስልፉን ማካሄድ መገዳዳቸውን
ገልጸዋል። የተቃውሞ ስልፉ ሰላማዊ እንዲሆን ጥረት ቢያደርጉም ፖሊስ ሰልፉን ለመበተን በወሰደው አላስፈላጊ እርምጃ ምክንያት
ግጭቶች የተከሰቱ መሆናቸውንም ተናግረዋል። ዘጠና ከመቶ የሚሆነውን የተማሪዎቹን ጥያቄዎች መመለሳቸውን የመንግስት ተወካዮች
ቢገልጹም ተማሪዎቹ ጥያቄያቸው ካልተመለሰ ተመሳሳይ ስልፎች ለማድረግ እቅድ ያላቸው መሆኑን ተናግረዋል። በተባበሩት መንግስታት
የእድገት መለከያ መሰረት በድህነት ከዓለም የመጨርሻውን ቦታዎች ከያዙት መካከል
አንዷ
ናይጀር መሆኗ ይታወቃል ።
ባለፈው ሰኞ በሊብያ ምስራቃዊ ከተማ ውስጥ በተተኮሰ የመድፍ ጥይት አምስት ሰዎች
መሞታቸውን የሆስፒታል ምንጮች ገልጸዋል። ከሞቱት መካከል አብዛኞቹ ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ሲሆኑ አድራጊው ማን
እንደሆን ባይታወቅም ጥቃቱ
የተፈጸመው ላይቲ በተባለቸው ከተማ ውስጥ እንደሆነ ተነግሯል።
በሌላ
በኩል ደግሞ
ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ቡድን ጥፋተኛ ናቸው ባላቸው ሁለት ሰዎች ላይ የቅጣት
እርምጃ የወሰደ መሆኑን ገልጿል። ቡድኑ በኢንተርኔት ባስተላለፈው የቪዲዮ መልእክት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውን መግንስት
በወታደርነት በማገልግል ወንጀል ፈጸመዋል ያላቸውን አንድ የደቡብ ሱዳን የክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆነው ግለሰብና
አንድ
የሊቢያ ተወላጅ የሆነውን መግደሉን አሳውቋል። ሰኞ ዕለት በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኘው የሊቢያ ምክር
ቤት የተመድን የዕርቅ ሀሳብ ውድቅ ማድረጉን የዜና ምንጮች ተናግረዋል።
ጥቅምት 8 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ትናንት እሁድ በኢየር ሸቫ በምትባለው የደቡብ እስራኤል ከተማ አንድ የኤርትራ ተወላጅ
ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ተመትቶ ከወደቀ በኋላ በአካባቢ በነበሩ ሰዎች ከባድ ድብደባ ስለደረሰብት ህይውቱ ሊያልፍ ችሏል።
የኤስራኤል የጸጥታ ኃይል ቃል አቀባይ በሰጠው መረጃ መሰረት ኤርትራዊ ስደተኛ በእስራኤል ወታደር በጥይት ሊመታ የቻለው
ቀደም ብሎ አንድ
የእስራኤል
ወታደር ገድሏል ከሚል የተሳሳተ መረጃ በእስራኤል ፖሊሶች በተተኮሰ ጥይት ከተመታ በኋላ በአካባቢ የነበሩ ሰዎች ተረባርበው
ቀጥቅተውታል ብሏል። ለህክምና ወደ ሆስፒታል ቢወሰደም ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነብር ከሞት ሊድን አልቻለም። በአካባቢዎ የነበሩ ሰዎች
ጭካኔ በተሞላበት መንገድ የደበደቡበት ምክንያት ግልጽ ባይሆንም
የግለሰቡ
በዚህ ዓይነት መንገድ መገደል በእስራኤል አገር ተስፋፍቶ የሚገኘው ዘረኛነት የደረሰበትን ደረጃ ያሳይል ሲሉ ታዛቢዎች ይተቻሉ።
Ø
በደቡብ
አፍሪካ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚማመሩ ተማሪዎች ለትምህርት የሚከፍሉት ገንዘብ በጨመሩ ምክንያት የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ
መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ተማሪዎቹ ወደዮኒቨርስቲዎቹ የሚያስገቡትን መንገዶች በመዝጋትና
ጎማና ላስቲኮችን በማቃጠል ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። በዚህ ዓመት የትምህርት ክፍያው
በ10 ከመቶ እንዲጨምር በመደረጉ በተለይ ከደሃ ቤተሰብ የመጡ በርካታ ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ጭማሪውን ለመክፈል የማይችሉ
መሆናቸውን ገልጸዋል። የዩኒቨርስቲዎቹ አስተዳዳሪዎች ትምህርት ለጊዜው ተቋርጦ ክፍሎቹ እንዲዘጉ ያደረጉ ሲሆን ችግሩ ለምን ያህል
ጊዜ ሊቆይ እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም። ጸጥታውን ለመቆጣጠር ፖሊስ በየኒቨርስቲዎቹ የተሰማራ መሆኑ ተነግሯል። የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ቀደም ብለው የገለጹ ሲሆን አሁን በመጨርሻ በተገኘው ዜና መሰረት መንግስት የ10 ከመቶ
ጭማሪውን ለጊዜው ያገደ መሆኑ ታውቋል።
Ø
እሁድ ዕለት በግብጽ የተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ አስመልክቶ ለምርጫው የወጣው ሕዝብ
ቁጥር በጣም አነስተኛ ሲሆን የግብጽ መንግስ ሰኞ ዕለት ለሚቀጥለው ምርጫ
ለሰራተኞች
የግማሽ ቀን ፈቃድ የሰጠ መሆኑ ተነገረ። የትናንቱና የዛሬው ምርጫ የተካሄደው በ ግብጽ 14 ጠቅላይ ግዛቶችና በ ጊዛ እና
በአሌክሳንድሪያ ከተሞች ሲሆን በሌሎች 13 ጠቅላይ ግዛቶችና በካይሮ ደግሞ በሚቀጥለው ወር ይካሄዳል ተብሏል። በትናትናው ዕለት
ምን ያህል ሰው ወጥቶ ድምጽ እንደሰጠ ከመንግስት በኩል የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም ሁኔታውን ተዘውረው የተመለከቱት ታዛቢዎች
ወደምርጫ ጣቢያዎቹ የሄደው ሰው ቁጥር በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጸዋል። እንዳዳዱቹ ቁጥሩ ከሁለት ከመቶ እንደማይበልጥ ሲገልጹ
የመረጡትም ቢሆን እድሜያቸው የገፋ እንጅ ወጣቶች እንዳልሆኑ ተናግረዋል። አንዳንድ ታዛቢዎች
ወደምርጫ ጣቢያዎቹ ቁጥር
አነስተኛ
መሆን
ሕዝቡ ለወታደራዊ መንግስት ያለው ድጋፍ አነስተኛ ነው በማለት የሙባረክ የስልጣን ዘመን
የፖሊቲካ ሁኔታ እየተደገመ መሆኑን ይገልጻሉ።
Ø
ባለፈው ቅዳሜ ምሽት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች የሆኑ ሴቶች
ባፈነዷቸው ቦምቦች 11 ሰዎች ሲሞቱ ሌሎች በርካታ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን ፖሊስ እሁድ ዕለት ከሰጠው መግለጫ ማወቅ ተችሏል።
አጥፍቶ ጠፊዎቹ ቦምቦቹን ያፈነዱት በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ “አዳማዋ” በሚባለው ግዛት ውስጥ ባለ “ዳር” በሚባለው መንደር
ሲሆን
ቦምቦቹን ለማፈንዳት የቻሉት የቦኮ ሃራምን ጥቃት ፈርተው ወደጫካ
በተሰደዱ ዜጎች መሀል ተመሳስለው በመቀላቀላቸው
መሆኑ ተዘግቧል። የሞቱትን ሰዎች ቁጥር አስመልክቶ በቦታው ላይ የነበሩ አንዳንድ
ሰዎች የሚሰጡት ግምት ከፍ ያለ ቢሆንም ፖሊስ
11 ሰዎች ብቻ መሆናቸውን አረጋግጧል። ከዚህ ቀደም አካባቢው በቦኮሃራም ታጣቂዎች በተደጋጋሚ የተጠቃ ሲሆን ጸጥታውን ለመቆጣጠር
በቂ ወታደሮች ባለመመደባቸው ሁልጊዜ በፍርሃት የሚኖሩ መሆናቸውን በመግለጽ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ያሰማሉ።
በተያያዘ ዜና በዚሁ በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በማይዱጉሪ ከተማ አንዲት አጥፍቶ
ጠፊ በቦርሳዋ የያዘችውን ቦምብ ለማፈንዳት ወደ ዋናው ወታደራዊ ካምፕ
ለመግባት ስትሞክር በአንድ ወታደር በተተኮስ ጥይት ስትመታ ቦምቡ ፈንድቶ
የገደደላት መሆኑ ታውቋል። የፈንዳው ቦምብ ሌላ ያስከተለው ጉዳት እንደሌለም ተገልጿል። ከመስከረም አጋማሽ እስካሁን ባለው ጊዜ
ብቻ በናይጄሪያ በቦኮሃራም ጥቃት ከ100 በላይ የሆኑ ሰላምዊ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ
የተመረጡት
ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ደግሞ 1370 ሰዎች መገደላቸው
ተነግሯል። ቦኮሃራም በሰሜን ምስራቅ እየሰነዘረ ያለውን ጥቃት የመንግስት ምንጮች የሽንፈትና የቀቢጸ ተስፋ ምልክት ነው ሲሉ
ሌሎች ደግሞ መንግስት አዳክሜዋለሁ ቢልም
ቦካሃራም አሁንም ቢሆን በጥንካሬ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ መሆኑን የሚያሳይ ነው
ይላሉ።
በሊቢያ ያሉት ተጻራሪ ወገኖች የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት በሊቢያ የእርቅና የአንድነት
መንግስት ስለሚቋቋምበት ሁኔታ ያቀረበውን ሀሳብ ተቀብለው ተግባራዊ እንዲያደርጉ
የምዕራብና የአረብ አገሮች ባወጡት የጋራ መግለጫ ጠይቀዋል። የጋራ መግለጫው የወጣው በአልጄሪያ፣ በእንግሊዝ፤ በፈረንሳይ፤
በጀርመን፤ በጣሊያን፤ በሞሮኮ፤ በቃጣር ፤ በስፔን፤ በቱኒሲያ በቱርክ በተባበሩት የአራብ ፤ኤምሬት እና
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የአውሮፓው ኅብረት የፖሊሲ ሹም
ሲሆን በሊቢያ በተመድ አማካይነት እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት እና ድርድር ላይ
የነበሩ ወገኖች ሁሉ የተደረሰበትን ስምምነት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጥሪ ያደርጋል። በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተመስርተው
የነበሩ ሁለት መንግስት ነን የሚሉ ክፍሎችን ለማስታረቅ በተመድ አማካይነት ድርድር ሲካሄድ የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ጊዚያዊ
የአንድነት መንግስት እንዲመሰረት ተመድ ሀሳብ ማቅረቡ ይታወቃል።
የአንድነት መንግስቱን
ፋይዝ ኤል ሲራጅ በተባሉ የትሪፖሊው ምክር አባል እንዲመሩትና
እንዲሁም ከምስራቅ ከምዕራብና ከደቡብ የሚወክሉ አንዳንድ ምክትል ጠቅላይ
ሚኒስትሮች እንዲመደቡ በተመድ በኩል
ሀሳብ መቅረቡ ይታወሳል።
ጥቅምት 6 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የዓለም ባንክ በትናንትናው ዕለት ይፋ ባደረገው ዓመታዊ ዘገባ
ባለፉት 20 ዓመታት በአፍሪካ ውስጥ ድህነት በመጠኑም የቀነሰ መሆኑን ጠቅሶ
የሕዝብ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ በመጨመሩ ምክንያት በከፍተኛ የኑሮ ችግርና በስቃይ የሚኖሩ ዜጎች ቁጥር አሁንም ቢሆን ከፍተኛ
መሆኑን ገልጿል። ባንኩ በ1982 ዓም ከአፍሪካ ሕዝብ መካከል 56 ከመቶ የሚሆነው
በቀን አንድ ዶላር ከዘጠና ሳንቲም በታች በሆነ ገቢ ይተዳደር እንደንበርና
በ
2005 ዓም ወደ ቁጥሩ ወደ 43 ከመቶ ዝቅ ማለቱን ጠቅሷል። የድህነቱ መጠን በ25 ዓመታት ውስጥ 13 ከመቶ ያህል ዝቅ ቢልም
አሁንም ቢሆን ወደ ግማሽ የሚሆነው የአፍሪካ ሕዝብ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይኖራል ተብሏል። ከሌሎቹ ክፍለ ዓለማት ይልቅ ድህነት
በአፍሪካ ውስጥ ስር ሰዶ የሚገኝ መሆኑን ዘገባው ጠቅሶ 388 ሚሊዮን የሚሆኑ የአፍሪካ ዜጎች በድህነት አረንቋ ውስጥ እንደሚኖሩ
ዘርዝሯል። የዛሬ 25 ዓመት 600 ሚሊዮን የነበረው የአፍሪካ የሕዝብ ብዛት ከአስራ አምስት ዓመት በኋላ ወደ 1.6 ቢሊዮን ከፍ
ሊል እንደሚችል ተገልጿል። ዘገባው የድህነቱ ሁኔታ ከአገር አገር ና በከተማና በገጠር መካከል ልዮነት እንዳለው በመግለጽ
አንዳንድ አገሮች መሻሻል ያሳዩ መሆናቸውን አትቶ የወያኔ አገዛዝ መጠነኛ መሻሻል ከታየባቸው አገሮች መካከል አንዱ መሆኑን
ጠቁሟል። ድህነት
ተስፋፍቶ በገሃድ በሚታይበት አገርና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ድህነትን ሸሽተው አገራቸውን እየጣሉ በሚወጡበት ሁኔታ መሻሻል አለ
የሚለውን የባንኩን ዘገባ የሚጠራጠሩ በርካታ ምሁራን ናቸው።
Ø
ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ
ባጋ
በተባለችው በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ውስጥ በምትገኘው ከተማ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች ያካሄዱትን ወረራና ያደረሱትን ጉዳት በሚገባ
አልተከላከልክም በሚል አንድ የናይጄሪያ ጄኔራል ተከሰው የተፈረደባቸው መሆኑ ተገለጸ። በተባለው ጊዜ ቦኮ ሃራም ጥቃቱን ሲፈጽም
በከተማዋ
የነበረው የናይጄሪያ ጦር በማፈግፈጉ ምክንያት
ታጣቂዎቹ በርካታ ወታደራዊ መኪናዎች 12 ፒክ አፕ ቶዮታዎች ሶስት የሮኬት አምጣቂ
መሳሪያዎችና ከ 12 የበለጡ አውቶማቲክ መሳሪያዎች እንዲሁም በጣም በርካታ ጥይቶች ሊማርክ ችሏል የሚል መረጃ የቀረበ ሲሆን
የቦካ ሃራም ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን ሲገድሉ ሌሎችንም በተለይ ሴቶችን ይዘው
ሄደዋል ተብሏል። በቦታው የነበረው የናይጄሪያ ጦር መሪ ብርጋዴር ጄኔራል ራንሳም ኩቲ ርዳታ በመጠየቅ ጭምር ጦሩ
የቦኮ
ሃራም ታጣቂዎችን በሚገባ እንዲቋቋም ባለማድረጋቸውና
እንዲያፈገፍግ
በመገፋፋታቸው ለስድስት ወራት ያህል እንዲታሰሩና ከሰራዊቱ
እንዲባረሩ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የፈረደባቸው መሆኑ ታውቋል።
ጠበቃቸው ጄኔራሉ ጦሩ እንዲያፈገፍግ ያደረጉት የቦካ ሃራም ታጣቂዎች በቁጥር
በመብለጣቸው ነው የሚል መከራከርያ ቢያቀርብም በዳኞቹ በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። የወታደራዊው ፍርድ ቤት ውሳኔ በወታደሩ
ውስጥ ተስፋፍቶ የነበረውን የተስፋ መቁረጥና የክህደት እንቅስቃሴ
ይቀንሳል
ተብሎ ተገምቷል። በተባበሩት መንግስታት እና በሌሎች
የሰብአዊ
መብት ድርጅቶች ዘገባ የቦኮ ሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረበት ከ2002 ዓም ጀምሮ ከ17 ሺ ሰዎች በላይ መገደላቸው ታውቋል።
Ø
ከጥቂት ሳምንታት በፊት በቡርኪና ፋሶ ተሞክሮ የከሸፈውን መንፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል
ዲየንዴሪ በወታደራዊ ፍርድ ቤት
በ 11 የወንጀል ክሶች መከሰሳቸው በትናንትናው ዕለት የወታደራዊ ፍርድ ቤት ቃል
አቀባይ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል። ከክሶቹ መካከል በሰው ልጆች ላይ ወንጀል መፈጸም የሚለው አንዱ ሲሆን ሌሎች
23
የሚሆኑ ሰዎች አብረው የተከሰሱ መሆናቸው ተነግሯል። ከጄኔራሉ ጋር ከተከሰሱት 23 ሰዎች መካከል
ለታቀደው አጠቃላይ የምክር ቤት
ምርጫ ራሳቸውን በእጩነት አቅርበው የተከለኩት የጄኔራሉ ሚስት አንደኛዋ ሲሆኑ
ሌሎቹ ደግም የምርጥ ቡድኑ ከፍተኛ መኮንኖችና የቀድሞ መንግስት ባለስልጣኖች መሆናቸው ታውቋል።
የቀድሞው ፕሬዚዳንት ባለሟሎች በምርጫ ውስጥ እንዳይገቡ መከልካላቸውን ምክንያት
በማድረግ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ የሚባለው ምርት ቡድን አባላት በአካሄዱት መፈንቅለ መንግስት ምክንያት በተከሰተው የስድስት ቀናት
አለመረጋጋትና የመንገድ ላይ ግጭት 14 ሰዎች መገደላቸውና ከ251 በላይ የሆኑ
መሞታቸው
ይታወቃል። የእነ ጄኔራል ዲየንዴሬ የክስ ሂደት የቀድሞውን ፕሬዚዳንት የሳንካራን ገዳዮች አጋልጦ ወደ ፍርድ ሊያመጣ ይችላል
የሚል ግምት ተሰጥቷል። የክሱና
የምርመራ ሁኔታ እየቀጠለ ከሄደ ከዛሬ 28
አመት በፊት በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነት የነበራቸውን የአገሪቱን ፕሬዚዳንት
ሳንካራን
አስገድለዋል ተብለው የሚጠረጥሩት የቀድሞ ፕሬዚዳንት ካምፕወሬ ለፍርድ ሊቀርቡ ይችላሉ በማለት የወታደራዊ ፍርድ ቤት ቃል አቀባይ
ለጋዘጠኞች ተናግረዋል። የሳንካራ አስከሬን ተመርምሮ በበርካታ ጥይቶች ተመተው እንደሞቱ ተረጋግጧል ተብሏል።
Ø
በማዕካለዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ዋና ከተማ በባንጉዊ ውስጥ በትናንትናው ዕለት በእስልምናና
በክርስቲያን ተከታዮች መካከል እንደ አዲስ በማገርሸት በተፈጠረው ግጭት
አንድ ሰው ሲሞት ሌሎች 10 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን የሆስፒታል
እና የወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል። ግጭቱ የተጀመረው ሐሙስ ማታ አንድ የእስልምና ተከተይ የሆነ ወጣት ጸረ ባላካ በተባሉ
የክርስቲያን ሚሊሺያዎች በመገደሉ ሲሆን በሁለቱ ወገኖች መካከል ግጭቱ ተባብሶ ሌላ አንድ ሰው ሲገደል 10 ሰዎች መቁሰላችው
ተነግሯል። አንዳንድ ነዋሪዎች የሞቱትን ሰዎች ቁጥር ወደ ሶስት ከፍ ያደርጉታል።
አርብ ጠዋት ሁኔታው መረጋጋት የታየበት ሲሆን ቀደም ብሎ ቤታቸውን ጥለው ሄደው
የነበሩ ነዋሪዎች ወደ ቤታቸው ሲመለሱ
ታይተዋል። የዛሬ
ሁለት ዓመት የአገሪቱ መሪና የክርስትና እምነት ተከታይ የነበሩት ፍራንስዋ ቦዚዝ “ሰለካ” የሚል ስም በያዙት
የእስልምና
ተከታይ አማጽያን ከተገለበጡ በኋላ በሁለቱ እምነቶች ተክታዮች መካከል የተፈጠረው ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወትን ያጠፋ መሆኑና
ወደ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብን ያሰደደ መሆኑ ይታወቃል። ለነገ ለመስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው አገራዊ
ምርጫ ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ይታወሳል።
ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ዛሬ አርብ በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በምትገኘው ማይዱጉሪ በምትባለው ከተማ ዕድሜያቸው ከ11 እስከ 15 የሚገመቱ ሴቶች ልጆች
አጥፍቶ ጠፊዎች በመሆን ባፈንዷቸው ቦምቦች 39 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና በርካት ያሉት ደግሞ የቆሰሉ መሆናቸው ከአካባቢው
ከተገኘው ዜና ማወቅ ተችሏል። በትናንትናው ዕለትም በዚሁ ከተማ በሚገኝ አንድ መስጊድ ውስጥ በፈነዱ ቦምቦች ከ32 ሰዎች በላይ
የሞቱ መሆናቸው ታውቋል። ቦምቦቹን ማን አንዳፈነዳቸው ኃይላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም ቦኮ ሃራም የሚባለው አሸባሪ ድርጅት
መሆኑ ተገምቷል። ባልፉት ጥቂት ቀናት ብቻ በዚሁ ከተማ ውስጥ በደረሱ የቦምብ ጥቃቶች ከ100 ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል።
Ø
የኬኒያ የታችኛው የሕግ አውጭ ምክር ቤት
በቅርቡ ህግ ሆኖ እንዲወጣ የወሰነው የሕግ ረቂቂ
በምክር
ቤት አባል ላይ የስም ማጥፋት ተግባር ያካሄደ ማንኛው የሚዲያ ተቋም
እስከ 500 ሺ የኬኒያ ሽልንግ ወይም እስከ 4850 ዶላር ድረስ መቀጫ እንዲከፍል
የሚደነግግ መሆኑ ተገለጸ። የታችኛው ምክር ቤት ምንም እንኳ በዚህ የህግ ረቂቅ ላይ ውሳኔውን ቢሰጥም የአገሪቱ ህግ ሆኖ
የሚወጣው ሴኔት የተባለው የላይኛው የሕግ አውጭ ምክር ቤት ሲስማማበትና ፕሬዚዳን ኡሁሩ ኬኒያታ ሲፈርሙበት ነው።
ከሶስት ዓምት በፊትም ተመሳሳይ የሕግ ረቂቆች ቀርበው የላይኛው የምክር ቤት አካል
ባለመስማማቱ ሕግ ሳይሆን መቅረቱ ይታወሳል። የሕግ አውጭዎቹ ሕጉን ለማውጣት ያስገደዳቸው በምክር ቤት አባላት ላይ በየጊዜው
መሰረት የሌለው ክስ በመገናኚያ ብዙሀን በመጻፉ ነው ይላሉ።
የተለያዩ
የኬኒያ
ጋዜጦች እና የመገኚያ ብዙሃን ተቋሞች በረቂቅ ሕጉ ላይ ያላቸውን ቅሬታ በከፍተኛ ስሜት የገለጹ ሲሆን በርካታ ጋዜጦች የሕግ
ረቂቁን ኮንነውታል፡፤ ዘ ዴይሊ ኔሽን የተባለው ጋዜጣ “ከእንግዲህ ወዲያ የፓርላማ አባላትን የማያስደስቱና በጋዜጣ
የሚወጡ ጽሁፎች ሁሉ ወንጀል ሊሆን ነው” ያለ ሲሆን ስታንዳርድ የተባለው ጋዜጣ
ደግሞ “ረቂቅ ህጉ የምክር ቤቱ አባላት ለመገኚያ ብዙሀን ያላቸውን ጥላቻ የገለጹበት ከመሆኑ ባሻገር የተዘፈቁበት ሙስና
እንዳይጋለጥ ለመከላከል ያደረጉት ጦርነት
ነው”
ብሎ
ይህ ለኬኒያ ትልቅ የሀዘን ቀን ነው ብሏል። ጋዜጠው አስተያየቱን በመቀጠል የምክር ቤት አባላት የሚዘርፉት የመንግስት ገንዘብ፤
የሚያስቀምጧቸው ቅምጦች እና በተቃዋሚዎቻቸው ላይ የሚያደርሱት በደል እንዳይጋለጥ ያቀዱት ተንኮል መሆኑን ገልጾ የመገኛያ ብዙሃን
ነጻነት የማገረሰስ መብት እንጅ ከመንግስት የተሰጠ ችሮታ አይደለም ብሏል። ትራስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም ከዚህ
በፊት ባወጣው ዘገባ መሰረት ኬኒያ በዓለም ካሉ 174 አገሮች ውስጥ 145ኛ በመሆን የተመደበች ሲሆን ባለስልጣኖችን በሙስና
ሲከሰሱ ቆይተዋል። በኬኒያ ሕዝቡ ለመንግስት ባለስልጣናት ጥሩ አመለካከት የሌለው ሲሆን የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ በኬኒያ
የመንግስት ሰራተኛ መሆን የግል ሀብትን ለማካባት ዋናው መንገድ ነው ተብሎ ይታመናል። የኬኒያ ዋናው ኦዲተር በቅርቡ ባደረገው
ምርመራ ከመንግስት ድርጅቶች መካከል ገቢና
እና ወጫቸውን በተገቢው የሂሳብ አያያዝ መንገድ የያዙ አንድ
ከመቶ ብቻ መሆናቸውን ገልጾ ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል።
Ø
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን ባለፈው ማክሰኞ በብሩንዲ ዋና ከተማ
አንድ የዓለም አቀፍ ስደተኛ ድርጅት ባልደረባን ጨምሮ ዘጠኝ ሰላማዊ ሰዎች የተገደሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ድርጊቱን ኮንነው
የብሩንዲ ባለስልጣኖች ጠልቅ ያለ ምርመራ አካሄደው ባስቸኳይ ጥፋተኞችን ለፍርድ ማቅረብ አለባቸው ብለዋል። በግጭቱ
ሁለት
ፖሊሶች የተገደሉ ሲሆን ከሟቾቹ መካከል አንድ የብሩንዲ ጋዘጠኛ እንዲሁም ሚስቱና ሁለት ልጆቹ የሚገኙበት መሆኑ ታውቋል።
የብሩንዲ
ፕሬዚዳንት ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ለምርጫ እቀርባለሁ ካሉበት ጊዜ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረው አመጽና አለመረጋጋት
የበርካታ ሰዎችን ህይወት ያጠፋ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በየቀኑ ሰዎች እየተገደሉ መሆናቸው ተዘግቧል። ባለፈው ነሐሴ ወር
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የብሩንዲ መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ባስቸኳይ እንዲነጋገር ውሳኔ መስጠቱና
ዋና ጸሐፊው ወደ ብሩንዲ መልእክተኛ እንዲልኩ መመሪያ መስጠቱ ይታወሳል። በብሩንዲ መንግስት እምቢተኛነት ምክንያት የተባበሩት
መንግስታት ድርጅት ወደ አገሩ ልዕክ ለመላክ አለመቻሉም ታውቋል።
Ø
በጂቡቲ የመንግስቱ ተቃዋሚ የሆነው ፍሩድ የሚባለው ድርጅት አባል እና ደጋፊ ናቸው ተብለው
የሚጠረጥሩና እንዲሁም የድርጅቱ መሪዎች ዘመዶች የሆኑ ግለስቦች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እየተያዙ መሆናቸውን በመግለጽ
ኦ አር ዲ ኤች ዲ (ORDHD)
በሚል
ምህጻረ ቃል የሚጠራው የጁቡቲ የሰብአዊ መብት ድርጅት
ገለጸ።
የሰብዓዊ መብት
ድርጅቱ የጂቡቱ የጸጥታ ኃሎች ከመስከረም 23 ቀ 2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች ያሰሯቸውን የፍሩድን አባላትና ደጋፊዎች
እና የባለስልጣኖችን ዘመዶች ስም በዝርዝር አውጥቶ ያጋለጠ ሲሆን የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች እርምጃ ፍሩድ የተባለው የአማጽያን
ኃይል በሚያደርገው ወታደራዊ ጥቃት ከመደናገጥ የመጣ ሳይሆን አይቀርም ብሏል።
ጥቅምት 4 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያ ለማድረግ ወደ ቦትስዋና ሄደው ከነበሩ የኤርትራ የእግር ኳስ
ተጨዋጮች መካከል 10 የሚሆኑት ቦትስዋና ውስጥ ቀርተው የፖሊቲካ ጥገኝነት የጠየቁ መሆናቸውን የቦትስዋና ባለስልጣኖች በዛሬው
ዕለት ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። ተጨዋጮቹ ወደ ማረፊያ ሆቴላቸው ከመሄድ ፈንታ በገበያ ውስጥ የቀይ መስቀል መስሪያ ቤትን
በመፈለግ ላይ ሳሉ በፖሊሶች ተይዘው የታሰሩ
መሆናቸው ታውቋል። በቦትስዋና
የሚገኘው የሻዕቢያ አምባሳደር ሰዎቹn ለመረከብ ጥረት ቢያደርግም ተጨዋቾቹ የፖሊቲካ ጥገኝነት ስለጠየቁ ያልተሳካለት መሆኑ
ተገልጿል። የኤርትራ የእግር ኳስ ተጨዋጮች የሻዕቢያው አገዛዝ የሚያካሄደውን አፈናና ጭቆና በመሸሽ
በጊዜው በተለያዩ አገሮች የቀሩ መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን የዛሬ ሶስት ዓመት
በኡጋንዳ ቀርተው የፖሊቲካ ጥገኛነት ያገኙት
15 ተጨዋጮችና አንድ ዶክተር ከብዙዎቹ መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። በቅርቡ አንድ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጥኝ ኮሚሽን ባወጣው ዘገባ የሻዕቢያ አገዛዝ የሚያካሄደውን የሰብአዊ መብት ረገጣ
ሰቆቃዊ
ድርጊቲ ያጋለጠ ሲሆን የኤርትራ ወጣቶች የጊዜ
ወሰን በሌለው ወታደራዊ አገልጎት አለፍላጎታቸው በግዳጅ እንደተሰማሩ ገልጿል። የስፖርተኞች ወሬ ከተነሳ የወያኔን አስከፊ
አገዛዝም በመሸሽ ባለፍቱ ዓመታት በተለያዩ አገሮች የፖሊቲካ ጥገኝነት በመጠየቀ በተለያዩ አገሮች
የቀሩት
ኢትዮጵያውያን አትሌቶችና የእግር ኳስ ተጭዋቾች
ከፍተኛ
ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ የነበሩት የቤኒን የቀድሞ ፕሬዚዳንት በትናንትናው ዕለት ያረፉ
መሆናቸው ተገለጸ። የዴሞክራሲ አባት ተብለው የሚጠሩት የቤኒን የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሚስተር ማቲው ኬሬኩ በተወለዱ
በ82 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሚስተር ኬሬኩ ወደ ስልጣን የመጡት
እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1972 ዓም በተደረገ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ሲሆን
ራሱን
የግራ ርዕዮተ ዓለም አራማጅ በማለት የሚጠራው ብቸኛ ፓርቲ መሪ በመሆን ለ20
ዓመታት በስልጣን ላይ ቆይተዋል።
እአአ
በ1991 ዓም. የብዙሃን ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በመቀበል ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ በመፍቀዳቸው
በወቅቱ
በተካሄደው ምርጫ ከስልጣን የወረዱ መሆናቸው ይታወቃል። እአአ በ1996 ዓም እና በ2001 በተካሄዱ አገራዊ ምርጫዎች በተከታታይ
አሸናፊ በመሆን አገሪቱን የመሩ መሆናቸው ይታወሳል።
Ø
ቦኮ ሃራም ላይ የሚካሄደውን ጥቃት ለማጠናከር የአሜሪካ ወታደሮች የተሰማሩ መሆናቸውን
ፕሬዚዳንት ባራክ
ኦባማ ገለጹ።
የእየር ላይ የስለላ ተግባራትን እንዲሁም ወታደራዊ አሰሳንና ቅኝትን ለማካሄድ
300 የሚሆኑ የአሜሪካ ወታደሮች ወደ ካሜሩን መላካቸው የተነገረ ሲሆን ለግዳጅ
እስከሚፈለጉበት ድረስ በዚያው እንደሚቆዩ ተገልጿል። ወታደሮቹ ለራሳቸው መጠበቂያ የሚሆን የተሟላ ወታደራዊ ቁሳቁሶች
የተመደበላቸው ሲሆን ከሶስት መቶ ወታደሮች ውስጥ ዘጠናዎቹ ባለፈው ሰኞ ወደ ቦታው በቅድሚያ የተላኩ መሆናቸው ተነግሯል።
Ø
የኢቦላ በሽታ ተዋስያን በወንድ አባለ ዘር ውስጥ ለዘጠኝ ወራት ያህል ሊቆይ እንደሚችል
ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገ ጥናት የታወቀ መሆኑን ኒው ኢንግላንድ ጆርናል ኦፍ ሜዲስን የሚባለው መጽሐት በአምዱ ላይ አስፍሮ
አውጥቶታል። በዚህ የመጀመሪያ ጥናት የተደረሰበት ግኝት ከ11 ሺ በላይ የሆኑ ዜጎቻቸው በኢቦላ በሽታ ለተገደለባቸው የምዕራብ
አፍሪካ አገሮች በጣም አሳሳቢ የሆነ የጤና ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል። ከዚህ በፊት አንድ በኢቦላ በሽታ የተለከፈ
በሽተኛ በህክምና ርዳታ ተድርጎለት እስከ 82 ቀን ከቆየ ከኢቦላ ነጻ ይሆናል የሚል አመለካከት ነበር። በሽታው ከዚያን ጊዜ
በላይ የሚቆይ ከሆነ አስጊነቱ እየጨመረ ከመሄዱም በላይ ክትትሉ በርካታ የሰው ኃይልና የገንዘብ ወጭን ይጥይቃል የሚል ግምት
ተወስዷል።
Ø
በትናትናው ዕለት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የደቡብ አፍሪካ ዜጎች በጆሃንስበር ከተማ ዋና ዋና
መንገዶች የተቃውሞ ስልፎች አድርገዋል። በደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ የብረታብረት ሰራተኞች አንድነት ማህበር የተመራው ይህ ግዙፍ
የተቃውሞ ስልፍ በአገሪቱ ተስፋፍቶ የሚገኘው ዓይን ያወጣ የባልስልጣኖች ሙስና በመቃወም የተደረገ ነበር። በተቃውሞ ስልፈኞቹ
ተይዘው ከነበሩት መፈክሮች
መካከል“ ሙስና ይወገድ” “የዙማ መንግስት ይወገድ”
“ ሙስና ደሃውን እየቀረጠ ነው፤ እኛ ሀብታሞች ቀረጥ ይክፈሉ እንላለን”
የሚሉ
እንደነበሩበት ለማወቅ ተችሏል። 13 ሚሊዪን የሚሆነው ሕዝብ በየቀኑ የሚባለው አጥቶ ወደ መኝታ በሚሄድበት
እና 50 ከመቶ የሚሆነው ሰራተኛ ከድህነት መስመር በታች በሆነ ገቢ በስቃይ
በሚኖርበት ሁኔታ ጥቂት ባለስልጣኖች ዓይን ባወጣ መንገድ ተንደላቀው ይኖራሉ በማለት ስልፉን ካስተባበሩት መካከል አንደኛው
ተናግረዋል። ከፍተኛ ዋጋ ያለው የፕሬዚዳንት ዙማ የግል መኖሪያ ቤት ለባለስልጣኖች በሙስና መዘፈቅ እንደምሳሌ የተጠቀሰ ሲሆን
ለመኖሪያ ቤቱ የጸጥታ
መሳሪያዎችን ለማስገባት ብቻ 24 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መከፈሉ አይን ያወጣ የሙስና ተግባር ነው ተብሏል። ከተሰላፊዎቹ
መካከል አንዳንዶቹ በአገሪቱ የሙስናና ባህል ያመጡት ፕሬዚዳንት ዙማ እንደሆኑ ጠቅሰው “እኛን ድሆችን ነጻ ያወጣል ብለን ያልነው
ሰው ጩልሌ መንታፊ ሆነ” ብለው ከሰዋቸዋል። ከ1986 ዓም ጀምሮ በስልጣን ላይ ያለው ዙማ የሚመሩት የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ
በሙስና በመተብተቡ በሚቀጥለው ምርጫ ላያሸንፍ ይችላል የሚሉ በርካታ ናቸው።
በተያያዘ ዜና ረቡዕ ምሽት ላይ
የጆሃንዝበርግንና የፕሪቶሪያን ከተሞች በሚያገናኘው አውራ ጎዳና ላይ ተሰርቶ የነበረ አንድ ጊዜያዊ ድልድይ ወድቆ ሁለት ሰዎች
ሲሞቱ ከሃያ በላይ ሰዎች የቆሰሉ መሆናቸውን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። ከተጎዱት መካከል ቢያንስ አምስቱ በጸና የቆሰሉ በመሆናቸው
የማቾቹ ቁጥር ሊያድግ ይችላል የሚል ስጋት አለ። ድልድዩ ሊወድቅ የቻለበት ምክንያት ምን እንደሆን እስካሁን የተገለጸ ነገር
የለም::
ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በማላዊ እስር ቤት ታግተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ስደተኞች በከፍተኛ ስቃይ የሚኖሩ
መሆናቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና ምንጭ ገለጸ። ጋዜጣው የእስር ቤት ኃላፊዎችን ስደተኞችንና እንዲሁም ወሰን
የለሽ ዶክተሮች የሚባለውን የእርዳታ ሰጭ ተቋም አነጋግሮ ባወጣው ሰፊ ዘገባ ስደተኞቹ በተጨናነቀ ሁኔታ የታሰሩ መሆናቸውን፤ በቂ
የሆነ የመጸዳጃ አገልግሎት እንደሌላቸውና በእስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያለ መሆኑም ጠቅሷል። ጋዜጣው ከእስር ቤት
ኃልፊዎችና ከወሰን የለሽ ተቋሙ ባገኘው መረጃ መሰረት ለ100 ሰው ተብሎ በተሰራ ክፍል ውስጥ 380 እስረኞች ታጭቀው የሚገኙበት
ለ800 እስረኞች ይበቃል ተብሎ በተሰራ
እስር ቤት ውስጥ ደግሞ 2650 እስረኞች ታጭቀው የሚኖሩበት መሆኑን አጋልጠዋል። ዘጠኝ መቶ እስረኞች የሚገለገሉት በአንድ የውሃ
ቧንቧ ሲሆን አንድ መጸዳጂ 120 እስረኞች ይጠቀሙባቸዋል በማለት የእስር ቤቱን አሳዛኝ ሁኔታ ዘርዝሮ ገልጿል። ባሁኑ ወቅት
ከ317 ኢትዮጵያን ስደተኞች በማላዊ እስር ቤት ውስጥ ታግተው ያሉ ሲሆን የታሰሩትም ምክንያትም ኑሯቸንን እናሻሽላለን በማለት
ለስራ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ በህገ ወጥ መንገድ አገር ውስጥ ገብታችኋል ተብለው ነው። የዜና ምንጩ ያነጋገራቸው በርካታ
ኢትዮጵያውን ከአገራቸው የወጡት መኖር የማይችሉበት ችግር ውስጥ በመግባታቸው መሆኑ የገለጹለት ሲሆን ማላዊ ውስጥ በዚህ አሰቃቂ
ሁኔታ መታሰራቸው ደግሞ ከስቃይ ወደስቃይ እንደሆነባቸው ተናግረዋል። አንዱ ኢትዮጵያዊ ለጋዜጣው በሰጠው ቃል ይጓዝ የነበረው ወደ
ደቡብ አፍሪካ እንደነበር ገልጾ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አንድ ዓመት ቢሰራ ኑሮውን ለማሻሻል የሚችል ከመሆኑ ባሻገር ቤት ለመስራት
የሚችል አቅም ሊኖረው እንደሚችል ገልጾ መሆኑን
ገልጾ
ኢትዮጵያ ውስጥ ቀንቶት ስራ ያገኘ ሰው 20 ዓመትም ሆነ ከዚያ በላይ ቢሰራ እንኳን ቤት
ለመስራት ለኑሮው ጠብ የሚል ገቢ የማያገኝ መሆኑን አስረድቷል። አብዛኞች እስረኞች የታሰሩት ባለፈው ዓመት ሰኔ ላይ ሲሆን
የተጣለባቸውን የገንዘብ በመክፈልም ሆነ የተፈረደባችውን የእስራት ጊዜ ቢያጠናቅቁም ከእስር ሳይወጡ የስቃዩን ኑሮ እንዲኖሩ
የተገደዱ መሆናችውን ገልጸዋል። የማላዊ ባለስልጣኖች እስረኞቹን ለማጓጓዝ በቂ ገንዘብ ባለመኖሩ እስረኞቹ በእስር ቤት አጉረው
ለማቆየት የተገደዱ መሆናቸውን ይናገራሉ። ኢትዮጵያውያን በእንዲህ ዓይነት የስቃይ ኑሮ ውስጥ መውደቃቸው አሳዝዛኝና የሚወገዝ
ተግባር ሲሆን አስፈላጊው ጥረት ተደርጎ ነጻነታቸው ማግኘት የሚችሉበትን ሁኔታ መፍጠር ያስፈላጋል ተብሏል።
በርካታ
ኢትዮጵያን የወያኔ አስከፊ አገዛዝ እየሸሹ ከአገራችው መውጣት መቀጠላቸው የወያኔ ጥምር አሃዝ እድገት ምን ያህል ባዶ መሆኑን
ያሳያል ሲሉ በጉዳዩ ላይ እውቀት ያላቸው ዜጎች ይተቻሉ።
Ø
በብሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ ውስጥ አንድ የመንግስት ቴሌቪዥን የካሜራ አንሽ የሆነ ሰውና
ቤተሰቦቹ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች የተገደሉ መሆኑን የዜና ምንጮች ገለጹ። ሰዎቹ የተገደሉት በተጻራሪ ኃይሎች ታግቷል የተባለው
አንድ ሌላ ሰው ለማስፈታት ባካሄዱት የአሰሳ ተኩስ ሲሆን
በጠቃላላው አስር ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው ታውቋል። በከተማዋ
የመሳሪያና
የፈንጅ ድምጽ ሌሊቱን በሙሉ ሲሰማ ያደረ ሲሆን ያደረሰው ጉዳት ግን እስካሁን አልታወቀም። ባለፈው ሚያዚያ ወር ጀመሮ በብሩንዲ
የፖሊቲካ አለመረጋጋት ቀጥሎ በተቃዋሚዎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል በተካሄዱ ግጭቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸው ታውቋል።
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የብሩንዲ የጸጥታ ዋና ሹም ከግድያ ማምለጣቸውም ይታወሳል።
Ø
በመስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም
በናይጀሪያ
ዋና ከተማ በአቡጃ አጠገብ በሚገኙ ሁለት ቦታዎች ቦምቦች ፈንድተው ጉዳት ማድረሳቸው የሚታወስ ሲሆን
እነዚህን
የቦምብ ጥቃቶች በማቀድና ተግባራዊ በማድረግ በኩል አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን
ሁለት
ተጠርጣሪ ግለሰቦች ፖሊስ በቁጥጥር ስር ማድረጉን
አስታውቋል። ኩጄ እና ኒያና በሚባሉ ሁለት ከዋና ከተማዋ ቅርብ በሆኑ ከተሞች
ውስጥ በፈነዱት ቦምቦች 18 ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል። ፖሊስ በመግለጫው ላይ አክሎ እንዳሳወቀው ሌሎች
የቦምቦ ጥቃቶችን ለማድረስ ሲያቅዱ የነበሩ ሰዎች የተያዙ መሆናቸውን ገልጾ 12
በቤት ውስጥ የተሰሩ ቦምቦችና 28 የኢሌክትሮኒክ ማቀጣጠያ መሳሪያዎች አብረው የተያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተጥርጣሪውቹን ፍርድ
ቤት እንዲሚያቀርብ ፖሊስ ጨምሮ አስታውቋል።
በተያያዘ ዜና በትናንትናው ምሽት
በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ በምትገኘው ማይዱጉሪ በምትባለዋ ከተማ ሶስት አጥፍቶ ጠፊዎች በነዋሪዎች መንደር ውስጥ ባፈነዷቸው
ቦምቦች ሰባት ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ተገልጿል። ሶስቱም ቦምቦች የፈነዱት በየሶስት ደቂቃ ልዩነት ሲሆን ሶስቱም አጥፍቶ ጠፊዎች
አብረው መሞታቸውና ሌሎች 11 ሰዎች በፈንጅዎች ፍንጣሪ መጎዳታችው ተዘግቧል። ባለፉት አራት ሳምንት ብቻ በከተማዋ ከ100 በላይ
ሰዎች የሞቱ መሆናቸው ሲታወቅ የትናንቱም ጥቃት የተካሄደው በቦካሃራም መሆኑ ይጠረጣል።
Ø
ማክሰኞ ዕለት በሰሜን ማሊ በቲምበክቱ አካባቢ የሮኬት አምጣቂ መሳሪያዎችን የታጠቁ አማጽያን
በወታደሮች ታጅቦ በሚንቀሳቀስ ኮንቮይ ላይ ባካሄዱት ጥቃት ስድስት ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸውንና
ሌሎች
ሁለት ሰላማዊ ሰዎችና አንድ ወታደር ማቁሰላቸውን የማሊ መንግስት ቃል አቀባይ ገለጸ። እስካሁን ጥቃቱን መፈጸሙን አምኖ
ኃላፊነቱን የወሰደ ክፍል ባይኖርም መንግስት ሽብረተኞች የሚላቸው እስላማውያን አማጽያን ሳይሆኑ ናቸው የሚል ጥርጣሪ እንዳለው
ተናግሯል። በማሊ ያለው የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ኃይል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከስድስት በላይ ሊሆን እንደሚችል
ገምቷል ። ከሶስት
ዓመት በፊት ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለው እስላማዊ ቡድን የሰሜን ማሊን ግዛት
ቁጥጥር ስር ማድረጉና
በኋላም
በፈረንሳይ ወታድሮች ጥቃት
ደርሶበት አካባቢውን ለቅቆ መውጣቱ ይታወሳል። ባለፈው ሰኔ በማሊ መንግስትና
ቱዋረግ በሚባሉ አማጽያን መካከል የሰላም ስምምነት ቢፈረምም አሁንም ቢሆን ሰፋ ያሉ ግዛቶች ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ መሆናቸው
ይታወቃል።
ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በጊኒ የተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ውጤት በይፋ ከመነገሩ በፊት በምርጫው የተሳተፉት አብዛኞቹ
የገዥው ፓርቲ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ አለመሆኑን በመጥቀስ አዲስ ምርጫ እንዲካሄድ በትናንትናው ዕለት
ጠይቀዋል። እሁድ ዕለት በተካሄድው ምርጫ ላይ ምንም ዓይነት ግጭት ያልታየ ሲሆን የመራጩ ሕዝብ ቁጥርም በርካታ ነው ተብሏል።
ከተቃዋሚዎች ውስጥ በግምባር ቀደምትነት የተሰለፈው ፓርቲ መሪ ሴሉ ዳለየን ዲያሎ ሌሎች ስድስት የተቃዋሚ መሪዎች በተገኙበት
በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተደረገ የተባለው ምርጫ ማጭበርበር የሞላበት በመሆኑ እንዲሰረዝና ሌላ አዲስ ምርጫ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።
ምርጫው ነጻና ፍትሀዊ አለመሆኑን ከሰጡት ምክንያቶች አንዳንዶቹ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ዘግይተው መከፈታቸው፣ በርካታ መራጮች
ያለመታወቂያ እንዲመርጡ መደረጋቸው ፣ በመዝገብ ላይ ስማቸው የሌለ ሰዎች እንዲመርጡ የተፈቀደላቸው መሆኑ እና ሌሎችም ናቸው።
ሚስተር ዲያሎ ምርጫው ሲካሄድ ከፍተኛ ማጭበርበር ተደርጓል ካሉ በኋላ ደጋፊዎቻቸው ተከታታይ ሰልፎች ያደርጋሉ የሚል መልእክት
አስተላልፈዋል። የገዥው ፓርቲ ቃል አቀባይ በበኩላቸው ምርጫውን አስመልክቶ ተቃውሚዎች የሰነዘሩት
ክስ
አስገራሚና አስቂኝ ነው ካሉ በኋላ ህዝቡ በትዕግስት ውጤቱን እንዲጠብቁ ጠይቀዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባንኪ ሙን ምርጫው አለምንም ግጭት
መካሄዱ ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸው በሁሉም በኩል ትዕግስት እንዲኖር ተማጽነዋል። ሌሎቹ ስድስት የተቃዋሚ መሪዎች እንደ ሚስተር
ዲያሎ ምርጫው ነጻና ፍትሐዊ አይደለም ቢሉም ደጋፊዎቻቸው ተቃውሞ እንዲያሰማ አልጠየቁም። እንዲያውም ከእነሱ ውስጥ አንደኛዋ
የተቃዋሚ ድርጅት መሪ እንደገዥው ፓርቲ ሕዝቡ መረጋጋት ያለበት መሆኑን በመግለጽ ጥሪ አድርገዋል። የድምጽ ቆጠራው ከተጠናቀቀ
የምርጫው ውጤት
ማክሰኞ ዕለት ይገለጣል የተባለ ሲሆን በሕዝቡ በኩል ያለው ተቀባይነት ምን ሊሆን እንድሚችል
ወደፊት ሊታይ ይችላል ተብሏል።
Ø
በተባበሩት መንግስታት የሴቶች ተቋም ተዘጋጀቶ ትናንት ሰኞ ይፋ የተደረገው ባለ400 ገጽ
ዘገባ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በየቦታው የፈጸሟቸውን ወንጀሎች አይቶ ብይን ሊሰጥ የሚችል አንድ ዓለም አቀፍ
ትሪቡናል እንዲቋቋም ጠየቀ። ይህ ጥሪ የተደረገው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት በተለያዩ
የአፍሪካ አገሮች በተለይም በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ህጻናትን አስገድዶ መድፈር የሚለውን ጨምሮ የተለያዩ ወንጀሎች በዜጎች
ላይ ፈጽመዋል የሚሉ ክሶች
ከተሰሙ በኋላ ነው። ዘገባው የተዘጋጀው በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶችን እኩልነት ለማስጠበቅና ሰብእናቸው ለማስከበር በሚንቀሳቀሰው
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሴቶች ጉዳይ ተቋም ሲሆን ዘገባው የቀረበውም የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ሰለሴቶች ጉዳይ ያስተላለፈው
ታሪካው ውሳኔ 15ኛው ዓመት በተከበረበት ወቅት ነው። ዘገባውን ያዘጋጁት ክፍሎች በሰጡት መግለጫ አሁን ባለው አሰራርና ህግ
መሰረት ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ወታደሮች ጉድያቸው የሚታየው በየአገሮቻቸው ሕግና ደንብ መሰረት በመሆኑና እያንዳንዱ አገርም
የራሱን ወታደር ለፍርድ የማቅረብ ፍላጎት የሌለው በመሆኑ
አንዲሁም
በተጨማሪ አንዳንድ አገሮች ፍላጎቱ እንኳ ቢኖራቸው የተሟላ የፍርድ ተቋም የሌላቸው በመሆኑ ለሚፈጸሙት ወንጀሎች ፍትህን
ለማስገኘት
የተሟላ ዓለም አቀፍ የፍርድ ተቋም ያስፈልጋል ብለዋል። ዘገባው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት
የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ መጨመር ያለበት መሆኑን ጠቁሟል። በዛሬው ዕለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት
የጸጥታው ምክር ቤት ስለሴቶች ሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ይመክራል ተብሏል።
Ø
ወደ ሰባ የሚደርሱ የሱዳን ዜጎች ራሱን እስላማዊ መንግስት የተባለውን አሸባሪ ቡድን
የተቀላቀሉ መሆናቸውን የአገሪቱ የአገር ውስጥ ሚኒስቴር በትናትናው ዕለት ገለጹ። አሸባሪውን ቡድን ከተቀላቀሉት መካከል
የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚገኙባችው ሲሆን አንዳንዶቹም የአሜሪካ የካናዳና የእንግሊዝ ፓርስፖርቶች የያዙ መሆናቸው ታውቋል።
ሚኒስትሩ ከሌልች አገሮች ጋር ሲወዳደር ከሱዳን አሸባሪውን ቡድን ለመቀላቀል ከሱዳን የሄዱት አነስተኛ መሆናቸውን ገልጸው ከቱርክ
መንግስት ጋር በተደረገ ትብብር በርካታ የሱዳን ወጣቶች ወደዚያ መሄዳቸውን ለማገድ ተችሏል ብለዋል። የሱዳን መንግስት የጸጥታ
ኃይሎች እና የትምህርት ተቋሞች
ወጣቶቹ ወደዚያ እንዳይሄዱ ለማድረግ አስፈላጊውን የቅስቀሳና የትምህርት ስራ
እየሰሩ መሆናቸውንም ከመናገራቸውም በላይ ወደ ተወሰኑ አገሮች ለመውጣት በወጭ ቪዛ ላይ መንግስታቸው ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገ
መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ በካርቱም ዩኒቨርስቲ ይማሩ የነብሩ 12 የህክምናና የቴክኖሎጂ ተማሪዎች ከከርቱም
ተነስተው በቱርክ በኩል አይስስን የተቀላቀሉ መሆናቸውና በሌላ ጊዜ ደግሞ ሌሎች 9 የእንግሊዝ ፓርስፖርት የያይዙ ወጣቶች
ከካርቱም ተነስተው በተመሳሳይ መንገድ ወደ ሲሪያ መሄዳቸው ይታወሳል።
Ø
ከመስከረም 20 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ በየሩሳሌም በእስላራዕሎችና በፍልስጥዔሞች መክካል
የተጀመረው ግጭት የብዙ ሰዎችን ህይወት ያጠፋ ከመሆኑ በላይ ችግሩ እየተባበሰ የሄደ መሆኑ ተገለጸ። በዛሬው ዕለት በተለያዩ
ቦታዎች የተደረጉ ጥቃቶች ሶስት እስራዕሎች የተገደሉ መሆናቸውና ሌሎች የቆሰሉ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን አንድ የፍልስጥዔም ዜጋ
መሞቱና ሌሎች በርካታ መቁሰላቸው ተገልጿል። ችግሩ የተነሳው ለእስልምና እምነት ተከታዮች ከመካ እና ከመዲና ቀጥሎ ሶስተኛ ታላቁ
ክቡር ቦታ በሚባለውና በእየሩሳሌም ውስጥ ጉልህ ቦታ ላይ በሚገኘው በታዋቂው የአል አክሳ መስጊድ ውስጥ የአይሁድ እምነት
ተከታዮች እየገቡ ጸሎት ማድረጋቸው የፍልስጥኤም
ተወላጆችን
በማስቆጣቱ ነው። ከመስከረም 20 ቀን 2008 ዓም. ጀምሮ በተካሄዱ ግጭቶች
ሰባት እስራዕላውያን ሲሞቱ ከ28 በላይ የሆኑ ፍልስጥኤሞች ህይወታቸውን
ከ1900
በላይ
እንደቆሰሉ ጉዳዩን በቅርበት የተከታተሉ ወገኖች
ይገልጻሉ።
በዛሬው
ቀን የፓለስቲንያን ድርጅቶች በምዕራብ ዳርቻ በጋዛና በምስራቃዊ እየሩሳሌም የሚኖሩ የፓለስታይን ዜጎች የአንድ ቀን
የተቃውሞ
ቀን እንዲከበር ጥሪ አድርገዋል።
ሁኔታው እየተባባሰ ከሄደ ከፍተኛ ደም መፋሰስን ሊያስከትል የሚችል ሶስተኛው ጠቅላላ አመጽ ( ሶስተኛው እንቲፋዳህ) ሊከሰት
እንደሚችል ብዙዎች ይተነብያሉ።
ጥቅምት 1 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ቅዳሜ በቱርክ ዋና ከተማ በአንክራ ለበርካታ ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆኑትን ሁለት
ቦምቦች ያፈነዳቸው ራሱን የእስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው አይ ኤስ የተባለው ቡድን ነው ሲሉ የቱሪክ ጠቅላይ ሚኒስትር
ተናገሩ። ቦሞቦቹን በማፈንዳት በኩል እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ ባይኖርም መንግስታቸው ድርጊቱ የተፈጸመው በዚህ ቡድን
ለመሆኑ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንደሌላቸው ገልጸዋል። በቦምቦቹ ፍንዳታዎች የሞቱት ሰዎች በአንዳንድ ክፍሎች 128 ነው እየተባለ
ቢጠቀስም በመንግስት
በኩል እስካሁን ድረስ የተሰጠው
አሀዝ 98 መሆኑ ታውቋል። የአብዛኞቹ
የቀብር ሥነ ስርዓትም በዛሬው ዕለት ተፈጸሟል።
ቅዳሜ
ዕለት በቱርክ መንግስት እና ፒኬኬ በሚባለው የኩርድ የስራተኛ ፓርቲ መካከል ያለው ግጭት ቆሞ ሰላም እንዲወርድ የሚጠይቁ ዜጎች
ትዕይንተ ህዝብ ለማድረገ በሚሰናዱበት ወቅት ሁለቱ ቦምቦች በአጥፍቶ ጠፊዎች መፈንዳታቸው ይታወሳል።
Ø
ጄኔራል ጆንሰን ኦሎኒ የተባሉ አንድ የደቡብ ሱዳን አማጽያን መሪ በመንግስትና በአማጽያኑ
መካከል የተፈረመ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ሊሆን ባለመቻሉ ምክንያት
እንደገና
ወደጦርነት ለመግባት የሚገደዱ መሆናቸውን ቢቢሲ ለተባለው የዜና ወኪል በሰጡት ቃል አስታውቀዋል። ጄኔራሉ የመጡበት ጎሳ ለዘመናት
የያዘው መሬት በአሁኑ ወቅት በመንግስት ኃይሎች መያዙ እና አገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር የደቡብ ሱዳንን አስተዳደራዊ ክልሎች
ከ10 ወደ 28 ከፍ ለማድረግ የወሰኑት ውሳኔ በጣም ያበሳጫቸው መሆኑን ገልጸው መንግስቱ በሰላም ስምምነቱ ላይ እምነት እምነት
የለውም የሚል መደምደሚያ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በፊት የመሬት ቅሚያው ጦርነት ውስጥ የከተታቸው መሆኑን አስታውሰው
አሁንም ሊደገም
እንደሚችል ገልጸዋል። በአሁኑ
ወቅት በደቡብ ሱዳን አብዛኛው ሰው በጦርነቱ መሰላቸቱን ቢገልጽም
የተፈረመው
ስምምነት በስራ ላይ ይውላል የሚለው ተስፋው የመነመነ ነው በማለት የቢቢሲው ጋዜጠኛ አክሎ ዘግቧል።
በተያያዘ
ዜና ደቡብ ሱዳን ውስጥ የሰፈረው የኡጋንዳ መከላከያ ሰራዊት በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ ከደቡብ ሱዳን ለቅቆ መውጣት እንደሚጀምር
አስታወቀ። በደቡብ ሱዳን ያለው የኡጋንዳ ሰራዊት መሪ ብርጋድደር ካያንጃ ሙሀንጋ ጦራቸው
ደቡብ
ሱዳንን ለቅቆ እንዲወጣ መልእክት የደረሳቸው መሆኑ ገልጸው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ መልቀቅ ይጀምራል ብለዋል። በተለይ በዋና
ከተማዋ በጁባ ያለውን ጸጥታ በማስከበር በኩል አስተዋጾ አድርጓል ተብሎ የሚነገርለት የኡጋንዳ ሰራዊት ሳልቫኬርን ለመርዳት ህገ
ወጥ በሆነ መንገድ የገባ ነው በማለት በአማጽያኑ ሲከሰስ መቆየቱ ይታወሳል።
Ø
ትናንት እሁድ በሰሜናዊ ካሜሩን በአጥፍቶ ጠፊዎች የፈነዱ ሁለት ቦምቦች ዘጠኝ ሰዎች ሲገድሉ
29 የሚሆኑ ማቁሰላቸው ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል። ሞራ ከምትባለዋ ከተማ ርቆ በሚገኝ ካንጋለሪ እየተባለ በሚጠራ መንደር
ውስጥ ሁለት ቦምቦችን በማፈንዳት ጥቃቱን የፈጸሙት ሁለት
አጥፍቶ
ጠፊ የሆኑ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል። ከዚህ በፊት አካባቢው በተደጋጋሚ በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት የደረሰበት
በመሆኑ የትናንቱንም ጥቃት ያደረሰው ቦኮሃራም ለመሆኑ ጠንካራ ግምት አለ። በተመሳሳይ ደረጃ ባለፈው ቅዳሜ በቻድ የቦኮ ሃራም
ሽብረተኞች ያፈነዷቸው ሶስት ቦምቦች 41 ሰዎችን ሲገድሉ 48 ሰዎችን ያቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል።
Ø
በተያያዘ ዜና የናይጀረያ መከላከያ ኃይል የቦኮ ሃራምን ይዞታ ሙሉ በሙሉ የከበበው መሆኑን
ገልጾ በቡዱኑ ላይ የመጨርሻ ወሳኝ ጥቃት ለመፈጸም በዝግጅት ላይ እንዳለ በትናንትናው ዕለት አስታውቋል። የናይጄሪያ ወታደራዊ
ተቋም ቃል አቀባይ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ ከዚህ በፊት ከ200 በላይ የሚሆኑ የቦኮ ሃራም አባላት እጃቸውን በሰላም የሰጡ
መሆናቸውን በመጠቆም የቀሩት የቦኮሃራም አባላት በሰላም እጃቸውን እንዲሰጡ ጥሪ አድርገዋል። ታጣቂዎቹ እጃቸውን በሰላም የማይሰጡ
ከሆነ የናይጄሪያ መከለከያ ሰራዊት የተደበቁበትን
ካምፖች እና ጉድጓዶች ጠንቅቆ ስለሚያውቅ
ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስባችው የሚችል መሆኑን በመግለጽ የማስፈራሪያ መልእክት
አስተላፈዋል። ከዚህ ቀደም 200 የሚሆኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች
እጃቸውን
መስጠታችው የተዘገበ ሲሆን መረጃው
እስካሁን
ድረስ ከሶስተኛ
ወገን ማረጋገጫ አላገኘም። ቦኮሃራም
የከዱ አባላት የሌሉት መሆኑን በመግለጽ ዜናውን ማስተባበሉ ይታወሳል።
Ø
በጊኒ የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ በትናንትናው ምሽት የተጠናቀቀ ቢሆንም ተቃዋሚ ድርጅቶች
ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም በማለት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። የጊኒ የዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ትብብር ፓርቲ (The Union
for the Democratic Forces of Guine party) የተባለው ግምባር ቀደሙ የተቃዋሚ ድርጅት እሁድ ማታ በሰጠው
መግለጫ የምርጫ ሳጥኖችን በመንግስት ደጋፊዎች ሲሞሉ የነበሩ መሆናችውን ና ወታደሮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች እየተዘዋወሩ
በማጭበርበር ሲመርጡ የነበረ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪም ወታደሮች ድምጸ ቆጣሪዎችን ካንዳንድ ቦታችም ያባረሯቸው መሆናቸውንና
ከ400
የሚበልጡ የምርጫ ጣቢዎች ደግሞ ጭራሽ ያልተከፈቱ
መሆናቸውን አሳውቀዋል።
የተለይዩ የተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች ዛሬ ሰኞ ተመሳሳይ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በተቃዋሚ ድርጅቶች በመካሄድ ላይ ያለው ተቃውሞ ወደ
አመጽ ይሸጋገራል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለ።
መስከረም 29 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ዛሬ በቱርክ ዋና ከተማ በአንካራ የሰላምና የዴሞክራሲ መልእክት
ለማሰማት
ትዕየንተ ህዝብ እያደረጉ ባሉ ሰዎች መሀል የፈነዱ ሁለት ቦምቦች 30 ሰዎችን ለሞት ሲዳርጉ ከ128 በላይ የሆኑትን
አቁስለዋል።የ። ቦምቦቹ የፈነዱት በአንድ የባቡር ጣቢያ አጠገብ ሲሆን ትዕየንተ ህዝቡን የሚያደርጉት ጉዞ ለመጀመር በሚሰናዱበት
ወቅት ነው። ሰልፉ የተዘጋጀው በተለያዩ ድርጅቶች ሲሆን ኤች ዲ ፒ (HPD) የተባለው የኩርድ ፓርቲም አንዱ መሆኑ ታውቋል።
የመንግስቱ ባለስልጣኖች ፍንዳታው የሽበርተኞች ተግባር ነው ያሉ ሲሆን
ቦምቦቹ
በአጥፍቶ
ጠፊዎች ነው የፈነዱት
የሚለውን መረጃ የሚመረምሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኤች ዲ ፒ ኃላፊዎች ቦሞቦቹ የፈነዱት በመንግስት ኃይሎች እንደሆነ ገልጸው
የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል በሚያጓጓዙ ዜጎች ላይ ፖሊሶች ጥቃት ያደረሱባቸው መሆኑን
ተናግረዋል። በተፈጠረው ሁኔታ ስለፉ መሰረዙን አዘጋጆቹ ገልጸዋል። በሚቀጥለው ወር በቱርክ ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ
የተነገረ ሲሆን
ፒኬኬ በተባለው የኩርድ አማጽያን ቡድንና በቱርክ የጸጥታ ኃይሎች መካካል የተፈረመው የተኩስ አቁም ስምምነት በመፍረሱ ምክንያ
ምርጫው እንቅፋት ሊገጥመው ይችላል
የሚል ስጋት አለ።፡
Ø
ከጥቂት ቀናት በፊት ከመንግስት ኃይሎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ 23 አጃቢዎቻቸው
የተገደሉባቸው የሞዛምቢኩ የሬናሞ ፓርቲ መሪ አፎንሶ ድላካማ ከተደበቁበት ሲወጡ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው በቤት ውስጥ
ተገልለው እንዲቀመጡ የተደረጉ መሆናቸው ተገለጸ። መንግስት የፓርቲውን መሪ በቤት ውስጥ ለማሰር ለወሰደው እርምጃ የሰጠው
ምክንያት የለም።
አጃቢዎቻቸው የተገደሉት ሟቾቹ በአንድ ታክሲ ላይ ጥቃት በማድረሳችው በተደረገ የተኩስ ልውውጥ
ነው የሚል ምክንያት ከመንግስት በኩል ሲሰጥ የሬናሞ ቃል አቀባይ ደግሞ መንግስት የሬናሞ መሪን ለመግደል ያካሄደው የደፈጣ ጥቃት
ነው በማለት ይወነጅላል።
Ø
በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል የሰው አልባ
መንኮራኩር እንዳይጠቀም የደቡብ ሱዳን መንግስት የተቃወመ መሆኑ ተገለጸ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት
በደቡብ ሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመከታተልና ለማጠናከር በአገሪቱ ውስጥ የሚገኘው የሰላም አስከባሪ ኃይል ተጨማሪ
ሄሊኮፕተሮችና ሰው አልባ መንኩራሮች እንዲመደቡለት ወስኗል ። የሰው አልባ መንኮራኮሮች በደበብ ሱዳን እንዲበሩ የጸጥታው ምክር
ቤት የወሰነው ጉዳይ አጨቃጫቂ
ከመሆን አልፎ አለመግባባትና ጥላቻን ስለሚፈጥር መንግስታቸው የማይቀበለው መሆኑን
የደቡብ ሱዳን የተመድ አምባሳደር ገልጸዋል። ሰው አልባ መንኩራኩሮች በጥቅም ላይ ውለው አጥጋቢ ውጤት ካስገኙት አገሮች መካከል
አንዱ የኮንጎ
ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መሆኑን የምክር ቤቱ አባላት ገልጸው
በእግር ለመድረስ በማይቻሉ ወይም አደገኛ በሆኑ አካባቢዎች በማሰማራት ጥሩ ውጤት
ያስገኙ በመሆናቸው በደቡብ ሱዳንም መሰማራታቸው አስፈላጊ ነው
ብለዋል።
በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ኃይል ኃላፊ ኸርቭ ላድሱስ(Herve Ladsous) በደቡብ ሱዳን የሰላም
አስከባሪ ተግባራትን ለማከናወንና የሰላማዊ ሰዎችንም ሆነ የሰላም አስከባሪ ኃይሉ አባሎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሰው አልባ
መንኮራኩርን መጠቀም አስፈላጊ ነው ካሉ በኋላ የደቡብ ሱዳን መንግስት ትብብር አስፈላጊ ስለሆነ ጉዳዩን ከመንግስቱ ባለስልጣኖች
ጋር እንደሚመክሩበት ገልጸዋል።
Ø
በዓለማችን ላይ የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቆጣጠር መንግስታት
ከመደቡት በጀት ውስጥ አፍሪካ የሚገባት ድርሻ እየተሰጣት አይደለም በሚል የአፍሪካ የልማት ባንክ ዋና ጸሐፊ አኪንዉሚ አዴሴና
ገለጹ።የአየር ንብረት መዛባትን አስመልክቶ የሚካሄደው ስብስባ በሚቀጥለው ታህሳስ ወር የሚካሄድ ሲሆን
የዓለም
ሀብታም አገሮች ለሚቀጥሉት
አራት አመታት የአየር ንበረት መዛባትን ለመቆጣጠር አንድ መቶ ቢሊዮን ዶላር ለመመደብ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ተገልጿል። የአየር
ንብረቱን ለማዛባት ከጋዝና ከመሳሰሉት የሚመጣ የካርቦን
ብክለት ዋነኛው ሲሆን
ለብክለቱ
የአፍሪካ
ድርሻ ሁለት ከመቶ ብቻ ነው፣ የአይር ንብረቱ መዛባት የሚያስከትለው የአየር ሙቀት መጨመርና ድርቅት አስመልክቶ
በብዛት
የሚጎዱት የአፍሪካ
አገሮች ናቸው በማለት ዋና ጸፊው ተናግረዋል። ባለፈው ዓመት የአየር ንብረት መዛባትን ለመቆጣጠር የወጣው ወጭ 62 ቢሊዮን ዶላር
ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 76 ከመቶ የሚሆነው ገንዘብ የተመደበው
ከተሽከርካሪዎች ከፋብሪካዎችና ከመብራት አመንጭ ኩባንያዎች የሚወጣውን የጋዝ ጭስ
ለመቀነስ ነው ብለዋል። በአፍሪካ የሚገኙት የተሽከርካሪዎችም
ሆነ የፋብሪካ ብዛት አነስተኛ ስለሆነ አብዛኛው ገንዘብ የሄደው
እንደ ህንድና ቻይና ለመሳሰሉ ለእስያ አገሮች ነው። የአየር ንብረትን የሚያዛቡ
ሁኔታዎችን ከመቀነስ በተጨማሪ የአየር ንብረቱ ለውጥ ለሚያስከትለው አዲስ ሁኔታ ተስማሚ የሆኑ ስራዎችን መስራት አስፈላጊ
ስለሚሆን በዚህ በኩል አፍሪካ ተጨማሪ ገንዘብ እንዲመደብላት ያስፈልጋል በማለት ዋና ጸሐፊው ተናግረዋል።
መስከረም 28 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
አራት የቱኒዚያ ሕዝባዊ ድርጅቶች የዚህ ዓመት የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚዎች ሆነዋል።
ሽልማቱን ያገኙት አራቱ
ድርጅቶች የቱኒዚያ የስራተኛ ማኅበር፤ የቱኒዚያ ኢንደስትሪ ኮንፌዴሬሽን፤ የቱኒዚያ
ንግድ እና የእጃ ሥራዎች ማህበር፤ እና የቱኒዚያ ሰብአዊ መብት ሊግ የተባሉት ድርጅቶች ናቸው። በ2002 ዓም.
የቱኒዚያ የሽግግር ሂደት ወደ እርስ በርስ ጦርነትና ወደ ደም መፋሰሰ በማራበት
ወቅት እነዚህ ድርጅቶች “አራቱ
የቱኒሲያ ብሔራዊ ውይይት አካል” (National Dialogue Quartet)
በሚል ስም ተሰባሰበው እንቅስቃሴ የጀመሩና በኋላም ለተፈጠረው የፖሊቲካ መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ናቸው። የአራቱ
ድርጅቶች ስብስብ በቱኒሲያ ግድያና ሽብር ተስፋፍቶ በነበረበት ወቅት በህብረተሰብ ውስጥ ሰላማዊ ውይይቶች እንዲካሄዱና ብሔራዊ
መግባባት እንዲፈጠር እንዲሁም የአንዳንዱ ዜጋ ሰብዕዊ መብቱ እንዲከበርና አገሪቱም ሕገ መንግስታዊ አስተዳደር እንዲኖራት
በማድረግ በኩል ከፍተኛ ሚና ነበረው ተብሏል።
የኖቤል ኮሚቴ ተጠሪ በሽልማቱ አሰጣጥ
ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የአራቱ ድርጅቶች ስብስብ በቱኒሲያ ያበረከተው
አስተዋጾ ጉልህ በመሆኑ በመካከለኛው ምስራቅ፤ በሰሜን አፍሪካ እና እንዲሁን በሌላው ዓለም ሰላምንና ዴሞክራሲን ለማራመድ ፍላጎት
እና እምነት ላላቸው ወገኖች ከፍተኛ አርአያ ሊሆን ይችላል ብለዋል።
Ø
በዛሬው ዕለት 20 የሚሆኑ ከኤርትራ የመጡ ስደተኞች በአውሮፕላን ከጣሊያን ወደ ስዊድን የሄዱ መሆናቸው ተገልጿል። የአውሮፓ
ህብረት አገሮች በጣሊያንና በግሪክ ካሉ ስደተኞች መካከል 120 ሺ የሚሆኑትን ለመውሰድና በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች ለማስፈር
የተስማሙ ሲሆን በዛሬው ቀን የተጓጓዙት 20 ኤርትራውያን የመጀመሪያው መሆናቸው ነው። ከአፍሪካ እና ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ
ጣሊያን እና ወደ ግሪክ የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ መሄዱ የተነገረ ሲሆን በዚህ ሳምንት በአንድ ቀን ብቻ
2000 ስደተኞች ጣሊያን የገቡ መሆናችው ታውቋል። የአውሮፓው ህብረት የአገር ውስጥ ሚኒስትሮች ባስተላለፉት ውሳኔ መሰረት
ለፖሊቲካ ጥገኝነት ብቁ አይደሉም የሚባሉትን ስደተኞች ወደመጡበት ለመመለስ ካለፈው ረቡዕ ጀመሮ ከተለያዩ አገሮች የተውጣጡ
መርከቦችና የጠረፈ ጠባቂዎች በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የተሰማሩ መሆናቸው ተነግሯል።
Ø
ሐሙስ ዕለት የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ባለስልጣኖች
አቺሌ ታብሶባ የተባሉትንና
የኮንግሬስ ፎር ዴሞክራሲ አንድ ፕሮግሬስ (Congress for democracy
and Progress )
ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትን በቁጥጥር ስር ያደረጉ መሆናቸው ተነገረ። ፓርቲው
የቀድሞ ፕሬዚዳንት ካምፕወሬ የሚመሩት ሲሆን ለረዥም ዓመታት ስልጣን ላይ የነበረ ፓርቲ ነው።
አቺሌ
የታሰሩት ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ በተሞከረው መፈንቅለ መንግስት ሴራ ውስጥ እጃቸው አለበት ተብሎ ሲሆን በዚህ ሳምንት
ውስጥ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የቅርብ ሰው በመሆን በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሰዎች መካከል ሶስተኛው መሆናቸው ነው። የመፈንቅለ መንግስቱ
መሪ ጄኔራል ዲየንዴሪ እና የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጅብሪል ባሶል በመንግስት ላይ ጥቃት መፈጸም እና ግድያ ማካሄድ በሚሉ
ወንጀሎች መከሰሳችው ይታወቃል። መሆናቸው ታውቋል።
Ø
በሚቀጥለው እሁድ በጊኒ ብሔራዊ ምርጫ የሚካሄድ ሲሆን ዛሬ በአግሪቱ ዋና ከተማ ኮናክሪ ውስጥ
በፕሬዚዳንት ኮንዴ ደጋፊዎችና ግምባር ቀደም ተቃዋሚ በመሆን በሚወዳደሩት በሴሉ ዳሊየን ዲያሎ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት
ቢያንስ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ከ20 በላይ የሆኑ የቆሰሉ መሆናችው ተነግሯል። ግጭቱ በአገሪቱ ያለውን የጎሳ ልዩነት ውጥረት ውስጥ
የከተተ ሲሆን አየተባባሰ ከሄደ አደገኛ ሊሆን ይችላል ተብሏል። ማሊንኬ የሚባሉ የፕሬዚዳንት ኮንቴ ደጋፊ ጎሳ አባላት የፉላኔ
ነጋዴዎችን መዲና ወደተባለው የገበያ ቦታ እንዳይገቡ በመከልከላቸው ከፍተኛ ግጭት ሊነሳ ችሏል። የፉላኔ ጎሳ አባላት የተቃዋሚው
መሪ ደጋፊዎች ናቸው። ሀሙስ ዕለት ለአርብ አጥቢያም 20 የሚሆኑ
የፉላኒ ጎሳዎች ሱቆች በኮንዴ ደጋፊዎች የተዘረፉና የተቃጠሉ መሆናቸው ታውቋል።
Ø
በምዕራብ እና በምስራቅ
ሊቢያ መንግስት ያቋቋሙትን የሊቢያን ተጻራሪ ኃይሎች ለማስታረቅ
አደረዳሪ የሆኑት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መልእክተኛ በሊቢያ ሊመሰረት ለታቀደው
የብሔራዊ የአንድነት
መንግስት በመሪነት ደረጃ ኃላፊነት ሊወስዱ ሰዎችን ስም ዝርዝር በሀሳብ ደረጃ ያቀርቡ መሆናቸው ታወቀ። በልዑኩ ሀሳብ
መሰረት መንግስቱን የሚመራ አንድ ጠቃላይ ሚኒስትር እንዲኖርና የምዕራቡን የመካከለኛ ግዛቱንና የምስራቁን ግዛቶች ሊወክሉ የሚችሉ
የሚችሉ ሶስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ይመደባሉ የተባለ ሲሆን
ፋይዝ ሳራጅ የተባሉት ሰው ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ሀሳብ ቀርቧል። የተመድ ሉዑክ ያቀረቡት ሀሳብ ከሁለቱም ወገኖች በኩል
ጠንካራ ተቃውሞ የገጠመው በመሆኑ በስራ ላይ ሊውል የሚችልበት ሁኔታ አነስተኛ ነው
በማለት ታዛቢዎች ይተቻሉ።
Ø
እውቁ ጸሐፊ፣ ጋዜጠኛ
እና ዲፕሎማት አምባስደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ረቡዕ በእንግሊዝ አገር በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አምባሰደር ዘውዴ ረታ በመጨርሻ የጻፉትን መጽሐፍ ለማስመረቅ
በእንግሊዝ አገር በጉብኝት ላይ የነበሩ ሲሆን በመንገድ ላይ እየሄዱ ባልታሰበ ሁኔታ ስለወደቁ ወደ ሆስፒታል ተወስደው
በህክምና እየተረዱ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። አምባሰደር ዘውዴ ረታ ከዚህ በፊት የተለያዩ መጽሐፍትን ደረሰው
ለአንባብያን ያቀረቡ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የኢርትራ ጉዳይ፤ ተፈሪ መኮንን፤ እና የቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ መንግስት የሚባሉ
ይገኙባቸዋል። አምባሰደር ዘውዴ ራታ በንጉሱ ዘመን በጣሊያንና በቱኒሲያ በአምባሳደርነት፤ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
በካውንሰለርነት የሰሩ ሲሆን በአገር ውስጥም በማስታወቂያ ሚኒስቴር በተለያዩ ኃላፊነቶች ሰርተዋል። ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ
ከአገር ተሰደው በጣሊያን አገር የተቀመጡ ሲሆን
ኢንተርናሽናል ፈንድ ፎር አግሪካልቸራል ዴቨሎፕመንት (አይፋድ ) በሚባል አንድ ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸው
ታውቋል። ለቤተሰቦቻቸውና ለሚያውቋቸው መጽናናትን እንመኛለን።
መስከረም 27 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ድንበር የለሽ ጋዘጠኞች (Reporters Without Borders) የተባለው ማዕከሉ
ፈረንሳይ አገር የሆነው የመገናኚያ ብዙሐን አባላት መብትን
ለመንከባከብ
የተቋቋመው ተቋም የወያኔ አገዛዝ በግፍ ያያዛቸውን አራት ጦማርያን እንዲፈታ በድጋሚ ጠየቀ። ተቋሙ ይህን ጥያቄ ያቀረበው
የወያኔው ፍርድ ቤት የጦማርያኑን ጉዳይ ለማየት እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ነው። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር ላይ ዞን 9 በሚል
ስም ተደራጅተው በወያኔ አገዛዝ ላይ ነቀፌታን ያዘለ ጽሁፍ በመጻፋቸው ብቻ
ስደስት
ጦማርያንና ሶስት ጋዘጠኞች መታስራቸው ይታወሳል። የወያኔ አገዛዝ ግብሩን ለመሸፈን ባለፈው ሐምሌ ወር ላይ የተወሰኑትን የፈታ
ቢሆንም አራቱ ማለትም አቤል ዋቤላ፣ ናትናኤል ፈለቀ፤ አጥናፍ ብርሃኔና በፈቃዱ ኃይሉ
በእስር
ቤት የቀሩ መሆናቸው ይታወቃል። የወያኔው አቃቤ ህግ በእነዚህ እስርኞች ላይ በሀምሌ ወር ላይ በተፈተቱ በሁለቱ ጦማርያን ላይ
ከአቀረበው የተለየ
መረጃ
ያላቀረበ መሆኑን በመጥቀስ ድንበር የለሽ የጋዘጠኞች ተቋም እስረኞቹ ባስቸኳ እንዲፈቱ
ጠይቋል። የወያኔ አገዛዝ በአገዛዙ ላይ ነቀፌታ የሚያሰሙ
የመገናኚያ ብዙሀን አባላትን
የአሸባሪነ ስም በመስጠትና ህገ ወጥ
በሆነ መንገድ
በማሰረና በማሰቃየት በኩል አፋኝ ከሚባሉት የአፍሪካ አገዛዞች መካከል ሁለተኛ
ደረጃውን የያዘ ሲሆን የፕሬስ ነጻነትን ሙሉ በሙሉ ከሚያስከብሩ 180 አገሮች ውስጥ
ደግሞ
ደረጃው ወደ መጨረሻዎቹ አስከፊ አገሮች ተርታ የተቀመጠ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
የብሩንዲ መንግስት አንድ የሩዋንዳን ከፍተኛ ዲፕሎማት ከአገሩ ያባረረ መሆኑ ተገለጸ። ዲዛየር ኒያሩሂሪራ የሚባሉትና ብሩንዲ
በሚገኘው የሩዋንዳ ኤምባሲ ውስጥ ለረዥም ዓመታ ሲያገለግሉ የነበሩት ዲፕሎማት ከአገር እንዲወጡ የታዘዙት በአገሪቱ ውስጥ የሽብር
ስራዎችን ከጀርባ ሆነው ያቀናጃሉ በሚል ምክንያት ነው። በአሁኑ ወቅት በብሩንዲና በሩዋንዳ መካከል ያለው ግንኙነት በጣም
የቀዘቀዘ ሲሆን ባለፈው ሳምንት ውስጥ የቡሩንዲ ተቃዋሚዎች የሽብር ተግባር እንዲያካሄዱ ሩዋንዳ ስልጠና እየሰጠች ነው በማለት
የብሩንዲ መንግስት የከሰሰ መሆኑ ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና የሩዋንዳ ከፍተኛ
ፍርድ ቤት ግሪን ፓርቲ የተባለው የተቀዋሚ ፓርቲ አቅርቦት የነበረውን ክስ ውድቅ ያደረገው መሆኑ ተገለጸ። የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት
ለሶስተኛ ጊዜ መወዳደር የሚያስችላቸው የህገ መንግስት መሻሻል አስመልክቶ
ሕዝበ
ውሳኔ እንዲደረግ የሩዋንዳው
ምክር ቤት የደረሰበትን ውሳኔ በመቃወም ግሪን ፓርቲ የተባለው የሩዋንዳ ተቃዋሚ ፓርቲ ያቀረበው ክስ በከፍተኛው ፍርድ ቤቱ
አይቶት ውድቅ
አድርጎታል። ፍርድ ቤቱ
ሕዝብ እንዴት ሊገዛ እንደሚችል የመወሰን መብት ሊኖረው ይገባል የሚል ምክንያት
በመስጠት ክሱን ውድቅ ያደረገው መሆኑን ገልጿል። ፕሬዚዳንት ካጋሜ በ1993 እና በ2003 ዓ.ም በተደረጉ ብሔራዊ ምርጫዎ
አሸናፊ ተብለው ስልጣን ላይ መቆየታቸው ሲታወቅ አሁን ያለው ሕገ መንግስት የፕሬዚዳንቱን የምርጫ ጊዜ በሁለት የምርጫ ዘመን
ይወስናል።
Ø
በአውሮፓ ውስጥ የፖሊቲካ ጥገኝነት የተነፈጉት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ አገራቸው
ባስቸኳይ የሚመለሱበትን ሁኔታ ለመወሰን የአውሮፓው
ህበረት የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስትሮች በዛሬው ቀን የሚሰበሰቡ መሆናቸው ታወቀ። ሚኒስትሮቹ የተደበቁ ስደተኞችን እንዴት መያዝ
እንደሚቻልና በምን ዓይነት መንገድ በፍጥነት ወደ አገራቸው መመለስ እንደሚቻል ባካተቱት የውሳኔ ረቂቆች ላይ ውሳኔ ይሰጣሉ ተብሎ
ይጠበቃል። በተጨማሪም ስደተኞቹ የመጡባቸው አገሮች ዜጎቻቸውን እንዲቀበሉ ለማድረግ
ጫና
ማድረግ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ይወያያሉ ተብሏል።
Ø
ከለፈው አንድ አመት ተኩል ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በጊኒ እና በሲየራ ሊዮን የኢቦላ በሽታ ለአንድ ሳምንት ያህል ሳይገኝ በመቅረቱ
በሽታው ሊጠፋ ይችላል የሚል ተስፋን ፈንጥቋል። ላይቤሪያ ላለፉት 42 ቀናት አንድም የኢቦላ በሽተኛ ያልተየባት ስለሆነች ከኢቦላ
ነጻ የሆነች አገር የሚል ስያሜ ተሰጥቷል። ጊኒ ካለፈው መስከረም 16 ውዲህ ፣ ሲየራ ሊዮን ደግም ከመስከረም 17 ወዲህ አንድም
የኢቦላ በሽተኛ ያልተየባቸው በመሆኑ ከኢቦላ ነጻ የሆኑበትን የመጀመሪያ ሳምንት አክብረዋል። በጊኒ በላይቤሪያ እና በሲየራሊዮን
እስካሁን ድረስ ከ አስራ አንድ ሺ ሰዎች በላይ በበሽታው የሞቱ መሆናቸው ይታወቃል። የተባበሩት መንግስታት የጤና ድርጅት በሽታው
ባለፉት 10 ወራት በጣም እየቀነሰ የመጣ መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት እንደገና ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ብሏል።
Ø
በትናንትናው ዕለት በየመን ከዋናው ከተማ ከሳንአ 100 ኪሎሜትር ላይ ርቃ በምትገኝ ሳንባን
በተባለች ከተማ ውስጥ በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል በሰርገኞች በነበሩ ሰዎች ላይ ባደረሰው የአየር ጥቃት 13 ሰዎች
መሞታቸውንና ክ
38 ሰዎች በላይ የቆሰሉ መሆናቸውን የሆስፒታል ምንጮች ገለጹ። ላለፉት ሰባት ወራት በሁቲ አማጽያን ይዞታ ላይ ተከታታይ የአየር
ጥቃት ሲያካሂድ የነበረው በሳኡዲ የሚመራው ጥምር ኃይል ስላካሄደው ጥቃትና ስላደረሰው ጉዳት የሰጠው መግለጫ
የለም። ጥምር ኃይሉ በሰረገኞች ላይ ጥቃት ሲፈጽም
በአንድ
ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህ ሁለተኛ ጊዜው መሆኑ ነው። ባለፈው ሳምንት አልሞክሃ በተባለች የቀይ ባህር ዳርቻ ከተማ ውስጥ እየተካሄደ
በነበረ አንድ የሰርግ በአል ላይ ጥምር ኃይሉ ባካሄደው የአየር ጥቃት ቢያንስ 131 ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል። በተያያዘ ዜና
በየመን የስደተኛው መንግስት እና በሁቲ አማጽያን መካከል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት ሲካሄድ የቆየውና
በመሀሉ
ተቋርጦ የነበረውን የእርቅ ውይይት እንደገና ለመጀመር ሁለቱም ወገኖች የተስማሙ መሆናቸው ተገልጿል።
Ø
የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ፌዴርሽን ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላትር፣ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ማይክል
ፕላቲኒ እና ዋና ጸሐፈው ጀሮሜ ዋልኬ ለ90 ቀናት ያህል ከስራቸው የታገዱ መሆናቸው ተነገረ።
ፕሬዚዳንቱ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እና ዋና ጸሐፊው ላይ እገዳ የተደረገው ሰዎቹ
በከፍተኛ ሙስና ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው በመሆኑ ነው። በእገዳ ጊዜያቸው ወቅት ሰዎቹ ከማናቸውም የእግር ኳስ ስራዎች
የተገለሉ መሆናችው ተገልጿል። የቀድሞ የፊፋ ምክትል ፕሬዚዳንት ቹንግ ሞንግጁን በሙስና ተግባር ውስጥ መሳተፋችው በመረጋገጡ
ለስድስት ዓመታት ያህል ከእግር ኳስ ስራዎች የታገዱ ሲሆን 100 ሺ የስዊስ
ፍራንክ መቀጫ እንዲከፍሉ ተበይኖባቸዋል።
መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
ባለፈው ሰኞ 14 ኢትዮጵያን በኬኒያ ፍርድ ቤት የቀረቡ መሆናቸውና እያንዳንዳቸው
20
ሺ የኬኒያ ሽልንግ ከፍለው እንዲለቀቁ የማይችሉ ከሆነም ለ 130 ቀናት ያህል እንዲታሰሩ
ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሲሆን
የተከሰሱት ደግሞ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ አገር ውስጥ ገብተዋል በሚል ክስ ነው።
የኬኒያ ባለስልጣኖች ከኢትዮጵያ ወደኬኒያ
ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የሚገቡት ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መሄዱን
ገልጸው ቦታው ሰፊ በመሆኑ ለመቆጣጠር አዳጋቸ መሆኑን ተናገረዋል። የወያኔ ግፈኛና አስከፊ አገዛዝ በመሸሽና ኑሯቸውን ለማሻሻል
ወደ ኪኒያ እና ከዚያም አልፈው ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መሆኑን ጉዳዮን በቅርብ
የሚከታተሉት ክፍሎች ይገልጻሉ። የዓለም አቀፉ የስደተኛ ድርጅት በቅርቡ ባወጣው ዘገባ በየቀኑ በአማካይ 30 ኢትዮዮጵያውያን
ወደ ኬኒያ እንደሚገቡና በወር ከ90 ሚሊዮን የኬኒያ ሽልንግ በላይ
ለአስተላላፊዎች ጉቦ እንደሚከፍሉ ገልጿል። ራሱ የወያኔ ኢምባሲ በሰጠው ግምት እንኳ በደቡብ አፍሪካ ከ45 ሺ እስከ 50 ሺ
የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ገልጿል። በሁሉም አቅጣጫ
ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚሰደደው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ
የሄደ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ይህም ሀቅ ወያኔ ኢኮኖሚውን በጥምር አሃዝ እያሳደገነ ነው ብለው ከበሮ የሚደልቁትን ክፍሎች እያሳፈረ
ነው በማለት ታዛብዎች ይተቻሉ።
Ø
ከጥቂት ሳምንታት በፊት
በቡርኪና ፋሶ የተካሄደውንና ባጭር የተቀጨውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል
ዲየንዴሬ በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው ለፍርድ የቀረቡ መሆናቸው ተነገረ። የጄኔራል ዴየንዴሬን ጉዳይ አይቶ ፍርድ የሚሰጠው አካል
ወታደራዊ ፍርድ ቤት ሲሆን ጄኔራሉ በአስራ አንድ ወንጀሎች የተከሰሱ መሆናቸውና ከነዚህም ውስጥ የመንግስትን ጸጥታ ማናጋት፤
ግድያ፤ ከውጭ ኃይሎች ጋር ተባብሮ አገርን ማጥቃት እና የንብረት ማውደም የሚሉ እንደሚገኙበት ተገልጿል። የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ጂብሪል ባሶል ከመፈንቅለ መንግስት አድራጊዎች ጋር ተባባሪ ናቸው የሚል ክስ ተመስርቶባቸው
በወታደራዊ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ መሆናቸው ሲገለጽ ከቀረበባቸው የክስ ወንጀል ነጻ መሆናችውን መግለጻቸው ግታውቋል። ባለፈው
ሳምንት ጄኔራል ዲየንዴሬ በቫቲካን ኤምባሲ መሸሸጋቸውና በኋላም ለቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ባለስልጣኖች እጃቸውን መስጠታቸው
ይታወሳል። እሳቸው ከሚመሩት የወታደር ክፍል ውስጥ የተወሰኑት
ትጥቅ አናወርድም በማለታቸው የአገሪቱ መከላከያ ኃይል በወታደራዊ ሰፈራቸው ላይ ጥቃት
ለማድረግ ተገዶ የነበረ መሆኑም አይዘነጋም።
Ø
በሚዲትራኒያን ባህር ላይ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ ስደተኞችን ወደ አውሮፓ ለማስረግ
የሚንቀሳቀሱ ጀልባዎችንና መርከቦችን ለመቆጣጠር የአውሮፓው ህበረት አዲስ ስምሪት የጀመረ መሆኑ ታወቀ። የሶፊያ ኦፕሬሽን በሚል
ስም በዛረው ቀን በተጀመረው እንቅስቃሴ
መሰረት በአውሮፓው ህብረት የተሰማሩ የባህር ኃይል አባሎች ስደተኞች አሉበት ብለው
የሚጠርጥሯቸውን ማናቸውንም አነስተኛ መርከቦችና ጀልባዎች አስቁመው የሚመረምሩ መሆናቸውና እነዳስፈላጊነቱ መርከቦቹንና ጀልባዎችን
ይዞ በቁጥጥር ስር ለማድረግም ሆነ ወደ መጡበት ለመመለስ ስልጣን የተሰጣቸው መሆኑ ታውቋል። እስካሁን ድረስ የአዎሮፓው ህብረት
የባህር ኃይል መርከቦች በቅኝትና በነፍስ ማዳን ተግባር ላይ ብቻ ተሰማርተው የነበሩ መሆናቸው ይታወቃል። በዚህ ስራ ላይ ስድስት
የጦር መርከቦች እንዲሁም በርካታ ሂሊኮፕተሮችና ስው አልባ ተንቀሳቃሽ በራሪዎች (ድሮኖች) የተሰማሩ መሆናቸውም ተገልጿል።
ባለፉት
10 ወራት ከ 130 ሺ ሰደተኞች በላይ ከሰሜን አፍሪካ የባህር ዳርቻዎች ተነስተው
አውሮፓ የገቡ መሆናቸው ሲታወቅ 2700 የሚሆኑት
ባህሩ
ውስጥ ሰጥመው የሞቱ መሆናቸው ተዘግቧል።
Ø
ቦኮሃራም በሚባለው አሸባሪ ቡድን ጥቃት እየታመሰ የሚገኘው የሰሜን ምስራቅ ናይጀሪያ ግዛት
በዛሬው ዕለት በፈንጅ ጥቃት ጉዳት እየደረሰበት መሆኑ ተዘገበ። ዳማቱሩ በምትባለው የዩቤ አውራጃ ዋና ከተማ ውስጥ የአሸባሪው
ቡድን አባሎች ባፈነዷቸው ሁለት ቦምቦች 14 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ገለጸ።
የቦኮ ሃራም አባል የሆነው አንደኛው አጥፍቶ ጠፊ በተወሰኑ ወጣቶች መካከል ያፈነዳው ቦምብ
አራት ወጣቶችን ሲገድል ሌላኛው ደግሞ ቤተሰቦቹንና ጎረቤቶችን ሰብስቦ የሃይማኖት ስብከት እያደረገ እያለ የያዘውን ቦምብ
በማፈንዳቱ 10 ሰዎች ሞተዋል። በተያያዘ ዜና የመንግስቱ ወታደራዊ ቃል አቀባይ በሰጠው መግለጫ የተወሰኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች
በዮቤ አውራጃ ውስጥ ባለው ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ሰንዝረው የተኩስ ልውውጥ
የተደረገ መሆኑንና በግጭቱም ከ100 በላይ የሆኑ ታጣቂዎችን ተገድለው ሌሎች መያዛቸውን እንዲሁም ከወታደሩ በኩል ሰባት ወታደሮች
መሞታቸውን አሳውቋል። የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በቅርቡ በለቀቁት ተንቀሳቃሽ ስዕል ደግሞ አሸባሪዎቹ ለአይሲስ ታማኝ መሆናቸውንና
እንዲሁም በመንግስት በኩል ተድረገ የተባለው ውታደራዊ ድል ውሸት መሆኑን ተናግረዋል።
Ø
የደቡብ ሱዳን መንግስት ከስምምነቱ ውጭ በገዛ ስልጣኑ የአካባቢ ግዛቶችን ቁጥር ከ10
ወደ 28 ከፍ እንዲል በማድረጉ
በመንግስቱና
በአማጽያኑ መካከል ባለፈው ዓመት ነሐሴ 20 ቀን 2007 ዓ፣ም ተደርጎ የነበረው ስምምነት አደጋ ሊያጋጠመው እንደሚችል
የአማጽያኑ ቃል አቀባዮች ማክሰኞ ዕለት አስታውቀዋል። በስምምነቱ ውስጥ የተቀመጠውን
የስልጣን ድርሻ በሚጻረር መልክ ባለፈው አርብ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ስልጣን
የሚኖራቸውና በጎሳ ላይ የተመሰረቱ ግዛቶች ቁጥር ከ10 ወደ 28 ከፍ እንዲል አድርገዋል። አማጽያኑንም ሆነ ስምምነቱን የደገፉት
አሜሪካ እንግሊዝ እና ኖርዌይ ይህ የሳልቫኬር ርምጃ
ቀደም ብሎ ተደረጎ የነበረውን የስልጣን ክፍፍል ስምምነት የሚጻረር መሆኑን
ሲገልጹ የአውሮፓው ህበረት ደግሞ ሳልቫኬር ውሳኔያቸውን እንዲሽሩ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
በመንግስቱ በኩል የተወሰደው እርምጃ በደቡብ ሱዳን ጎሳዊ ስሜቶችን አነሳስቶ
በመካከላቸው ያልተቋረጠ ጦርነት እንዲካሄድ ነው በማለት የአማጽያኑ ቃል አቀባይ ተናግሯል። ባለፈው ዓመት በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎ
ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ በሁለቱ ተጻራሪ ኃይሎች መካከል ጦርነት ያላቆመ መሆኑ በየጊዜው ተዘግቧል።
ለተኩስ
አቁሞ መጣስ ምክንያት አንዱ ሌላኛውን እየከሰሰ ቢሆንም የሚካሄደው ጦርነቱ ጉዳት ማድረሱ አልቀረም። በአካባቢው የሚገኙ የእርዳታ
ሰጭ ድርጅቶች በጦርነቶቹ ምክንያት ስራቸውን ያቋረጡ በተለያዩ ቦታዎች ስራቸውን ማቋረጠቸው የተነገር ሲሆን የተባበሩት መንግስታት
የምግብና የእርሻ ድርጅትም በዚህ ዓመት በደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ረሃብ ሊከሰት እንደሚችል ተንብየዋል።፡
መስከረም 25 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በየመን ደቡባዊ ግዛት በኤደን ከተማ ከስደት የተመለሱት የየመን ጠቅላይ ሚኒስትርና
የካቢኔ አባሎቻቸው አርፈውበት የነበረበት ካስር የሚባለው ሆቴል በሮኬት በመደብደቡ ምክንያት በርካታ ሰዎች መገደላቸውና
መጎዳታቸው ተገለጸ። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ
ከሞቱት መካከል 15 የሚሆኑት በሳኡዲ የሚመራው የአረብ ጥምር ኃይል አባላት
መሆናቸው ሲገለጽ ከእነዚህም ውስጥ 4 የኤምሬት ተወላጅ እና አንድ የሳዑዲ ተወላጅ ናቸው።
ጠቅላይ
ሚኒስትሩ በወቅቱ በሆቴል ያልነበሩ መሆኑ የተነገረ ሲሆን
የካቢኒ ሚኒስትሮችም ከአደጋው የዳኑ መሆናቸው ታውቋል። በሳኡዲ የሚመራው ጦር
የሁቲ አማጽያንን ከኤደን ካስወጣ ጀምሮ የካስር ሆቴል ለየመን ስደተኛ መንግስት መቀመጫ ሆኖ በማገልገል ላይ ነበር። እስካሁን
ድረስ በሆቴሉ ላይ ለደረሰው የሮኬት ጥቃት ኃይላፊነቱን የወሰደ ቡድን የለም። የሁቲ አማጽያን ከተማውን ከለቀቁ ጀምሮ በርካታ
ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያላቸው ኃይሎችና ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ኃይል አባሎች ነን የሚሉ ቡድኖች
እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ባለፈው ዓመት መጋቢት ላይ የሁቲ አማጽያን የአገሪቱን ዋና ዋና ከተሞች
በመቆጣጠራቸው የየመን
ፕሬዚዳንትና ሃዲና መንግስታቸው አገር ጥለው የተሰደዱ መሆንቸው ሲታወቅ ባለፈው ሐምሌ ወር በሳዑዲ የሚመራው ኃይልና የመንግስቱ
ደጋፈዎች የሁቲ አማጽያንን ከኤደን ማስወጣቸው ይታወሳል። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግምት የየመን ችግር ከተፈጠረ ካለፈው
ስድስት ወር ጀምሮ በጠቅላላው 4900 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 2300 የሚሆኑት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።
Ø
ሰኞ ሌሊት ለማክሰኞ አጥቢያ
የቦኮ
ሃራም ታጣቂዎች በቻድ ባህር አጠገብ አንድ የቻድ ወታደራዊ ካምፕ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 13 የቻድ ወታደሮች የሞቱ መሆናቸው
የቻድ ወታደራዊ ተቋም ቃል አቀባይ ለዜና ምንጮች ገልጿል። 17 የሚሆኑ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች መገደላቸውንም ቃል አቀባዩ ጨምሮ
ተናግሯል። ወታደሮቹ በወሰዱት የመልሶ ማጥቃት እርምጃ የቦኮሃራም ታጣቂዎች ወደመጡበት ያፈገፈጉ መሆናቸውና ወታደራዊ ኃይሉ
እየተከታተላቸው መሆኑም ተገልጿል። ቻድ ቦኮ ሃራምን ለማዳከምና ለማጥፋት ከተለያዩ አገሮች ተውጣቶ የተቋቋመው ጥምር ኃይል ውስጥ
አባል ከሆነችበት ጊዜ ጀምሮ በቦካሃራም ተከታታይ ጥቃት ሲደርስባት የቆየ መሆኑ ይታወሳል። የቦኮሃራም እንቅስቃሴ ከተጀመረ ጀምሮ
በጠቅላላው በናይጄሪያና በአካባቢው አገሮች ከ17 ሺ ሰው በላይ ህይወቱን ማጣቱና ከ2.5 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ቤቱን ጥሎ
የተሰደደ መሆኑ ይታወቃል።
Ø
በትናንተናው ዕለት ከሊቢያ ጠረፍ ተነስተው ወደ አውሮፓ ይጓዙ የነበሩ 1800 ስደተኞች
ከመስጠም
አደጋ የዳኑ መሆናቸውን
የጣሊያን ጠረፍ ጠባቂዎች ገለጹ። ከጣሊያን፣ ከእንግሊዝ እና ከአየርላንድ የተውጣጡ መርከቦችን በመጠቀም እና ስድስት ዙር የማዳን
ተግባሮችን በማካሄድ የስደተኞቹን ህይወት ለማትረፍ የተቻለ መሆኑ ታውቋል። ባለፉት 10 ወራት ግማሽ ሚሊዮን ሰደተኞች ከተለያዩ
ቦታዎች ወደ አውሮፓ የተሻገሩ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን 2980 የሚሆኑ በባህሩ ውስጥ ሰጥመው ሞተዋል ተብሏል። ከቱርክ ተነስተው
ባህር አቋርጠው ወደ አውሮፓ የሚሻገሩት ስደተኞች ከሶሪያ እና እንደአፍጋኒስታን ከመሳሰሉ የኤሽያ አገሮች የመይጡ ሲሆን ከሊቢያ
ጠረፍ የሚነሱ ስደተኞች ደግሞ አብዛኞቹ ከአፍሪካ የመጡ መሆናቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ሰዎች ይናገራሉ። ከነገ እሮብ
ጀምሮ ማንኛቸውም
በዓለም አቀፍ ባህር ላይ ስደተኞችን ያመላልሳሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ጀልባዎችና አነስተኛ መርከቦች ፍተሻ እንዲካሄድባቸውና
በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የአውሮፓው ህበረት ለጠረፍ ጠባቂ ባለስልጣኖች ማዘዣ የሰጠ መሆኑ ታውቋል።
Ø
የጋና መንግስት ሰባት የሚሆኑ የጋና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኖችን ከስራቸው ያገደ መሆኑ
ተነገረ። በዳኖቹ ላይ ውሳኔ መደረጉ የታወቀው ፕሬዚዳንቱን በመወከል ምክትል ፕሬዚዳንቱ በሰጡት መግለጫ ሲሆን ውሳኔው የተደረሰው
የፍርድ
ነክ ጉዳዮች ካውንስል የደረሰበትን ውሳኔ ተመርኮዞ
መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ወቅት ለጉብኝት ፈረንሳይ
የሚገኙት
የጋናው
ፕሬዚዳንት ከዚህ በፊት አንድ የጋና ጋዜጣ
የዳኞችን ሙስና አስመልክቶ በአምዱ ላይ ያሰፈረውን መረጃ በማድረግ ጉዳዩን
እንዲመረመርና ውሳኔ
እንዲሰጥበት ለአገሪቱ ዋና ዳኛ መመሪያ ማስተላፋቸው ይታወሳል። በከፍተኛ ዳኖች ላይ የተሰጠው ይህንን ጉዳይ ለመመረመር
የተቋቋመው የፍርድ ጉዳይ ኮሚሽን ጉዳዩን አጣርቶ ባቀረበው ሀሳብ መሰረት መሆኑ ታውቋል።
ባለፈው
ወር 22 የዝቅተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ከስራ መባረራቸውና 12 የሚሆኑ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ምርመራ እንደደረግባቸው መታዘዙ
ይታወሳል። የጋና መንግስት ይህንን እርምጃ ለመውስድ የተገደደው የጋና መገናኚያ ብዙሃን አባላት በርካታ ዳኞች ጉቦ ሲበሉ በድብቅ
ያነሱት ፊልም ለሕዝብ እንዲታይ ተደርጎ በመጋለጡ ነው።
Ø
በምስራቅ ሊቢያ የሚገኘውና ዓለም አቀፍ እውቅና የተሰጠው የሊቢያ ምክር ቤት
ስልጣኑ
የሚያበቃበትን ቀን ላልተወሰነ ጊዜ ያስተላለፈው መሆኑ ተገለጸ። ምክር ቤቱ በስልጣን እንዲቆይ ተወስኖ የነበረው እስከ ጥቅምት 9
ቀን 2008 ዓ.ም. (October 20, 2015) ድረሰ የነበረ ሲሆን ቀኑ እንዲራዘም የቀረበው ሀሳብ ከ131 አባላት 129ኙ
ደግፈውት የስልጣኑን እድሜ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። አንዳንድ የፖሊቲካ ታዛቢዎች ምክር ቤቱ ይህንን የወሰነው
ትሪፖሊ ላይ ከሚገኘው ተጻራሪ መንግስት ካቋቋመው
ክፍል
በመካሄድ
ላይ ያለው የእርቅ ድርድር ላይ
ብዙዎቹ አባላት ተስፋ በመቁረጣቸው ነው የሚል አስተያየቶች ሲሰጡ ሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ደግሞ ውሳኔውን ለመወሰን የገፋፋቸው
እርቁ
የማይሳካ ከሆነ የስልጣን ገዋ እንዳይፈጠር ነው ይላሉ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አደራዳሪነት እየተካሄደ ያለው የእርቅ
ድርድር የቀን ገደቡ ጥቅምት 9 ቀን 2008 ዓ.ም (October 20, 2015) መሆኑ ይታወቃል።
መስከረም 24 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በሳምንቱ
መጨረሻ በብሩንዲ ዋና ከተማ በቡጁምቡራ በመንግስቱ ተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት 12 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውን
አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የተባለው የዜና ወኪል ከስፍራው የደረሰውን ዜና ዋቢ በማድረግ ገልጿል። ግጭቱ የተጀመረው ቅዳሜ እኩለ ቀን
ላይ ሲሆን እስከ አሁድ ድረስ የዘለቀ መሆኑ ታውቋል። የፖሊስ ቃል አቀባይ በሰጠው መረጃ ቅዳሜ ዕለት
የመንግስት ተቃዋሚዎች በፖሊስ አባላት ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ሁለት ፖሊሶች
መጎዳታቸውን የገለጸ ሲሆን ፖሊሶች በወሰዱት የአጸፋ ጥቃት ደግሞ ሁለት ሰዎች ሞተዋል ብሏል። በቦታ የነበሩ የአይን እማኞች
በሰጠቱ መረጃ ግን ግጭቱ ከዚህ የሰፋ እንድነበርና የሞቱት ሰዎች ቁጥርም በርካታ እንደነበር ገልጸዋል። እሁድ ጠዋት ሲቢቶኬ
በሚባለው የከተማው ቀበሌ ስድስት የሰላማዊ ሰዎች አስከሬን የተገኘ ሲሆን
ማታኩራ በሚባለው ደግሞ ሌሎች አራት አስከሬኖች መገኘታቸውን በቦታው የነበሩ ሰዎች
ገልጸዋል። አንዳንዶቹ የተገደሉት ግምባራቸው ላይ በተተኮሰ ጥይት መሆኑም ተጠቅሷል። በአይን እማኞቹ መረጃ መሰረት ሊጀመር
የቻለው ፖሊሶች ማታኩራ ከሚባለው የከተማው ክፍል ፖሊሶች ወጣቶችን ለማሰር ሙከራ ባደረጉበት ወቅት የአክባቢው ነዋሪ ተቃውሞ
በማስነሳቱና ፖሊሶቹ ላይ ጥቃት በመሰንዘሩ ሲሆን ግጭቱ ወደ ሌላ ቀበሌ ተዛምቶ በርካታ ሰዎች ሊሞቱ ችለዋል ተብሏል። ቀኑን ሙሉ
የአውቶማቲክ መሳሪዎች እና የፈንጅዎች ድምጽ ሲሰማ የዋለ እንደነበርም የአይን እማኞች ገልጸዋል።
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለሶስተኛ ጊዜ ለመወዳደር ለምርጫ እቀርባለሁ ካሉበት ካለፈው
ሚያዚያ ወር ጀምሮ በአንድ በኩል
መንግስት የጸጥታ ኃይሎችና ታጣቂ ቡድኖች
በሌላ በኩል
በመንግስት ተቅዋሚ
ኃይሎች መካከል ሲካሄዱ በቆዩ ግጭቶች በርካታ ሰዎች መሞታቸውና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ
መሰደዳቸው ይታወቃል።
Ø
የሱዳን
መንግስት ሁለት የታወቁ የኮንግረስ ፓርቲ አባላትን ከአገር እንዳይወጡ የከለለከ መሆኑ ታወቀ። ለበሽር መንግስት ጠንካራ ተቃዋሚ
የሆነው የኮንግሬስ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አብዱል ጋይም ባዱር ቅዳሜ እለት በአውሮፕላን ወደ ካይሮ ለመጓዝ
ሲሞክሩ ከመውጣት የታገዱ ሲሆን ሲዲቅ ዩሱፍ የሚባሉ ሌላው የፓርቲው ባለስልጣንም
እንደዚሁ በሌላ አውሮፕላን ወደ ካይሮ ለመሄዱ ሲሞክሩ ታግደዋል። ሁለቱ ሰዎች የሚወጡት ሌሎች የተቃዋሚ ኃይል መሪዎችን በካይሮና
በፓሪስ ለመገናኘት እንደነበር ተገልጿል። ላለፈው 25 ዓመታት ስልጣን ጨብጠው የሚገኙት አል በሽር ወታደሩን ተገን በማድረግ
ያካሄዱት አፈና የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን አድክሞ ይገኛል።
Ø
በደቡብ
ምስራቅ ናይጀር በምትገኘው ዲፋ በተባለች ከተማ በሁለት አካባቢዎች በፈነዱ ቦምቦች አራት አጥፍቶ ጠፊዎች፣ አምስት ሰላማዊ
ሰዎችና አንድ የፖሊስ አባል በድምሩ አስር ሰዎች የተገደሉ መሆናቸው ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል።
ቦምቡን ያፈነዱትና የተገደሉት አራት አጥፍቶ ጠፊዎች የቦኮሃራም አባላት መሆናቸው
ፖሊስ የገለጸ ሲሆን ዓላማቸው በወታደሩ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ነበር ብሏል። በፈንጅው የቆሰሉ ሰዎች በህክምና እየተረዱ
መሆናችውም ተገልጿል። ናይጀር ከሌሎች የምዕራብ አፍሪካ አገሮች ጋር በመሆን በቦካ ሃራም ላይ ጥቃት የሚፈጸም ጥምር ኃይል
ካቋቋመችበት ጊዜ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ ቦኮሃራም ጥቃቱን አጠነክሮ በርካታ ሰዎች መግደሉ ይታወሳል።
በተያያዘ ዜና ባለፈው አርብ በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ አቅራቢያ ፈንድተው ከ18 በላይ
ሰዎችንና የገደሉትንና ከ41 ሰዎች በላይ ያቆሰሉትን ፈንጅዎች በማፈንዳትና ጥቃቱን በመፈጸም በኩል ቦኮ ሃራም ኃላፊነቱን የወሰደ
መሆኑን ገልጿል። የአገሪቱ
ፕሬዚዳንት ቡሃሪም እሁድ ዕለት ወደ ቦታው በመሄድ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች አግኝተው ሲያበረታቱ መቆየታቸውንና
የህክምና
ወጭአቸውንም መንግስት እንደሚሸፍነው ቃል የገቡላቸው መሆኑ ተነግሯል።
Ø
በደቡብ
አፍሪካ በማዕድን ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል ሲካሄድ በነበረው የክፍያ ድርድር ላይ ስምምነት ሊደረስ ባለመቻሉ 30 ሺ
የሚሆኑ የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሰራተኞች ከእሁድ ጅምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ የሚያደርጉ መሆኑ ተገለጸ። ናሽናል
ዩኒየን ኦፍ ማይን ዎርከርስ (National Union of Mine workers) የተባለው የሰራተኞቹ ማህበር ድርጅት መሪዎች
ማህበሩ
እዚህ ውሳኔ ላይ ሊደርስ የቻለው ድርድሩ የትም ሊደርስ ስላልቻለ ነው ብለዋል። ማህበሩ
ለሰራተኞቹ ከ13 እስከ አ14 ከመቶ የደሞዝ ጭማሪ የጠየቀ ሲሆን ከሶስት ወር ድርድር በኋላ አሰሪዎቹ ለመክፈል የተስማሙት
የዚህን ግማሽ ብቻ መሆኑም ተገልጿል። የስራ ማቆም አድማው የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚን ሊጎዳ ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለ።
Ø
በተመሳሳይ
ዜና ላለፉት አምስት ሳምንታት ስራ አቁመው የነበሩ የኬኒያ መምህራን አንድ የኬኒያ ፍርድ ቤት በቅርቡ ያስተላለፈውን ትእዛዝ
በመቀበል ወደ ስራ ገበታቸው የተመለሱ መሆናቸውና በዚህም ምክያት በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኬኒያ ተማሪዎች ትምህርት የጀመሩ መሆናቸው
ታውቋል።
በ90 ቀናት ውስጥ ጉዳያቸውን ተነጋግረው በስምምነት እንዲጨርሱና እስከዚያው ድረስ
አስተማሪዎቹ የስራ ማቆም አድማውን አቁመው ወደ ስራቸው እንደሚለሱ የሚለውን የፍርድ ቤት ውሳኔ የኬኒያ መምህራን ማህበር
የሚያከብር መሆኑን ጠቅሶ በዚህ ሶስት ወር ውስጥ
የደምዝ
ጭማሪ ጥያቄው በመንግስት በኩል በስራ ላይ የማይውል ከሆነ
መምህራኑ
እንደገና ስራ ለማቆም የሚገደዱ መሆናቸውን
ገልጿል።
Ø
የጊኒ
ሁለተኛ ከተማ በሆነችው እንዜሬኮሬ በተባለችው ከተማ በተጻራሪ ቡድኖች መካከል ግጭት ተፈጥሮ ጉዳት በመድረሱ የሰዓት እላፊ አዋጅ
የታወጀ መሆኑ ተገለጸ። በሚቀጥለው እሁድ ሊካሄድ የታቀደውን ብሔራዊ ምርጫ አስመልክቶ በድጋሜ የሚወዳደሩት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት
የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርገው ከሄዱ በኋላ በፕሬዚዳንቱ ደጋፍዎችና ተቃዋሚዎች መካከል በተነሳ ግጭት አንድ ሰው ሲሞት ከ80 በላይ
ሰዎች
የቆሰሉ መሆናቸው ተዘግቧል።
መስከረም 22 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
Ø
ትናንት አርብ ከናይጄሪያ ዋና ከተማ ከአቡጃ ወጣ ብለው ባሉ ቦታዎች ላይ ሁለት ቦምቦች
ፈንድተው 15 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውና በርካታ መቁሰላቸውን ከስፍራው የተገኘ ዜና ይገልጻል። አንደኛው ቦምብ የፈነዳው
ከአቡጃ 40 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ኩጄ ከተባለ ቦታ ከአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ ሲሆን 15 ሰዎች መሞታቸውና በርካታ
መቁሰላቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ጊዜ የፈነዳው ሁለተኛ ቦምብ ደግሞ ኒያና በተባለ ቦታ ከአንድ የአውቶቡስ ማቆሚያ ላይ ሲሆን
በፍንዳታው ሁለት ሰዎች ሞተዋል፣ ሌሎች ቆስለዋል። ለዚህ እኩይ ተግባር ኃይላፊነቱን እስካሁን የወሰደ ባይኖርም የቦኮሃራም
ታጣቂዎች ስራ እንደሆነ ተገምቷል። ቦኮ ሃራም ከዚህ በፊት አቡጃን ያጠቃ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ በፊት ትኩረቱ በሰሜን ምስራቅ
ናይጀሪያ የምትገኘውና የቦርኖ ክፍለሃገር ዋና ከተማ በሆነችው በማይዱጉሪ ላይ እንድነበር አይዘነጋም። ባለፈው ዓመት ኒያና
በተባለው ቦታ በፈነዳ ቦምብ ምክንያት ዘጠና ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል። ቦኮ ሃራም እንቅስቃሴውን
በ2002 ዓም ከጀመረ ወዲህ
ከ17 ሺ ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል። ባለፈው ሐሙስ በደቡብ ምስራቅ ናይጀርም
የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በናይጀር ወታደሮች ላይ ደፈጣ አካሄደው ሁለት ወታደሮች መግደላቸውና ሰባት መቁሰላቸው ተነግሯል።
Ø
የቀድሞ የናይጀሪያ የነዳጅ ሚኒስትር የነበሩት ሚስስ ዲየዛኒ አሊስን ለንደን ውስጥ መታስራቸው
ተነገረ። ወይዘሮዋ ከ 2002 ዓም እስከ 2007 ዓም ድረስ የናይጄሪያ የነዳጅ ሚኒስትር የነበሩ ሲሆን በሃላፊነት ላይ
በነበሩበት ወቅት ከነዳጅ ሽያጭ ገቢ
20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር መሰረቁ ተገልጿል። ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት
ገንዘቡ መጉደሉን ያጋለጡት ሳኑሲ ላሚዶ የሚባሉ የናይጄሪያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ሲሆኑ ሴትየዋ እጃቸው የሌለበት መሆኑን በወቅቱ
ገልጸው እንደነበር ይታወሳል። የብሔራዊ ወንጀል ክፍል የተባለው ተቋም በቅርቡ
ዓለም አቀፍ የሙስና ወንጀለኞችን የሚከታተል ቡድን ያቋቋመ መሆኑን ገልጾ አምስት
ሰዎችን የያዘ መሆኑን አስታውቋል። የተያዙት ሰዎች እነማን እንደሆኑ
ተቋሙ ባይገልጽም የሚስስ ዳይዛኒ አሊሰን ቤተሰቦች ሴትየዋ በዚሁ ተቋም መያዛቸውን
ተናግረዋል። በቅርቡ የተመረጡት የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ቃለ መሃላ በፈጸሙት በወቅት ከነዳጅ ገቢ
የተሰረቀውን
በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ
ለማስመለስ ቃል መግባታቸው ይታወሳል።
Ø
የቱኒስያ ባለስልጣኖች ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ሱስ በተባለች ከተማ አሸባሪዎች 38
ቱሪስቶችን በገደሉበት ወቅት አውጀውትና በስራ ላይ አውለውት የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከአርብ እኩለ ሌሊት ጀመሮ ያነሱ
መሆናቸውን በመገናኛ ብዙሃን አማካይነት ባስተለለፉት መግለጫ ገልጸዋል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ስልጣን
የሰጠ ሲሆን የሕዝብን የመሰብሰብና ሌሎች
የመንቀሳቀስ መብት የሚገድብ ነበር። ባለፈው
ሐምሌ ወር አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለሁለት ወር የተራዘመ ሲሆን በዚሁ ወር የቱኒሲያ ፓርላማ አሸባሪዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ
ጠንካራ የሆኑ ህጎችን ማጽደቁ ይታወሳል።
Ø
በደቡብ ሱዳን ዩኒቱ በተባለው ክፍለ ሃገር ካለፈው ሰኞ ጀምሮ እስከ ትናንት አርብ ድረስ
በመንግስቱ ወታደሮችና በአማጽያኑ መካከል በተደረጉ ውጊያዎች ከሁለቱም በኩል ጉዳት የደረሰ መሆኑ የመንግስቱ
ወታደራዊ
ቃል አቀባይ ለአሶስየትድ ፕሬስ የዜና ወኪል ገልጾ አማጽያኑ ስምምነቱ አፍርሰዋል ሲል ከሷል። ። የአማጽያኑ ቡድን የመንግስት
ወታደሮች ይዞዎችን ባጠቃበት ወቅት 14 የመንግስት ወታደሮች ሲገደሉ ሌሎች 42 ቆስለዋል። በሌላ ውጊያ ደግሞ የመንግስት
ወታደሮች 38 የሚሆኑ የአማጽያኑን ታጣቂዎችን ሲገድሉ ሁለት የያዙ መሆናቸውና 50 የሚሆኑ የሮኬት ማምጠቂያ መሳሪያዎችን የማረኩ
መሆናቸው ተገልጿል። የመንግስት ውታደሮች ይዘውት የተባለውን ቦታ ኮችክ የሚባለውን ቦታ በከፍተኛ ውጊያ የለቀቁ መሆናቸው
የተገለጸ ሲሆን አማጽያኑ አፐር ናይል በተባለው ግዛት ጥቃታቸው ያፋፍማሉ በማለት ቃል አቀባዩ ተናግሯል። አያይዞም የተደረገውን
ስምምነት በማፍረስ አማጽያኑ ጦርነቱን እያፋፋሙ ይገኛሉ የሚል ክስ ያቀረበ ሲሆን ስለ ቀረበው ክስ ከሶስተኛ ወገን ማረገጫ ወይም
በአማጽያኑ በኩል መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።
መስከረም 21 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኡማር አል በሽር የሻዕቢያውን የገንዘብ ሚኒስትር ብርሃኔ ሃብተማሪያምን
ሐሙስ ዕለት ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ሱዳን ከሻእቢያው ኤርትራ ጋር ያላት
ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን ገልጸው በሁለቱ አገሮች መካከል እየተደረገ ያለውን ትብብር አመሰግነዋል።
ይህ
የበሽር ንግግር ባለፈው ሰሞን ከሻእቢያ ሸሽተው ወደ ሱዳን የገቡትን የወያኔ ተቃዋሚ ኃይል አባላት ሱዳን በማስተናገዷና ወደ
ኢትዮጵያ እንዲሄዱ በማድረጓ በሁለቱ አገሮች መካከል የግንኙነት መሻከር ተፈጥሯል የሚለውን ጥርጣሬ አዳክሞታል።
ከጥቂት ቀናት በፊት የወያኔ ባለስልጣኖች በሞላ አስገዶም የሚመሩ ወደ 800
የሚደርሱ ታጣቂዎች የሱዳን መንግስት ተቀብሎና ተንከባክቦ ለኢትዮያ መንግስት ባለስልጣኖች አስርክቧል፤ የሻእቢያ ድንበር ጠባቂዎች
የሚከሩትን አደጋ እንዲቋቋሙ አድርጎ ታጣቂዎቹ ምግብና መጠለያ በመስጠት ወደ ኢትዮያ እንዲሄዱ አድርጓል በማለት የወያኔ
ባለስልጣኖች የሱዳን መንግስት አመስግነው መግለጫ ማውጣታቸው ይታወሳል። በሽር በሱዳን እና በኤርትራ መካከል የጠነከረ ወዳጅነትና
ግንኙነት አለ ብለው በይፋ መናገራቸው
ቀደም ብሎ በተፈጠረ ሁኔታ ምክንያት በሻእቢያና በሱዳን መካከል የግንኙነት መሻከር
ተፈጥሯል በማለት የተሳሳተ መደምደሚያ ወስደው የነበሩ ክፍሎችን አስገርሟል። የሻዕቢያው የገንዘብ ሚኒስትር እና
አቻቸው
የሱዳን የገንዘብ ሚኒስትር ስለ
ገንዘብ፤ ንግድ፤ ባንክ፤ ቀረጥ፤ ኢንሹራንስ እና ሌሎች ጉዳዮች ሰፋ ያለ ውይይት አድርገው አንዳንድ ስምንንት የደረሱ መሆናቸውን
ሱዳን ትሪቡን ገልጿል።
Ø
ሐሙስ ጠዋት በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ማይዱጉሪ በተባለችው ከተማ አጥፍቶ ጠፊ የሆኑ አምስት ሴት ልጆች የታጠቋቸውን ቦምቦች
በአንድ መስጊድ ውስጥ በማፈንዳታቸው ልጆቹን ጨምሮ 14 ሰዎች ሲሞቱ 39 የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸውን ወታደራዊ የዜና ምንጮች
ገልጸዋል። ሴቶቹ የቦኮ ሃራም አባላት ናቸው ተብለው ይጠረጠራሉ። ማይዱጉሪ ቦኮ ሃራም እንቅስቃሴውን የጀመረባት ከተማ ስትሆን
በዚህ በዱን በተድጋጋሚ ተጠቅታለች። ከሁለት ሳምንት በፊት በቡድን ተደረገ ጥቃት ከ100 ሰዎች በላይ መሞታቸው ይታወቃል። ቦኮ
ሃራም እንቅስቃሴ ከጀመረ ጀምሮ 17 ሺ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸው ማጣታተቸውና አዲሱ ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ
ቡድኑ የሚያካሄደውን ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ አይዘነጋም።
Ø
ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ መፈንቅለ መንግስት ያካሄደው ወታደራዊ ተቋም መሪ ጄኔራል
ዲየንዴሬ በትናንትናው ዕለት ሸሽተው ተሽሽገውበት ከነበረው ከቫቲካኑ አምባሰደር መኖሪያ ቤት እጃጀቸውን መስጠታቸውና በአሁኑ
ወቅት በቡርኪና ፋሶ የጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ያሉ መሆናቸው ተገለጸ። የሚበየንብኝን ፍርድ ለመቀበል ወደ ኋላ አልልም በማለት
በተደጋጋሚ ሲናገሩ የቆዩት ጄኔራል በአሁኑ ወቅት በዋና ከተማዋ ማህከል በሚገኘውና ፓስፓንጋ በሚባለው የፖሊስ ጣቢያ ታስረው
ይገኛሉ። የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ
መፈንቅለ መንግስቱን የመሩት ጄኔራል እና ተባባሪዎቻቸው
ለፍርድ የሚቀርቡ መሆናቸውን ገልጾ የመፈንቅለ መንግስቱን ሁኔታ የሚያጣራ ኮሚሽን
ያቋቋመ መሆኑ አሳውቋል። ክዴኢየንዴሬ
በተጨማሪ ስድስት ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸው የተገለጸ ሲሆን በግለሰቦቹ
መያዝ
በርካታ
ስው ደስታ እርካታ ያገኘ መሆኑ ታውቋል።
አር
ኤስ ፒ እየተባለ የሚጠራው የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደራዊ ተቋም በጠቅላላ 1300 አባላት የነበሩት ሲሆን ከዚሁ ውስጥ 800
የሚሆኑት እጃቸውን ሰጥተው በመከላከያ ተቋም ልዩ ልዩ ቦታዎች የተመደቡ መሆናቸውና
የተቀሩት
ደግሞ እየተፈለጉ
ናቸው ተብሏል።
Ø
በትናንትናው ዕለት የአውሮፓው ኅብረት በአራት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ላይ ማዕቀብ ያደረገ
መሆኑ ተገለጸ። የአውሮፓው ህበረት ባወጣው መግለጫ ማዕቀብ የተጣለባቸው ባለስልጣኖች በብሩንዲ ውስጥ ዴሞክራሲ በትክክል ተግባራዊ
እንዳይሆን እንቅፋት ሆነዋል ችግሩ ተገቢ መፍትሔ እንዳያገኝ መሰናክሎች የተባሉት ሲሆኑ በግለሰቦቹ ላይ የተጣለው ማእቀብ የጉዞ
መከልከል እና በባንክ ያላቸው ሂሳብ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግን የሚያካታት መሆኑ መግለጫው አስታውቋል። በተጨማሪም መግለጫው
በብሩንዲ የፖሊቲካ መፍትሔ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት በጣም እየተጓተተና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱንና ወደ ከፍተኛ ደም መፋሰስ
እያመራ መሄዱን ገልጾ የፖሊቲካ መፍትሔ እውን እንዳይሆን እንቅፋት በሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ መጣል ግድ ሆኗል ብሏል።
መግለጫው ማዕቀብ የተደረገባቸው ግለስቦች ማንነት
ግልጽ ባያደረግም ኤ ኤፍ ፒ የተባለው የዜና ተቋም ዲፕሎማቶችን ዋቤ በማድረግ
ባሰራጨው ዜና የብሩንዲ
ብሔራዊ ፖሊስ ምክትል፤ በብሔራው ፖሊስ ጉዳይ የካቢኔ ሚኒስትር፤ የጸጥታ ሰራተኛ እና አንድ የቀድሞ ጄኔራል እንድሆኑ ገልጿል ።
በተያያዘ ዜና የብሩንዲው መንግስት
ተቃዋሚ ናቸው ለሚባሉ ቡድኖች ሩዋንዳ ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠች ነው የሚል ክስ የብሩንዲ ባለስልጣኖች የከሰሱ መሆናቸው ታወቀ።
ከ70ሺ በላይ የሆኑ የብሩንዲ ስደተኞች ሩዋንዳ በካምፕ ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን
ከእነዚሁ መካከል በሩዋንዳ ወታደራዊ ተቋም አሰልጣኝነት
ወታደራዊ ትምህርት እየተሰጣቸው ነው የሚል ክስ የብሩንዲ ባለስልጣኖች ይከሳሉ።
ባለፈው ጊዜ ብሩንዲ ውስጥ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሙከራ ያደረገው የወታደር
ክፍል መሪንና ተባባሪዎቻቸውን ሩዋንዳ እያስተናገደች መሆኑ ግልጽ ሲሆን እነዚህ ሰዎች የሚመሩት ቡድን ወታደራዊ ጥቃት ለመሰንዘር
በዝግጅት ላይ ናቸው በማለት የብሩንዲ ባለስልጣኖች ተናግረዋል። የሩዋንዳ ባለስልጣኖች ብሩንዲ ያለባትን የውስጥ ችግር ለመሸፈን
የምታወራው የፈጠራ ወሬ ነው በማለት ክሱን ያጣጣሉ መሆናቸው ተነግሯል። ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው
ግንኙነት ውጥረት የተሞላበት ሲሆን በሁለቱም አገሮች ውስጥ ጎሳን መሰረት ያደረገ ተመሳሳይ ውጥረቶች ያሉ መሆናቸው ይታወቃል።
መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በኒውዮርክ በመካሄድ ላይ ከሚገኘው የተመድ አመታዊ ስብስባ
ተነስተው ባስቸኳይ ወደ አገራቸው የተመለሱት የማእከላዊ አፍሪካ ሪፕብሊክ ጊዜያዊ
ፕሬዚዳንት ካትሪን ሳምባ ፓንዛ
ባለፉት ጥቂት ቀናት በአገሪቱ ውስጥ
ብጥብጥ ያስነሱት ቡድኖች
ዓላማቸው መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ነበር ብለዋል። ፕሬዚዳንቷ በብሔራዊ ራዲዮ
አማካይነት ለሕዝብ ባስተላለፉት መልእክት ብጥብጡን ያነሳሱት ክፍሎች ፍላጎታቸው አንዱን የሕዝብ ክፍል በተቀነባበረ መንገድ
በሌላው ላይ በማነሳሰት የአገሪቱ ሕዝብ በዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል ላይ እንዲነሳ ነበር ብለዋል።
ድርጊቱ
የመፈንቅለ
መንግስት ሙኩራ ከማለት ውጭ ሌላ ስም ሊሰጠው የማይችል መሆኑን ገልጸው ሁሉም ታጣቂ ኃይሎች መሳሪያቸውን እንዲያወርዱ ጥሪ
አድርገዋል። ሁከቱ በተካሄደበት ወቅት በተደረጉ ሰላማዊ ስልፎች ላይ
“ጊዜያዊ
ፕሬዚዳንቷ ከስራቸው ይባረሩ”፤ “የፈረንሳይ ወታደሮችን ጨምሮ
የዓለም
አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይሎች ከአገሪቷ ይውጡ” የሚሉ መፈክሮች ተይዘው የነበሩ መሆናቸው ታውቋል። ባለፈው ቅዳሜ የእስልምና
ሃይማኖት ተከታይ የሆነ
አንድ ታክሲ ነጅ መገደሉን ተከትሎ በተነሳው ግጭት 36 ሰዎች ሲሞቱ ከ30 ሺ
ሰዎች በላይ ቤታቸውን እየለቀቁ ተሰደዋል።
በዋናዋ ከተማ በባንጉወየ የታወጀው
የሰዓት
እላፊ አዋጅ በተግባር እየዋለ ሲሆን በዛሬው ቀንም በከተማዋ የተረጋጋ ሁኔታ ይታያል። በሚቀጥለው ጥቅምት ወር ሊካሄድ ታቅዶ
የንበረው ጠቅላላ ብሔራዊ ምርጫ የተሰረዘ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጿል።
Ø
በትናንትናው እለት በደቡብ አፍሪካ በፕሪቶሪያ እና በኬፕ ታውን ከተሞች በአገሪቱ ውስጥ
እየተስፋፋ የሚገኘውን ሙስና በመቃወም ሰላማዊ ስልፎች የተደረጉ መሆናቸውን በሁለቱም ከተሞች የነበሩ የዜና ምንጮች ገልጸዋል።
ደቡብ አፍሪካን የሚመራው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግሬስ የነጮችን አገዛዝ አስወግዶ ስልጣን በያዘበት ወቅት ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበት
የነበረ ቢሆንም በሃያ ዓመት የአገዛዝ ዘመኑ
ብዙሃኑ
ችላ ተብለው ጥቂት ሰዎች ብቻ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል
የሚል ተቃውሞ ከሕዝብ እየተሰማ መሆኑ ታውቋል። በየአንዳንዱ ከተማ ለሰላማዊ ሰልፍ
የወጣው ሕዝብ ብዛት ወደ 2000 ገደማ ቢሆንም እንቅስቃሴው እያደገ ሊሄድ እንደሚችል አደራጆቹ ገልጸዋል። በሰልፉ ላይ የፖለቲካ
ፓርቲዎች፤ የሰራተኛ ማህበሮች መሪዎችና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለረጅም አመታት የመንፈስና የእምነት መሪ በመሆን
ሲታገሉ የነበሩት ዴዝመንድ ቱቱ ሰልፉን የደገፉት መሆኑን ቢገልጹም በህመም ምክንያት በቦታው ሳይገኙ ቀርተዋል። በሰልፉ ላይ “
ሙስና በደሃው ላይ የተጫነ ቀረጥ ነው” እኛ
ሀብታሞች ታክስ ይክፈሉ እንላለን” “ አፓርታይድ ታሪካችንን ሲሰርቅ ሙስና ደግሞ ተስፋችንን ሰረቀ የሚሉ መፈክሮች ታይተዋል።
በደቡብ አፍሪካ የሚታየው የሙስና መጠን ብዞዎችን አሳስቧል። የወጣት ስራ አጥ
ቁጥር 50 ከመቶ በደረሰበትና የኢኮኖሚ እድገቱ ወደ 2 ከመቶ ዝቅ ባለበት ሁኔታ
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዙማ 24 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት መኖሪያ ቤታቸውን ለማሻሻል
ማቀዳቸው በርካታ ዜጎችን ያስቆጣ መሆኑ ታውቋል።
ማክሰኞ
ዕለት የጃፓኑ ኩባንያ ሂታቺ በአገሪቷ ውስጥ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ለመስራት ለአገሪቱ ባለስልጣኖች የማይገባ ጉቦ ከፍሏል በሚል
አሜሪካ ያቀርበቸውን ክስ የደቡብ አፍሪካ ባለስልጣኖች ያስተባበሉ መሆናቸውም ተገልጿል። የጸር ሙስናው ሰልፍ ከአስራ አምስት ቀን
በኋላ በተጠናከረ መንገድ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
Ø
በናይጄሪያ የነዳጅ ዘይት በማውጣት ላይ የሚገኘው የሼል ኩባንያ ነዳጁ የሚጓጓዝበት ቱቦ ላይ ብልሽት በማጋጠሙና ነዳጅ ባልሆነ
መንገድ በመፍሰሱ ምክንያት የነዳጅ ማውጣት ስራውን ለጊዜው ያቋረጠ መሆኑን ገልጿል። ኩባንያው በቀን 400 ሺ በርሚል ድፍድፍ
ዘይት ያወጣ ስለነበር ስራውን ማቋረጡ በናይጄሪያ ኢኮኖሚ ላይ በቀላሉ የማይገመት ጉዳት ሊያመጣ ይችላል ብለው ታዛቢዎች ይተቻሉ።
ናይጄሪያ በቀን 2 ሚሊዮን በርሚል ድፍድፍ ዘይት የምታመርት ሲሆን ይቋረጣል የተባለው የአገሪቱን አንድ አምስተኛ መሆኑ ነው።
ከዚህ በፊት የነዳጁ ቱቦ ከመሃል እየተከፈተ ነዳጅ እንደሚሰረቅ እና እንዲሁም ነዳጁ አለአግባብ ፈስሶ አየሩን እንደሚበክል
በመግለጽ የሼል ኩባንያ በተደጋጋሚ ቅሬታ ያሰማ ቢሆንም ሁኔታውን ለመቀልበስ የተወሰደው እርምጃ አነስተኛ መሆኑ ይታወቃል።
በአመት 6 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ድፍድፍ የነዳጅ ዘይት ከናይጀሪያ በስርቆት እንድሚዘረፍ ተገምቷል።
Ø
የፍልስጥኤም ባለስልጣን ፕሬዚዳንት ሙሐሙድ አባስ
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመታዊ ጉባዔ ላይ ንግግር ካደረጉ
በኋላ
የአገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ለመጀመሪያ ጊዜ ኒውዮርክ በሚገኘው በተመድ ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሌሎች አገሮች ሰንደቅ
ዓላማዎች ጎን እንዲውለበለብ ተደርጓል። ትናንት ረቡዕ መስከረም 19 ቀን በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ ሰባት ሰዓት
በተደረገው ስነስርዓት ላይ ፕሬዚዳንት አባስ ባደረጉት ንግግር ቀኑ ታሪካዊ ቀን
መሆኑን ገልጸው የአገራቸውን ነጻነት ለማስከበር ህይወታቸውን ለሰጡትና
ለታሰሩት ማስታወሻ ይሆናል ብለዋል። ዌስት ባንክ እየተባለ በሚጠራው የፍልስጥዔም
ግዛት በምትገኘው በራማላህ ከተማ በርካታ ፍልስጥኤማውያን በትልቅ የተሌቪሽን ስክሪን ስነስርዓቱን ተከታትለዋል። በ2005 ዓ.ም.
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ፍልስጥኤምን በታዛቢነት ደረጃ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል እንደትሆን
የወሰነ መሆኑና በጳጉሜ 5 ቀን 2007 ዓ.ም ደግሞ የፍልስጥኤም ሰንደቅ ዓላማ በቅጥር ግቢው እንዲውለበለብ መወሰኑ ይታወሳል።
Ø
ከጥቂት ቀናት በፊት በቡርኪና ፋሶ ተሞክሮ የነበረውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ጄኔራል
ዲየንዴሬ ትናንት የአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት የጀመረውን በኃይል መስርያ ማስፈታት እርምጃ በመሸሽ
በአገሪቱ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ ውስጥ ወደሚገኘው ወደቫቲካን ኤምባሲ ሄደው ጊዜያዊ
መጠጊያ የጠየቁ መሆናቸው ታውቋል። ከቡርኪና ፋሶ ባለስልጣኖች ጋር እጃቸውን ስለሚሰጡበት ሁኔታ እየተወያዩ መሆናቸው ተገልጿል።
ጄኔራል ዲየንዴሬ ከተደበቁበት ሆነው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ “እኔ እጄን ሰጥቸ የሚሰጠኝን ፍርድ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ”
“የቡርኪና ፋሶ ሕዝብ የተደቀነበትን ችግር በውይይት እንደሚፈታ እምነቴ ነው”፣ “ቡርኪና ፋሶ ሁሉን የሚያካትት መፍትሔ
ያስፈልጋታል” ብለዋል። የአገሪቱ
ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት በትናንትናው ቀን ባደረጉት ንግግር የአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት የወሰደውን እርምጃ ካመሰገኑ በኋላ የአገሪቱ
ልዕልናና ክብር በአስተማማኝ ደረጃ ላይ ያለ መሆኑን ገልጸው ለቡርኪና ፋሶ አዲስ ምዕራፍ መጀመሩን አብስረዋል። አር ኤስ ፒ
የተባለው የፕሬዘዳንቱ ጠባቂ
ወታደራዊ ቡድን አባላት ቀደም ብሎ ተደርጎ የነበረውን ስምምነት በመጣስ
መሳሪያ አንፈታም በማለታቸው
በትናንትናው ቀን የአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት በኃይል ለማስፈታት እርምጃ መውሰዱ
ይታወሳል። የቡርኪና ፋሶ ጊዜያዊ መንግስት ሕዝቡ በእነዚህ ወታደሮች ላይ ቂም እንዳይዝ የተማጠነ ሲሆን ብዙዎች የክፍሉ አባላት
ከሌላው ወታደር ክፍል ጋር እንዲቀላቀሉ የሚደረጉ መሆኑን ቃል ሰጥቷል ።
መስከረም 19 ቀን 2008 ዓ.ም
Ø
በትናንትናው ዕለት የቡርኪና ፋሶ መከላከያ ሰራዊት አር ኤስ ፒ (RSP) እየተባለ በሚጠራው
እና
የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ በሆነው ወታደራዊ ተቋም ጦር ሰፈር ላይ
ጥቃት በማድረስ ካምፑን የተቆጣጠረ
መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዜና ይገልጻል። የደረሰው ጉዳት በውል ባይታወቅም
የቀላልና የከባድ መሳሪያ ድምጽ ሲሰማ የዋለ መሆኑ ተነግሯል። መከላከያ ሠራዊቱ ይህንን እርምጃ የወሰደው የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ
የሆነውና ከጥቂት ቀናት በፊት መፈንቅለ መንግስት አካሂዶ የነበረው ወታደራዊ ተቋም
በተደረገው
ስምምነት መሰረት የታጠቀውን መሳሪያ ለመፍታት ፈቃደኛ ሆኖ ባለመገኘቱ ነው ተብሏል። የቡድኑ መሪ ጄኔራል ዲየንዴሬ ካልታወቀ
ስፍራ ላይ ሆነው ኤፍፒ ለተባለው የዜና ምንጭ በሰጡት ቃለ ምልልስ የደም መፋሰስ እንዳይኖር ወታደሮቻቸው እጃጀቸውን እንዲሰጡ
የገፏፏቸው መሆኑን ገልጸው መከላከያ ሰራዊቱ በወሰደው እርምጃ በርካታ ወታደሮች ሳይሞቱ እንዳልቀሩ ተናግረዋል። ዲየንዴሬ
ወታደሮቹ እና የወታደሮቹ ቤተ ሰቦቹ በካምፑ ውስጥ እንደነበሩ
ይናገሩ
እንጅ የአገሪቱ መከላከያ ሰራዊት
ዋና አዛዥ ጄኔራል ፒንግሬኖማ ዛግሬ በሰጡት መግለጫ ካምፑን የተቆጣጠረው ሰራዊት በቦታው ምንም ሰው እንዳላገኘ ተናግረዋል።
እሮብ ጠዋት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በዋናው ከተማዋ “ኡአጋ 2000” እየተባለ በሚጠራው ቀበሌ በብዛት ሆነው ፍተሻ ሲያካሄዱ
የታዩ ሲሆን ያልተያዙ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ወታደሮችን እየፈለጉ መሆናቸውን ተገልጿል።
Ø
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለመጭው ጥቅምት ወር ታቅዶ የነበረው ብሔራዊ ምርጫ የተሰረዘ
መሆኑን በኒውዮርክ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስበሰባ ላይ የነበሩትና ሰሞኑን በተፈጠረው ሁኔታ ባስቸኳይ ወደ አገራቸው
የተመለሱት የአገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ካትሪን ሳምባ ፓንዛ ገልጸዋል። ባለፈው ቅዳሜ አንድ ታክሲ ነጅ መገደሉን ተከትሎ
በክርስቲያን እና በሙስሊም ቡድኖች መካከል በተነሳው ግጭት ምክንያት ሰላሳ ስድስት ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ቢያንስ 10 ሺ
የሚሆኑ ሰዎች ከአካባቢያቸው ሸሽተው ወደ ሌላ ስፍራ የሄዱ መሆናቸው ይታወቃል፡፤ ጸጥታውን ለማረጋጋት ባለስልጣኖቹ የሰዓት እላፊ
አዋጅ አውጀዋል። አገሪቷ ባሁኑ ወቅት ውጥረት የስፈራባት ሲሆን
በ2005 እና በ2007 ወደነበረው የግጭትና የደም መፋሰስና ሁኔታ ውስጥ ልትገባ
ትችላለች የሚል ስጋት ሰፍኗል።
የአገሪቷ ጊዚያዊ መንግስት የአገር ውስጥ ሚኒስትር
መንግስታቸው
ሁኔታውን በቁጥጥር ስር ማድረጉን ቢገልጹም በአገሪቱ ውስጥ ሊፈነዳ የሚችል ከፍተኛ ውጥረት መኖሩን አልሸሸጉም። የጊዜያዊ
መንግስት ፕሬዚዳንት ካትሪን ግጭቱ እንዲፈጠር በመቀስቀስና ሁኔታውን በማባባስ በኩል የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቦዚዜ እና ተከታዮቻቸው
ቁል ሚና ተጫውተዋል በማለት ከሰዋል። የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቦዚዜ በሚቀጥለው ምርጫ እንዳይሳተፉ በመከልከላቸው ቅሬታ ያላቸው
መሆኑን መግለጻቸው ይታወሳል።
Ø
ላለፉት 21 ወራት በደቡብ ሱዳን ውስጥ ሲካሄድ በቆየው
የእርስ
በርስ ጦርነት የተፈጸመውን
ወንጀል መርምሮ ፍርድ የሚሰጥ አካል ያቋቋመ መሆኑን የአፍሪካ ህብረት ገለጸ።
እርምጃው ለአፍሪካ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ለመስጠት ነው ተብሏል። ፍርድ ቤቱ እንዲቋቋም የተደረገው የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት
ሳልቫኬር እና የአማጽያኑ መሪ ሬክ ማቻር አዲስ አበባ ላይ በፈረሙት ስምምነት መሰረት ሲሆን መቋቋሙ የተገለጸውም ሰሞኑን
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓመታዊ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ወቅት በተካሄደው የደቡብ ሱዳን ጉዳይ ስብሰባ ለይ ነው።
በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ መሞታቸውና ከ2.2 ሚሊዮን
ሕዝብ በላይ ቤቱን ጥሎ መሰደዱ ይታወቃል። በቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት በኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ሊቀመንበርነት ባለፈው ዓመት
የተቋቋመው መርማሪ ኮሚቴ በደቡብ ሱዳን ግጭት በርካታ ግድያዎች፤ የማሰቃያ ምርመራዎች፤ ዝርፊያዎች እና የአስገድዶ መድፈር
ወንጀሎች መፈጸማቸውን ያረጋገጠ ሲሆን የጅምላ ግድያ መድረጉን ግን መረጃ ያላገኘ መሆኑን ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት
ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን
ልዩ ፍርድ ቤት መቋቋሙን ደግፈው በጦርነቱ ምክንያት የተካሄደውን ወንጀል ለማካካስ ፍትህና
ተጠያቂነትን ተግባራዊ ለማድረግ ይረዳል ብለዋል፡፤
Ø
በቲምበክቱ የሚገኘውን ታሪካዊ ቦታ በማቃጠልና በማጥፋት የተወነጀለው አህመድ አልፋህኪ
አልማህዲ የተባለ የእስላማውያን አክራሪ ቡድን አባል ረቡዕ ዕለት ሄግ በሚገኘው
ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረበ መሆኑ ተገለጸ። አልማህዲ
የተከሰሰው ከሶስት ዓመት በፊት በማሊ ቲምበክቱ የሚገኘውን ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎችና እንዲሁም
መስጊዶች
በማቃጠልና በማጥፋት ወንጀል መሆኑ ተገልጿል። በቲምበክቱ የሚገኘው ታሪካዊ ቦታ በዓለማችን ውስጥ ካሉ ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎች
ውስጥ አንዱ ነው
ተብሎ በዪኔስኮ የተመደበ ስፍራ ሲሆን የዛሬ ሶስት ዓ.ም. በቦታው ከሚገኙ 16 ታሪካዊ ቦታዎ
ውስጥ 14 ቱ ላይ ወረራ በማካሄድ
የእስላማውያን አክራሪ ድርጅት አባሎች እነዚህን ታሪካዊ የቅርስ ቦታዎች ማቃጠላቸው
ይታወሳል። የተቃጠሉት የተደረመሱት 14 ታሪካዊ ቦታዎች
በዮኔስኮ እንደገና ታድሰዋል። ከአልማህዲ ጋር ግብረ አበር በመሆን ወንጀሉን
የፈጸሙት እስካሁን አልተያዙም።
ፍርድ ቤቱ መስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠውም
የመያዥ ትእዛዝ መሰረት የናይጀር መንግስት አልማህዲን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ
ወደ ሄግ የላከው መሆኑ ተዘግቧል።
መስከረም 18 ቀን 2008 ዓ.ም
መ
|